#DStvEthiopia
ደማቁ እንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታዎች ወደ ሜዳ ተመልሰዋል💥
👉እነዚህን ድንቅ ፍልሚያዎች ጨምሮ ሌሎች የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታዎችን በቀጥታ በዲኤስቲቪ ሱፐርስፖርት ይመልከቱ።
ዲኤስቲቪ ያስገቡ ፣ ደንበኝነትዎን ያራዝሙ!
👇
https://bit.ly/3RFtEvh
ደንብና ሁኔታዎች ተፈፀሚነት አላቸው! ለበለጠ መረጃ
👇
www.dstv.com/en-et
#PremierLeagueallonDStv #ሁሉምያለውእኛጋርነው
ደማቁ እንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታዎች ወደ ሜዳ ተመልሰዋል💥
👉እነዚህን ድንቅ ፍልሚያዎች ጨምሮ ሌሎች የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታዎችን በቀጥታ በዲኤስቲቪ ሱፐርስፖርት ይመልከቱ።
ዲኤስቲቪ ያስገቡ ፣ ደንበኝነትዎን ያራዝሙ!
👇
https://bit.ly/3RFtEvh
ደንብና ሁኔታዎች ተፈፀሚነት አላቸው! ለበለጠ መረጃ
👇
www.dstv.com/en-et
#PremierLeagueallonDStv #ሁሉምያለውእኛጋርነው
TIKVAH-ETHIOPIA
#Syria : የ24 ዓመታት የፕሬዜዳንት በሽር አልአሳድን አገዛዝ ያስወገዱት የታጠቁት ተቃዋሚዎች አልአሳድ ሀገር ጥለው መጥፋታቸውን ገልጸዋል። የሶሪያ ተዋጊዎች በደማስቆ የሚገኘውን የአውሮፕላን ማረፊያን ከመቆጣጠራቸው ጥቂት ጊዜ በፊት በሶሪያ አየር ክልል ውስጥ የአንድ አውሮፕላን እንቅስቃሴ ተመዝግቧል። የIL76 አውሮፕላን የበረራ ቁጥሩ ' የሶሪያ አየር 9218 ' ከደማስቆ የተነሳ የመጨረሻ በረራ…
#SYRIA : የ24 ዓመታት የአልአሳድ አገዛዝ እንዴት ተገረሰሰ ?
በፕሬዜዳንት በሽር አላሳድ አገዛዝ ላይ እ.ኤ.አ. በ2011 / ከዛሬ 13 ዓመት በፊት ነው ህዝባዊ አመጽ የተነሳው።
ከዛ ጊዜ አንስቶ ሀገሪቱ መረጋጋት አልቻለችም።
ታጣቂዎች በየቦታው ተነሱ ሀገሪቱ የከፋ የእርስ በርስ ጦርነት ውስጥ ገባች።
ይኸው 13 ዓመታት በሆነው የማያባራ እልቂት በርካታ ህጻናት፣ እናቶች፣ ወጣቶች ፣ አዛውንቶች ተቀጥፈዋል።
ሀገሪቱ እንዳልነበር ሆና ወድማለች።
ሶሪያ ዳግም ከወደቀችበት አዘቅት ለመውጣት ዘመናት የሚያስፈልጋት ሆናለች።
በዚህ 13 ዓመታትን በቆየው የእርስ በርስ ጦርነት የውጭ ሀይሎች እነ ሩስያ፣ ኢራን፣ አሜሪካ ፣ ቱርክ ... እጃቸው አለበት።
የውጭ ኃይሎቹ እንደግፈዋለን የሚሉትን ኃይል በማገዝ እልቂቱን እንዳያባራ አድርገዋል።
ምንም እንኳን በሀገሪቱ ያሉ የታጠቁ ተቃዋሚዎች የአላሳድን አገዛዝ ለመገርሰስ ሲዋጉ ፣ የተለያዩ ቦታዎችን ሲይዙ ለዓመታት ቢቆዩም የሰሞኑን ከፍተኛ ፍጥነት የታየበት ድንገታዊ ጥቃት ግን " ድራማዊ " ተብሎለታል።
ካለፈው ሳምንት አንስቶ ተጣቂዎቹ በተለያየ የሀገሪቱ አቅጣጫ በከፈቱት መጠነ ሰፊ ጥቃት የሶሪያ ጦር ፈራርሷል።
ወታደሮች ሀገር ጥለው ሸሽተዋል ፤ የአላሳድ መቀመጫ ደማስቆን ጨምሮ ትልልቅ እና ቁልፍ የሚባሉ ከተሞች በፍጥነት በታጠቁት ተቃዋሚዎች እጅ ወድቀዋል።
የአላሳድ ደጋፊ ከሆኑ ሀገራት አንዷ ሩስያ በጦር አውሮፕላኖች ታግዛ ጭምር ለአላሳድ ድጋፍ ብታደርግም ፤ ኢራንም አለሁ " አግዛለሁ " ብትልም አገዛዙን ከውድቀት አልታደጉም።
ተንታኞች የአሳድ ጦር ኃይሎች በዝቅተኛ ደሞዝ እና በመኮንኖች መካከል በተንሰራፋው ሙስና የተነሳ የውግያ ሞራላቸው ተንኮታኩቷል ብለዋል።
ምንም እንኳን በቅርቡ ለሰራዊቱ የ50 በመቶ የደመወዝ ጭማሪ ቢደረግም ይህ ነው የሚባል ለውጥ ሊፈጠር ባለመቻሉ አገዛዙ ፈርሷል።
በአላሳድ ስር ሲዋጉ የነበሩ ወታደሮች ልብሳቸውን እያወለቁ ሲቪል መስለው ሲሸሹ ታይተዋል።
አላሳድም ሀገር ጥለው ጥፍተዋል። የት እንዳሉ አይታወቅም።
ቀጣዩ የሶሪያ ዕጣፋንታ ምንድነው ? ጁላኒ ማናቸው ?
