📣 ኢትዮ ቴሌኮም የዲጂታል መታወቂያ ካርድ ኅትመት በቴሌብር ሱፐርአፕ ጀመረ!!
💁♂️ ቴሌብር ሱፐርአፕ ላይ ‘’NID (Fayda) Printing’’ በሚለው ሚኒ መተግበሪያ ተጠቅመው የፋይዳ ቁጥርዎን በማስገባትና ክፍያዎን በመፈጸም በመረጡት የመረከቢያ ቀንና ቦታ የዲጂታል መታወቂያ ካርድዎን ይረከቡ፡፡
📍 በመዲናችን የሚገኙ የመረከቢያ ቦታዎችን ለመመልከት፡ https://bit.ly/3UT6rY3
🔗 ቴሌብር ሱፐርአፕን https://onelink.to/uecbbr ይጫኑ!
ቴሌብር - እጅግ ቀላል፣ ፈጣን፣ ምቹ እና አስተማማኝ!
#Ethiotelecom #telebirr #telebirrSupperApp #DigitalEthiopia #DigitalAfrica #RealizingDigitalEthiopia
💁♂️ ቴሌብር ሱፐርአፕ ላይ ‘’NID (Fayda) Printing’’ በሚለው ሚኒ መተግበሪያ ተጠቅመው የፋይዳ ቁጥርዎን በማስገባትና ክፍያዎን በመፈጸም በመረጡት የመረከቢያ ቀንና ቦታ የዲጂታል መታወቂያ ካርድዎን ይረከቡ፡፡
📍 በመዲናችን የሚገኙ የመረከቢያ ቦታዎችን ለመመልከት፡ https://bit.ly/3UT6rY3
🔗 ቴሌብር ሱፐርአፕን https://onelink.to/uecbbr ይጫኑ!
ቴሌብር - እጅግ ቀላል፣ ፈጣን፣ ምቹ እና አስተማማኝ!
#Ethiotelecom #telebirr #telebirrSupperApp #DigitalEthiopia #DigitalAfrica #RealizingDigitalEthiopia
#ሴጅ_ማሰልጠኛ
ሙሉ የሒሳብ መዝገብ አያያዝ (Principles and Practices of Accounting) የ3 ወር እና 6 ወር የቀንና የማታ መርሐግብር ስልጠና በፒያሣ እና መገናኛ ካምፓስ ካምፓስ ሰኞ ህዳር 23/2017 ዓ.ም ይጀምራል።
👉 100% በተግባር የተደገፈ ስልጠና
👉 መሠረታዊ አካውንቲንግ እና ኦዲት አሰራር፣ ሙሉ የአካውንቲንግ ሒሳብ አሰራር በፒስቺሪ ተደግፎ እና የግብር አያያዝ ትምህርቶችን አካቶ የሚሰጥ
👉 የሥራ ላይ ስልጠና (Internship) የተመቻቸለት
ስልክ፦ 0906777799 / 0906777755
አድራሻ፦ ቁ.1: ፒያሣ ቸርችል ጎዳና ኤልያና ሆቴል 2ኛ ፎቅ እና ቁ.2 መገናኛ ታሜጋስ ህንፃ 2ኛ ፎቅ
Telegram: https://t.iss.one/sagetraininginstitute
Tiktok: https://www.tiktok.com/@sage_training_institute
Linkedin: https://www.linkedin.com/company/sage-training-institute
ሙሉ የሒሳብ መዝገብ አያያዝ (Principles and Practices of Accounting) የ3 ወር እና 6 ወር የቀንና የማታ መርሐግብር ስልጠና በፒያሣ እና መገናኛ ካምፓስ ካምፓስ ሰኞ ህዳር 23/2017 ዓ.ም ይጀምራል።
👉 100% በተግባር የተደገፈ ስልጠና
👉 መሠረታዊ አካውንቲንግ እና ኦዲት አሰራር፣ ሙሉ የአካውንቲንግ ሒሳብ አሰራር በፒስቺሪ ተደግፎ እና የግብር አያያዝ ትምህርቶችን አካቶ የሚሰጥ
👉 የሥራ ላይ ስልጠና (Internship) የተመቻቸለት
ስልክ፦ 0906777799 / 0906777755
አድራሻ፦ ቁ.1: ፒያሣ ቸርችል ጎዳና ኤልያና ሆቴል 2ኛ ፎቅ እና ቁ.2 መገናኛ ታሜጋስ ህንፃ 2ኛ ፎቅ
Telegram: https://t.iss.one/sagetraininginstitute
Tiktok: https://www.tiktok.com/@sage_training_institute
Linkedin: https://www.linkedin.com/company/sage-training-institute
TIKVAH-ETHIOPIA
#Ethiopia የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ለ2017 በጀት አመት 971.2 ቢሊዮን ብር በጀት በሙሉ ድምጽ አጽድቋል። ከጸደቀው ገንዘብ ውስጥ ፦ ➡️ 451,307,221,052 ለመደበኛ ወጪዎች ➡️ 283,199,335,412 ለካፒታል ወጪዎች ➡️ 222,694,109,445 ለክልሎች የሚሰጥ ድጋፍ ➡️ 14,000,000,000 ለዘላቂ የልማት ግቦች ማስፈጸሚያ የተመደበ ነው፡፡ @tikvahethiopia
#ኢትዮጵያ
የዘንድሮው በጀት ዓመት የፌዴራል መንግስት የአጠቃላይ በጀት 1.5 ትሪሊየን ብር ሆኗል።
ዛሬ የህዝብ ተወካዮች ም/ቤት 582 ቢሊየን ብር ተጨማሪ የፌደራል መንግስት በጀት አፅድቋል።
ለ2017 በጀት ዓመት ተጨማሪ ሆኖ የፀደቀው በጀት ፦
- ለውጭ እና ለሀገር ውስጥ ዕዳ ክፍያ፣
- ለማህበራዊ በጀት ድጎማ (ለነዳጅ፣ ለማዳበሪያ፣ ለመድሐኒት፣ ለምግብ ዘይትና ሌሎች)፣
- ለካፒታል ፕሮጀክቶች ማስፋፊያ፣
- ለማህበራዊ ሴፍቲኔት ፕሮግራም እና ለመንግስት ሰራተኞች ደመወዝ ማሻሻያ እንደሚውል የመንግስት ዋና ተጠሪ ሚኒስትር ተስፋዬ በልጅጌ (ዶ/ር) አሳውቀዋል።
ከተጨማሪ በጀቱ ለመደበኛ ወጪ 393 ቢሊዮን ፣ ለካፒታል ወጪ 70 ቢሊዮን ብር፣ ለወጪ አሸፋፈን ማስተካከያ 119 ቢሊዮን ብር ይውላል።
የምክር ቤት አባላት ምን ጠየቁ ?
- ተጨማሪ በጀቱ አልባዛም ወይ ?
- በገበያ ውስጥ የዋጋ ግሽበትን አያስከትምልም ወይ ?
- ከተጨማሪ በጀቱ 282 ቢሊየን ብር ከግብር የሚሰበሰብ ከሆነ በግብር ከፋዮች ላይ ጫና አያሳድርም ወይ ? የሚል ጥያቄ አቅርበዋል።
የገንዘብ ሚኒትሩ አቶ አህመድ ሽዴ ፤ " የቀረበው ተጨማሪ በጀት120 ሚሊየን ህዝብ ላላትና በኢኮኖሚ በማደግ ላይ ላለች ሀገር ብዙ የሚባል አይደለም " ብለዋል።
" በጀቱ ከሀገር ውስጥ እና ከውጪ ከሚገኝ ገቢ የሚሸፈንና ዝቅተኛ ተከፋይ ለሆኑ የመንግስት ሰራተኞች እንዲሁም ለሴፍቲኔት ተጠቃሚዎች የሚውል በመሆኑ በዋጋ ግሽበቱ ላይ ለውጥ አያመጣም " ሲሉ መልሰዋል።
ምክር ቤቱ ተጨማሪ በጀቱን በ3 ተቃውሞ እና በ5 ድምፀ ተዓቅቦ በአብላጫ ድምጽ አፅድቆታዋል።
ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ነው።
@tikvahethiopia
የዘንድሮው በጀት ዓመት የፌዴራል መንግስት የአጠቃላይ በጀት 1.5 ትሪሊየን ብር ሆኗል።
ዛሬ የህዝብ ተወካዮች ም/ቤት 582 ቢሊየን ብር ተጨማሪ የፌደራል መንግስት በጀት አፅድቋል።
ለ2017 በጀት ዓመት ተጨማሪ ሆኖ የፀደቀው በጀት ፦
- ለውጭ እና ለሀገር ውስጥ ዕዳ ክፍያ፣
- ለማህበራዊ በጀት ድጎማ (ለነዳጅ፣ ለማዳበሪያ፣ ለመድሐኒት፣ ለምግብ ዘይትና ሌሎች)፣
- ለካፒታል ፕሮጀክቶች ማስፋፊያ፣
- ለማህበራዊ ሴፍቲኔት ፕሮግራም እና ለመንግስት ሰራተኞች ደመወዝ ማሻሻያ እንደሚውል የመንግስት ዋና ተጠሪ ሚኒስትር ተስፋዬ በልጅጌ (ዶ/ር) አሳውቀዋል።
ከተጨማሪ በጀቱ ለመደበኛ ወጪ 393 ቢሊዮን ፣ ለካፒታል ወጪ 70 ቢሊዮን ብር፣ ለወጪ አሸፋፈን ማስተካከያ 119 ቢሊዮን ብር ይውላል።
የምክር ቤት አባላት ምን ጠየቁ ?
