#DStvEthiopia
⚽️አዲስ ነገር ለኳስ አፍቃሪያን...
👉ከሕዳር 16 ጀምሮ ፈጥነው ወደ ሜዳ ስፖርት ፓኬጅ ከፍ ይበሉ! ሁሉንም የአውሮፓ ቻምፒዮንስ ሊግ ጨዋታዎችን፣ የእንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ ፣ ሎችም ዋና ዋና እግር ኳስ እና ምርጥ ምርጥ መዝናኛዎችን ያካተቱ ከ129 በላይ ቻናሎችን በወር በ1699 ብር ብቻ!
ደንብና ሁኔታዎች ተፈፀሚነት አላቸው! ለበለጠ መረጃ
👇
www.dstv.com/en-et
ደንበኝነትዎን ያራዝሙ!
👇
https://bit.ly/48oVhj8
#ሁሉምያለውእኛጋርነው #MedaSport
⚽️አዲስ ነገር ለኳስ አፍቃሪያን...
👉ከሕዳር 16 ጀምሮ ፈጥነው ወደ ሜዳ ስፖርት ፓኬጅ ከፍ ይበሉ! ሁሉንም የአውሮፓ ቻምፒዮንስ ሊግ ጨዋታዎችን፣ የእንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ ፣ ሎችም ዋና ዋና እግር ኳስ እና ምርጥ ምርጥ መዝናኛዎችን ያካተቱ ከ129 በላይ ቻናሎችን በወር በ1699 ብር ብቻ!
ደንብና ሁኔታዎች ተፈፀሚነት አላቸው! ለበለጠ መረጃ
👇
www.dstv.com/en-et
ደንበኝነትዎን ያራዝሙ!
👇
https://bit.ly/48oVhj8
#ሁሉምያለውእኛጋርነው #MedaSport
TIKVAH-ETHIOPIA
#ጥንቃቄ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ፥ " ዜጎች በሕገ ወጥ ደላሎች ማታለያ ወደ ማይናማር እና ታይላንድ ከመጓዝ ሊታቀቡ ይገባል " ሲል አሳስቧል። ሕገ ወጥ አዘዋዋሪዎች በይነ መረብን በመጠቀም በርካታ ዜጎች ችግር ላይ እንዲወድቁ ማድረጋቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነብያት ጌታቸው ተናግረዋል። " ዜጎች ባልተረጋገጡ አማላይ ማስታወቂያዎች ጉዳት እየደረሰባቸው ነው " ብለዋል። "…
#ማይናማር🚨
🔴 “ አምልጠን እንኳ ብንወጣ ያመለጠውን ኢትዮጵያዊ ለሚይዙ 500 ዶላር ይከፈላቸዋል። ” -ኢትዮጵያዊያን በማይናማር
🔵 “ ደብድበውት ራሱን አያውቅም ወጣቶች ተሸክመው ሆስፒታል ሲወስዱት የውጪ ዜጋ አናክምም ብለው መለሱት ” - በእንባ የታጀቡ እናት
ሰርተን እንለወጣለን፣ ቤተሰብም እንለውጣለን ብለው ከአገር የወጡ በርካታ ኢትዮጵያዊያን በማይናማር በስቃይ ውስጥ መሆናቸው ከዚህ ቀደም በተደጋጋሚ መገለጻችን አይዘነጋም።
ኢትዮጵያዊያኑ ከሀገር ሲወጡ የተነገራቸውና አሁን ያሉበት ሁኔታ የማይገናኝ ነው።
ጉልበታቸው እየተበዘበዘ ከሆኑም ባሻገር የሚፈጸምባቸው ድብደባና የአካል ጉዳት አሰቃቂ መሆኑን የገፈቱ ቀማሾች ከዚህ ቀደም ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸው ነበር።
የውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር በበኩሉ፣ ኢትዮጵያዊያኑን ወደ አገራቸው ለመመለስ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር እየተየጋገረ መሆኑን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ መግለጹ ይታወሳል።
የኢትዮጵያዊያኖቹ ጉዳይ አሁንስ ከምን ደረሰ ?
በምን ሁኔታ ላይ እንደሚገኙ፣ ያገቷቸው አካላት ካሉበት አገር መንግስት ጋር ያላቸውን ግንኙት…በተመለከተ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ማብራሪያ የጠየቃቸው በማይናማር የሚገኙት ኢትዮጵያዊያን፣ በጣም በከፋ ሁኔታ ውስጥ መሆናቸውን በሀዘን ስሜት ገልጸው፣ የመንግስትን እርዳታ ጠይቀዋል።
በዝርዝር ምን አሉ ?
“ የኢትዮጵያ መንግስት ሙሉ ኃላፊነት ወስዶ ከረዳን ብቻ ነው መውጣት የሚቻለው። የሌሎች አገራት እንዳደረጉት። ነገር ግን የተባልነው ነገር የለም እስካሁን በስቃይ ላይ ነን።
ያለንበት አገር ብዙም የተጠናከረ መንግስት የለውም። እንደሚታወቀው ወታደራዊ መንግስት ነውና። መንግስት ከመንግስት ጋር ተነጋግሮ ሊያስወጣን ከቻለ ብቻ ነው እንጂ።
እንወጣለን በሚል ተስፋ እያደረግን፣ እያለምን ነው እንጂ እስካሁን ምንም የተባልነው ነገር የለም። የኢትዮጵያ መንግስት ጫና ካላደረገ በስተቀር የያዙን ሽፍታዎችና የአገሪቱ መንግስት በጥቅም የተሳሰሩ ናቸውና መውጣት ይከብዳል።
አምልጠን እንኳ ብንወጣ ያመለጠውን ኢትዮጵያዊ ለሚይዙ 500 ዶላር ይከፈላቸዋል። ስለዚህ ተሳክቶልን ብናመልጥ እንኳ የአካባቢው ማህበረሰብ ይዞ አሳልፎ ይሰጠናል።
ሽፍቶቹ በቁጥር ብዙ ባይሆኑም መመሪያ የተሰጣቸው ናቸው። በዬቦታው ተሰራጭተው ነው የሚጠብቁት። ከእገታ ቦታው ወጣ ብለው በእስናይፐር የሚጠብቀ አሉ። በቁጥር ትንሽ ቢሆኑም የተጠናከረ ጥበቃ ላይ ያሉ ሽፍቶች ናቸው የያዙን።
የሚያሰሩን ቻይያዎች ናቸው። ያለነው ማይናማር ነው። ዜጎቹ ግን የቻይና ናቸው። ከአገሪቱ መንግስት ጋር በጥቅም የተሳሰሩ ናቸው። ለዚሁ መንግስት ግብር ይከፍላሁና ነገሩን ከባድ ያደረገው ከመንግስት ጋር የተያያዙ መሆናቸው ነው።
ወታደራዊ መንግስት ነው ያለው። ስለዚህ ከእኛ ከሚሰበሰው ገቢ ውስጥ ለመንግስት ይከፈላል። ለዛም ነው ሽፍቶቹ ደኀንነታቸው ተጠብቆ ሙሉ ድፍረት አግኝተው የሚሰሩት። የሕግ ከለላም አላቸው ነገሩ የተሳሰረ ነው። አጠቃላይ የአገራቱ መንግስት ሁኔታውን ሁሉ ያውቃል።
በስልክ እየደወልን ቤተሰብን ከመጠየቅ በስተቀር የኢትዮጵያ መንግስት ስለመውጣታችን እንዲህ ነው ያለን የሰማነው ነገር የለም። እባካችሁ በሕይወት ድረሱልን ” ሲሉ ተማጽነዋል።
ልጆቻቸው፣ የትዳር አጋሮቻቸው፣ እህትና ወንድሞቻቸው በማይናማር በከፋ ሁኔታ የሚገኙ ቤተሰቦች በበኩላቸው፣ ለወራት በከፍተኛ ጭንቀት ውስጥ እንደሆኑ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
ልጃቸው የታገተባቸው አንዲት እናት እያለቀሱ በሰጡን ቃል፣ “ እኛም በጭንቀት ተሰቃዬን እንዴት አድርጌ እንደምገልጽ አላውቅም ” ሲሉ ጭንቀታቸውን አጋርተዋል።
እኝሁ እናት አክለው ፦
“ ደብድበውት ራሱን አያውቅም ወጣቶች ተሸክመው ሆስፒታል ቢወስዱት 'የውጪ አገር ዜጋ አናክምም ' ብለው መለሱት።
እንደ ዜጋ መንግስት በዚህ ጉዳይ ላይ ጣልቃ መግባት ሲገባው ‘የራሳቸው ጉዳይ’ የተባለ ነው የሚመስለው። በጣም ያሳዝናል ለመናገር በጣም ነው የሚቸግረኝ።
እንደ ወላድ ይጨንቃል። ተቸግረን አሳድገን እንዲህ ሲሆኑ። እንደ ሀገር እኛ ከኡጋንዳ ሀገር በታች ነው እንዴ የኛ ሀገር መንግስት ! እንዲያው ጆሮ ዳባ ብለውን ነው እንጂ።
ስቲል ይሄዳሉ ልጆች ወደ ውጪ አገር። አምባሳደሩን ገብተን የውጪ ጉዳይ ቆንጽላ ጽህፈት ቤት ተሰባስበን አነጋግረን ነበር ከ15 ቀናት በፊት።
ልጆቻችን አካለ ጎደሎ እየሆኑ፣ በሥነ ልቦና እየተሰቃዩ፣ እየተጎዱ ነው ዳግም ሌላ ወጣት እንዳይሄድ ስንል ‘የመንቀሳቀስ መብትን መንፈግ ነው የሚሆነው እኛ እንዴት ብለን እናሳግዳለን ?’ ነው ያሉን ” ሲሉ ገልጸዋል።
ገና የ8 ወር ልጅ ይዘው የቀሩ የትዳር አጋራቸው በማይናማር እንደታገተባቸው የገለጹ ሌላኛዋ እናት በበኩላቸው፣ ባለቤታቸው በከፋ ሁኔታ እንደሚገኝ፣ ልጅ አዝለው ውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር ድረስ ቢሄዱም አጥጋቢ ምላሽ እንዳላገኙ ተናግረዋል።
በዝርዝር ምን አሉ ?
