🔴 " እስከሚከፈለን ድረስ ወደ ሥራ ላለመመለስ ተስማምተናል ለሁሉም ባለሞያ እስከሚከፈል ድረስ አንሰራም " - የጤና ባለሞያዎች
🔵 " ዝም ያለ አካል የለም ዘግቶ መሄዳቸው ትክክል አይደለም " - የጤና ቢሮ ሃላፊ
በኦሮሚያ ክልል፣ ምዕራብ አርሲ ዞን አዳባ ወረዳ በዘጠኝ ጤና ጣቢያዎች ውስጥ የሚሰሩ የጤና ባለሞያዎች የትርፍ ሰዓት ስራ(ዲዩቲ) ክፍያ ስላልተከፈላቸው 05/05/17 ዓ/ም ጀምሮ የስራ ማቆም አድማ ማድረጋቸውን ቃላቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የሰጡ የጤና ባለሞያዎች ተናግረዋል።
ባለሞያዎቹ ከ2015 ዓ/ም ጀምሮ እስከአሁን ድረስ በተለያዩ ጊዜያት ያልተከፈላቸው የ1 አመት ከ 5 ወር በላይ የትርፍ ሰዓት ስራ ክፍያ መኖሩን ተናግረዋል።
እስከ ክልሉ የበላይ አካላት ድረስ ሄደን ጠይቀናል በተደጋጋሚ የሚሰጠን ምላሽ ግን " ታገሱ " የሚል ነው በዚህ ምክንያት ተነጋግረን ስራ ለማቆም ተገደናል ነው ያሉት።
" አብዛኛው ባለሞያ ከወረዳው ሸሽቶ ወደተለያዩ አካባቢዎች በመሄድ ተደብቆ ነው ያለው አመራሮችም በአንቡላንስ ቤት ለቤት በመሄድ የህክምና ባለሞያዎችን እያፈለጉ እያስፈራሩ ነው " ብለዋል።
ባለሞያዎቹ " በተለያዩ ጊዜያት ከወረዳ እና ከዞን አመራሮች ጋር በርካታ ውይይቶችን አድርገናል ነገር ግን ' ግብር እስከሚሰበሰብ ጠብቁ፣ ገንዘብ የለም ታገሱ ' ከማለት የዘለለ እስካሁን ምንም ምልሻ ባለመግኘታችን እዚህ ውሳኔ ላይ ለመድረስ ተገደናል ነው " ያሉት።
" እስከሚከፈል ድረስ ወደ ሥራ ላለመመለስ ተስማምተናል ለሁሉም ባለሞያ እስከሚከፈል ድረስ አንሰራም የተጠራቀመ ክፍያው እስከ 100 ሺ የደረሰለት ባለሞያም አለ " ብለዋል።
" በዚህ ደመወዝ ፣በዚህ ኑሮ ውድነት መኖር አልቻልንም የመጨረሻ ደረጃ ላይ ነው የደረስነው ልጆች ያላቸው ልጆቻቸውን ማሳደግ አልቻሉም መስራትም መኖርም አልቻልንም ይሄንን እርምጃ ስንወስድም ወደ ፖለቲካ ተቀይሮ ' ትታሰራላቹ ' ወደ ሚል ማስፈራሪያ ተሸጋግረዋል " ሲሉ አክለዋል።
ባለሞያዎቹ በወረዳው በሚገኙ ሁሉም ጤና ጣቢያዎች አድማው ቢቀጥልም ለወሊድ ለሚመጡ እናቶች ብቻ አንዳንድ ጤና ጣቢያዎች ውስጥ አገልግሎት እየሰጡ መሆኑን የገለጹ ሲሆን ነገር ግን በሁሉም ጤና ጣቢያዎች መደበኛ ስራዎች ማቆማቸውን ተናግረዋል።
የአዳባ ወረዳ የጤና መምሪያ ሃላፊ አቶ ሽመልስ ፈይሳ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል የባለሞያዎቹ የትርፍ ሰዓት ስራ ክፍያ አለመከፈሉን አረጋግጠዋል።
ሃላፊው በዝርዝር ምን አሉ ?
" በየደረጃ ያሉ ቢሮዎችን እየጠየቁ መምጣት ይችሉ ነበር እኔ የቢሮ ሃላፊ ነኝ ወደ እኔ የመጣ የለም ስራቸውን ነው ዝም ብለው ያቆሙት።
የኑሮ ውድነት በሃገሪቱ እና በአለም ያለ ሁኔታ ነው የትርፍ ሰዓት ስራ ባይሰሩም በመደበኛ ስራቸው መገኘት ነበረባቸው የሙያ ስነምግባሩ ይህንን አይፈቅድም።
የገቢ ማነስ ይኖራል፣ የጸጥታ ችግርም ሊኖር ይችላል በእነዚህ ምክንያቶች ነው እንጂ ዝም ያለ አካል የለም ዘግቶ መሄዳቸው ትክክል አይደለም " ብለዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ባለሞያዎቹ የጠየቁት ከአመት በላይ ሳይከፈላቸው ስለቀረ ክፍያ ነው ችግሩ በምን ያህል ጊዜ ይፈታል ብለን እንጠብቅ ሲል ጠይቀናቸዋል ? በምላሻቸው ፦
" ከእዚህ በፊት ጥያቄውን ለበላይ አካል አቅርበው ጉዳዩ ወደ ወረዳ እንዲመለስ ተደርጎ በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ ይፈታል ተብሎ ነበር ለዚህ እንቅስቃሴ እያደረግን ባለበት ሰዓት ነው ይሄ የተፈጠረው ገቢ ላይ የተመሰረት አከፋፈል ነው የሚኖረው ከስር ከስር እየተከፈለ በጊዜ ሂደት ችግራቸው ይፈታል " ብለዋል።
የቦርድ አባላት በየጤና ጣቢያው በመሄድ ሰራተኛው መጥቶ የራሱን ቅሬታ እንዲያቀርብ ጠይቀው እስካሁን መጥቶ ያቀረበ አካል የለም እኛም መፍትሄ ለመስጠት ተቸግረናል ብለዋል።
ሃላፊው ባለው ሰራተኛ ስራው እንዲቀጥል ለማድረግ እየጣርን ነው ያሉ ሲሆን " የሰራተኛው ችግር ምን እንደሆነ በቢሮ ደረጃ አናውቅም መጥቶ ያቀረበልን አካልም የለም " ነው ያሉት።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ በወረዳው የሚገኙ የጤና ባለሞያዎች ከክፍያ ጋር ተያይዞ የሚያነሱትን ጥያቄ ለመቅረፍ ወረዳው ምን ያህል ብር ይፈልጋል ሲል ጠይቋል።
ሃላፊው " የሚያስፈልገው የገንዘብ መጠን በየጊዜው ስለሚጨምር ይሄን ያህል ነው ማለት ያስቸግራል ነገር ግን በ 2016 ዓም ብቻ ያልተከፈላቸውን ክፍያ ለመፈጸም እስከ 5 ሚሊየን ብር ያስፈልጋል " ብለዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
