TIKVAH-ETHIOPIA
#Update ወጣት እንስቶችን በግፍ ከገደሉ ውስጥ አንዱ በእድሜ ልክ አስራት ሲቀጣ ፤ የተቀሩት ለፍርድ ተቀጥረዋል። የመቐለ የማእከላዊው ፍርድ ቤት ትላንት ባዋለው ችሎት ኣፀደ ታፈረ በተባለች እንስት ወጣት በተፈፀመ የግድያ ወንጀል በይን የሰጠ ሲሆን ዓድዋ ከተማ ላይ በተገደለችው ተማሪ ማህሌት ተኽላይ ግድያ ተጠርጣሪዎች ላይ ውሳኔ ለመስጠት ቀነ ቀጠሮ ሰጥቷል። ሟች ወጣት ኣፀደ ታፈረን በአሰቃቂ…
#Update
" ውሳኔው በሌሎች ሴቶች ላይ ጥቃት ለመፈጸም የሚያስቡ ቆመም ብለው እንዲያስቡ የሚያስተምርና የሚያደርግ ነው " - አባት
በግፍ የተገደለችው የዓድዋዋ ተማሪ ማህሌት ተኽላይ የፍርድ ሂደት ገዳዮች ላይ የሞት እና የእድሜ ልክ ፅኑ እስራት በማስተላልፈ እልባት አግኝቷል።
የመቐለ ማእከላዊ ፍርድ ቤት ዛሬ ህዳር 23/2017 ዓ.ም ባዋለው ችሎት በተማሪ ማህሌት ግድያ የተጠረጠሩት ሁለት ግለሰቦች ወንጀለኝታቸውን አረጋግጦ ፍርድ ሰጥቷል።
አንደኛው ወንጀለኛ በሞት ሁለተኛው ደግሞ በፅኑ የዕድሜ ልክ እስራት እንዲቀጣ ወስኗል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ በትግራይ ማእከላዊ ዞን ዓድዋ ከተማ ታግታ ከወራት መሰወር በኋላ ተገድላ ተቀብራ ስለተገኘችው ወጣት ማህሌት ተኽላይ ጉዳይ ካለፈው ዓመት 2016 ዓ.ም ጀምሮ ተከታታይ መረጃዎች ሲያቀርብ መቆየቱ ይታወሳል።
ፍርድ ቤቱ ውሳኔ ከሰጠ በኋላም የሟች አባት አቶ ተኽላይ አጭር አስተያየት ተቀብሏል።
የሟች አባት አቶ ተኽላይ " የመቐለ ማእከላዊ ፍርድ ቤት የሰጠው ውሳኔ እንደ ቤተሰብ ትክክል እና የሚሳምን ፤ በሌሎች ሴቶች ጥቃት ለመፈጸም የሚያስቡ ቆመም ብለው እንዲያስቡት የሚያስተምርና የሚያደርግ ነው " ብለውታል።
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia
" ውሳኔው በሌሎች ሴቶች ላይ ጥቃት ለመፈጸም የሚያስቡ ቆመም ብለው እንዲያስቡ የሚያስተምርና የሚያደርግ ነው " - አባት
በግፍ የተገደለችው የዓድዋዋ ተማሪ ማህሌት ተኽላይ የፍርድ ሂደት ገዳዮች ላይ የሞት እና የእድሜ ልክ ፅኑ እስራት በማስተላልፈ እልባት አግኝቷል።
የመቐለ ማእከላዊ ፍርድ ቤት ዛሬ ህዳር 23/2017 ዓ.ም ባዋለው ችሎት በተማሪ ማህሌት ግድያ የተጠረጠሩት ሁለት ግለሰቦች ወንጀለኝታቸውን አረጋግጦ ፍርድ ሰጥቷል።
አንደኛው ወንጀለኛ በሞት ሁለተኛው ደግሞ በፅኑ የዕድሜ ልክ እስራት እንዲቀጣ ወስኗል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ በትግራይ ማእከላዊ ዞን ዓድዋ ከተማ ታግታ ከወራት መሰወር በኋላ ተገድላ ተቀብራ ስለተገኘችው ወጣት ማህሌት ተኽላይ ጉዳይ ካለፈው ዓመት 2016 ዓ.ም ጀምሮ ተከታታይ መረጃዎች ሲያቀርብ መቆየቱ ይታወሳል።
ፍርድ ቤቱ ውሳኔ ከሰጠ በኋላም የሟች አባት አቶ ተኽላይ አጭር አስተያየት ተቀብሏል።
የሟች አባት አቶ ተኽላይ " የመቐለ ማእከላዊ ፍርድ ቤት የሰጠው ውሳኔ እንደ ቤተሰብ ትክክል እና የሚሳምን ፤ በሌሎች ሴቶች ጥቃት ለመፈጸም የሚያስቡ ቆመም ብለው እንዲያስቡት የሚያስተምርና የሚያደርግ ነው " ብለውታል።
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia
#SafaricomEthiopia
የምስራች! 🥳 💫 ፈጣኑን 4G ኔትወርካችንን የኩምሳ ሞረዳ መቀመጫ ወደ ነበረችው: በቡና እና በቂቤ የምትታወቀውና ለምለም ወደ ሆነችው ነቀምቴ ይዘን መጥተናል::
ፈጣኑን ኔትወርክ ዛሬውኑ እንቀላቀል!🙌🏼
#MPESASafaricom #SafaricomEthiopia #1Wedefit
#Furtheraheadtogether
የምስራች! 🥳 💫 ፈጣኑን 4G ኔትወርካችንን የኩምሳ ሞረዳ መቀመጫ ወደ ነበረችው: በቡና እና በቂቤ የምትታወቀውና ለምለም ወደ ሆነችው ነቀምቴ ይዘን መጥተናል::
ፈጣኑን ኔትወርክ ዛሬውኑ እንቀላቀል!🙌🏼
#MPESASafaricom #SafaricomEthiopia #1Wedefit
#Furtheraheadtogether
#AddisAbaba
በተለያዩ ቀናት ከሦስት ድርጅቶች ስልክና ላፕቶፕ ሲሰርቅ በካሜራ ዕይታ የገባው ግለሰብ በፖሊስ እየተፈለገ ነው።
በአዲስ አበባ ከተማ በቂርቆስ እና በቦሌ ክፍለ ከተማ በቀናት ልዩነት በ 3 ድርጅቶች የላፕቶፕ እና የሞባይል ስልኮች ስርቆት በተመሳሳይ ግለሰብ መፈጸሙን ዝርፊያው የተፈጸመባቸው የንብረቱ ባለቤቶች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል ።
ግለሰቡ የስርቆት ድርጊቱን ፈጸመ የተባለው በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ ሁለት እና ሦስት እንዲሁም በቦሌ ክፍለ ከተማ ቦሌ መድኃኒአለም አቢሲኒያ ህንጻ አካባቢ ነው።
ለቲክቫህ ቃላቸውን የሰጡ ስርቆቱ የተፈጸመባቸው ግለሰብ "ህዳር ዘጠኝ ስምንት ሰዓት ላይ ወሎ ሰፈር አካባቢ የሚገኝ ህንጻ ስድስተኛ ፎቅ ወደሚገኝ ቢሮአችን ነጭ ቲሸርት እና ጅንስ ሱሪ አድርጎ የገባ ግለሰብ ሪሰፕሽን ላይ ሰው አለመኖሩን በማረጋገጥ ላፕቶፕ ይዞ ተሰውሯል" ብለዋል።
ግለሰቡ የስርቆት ድርጊቱን ሲፈጽም በድርጅቱ በተገጠመ የደህንነት ካሜራ የተቀረጸ ሲሆን ላፕቶፑን በቲሸርቱ ውስጥ በመደበቅ ይዞ ሲወጣ ይታያል።
ስርቆቱ የተፈጸመባቸው ግለሰብ ግለሰቡን የሚያውቀው ሰው ካለ በሚል በማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በደህንነት ካሜራ የተቀረጸውን ቪዲዮ ማጋራታቸውን ተናግረዋል።
መረጃውን በማህበራዊ ሚዲያ ካጋሩት በኋላ በቀናት ልዩነት እኛም በተመሳሳይ ሰው ተዘርፈናል የሚሉ ግለሰቦች እንዳነጋገሯቸው ገልጸውልናል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያም ስርቆቱ የተፈጸመባቸው ሌላኛውን ተበዳይ በማነጋገር ዝርፊያው መፈጸሙን አረጋግጧል።
ግለሰቡ ቦሌ መድኃኒአለም አካባቢ ወደሚገኝ ህንጻ በመግባት ስርቆቱን የፈጸመው ህዳር 9 ሰኞ የስርቆት ድርጊቱን ከፈጸመ ከአምስት ቀናት በኋላ ማለትም ህዳር 14 ቅዳሜ ቀን ሲሆን በዕለቱ ጥቁር ቲሸርት እና ጅንስ ሱሪ በመልበስ ስልኮቹን ሲያነሳ በተመሳሳይ በደህንነት ካሜራ እይታ ውስጥ ገብቷል።
በቀናት ልዩነት አንድ ላፕቶፕ እና ሁለት ስልኮችን ከሁለት የተለያዩ ድርጅቶች ሰርቆ የተሰወረው ይህ ግለሰብ ጻጉሜ 4/2016 ዓም ቂርቆስ ክፍለ ወረዳ ሁለት ፍላሚንጎ አካባቢ በተመሳሳይ ሰው የስርቆት ድርጊት ተፈጽሞብኛል ያሉ ግለሰብም ቃላቸው ለቲክቫህ ሰጥተዋል።
"ፍላሚንጎ ሰንሻይን ኮንስትራክሽን አካባቢ ወደሚገኝ ቢሮአችን በመግባት ላፕቶፕ በመስረቅ ተሰውሯል ለፖሊስ ብናመለክትም ስሙንም ሆነ አድራሻውን ማወቅ አልተቻለም" ሲሉ ነግረውናል።
ሶስቱም ግለሰቦች በተመሳሳይ ሰው መሰረቃቸውን ያወቁት ወሎ ሰፈር ከሚገኝ ቢሮአቸው ላፕቶፕ የተሰረቁት ግለሰብ ተንቀሳቃሽ ምስሉን በማህበራዊ ሚዲያ ማጋራታቸውን ተከትሎ ነው።
የስርቆቱ ድርጊቱ የተፈጸመባቸው ግለሰቦች ውስጥ ሁለቱ የደህንነት ካሜራውን ምስሎች እና አስፈላጊውን መረጃዎች በመያዝ ለፖሊስ ቢያመለክቱም ግለሰቡ እስካሁን በቁጥጥር ስር አልዋለም።
ፖሊስ ምን አለ?
ቲክቫህ ኢትዮጵያ መረጃውን በመያዝ ጉዳዩን እየተከታተለ የሚገኘውን በአዲስ አበባ ፖሊስ የመስቀል ፍላወር አከባቢ ፖሊስ ጣቢያ አነጋግሯል።
ፖሊስ "በእኛ በኩል ሰውዬውን ለመያዝ በክትትል ላይ ነው የምንገኘው እስካሁን ገና አልተያዘም ቦሌ እና ቂርቆስ ላይ ወንጀሉን ፈጽሟል በክትትል ላይ ነው ያለነው " የሚል ምላሽ ሰጥቷል።
ግለሰቡን ያያቹ ወይም ያለበትን የምታውቁ ከታች በተቀመጡት ስልኮች በመጠቆም ትብብር እንድታደርጉ ጥሪ ቀርቧል።
ለጥቆማ፡ 0114621442, 0911115656
@tikvahethiopia
በተለያዩ ቀናት ከሦስት ድርጅቶች ስልክና ላፕቶፕ ሲሰርቅ በካሜራ ዕይታ የገባው ግለሰብ በፖሊስ እየተፈለገ ነው።
በአዲስ አበባ ከተማ በቂርቆስ እና በቦሌ ክፍለ ከተማ በቀናት ልዩነት በ 3 ድርጅቶች የላፕቶፕ እና የሞባይል ስልኮች ስርቆት በተመሳሳይ ግለሰብ መፈጸሙን ዝርፊያው የተፈጸመባቸው የንብረቱ ባለቤቶች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል ።
ግለሰቡ የስርቆት ድርጊቱን ፈጸመ የተባለው በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ ሁለት እና ሦስት እንዲሁም በቦሌ ክፍለ ከተማ ቦሌ መድኃኒአለም አቢሲኒያ ህንጻ አካባቢ ነው።
ለቲክቫህ ቃላቸውን የሰጡ ስርቆቱ የተፈጸመባቸው ግለሰብ "ህዳር ዘጠኝ ስምንት ሰዓት ላይ ወሎ ሰፈር አካባቢ የሚገኝ ህንጻ ስድስተኛ ፎቅ ወደሚገኝ ቢሮአችን ነጭ ቲሸርት እና ጅንስ ሱሪ አድርጎ የገባ ግለሰብ ሪሰፕሽን ላይ ሰው አለመኖሩን በማረጋገጥ ላፕቶፕ ይዞ ተሰውሯል" ብለዋል።
ግለሰቡ የስርቆት ድርጊቱን ሲፈጽም በድርጅቱ በተገጠመ የደህንነት ካሜራ የተቀረጸ ሲሆን ላፕቶፑን በቲሸርቱ ውስጥ በመደበቅ ይዞ ሲወጣ ይታያል።
ስርቆቱ የተፈጸመባቸው ግለሰብ ግለሰቡን የሚያውቀው ሰው ካለ በሚል በማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በደህንነት ካሜራ የተቀረጸውን ቪዲዮ ማጋራታቸውን ተናግረዋል።
መረጃውን በማህበራዊ ሚዲያ ካጋሩት በኋላ በቀናት ልዩነት እኛም በተመሳሳይ ሰው ተዘርፈናል የሚሉ ግለሰቦች እንዳነጋገሯቸው ገልጸውልናል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያም ስርቆቱ የተፈጸመባቸው ሌላኛውን ተበዳይ በማነጋገር ዝርፊያው መፈጸሙን አረጋግጧል።
ግለሰቡ ቦሌ መድኃኒአለም አካባቢ ወደሚገኝ ህንጻ በመግባት ስርቆቱን የፈጸመው ህዳር 9 ሰኞ የስርቆት ድርጊቱን ከፈጸመ ከአምስት ቀናት በኋላ ማለትም ህዳር 14 ቅዳሜ ቀን ሲሆን በዕለቱ ጥቁር ቲሸርት እና ጅንስ ሱሪ በመልበስ ስልኮቹን ሲያነሳ በተመሳሳይ በደህንነት ካሜራ እይታ ውስጥ ገብቷል።
በቀናት ልዩነት አንድ ላፕቶፕ እና ሁለት ስልኮችን ከሁለት የተለያዩ ድርጅቶች ሰርቆ የተሰወረው ይህ ግለሰብ ጻጉሜ 4/2016 ዓም ቂርቆስ ክፍለ ወረዳ ሁለት ፍላሚንጎ አካባቢ በተመሳሳይ ሰው የስርቆት ድርጊት ተፈጽሞብኛል ያሉ ግለሰብም ቃላቸው ለቲክቫህ ሰጥተዋል።
"ፍላሚንጎ ሰንሻይን ኮንስትራክሽን አካባቢ ወደሚገኝ ቢሮአችን በመግባት ላፕቶፕ በመስረቅ ተሰውሯል ለፖሊስ ብናመለክትም ስሙንም ሆነ አድራሻውን ማወቅ አልተቻለም" ሲሉ ነግረውናል።
ሶስቱም ግለሰቦች በተመሳሳይ ሰው መሰረቃቸውን ያወቁት ወሎ ሰፈር ከሚገኝ ቢሮአቸው ላፕቶፕ የተሰረቁት ግለሰብ ተንቀሳቃሽ ምስሉን በማህበራዊ ሚዲያ ማጋራታቸውን ተከትሎ ነው።
የስርቆቱ ድርጊቱ የተፈጸመባቸው ግለሰቦች ውስጥ ሁለቱ የደህንነት ካሜራውን ምስሎች እና አስፈላጊውን መረጃዎች በመያዝ ለፖሊስ ቢያመለክቱም ግለሰቡ እስካሁን በቁጥጥር ስር አልዋለም።
ፖሊስ ምን አለ?
ቲክቫህ ኢትዮጵያ መረጃውን በመያዝ ጉዳዩን እየተከታተለ የሚገኘውን በአዲስ አበባ ፖሊስ የመስቀል ፍላወር አከባቢ ፖሊስ ጣቢያ አነጋግሯል።
ፖሊስ "በእኛ በኩል ሰውዬውን ለመያዝ በክትትል ላይ ነው የምንገኘው እስካሁን ገና አልተያዘም ቦሌ እና ቂርቆስ ላይ ወንጀሉን ፈጽሟል በክትትል ላይ ነው ያለነው " የሚል ምላሽ ሰጥቷል።
ግለሰቡን ያያቹ ወይም ያለበትን የምታውቁ ከታች በተቀመጡት ስልኮች በመጠቆም ትብብር እንድታደርጉ ጥሪ ቀርቧል።
ለጥቆማ፡ 0114621442, 0911115656
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#TPLF ለመሆኑ አቶ ጌታቸው ረዳ ' የቀድሞው ' ከተባሉ ክልሉን (ትግራይን) ማነው እያስተዳደረ ያለው ? ይህ በደብረጽዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) ለሚመራው ህወሓት ምክትል ሊቀመንበር አቶ አማኑኤል አሰፋ የቀረበ ጥያቄ ነው። አቶ አማኑኤል አሰፋ ይህን ጥያቄ የተጠየቁት አቶ ጌታቸው ረዳን " የቀድሞው ፕዜዳንት " ብለው በመጥራታቸው ነው። " የፕሬዜዳንት ውክልና ሲነሳ ፕሬዜዳንቱ በሌለበት ማን እንደሚሰራ…
" የቀድሞ / ነባር ነኝ አይደለሁም የሚለውን ከፓሊስ እንነጋገርበታለን ፤ ያኔ ግልፅ ይሆንላቸዋል !! " - አቶ ጌታቸው ረዳ
ባለፈው ሳምንት ህዳር 17/2017 ዓ.ም በደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) በሚመራው ህወሓት ቡድን ምክትል ሊቀ መንበር የሆኑት አቶ አማኒኤል አሰፋ በሰጡት መግለጫ የጊዚያዊ አስተዳደሩ ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳን " የቀድሞ ፕሬዜዳንት " ሲሉ ጠርተዋቸው ነበር።
ህዳር 22/2017 ዓ/ም በመቐለ ከተማና ዙሪያዋ ከሚገኘው ደቡባዊ ምስራቃዊ ዞን ከተውጣጡ ወጣቶች ጋር የተወያዩት ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ በመድረኩ ለአቶ አማኒኤል ንግግር በስሜትና ኃይለ ቃል በመጠቀም " እሳቸው ለሚገኙበት ቡድን " ሲሉ ምላሽ ሰጥተዋል።
ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ ምን አሉ ?
" ባለፈው ጊዜ አንድ ሃላፊ ነኝ ባይ በመንግስት ሚድያ ' ነባር / የቀድሞ ፕሬዜዳንት ' ሲል ሰምታቹሃል ? ተልካሻ ነው። የቀድሞ / ነባር ነኝ አይደለሁም የሚለውን ከፓሊስ እንነጋገርበታለን ፤ ያኔ ግልፅ ይሆንላቸዋል።
እነዚህ አንድ ቀን ቁምነገር ሰርተው አያውቁም። መዋቅራቸው ስርቆት ላይ የተሰማራ ነው። አሁን የልዩነት ነጥቡ ፓለቲካ መሆኑ ቀርቷል።
የኔ ሳምንት ይሁን ወር በዚህ ወንበር መቆየት ያን ያህል አያሳስበኝም ፤ ይህን አደገኛ ቡድን ግን የወንጅል ትስስር (Crime network ) ነው የሚመራው።
በሰሜን ምዕራብ ማእከላዊ ዞኖች ወርቅ ፣ መዳብ እና ሌላ ማዕድናት ያካተተ ዘረፋ የሚያካሄደው ይህን በወንጀል የተሳሰረ ቡድን ነው ፤ ስለሆነም ዞኖቹን ከሱ ቁጥጥር ውጪ እንዲወጡ ፍላጎት የለውም።
ቡድኑ ይህን የዘረፋ ባህሪ አሁን ያመጣው አዲስ ነገር አይደለም ፤ የቆየበት ነው ፤ ሃሜት አይደለም እየነገርኳችሁ ያለሁት ተደራጅቶ እየዘረፈ ነው ያለው።
በስንፍናችን ይሁን ድንገት ወደ ስርቆት ኔትወርክ ያልገባን ሰዎች አለን። ስለሆነም እነዚህን ያለ የሌለ ውሸት ፈጥሮ ስማችን በማጥፋትና በማጠልሸት ' ከጨዋታ ውጪ ማድረግ አለብን ' ብለው ነው በኛ ላይ የዘመቱት።
ስለዚህ ይህንን የቡድኑን ተግባር እንደ ፓለቲካ ሳይሆን እንደ ሌብነት ነው መቆጠር ያለበት፤ ስለሆነም ቡድኑ አንድ እሱን የመሰለ ሌባ አቀፎ ለመያዝ የመጣበት አከባቢ ሳይለይ አባሉ ያደርገዋል " ብለዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia
ባለፈው ሳምንት ህዳር 17/2017 ዓ.ም በደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) በሚመራው ህወሓት ቡድን ምክትል ሊቀ መንበር የሆኑት አቶ አማኒኤል አሰፋ በሰጡት መግለጫ የጊዚያዊ አስተዳደሩ ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳን " የቀድሞ ፕሬዜዳንት " ሲሉ ጠርተዋቸው ነበር።
ህዳር 22/2017 ዓ/ም በመቐለ ከተማና ዙሪያዋ ከሚገኘው ደቡባዊ ምስራቃዊ ዞን ከተውጣጡ ወጣቶች ጋር የተወያዩት ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ በመድረኩ ለአቶ አማኒኤል ንግግር በስሜትና ኃይለ ቃል በመጠቀም " እሳቸው ለሚገኙበት ቡድን " ሲሉ ምላሽ ሰጥተዋል።
ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ ምን አሉ ?
" ባለፈው ጊዜ አንድ ሃላፊ ነኝ ባይ በመንግስት ሚድያ ' ነባር / የቀድሞ ፕሬዜዳንት ' ሲል ሰምታቹሃል ? ተልካሻ ነው። የቀድሞ / ነባር ነኝ አይደለሁም የሚለውን ከፓሊስ እንነጋገርበታለን ፤ ያኔ ግልፅ ይሆንላቸዋል።
እነዚህ አንድ ቀን ቁምነገር ሰርተው አያውቁም። መዋቅራቸው ስርቆት ላይ የተሰማራ ነው። አሁን የልዩነት ነጥቡ ፓለቲካ መሆኑ ቀርቷል።
የኔ ሳምንት ይሁን ወር በዚህ ወንበር መቆየት ያን ያህል አያሳስበኝም ፤ ይህን አደገኛ ቡድን ግን የወንጅል ትስስር (Crime network ) ነው የሚመራው።
በሰሜን ምዕራብ ማእከላዊ ዞኖች ወርቅ ፣ መዳብ እና ሌላ ማዕድናት ያካተተ ዘረፋ የሚያካሄደው ይህን በወንጀል የተሳሰረ ቡድን ነው ፤ ስለሆነም ዞኖቹን ከሱ ቁጥጥር ውጪ እንዲወጡ ፍላጎት የለውም።
ቡድኑ ይህን የዘረፋ ባህሪ አሁን ያመጣው አዲስ ነገር አይደለም ፤ የቆየበት ነው ፤ ሃሜት አይደለም እየነገርኳችሁ ያለሁት ተደራጅቶ እየዘረፈ ነው ያለው።
በስንፍናችን ይሁን ድንገት ወደ ስርቆት ኔትወርክ ያልገባን ሰዎች አለን። ስለሆነም እነዚህን ያለ የሌለ ውሸት ፈጥሮ ስማችን በማጥፋትና በማጠልሸት ' ከጨዋታ ውጪ ማድረግ አለብን ' ብለው ነው በኛ ላይ የዘመቱት።
ስለዚህ ይህንን የቡድኑን ተግባር እንደ ፓለቲካ ሳይሆን እንደ ሌብነት ነው መቆጠር ያለበት፤ ስለሆነም ቡድኑ አንድ እሱን የመሰለ ሌባ አቀፎ ለመያዝ የመጣበት አከባቢ ሳይለይ አባሉ ያደርገዋል " ብለዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia
#Ethiotelecom
የድኅረ ክፍያ የሞባይል ጥቅል ለድርጅትዎ በተመጣጣኝ ዋጋ!
💁♂️ በወር ከ270 ብር ጀምሮ በብዙ አማራጭ ቀርበዋል፤ የ2 ዓመት ውል በመግባት እስከ 45% የሚደርስ ተጨማሪ ስጦታ ያግኙ።
📍 በአቅራቢያዎ ወደሚገኝ የድርጅት አገልግሎት ማዕከል ጎራ ይበሉ!
ለተጨማሪ መረጃ https://bit.ly/3Zect70 ይጎብኙ!
#Ethiotelecom #telebirr #DigitalAfrica #SmartAfrica #DigitalEthiopia #RealizingDigitalEthiopia
የድኅረ ክፍያ የሞባይል ጥቅል ለድርጅትዎ በተመጣጣኝ ዋጋ!
💁♂️ በወር ከ270 ብር ጀምሮ በብዙ አማራጭ ቀርበዋል፤ የ2 ዓመት ውል በመግባት እስከ 45% የሚደርስ ተጨማሪ ስጦታ ያግኙ።
📍 በአቅራቢያዎ ወደሚገኝ የድርጅት አገልግሎት ማዕከል ጎራ ይበሉ!
ለተጨማሪ መረጃ https://bit.ly/3Zect70 ይጎብኙ!
#Ethiotelecom #telebirr #DigitalAfrica #SmartAfrica #DigitalEthiopia #RealizingDigitalEthiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" የቀድሞ / ነባር ነኝ አይደለሁም የሚለውን ከፓሊስ እንነጋገርበታለን ፤ ያኔ ግልፅ ይሆንላቸዋል !! " - አቶ ጌታቸው ረዳ ባለፈው ሳምንት ህዳር 17/2017 ዓ.ም በደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) በሚመራው ህወሓት ቡድን ምክትል ሊቀ መንበር የሆኑት አቶ አማኒኤል አሰፋ በሰጡት መግለጫ የጊዚያዊ አስተዳደሩ ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳን " የቀድሞ ፕሬዜዳንት " ሲሉ ጠርተዋቸው ነበር። ህዳር 22/2017…
#ሹመት
የትግራይ ክልል ጊዚያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ ከሰሞኑን 6 አዳዲስ ሹመቶች ሰጥተዋል።
ከስድስቱ ሽመቶች ሁለቱ በደብረፅዮን ገ / ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራው ህወሓት የተሾሙትን በማንሳት የተሰጠ ነው።
በዚሁ መሰረት ፕሬዜዳንቱ ከህዳር 20/2017 ዓ.ም ጀምሮ የሚፀና በደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራው ህወሓት የመቐለ ከንቲባ በመሆኑ የተሾሙት ረዳኢ በርሀ (ዶ/ር) በመሻር በብርሃነ ገ/ዮሱስ ተክተዋል።
የትግራይ ትምህርት ቢሮ ምክትል የስራ ሃላፊ ሆነው ሲያገለግሉ ቆይተው ከህዳር 17/2017 ዓ.ም ጀምሮ በደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራው ህወሓት የዓዲግራት ከንቲባ በመሆን የተሾሙት ረዳኢ ገ/ሄር ምትክ ኪ/ማርያም ወ/ሚካኤል ምክትል የቢሮ ሃላፊ ሆነው ተሹመዋል።
ፕሬዜዳንቱ በጡሮታ በተገለሉት ሓዱሽ ካሱ ምትክ ዶ/ር ገብሩ ካሕሳይ የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ምክትል ፅሕፈት ቤት ሃላፊ አድርገዋቸዋል።
ኮማንደር ተስፋይ ገ/ማርያም በምክትል ኮሚሽነር መዓርግ የወንጀል ማጣራት ሃላፊ ፤ ኮማንደር ጌታቸው ኪሮስን በምክትል ኮሚሽነር መዓርግ የወንጀል መከላከል ሃላፊ እንዲሁም አቶ ሃይላይ ኣብራሃ በምክትል ኮሚሽነር መዓርግ የሰው ሃይል ልማት ዘርፍ ሃላፊ አደርገው ሹመዋል።
በቅርቡ የግድያ ሙከራ እንደተደረገባቸው በተናገሩት የትግራይ ማእከላዊ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ሰለሞን መዓሾ ምትክ ጉዕሽ ግደይ ሓድጉ የትግራይ ማእከላዊ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ሆነው በፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ደብዳቤ መሾማቸው ይታወሳል።
#TikvahEthiopiaMekelle
@tikvahethiopia
የትግራይ ክልል ጊዚያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ ከሰሞኑን 6 አዳዲስ ሹመቶች ሰጥተዋል።
ከስድስቱ ሽመቶች ሁለቱ በደብረፅዮን ገ / ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራው ህወሓት የተሾሙትን በማንሳት የተሰጠ ነው።
በዚሁ መሰረት ፕሬዜዳንቱ ከህዳር 20/2017 ዓ.ም ጀምሮ የሚፀና በደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራው ህወሓት የመቐለ ከንቲባ በመሆኑ የተሾሙት ረዳኢ በርሀ (ዶ/ር) በመሻር በብርሃነ ገ/ዮሱስ ተክተዋል።
የትግራይ ትምህርት ቢሮ ምክትል የስራ ሃላፊ ሆነው ሲያገለግሉ ቆይተው ከህዳር 17/2017 ዓ.ም ጀምሮ በደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራው ህወሓት የዓዲግራት ከንቲባ በመሆን የተሾሙት ረዳኢ ገ/ሄር ምትክ ኪ/ማርያም ወ/ሚካኤል ምክትል የቢሮ ሃላፊ ሆነው ተሹመዋል።
ፕሬዜዳንቱ በጡሮታ በተገለሉት ሓዱሽ ካሱ ምትክ ዶ/ር ገብሩ ካሕሳይ የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ምክትል ፅሕፈት ቤት ሃላፊ አድርገዋቸዋል።
ኮማንደር ተስፋይ ገ/ማርያም በምክትል ኮሚሽነር መዓርግ የወንጀል ማጣራት ሃላፊ ፤ ኮማንደር ጌታቸው ኪሮስን በምክትል ኮሚሽነር መዓርግ የወንጀል መከላከል ሃላፊ እንዲሁም አቶ ሃይላይ ኣብራሃ በምክትል ኮሚሽነር መዓርግ የሰው ሃይል ልማት ዘርፍ ሃላፊ አደርገው ሹመዋል።
በቅርቡ የግድያ ሙከራ እንደተደረገባቸው በተናገሩት የትግራይ ማእከላዊ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ሰለሞን መዓሾ ምትክ ጉዕሽ ግደይ ሓድጉ የትግራይ ማእከላዊ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ሆነው በፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ደብዳቤ መሾማቸው ይታወሳል።
#TikvahEthiopiaMekelle
@tikvahethiopia
" ሃይማኖቴ አይፈቅድልኝም !! "
" ሃይማኖቴ አይፈቅድልኝም ! " ያለው የእግር ኳስ ተጫዋች ግብረሰዶማውያን ለመደገፍ ሲባል ክንድ ላይ የሚጠለቀውን ምልክት ሳያደርግ ቀርቷል።
በዓለም ላይ በቢሊዮኖች የሚቆጠሩ የእግር ኳስ ፍልሚያ አፍቃሪያን እንዳሉ ይታወቃል።
ከየትኛውም ሀገራት በላይ ደግሞ የአውሮፓ ሀገራት ውስጥ የሚካሄዱት ፍልሚያዎች እጅግ ብዙ ተመልካች ያላቸውና ከፍተኛ ተወዳጅነትን ከፉክክር ጋር ያጣመሩ ናቸው።
በተለይም የእንግሊዝ ፕሪሜየርሊግ በሀገራችን ኢትዮጵያ ሳይቀር እጅግ ከፍተኛ ተወዳጅነት ያለውና ብዙ ተመልካች ያለው ነው።
ከህጻን እስከ አዋቂ፣ አዛውንቶች ሳይቀሩ ነው ፍልሚያውን የሚከታተሉት።
ነገር ግን በየዓመቱ ይህ የእግር ኳስ ፍልሚያ የሚደራበት ወር በተለይም ሃይማኖተኛ የሆኑ የእግር ኳስ ተመልካቾችን የሚያስቀይም ነው።
ምክንያት ? ሊጉ ውስጥ ግብረሰዶማውያንን ለመደገፍ ሲባል ዘመቻ ስለሚካሄድበት ነው።
ሰዎቹ " እኩልነትን ለማምጣት " ይበሉት እንጂ በበርካታ ሃይማኖተኛ እግር ኳስ ተመልካቾች እና ተጫዋቾች ዘንድ የሚወገዝ ተግባር ነው የሚፈጽሙት።
የፕሪሚዬር ሊግ ክለቦች ለግበረሰዶማውያን ያላቸውን ድጋፍ ለማሳየት አምበሎቻቸው የግብረሰዶማውያኑን መለያ ምልክት ክንዳቸው ላይ እንዲያጠልቁ ያደርጋሉ።
ይህን ዘመቻ የሚያደርጉትም እኤአ ከኅዳር 29 እስከ ታኅሣሥ 5 ነው።
ከቀናት በፊት በነበረ አንድ ጨዋታ ላይ ግን የአንድ ክለብ አምበል " እኔ ሃይማኖቴ አይፈቅድልኝም " በማለት ምልክቱን ሳያድረግ ቀርቷል።
የተጨዋቹ ስም ሳም ሞርሲ ይባላል ፤ ኢፕስዊች ታውን የተባለው ክለብ አምበል ነው።
በእምነቱም የእስልምና እምነት ተከታይ ሲሆን የግብፅ ዜጋ ነው።
ይኸው ተጫዋች ነው ቡድኑ ኖቲንግሃም ፎረስት ከተባለው ቡድን ጋር በተጫወተበት ወቅት ክንዱ ላይ ምልክቱን " አላጠልቅም " ብሎ ጨዋታውን ያካሄደው።
ክለቡ ባወጣው መግለጫ ምልክቱን ያላደረገው " በሃይማኖቱ ምክንያት ነው ፤ ውሳኔውን እናከብራለን " ብሏል።
ክለቡ አክሎም ፤ የግብረሰዶማውያኑን ምልክት የሚያሳየውን የአምበሎች መለያ በኩራት እንደሚደግፍ ፤ ከግብረሰዶማውያን ማኅበረሰብ ጋር አብሮ እንደሚቆም ፤ እኩልነት እና ተቀባይነት እንዲንሰራፋ እንደሚሰራ ገልጿል።
ከሳም ሞርሲ በስተቀር ሌሎች የፕሪሚዬር ሊጉ አምበሎች የግብረሰዶማውያንን ባንዲራ አጥልቀው ሲጫወቱ ነበር።
#SamMorsy #PremierLeague #Muslim
@tikvahethiopia
" ሃይማኖቴ አይፈቅድልኝም ! " ያለው የእግር ኳስ ተጫዋች ግብረሰዶማውያን ለመደገፍ ሲባል ክንድ ላይ የሚጠለቀውን ምልክት ሳያደርግ ቀርቷል።
በዓለም ላይ በቢሊዮኖች የሚቆጠሩ የእግር ኳስ ፍልሚያ አፍቃሪያን እንዳሉ ይታወቃል።
ከየትኛውም ሀገራት በላይ ደግሞ የአውሮፓ ሀገራት ውስጥ የሚካሄዱት ፍልሚያዎች እጅግ ብዙ ተመልካች ያላቸውና ከፍተኛ ተወዳጅነትን ከፉክክር ጋር ያጣመሩ ናቸው።
በተለይም የእንግሊዝ ፕሪሜየርሊግ በሀገራችን ኢትዮጵያ ሳይቀር እጅግ ከፍተኛ ተወዳጅነት ያለውና ብዙ ተመልካች ያለው ነው።
ከህጻን እስከ አዋቂ፣ አዛውንቶች ሳይቀሩ ነው ፍልሚያውን የሚከታተሉት።
ነገር ግን በየዓመቱ ይህ የእግር ኳስ ፍልሚያ የሚደራበት ወር በተለይም ሃይማኖተኛ የሆኑ የእግር ኳስ ተመልካቾችን የሚያስቀይም ነው።
ምክንያት ? ሊጉ ውስጥ ግብረሰዶማውያንን ለመደገፍ ሲባል ዘመቻ ስለሚካሄድበት ነው።
ሰዎቹ " እኩልነትን ለማምጣት " ይበሉት እንጂ በበርካታ ሃይማኖተኛ እግር ኳስ ተመልካቾች እና ተጫዋቾች ዘንድ የሚወገዝ ተግባር ነው የሚፈጽሙት።
የፕሪሚዬር ሊግ ክለቦች ለግበረሰዶማውያን ያላቸውን ድጋፍ ለማሳየት አምበሎቻቸው የግብረሰዶማውያኑን መለያ ምልክት ክንዳቸው ላይ እንዲያጠልቁ ያደርጋሉ።
ይህን ዘመቻ የሚያደርጉትም እኤአ ከኅዳር 29 እስከ ታኅሣሥ 5 ነው።
ከቀናት በፊት በነበረ አንድ ጨዋታ ላይ ግን የአንድ ክለብ አምበል " እኔ ሃይማኖቴ አይፈቅድልኝም " በማለት ምልክቱን ሳያድረግ ቀርቷል።
የተጨዋቹ ስም ሳም ሞርሲ ይባላል ፤ ኢፕስዊች ታውን የተባለው ክለብ አምበል ነው።
በእምነቱም የእስልምና እምነት ተከታይ ሲሆን የግብፅ ዜጋ ነው።
ይኸው ተጫዋች ነው ቡድኑ ኖቲንግሃም ፎረስት ከተባለው ቡድን ጋር በተጫወተበት ወቅት ክንዱ ላይ ምልክቱን " አላጠልቅም " ብሎ ጨዋታውን ያካሄደው።
ክለቡ ባወጣው መግለጫ ምልክቱን ያላደረገው " በሃይማኖቱ ምክንያት ነው ፤ ውሳኔውን እናከብራለን " ብሏል።
ክለቡ አክሎም ፤ የግብረሰዶማውያኑን ምልክት የሚያሳየውን የአምበሎች መለያ በኩራት እንደሚደግፍ ፤ ከግብረሰዶማውያን ማኅበረሰብ ጋር አብሮ እንደሚቆም ፤ እኩልነት እና ተቀባይነት እንዲንሰራፋ እንደሚሰራ ገልጿል።
ከሳም ሞርሲ በስተቀር ሌሎች የፕሪሚዬር ሊጉ አምበሎች የግብረሰዶማውያንን ባንዲራ አጥልቀው ሲጫወቱ ነበር።
#SamMorsy #PremierLeague #Muslim
@tikvahethiopia