- ተጨማሪ በጀቱ አልባዛም ወይ ?
- በገበያ ውስጥ የዋጋ ግሽበትን አያስከትምልም ወይ ?
- ከተጨማሪ በጀቱ 282 ቢሊየን ብር ከግብር የሚሰበሰብ ከሆነ በግብር ከፋዮች ላይ ጫና አያሳድርም ወይ ? የሚል ጥያቄ አቅርበዋል።
የገንዘብ ሚኒትሩ አቶ አህመድ ሽዴ ፤ " የቀረበው ተጨማሪ በጀት120 ሚሊየን ህዝብ ላላትና በኢኮኖሚ በማደግ ላይ ላለች ሀገር ብዙ የሚባል አይደለም " ብለዋል።
" በጀቱ ከሀገር ውስጥ እና ከውጪ ከሚገኝ ገቢ የሚሸፈንና ዝቅተኛ ተከፋይ ለሆኑ የመንግስት ሰራተኞች እንዲሁም ለሴፍቲኔት ተጠቃሚዎች የሚውል በመሆኑ በዋጋ ግሽበቱ ላይ ለውጥ አያመጣም " ሲሉ መልሰዋል።
ምክር ቤቱ ተጨማሪ በጀቱን በ3 ተቃውሞ እና በ5 ድምፀ ተዓቅቦ በአብላጫ ድምጽ አፅድቆታዋል።
ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ነው።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ኢትዮጵያ የዘንድሮው በጀት ዓመት የፌዴራል መንግስት የአጠቃላይ በጀት 1.5 ትሪሊየን ብር ሆኗል። ዛሬ የህዝብ ተወካዮች ም/ቤት 582 ቢሊየን ብር ተጨማሪ የፌደራል መንግስት በጀት አፅድቋል። ለ2017 በጀት ዓመት ተጨማሪ ሆኖ የፀደቀው በጀት ፦ - ለውጭ እና ለሀገር ውስጥ ዕዳ ክፍያ፣ - ለማህበራዊ በጀት ድጎማ (ለነዳጅ፣ ለማዳበሪያ፣ ለመድሐኒት፣ ለምግብ ዘይትና ሌሎች)፣ - ለካፒታል ፕሮጀክቶች…
#ኢትዮጵያ
" ... የውጭ ምንዛሬ ለውጡ in in terms of Dollar ያመጣውን ለውጥ ሊያካክስ የሚችል የደመወዝ ጭማሪ መጨመር ነበረበት " - ደሳለኝ ጫኔ (ዶ/ር)
🔴 " አንድ ደመወዝተኛ በውጭ ምንዛሬ ስናሰላው ያገኝ የነበረው ገቢ በዶላር ከ50% በላይ እንዲቀነስ ተደርጓል !! "
የህ/ተ/ም/ቤት አባሉና የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) ተወካዩ ደሳለኝ ጫኔ (ዶ/ር) በተጨማሪ በጀቱ ዙሪያ ስጋቶች እንዳላቸው ገልጸዋል።
የማክሮ ኢኮኖሚ እና ፊስካል ማዕቀፍ ማሻሻያው ሀገራዊ ውጥቅጥ ውስጥ እንዳስገባን በግልጽ እንደሚታይ ተናግረው ይሄ በጀት እሱን ምን ያህል አ
ተደራሽ ያደርጋል ? ሲሉ ጠይቀዋል።
ከዚህ ባለፈም ደሳለኝ (ዶ/ር) ፤ ስለ ኑሮ ውድነት ፣ ስለሰራተኞች የደመወዝ ጭማሪ ፣ በጀቱን ለመሸፈን ስለሚጣል ግብር አንስተው ጠይቀዋል ፤ ሃሳባቸውን አካፍለዋል።
ምን አሉ ?
" በኑሮ ውድነት ላይ / ቋሚ ደመወዝተኛ በሆነው አካል ላይ የውጭ ምንዛሬው (Foreign exchange) ለውጡ የፈጠረው ጫና አለ።
አንድ ደመወዝተኛ በውጭ ምንዛሬ ስናሰላው ያገኝ የነበረው ገቢ በዶላር ከ50% በላይ እንዲቀነስ ተደርጓል ፤ በውጭ ምንዛሬው ለውጥ ምክንያት።
መንግሥት የደመወዝ ማሻሻያ በተለይ ዝቅተኛ ገቢ ያላቸውን ተቀጣሪዎችን ደመወዝ ማሻሻያ አድርጊያለሁ ቢልም አብዛኛው ደመወዝተኛ ከ1 ሺህ ብር እና ከ2 ሺህ ብር በላይ ጭማሪ አልተደረገለትም። ስለዚህ እነዚህ የማህበረሰብ ክፍሎች ኑሯቸውን እንዴት እንዲመሩ ታስቦ ነው ?
በእኔ በኩል ቢያንስ መንግሥት ሌሎች የmarket variables ትቶ የውጭ ምንዛሬ ለውጡ in in terms of Dollar ያመጣውን ለውጥ ሊያካክስ የሚችል ጭማሪ መጨመር ነበረበት።
አንድ የ12 ሺህ ብር ደመወዝተኛ ከምንዛሬ ለውጡ በፊት ወደ 300 እስከ 350 ዶላር አካባቢ ያገኝ ነበር አሁን መንግሥት ጨመርኩ ያለው 1 ሺህ ብር ነው ወደ ዶላር ሲቀየር ደመወዙ የሚወድቀው ወደ 150 ዶላር አካባቢ ነው።
ይህ ከፍተኛ ጫና፣ የመንግሥት ሰራተኛውን ወደ ልመና፣ ወደ ጎዳና እያስወጣው እንደሆነ መሸፈን በማንችልበት ሁኔታ ዘገባዎች እየወጡ ነው።
ስለዚህ ይህን በስነስርዓት address በሚያደርግ መንገድ የደመወዝ ማስተካከያው መስተካከል ነበረበት። ጭማሪውም ለዛ ትኩረት መስጠት ነበረበት።
ሌላው የ281.5 ቢሊዮን ተጨማሪ ታክስ raise በማድረግ ይሄን 532 ቢሊዮን ተጨማሪ በጀት ለመሸፈን ከሚደረገው ውስጥ አንደኛው ታክሱ ነው።
ይህ ከፍተኛ የታክስ ጫና (burden) ነጋዴው ላይ የሚጭን ነው። ነጋዴው ላይ ከፍተኛ የታክስ ጫና እየፈጠረ ነው። የንግዱ ማህበረሰብን ከፍተኛ confusion (መደናገር) ውስጥ እየተከተተው ነው።
የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው ጋር ተያይዞ ቀድሞውኑ shock ውስጥ ነው ቢዝነሱ ፤ ብዙ ነጋዴዎች confusion ውስጥ እንደገቡ ይናገራሉ ከዛ ላይ ተጨማሪ confusion እና ተጨማሪ መደናገጥ እንዲሁም shock የሚፈጥር ነው ይሄ እንዴት ታስቦ ነው ?
መንግሥት fair በሆነ መንገድ ከከፍተኛ ታክስ ከፋዩ ላይ ከሚደበቁትን፣ የታክስ ሆሎችን ተጠቅመው የሚሰወሩትን እሱን መሰብሰብ አለበት በእርግጠኝነት ፤ ግን ደግሞ ከአቅም በላይ የሆነውን የመንግሥት spending compensate ለማድረግ ሲባል የታክስ ጫናውን ከአቅም በላይ መለጠጥ በንግድ እንቅስቃሴው ላይ በተለይ በሀገር ውስጥ የንግድ እንቅስቃሴ ላይ ያለው ችግር በደንብ ተገምግሟል ? የሚኒስትሮች ም/ቤት ይሄን እንዴት አይቶት ነው ?