“ ባለቤቴ ማይናማር በስቃይ ውሰጥ ነው። ከሄደ 5 ወራት አስቆጥሯል። ‘የሥራ እድል አለ’ ተብሎ በደላሎች አማካኝነት ነበር ወደ ታይላንድ የሄደው። በሙያው ሐኪም ነው። ከሄደ በኋላ ግን ታይላንድ አይደለም የቀረው ወደ ማይናማር ነው የወሰዱት።
ያለበት ሁኔታ በጣም ከባድ ነው። የጨለማ ክፍል የሚባል አለ፤ ድብደባ አለ። በነገረኝ መሠረት አሰቃቂ ሁኔታ ነው። እኔም መፍትሄ ፍለጋ የውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር ልጅ አዝዬ ጭምር ብዙ ጊዜ ተመላልሻለሁ።
የሚሰጠኝ ምላሽ በራሳቸው ፍላጎት እንደሄዱ፣ በሕገወጥ መንገድ እንደሄዱ ነው። ከሦስት ቀናት በፊትም ሂጀ ነበርና ከታች ያሉት የቀረበውን ቅሬታ ካሳወቁ ከ10 ወራት በላይ እንዳስቆጠረ፣ ግን መፍትሄ እንዳልተገኘለት ነው የነገሩኝ።
‘ ከላይ ያሉት አካላት ናቸው መስራት ያለባቸው ’ ነው ያሉኝ። ጥሩ መልስ የሰጠን የኤምባሲ አካል ግን አላገኘንም። ቤተሰቡ በጭንቀት ውስጥ ነው ያለው። ባለቤቴ ከሄደ በኋላ ኑሮው ከብዶኛል።
ስለእርሱ መጨነቁ፣ የኑሮ ውድነቱ ተደራረቡብኝ። የባለቤቴ ደመወዝ ተቋርጧል። አዲስ አበባ ከተማ ላይ ብቻዬን ልጅ እያሳደኩ ስቃይ ላይ ነኝ።
የኢትዮጵያ መንግስት በደንብ ትኩረት ሰጥቶ ቢሰራበት የማይናማር መንግስት ሊለቃቸው እንደሚችል ባለቤቴ ነገሮኛል። ባለቤቴ ጋር የነበሩ የህንድ አገር ዜጎች ወጥተዋል። መንግስት መፍትሄ ይስጠን ” ሲሉ ተማጽነዋል።
ማይናማር ውስጥ የሚገኙ የታጋች ኢትዮጵያዊያኑ ወላጅች ያቋቋሙት ኮሚቴ በበኩሉ፣ መፍትሄ እየጠየቀ መሆኑን የገለጸ ሲሆን፣ የውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር ምን እየሰራ እንሆነ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ከሰጠው ምላሽ ጋር በቀጣይ ይቀርባል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
🔴 “ አምልጠን እንኳ ብንወጣ ያመለጠውን ኢትዮጵያዊ ለሚይዙ 500 ዶላር ይከፈላቸዋል። ” -ኢትዮጵያዊያን በማይናማር
🔵 “ ደብድበውት ራሱን አያውቅም ወጣቶች ተሸክመው ሆስፒታል ሲወስዱት የውጪ ዜጋ አናክምም ብለው መለሱት ” - በእንባ የታጀቡ እናት
ሰርተን እንለወጣለን፣ ቤተሰብም እንለውጣለን ብለው ከአገር የወጡ በርካታ ኢትዮጵያዊያን በማይናማር በስቃይ ውስጥ መሆናቸው ከዚህ ቀደም በተደጋጋሚ መገለጻችን አይዘነጋም።
ኢትዮጵያዊያኑ ከሀገር ሲወጡ የተነገራቸውና አሁን ያሉበት ሁኔታ የማይገናኝ ነው።
ጉልበታቸው እየተበዘበዘ ከሆኑም ባሻገር የሚፈጸምባቸው ድብደባና የአካል ጉዳት አሰቃቂ መሆኑን የገፈቱ ቀማሾች ከዚህ ቀደም ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸው ነበር።
የውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር በበኩሉ፣ ኢትዮጵያዊያኑን ወደ አገራቸው ለመመለስ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር እየተየጋገረ መሆኑን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ መግለጹ ይታወሳል።
የኢትዮጵያዊያኖቹ ጉዳይ አሁንስ ከምን ደረሰ ?
በምን ሁኔታ ላይ እንደሚገኙ፣ ያገቷቸው አካላት ካሉበት አገር መንግስት ጋር ያላቸውን ግንኙት…በተመለከተ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ማብራሪያ የጠየቃቸው በማይናማር የሚገኙት ኢትዮጵያዊያን፣ በጣም በከፋ ሁኔታ ውስጥ መሆናቸውን በሀዘን ስሜት ገልጸው፣ የመንግስትን እርዳታ ጠይቀዋል።
በዝርዝር ምን አሉ ?
“ የኢትዮጵያ መንግስት ሙሉ ኃላፊነት ወስዶ ከረዳን ብቻ ነው መውጣት የሚቻለው። የሌሎች አገራት እንዳደረጉት። ነገር ግን የተባልነው ነገር የለም እስካሁን በስቃይ ላይ ነን።
ያለንበት አገር ብዙም የተጠናከረ መንግስት የለውም። እንደሚታወቀው ወታደራዊ መንግስት ነውና። መንግስት ከመንግስት ጋር ተነጋግሮ ሊያስወጣን ከቻለ ብቻ ነው እንጂ።
እንወጣለን በሚል ተስፋ እያደረግን፣ እያለምን ነው እንጂ እስካሁን ምንም የተባልነው ነገር የለም። የኢትዮጵያ መንግስት ጫና ካላደረገ በስተቀር የያዙን ሽፍታዎችና የአገሪቱ መንግስት በጥቅም የተሳሰሩ ናቸውና መውጣት ይከብዳል።
አምልጠን እንኳ ብንወጣ ያመለጠውን ኢትዮጵያዊ ለሚይዙ 500 ዶላር ይከፈላቸዋል። ስለዚህ ተሳክቶልን ብናመልጥ እንኳ የአካባቢው ማህበረሰብ ይዞ አሳልፎ ይሰጠናል።
ሽፍቶቹ በቁጥር ብዙ ባይሆኑም መመሪያ የተሰጣቸው ናቸው። በዬቦታው ተሰራጭተው ነው የሚጠብቁት። ከእገታ ቦታው ወጣ ብለው በእስናይፐር የሚጠብቀ አሉ። በቁጥር ትንሽ ቢሆኑም የተጠናከረ ጥበቃ ላይ ያሉ ሽፍቶች ናቸው የያዙን።
የሚያሰሩን ቻይያዎች ናቸው። ያለነው ማይናማር ነው። ዜጎቹ ግን የቻይና ናቸው። ከአገሪቱ መንግስት ጋር በጥቅም የተሳሰሩ ናቸው። ለዚሁ መንግስት ግብር ይከፍላሁና ነገሩን ከባድ ያደረገው ከመንግስት ጋር የተያያዙ መሆናቸው ነው።
ወታደራዊ መንግስት ነው ያለው። ስለዚህ ከእኛ ከሚሰበሰው ገቢ ውስጥ ለመንግስት ይከፈላል። ለዛም ነው ሽፍቶቹ ደኀንነታቸው ተጠብቆ ሙሉ ድፍረት አግኝተው የሚሰሩት። የሕግ ከለላም አላቸው ነገሩ የተሳሰረ ነው። አጠቃላይ የአገራቱ መንግስት ሁኔታውን ሁሉ ያውቃል።
በስልክ እየደወልን ቤተሰብን ከመጠየቅ በስተቀር የኢትዮጵያ መንግስት ስለመውጣታችን እንዲህ ነው ያለን የሰማነው ነገር የለም። እባካችሁ በሕይወት ድረሱልን ” ሲሉ ተማጽነዋል።
ልጆቻቸው፣ የትዳር አጋሮቻቸው፣ እህትና ወንድሞቻቸው በማይናማር በከፋ ሁኔታ የሚገኙ ቤተሰቦች በበኩላቸው፣ ለወራት በከፍተኛ ጭንቀት ውስጥ እንደሆኑ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
ልጃቸው የታገተባቸው አንዲት እናት እያለቀሱ በሰጡን ቃል፣ “ እኛም በጭንቀት ተሰቃዬን እንዴት አድርጌ እንደምገልጽ አላውቅም ” ሲሉ ጭንቀታቸውን አጋርተዋል።
እኝሁ እናት አክለው ፦
“ ደብድበውት ራሱን አያውቅም ወጣቶች ተሸክመው ሆስፒታል ቢወስዱት 'የውጪ አገር ዜጋ አናክምም ' ብለው መለሱት።
እንደ ዜጋ መንግስት በዚህ ጉዳይ ላይ ጣልቃ መግባት ሲገባው ‘የራሳቸው ጉዳይ’ የተባለ ነው የሚመስለው። በጣም ያሳዝናል ለመናገር በጣም ነው የሚቸግረኝ።
እንደ ወላድ ይጨንቃል። ተቸግረን አሳድገን እንዲህ ሲሆኑ። እንደ ሀገር እኛ ከኡጋንዳ ሀገር በታች ነው እንዴ የኛ ሀገር መንግስት ! እንዲያው ጆሮ ዳባ ብለውን ነው እንጂ።
ስቲል ይሄዳሉ ልጆች ወደ ውጪ አገር። አምባሳደሩን ገብተን የውጪ ጉዳይ ቆንጽላ ጽህፈት ቤት ተሰባስበን አነጋግረን ነበር ከ15 ቀናት በፊት።
ልጆቻችን አካለ ጎደሎ እየሆኑ፣ በሥነ ልቦና እየተሰቃዩ፣ እየተጎዱ ነው ዳግም ሌላ ወጣት እንዳይሄድ ስንል ‘የመንቀሳቀስ መብትን መንፈግ ነው የሚሆነው እኛ እንዴት ብለን እናሳግዳለን ?’ ነው ያሉን ” ሲሉ ገልጸዋል።
ገና የ8 ወር ልጅ ይዘው የቀሩ የትዳር አጋራቸው በማይናማር እንደታገተባቸው የገለጹ ሌላኛዋ እናት በበኩላቸው፣ ባለቤታቸው በከፋ ሁኔታ እንደሚገኝ፣ ልጅ አዝለው ውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር ድረስ ቢሄዱም አጥጋቢ ምላሽ እንዳላገኙ ተናግረዋል።
በዝርዝር ምን አሉ ?
“ ባለቤቴ ማይናማር በስቃይ ውሰጥ ነው። ከሄደ 5 ወራት አስቆጥሯል። ‘የሥራ እድል አለ’ ተብሎ በደላሎች አማካኝነት ነበር ወደ ታይላንድ የሄደው። በሙያው ሐኪም ነው። ከሄደ በኋላ ግን ታይላንድ አይደለም የቀረው ወደ ማይናማር ነው የወሰዱት።
ያለበት ሁኔታ በጣም ከባድ ነው። የጨለማ ክፍል የሚባል አለ፤ ድብደባ አለ። በነገረኝ መሠረት አሰቃቂ ሁኔታ ነው። እኔም መፍትሄ ፍለጋ የውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር ልጅ አዝዬ ጭምር ብዙ ጊዜ ተመላልሻለሁ።
የሚሰጠኝ ምላሽ በራሳቸው ፍላጎት እንደሄዱ፣ በሕገወጥ መንገድ እንደሄዱ ነው። ከሦስት ቀናት በፊትም ሂጀ ነበርና ከታች ያሉት የቀረበውን ቅሬታ ካሳወቁ ከ10 ወራት በላይ እንዳስቆጠረ፣ ግን መፍትሄ እንዳልተገኘለት ነው የነገሩኝ።
‘ ከላይ ያሉት አካላት ናቸው መስራት ያለባቸው ’ ነው ያሉኝ። ጥሩ መልስ የሰጠን የኤምባሲ አካል ግን አላገኘንም። ቤተሰቡ በጭንቀት ውስጥ ነው ያለው። ባለቤቴ ከሄደ በኋላ ኑሮው ከብዶኛል።
ስለእርሱ መጨነቁ፣ የኑሮ ውድነቱ ተደራረቡብኝ። የባለቤቴ ደመወዝ ተቋርጧል። አዲስ አበባ ከተማ ላይ ብቻዬን ልጅ እያሳደኩ ስቃይ ላይ ነኝ።
የኢትዮጵያ መንግስት በደንብ ትኩረት ሰጥቶ ቢሰራበት የማይናማር መንግስት ሊለቃቸው እንደሚችል ባለቤቴ ነገሮኛል። ባለቤቴ ጋር የነበሩ የህንድ አገር ዜጎች ወጥተዋል። መንግስት መፍትሄ ይስጠን ” ሲሉ ተማጽነዋል።
ማይናማር ውስጥ የሚገኙ የታጋች ኢትዮጵያዊያኑ ወላጅች ያቋቋሙት ኮሚቴ በበኩሉ፣ መፍትሄ እየጠየቀ መሆኑን የገለጸ ሲሆን፣ የውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር ምን እየሰራ እንሆነ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ከሰጠው ምላሽ ጋር በቀጣይ ይቀርባል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ማይናማር🚨 🔴 “ አምልጠን እንኳ ብንወጣ ያመለጠውን ኢትዮጵያዊ ለሚይዙ 500 ዶላር ይከፈላቸዋል። ” -ኢትዮጵያዊያን በማይናማር 🔵 “ ደብድበውት ራሱን አያውቅም ወጣቶች ተሸክመው ሆስፒታል ሲወስዱት የውጪ ዜጋ አናክምም ብለው መለሱት ” - በእንባ የታጀቡ እናት ሰርተን እንለወጣለን፣ ቤተሰብም እንለውጣለን ብለው ከአገር የወጡ በርካታ ኢትዮጵያዊያን በማይናማር በስቃይ ውስጥ መሆናቸው ከዚህ ቀደም በተደጋጋሚ…
#ማይናማር🚨
🔴 “ ልጆቻችን በስቃይ ውስጥ ነው ያሉት። መንግስት አንድ መፍትሄ ይፍጠርልን ” - የወላጆች ኮሚቴ
🔵 “ ከአገራቱ ጋር የስራ ሥምሪት ስምምነት ባለመኖሩ፣ ሰዎቹም ያቀኑት በህገ ወጥ መንገድ በመሆኑ ያሉበት ቦታና ቁጥራቸውን በትክክል ለማወቅ አስቸጋሪ ሆኗል ” - ውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር
ማይናማር የሚገኙ ኢትዮጵያዊያን ወላጆች ኮሚቴ አዋቅረው የውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር ልጆቻቸው ካሉበት አስከፊ ሁኔታ እንዲያወጣላቸው እየጠየቁ ቢሆንም እስካሁን ልጆቻቸው ወደ አገር ባለመመለሳቸው ጥልቅ ጭንቀት ላይ መሆናቸውን በቲክቫህ ኢትዮጵያ በኩል ተናግረዋል።
መንግስት ለጉዳዩ ይበልጥ ትኩረት እንዲሰጥም በአጽንኦት ጠይቀዋል።
የኮሚቴው በዝርዝር ምን አለ ?
“ ልጆቻችን አሁንም እየተገረፉ፤ እየተደበደቡ ነው። 18 ሰዓት እያሰሯቸው ነው። ጭራሽ ገንዘብ ካልገባና አጨበርብረው ብር ካላመጡ 24 ሰዓት ሙሉ ኮምፑዩተር ላይ ቁጭ ስለሚያደርጓቸው ፌንት እየነቀሉ የሚወድቁበት ሁኔታ አለ።
ልጆቻችን በስቃይ ውስጥ ነው ያሉት። መንግስት አንድ መፍትሄ ይፍጠርልን። በአካባቢው ያሉ ዲፕሎማቶች እንዲሰሩ የሚያሳስብ ነው የኛ ማመልከቻ።
ታግተው ካሉት ውስጥ 2 ሴት ወጣቶች መለቀቃቸውን ብቻ ነው የማውቀው። እኛ ወደ 153 ወጣቶችን ዝርዝር ነው ይዘን ወደ ውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር እየሄድን ያለው።
ከእነዛ ውስጥ ወደ 2 ሴቶች ብቻ ናቸው የወጡት። በመንግስት በኩል ወደ 31 ወጣቶች ወጥተዋል የሚል ዜና ነው ያየነው። በተጨባጭ የወጡትን ልጆች አላየናቸውም።
ይሄው 11ኛ ወራችን ነው በማመልከቻ ውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር መመላለስ ከጀመርን እካሁን ጠብ ያለ መፍትሄ የለም። ከ3,000 በላይ ኢትዮጵያን ናቸው እዛ እየተሰቃዩ ያሉት።
በስቃይ ላይ የሚገኙት ቢያንስ ከመጀመሪያ ድግሪ በላይ የትምህርት ደረጃ ያላቸው ልጆች ናቸው። ይሄ ለቤተሰብ ብቻ ሳይሆን ለአገርም ኪሳራ ነው። ለኛም ትልቅ ጭንቀት ነው ሆኖብን ያለው ” ብሏል።
የኢትዮጵያ ውጪ ጉዳይ ሚኒስትርን እየተመላለሳችሁ እየጠየቃችሁ ከሆነ ምን ምላሽ ሰጣችሁ? የሚል ጥያቄ ያቀሰብንለት ኮሚቴው፣ “ ‘ለተወካዮች እናሳውቃለን በዛ በኩል ነው መታዬት ያለበት፤ ቶኪዮ ያለው ነው ማይናማርን የሚመለከተው’ የሚል መልስ የሚሰጡን ” ብሏል።
በማይናማር ስለሚገኙ ኢትዮጵያዊያንና ቤተሰቦቻቸው ዜጎቹ በስቃይ ውስጥ እንደሆኑ፣ ለዚህም መንግስት መፍትሄ እንዲሰጣቸው እየተማጸኑ እንደሆነ በመግለጽ፣ ምን እየሰራ ነው ? ጉዳዩ ተስፋ አለው ? ስንል የውጪ ጉዳይ ሚኒስቴርን ጠይቀናል።
የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ቃል አቀባይ አምባሳደር ነብያት ጌታቸው በበኩላቸው ተከታዩን አጭር ምላሽ ሰጥተዋል።
አምባደር ነብያት ጌታቸው ፦
“ ባለፈው ሳምንት መግለጫ ሰጥተን ነበር። በዛ ላይ እስከ ባለፈው ሳምነት መጨረሻ ያሉ ደቨሎፕመንቶችን ነው ያቀረብነው።
ከዚያ ወዲህ የክትትል ሥራ ነው የተሰራው ቶኪዮ ያለው ኤምባሲያችን ከማይናማር መንግስት አካላት ጋር በዚህ ሳምነት ውስጥ ክትትል እንደተደረገ ተገልጾልናል። እስካሁን ያለው ሂደት እዚህ ላይ ነው ያለው።
እስካሁን በተደረገ ጥረት 31 ዜጎቻችን ከነበሩበት አስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ወጥተው ወደ አገራቸው እንዲመለሱ ማድረግ ተችሏል።
ከአገራቱ ጋር የስራ ሥምሪት ስምምነት ባለመኖሩ እና ሰዎቹም ያቀኑት በህገ ወጥ መንገድ በመሆኑ ያሉበት ቦታ እና ቁጥራቸውን በትክክል ለማወቅ አስቸጋሪ ሆኗል።
መንግሥት ለዜጋ ተኮር ቅድሚያ ትኩረት ስለሚሰጥ ጥረቱን አጠናክሮ ይቀጥላል።
አሁንም ህብረተሰባችን ከህገ ወጥ የሰዎች አዘዋዋሪዎችና ህገ ወጥ ጉዞ ራሱንና ልጆቹን መጠበቅ አለበት።
መገናኛ ብዙኃንም ይህን ጉዳይ ልዩ ትኩረት ሰጥተው መስራት ይገባል። ዜጎቻችን የህገ ወጥ ሰዎች አዘዋዋሪዎች ሰለባ መሆን የለባቸውም ” ብለዋል።
ቤተሰቦቻቸው በጣም ተጨንቀው እያለቀሱ ነው። ታጋቾቹም አብረዋቸው የነበሩ የሌሎች አገራት እየተለቀቁ ስለሆነ የኢትዮጵያ መንግስትም ጫና ቢያደርግ የመውጣት እድል እንዳላቸው እየገለጹ ነው፤ እንዲያው ሚኒስቴር መስሪያ ቤትዎ ምን ያህል ጥረት አድርጓል ? ስንል ለአምባሳደሩ ጥያቄ አቅርበናል።
አምባሳደር ነብያት ፤ “ ከአገራቱ ጋር የሥራ ስምሪት ስምምነት ያለበት ቦታ አይደለም። ሰዎቹም የሄዱት ሕገ ወጥ በሆነ መንገድ ነው። ያሉበትን ቦታና ቁጥራቸውን ራሱ በትክክል ለማወቅ እጅግ አዳጋች ነው ” ብለዋል።
“ የማይናማር መንግስት ከሚቆጣጠረው አካባቢም ያሉ አይደሉም ለዛነው ችግሩ እጅግ አስቸጋሪ የሆነው ” ሲሉ አክለዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
🔴 “ ልጆቻችን በስቃይ ውስጥ ነው ያሉት። መንግስት አንድ መፍትሄ ይፍጠርልን ” - የወላጆች ኮሚቴ
🔵 “ ከአገራቱ ጋር የስራ ሥምሪት ስምምነት ባለመኖሩ፣ ሰዎቹም ያቀኑት በህገ ወጥ መንገድ በመሆኑ ያሉበት ቦታና ቁጥራቸውን በትክክል ለማወቅ አስቸጋሪ ሆኗል ” - ውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር
ማይናማር የሚገኙ ኢትዮጵያዊያን ወላጆች ኮሚቴ አዋቅረው የውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር ልጆቻቸው ካሉበት አስከፊ ሁኔታ እንዲያወጣላቸው እየጠየቁ ቢሆንም እስካሁን ልጆቻቸው ወደ አገር ባለመመለሳቸው ጥልቅ ጭንቀት ላይ መሆናቸውን በቲክቫህ ኢትዮጵያ በኩል ተናግረዋል።
መንግስት ለጉዳዩ ይበልጥ ትኩረት እንዲሰጥም በአጽንኦት ጠይቀዋል።
የኮሚቴው በዝርዝር ምን አለ ?
“ ልጆቻችን አሁንም እየተገረፉ፤ እየተደበደቡ ነው። 18 ሰዓት እያሰሯቸው ነው። ጭራሽ ገንዘብ ካልገባና አጨበርብረው ብር ካላመጡ 24 ሰዓት ሙሉ ኮምፑዩተር ላይ ቁጭ ስለሚያደርጓቸው ፌንት እየነቀሉ የሚወድቁበት ሁኔታ አለ።
ልጆቻችን በስቃይ ውስጥ ነው ያሉት። መንግስት አንድ መፍትሄ ይፍጠርልን። በአካባቢው ያሉ ዲፕሎማቶች እንዲሰሩ የሚያሳስብ ነው የኛ ማመልከቻ።
ታግተው ካሉት ውስጥ 2 ሴት ወጣቶች መለቀቃቸውን ብቻ ነው የማውቀው። እኛ ወደ 153 ወጣቶችን ዝርዝር ነው ይዘን ወደ ውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር እየሄድን ያለው።
ከእነዛ ውስጥ ወደ 2 ሴቶች ብቻ ናቸው የወጡት። በመንግስት በኩል ወደ 31 ወጣቶች ወጥተዋል የሚል ዜና ነው ያየነው። በተጨባጭ የወጡትን ልጆች አላየናቸውም።
ይሄው 11ኛ ወራችን ነው በማመልከቻ ውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር መመላለስ ከጀመርን እካሁን ጠብ ያለ መፍትሄ የለም። ከ3,000 በላይ ኢትዮጵያን ናቸው እዛ እየተሰቃዩ ያሉት።
በስቃይ ላይ የሚገኙት ቢያንስ ከመጀመሪያ ድግሪ በላይ የትምህርት ደረጃ ያላቸው ልጆች ናቸው። ይሄ ለቤተሰብ ብቻ ሳይሆን ለአገርም ኪሳራ ነው። ለኛም ትልቅ ጭንቀት ነው ሆኖብን ያለው ” ብሏል።
የኢትዮጵያ ውጪ ጉዳይ ሚኒስትርን እየተመላለሳችሁ እየጠየቃችሁ ከሆነ ምን ምላሽ ሰጣችሁ? የሚል ጥያቄ ያቀሰብንለት ኮሚቴው፣ “ ‘ለተወካዮች እናሳውቃለን በዛ በኩል ነው መታዬት ያለበት፤ ቶኪዮ ያለው ነው ማይናማርን የሚመለከተው’ የሚል መልስ የሚሰጡን ” ብሏል።
በማይናማር ስለሚገኙ ኢትዮጵያዊያንና ቤተሰቦቻቸው ዜጎቹ በስቃይ ውስጥ እንደሆኑ፣ ለዚህም መንግስት መፍትሄ እንዲሰጣቸው እየተማጸኑ እንደሆነ በመግለጽ፣ ምን እየሰራ ነው ? ጉዳዩ ተስፋ አለው ? ስንል የውጪ ጉዳይ ሚኒስቴርን ጠይቀናል።
የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ቃል አቀባይ አምባሳደር ነብያት ጌታቸው በበኩላቸው ተከታዩን አጭር ምላሽ ሰጥተዋል።
አምባደር ነብያት ጌታቸው ፦
“ ባለፈው ሳምንት መግለጫ ሰጥተን ነበር። በዛ ላይ እስከ ባለፈው ሳምነት መጨረሻ ያሉ ደቨሎፕመንቶችን ነው ያቀረብነው።
ከዚያ ወዲህ የክትትል ሥራ ነው የተሰራው ቶኪዮ ያለው ኤምባሲያችን ከማይናማር መንግስት አካላት ጋር በዚህ ሳምነት ውስጥ ክትትል እንደተደረገ ተገልጾልናል። እስካሁን ያለው ሂደት እዚህ ላይ ነው ያለው።
እስካሁን በተደረገ ጥረት 31 ዜጎቻችን ከነበሩበት አስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ወጥተው ወደ አገራቸው እንዲመለሱ ማድረግ ተችሏል።
ከአገራቱ ጋር የስራ ሥምሪት ስምምነት ባለመኖሩ እና ሰዎቹም ያቀኑት በህገ ወጥ መንገድ በመሆኑ ያሉበት ቦታ እና ቁጥራቸውን በትክክል ለማወቅ አስቸጋሪ ሆኗል።
መንግሥት ለዜጋ ተኮር ቅድሚያ ትኩረት ስለሚሰጥ ጥረቱን አጠናክሮ ይቀጥላል።
አሁንም ህብረተሰባችን ከህገ ወጥ የሰዎች አዘዋዋሪዎችና ህገ ወጥ ጉዞ ራሱንና ልጆቹን መጠበቅ አለበት።
መገናኛ ብዙኃንም ይህን ጉዳይ ልዩ ትኩረት ሰጥተው መስራት ይገባል። ዜጎቻችን የህገ ወጥ ሰዎች አዘዋዋሪዎች ሰለባ መሆን የለባቸውም ” ብለዋል።
ቤተሰቦቻቸው በጣም ተጨንቀው እያለቀሱ ነው። ታጋቾቹም አብረዋቸው የነበሩ የሌሎች አገራት እየተለቀቁ ስለሆነ የኢትዮጵያ መንግስትም ጫና ቢያደርግ የመውጣት እድል እንዳላቸው እየገለጹ ነው፤ እንዲያው ሚኒስቴር መስሪያ ቤትዎ ምን ያህል ጥረት አድርጓል ? ስንል ለአምባሳደሩ ጥያቄ አቅርበናል።
አምባሳደር ነብያት ፤ “ ከአገራቱ ጋር የሥራ ስምሪት ስምምነት ያለበት ቦታ አይደለም። ሰዎቹም የሄዱት ሕገ ወጥ በሆነ መንገድ ነው። ያሉበትን ቦታና ቁጥራቸውን ራሱ በትክክል ለማወቅ እጅግ አዳጋች ነው ” ብለዋል።
“ የማይናማር መንግስት ከሚቆጣጠረው አካባቢም ያሉ አይደሉም ለዛነው ችግሩ እጅግ አስቸጋሪ የሆነው ” ሲሉ አክለዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#ትግራይ
" ' ተቀምተናል ' የሚሉትን ስልጣን ለማስመለስ ስም ከማጥፋት ባለፈ እስከ ፕሬዜዳንት መቀየር ያለመ አደገኛ እንቅስቃሴ እየተካሄደ ነው " - ፕረዚደንት አቶ ጌታቸው ረዳ
ዛሬ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ በወቅታዊ የፀጥታ እና ማህበራዊ ጉዳዮች ላይ መግለጫ ሰጥተው ነበር።
በዚህም ወቅት አቶ ጌታቸው ፥ " የህዝብ ጥቅም ማእከል አድርጎ በሚንቀሳቀስ የፓለቲካ ፓርቲ ውስጥ ለግሉ ጥቅም ብቻ የሚያስብ አመራር ከተፈጠረ ረጅም ጊዜ ሆኗል " ብለዋል።
" ' ስልጣን ለኛ ነው የሚገባው ' የሚሉ የህዝብ አጀንዳ በማፈን ፍላጎታቸው ለማሳካት የግጭትና የግርግር መልእክቶች በማስተላለፍ ላይ ይገኛሉ " ሲሉም ገልጸዋል።
እነዚህን አካላት በስም አልጠቀሷቸውም።
ፕሬዜዳንቱ በስም ያልገለፁዋቸው አካላት " ተቀምተናል " የሚሉት ስልጣን ለማስመለስ ስም ከማጥፋት ባለፈ እስከ ፕሬዜዳንት መቀየር ያለመ አደገኛ እንቅስቃሴ እያካሄዱ እንደሆነ አመላክተዋል።
" ትኩረታችን የትግራይ ህዝብ መሆን ይገባ ነበር " ያሉት ፕሬዜዳንቱ " ለወንበር ሲባል የጊዚያዊ አስተዳደሩ ስራዎች የማደናቅፍ ስራዎች ተባብሰው ቀጥለዋል " ሲሉ ገልፀዋል።
" ' ሰራዊት ከኛ ጎን ነው ' በማለት የግለሰቦችን ስልጣን ለማርካት ታስቦ የፀጥታ ሃይል ለመከፋፈል አልሞ እየተሰራ ነው " ሲሉም አክለዋል።
አቶ ጌታቸው ፥ " በትግራይ ሁሉንም ነገር በብቸኝነት ተቆጣጥሮ የቆየ ሃይል አሁንም የፀጥታ ሃይል ፤ ሚድያ ተቆጣጥሮ በለመደው መንገድ በመሄድ የግል ጥቅሙን ለማረጋገጥ ጠላት ከሚለው እየተደራደረ ይገኛል " ብለዋብ።
" ጠላት " ያሉትን ሃይል በስም አልገለፁም።
የም/ ቤት አባላት በማንሳት የአስተዳዳሪዎች ስልጣን እንዲለወጥ መስራት መፈንቅለ መንግስት ነው ያሉት አቶ ጌታቸው " መንግስትን ለማፍረስ የሚደረጉ መድረኮች በመንግስት በጀት ነው የሚካሄዱት " ሲሉ ተግባሩን ኮንነዋል።
" ' የፀጥታ ሃይል ከኛ ነው ' የሚለው አነጋገር የፀጥታ ሃይሉን በመጠቀም ' ከስልጣን እናስወግዳችኋለን ' የሚል መልእክት ለማስተላለፍ ተፈልጎ የሚሰራ ነው " ሲሉም ተናግረዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
ፎቶ፦ DW
@tikvahethiopia
" ' ተቀምተናል ' የሚሉትን ስልጣን ለማስመለስ ስም ከማጥፋት ባለፈ እስከ ፕሬዜዳንት መቀየር ያለመ አደገኛ እንቅስቃሴ እየተካሄደ ነው " - ፕረዚደንት አቶ ጌታቸው ረዳ
ዛሬ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ በወቅታዊ የፀጥታ እና ማህበራዊ ጉዳዮች ላይ መግለጫ ሰጥተው ነበር።
በዚህም ወቅት አቶ ጌታቸው ፥ " የህዝብ ጥቅም ማእከል አድርጎ በሚንቀሳቀስ የፓለቲካ ፓርቲ ውስጥ ለግሉ ጥቅም ብቻ የሚያስብ አመራር ከተፈጠረ ረጅም ጊዜ ሆኗል " ብለዋል።
" ' ስልጣን ለኛ ነው የሚገባው ' የሚሉ የህዝብ አጀንዳ በማፈን ፍላጎታቸው ለማሳካት የግጭትና የግርግር መልእክቶች በማስተላለፍ ላይ ይገኛሉ " ሲሉም ገልጸዋል።
እነዚህን አካላት በስም አልጠቀሷቸውም።
ፕሬዜዳንቱ በስም ያልገለፁዋቸው አካላት " ተቀምተናል " የሚሉት ስልጣን ለማስመለስ ስም ከማጥፋት ባለፈ እስከ ፕሬዜዳንት መቀየር ያለመ አደገኛ እንቅስቃሴ እያካሄዱ እንደሆነ አመላክተዋል።
" ትኩረታችን የትግራይ ህዝብ መሆን ይገባ ነበር " ያሉት ፕሬዜዳንቱ " ለወንበር ሲባል የጊዚያዊ አስተዳደሩ ስራዎች የማደናቅፍ ስራዎች ተባብሰው ቀጥለዋል " ሲሉ ገልፀዋል።
" ' ሰራዊት ከኛ ጎን ነው ' በማለት የግለሰቦችን ስልጣን ለማርካት ታስቦ የፀጥታ ሃይል ለመከፋፈል አልሞ እየተሰራ ነው " ሲሉም አክለዋል።
አቶ ጌታቸው ፥ " በትግራይ ሁሉንም ነገር በብቸኝነት ተቆጣጥሮ የቆየ ሃይል አሁንም የፀጥታ ሃይል ፤ ሚድያ ተቆጣጥሮ በለመደው መንገድ በመሄድ የግል ጥቅሙን ለማረጋገጥ ጠላት ከሚለው እየተደራደረ ይገኛል " ብለዋብ።
" ጠላት " ያሉትን ሃይል በስም አልገለፁም።
የም/ ቤት አባላት በማንሳት የአስተዳዳሪዎች ስልጣን እንዲለወጥ መስራት መፈንቅለ መንግስት ነው ያሉት አቶ ጌታቸው " መንግስትን ለማፍረስ የሚደረጉ መድረኮች በመንግስት በጀት ነው የሚካሄዱት " ሲሉ ተግባሩን ኮንነዋል።
" ' የፀጥታ ሃይል ከኛ ነው ' የሚለው አነጋገር የፀጥታ ሃይሉን በመጠቀም ' ከስልጣን እናስወግዳችኋለን ' የሚል መልእክት ለማስተላለፍ ተፈልጎ የሚሰራ ነው " ሲሉም ተናግረዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
ፎቶ፦ DW
@tikvahethiopia
#SafaricomEthiopia
💫ከዳር እስከ ዳር አስተማማኙን ኔትወርካችንን እያሰፋን ወደ እናንተ እየቀረብን ነው!🙌👏ከአስተማማኙ ኔትወርካችን ጋር አሁንም በአብሮነት ወደፊት!
አስተማማኙን ኔትወርክ ዛሬውኑ እንቀላቀል!
የቴሌግራም ቦታችንን https://t.iss.one/official_safaricomet_bot በመጠቀም የአየር ሰዓት ወይንም ልዩ ልዩ ጥቅሎችን እንግዛ!
#MPESASafaricom #1Wedefit
#Furtheraheadtogether
💫ከዳር እስከ ዳር አስተማማኙን ኔትወርካችንን እያሰፋን ወደ እናንተ እየቀረብን ነው!🙌👏ከአስተማማኙ ኔትወርካችን ጋር አሁንም በአብሮነት ወደፊት!
አስተማማኙን ኔትወርክ ዛሬውኑ እንቀላቀል!
የቴሌግራም ቦታችንን https://t.iss.one/official_safaricomet_bot በመጠቀም የአየር ሰዓት ወይንም ልዩ ልዩ ጥቅሎችን እንግዛ!
#MPESASafaricom #1Wedefit
#Furtheraheadtogether
#ሴጅ_ማሰልጠኛ
የግራፊክ ዲዛይን፣ ቪዲዮ ኢዲቲንግ፣ ሞሽን ግራፊክ እና ዲጂታል ማርኬቲንግ ስልጠና በፒያሣ እና መገናኛ ካምፓስ ሰኞ ህዳር 23/2017 ዓ.ም ይጀምራል።
👉 100% በተግባር የተደገፈ ስልጠና
👉 Advanced Graphics + Video Editing + Motion Graphics + Digital Marketing በአንድ ላይ
👉 ከ50 በላይ ፕሮጀክቶች ያሉት
👉 የሥራ ላይ ስልጠና (Internship) የተመቻቸለት
ስልክ ፦ 0906777799 / 0906777755
አድራሻ፦ ቁ.1: ፒያሣ ቸርችል ጎዳና ኤልያና ሆቴል 2ኛ ፎቅ እና ቁ.2 መገናኛ ታሜጋስ ህንፃ 2ኛ ፎቅ
Telegram: https://t.iss.one/sagetraininginstitute
Tiktok: https://www.tiktok.com/@sage_training_institute
Linkedin: https://www.linkedin.com/company/sage-training-institute
የግራፊክ ዲዛይን፣ ቪዲዮ ኢዲቲንግ፣ ሞሽን ግራፊክ እና ዲጂታል ማርኬቲንግ ስልጠና በፒያሣ እና መገናኛ ካምፓስ ሰኞ ህዳር 23/2017 ዓ.ም ይጀምራል።
👉 100% በተግባር የተደገፈ ስልጠና
👉 Advanced Graphics + Video Editing + Motion Graphics + Digital Marketing በአንድ ላይ
👉 ከ50 በላይ ፕሮጀክቶች ያሉት
👉 የሥራ ላይ ስልጠና (Internship) የተመቻቸለት
ስልክ ፦ 0906777799 / 0906777755
አድራሻ፦ ቁ.1: ፒያሣ ቸርችል ጎዳና ኤልያና ሆቴል 2ኛ ፎቅ እና ቁ.2 መገናኛ ታሜጋስ ህንፃ 2ኛ ፎቅ
Telegram: https://t.iss.one/sagetraininginstitute
Tiktok: https://www.tiktok.com/@sage_training_institute
Linkedin: https://www.linkedin.com/company/sage-training-institute
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#ነጋዴዎች #ደረሰኝ #መርካቶ
" ደረሰኝ መቆረጥ አለበት በዚህ ላይ ምንም አይነት ድርድር የለውም " - የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር
ከሰሞኑን በአዲስ አበባ በተለይ በግዙፉ የገበያ ማዕከል ' መርካቶ ' በንግድ ስርዓቱ ጋር በተያያዘ ቅሬታ አለን ያሉ ነጋዴዎች ሱቅ የመዝጋትና ስራ የማቆም እንቅስቃሴ ማድረጋቸው ይታወሳል።
ሰሞነኛውን የመርካቶ ገበያ ሁኔታ በተመለከተም ነጋዴዎቹ ከከተማ አስተዳደር ኃላፊዎች ጋር ውይይት ተቀምጠው ነበር።
በውይይቱ በነጋዴዎቹ በኩል በርካታ ጥያቄዎችና ሃሳቦች ተነስተው ነበር። ለተነሱት ጥያቄዎች የመንግሥት አካላት ምላሽ ሰጥተዋል።
ነጋዴዎች ሃሳባቸው ፣ ጥያቄያቸው፣ ቅሬታቸው ምንድነው ?
➡️ ደረሰኝ መቁረጥ ፣ ግብር መክፈል ለሀገር ወሳኝ ፤ ለራስም ይጠቅማል። ግን አከፋፈሉ ጥያቄ የሚያስነሳ ነው።
➡️ እኛ ስንገበያይ ደረሰኝ እናገኛለን ወይ ? አንዳንድ ምርት የሚነሳው ከገበሬ ነው። ከገበሬ ነጋዴ ይሰበስባል ይከፍላል፣ ተረካቢው ይረከባል ይከፍላል፣ ተጭኖ ይመጣል እኛ እንረከባለን ይሄ ሁሉ ይከፍላል ብዙ ነገር ነው ያለው። የቆረጠው ይቆርጥልናል የሌለውን ንግድ ፍቃድ እናያይዛለን። እንዲህ ስንሰራ ነው የቆየነው።
➡️ ሁሉም እየመጣ ባለድርሻ ነኝ ይላል። መርካቶ እንደምንታመስ ያውቃል ሌባው ይገባና " ሄደህ 100 ሺህ ብር ከምትቀጣ ለኔ ይሄን ስጠኝ " ይላል።
➡️ እቃው በደላላ ነው የሚመጣው ፤ ድሮ አስመጪ በእያንዳንዱ ሱቅ ሄዶ እቃ ይበትን ነበር አሁን ግን አስመጪው ለደላላ፣ ለቤተሰብ ፣ ለዘመዱ ፣ ለጎረቤት፣ ለጓደኛ ነው የሚሰጠው። እቃው ይመጣና በተለያየ መጋዘን ይቅመጣል ከዛ በስልክ ነው ልውውጥ የሚደረገው ነጋዴው ደላላውን ' ደረሰኝ ስጠኝ ' ካለው ነገ እቃ አይሰጥም።
➡️ ቁጥጥር እየተባሉ የሚመደቡ ሰዎች ባጅ የላቸው፣ ምናቸውም አይታውቅ፣ ሱቅ የሚገቡት እንደ ሌባ 3 እና 2 እየሆኑ ነው ስለዚህ ህጋዊ ይሁኑ ህገወጥ ምናቸው ይለያል ?
➡️ ባልተማከለ ሲስተም ውስጥ ነው ያለነው። ደረሰኝ አልቆረጣችሁም በሚል መቶ ብር አትርፈን 100 ሺህ ብር ነው የምንጠየቀው።
➡️ እስቲ ኢንዱስትሪውን ተቆጣጠሩ ደረሰኝ ቼክ ይደረግ የሚወጣው አንደርኢንቮይስ ከሆነ በምን አግባብ ነው ነጋዴው የሚጠየቀው ?
➡️ " ደረሰኝ ቁረጡ ደረሰኝ ቁረጡ " ሲባል ሌላ ነገር ነው የሚመስለው ደረሰኝ ይዞት የሚመጣው ገንዘብ ነው። መጀመሪያ የንግድ ስርዓቱ መስተካከል አለበት።
➡️ ለ100 ሺህ ብር ቅጣት በዚህ ፍጥነት ከተሰራ ነጋዴውን ለማገዝ በገንዘብ ሚኒስቴር የሚሰጠቱን ዕድሎች ተፈጻሚ ለማድረግ ለምን አልተቻለም ?
➡️ አሰራሩ እኮ ብዙ ነው። አልታየም። እንደ ከተማ አንድም አስመጪ የለም። አስመጪዎቹ ' መርካቶ መጥተን አንሸጥም ጅግጅጋ መጥታችሁ ግዙ ' ይሉናል። በደረሰኝ ስንት ስቃይ ነው ያለው። እዛ ተኪዶ ነው ሚገዛው ? እሺ እዚህ ስናመጣ ገቢዎች ላይ ብዙ ነገር አለ ፤ ደረሠኝ ይጥላሉ፣ ' አንቀበልም ' ይላሉ የት እንሂድ ?
➡️ አሰራሩ ላይ ትልቅ ችግር አለ።
➡️ አምራቾች፣ አከፋፋዮች፣ አስመጪዎች ደረሰኝ ይሰጣሉ ወይ ? የሚለው ትልቁ ጥያቄ ነው።
ለነጋዴዎች ጥያቄ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ኃላፊዎች ምን መለሱ ?
🔴 የገቢዎች የቁጥጥር ሰራተኞችን በተመለከተ መታወቂያ አላቸው፣ 3 እና 4 ሆነው ነው የሚገቡት። መታወቂያ የሌለው ካለ ህገወጥ አጭበርባሪ ነው ተከላከሉት።
🔴 " የገቢዎች ሰራተኛ ነን " ብለው ሲያጭበረብሩ የተያዙ ሰዎች አሉ።
🔴 ለገቢዎች ሰራተኞች መታወቂያ ተሰጥቷል። መታወቂያ ማሳየት አለባቸው። እናተም ጠይቋቸው።
🔴 ደረሰኝ ላለመቁረጥ የሚሰጡትን ምክንያቶች በጋር እየተነጋገርን እንፈታለን እንጂ ደረሰኝ መቁረጥ እንዲቆምላችሁ የምትጠይቁትን ጥያቄ መንግስት መመለስ አይችልም። ይሄን በግልጽ እወቁት።
🔴 በገቢዎች ውስጥ ያሉ ችግሮች ይታወቃሉ መፈታት አለባቸው። ከብልሹ አሰራር፣ ከሌብነት ጋር በተያያዘ የተነሱ ችግሮች ይታረማሉ።
🔴 ቫትን በተመለከተ በአዲሱ አሰራር 7 ሺህ ብር ነው የቀን ግምቱ የተቀመጠው። ቀደም ሲል ቫት የነበረ ወደ ታች ሊወርድ አይችልም። በቀን 7 ሺህ ብር የሚሸጥ ሰው ምን ያክል ነው የሚለውን እናተው ታውቃላችሁ። ቅድሚያ እየተሰጠ ያለው ቫት ውስጥ መግባት እያለበት ቫት ውስጥ ያልገባው ነጋዴ በተለይ መርካቶ እሱ ባለመግባቱ በሚሸጠው እቃ ላይ የዋጋ ልዩነት እየመጣ ስለሆነ ቫት ውስጥ መግባት ያለበትን ቫት ውስጥ እያስገባን ነው።
🔴 ቫት ውስጥ የነበረ ነጋዴ ልወርድ ይገባል ብሎ ተጨባጭ ማስረጃ ካቀረበ ይታያል። አሁን ባለው የዋጋ ንረት እታች ያለው ወደላይ ይወጣል እንጂ እላይ የነበረው ወደ ታች አይወርድም።
🔴 የቁጥጥር ስርዓቱ እየጠበቀ ነው የሚሄደው።
🔴 እኛ ስለትላንቱ አለነሳንም አሁን ግን መርካቶ የሚደርገው ግብይት በደረሰኝ እና በደረሰኝ ብቻ መሆን አለበት። ይህን የሚያደርገውን ነጋዴ እንደግፋለን።
🔴 ነጋዴው በህጋዊ መንገድ ይጠቀም አልን እንጂ ነጋዴውን የሚያስቀይም ፣ የሚያሳድድ እርምጃ ለመውሰድ የሚፈልግ አካል የለም።
🔴 መርካቶ የሚደረገው እንቅስቃሴ በክልል ጥያቄ ያስነሳል። መረካቶ ደረሰኝ ስለማይቆረጥ የንግዱ ማህበረሰብ ክልል ሄዶ ሲነግድ ደረሰኝ አቅርቡ ሲባል " ያለ ደረሰኝ ነው የገዛነው እዛ ደረሰኝ አልተቆረጠም " የሚሉ አሉ።
🔴 የዚህ አመት እቅዳችን ግዙፍ የሆነ ገቢ ለመሰብሰብ አቅደናል። ይህን የምናደርገው የታክስ ቤዛችንን በማስፋት፣ ኢመደበኛውን ንግድ ወደ መደበኛ በመቀየር ነው።
🔴 ኢ-መደበኛ እናሳድዳለን አላልንም ግን ወደ መደበኛ ይግባ እያልን ነው።
🔴 ብዙዎቻችሁ (ነጋዴዎች) ያነሳችሁት ጥያቄ ደረሰኝ እንዳይቆረጥ የሚጠይቅ ዝንባሌ አለው። " ደረሰኝ አያስፈልግም " አትሉም ግን ጅምላውን፣ አከፋፋዩን ፣ አምራቹን ቅድሚያ ስጡ ነው የምትሉት። ጅምላውም ላይ፣ አከፋፋዩም ላይ ፣ አምራቹም ላይ እንሰራለን ቸርቻሪም ላይ እንደዛው ይሰራል። ሁሉም ደረሰኝ መቁረጥ አለበት።
🔴 ደረሰኝ ለመቁረጥ የማይስችል ሁኔታ ካለ ማስረዳት ነው እንጂ " ደረሰኝ አንቆርጥ " የሚል እሳቤ ተቀባይነት የለውም።
🔴 በደረሰኝ መቆረጥ አለበት ምንም አይነት ድርድር የለውም በዚህ ጉዳይ። እኛ ኢመደበኛውን ንግድ ወደ መደበኛ እናስገባለን።
🔴 አቤቱታ ካላችሁ በማንኛውም ጊዜ አቅርቡ። ገቢዎች አካባቢ ያለውን ነገርም እንፈትሻለን።
#AddisAbaba #Merkato
@tikvahethiopia
" ደረሰኝ መቆረጥ አለበት በዚህ ላይ ምንም አይነት ድርድር የለውም " - የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር
ከሰሞኑን በአዲስ አበባ በተለይ በግዙፉ የገበያ ማዕከል ' መርካቶ ' በንግድ ስርዓቱ ጋር በተያያዘ ቅሬታ አለን ያሉ ነጋዴዎች ሱቅ የመዝጋትና ስራ የማቆም እንቅስቃሴ ማድረጋቸው ይታወሳል።
ሰሞነኛውን የመርካቶ ገበያ ሁኔታ በተመለከተም ነጋዴዎቹ ከከተማ አስተዳደር ኃላፊዎች ጋር ውይይት ተቀምጠው ነበር።
በውይይቱ በነጋዴዎቹ በኩል በርካታ ጥያቄዎችና ሃሳቦች ተነስተው ነበር። ለተነሱት ጥያቄዎች የመንግሥት አካላት ምላሽ ሰጥተዋል።
ነጋዴዎች ሃሳባቸው ፣ ጥያቄያቸው፣ ቅሬታቸው ምንድነው ?
➡️ ደረሰኝ መቁረጥ ፣ ግብር መክፈል ለሀገር ወሳኝ ፤ ለራስም ይጠቅማል። ግን አከፋፈሉ ጥያቄ የሚያስነሳ ነው።
➡️ እኛ ስንገበያይ ደረሰኝ እናገኛለን ወይ ? አንዳንድ ምርት የሚነሳው ከገበሬ ነው። ከገበሬ ነጋዴ ይሰበስባል ይከፍላል፣ ተረካቢው ይረከባል ይከፍላል፣ ተጭኖ ይመጣል እኛ እንረከባለን ይሄ ሁሉ ይከፍላል ብዙ ነገር ነው ያለው። የቆረጠው ይቆርጥልናል የሌለውን ንግድ ፍቃድ እናያይዛለን። እንዲህ ስንሰራ ነው የቆየነው።
➡️ ሁሉም እየመጣ ባለድርሻ ነኝ ይላል። መርካቶ እንደምንታመስ ያውቃል ሌባው ይገባና " ሄደህ 100 ሺህ ብር ከምትቀጣ ለኔ ይሄን ስጠኝ " ይላል።
➡️ እቃው በደላላ ነው የሚመጣው ፤ ድሮ አስመጪ በእያንዳንዱ ሱቅ ሄዶ እቃ ይበትን ነበር አሁን ግን አስመጪው ለደላላ፣ ለቤተሰብ ፣ ለዘመዱ ፣ ለጎረቤት፣ ለጓደኛ ነው የሚሰጠው። እቃው ይመጣና በተለያየ መጋዘን ይቅመጣል ከዛ በስልክ ነው ልውውጥ የሚደረገው ነጋዴው ደላላውን ' ደረሰኝ ስጠኝ ' ካለው ነገ እቃ አይሰጥም።
➡️ ቁጥጥር እየተባሉ የሚመደቡ ሰዎች ባጅ የላቸው፣ ምናቸውም አይታውቅ፣ ሱቅ የሚገቡት እንደ ሌባ 3 እና 2 እየሆኑ ነው ስለዚህ ህጋዊ ይሁኑ ህገወጥ ምናቸው ይለያል ?
➡️ ባልተማከለ ሲስተም ውስጥ ነው ያለነው። ደረሰኝ አልቆረጣችሁም በሚል መቶ ብር አትርፈን 100 ሺህ ብር ነው የምንጠየቀው።
➡️ እስቲ ኢንዱስትሪውን ተቆጣጠሩ ደረሰኝ ቼክ ይደረግ የሚወጣው አንደርኢንቮይስ ከሆነ በምን አግባብ ነው ነጋዴው የሚጠየቀው ?
➡️ " ደረሰኝ ቁረጡ ደረሰኝ ቁረጡ " ሲባል ሌላ ነገር ነው የሚመስለው ደረሰኝ ይዞት የሚመጣው ገንዘብ ነው። መጀመሪያ የንግድ ስርዓቱ መስተካከል አለበት።
➡️ ለ100 ሺህ ብር ቅጣት በዚህ ፍጥነት ከተሰራ ነጋዴውን ለማገዝ በገንዘብ ሚኒስቴር የሚሰጠቱን ዕድሎች ተፈጻሚ ለማድረግ ለምን አልተቻለም ?
➡️ አሰራሩ እኮ ብዙ ነው። አልታየም። እንደ ከተማ አንድም አስመጪ የለም። አስመጪዎቹ ' መርካቶ መጥተን አንሸጥም ጅግጅጋ መጥታችሁ ግዙ ' ይሉናል። በደረሰኝ ስንት ስቃይ ነው ያለው። እዛ ተኪዶ ነው ሚገዛው ? እሺ እዚህ ስናመጣ ገቢዎች ላይ ብዙ ነገር አለ ፤ ደረሠኝ ይጥላሉ፣ ' አንቀበልም ' ይላሉ የት እንሂድ ?
➡️ አሰራሩ ላይ ትልቅ ችግር አለ።
➡️ አምራቾች፣ አከፋፋዮች፣ አስመጪዎች ደረሰኝ ይሰጣሉ ወይ ? የሚለው ትልቁ ጥያቄ ነው።
ለነጋዴዎች ጥያቄ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ኃላፊዎች ምን መለሱ ?
🔴 የገቢዎች የቁጥጥር ሰራተኞችን በተመለከተ መታወቂያ አላቸው፣ 3 እና 4 ሆነው ነው የሚገቡት። መታወቂያ የሌለው ካለ ህገወጥ አጭበርባሪ ነው ተከላከሉት።
🔴 " የገቢዎች ሰራተኛ ነን " ብለው ሲያጭበረብሩ የተያዙ ሰዎች አሉ።
🔴 ለገቢዎች ሰራተኞች መታወቂያ ተሰጥቷል። መታወቂያ ማሳየት አለባቸው። እናተም ጠይቋቸው።
🔴 ደረሰኝ ላለመቁረጥ የሚሰጡትን ምክንያቶች በጋር እየተነጋገርን እንፈታለን እንጂ ደረሰኝ መቁረጥ እንዲቆምላችሁ የምትጠይቁትን ጥያቄ መንግስት መመለስ አይችልም። ይሄን በግልጽ እወቁት።
🔴 በገቢዎች ውስጥ ያሉ ችግሮች ይታወቃሉ መፈታት አለባቸው። ከብልሹ አሰራር፣ ከሌብነት ጋር በተያያዘ የተነሱ ችግሮች ይታረማሉ።
🔴 ቫትን በተመለከተ በአዲሱ አሰራር 7 ሺህ ብር ነው የቀን ግምቱ የተቀመጠው። ቀደም ሲል ቫት የነበረ ወደ ታች ሊወርድ አይችልም። በቀን 7 ሺህ ብር የሚሸጥ ሰው ምን ያክል ነው የሚለውን እናተው ታውቃላችሁ። ቅድሚያ እየተሰጠ ያለው ቫት ውስጥ መግባት እያለበት ቫት ውስጥ ያልገባው ነጋዴ በተለይ መርካቶ እሱ ባለመግባቱ በሚሸጠው እቃ ላይ የዋጋ ልዩነት እየመጣ ስለሆነ ቫት ውስጥ መግባት ያለበትን ቫት ውስጥ እያስገባን ነው።
🔴 ቫት ውስጥ የነበረ ነጋዴ ልወርድ ይገባል ብሎ ተጨባጭ ማስረጃ ካቀረበ ይታያል። አሁን ባለው የዋጋ ንረት እታች ያለው ወደላይ ይወጣል እንጂ እላይ የነበረው ወደ ታች አይወርድም።
🔴 የቁጥጥር ስርዓቱ እየጠበቀ ነው የሚሄደው።
🔴 እኛ ስለትላንቱ አለነሳንም አሁን ግን መርካቶ የሚደርገው ግብይት በደረሰኝ እና በደረሰኝ ብቻ መሆን አለበት። ይህን የሚያደርገውን ነጋዴ እንደግፋለን።
🔴 ነጋዴው በህጋዊ መንገድ ይጠቀም አልን እንጂ ነጋዴውን የሚያስቀይም ፣ የሚያሳድድ እርምጃ ለመውሰድ የሚፈልግ አካል የለም።
🔴 መርካቶ የሚደረገው እንቅስቃሴ በክልል ጥያቄ ያስነሳል። መረካቶ ደረሰኝ ስለማይቆረጥ የንግዱ ማህበረሰብ ክልል ሄዶ ሲነግድ ደረሰኝ አቅርቡ ሲባል " ያለ ደረሰኝ ነው የገዛነው እዛ ደረሰኝ አልተቆረጠም " የሚሉ አሉ።
🔴 የዚህ አመት እቅዳችን ግዙፍ የሆነ ገቢ ለመሰብሰብ አቅደናል። ይህን የምናደርገው የታክስ ቤዛችንን በማስፋት፣ ኢመደበኛውን ንግድ ወደ መደበኛ በመቀየር ነው።
🔴 ኢ-መደበኛ እናሳድዳለን አላልንም ግን ወደ መደበኛ ይግባ እያልን ነው።
🔴 ብዙዎቻችሁ (ነጋዴዎች) ያነሳችሁት ጥያቄ ደረሰኝ እንዳይቆረጥ የሚጠይቅ ዝንባሌ አለው። " ደረሰኝ አያስፈልግም " አትሉም ግን ጅምላውን፣ አከፋፋዩን ፣ አምራቹን ቅድሚያ ስጡ ነው የምትሉት። ጅምላውም ላይ፣ አከፋፋዩም ላይ ፣ አምራቹም ላይ እንሰራለን ቸርቻሪም ላይ እንደዛው ይሰራል። ሁሉም ደረሰኝ መቁረጥ አለበት።
🔴 ደረሰኝ ለመቁረጥ የማይስችል ሁኔታ ካለ ማስረዳት ነው እንጂ " ደረሰኝ አንቆርጥ " የሚል እሳቤ ተቀባይነት የለውም።
🔴 በደረሰኝ መቆረጥ አለበት ምንም አይነት ድርድር የለውም በዚህ ጉዳይ። እኛ ኢመደበኛውን ንግድ ወደ መደበኛ እናስገባለን።
🔴 አቤቱታ ካላችሁ በማንኛውም ጊዜ አቅርቡ። ገቢዎች አካባቢ ያለውን ነገርም እንፈትሻለን።
#AddisAbaba #Merkato
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ExchangeRate የዶላር ምንዛሬ ዋጋ ጭማሪ አሳየ። ባለፉት ቀናት በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አንድ የአሜሪካ ዶላር መግዣው 116 ብር ከ6699 ሳንቲም ፤ መሸጫው ደግሞ 119 ብር ከ0033 ሳንቲም ነበር። ዛሬ ይፋ በሆነው ምንዛሬ ዋጋው ጨምሯል። ባንኩ በመግዣ ዋጋው ላይ ከ2 ብር በላይ ጭማሪ በማድረግ 119 ብር ከ2044 ሳንቲም አስገብቶታል። መሸጫውም በተመሳሳይ ከ2 ብር በላይ ጨምሮ 121…
#ExchangeRate
ከሰሞኑን የዶላር ምንዛሬ ዋጋ ጭማሪ እያሳየ ነው።
ባለፉት በርካታ ቀናት በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አንድ የአሜሪካ ዶላር መግዣው 119 ብር ከ2044 ሳንቲም ፤ መሸጫው ደግሞ 121 ብር ከ5885 ሳንቲም ነበር።
ካለፈው ቅዳሜ አንስቶ ግን የምንዛሬ ዋጋው ጨምሯል።
ባንኩ በመግዣ ዋጋው ላይ ከ3 ብር በላይ ጭማሪ በማድረግ 122 ብር ከ5986 ሳንቲም አስገብቶታል።
መሸጫውም በተመሳሳይ ከ3 ብር በላይ ጨምሮ 125 ብር ከ0506 ሳንቲም ገብቷል።
ከግል ባንኮች በአቢሲንያ ባንክ ዶላር 123 ብር ከ0001 ሳንቲም እየተገዛ በ125 ብር ከ4601 ሳንቲም እየተሸጠ ነው።
በሕብረት ባንክ ደግሞ መግዣው 121 ብር ሲሆን መሸጫው 123 ብር ከ4200 ሳንቲም ነው።
(ከዶላር ውጭ የሌሎች ሀገራት ገንዘብ ምንዛሬ ከላይ ተያይዟል)
@tikvahethiopia
ከሰሞኑን የዶላር ምንዛሬ ዋጋ ጭማሪ እያሳየ ነው።
ባለፉት በርካታ ቀናት በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አንድ የአሜሪካ ዶላር መግዣው 119 ብር ከ2044 ሳንቲም ፤ መሸጫው ደግሞ 121 ብር ከ5885 ሳንቲም ነበር።
ካለፈው ቅዳሜ አንስቶ ግን የምንዛሬ ዋጋው ጨምሯል።
ባንኩ በመግዣ ዋጋው ላይ ከ3 ብር በላይ ጭማሪ በማድረግ 122 ብር ከ5986 ሳንቲም አስገብቶታል።
መሸጫውም በተመሳሳይ ከ3 ብር በላይ ጨምሮ 125 ብር ከ0506 ሳንቲም ገብቷል።
ከግል ባንኮች በአቢሲንያ ባንክ ዶላር 123 ብር ከ0001 ሳንቲም እየተገዛ በ125 ብር ከ4601 ሳንቲም እየተሸጠ ነው።
በሕብረት ባንክ ደግሞ መግዣው 121 ብር ሲሆን መሸጫው 123 ብር ከ4200 ሳንቲም ነው።
(ከዶላር ውጭ የሌሎች ሀገራት ገንዘብ ምንዛሬ ከላይ ተያይዟል)
@tikvahethiopia