አሁን ወደፊት ወጥተው የሚታዩት የቀድሞ ' አል-ኑስራ ' መሪ አሁን ደግሞ ሃያት ታህሪር አል-ሻም (ኤችቲኤስ) የተባለው የታጠቀ ኃይል መሪ አቡ መሀመድ አል ጁላኒ ናቸው።
በበላይነት የታጣቂዎቹን እንቅስቃሴ እያስትባበሩ ያሉት እሳቸው እንደሆኑ ተነግሯል።
ኑስራን ከመመስረታቸው በፊት ኢራቅ ውስጥ ለ #አልቃይዳ ተዋግተዋል። ወደዛ የሄዱት የአሜሪካን ወራር ተከትሎ ነው።
እኚህ ሰው ለ5 ዓመታት በአሜሪካ እስር ቤት አሳልፈዋል።
የአላሳድን አገዛዝ ለመጣል እንቅስቃሴ ሲጀመር በአልቃይዳው መሪ አቡ ባከር አል ባግዳዲ አማካኝነት የአልቃይዳ ህዋስ እንዲኖር ለማድረግ ታስበው ወደ ሶሪያ ተልከዋል። (IS በኢራቅ በኃላ ISIS የሆነው)
አሜሪካ በ2013 አል-ጁላኒን በአሸባሪነት ፈርጃቸዋለች።
እ.ኤ.አ. 2016 ላይ ከአልቃይዳ መፋታታቸው ከተነገር በኃላ ሃያት ታህሪር አል-ሻም የተሰኘውን ቡድን ይዘው መጥተዋል።
ከአልቃይዳም ሆነ ከሌላ ቡድን መፋታታቸው ተነገረ በኃላ የሶሪያ ኢስላሚክ ሪፐብሊክን የመመስረት ዓላማ አንግበው አላሳድን ሲዋጉ ቆይተዋል።
ይኸው የጁላኒ ቡድን አሁን የአላሳድን አገዛዝ በመጣል ትልቁን ድርሻ እንደያዘ ነው የተነገረው።
አቡ መሀመድ አል ጁላኒ ከአላሳድ መገርሰስ በኃላ በሰጡት ቃል ፤ ሁሉም የመንግስት ተቋማት በይፋ ተላልፈው እስኪሰጡ / ርክክብ እስኪደረግ ድረስ በአላሳድ ጠቅላይ ሚኒስትር ቁጥጥር ስር እንደሚቆዩ ይፋ አድርገዋል።
ጠ/ሚኒስትር መሀመድ ጋዚ አል ጃላሊ በሰጡት መግለጫ ፥ በደማስቆ ቤታቸው እንደሚቆዩ እና የህዝብ ተቋማት ስራቸውን እንዲቀጥሉ ለማድረግ ቁርጠኛ መሆናቸውን ተናግረዋል።
በሽር አላሳድ ማን ናቸው ?
° እድሜያቸው 59 ነው። የተወለዱት ደማስቆ።
° ከህክምና ትምህርት ቤት ተመርቀዋል። ለንደን ውስጥ በኦፕታሞሎጂ ስፔሻላይዝድ አድርገዋል።
° የወንድማቸውን በመኪና አደጋ መሞት ተከትሎ ወደ ሶሪያ መጥተዋል።
° እኤአ 2000 ላይ ነው የአባታቸውን ሃፊዝ አላሳድን መሞት ተከትሎ ወደ አገዛዝ የመጡት። አባታቸው ከ1971 አንስቶ ሀገሪቱን ሲመሩ ነበር።
° ወንድማቸው ባሴል አላሳድ የአባታቸውን ስልጣን ይረከባሉ ተብሎ ቢጠበቅም በመኪና አደጋ በመሞታቸው በሽር አላሳድ ስልጣኑን መያዝ ችለዋል።
° የስልጣን ዘመናቸው ከ2011 በኃላ በጦርነት ተሞላ ነው።
አሁን ከሀገር ፍረጥጠዋል የተባሉት አላሳድ በበርካታ የየሰብዓዊ መብት ጥሰቶች፣ ኬሚካል ጦር መሳሪያ በመጠቀም፣ እና በሌሎችም በርካታ ጉዳዮች ይከሰሳሉ።
🚨በሶሪያ የ13 ዓመታት የእርስ በርስ ጦርነት ከ350 ሺህ በላይ ሰዎች እንደሞቱ ሪፖርቶች ያሳያሉ። ሚሊዮኖች ቤት ንብረታቸውን ጥለው ተሰደዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ መረጃዎቹን ከሮይተርስ ፣ አልጀዚራ ፣ ዋሽንግተን ፖስት ፣ከፍራንስ 24 ነው አሰባስቦ ያዘጋጀው።
#TikvahEthiopia
@tikvahethiopia
በፕሬዜዳንት በሽር አላሳድ አገዛዝ ላይ እ.ኤ.አ. በ2011 / ከዛሬ 13 ዓመት በፊት ነው ህዝባዊ አመጽ የተነሳው።
ከዛ ጊዜ አንስቶ ሀገሪቱ መረጋጋት አልቻለችም።
ታጣቂዎች በየቦታው ተነሱ ሀገሪቱ የከፋ የእርስ በርስ ጦርነት ውስጥ ገባች።
ይኸው 13 ዓመታት በሆነው የማያባራ እልቂት በርካታ ህጻናት፣ እናቶች፣ ወጣቶች ፣ አዛውንቶች ተቀጥፈዋል።
ሀገሪቱ እንዳልነበር ሆና ወድማለች።
ሶሪያ ዳግም ከወደቀችበት አዘቅት ለመውጣት ዘመናት የሚያስፈልጋት ሆናለች።
በዚህ 13 ዓመታትን በቆየው የእርስ በርስ ጦርነት የውጭ ሀይሎች እነ ሩስያ፣ ኢራን፣ አሜሪካ ፣ ቱርክ ... እጃቸው አለበት።
የውጭ ኃይሎቹ እንደግፈዋለን የሚሉትን ኃይል በማገዝ እልቂቱን እንዳያባራ አድርገዋል።
ምንም እንኳን በሀገሪቱ ያሉ የታጠቁ ተቃዋሚዎች የአላሳድን አገዛዝ ለመገርሰስ ሲዋጉ ፣ የተለያዩ ቦታዎችን ሲይዙ ለዓመታት ቢቆዩም የሰሞኑን ከፍተኛ ፍጥነት የታየበት ድንገታዊ ጥቃት ግን " ድራማዊ " ተብሎለታል።
ካለፈው ሳምንት አንስቶ ተጣቂዎቹ በተለያየ የሀገሪቱ አቅጣጫ በከፈቱት መጠነ ሰፊ ጥቃት የሶሪያ ጦር ፈራርሷል።
ወታደሮች ሀገር ጥለው ሸሽተዋል ፤ የአላሳድ መቀመጫ ደማስቆን ጨምሮ ትልልቅ እና ቁልፍ የሚባሉ ከተሞች በፍጥነት በታጠቁት ተቃዋሚዎች እጅ ወድቀዋል።
የአላሳድ ደጋፊ ከሆኑ ሀገራት አንዷ ሩስያ በጦር አውሮፕላኖች ታግዛ ጭምር ለአላሳድ ድጋፍ ብታደርግም ፤ ኢራንም አለሁ " አግዛለሁ " ብትልም አገዛዙን ከውድቀት አልታደጉም።
ተንታኞች የአሳድ ጦር ኃይሎች በዝቅተኛ ደሞዝ እና በመኮንኖች መካከል በተንሰራፋው ሙስና የተነሳ የውግያ ሞራላቸው ተንኮታኩቷል ብለዋል።
ምንም እንኳን በቅርቡ ለሰራዊቱ የ50 በመቶ የደመወዝ ጭማሪ ቢደረግም ይህ ነው የሚባል ለውጥ ሊፈጠር ባለመቻሉ አገዛዙ ፈርሷል።
በአላሳድ ስር ሲዋጉ የነበሩ ወታደሮች ልብሳቸውን እያወለቁ ሲቪል መስለው ሲሸሹ ታይተዋል።
አላሳድም ሀገር ጥለው ጥፍተዋል። የት እንዳሉ አይታወቅም።
ቀጣዩ የሶሪያ ዕጣፋንታ ምንድነው ? ጁላኒ ማናቸው ?
አሁን ወደፊት ወጥተው የሚታዩት የቀድሞ ' አል-ኑስራ ' መሪ አሁን ደግሞ ሃያት ታህሪር አል-ሻም (ኤችቲኤስ) የተባለው የታጠቀ ኃይል መሪ አቡ መሀመድ አል ጁላኒ ናቸው።
በበላይነት የታጣቂዎቹን እንቅስቃሴ እያስትባበሩ ያሉት እሳቸው እንደሆኑ ተነግሯል።
ኑስራን ከመመስረታቸው በፊት ኢራቅ ውስጥ ለ #አልቃይዳ ተዋግተዋል። ወደዛ የሄዱት የአሜሪካን ወራር ተከትሎ ነው።
እኚህ ሰው ለ5 ዓመታት በአሜሪካ እስር ቤት አሳልፈዋል።
የአላሳድን አገዛዝ ለመጣል እንቅስቃሴ ሲጀመር በአልቃይዳው መሪ አቡ ባከር አል ባግዳዲ አማካኝነት የአልቃይዳ ህዋስ እንዲኖር ለማድረግ ታስበው ወደ ሶሪያ ተልከዋል። (IS በኢራቅ በኃላ ISIS የሆነው)
አሜሪካ በ2013 አል-ጁላኒን በአሸባሪነት ፈርጃቸዋለች።
እ.ኤ.አ. 2016 ላይ ከአልቃይዳ መፋታታቸው ከተነገር በኃላ ሃያት ታህሪር አል-ሻም የተሰኘውን ቡድን ይዘው መጥተዋል።
ከአልቃይዳም ሆነ ከሌላ ቡድን መፋታታቸው ተነገረ በኃላ የሶሪያ ኢስላሚክ ሪፐብሊክን የመመስረት ዓላማ አንግበው አላሳድን ሲዋጉ ቆይተዋል።
ይኸው የጁላኒ ቡድን አሁን የአላሳድን አገዛዝ በመጣል ትልቁን ድርሻ እንደያዘ ነው የተነገረው።
አቡ መሀመድ አል ጁላኒ ከአላሳድ መገርሰስ በኃላ በሰጡት ቃል ፤ ሁሉም የመንግስት ተቋማት በይፋ ተላልፈው እስኪሰጡ / ርክክብ እስኪደረግ ድረስ በአላሳድ ጠቅላይ ሚኒስትር ቁጥጥር ስር እንደሚቆዩ ይፋ አድርገዋል።
ጠ/ሚኒስትር መሀመድ ጋዚ አል ጃላሊ በሰጡት መግለጫ ፥ በደማስቆ ቤታቸው እንደሚቆዩ እና የህዝብ ተቋማት ስራቸውን እንዲቀጥሉ ለማድረግ ቁርጠኛ መሆናቸውን ተናግረዋል።
በሽር አላሳድ ማን ናቸው ?
° እድሜያቸው 59 ነው። የተወለዱት ደማስቆ።
° ከህክምና ትምህርት ቤት ተመርቀዋል። ለንደን ውስጥ በኦፕታሞሎጂ ስፔሻላይዝድ አድርገዋል።
° የወንድማቸውን በመኪና አደጋ መሞት ተከትሎ ወደ ሶሪያ መጥተዋል።
° እኤአ 2000 ላይ ነው የአባታቸውን ሃፊዝ አላሳድን መሞት ተከትሎ ወደ አገዛዝ የመጡት። አባታቸው ከ1971 አንስቶ ሀገሪቱን ሲመሩ ነበር።
° ወንድማቸው ባሴል አላሳድ የአባታቸውን ስልጣን ይረከባሉ ተብሎ ቢጠበቅም በመኪና አደጋ በመሞታቸው በሽር አላሳድ ስልጣኑን መያዝ ችለዋል።
° የስልጣን ዘመናቸው ከ2011 በኃላ በጦርነት ተሞላ ነው።
አሁን ከሀገር ፍረጥጠዋል የተባሉት አላሳድ በበርካታ የየሰብዓዊ መብት ጥሰቶች፣ ኬሚካል ጦር መሳሪያ በመጠቀም፣ እና በሌሎችም በርካታ ጉዳዮች ይከሰሳሉ።
🚨በሶሪያ የ13 ዓመታት የእርስ በርስ ጦርነት ከ350 ሺህ በላይ ሰዎች እንደሞቱ ሪፖርቶች ያሳያሉ። ሚሊዮኖች ቤት ንብረታቸውን ጥለው ተሰደዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ መረጃዎቹን ከሮይተርስ ፣ አልጀዚራ ፣ ዋሽንግተን ፖስት ፣ከፍራንስ 24 ነው አሰባስቦ ያዘጋጀው።
#TikvahEthiopia
@tikvahethiopia
" ትውልድን በማበላሸትና ለተለያዩ የወንጀል ድርጊቶች መንስኤ እየሆኑ ባሉ ጉዳዮች ላይ እምርጃ መውሰድ እንቀጥላለን " - ድሬ ፖሊስ
የድሬዳዋ ፖሊስ ፤ " ወረዳ 2 ስር በሚገኙ በተለያዩ አካባቢዎች ኦፕሬሽን አድርጌ በርካታ የሺሻ ማጨሻ እቃዎች እና 54 ተጠርጣሪ ግለሰቦችን ይዣለሁ " አለ።
የሳቢያን ፖሊስ ጣቢያ ተወካይ አዛዥ ኢ/ር አበባ አሼቦ ከማህበረሰቡ በደረሰ ጥቆማ በቀጠናው ላይ በሚገኙ በ10 ቤቶች ላይ ብርበራ መደረጉን ገልጸዋል።
በዚህም ከ80 በላይ የሺሻ ማጨሻ ጠርሙስ ፤ ከመቶ በላይ ፓኬት ሺሻ፤ ከመቶ ሰላሳ ፍሬ በላይ ቡሪ፤ ሰላሳ ካርቶን ቀስቲር፤ ሌሎችም ... ቀሶች እንደተያዙ አመልክተዋል።
54 ተጠርጣሪዎችም የተያዙ ሲሆን 18ቱ በዋናነት 36ቱ በተባባሪነት የተያዙ ናቸው።
የድሬ ፖሊስ " ትውልድን በማበላሸት እንዲሁም ለተለያዩ የወንጀል ድርጊቶች መንስኤ እየሆኑ ባሉ ጉዳዮች ላይ እምርጃ መውሰድ እንቀጥላለን " ያለ ሲሆን በዚህ ላይ ህብረተሰቡ ተሳትፎ እንዲያደርግ ጥሪ ቀርቧል።
#DirePolice
@tikvahethiopia
የድሬዳዋ ፖሊስ ፤ " ወረዳ 2 ስር በሚገኙ በተለያዩ አካባቢዎች ኦፕሬሽን አድርጌ በርካታ የሺሻ ማጨሻ እቃዎች እና 54 ተጠርጣሪ ግለሰቦችን ይዣለሁ " አለ።
የሳቢያን ፖሊስ ጣቢያ ተወካይ አዛዥ ኢ/ር አበባ አሼቦ ከማህበረሰቡ በደረሰ ጥቆማ በቀጠናው ላይ በሚገኙ በ10 ቤቶች ላይ ብርበራ መደረጉን ገልጸዋል።
በዚህም ከ80 በላይ የሺሻ ማጨሻ ጠርሙስ ፤ ከመቶ በላይ ፓኬት ሺሻ፤ ከመቶ ሰላሳ ፍሬ በላይ ቡሪ፤ ሰላሳ ካርቶን ቀስቲር፤ ሌሎችም ... ቀሶች እንደተያዙ አመልክተዋል።
54 ተጠርጣሪዎችም የተያዙ ሲሆን 18ቱ በዋናነት 36ቱ በተባባሪነት የተያዙ ናቸው።
የድሬ ፖሊስ " ትውልድን በማበላሸት እንዲሁም ለተለያዩ የወንጀል ድርጊቶች መንስኤ እየሆኑ ባሉ ጉዳዮች ላይ እምርጃ መውሰድ እንቀጥላለን " ያለ ሲሆን በዚህ ላይ ህብረተሰቡ ተሳትፎ እንዲያደርግ ጥሪ ቀርቧል።
#DirePolice
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
" አሳድ የሩስያን ድጋፍ በማጣታቸው ሶሪያን ለቀው ሸሽተዋል " - ትራምፕ
ተመራጩ የአሜሪካው ፕሬዜዳንት ዶናልድ ትራምፕ፤ የሶሪያው ፕሬዜዳንት በሽር አላሳድ የሩስያን ድጋፍ በማጣታቸው ሀገራቸውን ጥለው መሸሻቸውን ገለጹ።
ይህን ያሉት ' ትሩዝ ' በሚሰኘው ማህበራዊ ሚዲያቸው ላይ ነው።
" አሳድ ሄዷል " ያሉት ትራምፕ " ጠባቂው በቭላድሚር ፑቲን የሚመራው ሩስያ፣ ሩስያ፣ ሩስያ ! ከዚህ በላይ እሱን (አሳድን) ለመጠበቅ ፍላጎት አልነበረውም " ሲሉ ገልጸዋል።
የትራምፕ ሀገር አሜሪካ በርካቶች ባለቁበት የባለፉት 13 ዓመታት የሶሪያ የእርስ በርስ ጦርነት ወቅት ሶሪያ ውስጥ ናት።
ሀገሪቱ ዋና አላማ ብላ የገባችው ' ISIS 'ን ለማፅዳት ቢሆንም በቀድሞ ፕሬዜዳንት ኦባማ ሰዓት " አሳድ መሄድ አለበት / ከአገዛዙ መወገድ አለበት " የሚል አቋም በይፋ ይንፀባረቅ ነበር።
እኤአ በ2013 ኦባማ እስራኤልን ሲጎበኙ ከቤኒያሚን ኔታንያሁ ጋር ሆነው " አሳድ መሄድ አለበት አገዛዙ ማብቃት አለበት " ሲሉ ተናግረዋል።
ከዚህም ባለፈ ፤ የአሳድን ተቃዋሚዎች በቁሳቁስ እና በስልጠና ድጋፍ ታደርግላቸው ነበር።
የፑቱን ሀገር ሩስያ የአላሳድን መንግሥት የምትደግፍ ሲሆን የአገዛዙ ጠላቶች ላይ እርምጃዎችን ስትወስድ ነበር።
#Syria
@tikvahethiopia
ተመራጩ የአሜሪካው ፕሬዜዳንት ዶናልድ ትራምፕ፤ የሶሪያው ፕሬዜዳንት በሽር አላሳድ የሩስያን ድጋፍ በማጣታቸው ሀገራቸውን ጥለው መሸሻቸውን ገለጹ።
ይህን ያሉት ' ትሩዝ ' በሚሰኘው ማህበራዊ ሚዲያቸው ላይ ነው።
" አሳድ ሄዷል " ያሉት ትራምፕ " ጠባቂው በቭላድሚር ፑቲን የሚመራው ሩስያ፣ ሩስያ፣ ሩስያ ! ከዚህ በላይ እሱን (አሳድን) ለመጠበቅ ፍላጎት አልነበረውም " ሲሉ ገልጸዋል።
የትራምፕ ሀገር አሜሪካ በርካቶች ባለቁበት የባለፉት 13 ዓመታት የሶሪያ የእርስ በርስ ጦርነት ወቅት ሶሪያ ውስጥ ናት።
ሀገሪቱ ዋና አላማ ብላ የገባችው ' ISIS 'ን ለማፅዳት ቢሆንም በቀድሞ ፕሬዜዳንት ኦባማ ሰዓት " አሳድ መሄድ አለበት / ከአገዛዙ መወገድ አለበት " የሚል አቋም በይፋ ይንፀባረቅ ነበር።
እኤአ በ2013 ኦባማ እስራኤልን ሲጎበኙ ከቤኒያሚን ኔታንያሁ ጋር ሆነው " አሳድ መሄድ አለበት አገዛዙ ማብቃት አለበት " ሲሉ ተናግረዋል።
ከዚህም ባለፈ ፤ የአሳድን ተቃዋሚዎች በቁሳቁስ እና በስልጠና ድጋፍ ታደርግላቸው ነበር።
የፑቱን ሀገር ሩስያ የአላሳድን መንግሥት የምትደግፍ ሲሆን የአገዛዙ ጠላቶች ላይ እርምጃዎችን ስትወስድ ነበር።
#Syria
@tikvahethiopia
#TecnoAI
ዘናጭ ቴክኖሎጂ እየመጣ ነው! ያሰቡትን ያለገደብ ሚከውኑበት ቴክኖ ኤ አይን በቅርቡ ይጠብቁ!!!
ከታች ያለውን ማስፈንጠሪያ በመከተል የቴክኖ ቲክቶክ ገጽ ፎሎው በማድረግ እና Bio ላይ ያለውን ሊንክ ተጭነው በመመዝገብ ታህሳስ 10 በስካይላይት ሆቴል በሚካሄደው የሀገራችን ትልቁ የኤ አይ ሁነት ላይ ይሳተፉ፡፡
https://www.tiktok.com/@tecnoet
@tecno_et @tecno_et
ዘናጭ ቴክኖሎጂ እየመጣ ነው! ያሰቡትን ያለገደብ ሚከውኑበት ቴክኖ ኤ አይን በቅርቡ ይጠብቁ!!!
ከታች ያለውን ማስፈንጠሪያ በመከተል የቴክኖ ቲክቶክ ገጽ ፎሎው በማድረግ እና Bio ላይ ያለውን ሊንክ ተጭነው በመመዝገብ ታህሳስ 10 በስካይላይት ሆቴል በሚካሄደው የሀገራችን ትልቁ የኤ አይ ሁነት ላይ ይሳተፉ፡፡
https://www.tiktok.com/@tecnoet
@tecno_et @tecno_et
" ወረዳው ከነእቃዬ ሜዳ ላይ ጥሎኝ የኔን ጉዳይ ይዞ የነበረውን ዳኛ ከቤቴ አስገባው " - እንባ የሚተናነቃት ወጣት
በአዲስ አበባ አስተዳደር የካ ክ/ከተማ ወረዳ 6 ቀበሌ 9/10 የምትገኝ ወጣት ከአሳዳጊ አክስቷ ጋር ትኖርበት ከነበረው የቀበሌ ቤት አሳዳጊዋ ስትሞት ከቤቱ እንድትወጣ ተደርጋ ጎዳና እንደወጣች በቲክቫህ ኢትዮጵያ በኩል እሮሮ አሰምታለች።
" ወረዳው ከነእቃዬን ሜዳ ጥሎ የኔን ጉዳይ ይዞ የነበረውን ዳኛ ከቤቴ አስገባው " ብላለች።
ወርቅነሽ አለሙ የምትባለው ይህች ወጣት የአባቷ ታላቅ እህት ከ3 ዓመቷ ጀምሮ ከባህር ዳር ወደ አ/አ አምጥታት ነው ያሳደገቻት።
እዚሁ ቤት እስከ 2016 ዓ/ም ማለቂያ ድረስ ነበሩ።
በ2016 ዓ/ም አሳዳጊ አክስቷ ከሞትች ከ40 ቀናት በኃላ ወረዳው " ወራሽ ልጅ ስላልሆሽ ልቀቂ " ይላታል።
ጉዳዩን ይዛ ፍርድ ቤት ሄደች። ፍርድ ቤትም ሄዳ መፍትሄ አልተሰጣትም።
" ወረዳ እኔን ጠዋት በግብረ ኃይል ከነእቃዬ አውጥቶ ጥሎኝ ከሰዓት በኋላ ራሱ የኔን ጉዳይ ይዞ የነበረውን ዳኛ ቤቴ ውስጥ አስገባው " ስትል ቅሬታ አሰምታለች።
ከዚህ አለፍ ሲል ቤቱ ሁለት ክፍል ሆኖ ሳለ ወደ አራት ክፍል አስፋፍቶ ሰርቶት ዞር ብሎ የጠየቀው አካል የለም ብላለች።
ወረዳው ምን ምላሽ ሰጠ ?
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ቅሬታውን ይዞ የወረዳ 6 ጽ/ቤት አስተዳደር ኃላፊ አቶ ምስጋናው ሂጂቱን አነጋግሯል።
ቅሬታዋ አቅራቢዋ ልጅ ከሆነች የመውረስ መብት እንዳላት አምነውበታል።
ኃላፊው ፤ " ባለመብት ናት የቀበሌ ቤት መውረስ የሚችለው ልጅ ነውና ልጅ ከሆነች መውረስ መብቷ ነው " ብለዋል።
" በሕጉ መሠረት የቀበሌ ቤት ፣ ልጅ ከሆነች የመውረስ መብቷ የተጠበቀ ነው ፤ በዚያ ደረጃ ሆኖ ከነበረ እኔ ጋ ይምጡ እናስተካክላለን ይሄ የተነሳው ጉዳይ ትክክል ከሆነ " ሲሉ ተናግረዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ይህ ጉዳይ ተጨማሪ ማብራሪያ እና ግልጽነት ስለሚፈልግ የሕግ ባለሙያ አነጋግሯል።
የሕግ ባለሙያ የሆኑት አቶ ጥጋቡ ደሳለኝ ምን አሉ ?
- ኑዛዜውን ማጽደቅ ትችላለች። ግን የቀበሌ ቤት ላይ ተወላጆች ካልሆኑ በስተቀር ከሕግ አንጻር በባዮሎጂካል ተወላጅ ያልሆነ ልጅ የጉጂፈቻ ማስረጃ ቀደም ሲል ሊኖር ይገባል።
- ለቀበሌ ቤት የጉዲፈቻ ማስረጃ ስሌላት ውርስ ተቀባዩዋን ከሞራልና ከአስተዳደራዊ አንጻር ካልሆነ በስተቀር ከሕግ አንጻር የወረዳው አስተደዳደር ሊያስተናግዳት አይችልም።
- ከሞራል አንጻር አሳዳጊዋ ስላረፉ፣ ልጅቷ ደግሞ ተተኪ ልጅ ናት፤ በሥነ ልቦና እናትና ልጅ ሆነው አብረው ኖረዋል። የቀበሌ ቤት የሚባለው ደግሞ አነስተኛ ገቢ ያላቸው ሰዎች የሚኖበት ነው። ስለዚህ ከሕግ አንጻር የኑዛዜ ተቀባይ መሆን ባትችልም አንዱ ወጥቶ ሌላው የሚገባበት፣ ለዜጎች የተሰራ ቤት በመሆኑ ልትኖርበት ይገባ ነበር ከሞራል አንጻር።
- ከሕግ አንጻር በቀበሌ ቤት ላይ ኑዛዜ ማድረግ አይቻልም።
- ለምሳሌ የፌደራል ኪራይ ቤቶችን አንድ ሰው ተከራይቶ ቢኖር ሲሞት ሊናዘዝበት አይችልም። ምክንያቱም የንብረቱ ባለቤት መንግስት ነው። በመሳሳይ ሁኔታ የቀበሌ ቤቶች ውስጥ የሚኖር ሰው ሲሞት ኑዛዜ ሊያደርግ አይችልም። ኑዛዜ ማድረጉ በሕግ ውጤት አያመጣም።
- በዜጎች ንብረትና ሕይወት ላይ ውሳኔ የሚሰጡ ሰዎች (ዳኞች) ከወረዳ ጋር በመመሳጠር ክርክር በተነሳበት የመንግስት ቤት ውስጥ መግባት የሕግ ጥሰት ነው። ሕግን ያልተከተለ አካሄድ ነው። በተወሰነ ደረጃ ሙስና ተብሎ ጉዳዩን ወደ ዳኞች አስተዳደር ጉባዔ ብታመለክትበት ዳኛው ከኃላፊነቱ የሚነሳበት ቀጥተኛ ማስረጃ ነው የሚሆነው።
- ክርክር በተነሳበት ጉዳይ ላይ የጥቅም ግንኙነት በመፍጠር እንዲህ ማድረግ ትልቅ የዲሲፒሊን ጥፋት ነው።
- ልጅቷ ቅጹ ላይ አለች፣ ደባል ናት፣ የቤተሰብ አባል ናት ቀጥተኛ ልጅ ባትሆንም፣ የቀበሌ ቤቶች ደግሞ አነስተኛ ገቢ ላላቸው ሰዎቸ ነው የተዘጋጁት፣ ሜዳ ላይ መጣል የለባትም ብሎ የወረዳው አስተዳደር ወስኖ ወይ በዚያው ቤት ሊያስቀጥላት ይገባል የቀበሌ ቤቱ የሚፈርስ ከሆነም ምትክ የመንግስት ቤት እንድታገኝ ሁኔታዎችን ማመቻቸት አለበት።
- በህሊና ፍርድ ወይ አስተዳደራዊ በሆነ መንገድ የወረዳው አስተዳደር መፍትሄ ሊሰጣት ይገባል።
ያንብቡ ፦ https://telegra.ph/Tikvah-Ethiopia-12-08
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
ፎቶ ፦ 19ኛው የኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦች ቀን ዛሬ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ፣ አርባ ምንጭ ከተማ ተከብሮ ውሏል።
ካለፉት ጥቂት ዓመታት በተሻለ ድምቀት በዓሉ መከበሩን አርባ ምንጭ የሚገኘው የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ገልጿል።
በዘንድሮው በዓል ላይ ጠ/ሚ ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር)ን ጨምሮ የክልል ርዕሰ መስተዳደሮች ፣ የፌዴራል እና የክልል ከፍተኛ ባለስልጣናት የተገኙበት ነበር።
በአዲሱ ክልል የተሰናዳው በዓሉ ለአርባ ምንጭ ከተማ ከፍተኛ መነቃቃትን የፈጠረ እንደሆነ ቀጣይ አመት በዓል ደግሞ በሌላኛው አዲስ ክልል ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል አስተናጋጅነት እንደሚካሄድ ተነግሯል።
#ArbaMinchLandofPeace
@tikvahethiopia
ካለፉት ጥቂት ዓመታት በተሻለ ድምቀት በዓሉ መከበሩን አርባ ምንጭ የሚገኘው የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ገልጿል።
በዘንድሮው በዓል ላይ ጠ/ሚ ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር)ን ጨምሮ የክልል ርዕሰ መስተዳደሮች ፣ የፌዴራል እና የክልል ከፍተኛ ባለስልጣናት የተገኙበት ነበር።
በአዲሱ ክልል የተሰናዳው በዓሉ ለአርባ ምንጭ ከተማ ከፍተኛ መነቃቃትን የፈጠረ እንደሆነ ቀጣይ አመት በዓል ደግሞ በሌላኛው አዲስ ክልል ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል አስተናጋጅነት እንደሚካሄድ ተነግሯል።
#ArbaMinchLandofPeace
@tikvahethiopia