ሌው ጭማሪው 532 ቢሊዮኑ በዋነኝነት ለዕዳ ክፍያ፣ ለማህበራዊ ድጎማ ፣ ለደመወዝ ጭማሪ እንደሚውል ነው የተገለጸው።
ባለፈው 971 ቢሊዮኑ በጀቱ ሲፀድቅ አሁንም የካፒታል ፕሮጀክቶችን ጉዳይ አንስቼ ነበር። መንግሥት literally ትቶታል።
- አዲስ መንገድ
- አዲስ ግድብ
- አዲስ ዩኒቨርሲቲ
- አዲስ ሆስፒታል ... አዳዲስ መሰረተ ልማቶችን መተው የሚታየው አሁን በተጨመረው 582 ቢሊዮን ውስጥ 90 ቢሊዮን ብቻ የካፒታል ፕሮጀክት ማሻሻያ ብቻ ነው የተካተተው።
ሌላው ነገር የለም። already እያልን ያለነው ኮሪደር ልማት ብቻ እንስራ ነው። እንደዚህ ሆኖ ሀገር እንዴት ሊለማ ይችላል ? መሰረታዊ የሚባሉ የ irrigation development ፣ ግድቦች ላይ ፣ አገር አቋራጭ መንገዶች ላይ፣ ፈጣን መንገዶች ላይ ፣ የኃይል ተቋማት ላይ፣ ሆስፒታሎች ፣ ዩኒቨርሲቲዎች ላይ እንዲህ አይነት critical የሆኑ የህዝብ መሰረተ ልማቶች ላይ በጀታችንን ካላዋልነው አሁንም ዞሮ ዞሮ የማብለጭለጭ አይነት ልማት structurally ምንም ለውጥ የማያመጣ ልማት ላይ ነው እንዳለ ገንዘባችንን ፈሰስ እያደረግን ያለነው። እዚህ ላይ ስጋት አለኝ።
መሰረታዊ የሚባሉ investment ላይ መንግሥት ውጪውን ቅድሚያ መስጠት አለበት። "
#TikvahEthiopia #ደመወዝ #ዶክተርደሳለኝጫኔ
@tikvahethiopia
" ... የውጭ ምንዛሬ ለውጡ in in terms of Dollar ያመጣውን ለውጥ ሊያካክስ የሚችል የደመወዝ ጭማሪ መጨመር ነበረበት " - ደሳለኝ ጫኔ (ዶ/ር)
🔴 " አንድ ደመወዝተኛ በውጭ ምንዛሬ ስናሰላው ያገኝ የነበረው ገቢ በዶላር ከ50% በላይ እንዲቀነስ ተደርጓል !! "
የህ/ተ/ም/ቤት አባሉና የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) ተወካዩ ደሳለኝ ጫኔ (ዶ/ር) በተጨማሪ በጀቱ ዙሪያ ስጋቶች እንዳላቸው ገልጸዋል።
የማክሮ ኢኮኖሚ እና ፊስካል ማዕቀፍ ማሻሻያው ሀገራዊ ውጥቅጥ ውስጥ እንዳስገባን በግልጽ እንደሚታይ ተናግረው ይሄ በጀት እሱን ምን ያህል አ
ተደራሽ ያደርጋል ? ሲሉ ጠይቀዋል።
ከዚህ ባለፈም ደሳለኝ (ዶ/ር) ፤ ስለ ኑሮ ውድነት ፣ ስለሰራተኞች የደመወዝ ጭማሪ ፣ በጀቱን ለመሸፈን ስለሚጣል ግብር አንስተው ጠይቀዋል ፤ ሃሳባቸውን አካፍለዋል።
ምን አሉ ?
" በኑሮ ውድነት ላይ / ቋሚ ደመወዝተኛ በሆነው አካል ላይ የውጭ ምንዛሬው (Foreign exchange) ለውጡ የፈጠረው ጫና አለ።
አንድ ደመወዝተኛ በውጭ ምንዛሬ ስናሰላው ያገኝ የነበረው ገቢ በዶላር ከ50% በላይ እንዲቀነስ ተደርጓል ፤ በውጭ ምንዛሬው ለውጥ ምክንያት።
መንግሥት የደመወዝ ማሻሻያ በተለይ ዝቅተኛ ገቢ ያላቸውን ተቀጣሪዎችን ደመወዝ ማሻሻያ አድርጊያለሁ ቢልም አብዛኛው ደመወዝተኛ ከ1 ሺህ ብር እና ከ2 ሺህ ብር በላይ ጭማሪ አልተደረገለትም። ስለዚህ እነዚህ የማህበረሰብ ክፍሎች ኑሯቸውን እንዴት እንዲመሩ ታስቦ ነው ?
በእኔ በኩል ቢያንስ መንግሥት ሌሎች የmarket variables ትቶ የውጭ ምንዛሬ ለውጡ in in terms of Dollar ያመጣውን ለውጥ ሊያካክስ የሚችል ጭማሪ መጨመር ነበረበት።
አንድ የ12 ሺህ ብር ደመወዝተኛ ከምንዛሬ ለውጡ በፊት ወደ 300 እስከ 350 ዶላር አካባቢ ያገኝ ነበር አሁን መንግሥት ጨመርኩ ያለው 1 ሺህ ብር ነው ወደ ዶላር ሲቀየር ደመወዙ የሚወድቀው ወደ 150 ዶላር አካባቢ ነው።
ይህ ከፍተኛ ጫና፣ የመንግሥት ሰራተኛውን ወደ ልመና፣ ወደ ጎዳና እያስወጣው እንደሆነ መሸፈን በማንችልበት ሁኔታ ዘገባዎች እየወጡ ነው።
ስለዚህ ይህን በስነስርዓት address በሚያደርግ መንገድ የደመወዝ ማስተካከያው መስተካከል ነበረበት። ጭማሪውም ለዛ ትኩረት መስጠት ነበረበት።
ሌላው የ281.5 ቢሊዮን ተጨማሪ ታክስ raise በማድረግ ይሄን 532 ቢሊዮን ተጨማሪ በጀት ለመሸፈን ከሚደረገው ውስጥ አንደኛው ታክሱ ነው።
ይህ ከፍተኛ የታክስ ጫና (burden) ነጋዴው ላይ የሚጭን ነው። ነጋዴው ላይ ከፍተኛ የታክስ ጫና እየፈጠረ ነው። የንግዱ ማህበረሰብን ከፍተኛ confusion (መደናገር) ውስጥ እየተከተተው ነው።
የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው ጋር ተያይዞ ቀድሞውኑ shock ውስጥ ነው ቢዝነሱ ፤ ብዙ ነጋዴዎች confusion ውስጥ እንደገቡ ይናገራሉ ከዛ ላይ ተጨማሪ confusion እና ተጨማሪ መደናገጥ እንዲሁም shock የሚፈጥር ነው ይሄ እንዴት ታስቦ ነው ?
መንግሥት fair በሆነ መንገድ ከከፍተኛ ታክስ ከፋዩ ላይ ከሚደበቁትን፣ የታክስ ሆሎችን ተጠቅመው የሚሰወሩትን እሱን መሰብሰብ አለበት በእርግጠኝነት ፤ ግን ደግሞ ከአቅም በላይ የሆነውን የመንግሥት spending compensate ለማድረግ ሲባል የታክስ ጫናውን ከአቅም በላይ መለጠጥ በንግድ እንቅስቃሴው ላይ በተለይ በሀገር ውስጥ የንግድ እንቅስቃሴ ላይ ያለው ችግር በደንብ ተገምግሟል ? የሚኒስትሮች ም/ቤት ይሄን እንዴት አይቶት ነው ?
ሌው ጭማሪው 532 ቢሊዮኑ በዋነኝነት ለዕዳ ክፍያ፣ ለማህበራዊ ድጎማ ፣ ለደመወዝ ጭማሪ እንደሚውል ነው የተገለጸው።
ባለፈው 971 ቢሊዮኑ በጀቱ ሲፀድቅ አሁንም የካፒታል ፕሮጀክቶችን ጉዳይ አንስቼ ነበር። መንግሥት literally ትቶታል።
- አዲስ መንገድ
- አዲስ ግድብ
- አዲስ ዩኒቨርሲቲ
- አዲስ ሆስፒታል ... አዳዲስ መሰረተ ልማቶችን መተው የሚታየው አሁን በተጨመረው 582 ቢሊዮን ውስጥ 90 ቢሊዮን ብቻ የካፒታል ፕሮጀክት ማሻሻያ ብቻ ነው የተካተተው።
ሌላው ነገር የለም። already እያልን ያለነው ኮሪደር ልማት ብቻ እንስራ ነው። እንደዚህ ሆኖ ሀገር እንዴት ሊለማ ይችላል ? መሰረታዊ የሚባሉ የ irrigation development ፣ ግድቦች ላይ ፣ አገር አቋራጭ መንገዶች ላይ፣ ፈጣን መንገዶች ላይ ፣ የኃይል ተቋማት ላይ፣ ሆስፒታሎች ፣ ዩኒቨርሲቲዎች ላይ እንዲህ አይነት critical የሆኑ የህዝብ መሰረተ ልማቶች ላይ በጀታችንን ካላዋልነው አሁንም ዞሮ ዞሮ የማብለጭለጭ አይነት ልማት structurally ምንም ለውጥ የማያመጣ ልማት ላይ ነው እንዳለ ገንዘባችንን ፈሰስ እያደረግን ያለነው። እዚህ ላይ ስጋት አለኝ።
መሰረታዊ የሚባሉ investment ላይ መንግሥት ውጪውን ቅድሚያ መስጠት አለበት። "
#TikvahEthiopia #ደመወዝ #ዶክተርደሳለኝጫኔ
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update
" ሰባቱን ፍርድ ቤት ዋስትና እያስሞሉ ነው። ሌሎቹን ደግሞ ፈተዋቸዋል " - የኮሬ ዞን መምህራን ማኀበር
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ኮሬ ዞን ሳርማሌ ወረዳ የሚገኙ መምህራን ያለፈቃዳቸው ከደመወዛቸው የተቆረጠ ገንዘብ እንዲመለስ በመጠየቃቸው መታሰራቸውን የዞኑና የክልሉ መምህራን ማኀበር ለቲክቫህ ኢትዮጵያ መግለጻቸው የሚታወስ ነው።
በአጠቃላይ ታስረው የነበሩት ከ66 በላይ እንደነበሩ፣ 22 የሚሆኑት መምህራን እስከዛሬ ድረስ በእስር ላይ እንደቆዩ፣ ቀሪዎቹ ግን ሰሞኑን እንደፈቷቸው የዞኑ መምህራን ማኀበር ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ሲገልጽ ነበር።
ከእስራት ያልተፈቱት ቀሪ 22ቱ መምህራን ዛሬ እንዲፈቱ ውይይት እየተደረገ እንደነበርም ማኀበሩ ጠቁሞ ነበር።
የዞኑ ትምህርት መምሪያ በበኩሉ፣ 22ቱ መምህራን እንዲፈቱ ውይይት እየተደረገ መሆኑን ገልጾ፣ ዛሬ እንደሚፈቱ ለቲክቫህ ተናግሯል።
የዞኑ ትምህርት መምሪያ ኃላፊ አቶ ሰርበ አሻግሬ ዛሬ ከሰዓት ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ጋር በነበራቸው ቆይታ ደመወዛቸው የተቆረጠው ተስማምተው ስለመሆኑ ስም ዝርዝር እንዳላቸው ፤ በእስር ላይ ያሉትም እንደሚፈቱ ገልጸዋል።
ጥያቄያቸው ወይ የእነርሱ ይስተካከል ወይ የእኛ ይመለስ የሚል ቢሆን እኔም ከጎናቸው ነኝ ብለዋል።
አቶ ሰርበ አሻግሬ ምን አሉ ?
“ ተስማምተው ከቆረጡ በኋላ እኔም ጋ የመጡት ‘እኛ ቆርጠን ሌሎቹ አልቆረጡም፤ ልክ አይደለም ተነጋገሩ’ ብለው ነበር። እኔም ስልጠና ላይ ስለነበርኩ ነው የቆየነው።
መምህራኑ ይፈታሉ። ማታ ለሁለት በድን ነግሬአለሁ። የመጀመሪያዎቹ ዋና በጥባጮቹ ሰባት ናቸው። ‘እነርሱ ለምን ታሰሩ?’ ብለው የገቡት 15 ናቸው። 15ቱ ከትላንትና ወዲያም ይውጡ ተብሎ ‘አንድ ላይ ነው የምንወጣው’ ብለው ነው።
የእናንት የሁለታችሁ ኬዝ የተለያዬ ስለሆነ ነው። የእናንተ ከፓሊስ ጋር በመጋጨት ነው ውጡ ተብለው እኮ 15ቱ መምህራን አንወጣም ነው እኮ ያሉት።
የታሰሩት 22 መምህራን ናቸው። ሰባቱ ተማሪዎቹን አባረው መምህራንንም የጠበጡ ናቸው። አሁን 66 ታሰሩ የሚለው ውሸት ነው። ሰባቱ መጀመሪያ ተያዙ፤ 15 በኋላ ገቡ። ትላንት ውጡ ተብለው እምቢ ብለው ነው። ዛሬ ይወጣሉ። ” ብለዋል።
መምህራኑ ተፈተዋል ?
የዞኑ መምህራን ማኀበር ሰብሳቢ አቶ ተስፋዬ ጭበጮ ምሽት 12 ሰዓት ገደማ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በገለጹት መሠረት፣ መምህራኑ ከእስር ተፈትተዋል።
የማኀበሩ ሰብሳቢ አቶ ተስፋዬ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል፣ ሰባቱን ፍርድ ቤት ዋስትና እያስሞሉ ነው። ሌሉሎቹን ደግሞ ፈትተዋቸዋል " ሲሉ ተናግረዋል።
ሁሉም ተፈትተዋል ማለት ይቻላል? ስንል ላቀረብነው ጥያቄ በሰጡት ምላሽ፣ "ኦረዲ አዎ ለሰባቱ ብቻ ተያዢ ፈልገው ነው፡፡ ተያዦቹም ኦረዲ እየጨረሱ ናቸው" ብለዋል።
ተደበደቡ የተባሉት ምህራን እስከዛሬ ህክምና አግኝተው ነበር ስንል ላቀረብነው ጥያቄም፣ ሳያገኙ እንደቆዩ የሚታከሙት ገና ካሁን ወዲያ እንደሆነ ምላሽ ሰጥተዋል።
የተፈቱት በምን ተስማምታችሁ ነው ? ለተሚለው የቲክቫህ ጥያቄ የሰጡት ማብራሪያ ደግሞ፣ መምህራኑና ትምህርት መምሪያው እንዲወያዩ፣ መምህራኑ ይመለስ ካሉ ገንዘቡ እንዲመለስ መወሰኑን ነው የገለጹት።
#Update - መምህራኑ ከእስር ተፈተዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
የሕግ ባለሙያውና ጠበቃው ምን ገጠማቸው ?
" ቅስም ይሰብራል ! " - የሕግ ባለሙያና ጠበቃ አንዷለም በውቀቱ
🔴 " ሰፈሩ መፍረሱና መልሶ መልማቱ ላይ ተቃውሞ የሌለውን ኮሚኒቲ በ2 እና በ3 ሰአት እያዋከቡ ማስወጣት መውደቂያውን ሳያውቅ ማሳቀቅ መጨረሻው ይሄ ነው !! "
የሕግ ባለሙያና ጠበቃ የሆኑት አንዷለም በውቀቱ ዛሬ እጅግ ቅስማቸውን የሰበረ ክስተት እንደገጠማቸው ገልጸዋል።
ነገሩ እንዲህ ነው ...
ባለፈው አርብ " ፒኮክ መናፈሻ " አካባቢ አትክልት በማምረት ስራ የሚተዳደሩ ቤተሰቦችና ልጆቻቸው ቢሯቸው ይመጣሉ።
እነዚሁ ነዋሪዎች " ሰፈሩ ለልማት ሊነሳ ነው እየተባለ ነው። ከወላጆቻችን ዘመን ጀምሮ በአካባቢው ለ73 አመታት ቆይተናል። ድንገት ተነሱ ብንባል ምን ይዋጠን!? " ሲሉ ይገልጹላቸዋል።
እሳቸውም " መጀመሪያ የምትሄዱበትን ቦታ ማመቻቸት የመንግስት ግዴታ ነው። ያ ሳይሆን ለማስነሳት እንቅስቃሴ የሚደረግ ቢሆን ለፍርድ ቤት አቤቱታ አቅርቤ እግድ እንዲሰጣችሁ አደርጋለሁ ! " ብለዋቸው ይለያያሉ።
ቅዳሜ ጉዳዩ የሚታይበትን አግባብ ሲያዘጋጁ እንደዋሉ የሚናገሩት የሕግ ባለሙያው ፤ እሁድ ጠዋት ግን ስልክ ይደወልላቸው። በዚህም " ከቤተክርስትያን ስንመለስ ቤታችን እየፈረሰ አገኘነው " ሲሉ እነዚሁ ቤተሰቦች ይነግሯቸዋል።
እሳቸውም ከባልደረባቸው ጋር ወደ ቦታው ሄዱ።
አፅናንተዋቸው " መትረፍ የሚችለውን ለማስቆም እንሞክራለን " ይሏቸዋል።
እስከ ማታ ድረስ ለኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ጨምሮ ለሚመለከታቸው አካላት የህግ አቤቱታዎችን ሲያዘጋጁ ያመሻሉ።
ሰኞ ጠዋት ኮሚኒቲው ህጋዊ የህብረት ስራ ማህበር ያላቸው በመሆኑ በማህበራቸው ስም ሊቀመንበሩ አቶ ዱላ ኑርጋ ውክልና እንዲሰጧቸው እንደተነጋገሩ የሕግ ባለሙያው አመክተዋል።
ትላንት ከሰአት ሊቀመንበሩ የጠበቃ ውክልና ለመስጠት የማህበሩን የመመስረቻ ጽሁፍ ስላጡት ለማክሰኞ ጠዋት እንደሚሰጧቸው ቀጥሮ ይይዛሉ።
ዛሬ ጠዋት ሊቀመንበሩ አቶ ዱላ ከቤታቸው ሲወጡ ግን የማህበሩ አባላት ሰፈር ውስጥ ለማፍረሻ የመጣ ዶዘር ቆሟል።
ሌሎች አባላቶች ውክልና ለመስጠት ውልና ማስረጃ እየጠበቋቸው ነበር።
እንደ ሕግ ባለሙያው ማብራሪያ ሊቀመንበሩ አብራቸው ከቤት የወጡትን ባለቤታቸውን " መጣሁ እየሄድሽ ጠብቂኝ ! " ብለዋቸው ወደ ቤት ይመለሳሉ።
በኃላም በአንዲት ቀጭን ሲባጎ እራሳቸውን አንጠልጥለው እንደተገኘ አስረድተዋል።
የሕግ ባለሙያው ዛሬ ጠዋት 3:00 ላይ አቤቱታውን ይዘው የአቶ ዱላን ስልክ ሲጠብቁ እንደነበር ገልጸዋል። መጨረሻው ግን ፍጹም አሳዛኝ ነው የሆነ።
" ሰፈሩ መፍረሱና መልሶ መልማቱ ላይ ተቃውሞ የሌለውን ኮሚኒቲ በ2 እና በ3 ሰአት እያዋከቡ ማስወጣት መውደቂያውን ሳያውቅ ማሳቀቅ መጨረሻው ይሄ ነው " ሲሉ የሕግ ባለሙያው ሁኔታውን በሀዘን ገልጸዋል።
" አቶ ዱላ ለ20 አመት ያህል በሊቀመንበርነት ያገለገሉትን ከ70 አመት በላይ በአንድ ቦታ የቆየውን ለፍቶ አዳሪ ማህበረሰብ ' ፌይል አደርጌያቸዋለሁ ' ብለው እራሳቸውን አጥፍተዋል " ያሉት የሕግ ባለሙያው " እኔም ያንን ኮሚኒቲ ፌይል አድርጌዋለሁ። ትላንት አቤቱታውን ባስገባ ምናልባት ሊቀመንበሩ ከውሳኔው ይቆጠብ ይሆን?! ከጠዋት ጀምሮ በሰቀቀን ውስጥ ነኝ! ቀብራቸው ነገ ይፈጸማል! ነፍሳቸውን ፈጣሪ ይቀበላት!! " ሲሉ ቃላቸውን ደምድመዋል።
#AddisAbaba
@tikvahethiopia
" ቅስም ይሰብራል ! " - የሕግ ባለሙያና ጠበቃ አንዷለም በውቀቱ
🔴 " ሰፈሩ መፍረሱና መልሶ መልማቱ ላይ ተቃውሞ የሌለውን ኮሚኒቲ በ2 እና በ3 ሰአት እያዋከቡ ማስወጣት መውደቂያውን ሳያውቅ ማሳቀቅ መጨረሻው ይሄ ነው !! "
የሕግ ባለሙያና ጠበቃ የሆኑት አንዷለም በውቀቱ ዛሬ እጅግ ቅስማቸውን የሰበረ ክስተት እንደገጠማቸው ገልጸዋል።
ነገሩ እንዲህ ነው ...