#MoE
በ2017 ዓ.ም አጋማሽ የሚሰጠውን የቅድመ-ምረቃ ፕሮግራሞች የመውጫ ፈተና (Exit Exam) ዳግም ለመውሰድ ፍላጎት ያላቸው አመልካቾች ምዝገባ ከትላንት ጀምሮ እየተካሄደ እንደሚገኝ ከትምህርት ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ ያሳያል።
ምዝገባው እስከ ጥር 14/2017 ዓ.ም ድረስ እንደሚከናወን ታውቋል።
ከተጠቀሰው ቀን ውጭ ምዝገባ ማድረግ አይቻልም።
ምዝገባው በ https://exam.ethernet.edu.et ላይ የሚካሄድ ሲሆን ፈተና የሚሰጥበት ጊዜ በቀጣይ ይፋ ይደረጋል።
የመፈተኛ User Name እንዲሁም Password በመመዝገቢያ ፖርታል በኩል የሚላክ ሲሆን የመመዝገቢያ ክፍያ ብር 500 በቴሌብር በኩል ብቻ መፈፀም እንዳለበት ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል።
አመልካቾች ከምዝገባ ጋር ተያይዞ ለሚኖራቸው ማንኛውም አይነት ጥያቄ ዘውትር በሥራ ሰዓት በኢሜል [email protected] በስልክ ቁጥር 0911824528 / 0913678404 / 0913949676 / 0910076453 / 0923106826 / 0913866717 / 0911335683 ላይ ደውሎ መጠየቅ ይቻላል ተብሏል።
Via @tikvahuniversity
በ2017 ዓ.ም አጋማሽ የሚሰጠውን የቅድመ-ምረቃ ፕሮግራሞች የመውጫ ፈተና (Exit Exam) ዳግም ለመውሰድ ፍላጎት ያላቸው አመልካቾች ምዝገባ ከትላንት ጀምሮ እየተካሄደ እንደሚገኝ ከትምህርት ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ ያሳያል።
ምዝገባው እስከ ጥር 14/2017 ዓ.ም ድረስ እንደሚከናወን ታውቋል።
ከተጠቀሰው ቀን ውጭ ምዝገባ ማድረግ አይቻልም።
ምዝገባው በ https://exam.ethernet.edu.et ላይ የሚካሄድ ሲሆን ፈተና የሚሰጥበት ጊዜ በቀጣይ ይፋ ይደረጋል።
የመፈተኛ User Name እንዲሁም Password በመመዝገቢያ ፖርታል በኩል የሚላክ ሲሆን የመመዝገቢያ ክፍያ ብር 500 በቴሌብር በኩል ብቻ መፈፀም እንዳለበት ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል።
አመልካቾች ከምዝገባ ጋር ተያይዞ ለሚኖራቸው ማንኛውም አይነት ጥያቄ ዘውትር በሥራ ሰዓት በኢሜል [email protected] በስልክ ቁጥር 0911824528 / 0913678404 / 0913949676 / 0910076453 / 0923106826 / 0913866717 / 0911335683 ላይ ደውሎ መጠየቅ ይቻላል ተብሏል።
Via @tikvahuniversity
#AddisAbaba #እንድታውቁት
የሚዘጉ መንገዶች ይፋ ሆኑ።
ከጥር 10 እስከ ጥር 12 ቀን 2017 ዓ/ም ድረስ ጃን ሜዳ እና አቃቂ ቃሊቲ ታቦት ማደሪያ በሚከበረው የከተራና የጥምቀት በዓል ምክንያት መንገዶች ይዘጋሉ።
አሽከርካሪዎች አማራጭ መንገዶችን እንዲጠቀሙ የአዲስ አበባ ፖሊስ ጥሪ አቅርቧል።
➡️ ከ6 ኪሎ አደባባይ - ምኒልክ ሆስፒታል
➡️ ከምኒልክ ሆስፒታል - መከላከያ 3ኛ ሻለቃ አደባባይ
➡️ ከ3ኛ ሻለቃ አደባባይ - 6 ኪሎ አደባባይ እንዲሁም አቃቂ ቃሊቲ አካባቢ
➡️ ከዋልያ ቢራ - ጥሩነሽ ቤይጂንግ ሆስፒታል
➡️ ከአቃቂ ዋናው መንገድ - ጥሩነሽ ቤይጂንግ ሆስፒታል
➡️ ከ08 - አቃቂ ድልድይ ድረስ ከጥር 10 ቀን 2017 ዓ/ም ከጠዋቱ 4:00 ሰዓት ጀምሮ ለተሽከርካሪዎች ዝግ ይሆናሉ።
በተጨማሪ ከጥር 10 ቀን 2017 ዓ/ም ጀምሮ በ11ዱም ክ/ከተሞች ጥምቀተ ባህር ባሉባቸው ቦታዎች ሁሉ በ500 ሜትር ክልል ውስጥ ታቦታት ሲወጡና ሲገቡ እንዲሁም በሚሄዱባቸው መንገዶች ለአጭር ጊዜም ይሁን ለረዥም ጊዜ ተሽከርካሪ አቁሞ መሄድ የተከለከለ መሆኑን ፖሊስ አስታውቋል።
@tikvahethiopia
የሚዘጉ መንገዶች ይፋ ሆኑ።
ከጥር 10 እስከ ጥር 12 ቀን 2017 ዓ/ም ድረስ ጃን ሜዳ እና አቃቂ ቃሊቲ ታቦት ማደሪያ በሚከበረው የከተራና የጥምቀት በዓል ምክንያት መንገዶች ይዘጋሉ።
አሽከርካሪዎች አማራጭ መንገዶችን እንዲጠቀሙ የአዲስ አበባ ፖሊስ ጥሪ አቅርቧል።
➡️ ከ6 ኪሎ አደባባይ - ምኒልክ ሆስፒታል
➡️ ከምኒልክ ሆስፒታል - መከላከያ 3ኛ ሻለቃ አደባባይ
➡️ ከ3ኛ ሻለቃ አደባባይ - 6 ኪሎ አደባባይ እንዲሁም አቃቂ ቃሊቲ አካባቢ
➡️ ከዋልያ ቢራ - ጥሩነሽ ቤይጂንግ ሆስፒታል
➡️ ከአቃቂ ዋናው መንገድ - ጥሩነሽ ቤይጂንግ ሆስፒታል
➡️ ከ08 - አቃቂ ድልድይ ድረስ ከጥር 10 ቀን 2017 ዓ/ም ከጠዋቱ 4:00 ሰዓት ጀምሮ ለተሽከርካሪዎች ዝግ ይሆናሉ።
በተጨማሪ ከጥር 10 ቀን 2017 ዓ/ም ጀምሮ በ11ዱም ክ/ከተሞች ጥምቀተ ባህር ባሉባቸው ቦታዎች ሁሉ በ500 ሜትር ክልል ውስጥ ታቦታት ሲወጡና ሲገቡ እንዲሁም በሚሄዱባቸው መንገዶች ለአጭር ጊዜም ይሁን ለረዥም ጊዜ ተሽከርካሪ አቁሞ መሄድ የተከለከለ መሆኑን ፖሊስ አስታውቋል።
@tikvahethiopia
ለጊዜው ቪድዮ የት ፣ መቼ እንደሆነ በዝርዝር የሚታወቅ ነገር ባይኖርም ለማየት የሚከብድ ጭካኔ መፈጸሙን ያመላክታል።
ቪድዮው ላይ 5 የፀጥታ ኃይል ልብስ በአግባቡና በስርዓት የለበሱ ሰዎች ይታያሉ።
ከነዛም አንዱ መሳሪያውን እንደታጠቀ አንድን የፊጢኝ ወደ ኃላ የታሰረ ወጣት አንገላቶት ሲያበቃ ከጀርባው ጭንቅላቱ ላይ ሲተኩስበት ይታያል።
በቪድዮው ላይ እንደማታየውም ይህ ድርጊት ሰዎች በተሰበሰቡበት ፊታቸው ላይ የተፈጸመ ነው።
ስለ ቪድዮውም ሆነ ስለ ድርጊቱ በይፋ ወጥቶ የተናገረና ያብራራ አካል እስካሁን ብቅ አላለም።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ድርጊቱን በተመለከተ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽንን ለማነጋገር ይጥራል።
ባለፉት ጊዜያት መሰል የጭካኔ ተግባራት በሀገራችን አንድም በፀጥታ አካላት፣ በታጣቂ ኃይሎች እንዲሁም ደግሞ ሲቪል በለበሱ አካላት ሲፈጸም ታይቷል።
ሰው በቁሙ ሲቃጠል፣ ተዘቅዝቆ ሲሰቀል፣ ገደል አፋፍ ላይ ተረሽኖ ወደ ገደል ሲከተት፣ በድንጋይ ተወግሮ ሲገደል ... ብዙ ብዙ ለማየት የሚከብዱ ድርጊቶች ተፈጽመው በቪድዮ ማስረጃ ጭምር ታይተዋል።
" በቪድዮ ያልተቀረፀ ስንት ጭካኔና ግፍ ይኖር ይሆን ? " የሚሉ ጥያቄዎችን ያስነሱ በርካታ ተግባራት ባለፉት ዓመታት ተመዝግበው ተቀምጠዋል ፤ የአሁኑ ቪድዮ ጉዳይ ምንድነው ? የተገደለው ወጣትስ ማነው ? የት ነው ? መቼ ነው ? የሚለውን የተደረሰበትን እና ያገኘነውን መረጃ እንለዋወጣለን።
@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
TIKVAH-ETHIOPIA
#TikTok ' ቲክቶክ ' የተሰኘው መተግበሪያ አልባኒያ ውስጥ ለአንድ አመት እንደሚታገድ መገለጹ ይታወሳል። " እገዳው በኦንላይ የንግድ ስራ የሚሰሩ / ማርኬቲንግ ላይ ያሉ እንዲሁም የንግግርና ሃሳብ ነጻነት ላይ አሉታዊ ተፅእኖ ያመጣል " በሚል የመብት ተሟጋች ነን በሚሉ አካላት እገዳው ቢተችም የሀገሪቱ መንግሥት እገዳውን ተግባራዊ ያደርጋል ተብሏል። ቲክቶክ በቀጣይ ሳምንታት ይወርዳል ተብሏል። …
#TikTok📱
' ቲክቶክ ' አሜሪካ ውስጥ ከእሁድ ጀምሮ እስከ ወዲያኛው እንዲዘጋ ወይም እንዲሸጥ የሚለውን ውሳኔ የአሜሪካ ጠቅላይ ፍ/ቤት ደገፈ።
ዛሬ የአሜሪካ ጠቅላይ ፍ/ቤት ' ቲክቶክ ' በአሜሪካ እንዲዘጋ ካልሆነም እዲሸጥ ለሚጠይቀው የፌደራል ህግ ድጋፍ ሰጥቷል።
' ቲክቶክ ' ይግባኝ ቢጠይቅም ውድቅ ሆናል።
ከዚህ ቀደም መተግበሪያው " የአሜሪካውያንን የግል መረጃ ለቻይና መንግሥት አሳልፎ ይሰጣል በዚህ የብሔራዊ ጸጥታ አደጋ ደቅኗል " በሚል እንዲታገድ ካልሆነም ለአሜሪካ ሰዎች እንዲሸጥ የሚል ውሳኔ መተላለፉ ይታወሳል።
ዛሬ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ከዚህ ቀደም የተላለፈውን ውሳኔ ደግፏል።
ይህን ውሳኔ ተከትሎ ' ቲክቶክ ' ከእሁድ ጀምሮ ይታገዳል።
የእግዱ ተግባራዊነት ' ቲክቶክ 'ን ከአፕስቶር እና ፕሌይስቶር ላይ እንዲወገድ ያደርጋል።
አዲስ ተጠቃሚዎች ' ቲክቶክ ' ማውረድ አይችሉም ፤ ነባር ተጠቃሚዎች አፕዴት ማድረግ አይችሉም።
ተመራጩ ፕሬዜዳንት ዶናልድ ትራምፕ ' ቲክቶክ ' ን ለመታደግ እና የመታገዱ ውሳኔ እንዲዘገይ ለጠቅላይ ፍርድ ቤቱ ጠይቀው የነበረ ቢሆንም ፍርድ ቤቱ ግን የመጨረሻ ያለውን ውሳኔ አሳልፏል።
እንሆ ስልጣኑ ያበቃው የባይደን አስተዳደር " ህጉን ማስተግበር የቀጣዩ አስተዳደር ኃላፊነት ነው " ብሏል።
የ' ቲክቶክ ' ን እገዳ ለማዘግየት የሞከሩት ትራምፕ ሰኞ ስልጣናቸውን ይረከባሉ። ህጉን ማስተግበርም በሳቸው ላይ ተጥሏል።
ትራምፕ ከፍርድ ቤቱ ውሳኔ በኃላ በሰጡት ቃል " ውሳኔውን እኔው ወስናለሁ ፤ ውሳኔው እኔ ጋር ነው ምን እንደማደርግ ታያላችሁ " ብለዋል።
170 ሚሊዮን ተጠቃሚ አሜሪካ ውስጥ ያለው ' ቲክቶክ ' እስከወዲያኛው ይታገድ ይሆን ? ወይስ ከዚህ በኃላ ትራምፕ ማድረግ የሚችሉት ነገር ይኖር ይሆን ? በቀጣይ ይታያል።
መረጃው ከኤፒ፣ ፎርብስ፣ ሲኤንኤን የተሰባሰበ ነው።
@tikvahethiopia
' ቲክቶክ ' አሜሪካ ውስጥ ከእሁድ ጀምሮ እስከ ወዲያኛው እንዲዘጋ ወይም እንዲሸጥ የሚለውን ውሳኔ የአሜሪካ ጠቅላይ ፍ/ቤት ደገፈ።
ዛሬ የአሜሪካ ጠቅላይ ፍ/ቤት ' ቲክቶክ ' በአሜሪካ እንዲዘጋ ካልሆነም እዲሸጥ ለሚጠይቀው የፌደራል ህግ ድጋፍ ሰጥቷል።
' ቲክቶክ ' ይግባኝ ቢጠይቅም ውድቅ ሆናል።
ከዚህ ቀደም መተግበሪያው " የአሜሪካውያንን የግል መረጃ ለቻይና መንግሥት አሳልፎ ይሰጣል በዚህ የብሔራዊ ጸጥታ አደጋ ደቅኗል " በሚል እንዲታገድ ካልሆነም ለአሜሪካ ሰዎች እንዲሸጥ የሚል ውሳኔ መተላለፉ ይታወሳል።
ዛሬ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ከዚህ ቀደም የተላለፈውን ውሳኔ ደግፏል።
ይህን ውሳኔ ተከትሎ ' ቲክቶክ ' ከእሁድ ጀምሮ ይታገዳል።
የእግዱ ተግባራዊነት ' ቲክቶክ 'ን ከአፕስቶር እና ፕሌይስቶር ላይ እንዲወገድ ያደርጋል።
አዲስ ተጠቃሚዎች ' ቲክቶክ ' ማውረድ አይችሉም ፤ ነባር ተጠቃሚዎች አፕዴት ማድረግ አይችሉም።
ተመራጩ ፕሬዜዳንት ዶናልድ ትራምፕ ' ቲክቶክ ' ን ለመታደግ እና የመታገዱ ውሳኔ እንዲዘገይ ለጠቅላይ ፍርድ ቤቱ ጠይቀው የነበረ ቢሆንም ፍርድ ቤቱ ግን የመጨረሻ ያለውን ውሳኔ አሳልፏል።
እንሆ ስልጣኑ ያበቃው የባይደን አስተዳደር " ህጉን ማስተግበር የቀጣዩ አስተዳደር ኃላፊነት ነው " ብሏል።
የ' ቲክቶክ ' ን እገዳ ለማዘግየት የሞከሩት ትራምፕ ሰኞ ስልጣናቸውን ይረከባሉ። ህጉን ማስተግበርም በሳቸው ላይ ተጥሏል።
ትራምፕ ከፍርድ ቤቱ ውሳኔ በኃላ በሰጡት ቃል " ውሳኔውን እኔው ወስናለሁ ፤ ውሳኔው እኔ ጋር ነው ምን እንደማደርግ ታያላችሁ " ብለዋል።
170 ሚሊዮን ተጠቃሚ አሜሪካ ውስጥ ያለው ' ቲክቶክ ' እስከወዲያኛው ይታገድ ይሆን ? ወይስ ከዚህ በኃላ ትራምፕ ማድረግ የሚችሉት ነገር ይኖር ይሆን ? በቀጣይ ይታያል።
መረጃው ከኤፒ፣ ፎርብስ፣ ሲኤንኤን የተሰባሰበ ነው።
@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
TIKVAH-ETHIOPIA
#TPLF : ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህ.ወ.ሓ.ት) ጠቅላላ ጉባዔውን እንዲያደርግ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አሳስቧል። ምርጫ ቦርድ ፤ ህወሓት በኢትዮጵያ የምርጫ የፖለቲካ ፖርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ስነምግባር አዋጅን ለማሻሻል በወጣው አዋጅ ቁጥር መሠረት በልዩ ሁኔታ መመዝገቡን አስታውሷል። ፖርቲው ከተመዘገበበት ቀን ጀምሮ ባሉት ስድስት ወራት ጊዜ ውስጥ የፓርቲውን ጠቅላላ ጉባኤ እንዲያደርግ…
#TPLF
" የኢትዮጵያ ብሄራዊ የምርጫ ቦርድ የተናጠል ውሳኔን ዛሬ ይሁን ነገ አልቀበልም " - በደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር ) የሚመራው ህወሓት ማእከላይ ኮሚቴ
በደብረጽዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራው የህወሓት ማእከላይ ኮሚቴ ከጥር 5 እስከ ጥር 7 ቀን 2017 ዓ.ም ድረስ በወቅታዊ የክልሉ ሁኔታ ላይ አተኩሮ ስብሰባ ተቀምጦ ነበር።
ይህንን ተከትሎ ዛሬ ምሽት መግለጫ አውጥቷል።
በዚህም ቡድኑ ፦
- እስከ አሁን ያልተረጋገጠው የትግራይ ግዛታዊ አንድነት፤
- ተፈናቃዮች እና ስደተኞች ወደ ቄያቸው አለመመለስ፤
- የኢትዮጵያ ብሄራዊ የምርጫ ቦርድ ያወጣውን መግለጫ፤
- የፕሪቶሪያ የሰላም ውል አፈፃፀም በሚሉ አጀንዳዎች ላይ መወያየቱን ገልጾ " ቀጣይ የመፍትሄ እና የትግል አቅጣጫ አስቀምጫለሁ " ብሏል።
የህወሓት ማእከላዊ ኮሚቴ ባወጣው መግለጫ ፤ በፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት መሰረት የኢፌዴሪ ህገ-መንግስት እውቅና የሰጠው የትግራይ ግዛታዊ አንድነት አለመረጋገጡ ጠቅሶ " ተፈናቃይ እና ስደተኞች ወደ ቄያቸው ባለመመለሳቸው ሃዘን እና ቁጣ ተስምተኞናል ይህንን አስመልክቶ ' ይበቃል ' በሚል የተካሄደው ሰላማዊ የተቃውሞ ሰልፍ እደግፋለሁ " ብሏል።
ቡድኑ በመግለጫው " የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት በአግባቡ እንዳይፈፀም የኢትዮጵያ መንግስት እንቅፋት እየሆነ ነው ፡ በትግራይ ውስጥ የበቀለ #ከሃዲ_ሃይልም በተጨማሪ ስምምነቱ እያደናቀፈ ነው " የሚል ክስ አሰምቷል።
እንዴት እንደሆነ ባያብራራም " ችግሩ ከስር መሰረቱ ለመለወጥ ቆርጬ ተነስቻለሁ " ብሏል።
በመሰረተ ሃሳብ ደረጃ DDR ተቀባይነት ያለው እንደሆነ የገለፀም ሲሆን " ይሁን እንጂ DDR እንደምክንያት በመጠቀም የትግራይ ሰራዊት ለማፍረስ እየተደረገ ያለው ሴራ ተቀባይነተ የለውም " ሲል ገልጿል።
የኢትዮጵያ ብሄራዊ የምርጫ ቦርድ ህወሓት ህጋዊ ጉባኤ እንዲያካሂድ በማስመልከት በቅርቡ ያወጣው ቀን ገደብ ያካተተ መግለጫ አስመልክቶ በሰጠው ምላሽ ፥ " ቦርዱ ' ጉባኤ አካሂዱ ' የሚል ጨምሮ በተንኮል የተተበተቡ የተለያዩ ትእዛዞች ከመስጠት ተቆጥቦ የተፈጠሩ ልዩነቶች በፓለቲካዊ ውይይት ለመፍታት የተጀመረው ጥረት በማስቀጠሉ ላይ ያተኩር " ብሏል።
" ህወሓት ሁሌም ለሁለትዮሽ ውይይት ዝግጁ ነው ፤ የትግራይ ህዝብ ትግል እና መስዋእትነት የሚያራክስ የኢትዮጵያ ብሄራዊ የምርጫ ቦርድ የተናጠል ውሳኔ ግን ዛሬ ይሁን ነገ አልቀበልም " ሲል አቋሙን አንጸባርቋል።
ህወሓት ጊዚያዊ አስተዳደሩ በማቋቋም የአንበሳ ድርሻ እንደነበረው እና እንዳለው የጠቀሰው መግለጫው " አሁንም እንዲጠናከር ይሰራል ይሁን እንጂ ጊዚያዊ አስተዳደሩ ለማጠናከር እና ለመቆጣጠር በሚል ይቋቋማል የሚባለው ካውንስል አካል መሆን አልፈግም " ሲል ግልፅ አድርጓል።
በሊቀመንበር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር ) የሚመራው ህወሓት ማእከላይ ኮሚቴ በመግለጫው ማጠቃለያ ፤ " የኢትዮጵያ መንግስት ከጣልቃ ገብነት ተቆጥቦ የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት በቅን ልቦና በመፈፀም ለዘላቂ ሰላም እንዲሰራ " የሚል ጥሪ አቅርበዋል።
የህወሓት ቡድን ለሁለት ተከፍሎ የለየለት አለመግባባት ውስጥ ከገባ ወራት የተቆጠሩ ሲሆን ከወራት በፊት ለሁለት የተከፈሉት አመራሮች እና የጊዜያዊ አስተዳደሩ አመራሮች አዲስ አበባ ሄደው ጠ/ሚ ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) በተገኙበት ውይይት አድርገው ነበር።
ወደ መቐለ ከተመለሱ በኃላ ግን እስከ ዛሬ መግባባት ሳይፈጥሩ በመግላጫ ምልልስ ላይ ናቸው።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ደግሞ ህወሓት በልዩ ሁኔታ የተመዘገበው ነሀሴ 3 ቀን 2016 ዓ.ም መሆኑን በመግለጽ ጠቅላላ ጉባኤውን እስከ የካቲት 3 ቀን 2017 ዓ.ም እንዲያደርግ አሳስቧል።
ይህ በሕግ ፓርቲው ላይ የተጣለ ግዴታ በወቅቱ ሳይፈፀም ቢቀር ቦርዱ ሕጉን መሠረት በማድረግ ተገቢ ነው የሚለውን ውሳኔ የሚሰጥ መሆኑንም ገልጾ ነበር።
ከዚህ ቀደም የህወሓት አመራሮችን ለሁለት የከፈለ ጉባኤ መደረጉ አይዘነጋም። በወቅቱም ምርጫ ቦርድ ያልተገኘበትን እና ስርዓቱን ያልተከተለ ጠቅላላ ጉባኤ እውቅና እንደማይሰጥ ማስገንዘቡ ይታወሳል።
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia
" የኢትዮጵያ ብሄራዊ የምርጫ ቦርድ የተናጠል ውሳኔን ዛሬ ይሁን ነገ አልቀበልም " - በደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር ) የሚመራው ህወሓት ማእከላይ ኮሚቴ
በደብረጽዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራው የህወሓት ማእከላይ ኮሚቴ ከጥር 5 እስከ ጥር 7 ቀን 2017 ዓ.ም ድረስ በወቅታዊ የክልሉ ሁኔታ ላይ አተኩሮ ስብሰባ ተቀምጦ ነበር።
ይህንን ተከትሎ ዛሬ ምሽት መግለጫ አውጥቷል።
በዚህም ቡድኑ ፦
- እስከ አሁን ያልተረጋገጠው የትግራይ ግዛታዊ አንድነት፤
- ተፈናቃዮች እና ስደተኞች ወደ ቄያቸው አለመመለስ፤
- የኢትዮጵያ ብሄራዊ የምርጫ ቦርድ ያወጣውን መግለጫ፤
- የፕሪቶሪያ የሰላም ውል አፈፃፀም በሚሉ አጀንዳዎች ላይ መወያየቱን ገልጾ " ቀጣይ የመፍትሄ እና የትግል አቅጣጫ አስቀምጫለሁ " ብሏል።
የህወሓት ማእከላዊ ኮሚቴ ባወጣው መግለጫ ፤ በፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት መሰረት የኢፌዴሪ ህገ-መንግስት እውቅና የሰጠው የትግራይ ግዛታዊ አንድነት አለመረጋገጡ ጠቅሶ " ተፈናቃይ እና ስደተኞች ወደ ቄያቸው ባለመመለሳቸው ሃዘን እና ቁጣ ተስምተኞናል ይህንን አስመልክቶ ' ይበቃል ' በሚል የተካሄደው ሰላማዊ የተቃውሞ ሰልፍ እደግፋለሁ " ብሏል።
ቡድኑ በመግለጫው " የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት በአግባቡ እንዳይፈፀም የኢትዮጵያ መንግስት እንቅፋት እየሆነ ነው ፡ በትግራይ ውስጥ የበቀለ #ከሃዲ_ሃይልም በተጨማሪ ስምምነቱ እያደናቀፈ ነው " የሚል ክስ አሰምቷል።
እንዴት እንደሆነ ባያብራራም " ችግሩ ከስር መሰረቱ ለመለወጥ ቆርጬ ተነስቻለሁ " ብሏል።
በመሰረተ ሃሳብ ደረጃ DDR ተቀባይነት ያለው እንደሆነ የገለፀም ሲሆን " ይሁን እንጂ DDR እንደምክንያት በመጠቀም የትግራይ ሰራዊት ለማፍረስ እየተደረገ ያለው ሴራ ተቀባይነተ የለውም " ሲል ገልጿል።
የኢትዮጵያ ብሄራዊ የምርጫ ቦርድ ህወሓት ህጋዊ ጉባኤ እንዲያካሂድ በማስመልከት በቅርቡ ያወጣው ቀን ገደብ ያካተተ መግለጫ አስመልክቶ በሰጠው ምላሽ ፥ " ቦርዱ ' ጉባኤ አካሂዱ ' የሚል ጨምሮ በተንኮል የተተበተቡ የተለያዩ ትእዛዞች ከመስጠት ተቆጥቦ የተፈጠሩ ልዩነቶች በፓለቲካዊ ውይይት ለመፍታት የተጀመረው ጥረት በማስቀጠሉ ላይ ያተኩር " ብሏል።
" ህወሓት ሁሌም ለሁለትዮሽ ውይይት ዝግጁ ነው ፤ የትግራይ ህዝብ ትግል እና መስዋእትነት የሚያራክስ የኢትዮጵያ ብሄራዊ የምርጫ ቦርድ የተናጠል ውሳኔ ግን ዛሬ ይሁን ነገ አልቀበልም " ሲል አቋሙን አንጸባርቋል።
ህወሓት ጊዚያዊ አስተዳደሩ በማቋቋም የአንበሳ ድርሻ እንደነበረው እና እንዳለው የጠቀሰው መግለጫው " አሁንም እንዲጠናከር ይሰራል ይሁን እንጂ ጊዚያዊ አስተዳደሩ ለማጠናከር እና ለመቆጣጠር በሚል ይቋቋማል የሚባለው ካውንስል አካል መሆን አልፈግም " ሲል ግልፅ አድርጓል።
በሊቀመንበር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር ) የሚመራው ህወሓት ማእከላይ ኮሚቴ በመግለጫው ማጠቃለያ ፤ " የኢትዮጵያ መንግስት ከጣልቃ ገብነት ተቆጥቦ የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት በቅን ልቦና በመፈፀም ለዘላቂ ሰላም እንዲሰራ " የሚል ጥሪ አቅርበዋል።
የህወሓት ቡድን ለሁለት ተከፍሎ የለየለት አለመግባባት ውስጥ ከገባ ወራት የተቆጠሩ ሲሆን ከወራት በፊት ለሁለት የተከፈሉት አመራሮች እና የጊዜያዊ አስተዳደሩ አመራሮች አዲስ አበባ ሄደው ጠ/ሚ ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) በተገኙበት ውይይት አድርገው ነበር።
ወደ መቐለ ከተመለሱ በኃላ ግን እስከ ዛሬ መግባባት ሳይፈጥሩ በመግላጫ ምልልስ ላይ ናቸው።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ደግሞ ህወሓት በልዩ ሁኔታ የተመዘገበው ነሀሴ 3 ቀን 2016 ዓ.ም መሆኑን በመግለጽ ጠቅላላ ጉባኤውን እስከ የካቲት 3 ቀን 2017 ዓ.ም እንዲያደርግ አሳስቧል።
ይህ በሕግ ፓርቲው ላይ የተጣለ ግዴታ በወቅቱ ሳይፈፀም ቢቀር ቦርዱ ሕጉን መሠረት በማድረግ ተገቢ ነው የሚለውን ውሳኔ የሚሰጥ መሆኑንም ገልጾ ነበር።
ከዚህ ቀደም የህወሓት አመራሮችን ለሁለት የከፈለ ጉባኤ መደረጉ አይዘነጋም። በወቅቱም ምርጫ ቦርድ ያልተገኘበትን እና ስርዓቱን ያልተከተለ ጠቅላላ ጉባኤ እውቅና እንደማይሰጥ ማስገንዘቡ ይታወሳል።
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Earthquake : ዛሬ ሰኞ ምሽት 5:24 ሲል በሬክተር ስኬል 4.8 የተለካ የመሬት መንቀጥቀጥ ከአዋሽ 17 ኪ/ሜ ርቀት ላይ መከሰቱን የአሜሪካ ጂኦሎጂካል ሰርቬይ አሳውቋል። የመሬት መንቀጥቀጥ ንዝረቱ አዲስ አበባና ሌሎችም ከተሞች ተሰምቷል። " አሁን ላይ ቀንሷል ቆሟል ፣ ከአሁን በኃላ ምንም ነገር አይፈጠርም " በሚል መዘናጋት ጥንቃቄ እና ትኩረት ማጣት እንዳይመጣ መጠንቀቅ ይገባል። የመሬት…
“ አዋሽ ፈንታሌ አካባቢ ነው እየመነጨ ያለው። ደብረ ብርሃን የተሰማ ነገር የለም” - አታላይ አየለ (ፕ/ር)
ትላንት ከሌሊቱ 10፡46 በደብረ ብርሃን አካባቢ በሬክተር ስኬል 4.9 የተመዘገበ የመሬት መንቀጥቀጥ መከሰቱን የጀርመን የጂኦ ሳይንስ ጥናትና ምርምር ማዕከል ድረጽ መረጃ አውጥቷል ፤ ይኸው መረጃም ሲዘገብ ተስተውለዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵዮጵያ በበኩሉ፣ በጉዳዩ ዙሪያ ከዘርፉ ተመራማሪ ማብራሪያ ጠይቋል።
ደብረ ብርሃን አካባቢ የመሬት መንቀጥቀጥ ተከስቷል መባሉን እውነት ነው ? ብለን የጠየቅናቸው በአዲስ አበባ የመሬት መንቀጥቀጥ ሳይንስ መምህርና ተመራማሪ አታላይ አየለ (ፕ/ሮ)፣ " ኧረ ውሸት ነው " ሲሉ መልሰዋል።
" ደብረ ብርሃን አካባቢ የለም። እዛው አዋሽ ፈንታሌ አካባቢ ነው እየመነጨ ያለው። ደብረ ብርሃን የተሰማ ነገር የለም " ነው ያሉት።
" የዘርፉ ተቋማት በሚያወጡት መረጃ፣ ' ከደብረ ብርሃን ይህን ያህል ኪሎ ሜትር፣ ወይ ከመተሃራ ይህንን ያህል ኪሎ ሜትር ' ይላሉ ስም እየጠሩ። ከዛ በመለስ ግን እንደዚህ የሚባል ነገር የለም። ደብረ ብርሃን አሁን ከየት የመጣ መንቀጥቀጥ ነው? " ሲሉ ነው ምላሽ የሰጡት።
ከዚህ ቀደም ከደብረ ሲና በ52 ኪሎ ሜትር ተከሰተ ለተባ የመሬት መንቀጥቀጥ በተለመለተ፣ ከሚከሰትበት የአዋሽ ፈንታሌ አካባቢ የቦታ ለውጥ አደረገ ማለት እንዳልሆነ ተመራማሪው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸው ነበር።
" በአንዳንድ አካባቢ ተደጋግሞ እየተከሰተ ነው ያለው እንጂ የቀረበ ነገር የለም " ነበር ያሉት።
አዋሽ ፈንታሌ እየተከሰተ ያለው የመሬት መንቀጥቀጥ አዲስ አበባን ጨምሮ በሌሎች ከተሞች ንዝረቱ እየተሰማ እንደሆነ ይታወቃል።
ሌላው በተያያዘ፣ የአዋሽ ፈንታሌ አካባቢ የመሬት መንቀጥቀጥ አሁንስ በምን ደረጃ ላይ ነው ያለው ? በሚል ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ዛሬ ለቀረበላቸው ተጨማሪ ምላሽ ሰጥተዋል።
አታላይ አየለ (ፕ/ር) ምን ምላሽ ሰጡ ?
" ምንም የተለዬ ነገር የለም እንደቀጠለ ነው። ከቀን ቀን ትንሽ ለውጥ ያለው ይመስላል። ግን ነገ ይቆማል የሚባል ነገር አይደለም።
ስቲል ይታያል እንቅስቃሴ። የሚረግብ አይመስልም በአጭሩ።
ዌብ ሳይት ተለጠፈ የሚለው ሳይሆን ለሊት 10 ገደማ ተፈጠረ የተባለው አካባቢ አንድ ነው ሪፓርት የተደረገው ግን ከእኩለ ለሊት ጀምሮ እስካሁን ስንት ተፈጠረ ብትለኝ ከ100ዎች በላይ ሊሆኑ ይችላሉ።
ያ ማለት የሚረግብ አይነት አይደለም " ብለዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
ትላንት ከሌሊቱ 10፡46 በደብረ ብርሃን አካባቢ በሬክተር ስኬል 4.9 የተመዘገበ የመሬት መንቀጥቀጥ መከሰቱን የጀርመን የጂኦ ሳይንስ ጥናትና ምርምር ማዕከል ድረጽ መረጃ አውጥቷል ፤ ይኸው መረጃም ሲዘገብ ተስተውለዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵዮጵያ በበኩሉ፣ በጉዳዩ ዙሪያ ከዘርፉ ተመራማሪ ማብራሪያ ጠይቋል።
ደብረ ብርሃን አካባቢ የመሬት መንቀጥቀጥ ተከስቷል መባሉን እውነት ነው ? ብለን የጠየቅናቸው በአዲስ አበባ የመሬት መንቀጥቀጥ ሳይንስ መምህርና ተመራማሪ አታላይ አየለ (ፕ/ሮ)፣ " ኧረ ውሸት ነው " ሲሉ መልሰዋል።
" ደብረ ብርሃን አካባቢ የለም። እዛው አዋሽ ፈንታሌ አካባቢ ነው እየመነጨ ያለው። ደብረ ብርሃን የተሰማ ነገር የለም " ነው ያሉት።
" የዘርፉ ተቋማት በሚያወጡት መረጃ፣ ' ከደብረ ብርሃን ይህን ያህል ኪሎ ሜትር፣ ወይ ከመተሃራ ይህንን ያህል ኪሎ ሜትር ' ይላሉ ስም እየጠሩ። ከዛ በመለስ ግን እንደዚህ የሚባል ነገር የለም። ደብረ ብርሃን አሁን ከየት የመጣ መንቀጥቀጥ ነው? " ሲሉ ነው ምላሽ የሰጡት።
ከዚህ ቀደም ከደብረ ሲና በ52 ኪሎ ሜትር ተከሰተ ለተባ የመሬት መንቀጥቀጥ በተለመለተ፣ ከሚከሰትበት የአዋሽ ፈንታሌ አካባቢ የቦታ ለውጥ አደረገ ማለት እንዳልሆነ ተመራማሪው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸው ነበር።
" በአንዳንድ አካባቢ ተደጋግሞ እየተከሰተ ነው ያለው እንጂ የቀረበ ነገር የለም " ነበር ያሉት።
አዋሽ ፈንታሌ እየተከሰተ ያለው የመሬት መንቀጥቀጥ አዲስ አበባን ጨምሮ በሌሎች ከተሞች ንዝረቱ እየተሰማ እንደሆነ ይታወቃል።
ሌላው በተያያዘ፣ የአዋሽ ፈንታሌ አካባቢ የመሬት መንቀጥቀጥ አሁንስ በምን ደረጃ ላይ ነው ያለው ? በሚል ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ዛሬ ለቀረበላቸው ተጨማሪ ምላሽ ሰጥተዋል።
አታላይ አየለ (ፕ/ር) ምን ምላሽ ሰጡ ?
" ምንም የተለዬ ነገር የለም እንደቀጠለ ነው። ከቀን ቀን ትንሽ ለውጥ ያለው ይመስላል። ግን ነገ ይቆማል የሚባል ነገር አይደለም።
ስቲል ይታያል እንቅስቃሴ። የሚረግብ አይመስልም በአጭሩ።
ዌብ ሳይት ተለጠፈ የሚለው ሳይሆን ለሊት 10 ገደማ ተፈጠረ የተባለው አካባቢ አንድ ነው ሪፓርት የተደረገው ግን ከእኩለ ለሊት ጀምሮ እስካሁን ስንት ተፈጠረ ብትለኝ ከ100ዎች በላይ ሊሆኑ ይችላሉ።
ያ ማለት የሚረግብ አይነት አይደለም " ብለዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
#ንጉስ
ጥምቀት ሲነሳ ሎሚ ውርወራ ፣ ሳቅ እና ጨዋታው አይረሳ!
እንኳን አደረሳችሁ! ደስ ደስ የሚል በዓል ይሁንላችሁ😊 ለተጨማሪ መረጃ የቴሌግራም ቻናላችን ይቀላቀሉ https://t.iss.one/Negus_Malt
#ደስደስበንጉስ #Epiphany
#nonalcoholic #ንጉስ #DesDesWithNegus #ደስደስበንጉስ #የጣዕምልኬት_የደስታስሜት#ንጉስማልት
ጥምቀት ሲነሳ ሎሚ ውርወራ ፣ ሳቅ እና ጨዋታው አይረሳ!
እንኳን አደረሳችሁ! ደስ ደስ የሚል በዓል ይሁንላችሁ😊 ለተጨማሪ መረጃ የቴሌግራም ቻናላችን ይቀላቀሉ https://t.iss.one/Negus_Malt
#ደስደስበንጉስ #Epiphany
#nonalcoholic #ንጉስ #DesDesWithNegus #ደስደስበንጉስ #የጣዕምልኬት_የደስታስሜት#ንጉስማልት
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ኢትዮ ኢንተርናሽናል ስተዲ ሴንተር ከፍተኛ ትምህርታቸውን በአለም አቀፍ ተቋማት መከታተል ለሚፈልጉ የግንዛቤ መርሃግብር አዘጋጅቷል።
የፊታችን ማክሰኞ ጥር 13 ከጥዋቱ 1 ሰዓት እስከ 6:30 ድረስ በአዲስ አበባ EISC አዘጋጅነት 65 ከሚሆኑ የNCUK አጋር ዩኒቨርስቲዎች በአለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ እና ተመራጭ የሆኑት ተቋማት ተወካዮች እዚሁ አዲስ አበባ ተገኝተው የተማሪዎችን ጥያቄዎች ያስተናግዳሉ።
በመርሃግብሩ ለይ ተሳታፊ ለመሆን በዚህ ሊንክ ይመዝገቡ : https://eisc.uk/universities-fair-2025/
#ማሳሰቢያ 1 : የፕሮግራሙ ተሳታፊ ለመሆን ምንም አይነት ክፍያ ተማሪዎች አይጠየቁም።
#ማሳሰቢያ 2 : ለትምህርት እድል ተብሎ የሚከፈል ምንም አይነት ቅድመ ክፍያ የለም። ፕሮግራሙ ከማንኛውም አይነት ክፍያ ጋር የሚገናኝ አይደለም።
የፊታችን ማክሰኞ ጥር 13 ከጥዋቱ 1 ሰዓት እስከ 6:30 ድረስ በአዲስ አበባ EISC አዘጋጅነት 65 ከሚሆኑ የNCUK አጋር ዩኒቨርስቲዎች በአለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ እና ተመራጭ የሆኑት ተቋማት ተወካዮች እዚሁ አዲስ አበባ ተገኝተው የተማሪዎችን ጥያቄዎች ያስተናግዳሉ።
በመርሃግብሩ ለይ ተሳታፊ ለመሆን በዚህ ሊንክ ይመዝገቡ : https://eisc.uk/universities-fair-2025/
#ማሳሰቢያ 1 : የፕሮግራሙ ተሳታፊ ለመሆን ምንም አይነት ክፍያ ተማሪዎች አይጠየቁም።
#ማሳሰቢያ 2 : ለትምህርት እድል ተብሎ የሚከፈል ምንም አይነት ቅድመ ክፍያ የለም። ፕሮግራሙ ከማንኛውም አይነት ክፍያ ጋር የሚገናኝ አይደለም።
መላው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ምዕመናን በሙሉ እንኳን ለ2017 ዓ/ም የጥምቀት #ከተራ በዓል አደረሳችሁ !
መልካም በዓል !
@tikvahethiopia
መልካም በዓል !
@tikvahethiopia
" ...ሙሉ ተሳፋሪውን ነው የወሰዷቸው። መጀመሪያ የተመታው ግን አንድ ሹፌር ነው - " ጣና የከባድ መኪና አሽከርካሪዎች ማኀበር
አዋሽ ፓርክ አካባቢ ሰሞኑን አንድ ሚኒባስ ተሽከርካሪ ሙሉ ተሳፋሪዎች ከነአሽከርካሪው መታገታቸውን ጣና የከባድ ተሽከርከሪ አሽከርካሪዎች ማኀበር ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።
ማኀበሩ በሰጠን ቃል " አዋሽ አካባቢ ፓርክ አለ። እዚያ አካባቢ ታጣቂዎች ተሽከርካሪውን በጥይት መትተውት ሰው ቆስሏል " ብሏል።
" ተሽከርካሪው ተቃጥሏል። ኤክስፓርት ይሁን ሌላ የጫነ ተሽከርካሪ አልታወቀም። ተሳፋሪ ሰዎችንም ይዞ ነበር " ሲል ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አስረድቷል።
ተሳፋሪዎቹና ሹፌሩ ከምን ደረሱ ? ለሚለው ጥያቄ ማኀበሩ በምላሹ፣ " ሹፌሩም ታግቷል። ተሳፋሪውንም እንደዚሁ ሙሉ ተሳፋሪ ወስደዋል " ነው ያለው።
ተሳፋሪ ከያዘ ተሽከርካሪው የህዝብ ማመላለሻ ነበር እንዴ ? ስንል ላቀረብንለት ጥያቄ ማኀበሩ፣ " በተለምዶ ' አባዱላ ' የሚባለድ ሚኒባስ ነው፣ አዎ የሕዝብ ተሽከርካሪ ነበር " የሚል ምላሽ ሰጥቷል።
ምን ያክል ሰዎች እንደታገቱ ሲጠየቅም፣ " ቁጥሩ አልታወቀም። ሙሉ ተሳፋሪውን ነው የወሰዷቸው። መጀመሪያ የተመታው ግን አንድ ሹፌር ነው " ሲል መልሷል።
ድርጊቱን የፈጸሙ አካላት እንነማን እንደሆነ ሲያስረዳ፣ በዛ አካባቢ ላይ ከሸኔ ታጣቂዎች ውጪ ከማኀበረሱ የወጣ እንዲህ አይነት ድርጊት ከዚህ ቀደም አጋጥሞ እንደማያውቅ ነው የገለጸው።
ለአመታት ይኸው የሚባል ዘላቂ መፍትሄ ያልተገኘለት የታጠቁ አካላት ሹፌሮች ላይ የሚፈጽሙት ጥቃት ልጅን ያለ አባት፣ ወላጅን ያለ ልጅ እያስቀረ በመቀጠሉ የሚመለከታቸው አካላት ለጉዳዩ አሁንም ልዩ ትኩረት እንዲሰጡ ተጠይቋል።
ደረሰ ለተባለው ጥቃትና እገታ የባለስልጣናትን ምላሽ ለማካተት የተደረገው ሙከራ ፈቃደኞች ባለመሆናቸው ለጊዜው አልተሳካም።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
አዋሽ ፓርክ አካባቢ ሰሞኑን አንድ ሚኒባስ ተሽከርካሪ ሙሉ ተሳፋሪዎች ከነአሽከርካሪው መታገታቸውን ጣና የከባድ ተሽከርከሪ አሽከርካሪዎች ማኀበር ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።
ማኀበሩ በሰጠን ቃል " አዋሽ አካባቢ ፓርክ አለ። እዚያ አካባቢ ታጣቂዎች ተሽከርካሪውን በጥይት መትተውት ሰው ቆስሏል " ብሏል።
" ተሽከርካሪው ተቃጥሏል። ኤክስፓርት ይሁን ሌላ የጫነ ተሽከርካሪ አልታወቀም። ተሳፋሪ ሰዎችንም ይዞ ነበር " ሲል ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አስረድቷል።
ተሳፋሪዎቹና ሹፌሩ ከምን ደረሱ ? ለሚለው ጥያቄ ማኀበሩ በምላሹ፣ " ሹፌሩም ታግቷል። ተሳፋሪውንም እንደዚሁ ሙሉ ተሳፋሪ ወስደዋል " ነው ያለው።
ተሳፋሪ ከያዘ ተሽከርካሪው የህዝብ ማመላለሻ ነበር እንዴ ? ስንል ላቀረብንለት ጥያቄ ማኀበሩ፣ " በተለምዶ ' አባዱላ ' የሚባለድ ሚኒባስ ነው፣ አዎ የሕዝብ ተሽከርካሪ ነበር " የሚል ምላሽ ሰጥቷል።
ምን ያክል ሰዎች እንደታገቱ ሲጠየቅም፣ " ቁጥሩ አልታወቀም። ሙሉ ተሳፋሪውን ነው የወሰዷቸው። መጀመሪያ የተመታው ግን አንድ ሹፌር ነው " ሲል መልሷል።
ድርጊቱን የፈጸሙ አካላት እንነማን እንደሆነ ሲያስረዳ፣ በዛ አካባቢ ላይ ከሸኔ ታጣቂዎች ውጪ ከማኀበረሱ የወጣ እንዲህ አይነት ድርጊት ከዚህ ቀደም አጋጥሞ እንደማያውቅ ነው የገለጸው።
ለአመታት ይኸው የሚባል ዘላቂ መፍትሄ ያልተገኘለት የታጠቁ አካላት ሹፌሮች ላይ የሚፈጽሙት ጥቃት ልጅን ያለ አባት፣ ወላጅን ያለ ልጅ እያስቀረ በመቀጠሉ የሚመለከታቸው አካላት ለጉዳዩ አሁንም ልዩ ትኩረት እንዲሰጡ ተጠይቋል።
ደረሰ ለተባለው ጥቃትና እገታ የባለስልጣናትን ምላሽ ለማካተት የተደረገው ሙከራ ፈቃደኞች ባለመሆናቸው ለጊዜው አልተሳካም።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia