#USA 🔥 በአሜሪካ ፤ በሎስ አንጀለስ ታሪክ አውዳሚ ነው በተባለ የሰደድ እሳት እስካሁን በውል ያልታወቁ ሰዎች ሲሞቱ ፤ በርካቶችም ተፈናቅለዋል።
እሳቱ በሎስ አንጀለስ ከተማ በብዙ ስፍራ እየተዛመተ ነው ተብሏል።
የሰደድ እሳቱ የሆሊውድ ምልክት በሚገኝበት የሆሊውድ ኮረብታማ ስፍራዎች ላይ እየተያያዘ መሆኑ ተነግሯል።
በሎስ አንጀለስ እና በአጎራባች ግዛቶች ቢያንስ 5 ሰደድ እሳቶች የተያያዙ ሲሆን ሶስቱን ሙሉ በሙሉ መቆጣጠር አልተቻለም።
1. ፓሊሳድስ
ፓሊሳድስ የተሰኘ መጠሪያ የተሰጠው ሰደድ እሳት በሎስ አንጀለስ የተቀሰቀሰው ማክሰኞ እለት ሲሆን በግዛቲቷ ትልቁ ነው። የፓስፊክ ፓሊሳድስ አካባቢን ጨምሮ ከ17 ሺህ 200 ሄክታር በላይ የሚሸፍን ሰፊ ግዛት አውድሟል።
2. ኢቶን
ኢቶን የተሰኘው ደግሞ በሰሜናዊ የሎስ አንጀለስ እን አልታዴና ባሉ ከተሞች እየተዛመተ የሚገኝ ሲሆን 10 ሺህ 600 ሄክታርን መሬት በመሸፈን በግዛቲቷ ሁለተኛው ትልቁ እሳት ሆኗል።
3. ኸረስት
ኸረትስ የተሰኘው ሰደድ እሳት ማክሰኞ እለት ተከስቶ ከሳን ፈርናንዶ በስተሰሜን በኩል እየተዛመተ ይገኛል። ይህም እሳት 855 ሄክታርን ይሸፍናል።
4. ሊዲያ
ይህ ደግሞ ረቡዕ ከሰዓት በኋላ በሎስ አንጀለስ በስተሰሜን ተራራማዋ አክቶን አካባቢ ተቀስቅሶ ወደ 350 ሄክታርን መሬት በመሸፈን ተዛምቷል።
5. ሰንሴት
ይህ ሰደድ እሳት ረቡዕ ምሽት ላይ በሆሊውድ ኮረብታማ ስፍራዎች የተከሰተው ሰደድ እሳት ሲሆን ከሰዓት ባነሰ ጊዜ ውስጥ ወደ 20 ሄክታር እያደገ ይገኛል። በአሁኑ ወቅት ወደ 43 ሄክታር ተዛምቷል።
ውድሌይ እና ኦሊቫስ የተሰኙት ሰደድ እሳቶች በአሁኑ ወቅት በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የአካባቢው የእሳት አደጋ ባስልጣናት ገልጸዋል።
የመረጃው ምንጮች ፦ ቢቢሲ እና ሲኤንኤን ናቸው።
ቪድዮ ፦ ከማህበራዊ ሚዲያ
@tikvahethiopia
እሳቱ በሎስ አንጀለስ ከተማ በብዙ ስፍራ እየተዛመተ ነው ተብሏል።
የሰደድ እሳቱ የሆሊውድ ምልክት በሚገኝበት የሆሊውድ ኮረብታማ ስፍራዎች ላይ እየተያያዘ መሆኑ ተነግሯል።
በሎስ አንጀለስ እና በአጎራባች ግዛቶች ቢያንስ 5 ሰደድ እሳቶች የተያያዙ ሲሆን ሶስቱን ሙሉ በሙሉ መቆጣጠር አልተቻለም።
1. ፓሊሳድስ
ፓሊሳድስ የተሰኘ መጠሪያ የተሰጠው ሰደድ እሳት በሎስ አንጀለስ የተቀሰቀሰው ማክሰኞ እለት ሲሆን በግዛቲቷ ትልቁ ነው። የፓስፊክ ፓሊሳድስ አካባቢን ጨምሮ ከ17 ሺህ 200 ሄክታር በላይ የሚሸፍን ሰፊ ግዛት አውድሟል።
2. ኢቶን
ኢቶን የተሰኘው ደግሞ በሰሜናዊ የሎስ አንጀለስ እን አልታዴና ባሉ ከተሞች እየተዛመተ የሚገኝ ሲሆን 10 ሺህ 600 ሄክታርን መሬት በመሸፈን በግዛቲቷ ሁለተኛው ትልቁ እሳት ሆኗል።
3. ኸረስት
ኸረትስ የተሰኘው ሰደድ እሳት ማክሰኞ እለት ተከስቶ ከሳን ፈርናንዶ በስተሰሜን በኩል እየተዛመተ ይገኛል። ይህም እሳት 855 ሄክታርን ይሸፍናል።
4. ሊዲያ
ይህ ደግሞ ረቡዕ ከሰዓት በኋላ በሎስ አንጀለስ በስተሰሜን ተራራማዋ አክቶን አካባቢ ተቀስቅሶ ወደ 350 ሄክታርን መሬት በመሸፈን ተዛምቷል።
5. ሰንሴት
ይህ ሰደድ እሳት ረቡዕ ምሽት ላይ በሆሊውድ ኮረብታማ ስፍራዎች የተከሰተው ሰደድ እሳት ሲሆን ከሰዓት ባነሰ ጊዜ ውስጥ ወደ 20 ሄክታር እያደገ ይገኛል። በአሁኑ ወቅት ወደ 43 ሄክታር ተዛምቷል።
ውድሌይ እና ኦሊቫስ የተሰኙት ሰደድ እሳቶች በአሁኑ ወቅት በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የአካባቢው የእሳት አደጋ ባስልጣናት ገልጸዋል።
የመረጃው ምንጮች ፦ ቢቢሲ እና ሲኤንኤን ናቸው።
ቪድዮ ፦ ከማህበራዊ ሚዲያ
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" ሰማይ ላይ ያየነዉ እንግዳ ነገር ፍርሀት ዉስጥ ጥሎናል " - ነዋሪዎች ዛሬ ምሽት በበአርባ ምንጭ ፣ ወላይታ ሶዶ ፣ ቡርጂ ፣ ሱሮ ባርጉዳ (ምዕራብ ጉጂ ዞን) እና ሌሎችም በርካታ ስፍራዎች በሰማይ ላይ የታየዉ ተምዘግዛጊ ሮኬት መሳይ ተቀጣጣይ ነገር ፍርሃት አንደጫረባቸዉ የአካባቢው ነዋሪዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል። ነዋሪዎቹ " ምሽት 2 ሰዓት ገደማ ሮኬት መሳይ ተቀጣጣይ ብርሃናማ ነገር በሰማይ…
" የማጣራት ሥራውን እስክናጠናቅቅ ሁሉም ሰው በተረጋጋ መንፈስ እንዲጠባበቅ በትህትና እንጠይቃለን " - የኢትዮጵያ የስፔስ ሳይንስ ሶሳይቲ
የኢትዮጵያ የስፔስ ሳይንስ ሶሳይቲ በትናንትናው ዕለት ከምሽቱ 1፡30 ገደማ በደቡብ እና ደቡብ ምዕራብ የሀገራችን ክፍሎች በሰማይ ላይ እየተቀጣጠሉ በከፍተኛ ፍጥነት ሲንቀሳቀሱ የነበሩ የቁስ አካላት ስብስብ መታየታቸው ሪፖርት እንደደረሰው ዛሬ ጥዋት አሳውቋል።
" በደረሰን ተንቀሳቃሽ ምስል ለመመልከት እንደቻልነው የእነዚህ አካላት ስብስብ የጠፈር ፍርስራሾች አልያም የሚቲዮር አለቶች ይመስላሉ " ብሏል።
" ስብስቡ ወደ ደቡባዊ የሃገሪቱ አቅጣጫ በከፍተኛ ፍጥነት በሰማይ ላይ ሲምዘገዘግ እንደነበረም ለማወቅ ተችሏል " ሲል አክሏል።
" የክስተቱን ተፈጥሮ በእርግጠኝነት ለማብራራት ያስችለን ዘንድ ሁኔታውን በቅርበት እያጣራን የምንገኝ ሲሆን ፤ ወቅታዊ መረጃዎችን እንደደረሱን የምናቀርብ ይሆናል " ብሏል።
" የማጣራት ሥራ እንኪጠናቀቅ ድረስ ሁሉም ሰው በተረጋጋ መንፈስ እንዲጠባበቅ በትህትና እንጠይቃለን " ሲል ጥሪውን አቅርቧል።
#ESSS
@tikvahethiopia
የኢትዮጵያ የስፔስ ሳይንስ ሶሳይቲ በትናንትናው ዕለት ከምሽቱ 1፡30 ገደማ በደቡብ እና ደቡብ ምዕራብ የሀገራችን ክፍሎች በሰማይ ላይ እየተቀጣጠሉ በከፍተኛ ፍጥነት ሲንቀሳቀሱ የነበሩ የቁስ አካላት ስብስብ መታየታቸው ሪፖርት እንደደረሰው ዛሬ ጥዋት አሳውቋል።
" በደረሰን ተንቀሳቃሽ ምስል ለመመልከት እንደቻልነው የእነዚህ አካላት ስብስብ የጠፈር ፍርስራሾች አልያም የሚቲዮር አለቶች ይመስላሉ " ብሏል።
" ስብስቡ ወደ ደቡባዊ የሃገሪቱ አቅጣጫ በከፍተኛ ፍጥነት በሰማይ ላይ ሲምዘገዘግ እንደነበረም ለማወቅ ተችሏል " ሲል አክሏል።
" የክስተቱን ተፈጥሮ በእርግጠኝነት ለማብራራት ያስችለን ዘንድ ሁኔታውን በቅርበት እያጣራን የምንገኝ ሲሆን ፤ ወቅታዊ መረጃዎችን እንደደረሱን የምናቀርብ ይሆናል " ብሏል።
" የማጣራት ሥራ እንኪጠናቀቅ ድረስ ሁሉም ሰው በተረጋጋ መንፈስ እንዲጠባበቅ በትህትና እንጠይቃለን " ሲል ጥሪውን አቅርቧል።
#ESSS
@tikvahethiopia
#telebirr
🌟 10% የገንዘብ ስጦታ ከተጨማሪ የዕድል ሽልማቶች ጋር!!
የገናን በዓል አስመልክቶ ከባህርማዶ በቴሌብር ሬሚት እና በአጋሮቻችን በኩል የተላከልዎን ዓለም አቀፍ ሐዋላ በቴሌብር ሲቀበሉ 10% የገንዘብ ስጦታ ያገኛሉ፡፡
💁♂️ በተጨማሪም 6ሺህ ብር እና ከዛ በላይ ሲቀበሉ አጓጊ ለሆነው ልዩ የዕድል ጨዋታ ብቁ ይሆናሉ!
1️⃣5️⃣ የቤት ዕቃዎች - እያንዳንዳቸው 100,000 ብር
2️⃣0️⃣ የበግ ስጦታዎች - እያንዳንዳቸው 15,000 ብር
5️⃣0️⃣ የበዓል አስቤዛ - እያንዳንዳቸው 10,000 ብር
3️⃣0️⃣0️⃣ የኪስ ገንዘብ - እያንዳንዳቸው 5,000 ብር
🌍🎁 እንዲሁም በርካታ የሞባይል ዳታ ጥቅሎች
የሚቀበሉት የገንዘብ መጠን ሲጨምር የጨዋታ ዕድልዎም ይጨምራል!
🗓 እስከ ጥር 16 ቀን 2017 ዓ.ም ብቻ!
ቴሌብር - እጅግ ቀላል፣ ፈጣን፣ ምቹ እና አስተማማኝ!
#Ethiotelecom #telebirrSupperApp #DigitalEthiopia #DigitalAfrica #RealizingDigitalEthiopia
🌟 10% የገንዘብ ስጦታ ከተጨማሪ የዕድል ሽልማቶች ጋር!!
የገናን በዓል አስመልክቶ ከባህርማዶ በቴሌብር ሬሚት እና በአጋሮቻችን በኩል የተላከልዎን ዓለም አቀፍ ሐዋላ በቴሌብር ሲቀበሉ 10% የገንዘብ ስጦታ ያገኛሉ፡፡
💁♂️ በተጨማሪም 6ሺህ ብር እና ከዛ በላይ ሲቀበሉ አጓጊ ለሆነው ልዩ የዕድል ጨዋታ ብቁ ይሆናሉ!
1️⃣5️⃣ የቤት ዕቃዎች - እያንዳንዳቸው 100,000 ብር
2️⃣0️⃣ የበግ ስጦታዎች - እያንዳንዳቸው 15,000 ብር
5️⃣0️⃣ የበዓል አስቤዛ - እያንዳንዳቸው 10,000 ብር
3️⃣0️⃣0️⃣ የኪስ ገንዘብ - እያንዳንዳቸው 5,000 ብር
🌍🎁 እንዲሁም በርካታ የሞባይል ዳታ ጥቅሎች
የሚቀበሉት የገንዘብ መጠን ሲጨምር የጨዋታ ዕድልዎም ይጨምራል!
🗓 እስከ ጥር 16 ቀን 2017 ዓ.ም ብቻ!
ቴሌብር - እጅግ ቀላል፣ ፈጣን፣ ምቹ እና አስተማማኝ!
#Ethiotelecom #telebirrSupperApp #DigitalEthiopia #DigitalAfrica #RealizingDigitalEthiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#Kenya
ትላንት ምሽት በኢትዮጵያ ደቡብ እና ደቡብ ምዕራብ ክፍሎች በሰማይ ላይ እየተቀጣጠሉ በከፍተኛ ፍጥነት ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ብርሃን ያላቸው የቁስ አካላት ስብስብ በኬንያ ሰሜናዊ ምስራቅ ክፍልም ታይተዋል።
እነዚህ ቁስ አካላት በኬንያ ቱርካና፣ ማርሳቢት፣ ሞያሌ አካባቢ መታየታቸውን የኬንያ የማህበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች ገልጸዋል።
ምንም እንኳን ቁስ አካላቱ " የጠፈር ፍርስራሾች ናቸው በገጠሪቱ የሀገሪቱ ክፍል (ኬንያ - ኢትዮጵያ ድንበር) ወድቀዋል ፤ ሲወድቁም ከፍተኛ ድምጽ ተሰምቷል ፤ ከሚቃጠል ነገር ጭስም ታይቷል ሽታም ነበረው " እያሉ ብዙ ተከታይ ያላቸው የኬንያ ፀሀፊዎች X ላይ ቢፅፉም የኬንያ ስፔስ ኤጀንሲ በይፋ የሰጠው ማረጋገጫ የለም።
እስካሁን የኬንያ ስፔስ ኤጀንሲ ፥ ቁስ አካላቱ ኬንያ ውስጥ ስለመውደቃቸው ማረጋገጫ አልሰጠም ስለ ጉዳዩ መግለጫም አላወዋጣም።
ከሰሞኑን በኬንያ ማኩኒ ካውንቲ ሙኩኩ በተባለች ትንሽዬ መንደር ከሰማይ ወርዷል የተባለ 2 ነጥብ 5 ሜትር ስፋት ያለውና 500 ኪሎግራም ክብደት ያለው ቁስ በርካቶችን አስደንግጦ ነበር።
የኬንያ የስፔስ ኤጀንሲ ሰዎች ቁሱ ወደወደቀበት ስፍ በማቅናት ምንነቱን ለማጥናት የሞከሩ ሲሆን ወደ ህዋ የመጠቀ ሮኬት ቁርጥራጭ ሊሆን እንደሚችል ገምተዋል።
ቀለበት ቅርጹ ከሮኬት ከተነጠለ በኋላ የሚፈረካከስ እንደነበር የተገለጸ ሲሆን የየትኛው ሀገር ወይም ኩባንያ ንብረት እንደሆነ የማጣራት ስራ እየተሰራ ነው። እስካሁን መደምደሚያ ላይ አልተደረሰም።
ተቋሙ " እንደዚህ አይነት ቁሶች (በኬንያ የወደቀው ቀለበት) ወደ ምድር ምህዋር ሲመለሱ ራሳቸውን እንዲያቃጥሉ አልያም ወደ ውቅያኖሶች እንዲገቡ ተደርገው የሚሰሩ ናቸው " ሲል ነው ያብራራው።
እንደ ኒውዮርክ ታይምስ መረጃ ከሆነ ባለፉት ስድስት አስርት አመታት በሀገራት መካከል የሚደረግ የህዋ ላይ ፉክክር መጠናከር ከሰማይ ላይ የሚወድቁ ቁሶች እንዲበራከቱ አድርጓል።
ባለፈው አመት ባወጣ የአውሮፓ የጠፈር ኤጀንሲ መረጃ በዝቅተኛ የምድር ምህዋር ውስጥ ከ14 ሺህ ቶን በላይ ቁሶች እንዳሉ ተገምቷል ፤ ከዚህ ውስጥም ከሲሶ በላዩ ለህዋ ምርምር የማያስፈልጉ ቁሳቁሶች ናቸው።
እንደ መረጀው ፥ በየአመቱ ከ110 በላይ የሳተላይት ማምጠቅ ሙከራዎች ይደረጋሉ ፤ በጥቂቱ 10 ሳተላይቶች እና ሌሎች የምርምር ቁሳቁሶች ወደ ትንንሽ ስብርባሪዎች ይቀየራሉ። ይህም ከህዋ ላይ ወደ መሬት የሚወድቁ ነገሮች እንዲበራከቱ አድርጓል።
መረጃው ከኬንያ የማህበራዊ ትስስር መድረኮች፣ ከኒውዮርክ ታይምስ፣ ከቢቢሲ፣ ከአል አይን ፣ ከኬንያ ስፔስ ኤጀንሲ ነው የተገኘው።
@tikvahethiopia
ትላንት ምሽት በኢትዮጵያ ደቡብ እና ደቡብ ምዕራብ ክፍሎች በሰማይ ላይ እየተቀጣጠሉ በከፍተኛ ፍጥነት ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ብርሃን ያላቸው የቁስ አካላት ስብስብ በኬንያ ሰሜናዊ ምስራቅ ክፍልም ታይተዋል።
እነዚህ ቁስ አካላት በኬንያ ቱርካና፣ ማርሳቢት፣ ሞያሌ አካባቢ መታየታቸውን የኬንያ የማህበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች ገልጸዋል።
ምንም እንኳን ቁስ አካላቱ " የጠፈር ፍርስራሾች ናቸው በገጠሪቱ የሀገሪቱ ክፍል (ኬንያ - ኢትዮጵያ ድንበር) ወድቀዋል ፤ ሲወድቁም ከፍተኛ ድምጽ ተሰምቷል ፤ ከሚቃጠል ነገር ጭስም ታይቷል ሽታም ነበረው " እያሉ ብዙ ተከታይ ያላቸው የኬንያ ፀሀፊዎች X ላይ ቢፅፉም የኬንያ ስፔስ ኤጀንሲ በይፋ የሰጠው ማረጋገጫ የለም።
እስካሁን የኬንያ ስፔስ ኤጀንሲ ፥ ቁስ አካላቱ ኬንያ ውስጥ ስለመውደቃቸው ማረጋገጫ አልሰጠም ስለ ጉዳዩ መግለጫም አላወዋጣም።
ከሰሞኑን በኬንያ ማኩኒ ካውንቲ ሙኩኩ በተባለች ትንሽዬ መንደር ከሰማይ ወርዷል የተባለ 2 ነጥብ 5 ሜትር ስፋት ያለውና 500 ኪሎግራም ክብደት ያለው ቁስ በርካቶችን አስደንግጦ ነበር።
የኬንያ የስፔስ ኤጀንሲ ሰዎች ቁሱ ወደወደቀበት ስፍ በማቅናት ምንነቱን ለማጥናት የሞከሩ ሲሆን ወደ ህዋ የመጠቀ ሮኬት ቁርጥራጭ ሊሆን እንደሚችል ገምተዋል።
ቀለበት ቅርጹ ከሮኬት ከተነጠለ በኋላ የሚፈረካከስ እንደነበር የተገለጸ ሲሆን የየትኛው ሀገር ወይም ኩባንያ ንብረት እንደሆነ የማጣራት ስራ እየተሰራ ነው። እስካሁን መደምደሚያ ላይ አልተደረሰም።
ተቋሙ " እንደዚህ አይነት ቁሶች (በኬንያ የወደቀው ቀለበት) ወደ ምድር ምህዋር ሲመለሱ ራሳቸውን እንዲያቃጥሉ አልያም ወደ ውቅያኖሶች እንዲገቡ ተደርገው የሚሰሩ ናቸው " ሲል ነው ያብራራው።
እንደ ኒውዮርክ ታይምስ መረጃ ከሆነ ባለፉት ስድስት አስርት አመታት በሀገራት መካከል የሚደረግ የህዋ ላይ ፉክክር መጠናከር ከሰማይ ላይ የሚወድቁ ቁሶች እንዲበራከቱ አድርጓል።
ባለፈው አመት ባወጣ የአውሮፓ የጠፈር ኤጀንሲ መረጃ በዝቅተኛ የምድር ምህዋር ውስጥ ከ14 ሺህ ቶን በላይ ቁሶች እንዳሉ ተገምቷል ፤ ከዚህ ውስጥም ከሲሶ በላዩ ለህዋ ምርምር የማያስፈልጉ ቁሳቁሶች ናቸው።
እንደ መረጀው ፥ በየአመቱ ከ110 በላይ የሳተላይት ማምጠቅ ሙከራዎች ይደረጋሉ ፤ በጥቂቱ 10 ሳተላይቶች እና ሌሎች የምርምር ቁሳቁሶች ወደ ትንንሽ ስብርባሪዎች ይቀየራሉ። ይህም ከህዋ ላይ ወደ መሬት የሚወድቁ ነገሮች እንዲበራከቱ አድርጓል።
መረጃው ከኬንያ የማህበራዊ ትስስር መድረኮች፣ ከኒውዮርክ ታይምስ፣ ከቢቢሲ፣ ከአል አይን ፣ ከኬንያ ስፔስ ኤጀንሲ ነው የተገኘው።
@tikvahethiopia
ሕብር ብልሕ የሴቶች ዋዲያህ የቁጠባ ሒሳብ
በሕብር ሐቅ ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎት መካከል አንዱ የሆነውን የሕብር ብልሕ የሴቶች ዋዲያህ የቁጠባ ሒሳብ በመክፈት ተጠቃሚ ይሁኑ፡፡
ጁመዓ ሙባረክ!
ሕብረት ባንክ
በሕብረት እንደግ!
📞 ለበለጠ መረጃ ወደ 995 ነፃ የጥሪ ማዕከል ይደውሉ፡፡
🤳 በቀላሉ አዳዲስ መረጃዎች እንዲደርስዎ የቴሌግራም ገፃችንን አሁኑኑ ይቀላቀሉ፡፡ https://t.iss.one/HibretBanket
🌐 ሌሎች የማህበራዊ ገፆቻችንን እና ድህረ ገፃችንን linktr.ee/Hibret.Bank ይጎብኙ፡፡
#interestfreebanking #womenssaving #Hibirhaq
በሕብር ሐቅ ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎት መካከል አንዱ የሆነውን የሕብር ብልሕ የሴቶች ዋዲያህ የቁጠባ ሒሳብ በመክፈት ተጠቃሚ ይሁኑ፡፡
ጁመዓ ሙባረክ!
ሕብረት ባንክ
በሕብረት እንደግ!
📞 ለበለጠ መረጃ ወደ 995 ነፃ የጥሪ ማዕከል ይደውሉ፡፡
🤳 በቀላሉ አዳዲስ መረጃዎች እንዲደርስዎ የቴሌግራም ገፃችንን አሁኑኑ ይቀላቀሉ፡፡ https://t.iss.one/HibretBanket
🌐 ሌሎች የማህበራዊ ገፆቻችንን እና ድህረ ገፃችንን linktr.ee/Hibret.Bank ይጎብኙ፡፡
#interestfreebanking #womenssaving #Hibirhaq
" ከ260 በላይ ቤተሰቦች ጦም ለማደርና ለለልመና ለመውጣት ይገደዳሉ " - ነዋሪዎች
በአማራ ክልል ሰሜን ወሎ ዞን ፤ በዋድላ ወረዳ በ11 ቀበሌዎች በተለያዩ ቀናት የሰብል ክምር ላይ ከፍተኛ የእሳት ቃጠሎ መድረሱ ተሰምቷል።
" ምክንያቱ አልታወቀም " በተባለው የእሳት ቃጠሎ የ154 አርሶ አደሮች እህል ሰብል ክምር መቃጠሉን የዋድላ ኮሚኒኬሽን ገልጿል።
በ03 ቤተሆር ቀበሌ ቀጭኔ ጎጥ ጥር 1/2017 ዓ/ም በደረሰው ቃጠሎ ጉዳት የደረሰባቸው አርሶ አደሮች የቃጠሎው መነሻ በውል አለመታወቁን ገልፀው ከፍተኛ ጉዳት መድረሱን አስረድተዋል፡፡
በዚህ ቀበሌ ብቻ የ52 አርሶ አደሮች የመህር ሰብል ክምር የተቃጠለ ሲሆን የአንዳንዶቹ ከዚህ ከተቃጠለው ሰብል ውጭ ሌላ ምንም ሰብል/አዝመራ እንደሌላቸው ገልፀዋል፡፡
በዚህ ቀበሌ ብቻ የ52 አርሶ አደሮች የሰብል ክምር ሙሉ በሙሉ ሲቃጠል በቤተሰብ ደረጃም ከ260 በላይ የቤተሰብ አባላት ጦም ለማደርና ለለልመና ለመውጣት እንደሚገደዱ የአካባቢው የህብረተሰብ ክፍሎች ተናግረዋል።
የዋድላ ወረዳ ቅድመ ማስጠንቀቂያ ቡድን መሪ አቶ ምትኩ ሞላ ምን አሉ ?
" በወረዳው በተለያዩ ቀበሌዎች የእሳት ቃጠሎ ተከስቷል።
እስካሁን ባለው መረጃ 770 የሚሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎች የጉዳቱ ሰለባ ሆነዋል " ብለዋል።
የዋድላ ወረዳ ግብርና ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ ሙሉየ ረታ ምን አሉ ?
" እንደ ወረዳ በ11 ቀበለሌዎች በ152 ክምር ላይ ቃጠሎ የደረሰ ሲሆን 154 አርሶ አደሮች የጉዳቱ አካል ሁናዋል።
የደረሰው ውድመት በኩንታል 4 ሺ 560 ሲሆን ከ32 ሚሊዮን ብር በላይ ጉዳት ደርሷል።
አሁንም ቢሆን አርሶ አደራችን የመውቂያ ማሽን ይምጣልን ጥያቄ እያቀረቡ ስለሆነ ማሽኑን መንግስት ቢያቀርብልን አርሶ አደራችን ተጠቃሚ እናደርጋለን።
አሁን ላይ በወረዳችን የደረሰው ጉዳት ከፍተኛ ስለሆነና ወረዳው ይህን የተጎዳ የህብረሰብ ክፍል መረዳት ስለማይችል መረጃውን ለረጅ ድርጅቶች በማጋራትና የምትችሉትን ሁሉ በማገዝ የሰብዓዊነታችሁን ሚና እንድተወጡ " ብለዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ መረጃውን ከዋድላ ወረዳ ኮሚኒኬሽን ነው ያገኘው።
@tikvahethiopia
በአማራ ክልል ሰሜን ወሎ ዞን ፤ በዋድላ ወረዳ በ11 ቀበሌዎች በተለያዩ ቀናት የሰብል ክምር ላይ ከፍተኛ የእሳት ቃጠሎ መድረሱ ተሰምቷል።
" ምክንያቱ አልታወቀም " በተባለው የእሳት ቃጠሎ የ154 አርሶ አደሮች እህል ሰብል ክምር መቃጠሉን የዋድላ ኮሚኒኬሽን ገልጿል።
በ03 ቤተሆር ቀበሌ ቀጭኔ ጎጥ ጥር 1/2017 ዓ/ም በደረሰው ቃጠሎ ጉዳት የደረሰባቸው አርሶ አደሮች የቃጠሎው መነሻ በውል አለመታወቁን ገልፀው ከፍተኛ ጉዳት መድረሱን አስረድተዋል፡፡
በዚህ ቀበሌ ብቻ የ52 አርሶ አደሮች የመህር ሰብል ክምር የተቃጠለ ሲሆን የአንዳንዶቹ ከዚህ ከተቃጠለው ሰብል ውጭ ሌላ ምንም ሰብል/አዝመራ እንደሌላቸው ገልፀዋል፡፡
በዚህ ቀበሌ ብቻ የ52 አርሶ አደሮች የሰብል ክምር ሙሉ በሙሉ ሲቃጠል በቤተሰብ ደረጃም ከ260 በላይ የቤተሰብ አባላት ጦም ለማደርና ለለልመና ለመውጣት እንደሚገደዱ የአካባቢው የህብረተሰብ ክፍሎች ተናግረዋል።
የዋድላ ወረዳ ቅድመ ማስጠንቀቂያ ቡድን መሪ አቶ ምትኩ ሞላ ምን አሉ ?
" በወረዳው በተለያዩ ቀበሌዎች የእሳት ቃጠሎ ተከስቷል።
እስካሁን ባለው መረጃ 770 የሚሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎች የጉዳቱ ሰለባ ሆነዋል " ብለዋል።
የዋድላ ወረዳ ግብርና ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ ሙሉየ ረታ ምን አሉ ?
" እንደ ወረዳ በ11 ቀበለሌዎች በ152 ክምር ላይ ቃጠሎ የደረሰ ሲሆን 154 አርሶ አደሮች የጉዳቱ አካል ሁናዋል።
የደረሰው ውድመት በኩንታል 4 ሺ 560 ሲሆን ከ32 ሚሊዮን ብር በላይ ጉዳት ደርሷል።
አሁንም ቢሆን አርሶ አደራችን የመውቂያ ማሽን ይምጣልን ጥያቄ እያቀረቡ ስለሆነ ማሽኑን መንግስት ቢያቀርብልን አርሶ አደራችን ተጠቃሚ እናደርጋለን።
አሁን ላይ በወረዳችን የደረሰው ጉዳት ከፍተኛ ስለሆነና ወረዳው ይህን የተጎዳ የህብረሰብ ክፍል መረዳት ስለማይችል መረጃውን ለረጅ ድርጅቶች በማጋራትና የምትችሉትን ሁሉ በማገዝ የሰብዓዊነታችሁን ሚና እንድተወጡ " ብለዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ መረጃውን ከዋድላ ወረዳ ኮሚኒኬሽን ነው ያገኘው።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Kenya ትላንት ምሽት በኢትዮጵያ ደቡብ እና ደቡብ ምዕራብ ክፍሎች በሰማይ ላይ እየተቀጣጠሉ በከፍተኛ ፍጥነት ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ብርሃን ያላቸው የቁስ አካላት ስብስብ በኬንያ ሰሜናዊ ምስራቅ ክፍልም ታይተዋል። እነዚህ ቁስ አካላት በኬንያ ቱርካና፣ ማርሳቢት፣ ሞያሌ አካባቢ መታየታቸውን የኬንያ የማህበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች ገልጸዋል። ምንም እንኳን ቁስ አካላቱ " የጠፈር ፍርስራሾች ናቸው በገጠሪቱ…
" የቁስ አካላቱ ሞያሌ ላይ አልወደቁም " - ነዋሪዎች
በሰማይ ላይ እየተቀጣጠሉ በከፍተኛ ፍጥነት ሲንቀሳቀሱ የነበሩ የቁስ አካላት ስብስብ ነገር ሞያሌ ላይ አለመዉደቁን ነዋሪዎች ገለጹ።
ትላንት ምሽት በደቡባዊ የሀገራችን ክፍሎች ሰማይ ላይ ከተለመዱት ተወርዋሪ ኮከቦች በተለየ መልኩ በመጠን የገዘፈና በዘገምተኛ አኳሃን ሲጓዝ እንደነበር የተገለጸው ብርሃናማ የተቀጣጠሉ ቁስ አካላት " ሞያሌ አከባቢ ወድቋል " እየተባለ በማህበራዊ ሚዲያ ምንጫቸው ያልተረጋገጠ መረጃዎች ሲሰራጩ ነበር።
ዛሬ ማለዳ ጀምሮ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከሞያሌ ኢትዮጵያ እና ጋምቦ አካባቢዎች ባደረገው ማጣራት ብርሃናማዉ አካል በተመሳሳይ መልኩ በሞያሌ ሰማይ ላይ ወደ ሶማሊያና ምስራቃዊ ኬንያ አቅጣጫ ማለፉንና በአከባቢው አለመዉደቁን ለማወቅ ችሏል።
በሞያሌ ጋምቦ የሚገኘው የመረጃ ምንጫችን ስለጉዳዩ በሰጠው ቃል " በሰሞኑ የመሬት መንቀጥቀጥ አፋር አከባቢ መደጋገሙን ስንሰማ ስለነበር በዚህም ክስተት ሰዉ ሁሉ ደንግጦ ነበር፤ ነገሩ በሞያሌ ሰማይ ላይ ሲያልፍ አይቻለሁ " ብሏል።
አክሎ " ሪችት ይመስላል-ሞያሌ ወደቀ የሚል ነገር ሰምቼ እስከ ማርሳቤትና ናይሮቢ ድረስ ደዋዉዬ አጣራሁ ያሉኝ ነገሩ ናይሮቢ አልደረሰም፤ ነገር ግን የማርሳቤት ሰዎች ሰማይ ላይ አይተነዉ ኡጂሩ በተባለች የኬንያ ድንበር አድርጎ ወደ ሶማሊያ መሄዱን ነግረዉኛል " ሲል ገልጿል።
አንዳንድ ጉዳዩ ላይ አስተያየታቸውን የሰጡ የስነ ከዋክብትና ስፔስ ሳይንስ አጥኝዎች ይኸው ተቀጣጣይ ነገር " የጠፈር ፍስራሾሽ " ሊሆኑ ይችላሉ ብለዋል።
በኢትዮጵያም ይሁን በኬንያ ተቋማት በኩል ቁርጥ ያለ ነገር ባይነገርም በኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስ ሶሳይቲ በኩል ጉዳይን በዝርዝር ለማሳወቅና ለማብራራት ስራዎች እየተሰሩ ነው።
ባሳለፍነው የፈረንጆች ዓመት ማገባደጃ በኬኒያ ሙኩኩ በተባለ ገጠራማ መንደር 500 ኪ.ግ የሚመዝን ቀለበታማ የጋለ ብረት መውደቁ የተነገረ ሲሆን የሀገሪቱ ስፔስ ኤጀንሲ ብረቱ በስፔስ ላይ ከሚገኙ ሮኬቶች ተገንጥሎ የወደቀ ሊሆን እንደሚችል ማስታወቁ አይዘነጋም።
#TikvahEthiopiaFamily #Moyalle #Gambo
@tikvahethiopia
በሰማይ ላይ እየተቀጣጠሉ በከፍተኛ ፍጥነት ሲንቀሳቀሱ የነበሩ የቁስ አካላት ስብስብ ነገር ሞያሌ ላይ አለመዉደቁን ነዋሪዎች ገለጹ።
ትላንት ምሽት በደቡባዊ የሀገራችን ክፍሎች ሰማይ ላይ ከተለመዱት ተወርዋሪ ኮከቦች በተለየ መልኩ በመጠን የገዘፈና በዘገምተኛ አኳሃን ሲጓዝ እንደነበር የተገለጸው ብርሃናማ የተቀጣጠሉ ቁስ አካላት " ሞያሌ አከባቢ ወድቋል " እየተባለ በማህበራዊ ሚዲያ ምንጫቸው ያልተረጋገጠ መረጃዎች ሲሰራጩ ነበር።
ዛሬ ማለዳ ጀምሮ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከሞያሌ ኢትዮጵያ እና ጋምቦ አካባቢዎች ባደረገው ማጣራት ብርሃናማዉ አካል በተመሳሳይ መልኩ በሞያሌ ሰማይ ላይ ወደ ሶማሊያና ምስራቃዊ ኬንያ አቅጣጫ ማለፉንና በአከባቢው አለመዉደቁን ለማወቅ ችሏል።
በሞያሌ ጋምቦ የሚገኘው የመረጃ ምንጫችን ስለጉዳዩ በሰጠው ቃል " በሰሞኑ የመሬት መንቀጥቀጥ አፋር አከባቢ መደጋገሙን ስንሰማ ስለነበር በዚህም ክስተት ሰዉ ሁሉ ደንግጦ ነበር፤ ነገሩ በሞያሌ ሰማይ ላይ ሲያልፍ አይቻለሁ " ብሏል።
አክሎ " ሪችት ይመስላል-ሞያሌ ወደቀ የሚል ነገር ሰምቼ እስከ ማርሳቤትና ናይሮቢ ድረስ ደዋዉዬ አጣራሁ ያሉኝ ነገሩ ናይሮቢ አልደረሰም፤ ነገር ግን የማርሳቤት ሰዎች ሰማይ ላይ አይተነዉ ኡጂሩ በተባለች የኬንያ ድንበር አድርጎ ወደ ሶማሊያ መሄዱን ነግረዉኛል " ሲል ገልጿል።
አንዳንድ ጉዳዩ ላይ አስተያየታቸውን የሰጡ የስነ ከዋክብትና ስፔስ ሳይንስ አጥኝዎች ይኸው ተቀጣጣይ ነገር " የጠፈር ፍስራሾሽ " ሊሆኑ ይችላሉ ብለዋል።
በኢትዮጵያም ይሁን በኬንያ ተቋማት በኩል ቁርጥ ያለ ነገር ባይነገርም በኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስ ሶሳይቲ በኩል ጉዳይን በዝርዝር ለማሳወቅና ለማብራራት ስራዎች እየተሰሩ ነው።
ባሳለፍነው የፈረንጆች ዓመት ማገባደጃ በኬኒያ ሙኩኩ በተባለ ገጠራማ መንደር 500 ኪ.ግ የሚመዝን ቀለበታማ የጋለ ብረት መውደቁ የተነገረ ሲሆን የሀገሪቱ ስፔስ ኤጀንሲ ብረቱ በስፔስ ላይ ከሚገኙ ሮኬቶች ተገንጥሎ የወደቀ ሊሆን እንደሚችል ማስታወቁ አይዘነጋም።
#TikvahEthiopiaFamily #Moyalle #Gambo
@tikvahethiopia
" የሟሟቱ ሁኔታ በሚመለከታቸው አካላት እየተጣራ ይገኛል " - አክሱም ዩኒቨርሲቲ
በአክሱም ዩኒቨርስቲ የሽረ ካምፓስ ተማሪ ህይወቱ እንዳለፈ ዩኒቨርስቲው አስታወቀ።
" ተማሪያችን ካሕሱ ሃይሉ በእፅዋት ሳይንስ የትምህርት ክፍል የአንደኛ ዲግሪ የሦስተኛ ዓመት ተማሪ ነበር ብሏል " ዩኒቨርስቲው።
ዩኒቨርሲቲው የተማሪው ሕይወት ያለፈው ከካምፓስ ውጪ ሌሊት ባጋጠመ ድንገተኛ ግጭት እንደሆነ ጠቁሟል።
ግጭቱ በምን ምክንያት እንደነበረ ፣ ከምን ጋር እንደሆነ በዝርዝር ያለው ነገር የለም።
የተማሪ ካሕሱ ሃይሉ ሃደራ የሟሟት ሁኔታ በሚመለከታቸው አካላት እየተጣራ ይገኛል ያለው ተቋሙ ውጤቱ በሚመለከታቸው አካላት ይፋ እንደሚደረግ ገልጿል።
@tikvahethiopia
በአክሱም ዩኒቨርስቲ የሽረ ካምፓስ ተማሪ ህይወቱ እንዳለፈ ዩኒቨርስቲው አስታወቀ።
" ተማሪያችን ካሕሱ ሃይሉ በእፅዋት ሳይንስ የትምህርት ክፍል የአንደኛ ዲግሪ የሦስተኛ ዓመት ተማሪ ነበር ብሏል " ዩኒቨርስቲው።
ዩኒቨርሲቲው የተማሪው ሕይወት ያለፈው ከካምፓስ ውጪ ሌሊት ባጋጠመ ድንገተኛ ግጭት እንደሆነ ጠቁሟል።
ግጭቱ በምን ምክንያት እንደነበረ ፣ ከምን ጋር እንደሆነ በዝርዝር ያለው ነገር የለም።
የተማሪ ካሕሱ ሃይሉ ሃደራ የሟሟት ሁኔታ በሚመለከታቸው አካላት እየተጣራ ይገኛል ያለው ተቋሙ ውጤቱ በሚመለከታቸው አካላት ይፋ እንደሚደረግ ገልጿል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update ሲጠበቁ የነበሩ ሁለት መመሪያዎች ፍትህ ሚኒስቴር ማጽደቁ ተሰምቷል። መመሪያዎቹ " የሰነደ ሙዓለ ነዋይን ለህዝብ የማቅረብ ግብይት መመሪያ " እና "ራሳቸውን በራሳቸው የሚያስተዳድሩ ድርጅቶች ቁጥጥር መመሪያ " ናቸው። ሁለቱን መመሪያዎች ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ በትላንትናው ዕለት መዝግቦ አጽድቋቸዋል። የሰነደ ሙዓለ ነዋይን ለህዝብ የማቅረብ ግብይት መመሪያን በሚመለከት የኢትዮጵያ…
በኢትዮጵያ በይፋ የአክሲዮን ግብይት ተጀመረ።
የኢትዮጵያ የሰነድ ሙዓለ ንዋይ ገበያ ዛሬ ዓርብ የአክሲዮን ሽያጭና ግዢ ግብይቱን በይፋ መጀመሩን አስታውቋል።
የአክሲዮን ገበያ ሥራውን በይፋ ያስጀመሩት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ (ዶ/ር) ፤ " በጉጉት ሲጠበቅ የቆየው የሰነድ ሙዓለ ንዋይ ግብይት በዛሬው ዕለት ጥር 2 ቀን 2017 ዓ.ም የመጀመሪያ የሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያ ደወል ደውለናል " ብለዋል።
የሰነድ ሙዓለ ንዋይ ገበያው ዋና ዳይሬክተር ጥላሁን ካሳሁን በቀጣዮቹ ዓመታት ውስጥ 50 ያህል ኩባንያዎች በዚህ ገበያ ላይ የአክሲዮን ድርሻዎችን ለግብይት እንደሚያቀርቡ ገልጸዋል።
በተለምዶ ክፍት ገበያ በመባል የሚታወቀው የሰነደ መዋዕለ ንዋይ ገበያ የተማከለ የፋይናንሺያል ገበያን የሚያመለክት ሲሆን የተዘረዘሩ ኩባንያዎችን የዋስትና ሰነዶች፣ኮሞዲቲዎች ጨምሮ በአክሲዮን ሻጮች እና ገዥዎች መካከል የሚገዙበት እና የሚሸጡበት ማዕከል መሆኑ ይታወቃል።
የመረጃው ባለቤት ካፒታል ጋዜጣ ነው።
@tikvahethiopia
የኢትዮጵያ የሰነድ ሙዓለ ንዋይ ገበያ ዛሬ ዓርብ የአክሲዮን ሽያጭና ግዢ ግብይቱን በይፋ መጀመሩን አስታውቋል።
የአክሲዮን ገበያ ሥራውን በይፋ ያስጀመሩት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ (ዶ/ር) ፤ " በጉጉት ሲጠበቅ የቆየው የሰነድ ሙዓለ ንዋይ ግብይት በዛሬው ዕለት ጥር 2 ቀን 2017 ዓ.ም የመጀመሪያ የሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያ ደወል ደውለናል " ብለዋል።
የሰነድ ሙዓለ ንዋይ ገበያው ዋና ዳይሬክተር ጥላሁን ካሳሁን በቀጣዮቹ ዓመታት ውስጥ 50 ያህል ኩባንያዎች በዚህ ገበያ ላይ የአክሲዮን ድርሻዎችን ለግብይት እንደሚያቀርቡ ገልጸዋል።
በተለምዶ ክፍት ገበያ በመባል የሚታወቀው የሰነደ መዋዕለ ንዋይ ገበያ የተማከለ የፋይናንሺያል ገበያን የሚያመለክት ሲሆን የተዘረዘሩ ኩባንያዎችን የዋስትና ሰነዶች፣ኮሞዲቲዎች ጨምሮ በአክሲዮን ሻጮች እና ገዥዎች መካከል የሚገዙበት እና የሚሸጡበት ማዕከል መሆኑ ይታወቃል።
የመረጃው ባለቤት ካፒታል ጋዜጣ ነው።
@tikvahethiopia
" ልጆቻችን በሰላም መኖር እንዲችሉ፣ በጦርነት እየተሰቃዩ የሕመማቸውን ልክ መናገር የማይቻለን የኦሮሚያና የአማራ ክልል ነዋሪዎች ሰላምን እንዲያገኙ ጥሪ እናስተላልፋለን " - ቅዱስነታቸው
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ወቅታዊ ጉዳዮችን አስመልክተው አባታዊ የሰላም ጥሪ አስተላለፉ።
ቅዱስነታቸው ፤ በሀገራችን በልዩ ልዩ አካባቢዎች ያሉ ጦርነቶች እንዲቆሙ ጥሪ አቅርበዋል።
" ልጆቻችን በሰላም መኖር እንዲችሉ፣ በጦርነት እየተሰቃዩ የሕመማቸውን ልክ መናገር የማይቻለን የኦሮሚያና የአማራ ክልል ነዋሪዎች ሰላምን እንዲያገኙ አባታዊ ጥሪ በድጋሚ እናስተላልፋለን " ብለዋል።
ቅዱስነታቸው ፤ በትግራይ ክልል ያለው የአስተዳዳሪዎች አለመግባባት በሕዝቡ ላይ ተጨማሪ ችግርና ጭንቀት እያመጣ መሆኑን ጠቁመዋል።
" በትሕትና መንፈስ እርስ በርስ መገናዘብ ተፈጥሮ ዕረፍት ያጣው ሕዝብ መረጋጋት እንዲችል ታደርጉ ዘንድ አደራችን የጠበቀ ነው " ብለዋል።
በተጨማሪም ቅዱስነታቸው በትግራይ ክልል ስለሚገኙ የሃይማኖት አባቶች ጉዳይ በአባታዊ የሰላም ጥሪ መልዕክታቸው አንስተዋል።
" መበደላችሁን እናውቃለን ፣ በኀዘናችሁ ሰዓት አብረን መቆም ባለመቻላችን ማዘናችሁም እርግጥና ተገቢ ነው " ያሉት ቅዱስነታቸው " ነገር ግን ሁሉም ነገር የሚካሰው በእርቅ ሲሆን እኛ የገፋነውን እርቅ ዓለም ሊቀበለው ስለማይችል፤ በእጃችንም የያዝነው መስቀለ ክርስቶስ የሰላም ዓርማ ነውና ልባችሁን ለሰላም፣ ለአንድነት እንድታዘጋጁ እንጠይቃለን " ብለዋል።
በሌላ በኩል ቅዱስነታቸው በመሬት መንቀጥቀጥ እየተጨነቁ ላሉ እና ስለተጎዱ ልጆቻቸው መልዕክት አስተላልፈዋል።
" የመሬት መንቀጥቀጥ ባለበት አካባቢ እየተጨነቃችሁ ያላችሁ ልጆቻችን ረድኤተ እግዚአብሔር ከእናንተ ጋር እንዲሆን ቤተ ክርስቲያን በጸሎት የምታስባችሁ መሆኑን እየገለጽን መላው ኢትዮጵያውያን ለጉዳቱ ተጋላጭ በሆኑ አካባቢዎች ለሚኖሩት ወገኖቻቸው አቅማቸው በፈቀደው መጠን ድጋፍ ያደርጉ ዘንድ አባታዊ መልእክታችንን በእግዚአብሔር ስም እናስተላልፋለን " ብለዋል።
(የቅዱስነታቸው ሙሉ መልዕክት ከላይ ተያይዟል)
@tikvahethiopia
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ወቅታዊ ጉዳዮችን አስመልክተው አባታዊ የሰላም ጥሪ አስተላለፉ።
ቅዱስነታቸው ፤ በሀገራችን በልዩ ልዩ አካባቢዎች ያሉ ጦርነቶች እንዲቆሙ ጥሪ አቅርበዋል።
" ልጆቻችን በሰላም መኖር እንዲችሉ፣ በጦርነት እየተሰቃዩ የሕመማቸውን ልክ መናገር የማይቻለን የኦሮሚያና የአማራ ክልል ነዋሪዎች ሰላምን እንዲያገኙ አባታዊ ጥሪ በድጋሚ እናስተላልፋለን " ብለዋል።
ቅዱስነታቸው ፤ በትግራይ ክልል ያለው የአስተዳዳሪዎች አለመግባባት በሕዝቡ ላይ ተጨማሪ ችግርና ጭንቀት እያመጣ መሆኑን ጠቁመዋል።
" በትሕትና መንፈስ እርስ በርስ መገናዘብ ተፈጥሮ ዕረፍት ያጣው ሕዝብ መረጋጋት እንዲችል ታደርጉ ዘንድ አደራችን የጠበቀ ነው " ብለዋል።
በተጨማሪም ቅዱስነታቸው በትግራይ ክልል ስለሚገኙ የሃይማኖት አባቶች ጉዳይ በአባታዊ የሰላም ጥሪ መልዕክታቸው አንስተዋል።
" መበደላችሁን እናውቃለን ፣ በኀዘናችሁ ሰዓት አብረን መቆም ባለመቻላችን ማዘናችሁም እርግጥና ተገቢ ነው " ያሉት ቅዱስነታቸው " ነገር ግን ሁሉም ነገር የሚካሰው በእርቅ ሲሆን እኛ የገፋነውን እርቅ ዓለም ሊቀበለው ስለማይችል፤ በእጃችንም የያዝነው መስቀለ ክርስቶስ የሰላም ዓርማ ነውና ልባችሁን ለሰላም፣ ለአንድነት እንድታዘጋጁ እንጠይቃለን " ብለዋል።
በሌላ በኩል ቅዱስነታቸው በመሬት መንቀጥቀጥ እየተጨነቁ ላሉ እና ስለተጎዱ ልጆቻቸው መልዕክት አስተላልፈዋል።
" የመሬት መንቀጥቀጥ ባለበት አካባቢ እየተጨነቃችሁ ያላችሁ ልጆቻችን ረድኤተ እግዚአብሔር ከእናንተ ጋር እንዲሆን ቤተ ክርስቲያን በጸሎት የምታስባችሁ መሆኑን እየገለጽን መላው ኢትዮጵያውያን ለጉዳቱ ተጋላጭ በሆኑ አካባቢዎች ለሚኖሩት ወገኖቻቸው አቅማቸው በፈቀደው መጠን ድጋፍ ያደርጉ ዘንድ አባታዊ መልእክታችንን በእግዚአብሔር ስም እናስተላልፋለን " ብለዋል።
(የቅዱስነታቸው ሙሉ መልዕክት ከላይ ተያይዟል)
@tikvahethiopia