ባለፈው አርብ " ፒኮክ መናፈሻ " አካባቢ አትክልት በማምረት ስራ የሚተዳደሩ ቤተሰቦችና ልጆቻቸው ቢሯቸው ይመጣሉ።
እነዚሁ ነዋሪዎች " ሰፈሩ ለልማት ሊነሳ ነው እየተባለ ነው። ከወላጆቻችን ዘመን ጀምሮ በአካባቢው ለ73 አመታት ቆይተናል። ድንገት ተነሱ ብንባል ምን ይዋጠን!? " ሲሉ ይገልጹላቸዋል።
እሳቸውም " መጀመሪያ የምትሄዱበትን ቦታ ማመቻቸት የመንግስት ግዴታ ነው። ያ ሳይሆን ለማስነሳት እንቅስቃሴ የሚደረግ ቢሆን ለፍርድ ቤት አቤቱታ አቅርቤ እግድ እንዲሰጣችሁ አደርጋለሁ ! " ብለዋቸው ይለያያሉ።
ቅዳሜ ጉዳዩ የሚታይበትን አግባብ ሲያዘጋጁ እንደዋሉ የሚናገሩት የሕግ ባለሙያው ፤ እሁድ ጠዋት ግን ስልክ ይደወልላቸው። በዚህም " ከቤተክርስትያን ስንመለስ ቤታችን እየፈረሰ አገኘነው " ሲሉ እነዚሁ ቤተሰቦች ይነግሯቸዋል።
እሳቸውም ከባልደረባቸው ጋር ወደ ቦታው ሄዱ።
አፅናንተዋቸው " መትረፍ የሚችለውን ለማስቆም እንሞክራለን " ይሏቸዋል።
እስከ ማታ ድረስ ለኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ጨምሮ ለሚመለከታቸው አካላት የህግ አቤቱታዎችን ሲያዘጋጁ ያመሻሉ።
ሰኞ ጠዋት ኮሚኒቲው ህጋዊ የህብረት ስራ ማህበር ያላቸው በመሆኑ በማህበራቸው ስም ሊቀመንበሩ አቶ ዱላ ኑርጋ ውክልና እንዲሰጧቸው እንደተነጋገሩ የሕግ ባለሙያው አመክተዋል።
ትላንት ከሰአት ሊቀመንበሩ የጠበቃ ውክልና ለመስጠት የማህበሩን የመመስረቻ ጽሁፍ ስላጡት ለማክሰኞ ጠዋት እንደሚሰጧቸው ቀጥሮ ይይዛሉ።
ዛሬ ጠዋት ሊቀመንበሩ አቶ ዱላ ከቤታቸው ሲወጡ ግን የማህበሩ አባላት ሰፈር ውስጥ ለማፍረሻ የመጣ ዶዘር ቆሟል።
ሌሎች አባላቶች ውክልና ለመስጠት ውልና ማስረጃ እየጠበቋቸው ነበር።
እንደ ሕግ ባለሙያው ማብራሪያ ሊቀመንበሩ አብራቸው ከቤት የወጡትን ባለቤታቸውን " መጣሁ እየሄድሽ ጠብቂኝ ! " ብለዋቸው ወደ ቤት ይመለሳሉ።
በኃላም በአንዲት ቀጭን ሲባጎ እራሳቸውን አንጠልጥለው እንደተገኘ አስረድተዋል።
የሕግ ባለሙያው ዛሬ ጠዋት 3:00 ላይ አቤቱታውን ይዘው የአቶ ዱላን ስልክ ሲጠብቁ እንደነበር ገልጸዋል። መጨረሻው ግን ፍጹም አሳዛኝ ነው የሆነ።
" ሰፈሩ መፍረሱና መልሶ መልማቱ ላይ ተቃውሞ የሌለውን ኮሚኒቲ በ2 እና በ3 ሰአት እያዋከቡ ማስወጣት መውደቂያውን ሳያውቅ ማሳቀቅ መጨረሻው ይሄ ነው " ሲሉ የሕግ ባለሙያው ሁኔታውን በሀዘን ገልጸዋል።
" አቶ ዱላ ለ20 አመት ያህል በሊቀመንበርነት ያገለገሉትን ከ70 አመት በላይ በአንድ ቦታ የቆየውን ለፍቶ አዳሪ ማህበረሰብ ' ፌይል አደርጌያቸዋለሁ ' ብለው እራሳቸውን አጥፍተዋል " ያሉት የሕግ ባለሙያው " እኔም ያንን ኮሚኒቲ ፌይል አድርጌዋለሁ። ትላንት አቤቱታውን ባስገባ ምናልባት ሊቀመንበሩ ከውሳኔው ይቆጠብ ይሆን?! ከጠዋት ጀምሮ በሰቀቀን ውስጥ ነኝ! ቀብራቸው ነገ ይፈጸማል! ነፍሳቸውን ፈጣሪ ይቀበላት!! " ሲሉ ቃላቸውን ደምድመዋል።
#AddisAbaba
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ወጣቶቻችን😥 " ከአንድ ወረዳ ብቻ ከ2 ሺህ በላይ ወጣቶች በህገ-ወጥ መንገድ ተሰደው 200 ያህሉ ለህልፈት ተዳርገዋል " - የእገላ ወረዳ አስተዳደር እገላ ከትግራይ ማእከላዊ ዞን ወረዳዎች አንድዋ ስትሆን የኤርትራዋ ፆሮና ጎረቤት ናት። ከትግራዩ ጦርነቱ በፊት የወረዳዋ ዋና ከተማ በሆነችው ገርሁስርናይ በቀን በርካታ የኤርትራ ስደተኞች በህገወጥ መንገድ ወደ ኢትዮጵያ ትግራይ ክልል የሚተላለፉባት ነበረች።…
#ወጣቶቻችን😭
" በሶስት ወራት ብቻ ከ6,600 በላይ ወጣቶች በህገ-ወጥ መንገድ ተሰድዋል !! " - የትግራይ የወጣቶች ጉዳይ ቢሮ
በትግራይ ክልል ከተሞች በሚገኙ አውራ መንገዶች " ልጄ በህገ-ወጥ መንገድ ወደ ስደት ሲሄድ በአጋቾች ተይዞ ይህንን ብር ክፈል ፣ ካልከፈልክ ትገደላለህ ብለውኛል እርዱኝ " የሚሉ በትልቅ ባነር በተቀመጠ የወጣቶች ፎቶ አስደግፈው እርዳታ የሚለሙኑ ወላጆች ተበራክተዋል።
ከነዚሁ ወላጆች የአክሱም ከተማ ነዋሪዋ ወ/ሮ ኣስካለ ውብኣንተ አንድዋ ሲሆኑ ፤ ይጦረኛል ብለው ኮስኩሰው አስተምረው ያሳደጉት ወንድ ልጃቸው ህገ-ወጥ ስደት የነጠቃቸው እናት ናቸው።
" ልጄ በጦርነቱ ማግስት በአከባቢው የስራ እድል በማጣቱ በህገ-ወጥ መንገድ የተለያዩ ሃገራት ደንበር አቋርጦ ሊብያ ሲደርስ ለሰው ህይወት ቁብ በሌላቸው ሽፍቶ እጅ ወድቆ ቁም ስቅሉን እያሳዩት ነው " ብለዋል።
" አካል ጉዳተኛ ነኝ ፤ ልጄ እኔ እናቱን ለመጦር ዳቦ መጋገሪያ ቤት ከፍቶ የነበረ ቢሆንም ንብረቱ መዘረፉ አናድዶት ነው በህገ-ወጥ መንገድ ወደ ስደት የሄደው " ወ/ሲሉ እኚሁ እናት እንባ እተናነቃቸው ተናግረዋል።
" ልጄ በአጋቾች ቁጥጥር ስር ውሎ ጥዋት እና ማታ በሚደርስበት ገርፋት እየተሰቃየ ሲያናገርኝ የምይዘው የምጨብጠው ይጠፋብኛል ፤ ' የጠየቁኝ ብር ካልተከፈለ ኩላሊቴ ያወጡታል ምን ማድረግ ነው ያለብኝ ? ' ካለኝ ቀንና ሰዓት ጀምሮ አእምሮየ ልክ አይደለም " ብለዋል።
" ልጄ በመጀመሪያው አከባቢ በሙሉ ጤንነት እያለ 1.5 ሚሊዮን ብር እንድከፍል ጠየቁኝ ደጋግመው ደብድበው አካል ጉዳተኛ እና በሽተኛ ካደረጉት በኋላ ግን 300 ሺህ ቀንሰው 1.2 ሚሊዮን ብር ጠይቀውኛል። ይህንን ገቢ ካላደረግኩ ድግሞ እንገድለዋለን ብለውኛል እባካችሁ አርዱኝ " ሲሉ ተማፅነዋል።
ወ/ሮ አስካለ ልጆቻቸው የህገ-ወጥ ስደት ገፋት ቀማሽ ሆኖውባቸው ሌት ተቀን ከሚያለቅሱ በሺህ የሚቆጠሩ የትግራይ እናቶች አንድዋ ናቸው።
እሳቸው ለሚድያ ቃላቸው በሰጡባት ቀን ሰዓትና ደቂቃ ሳይቀር በተለያዩ አቅጣጫዎች በርካታ ወጣቶች በአከባቢያቸው ተስፋ ሰጪ ሁኔታ በማጣት እግራቸው ወደ መራቸው ይሰደዳሉ።
የትግራይ የወጣቶች ጉዳይ ቢሮ ሃላፊ ሓይሽ ስባጋድስ ፣ የህገ-ወጥ ስደቱ ዋና መነሻ የሰራ እና መልካም አስተዳደር እጦት መሆኑ ገልጸዋል።
ወጣቶች በነዚህና ሌሎች ችግሮች ተማረው አደገኛ የሆነውን ስደት በመምረጥ ለተለያዩ አደገኛ ነገሮች እየተጋለጡ እንደሆነ አስረድተዋል።
በቢሮቸው የተካሄደው ዳሰሳ እንደሚያመለክተው ከሓምለ 2016 አስከ መስከረም 2017 ዓ.ም ባሉት ሦስት ወራት ብቻ በክልሉ ማእከላዊ ፣ ምስራቅ እና ሰሜናዊ ምዕራብ ከሚገኙ 11 ወረዳዎች ከ6,600 በላይ ወጣቶች በህገ-ወጥ መንገድ ተሰደዋል ሲሉ ገልጸዋል።
" የትግራይ የፓለቲካ አመራሮች ከገቡበት የስልጣን መቆራቆስ በመውጣት በህገ-ወጥ ስደት ለከፍተኛ አደጋ እና እልቀቂት የተጋለጠውን የወጣቱን ክፍል ለመታደግ ቅድሚያ መስጠት አለባቸው " ብለዋል።
የመረጃው ምንጭ ቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ እና ትግራይ ቴሌቪዥን የህዳር 17/2017 ዓ/ም የዜና ዘገባ ናቸው።
@tikvahethiopia
" በሶስት ወራት ብቻ ከ6,600 በላይ ወጣቶች በህገ-ወጥ መንገድ ተሰድዋል !! " - የትግራይ የወጣቶች ጉዳይ ቢሮ
በትግራይ ክልል ከተሞች በሚገኙ አውራ መንገዶች " ልጄ በህገ-ወጥ መንገድ ወደ ስደት ሲሄድ በአጋቾች ተይዞ ይህንን ብር ክፈል ፣ ካልከፈልክ ትገደላለህ ብለውኛል እርዱኝ " የሚሉ በትልቅ ባነር በተቀመጠ የወጣቶች ፎቶ አስደግፈው እርዳታ የሚለሙኑ ወላጆች ተበራክተዋል።
ከነዚሁ ወላጆች የአክሱም ከተማ ነዋሪዋ ወ/ሮ ኣስካለ ውብኣንተ አንድዋ ሲሆኑ ፤ ይጦረኛል ብለው ኮስኩሰው አስተምረው ያሳደጉት ወንድ ልጃቸው ህገ-ወጥ ስደት የነጠቃቸው እናት ናቸው።
" ልጄ በጦርነቱ ማግስት በአከባቢው የስራ እድል በማጣቱ በህገ-ወጥ መንገድ የተለያዩ ሃገራት ደንበር አቋርጦ ሊብያ ሲደርስ ለሰው ህይወት ቁብ በሌላቸው ሽፍቶ እጅ ወድቆ ቁም ስቅሉን እያሳዩት ነው " ብለዋል።
" አካል ጉዳተኛ ነኝ ፤ ልጄ እኔ እናቱን ለመጦር ዳቦ መጋገሪያ ቤት ከፍቶ የነበረ ቢሆንም ንብረቱ መዘረፉ አናድዶት ነው በህገ-ወጥ መንገድ ወደ ስደት የሄደው " ወ/ሲሉ እኚሁ እናት እንባ እተናነቃቸው ተናግረዋል።
" ልጄ በአጋቾች ቁጥጥር ስር ውሎ ጥዋት እና ማታ በሚደርስበት ገርፋት እየተሰቃየ ሲያናገርኝ የምይዘው የምጨብጠው ይጠፋብኛል ፤ ' የጠየቁኝ ብር ካልተከፈለ ኩላሊቴ ያወጡታል ምን ማድረግ ነው ያለብኝ ? ' ካለኝ ቀንና ሰዓት ጀምሮ አእምሮየ ልክ አይደለም " ብለዋል።
" ልጄ በመጀመሪያው አከባቢ በሙሉ ጤንነት እያለ 1.5 ሚሊዮን ብር እንድከፍል ጠየቁኝ ደጋግመው ደብድበው አካል ጉዳተኛ እና በሽተኛ ካደረጉት በኋላ ግን 300 ሺህ ቀንሰው 1.2 ሚሊዮን ብር ጠይቀውኛል። ይህንን ገቢ ካላደረግኩ ድግሞ እንገድለዋለን ብለውኛል እባካችሁ አርዱኝ " ሲሉ ተማፅነዋል።
ወ/ሮ አስካለ ልጆቻቸው የህገ-ወጥ ስደት ገፋት ቀማሽ ሆኖውባቸው ሌት ተቀን ከሚያለቅሱ በሺህ የሚቆጠሩ የትግራይ እናቶች አንድዋ ናቸው።
እሳቸው ለሚድያ ቃላቸው በሰጡባት ቀን ሰዓትና ደቂቃ ሳይቀር በተለያዩ አቅጣጫዎች በርካታ ወጣቶች በአከባቢያቸው ተስፋ ሰጪ ሁኔታ በማጣት እግራቸው ወደ መራቸው ይሰደዳሉ።
የትግራይ የወጣቶች ጉዳይ ቢሮ ሃላፊ ሓይሽ ስባጋድስ ፣ የህገ-ወጥ ስደቱ ዋና መነሻ የሰራ እና መልካም አስተዳደር እጦት መሆኑ ገልጸዋል።
ወጣቶች በነዚህና ሌሎች ችግሮች ተማረው አደገኛ የሆነውን ስደት በመምረጥ ለተለያዩ አደገኛ ነገሮች እየተጋለጡ እንደሆነ አስረድተዋል።
በቢሮቸው የተካሄደው ዳሰሳ እንደሚያመለክተው ከሓምለ 2016 አስከ መስከረም 2017 ዓ.ም ባሉት ሦስት ወራት ብቻ በክልሉ ማእከላዊ ፣ ምስራቅ እና ሰሜናዊ ምዕራብ ከሚገኙ 11 ወረዳዎች ከ6,600 በላይ ወጣቶች በህገ-ወጥ መንገድ ተሰደዋል ሲሉ ገልጸዋል።
" የትግራይ የፓለቲካ አመራሮች ከገቡበት የስልጣን መቆራቆስ በመውጣት በህገ-ወጥ ስደት ለከፍተኛ አደጋ እና እልቀቂት የተጋለጠውን የወጣቱን ክፍል ለመታደግ ቅድሚያ መስጠት አለባቸው " ብለዋል።
የመረጃው ምንጭ ቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ እና ትግራይ ቴሌቪዥን የህዳር 17/2017 ዓ/ም የዜና ዘገባ ናቸው።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ግብፅ ? ግብፅ፣ ሶማሊያን እያስታጠቀች ነው። ሶማሊያ የተለያዩ ከባድ የጦር መሳሪያዎች ከግብፅ እንደተሰጧትና ተጨማሪ መሳሪያዎችን በቀጣይነት እንደምትጠብቅ አንድ የሶማሊያ ከፍተኛ ባለሥልጣን ተናግረዋል። ስማቸው ሳይጠቀስ ለቢቢሲ ሶማሊኛ የተናገሩ ባለሥልጣን ባለፉት ቀናት በመርከብ ተጭነው ወደ ሞቃዲሾ ወደብ የደረሱት የጦር መሳሪያዎች እንዳሉ ጠቁመዋል። እነዚህ መሳሪያዎች የሶማሊያ መንግሥት ጦር የሚታጠቃቸው…
" ... ግብፆች መርዳት ከፈለጉ ለምን ፍልስጤሞችንና ሌሎች ዓረብ አገሮችን አይረዱም ? " - አምባሳደር አብዱላሂ መሐመድ ዱአሌ
አምባሳደር አብዱላሂ መሐመድ ዱአሌ ፤ የሶማሌላንድ የአፍሪካ ኅብረትና የኢጋድ ልዩ መልዕክተኛ ግብፅ በቀጣናው ስለምታደርገው እንቅስቃሴ ምን አሉ ?
(ለሪፖርተር ጋዜጣ ከተናገሩት የተወሰደ)
" የግብፅ እንቅስቃሴ በግልጽ ጣልቃ ገብነት ነው፡፡ ግብፅ ወደ ሶማሊያ መሣሪያ እያሠራጨች ነው፡፡
በመሣሪያ እየታመሰ ባለ ቀጣና ውስጥ ሌላ መሣሪያ እንዲመጣ አንፈልግም፣ በሶማሊያ እያንዳንዱ ግዛት መሣሪያ ተበትኗል፡፡ ነገር ግን ሶማሊያውያን መሣሪያ የተራቡ አይደሉም፡፡
ሶማሊያን ለመጠበቅ በርካታ አገሮች ማለትም ኢትዮጵያ፣ ብሩንዲ፣ ኡጋንዳና ሌሎች ልጆቻቸውን ገብረዋል፣ ውድ ቤተሰቦቻቸውን፣ ገብረዋል፡፡ አሁን በድንገት ግብፅ መጥታ አለሁላችሁ ብትል አይሠራም፡፡
ሶማሊያ የምትባል አገር መጀመሪያ የራሷን የቤት ሥራ ትሥራ፣ ቤቷን ትጠብቅ፡፡
ሶማሌላንዶች ከሕዝብ ገንዘብ ሰብስበን በጀት መድበን አገር እያስተዳደርን ያለን ሰላማዊ አገር ነን፡፡ ከማንም ለምነን አይደለም አገር የምንመራው፡፡
ሶማሊያን ተመልከት ማን እንደሚደግፋቸው፡፡ ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ፣ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅትና ዕርዳታ ሰጪ ድርጅቶች ናቸው፡፡
የሶማሊያ ፕሬዚዳንት ሐሰን ሼክ ኢትዮጵያንም ሶማሌላንድንም ከማን ጋር ስምምነት መፈጸም እንዳለባቸው ሊነግሯቸው አይገባም፡፡
ግብፆች መርዳት ከፈለጉ ለምን ፍልስጤሞችንና ሌሎች ዓረብ አገሮችን አይረዱም ? አሁን ግብፅ መሣሪያና ወታደር በአውሮፕላን እየጫኑ እያመጡ ነው፡፡
ይህ የግብጽ ጣልቃ ገብነት ትልቅ ሥጋት ነው፡፡ ለሶማሌላንድ ጭምር አደጋ ነው፡፡ ይህን ሥጋት ለአፍሪካ ኅብረትና ለዓለም አቀፍ ማኅበረሰቡ፣ እንዲሁም ለኢጋድ አሳውቀናል፡፡ "
#Somaliland #Egypt
@tikvahethiopia
አምባሳደር አብዱላሂ መሐመድ ዱአሌ ፤ የሶማሌላንድ የአፍሪካ ኅብረትና የኢጋድ ልዩ መልዕክተኛ ግብፅ በቀጣናው ስለምታደርገው እንቅስቃሴ ምን አሉ ?
(ለሪፖርተር ጋዜጣ ከተናገሩት የተወሰደ)
" የግብፅ እንቅስቃሴ በግልጽ ጣልቃ ገብነት ነው፡፡ ግብፅ ወደ ሶማሊያ መሣሪያ እያሠራጨች ነው፡፡
በመሣሪያ እየታመሰ ባለ ቀጣና ውስጥ ሌላ መሣሪያ እንዲመጣ አንፈልግም፣ በሶማሊያ እያንዳንዱ ግዛት መሣሪያ ተበትኗል፡፡ ነገር ግን ሶማሊያውያን መሣሪያ የተራቡ አይደሉም፡፡
ሶማሊያን ለመጠበቅ በርካታ አገሮች ማለትም ኢትዮጵያ፣ ብሩንዲ፣ ኡጋንዳና ሌሎች ልጆቻቸውን ገብረዋል፣ ውድ ቤተሰቦቻቸውን፣ ገብረዋል፡፡ አሁን በድንገት ግብፅ መጥታ አለሁላችሁ ብትል አይሠራም፡፡
ሶማሊያ የምትባል አገር መጀመሪያ የራሷን የቤት ሥራ ትሥራ፣ ቤቷን ትጠብቅ፡፡
ሶማሌላንዶች ከሕዝብ ገንዘብ ሰብስበን በጀት መድበን አገር እያስተዳደርን ያለን ሰላማዊ አገር ነን፡፡ ከማንም ለምነን አይደለም አገር የምንመራው፡፡
ሶማሊያን ተመልከት ማን እንደሚደግፋቸው፡፡ ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ፣ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅትና ዕርዳታ ሰጪ ድርጅቶች ናቸው፡፡
የሶማሊያ ፕሬዚዳንት ሐሰን ሼክ ኢትዮጵያንም ሶማሌላንድንም ከማን ጋር ስምምነት መፈጸም እንዳለባቸው ሊነግሯቸው አይገባም፡፡
ግብፆች መርዳት ከፈለጉ ለምን ፍልስጤሞችንና ሌሎች ዓረብ አገሮችን አይረዱም ? አሁን ግብፅ መሣሪያና ወታደር በአውሮፕላን እየጫኑ እያመጡ ነው፡፡
ይህ የግብጽ ጣልቃ ገብነት ትልቅ ሥጋት ነው፡፡ ለሶማሌላንድ ጭምር አደጋ ነው፡፡ ይህን ሥጋት ለአፍሪካ ኅብረትና ለዓለም አቀፍ ማኅበረሰቡ፣ እንዲሁም ለኢጋድ አሳውቀናል፡፡ "
#Somaliland #Egypt
@tikvahethiopia
ዶዳይ ማኑፋክቸሪንግ !
ታላቅ ቅናሽ እስከ ህዳር 22 ብቻ የሚቆይ
በአንድ ጊዜ ቻርጅ እስከ 150ኪሜ መጓዝ የሚችሉ
• ለሙሉ ቻርጅ 10ብር ብቻ ሚጠይቁ
• 150ኪሎ ተሸክመው በሰአት እስከ 60ኪሜ የሚሄዱ
• ለእለት ተለት ጉዞ ቢሉ ፣ አልያም ለዲሊቨሪ ስራ የሚሆኑ
ዋጋውስ ለምትሉ
• V3 Lite: በ165ሺ
• V3: በ200ሺ
ይፍጠኑ ይሂዱ > ይጎብኙ > ይግዙ!
ለበለጠ መረጃ :📍ሾው ሩም: ጎፋ ገብርኤል
📲 ስልክ: 0938022222
🌐 ethiopia.dodai.co
• TikTok Page: https://www.tiktok.com/@dodai_et?is_from_webapp=1&sender_device=pc
• Telegram Page: https://t.iss.one/+z09SxQgb6vsyNzU8
ታላቅ ቅናሽ እስከ ህዳር 22 ብቻ የሚቆይ
በአንድ ጊዜ ቻርጅ እስከ 150ኪሜ መጓዝ የሚችሉ
• ለሙሉ ቻርጅ 10ብር ብቻ ሚጠይቁ
• 150ኪሎ ተሸክመው በሰአት እስከ 60ኪሜ የሚሄዱ
• ለእለት ተለት ጉዞ ቢሉ ፣ አልያም ለዲሊቨሪ ስራ የሚሆኑ
ዋጋውስ ለምትሉ
• V3 Lite: በ165ሺ
• V3: በ200ሺ
ይፍጠኑ ይሂዱ > ይጎብኙ > ይግዙ!
ለበለጠ መረጃ :📍ሾው ሩም: ጎፋ ገብርኤል
📲 ስልክ: 0938022222
🌐 ethiopia.dodai.co
• TikTok Page: https://www.tiktok.com/@dodai_et?is_from_webapp=1&sender_device=pc
• Telegram Page: https://t.iss.one/+z09SxQgb6vsyNzU8
#ነቀምቴ
ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ በኦሮሚያ ክልል ነቀምቴ ከተማ የ4G አገልግሎት አስጀመረ።
ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ አገልግሎቱት ማስጀመሩን ከመግለጹ ጋር አያይዞ ለሃይስኩል ተማሪዎች የላፕቶፕና የራውተር ስጦታ ማበርከቱን ገልጿል።
በዚሁ መርሃ ግብር የተገኙት የከተማዋ አካላት፣ የኔቶርክ አገልግሎቱ መዘርጋት ለማህበረሰቡ ከፍተኛ ጥቅም እንዳለው በመግለጽ፣ ድርጅቱን አመስግነዋል።
በፕሮግራሙ የተገኘው ቲክቫህ ኢትዮጵያም፣ ከከተማዎች በተጨማሪ አገልሎቱን በገጠር አካባቢዎች ለማድረስ ምን ታቅዷል ? ሲል ለድርጅቱ ጥያቄ አቀርቧል።
ለዚሁ ጥያቄ ምላሽ የሰጡት የድርጅቱ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ዊም ቫንሄልፑት፣ " በነቀምቴ ከተማ አገልግሎቱን አስጀምረናል ፤ ቀጣይ በአሶሳ ከተማ እናስጀምራለን በዚህም 50 በመቶ የሚሆነውን ህዝብ ተጠቃሚ እናደርጋለን " ብለዋል።
ኔትዎርኩን በሁሉም አካባቢዎች ለማዳረስ ከመንግስት የአምስት ዓመት ጊዜ እንደተሰጣቸው፣ አሁን ሁለት ዓመት እንዳስቆጠሩ፣ በቀሪው ሦስት ዓመት 80 በመቶ ለሚሆነው ህዝብ አገልግሎቱን ለማዳረስ እንዳቀዱ ገልጸዋል።
በተለያዩ አካባቢዎች የጸጥታ ችግሮች ይስተዋላሉ፣ ይህ አገልግሎቱን ተደራሽ ከማድረግ አንጻር በድርጅትዎ ላይ የደቀነው ፈተና አለ ? ስንል ላቀረበላቸው ጥያቄ በሰጡት ማብራሪያ የጸጥታ ችግር አገልግሎቱን ተደራሽ ለማድረግ ተፅዕኖ እንዳለው አስረድተዋል።
የጸጥታ ችግር ከሚስተዋልባቸው አካባቢዎች መካከል ነቀምቴ ከተማን ጠቅሰው፣ በጸጥታው ችግር ድርጅቱ የአገልግሎት ተጠቃሚ ለማድረግ ሳያስችለው እንደቆዬ፣ “ አሁን አንጻራዊ ሰላም ስላለ ” አገልግሎቱን እንዳስጀመሩ አስረድተዋል።
አገልግሎቱን ለማዳረስ በመቐለ ከተማ ተመሳሳይ ችግር ገጥሟቸው እንደነበር፣ በኋላም እንዳስጀመሩ፣ ከሁለት ሳምንታት በፊት በሶማሌ ክልል በጎዴ የኔቶርክ አገልግሎት እንዳስጀመሩ አስታውሰው፣ አንጻራዊ ሰላም ባለባቸው አካባቢዎች የኔትዎርክ ዝርጋታውን እንደሚቀጥሉ ጠቁመዋል።
የኔትዎርክ አገልግሎቱን ተደራሽ ለማድረግ ፈልጋችሁ ግን ያን እንዳታደርጉ የጸጥታው ችግር የገደባችሁ አካባቢዎች አሉ ? ሲል ቲክቫህ ኢትዮጵያ ላቀረቀው ጥያቄም፣ ዊም አማራ ክልልን ጠቅሰው ምላሽ ሰጥተዋል።
በአማራ ክልል ለኔቶርክ መሠረተ ልማት የሚሆኑ 800 ታውሮች እንዳሏቸው ጠቅሰው፣ የተለያዩ አካባቢዎች ባለው የአስቸጋሪ ጸጥታ ችግር በመቶዎች የሚቆጠሩት ታወሮች ኦፕሬሽናል እንዳልሆኑ፣ በቀጣዩቹ ዓመታት ችግሩ ሲቀረፍ አገልግሎቱን ተደራሽ እንደሚያደርጉ ጠቁመዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ በኦሮሚያ ክልል ነቀምቴ ከተማ የ4G አገልግሎት አስጀመረ።
ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ አገልግሎቱት ማስጀመሩን ከመግለጹ ጋር አያይዞ ለሃይስኩል ተማሪዎች የላፕቶፕና የራውተር ስጦታ ማበርከቱን ገልጿል።
በዚሁ መርሃ ግብር የተገኙት የከተማዋ አካላት፣ የኔቶርክ አገልግሎቱ መዘርጋት ለማህበረሰቡ ከፍተኛ ጥቅም እንዳለው በመግለጽ፣ ድርጅቱን አመስግነዋል።
በፕሮግራሙ የተገኘው ቲክቫህ ኢትዮጵያም፣ ከከተማዎች በተጨማሪ አገልሎቱን በገጠር አካባቢዎች ለማድረስ ምን ታቅዷል ? ሲል ለድርጅቱ ጥያቄ አቀርቧል።
ለዚሁ ጥያቄ ምላሽ የሰጡት የድርጅቱ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ዊም ቫንሄልፑት፣ " በነቀምቴ ከተማ አገልግሎቱን አስጀምረናል ፤ ቀጣይ በአሶሳ ከተማ እናስጀምራለን በዚህም 50 በመቶ የሚሆነውን ህዝብ ተጠቃሚ እናደርጋለን " ብለዋል።
ኔትዎርኩን በሁሉም አካባቢዎች ለማዳረስ ከመንግስት የአምስት ዓመት ጊዜ እንደተሰጣቸው፣ አሁን ሁለት ዓመት እንዳስቆጠሩ፣ በቀሪው ሦስት ዓመት 80 በመቶ ለሚሆነው ህዝብ አገልግሎቱን ለማዳረስ እንዳቀዱ ገልጸዋል።
በተለያዩ አካባቢዎች የጸጥታ ችግሮች ይስተዋላሉ፣ ይህ አገልግሎቱን ተደራሽ ከማድረግ አንጻር በድርጅትዎ ላይ የደቀነው ፈተና አለ ? ስንል ላቀረበላቸው ጥያቄ በሰጡት ማብራሪያ የጸጥታ ችግር አገልግሎቱን ተደራሽ ለማድረግ ተፅዕኖ እንዳለው አስረድተዋል።
የጸጥታ ችግር ከሚስተዋልባቸው አካባቢዎች መካከል ነቀምቴ ከተማን ጠቅሰው፣ በጸጥታው ችግር ድርጅቱ የአገልግሎት ተጠቃሚ ለማድረግ ሳያስችለው እንደቆዬ፣ “ አሁን አንጻራዊ ሰላም ስላለ ” አገልግሎቱን እንዳስጀመሩ አስረድተዋል።
አገልግሎቱን ለማዳረስ በመቐለ ከተማ ተመሳሳይ ችግር ገጥሟቸው እንደነበር፣ በኋላም እንዳስጀመሩ፣ ከሁለት ሳምንታት በፊት በሶማሌ ክልል በጎዴ የኔቶርክ አገልግሎት እንዳስጀመሩ አስታውሰው፣ አንጻራዊ ሰላም ባለባቸው አካባቢዎች የኔትዎርክ ዝርጋታውን እንደሚቀጥሉ ጠቁመዋል።
የኔትዎርክ አገልግሎቱን ተደራሽ ለማድረግ ፈልጋችሁ ግን ያን እንዳታደርጉ የጸጥታው ችግር የገደባችሁ አካባቢዎች አሉ ? ሲል ቲክቫህ ኢትዮጵያ ላቀረቀው ጥያቄም፣ ዊም አማራ ክልልን ጠቅሰው ምላሽ ሰጥተዋል።
በአማራ ክልል ለኔቶርክ መሠረተ ልማት የሚሆኑ 800 ታውሮች እንዳሏቸው ጠቅሰው፣ የተለያዩ አካባቢዎች ባለው የአስቸጋሪ ጸጥታ ችግር በመቶዎች የሚቆጠሩት ታወሮች ኦፕሬሽናል እንዳልሆኑ፣ በቀጣዩቹ ዓመታት ችግሩ ሲቀረፍ አገልግሎቱን ተደራሽ እንደሚያደርጉ ጠቁመዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia