TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
58.9K photos
1.5K videos
211 files
4.07K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#Urgent🚨

እየደበደቡት ጥርሱን አውልቀውታል። ሙሉውን ቪዲዮ ለመመልከት ሰቀጠጠኝ። አጋቾቹ 800 ሺሕ ብር ጠይቀዋል” - እርዱኝ ያሉ የታጋች ወንድም

በባህር ዳር ዩቨርቨሲቲ የ4 ዓመት የመካኒካል ኢንጅነሪንግ ተማሪ የነበረው ወጣት ሙላት ተቀባ አስረሴ በሊቢያ በአጋቾች ተይዞ በድብደባ አካላዊ ጉዳት እየደረሰበት መሆኑን ቤተሰቦቹና የቅርብ ሰዎቹ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገለጹ።

የታጋች ወንድም አቶ ደጉ ተቀባ አስረሴ፣ “ ጎንደር ጦርነት ስላለ ገንዘቡን ለመላክ ተንቀሳቅሶ መስራት አልተቻለም። ቦታ ነበረችኝ ለመሸጥ እንኳ በዚሁ በጸጥታው ችግር ገዢ የለም። እባካችሁ ወንድሜን አድኑልኝ ” ሲሉ ተማጽዋል።

ታጋቹ ያለበትን ሁኔታ ሲገልጹም፣ “ እየደበደቡት ጥርሱን አውልቀውታል። ሙሉውን ቪዲዮ ለመመልከት ሰቀጠጠኝ። አጋቾቹ 800 ሺሕ ብር ጠይቀዋል። ገንዘቡን መላክ አልቻልኩም። ወላጆቻችን አዛውንቶች ናቸው ” ነው ያሉት።

በሰሜን ጎንደር ዞን ጠለምት ወረዳ አቃቢ ሕግ በመሆን ተቀጥረው እንደሚሰሩ ገልጸው፣ አሁን ባላቸው አነስተኛ ደመወዝ የተጠየቀውን ገንዘብ ማሟላት እንደማይችሉ አስረድተዋል።

“ አጋቾቹ ‘ቶሎ ካላክ እንገለዋለን እያሉኝ’ ነው ” ያሉቴ አቶ ደጉ፣ ወጣቱ ዘንድሮ ተመራቂ እንደነበር፣ ወደ አውሮፓ ድንበር ሊያቋርጥ ሲል ከታገተ ወራቶች እንዳስቆጠረ ገልጸዋል።

በባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ትምህርታቸውን እየተከታተሉ የሚገኙ ሁለት የታጋቹ የቅርብ ጓደኞች በበኩላቸው፣ ተማሪ ሙላት ታግቶ እየተደበደበ እንደሆነ፣ ከዩኒቨርሲቲው ደብዳቤ አጽፈው ገንዘብ እያሰባሰቡ መሆኑን ነግረውናል።

ከጓደኞቹ አንዱ በሰጠው ቃል፣ “ ተማሪ ሙላት ወደ አውሮፓ ሊወጣ ሲል ታግቶ ይገኛል። እንደኛ ተመራቂ ነው የነበረው በዚህ ዓመት። የሰሜን ጎንደር ዞን ጠለምት ወረዳ ነዋሪ ነው ” ብሏል።

የታጋቹ ወንድምና ጓደኞቹ፣ ታጋቹ በአጋቾች እየደረሰበት ያለውን ስቃይ የሚያሳይ ቪዲዮ የላኩ ሲሆን፣ ከላይ ተያይዟል።

መርዳት ለምትሹ 1000281326795 የአቶ ደጉ ተቀባ አስረሴ የንግድ ባንክ ሒሳብ ቁጥር ነው። አቶ ደጉን በዚህ ስልክ 0931494332 ማግኘት ይቻላል።

የፖሊ ግቢ ተማሪዎችም በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 1000660181036 እና በአቢሲንያ ባንክ 209476797 አካውንት በመክፈት ድጋፍ እያሰባሰበ ነው።

#TikvahErhiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
#ብርሃን_ባንክ
#በቀላሉ_ይቀበሉ!

ከውጪ ሃገራት የሚላክልዎትን ገንዘብ በባንኩ የስዊፍት ኮድ (BERHETAA) እና ከብርሃን ጋር በሚሰሩ አለምአቀፍ የገንዘብ አስተላላፊዎች #ሪያ #ዳሃብሽል #ዌስተርን_ዩኒየን #መኒግራም #ትራንስ_ፋስትና #ወርልድ_ረሚት በኩል በቀላሉ ይቀበሉ!
#moneytransfer #Stressfreebanking #berhanbank #bank #finance #bankinethiopia

ከታች የሚገኙትን ሊንኮች በመጫን የማህበራዊ ድህረ-ገጾቻችንን ይቀላቀሉ!
➡️ Facebook
➡️ Telegram
➡️ Instagram
➡️ Twitter
➡️ LinkedIn
➡️ YouTube
#InfinixEthiopia

የኢንፊኒክስን Note, Hot, Zero ስማርት ስልኮችን እና የኢንፊኒክስ TVን ሲገበያዩ አብሮት ካለ ወዳጅ ዘመድ ወይም ጓደኛ ጋር በመረጡት ስፍራ ፎቶ በመነሳት #InfinixEthiopia የሚለውን ሃሽ ታግ በመጠቀም የማህበራዊ ገጾት ላይ በመለጠፍ የዛንዚባር የቢዝነስ ክላስ ደርሶ መልስ የአውሮፕላን ቲኬት ፣ የኢንፊኒክስ ስማርት ቲቪ ፣ የኢንፊኒክስ ላፕቶፕ እንዲሁም ሌሎች አጓጊ ሽልማቶችን ያሸንፉ፡፡

መመሪያ

1. የኢንፊኒክስ ኢትዮጵያን ፌስ ቡክ ፣ ኢንስታግራም እና ቲክቶክ ገጾችን ፎሎው ያድርጉ፡፡
2. የተነሱትን ፎቶ በመረጡት ማህበራዊ ሚዲያ ሲለጥፉ የኢንፊኒክስ ኢትዮጵያን ገፅ ከፖስቶት ጋር ታግ ያድርጉ፡፡
3. #InfinixEthiopia የሚለውን ሃሽታግ መጠቀሞን አይርሱ፡፡

Tag ሲያደርጉ ለ Facebook @InfinixMobileEthiopia ፣ ለ Instagram @infinixethiopia ለ TikTok @Infinixet እና ለ Telegram @Infinixeth ሜንሽን ማድረግ እንዳይረሱ።
#MPESASafaricom

ለማይቋረጥ የኢንተርኔት ጌም ወሳኙ የማይቋረጥ ኢንተርኔት ነው ፤ አሁኑኑ የሳፋሪኮምን የ4G ዋይ ፋይ ጥቅል ከM-PESA ሳፋሪኮም mini app በመግዛት በጌማችን እንፍታታ!


#SafaricomEthiopia
#FurtherAheadTogether
“ የትምህርት ጥራት ከዓመት ወደ ዓመት እየወረደ መጥቷል ” - ሰሎሞን አብርሃ (ዶ/ር)

የአሜሪካ ኤምባሲ በኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ በኩል በኢትዮጵያ ለራስ ገዝ ዩኒቨርሲቲዎች ማጠናከሪያ የሚሆን 522 ሺሕ ዶላር የድጋፍ ስምምነት አድርጓል።

የድጋፍ ስምምነቱ በኢትዮጵያ ዘጠኝ ዩኒቨርሲቲዎች በቀጣይ ራስ ገዝ እንዲሆኑ የሚያርችላቸውን ሁኔታዎች ለማመቻቸት የሚረዳ መሆኑ ተገልጿል።

ስለስምምነቱ ምንነት የጠየቅናቸው የኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ ፕሬዜዳንት በላይ ካሳ (ፕ/ር)፣ “ ዛሬ ከአሜሪካ ኤምባሲ ጋር የተፈራረምነው ስምምነት በኢትዮጵያ ዘጠኝ የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎችን ወደ ራስ ገዝነት እንዲሸጋገሩ ቅድመ ዝግጅት የማድረጊያ የሚሰጥ ድጋፍ የሚይዝ ነው ” ብለዋል።

የከፍተኛ ትምህርት ተቋምን ወክለው በመርሃ ግብሩ የተገኙት ሶሎሞን አብርሃ (ዶ/ር) በበኩላቸው፣ የድጋፍ ስምምነቱ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በመቀጠል ዘጠኝ ዩኒቨርሲቲዎች አቅማቸውን አጠናክረው በአጭር ጊዜ ውስጥ ወደ ራዝ ገዝነት ለማሸጋገር እንደሚረዳ አስረድተዋል።

ዘጠኙ ዩኒቨርሲቲዎች መቼ ራስ ገዝ እንደሚሆኑ ማብራሪያ እንዲሰጡ ሲጠየቁም፣ ዩኒቨርሲቲዎቹ እንደዬ አፈጻጸማቸው ከጊዜ ወደ ጊዜ ራስ ገዝ እንደሚሆኑ፣ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሽግግር ጊዜ በዚህ አመት እንደሚጠናቀቅ፣ በ2018 ዓ/ም ከዘጠኙ ዩኒቨርቲዎች ውስጥ የተወሰኑት ወደዚሁ ጉዞ እንደሚገቡ አመላክተዋል።

ጥናት እንደሚያመለክተው፣ “ የትምህርት ጥራት ከዓመት ወደ ዓመት እየወረደ መጥቷል ” ብለው፣ “ የተሰሩት ሥራዎች አመርቂና አበረታች ቢሆንም የዩኒቨርሲቲዎች መስፋፋት እንዳለ ሆኖ ትምህርት ጥራት ላይ ግን ያለው ውጤት በጣም ስብራት ያለበት ነውና መታረም ይገባዋል ” ሲሉ ገልጸዋል።

“ በአጠቃላይ በብዙ ፋክተሮች አስተዋፅኦ ያደረጉበት ጉዳይ ነው የትምህርት ጥራት መጓደል። አንዱና ዋነኛ ተብሎ የተወሰደው ደግም የገነባናቸው ዩኒቨርሲቲዎች ብቃታቸው፣ ውጤታማነታቸው፣ ቀልጣፋነታቸው በጣም ችግር ላይ ነው ” ሲሉ ተናግረዋል።

“ ብቁና ተወዳዳሪ ትምህርት ተቋም አልፈጠርንም። ብቁ ተወዳዳሪ ተቋማትን ለመፍጠር ደግሞ ከሚደረጉ ዘርፈ ብዙ ሥራዎች ውስጥ አንዱና ዋነኛው ተቋማትን ራስ ገዝ ማድረግ ነው ” በማለት አክለዋል።

ዩኒቨርቲዎች ራስ ገዝ ሲሆኑ የትምህርት ጥራት፣ ጥሩ ምርምር እንደሚኖር ያስረዱት ሰለሞን (ዶ/ር)፣ አዲስ አበባ የመጀመሪያው ራስ ገዝ ዩኒቨርሲቲ መሆኑን በማስታወስ ዩኒቨርሲቲዎችን በአንድ ጀንበር ራስ ገዝ ማድረግ ስለማይቻል የሁሉም ርብርብ እንደሚያሻ አስገንዝበዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#AddisAbaba

" በቦታው ተመሳሳይ ችግር እንዳያጋጥም ምክረ ሃሳብ ቀርቧል። ያቀረብነው ምክረ ሃሳብ ቦታው እንደ አዲስ በመልሶ ማልማት እንዲለማ ነው " - የእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን

ከአንድ ወር ባነሰ ጊዜ ውስጥ በትላንትናው ዕለት ለሁለተኛ ጊዜ የእሳት አደጋ ያጋጠመው በአዲስ አበባ ከተማ መርካቶ ገበያ የሚገኝ አካባቢ፤ " በመልሶ ማልማት እንዲለማ " ምክረ ሃሳብ ቀረበ።

ምክረ ሃሳቡን ያቀረበው የአዲስ አበባ ከተማ የእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ነው።

ትላንት እሁድ ህዳር 8/2017 እኩለ ቀን ገደማ የእሳት አደጋ የደረሰበት የመርካቶ ገበያ ስፍራ፤ በተለምዶ " ድንች ተራ " የሚል ስያሜ ያለው ነው።

ስፍራው ከሁለት ሳምንት በፊት በተመሳሳይ አደጋ ከፍተኛ ጉዳት ደርሶበት ከነበረው " ነባር የገበያ ማዕከል " በቅርብ ርቀት ላይ የሚገኝ ነው።

የእሁዱ ቃጠሎ የደረሰበት ስፍራ፤ " በነባር የገበያ ማዕከል " ላይ የሚነግዱ ነጋዴዎች ንብረቶቻቸውን የሚያስቀምጡበት መጋዘን እንደነበር የአካባቢው ነዋሪዎች " ለኢትዮጵያ ኢንሳይደር " ድረገጽ ተናግረዋል። 

የእሳት አደጋው " ጌሾ ግቢ " ተብሎ በሚጠራው ስፍራ ከሚገኘው መጋዘን በተጨማሪ በአቅራቢያው የሚገኙ መደብሮች እና መኖሪያ ቤቶች ላይ ውድመት አድርሷል። 

ትላንት በአደጋው ወቅት በርካታ የአካባቢው ነዋሪዎች እና ነጋዴዎች የእሳት ቃጠሎው ወደ ሌሎች የገበያ ማዕከሎች እና መደብሮች እንዳይዛመት በስጋት ሲያስተውሉ ነበር።

የተወሰኑ የአካባቢው ወጣቶች እና ከእሳት አደጋ ተከላካይ ሰራተኞች ጋር በመሆን ቃጠሎውን በቁጥጥር ስር ለማድረግ ርብርብ ሲያደርጉ ነበር።

በአንድ ሰዓት ተኩል ውስጥ በቁጥጥር ስር የዋለውን የእሳት አደጋ ለመከላከል፤ ሰባት የውሃ ቦቴዎች እና 18 የአደጋ መቆጣጠር ተሽከርካሪዎች ተሰማርተው እንደነበር የአዲስ አበባ ከተማ የእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ንጋቱ ማሞ ለ " ኢትዮጵያ ኢንሳይደር " ድረገጽ ገልጸዋል።

ከእነዚህ ተሽከርካሪዎች በተጨማሪ የኮሚሽኑ እና የቀይ መስቀል ማህበር አምቡላንሶች፤ በአደጋው ጉዳት የደረሰባቸውን ግለሰቦች ወደ ህክምና ተቋማት በመውሰድ ተሳትፈዋል። 

በትላንቱ የእሳት አደጋ ሶስት የአካባቢው ነዋሪዎች እና ሁለት የኮሚሽኑ ሰራተኞች ላይ ቀላል ጉዳት ደርሷል።

ከሁለት ሳምንት በፊት በዚሁ አካባቢ በደረሰው ተመሳሳይ አደጋ፤ ዘጠኝ ሰዎች መጎዳታቸውን የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ማስታወቁ አይዘነጋም።

የትላንቱ አደጋ ከደረሰበት ጊዜ ጀምሮ እስከ ዛሬ ረፋድ ድረስ፤ የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ባልደረቦች አካባቢውን በገመድ በማጠር ጥበቃ ሲያደርጉ ነበር።

ክልከላውን አልፈው ለመግባት ሲሞክሩ የነበሩ ነዋሪዎች እና ነጋዴዎችን፤ የፖሊስ አባላቱ ወደ ቦታው እንዳይጠጉ በኃይል ሲከላከሉም ነበር።

ፖሊሶች እና የእሳት አደጋ ተከላካይ ሰራተኞች ከመድረሳቸው በፊት ግን የተወሰኑ ነጋዴዎች ንብረቶቻቸውን ከቃጠሎ ማትረፍ ችለዋል።

በዚህም ምክንያት በአደጋው " የከፋ ጉዳት " አለመድረሱን አቶ ንጋቱ አስረድተዋል።

ቃጠሎው በቁጥጥር ስር ከዋለ በኋላም፤ ነጋዴዎች ንብረታቸውንን ከአካባቢው ለማራቅ ሲጥሩ ታይተዋል። 

ነጋዴዎች፤ አካባቢው በተደጋጋሚ የእሳት አደጋ እያጋጠመው በመሆኑ ምክንያት " መንግስት ከስፍራው ያነሳናል " የሚል ከፍተኛ ስጋት አላቸው።

የአዲስ አበባ ከተማ የእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አካባቢውን " ለአደጋ ተጋላጭ " በሚል አስቀድሞ መለየቱን የገለጹት አቶ ንጋቱ፤ በቦታው ተመሳሳይ ችግር እንዳያጋጥም ምክረ ሃሳብ ማቅረቡን አስረድተዋል። 

" ያቀረብነው ምክረ ሃሳብ ቦታው እንደ አዲስ በመልሶ ማልማት ወይም የአደጋ ደህንነት መስፈርትን ቧሟላ፣ ደረጃውን በጠበቀ መንገድ መገንባት ይኖርበታል ነው። ምክረ ሃሳቡን ተቀብሎ በመልሶ ማልማት ለመስራት የተጀመሩ ስራዎች እንዳሉ መረጃው አለን። በሂደት ላይ ነው ያለው። ታምኖበታል። ምን አልባትም በዚህ አመት ሊጀመር ይችላል ብዬ አስባለሁ " ሲሉ ተናግረዋል።

ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የኢትዮጵያ ኢንሳይደር ድረገጽ ነው።

#AddisAbaba #Merkato #EthiopiaInsider

@tikvahethiopia
#NewsAlert

የአዲስ አበባ ካቢኔ ሁለት አጀንዳዎች ላይ ውሳኔ ማሳለፉ ተሰምቷል።

ካቢኔው " በኮሪደር ልማት አካባቢ ያሉ የግል ባለይዞታዎች የቅድሚያ የማልማት ጥያቄዎች ፈጣን ምላሽ የሚሰጥበት አግባብ፣ የተጀመሩ ግንባታዎች የቦታ ማስፋፊያ ጥያቄዎች፣ ለኃይማኖት ተቋማት እና የባለ 5 ኮከብ ሆቴሎች ግንባታ የቦታ ጥያቄዎች ላይ በመወያየት ከማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳቸዉ አኳያ በመመርመር እንዲፈቀድላቸውና ወደ ልማት እንዲገቡ " ሲል ውሳኔ አሳልፏል።

ሌላው የአዲስ አበባ ከተማ የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች ለማስተዳደርና ለማልማት የወጣው ረቂቅ ደንብን መርምሮ ለማህበረሰቡ ከሚኖራቸው የጎላ አገልግሎት አኳያ በወጣቶችና ስፖርት ቢሮ አስተባባሪነት እንዲፈፀም መወሰኑን ታውቋል።

@tikvahethiopia
#ጥቆማ

የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የበጎ ፍቃድ አገልግሎት ጥሪ ማስታወቂያ አውጥቷል።

ኢትዮጵያ በቀጣይ የካቲት ወር በአፍሪካ ህብረት ጉባኤ የሚሳተፉ እንግዶችን ለመቀበል ዝግጅት እያደረገች ነው።

የኢ.ፌ.ዲ.ሪ. የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ከአቀባበል እስከ አሸኛኘት ባለው የመስተንግዶ መርሃግብር በጎ ፍቃደኛ ፕሮቶኮል ካዴቶችን በመቀበል አሰልጥኖ በተለያዩ የፕሮቶኮል ሥራዎች ላይ ማሰማራት እንደሚፈልግ ገልጿል።

በመሆኑም ፦

- የእንግሊዘኛ፣
- የፈረንሳይኛ
- የዓረብኛ ቋንቋዎችን መናገርና መጻፍ የሚችሉ እና ዕድሚያቸው ከ18-30 የሆነ ኢትዮጵያዊና ትውልደ ኢትዮጵያዊያን ከህዳር 12 ቀን 2017 ዓ.ም. ባሉት 5 ተከታታይ የሥራ ቀናት ውስጥ እ እንዲመዘገቡ ጥሪ ቀርቧል።

ምዝገባው በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ዋናው መ/ቤት በአካል በመገኘት ነው የሚከናወነው።

ተመዝጋቢዎች ለምዝገባ ሲመጡ የትምህርት ማስረጃቸውን እና ማንነታቸውን የሚገልፅ መታወቂያ ይዘው እንዲቀርቡ ተብሏል።

ሚኒስቴሩ " የአገራት መሪዎች፣ የዓለምአቀፍና ቀጠናዊ ተቋማት ኃላፊዎች እንዲሁም ተፅዕኖ ፈጣሪ ግለሰቦች በሚሳተፉበት የአህጉራችን ትልቁ ጉባዔ ላይ በጎ ፍቃደኛ ፕሮቶኮል በመሆን የዚህ ታሪክ አካል ሆናችሁ አገራችሁን ያለ ክፍያ በኩራት እንድታገለግሉ " ሲል ጥሪ አቅርቧል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#ማስታወሻ #የኢትዮጵያአየርመንገድ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ በTRAINEE CABIN CREW ፣ በSENIOR ACCOUNTANT I እንዲሁም በሌሎች ዘርፎች ማስታወቂያ አውጥቷል።

ለTRAINEE CABIN CREW በኢትዮጵያ ሀገር አቀፍ የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና ቢያንስ (ዝቅተኛው) 200 ነጥብ ያስመዘገበ ለማመልከት ብቁ ነው።

የዕድሜ ገደቡ ከ19 እስከ 30 ዓመት ነው።

ቁመት ቢያንስ 1.58 ሜትር እና 212 ሴ.ሜ የሆነ ክንድ ለሴት እንዲሁም ለወንድ ቢያንስ 1.70 ሜትር ቁመት መሆን አለበት።

ምዝገባ የተጀመረ ሲሆን እስከ ህዳር 12/2017 ዓ/ም ድረስ ይቆያል።

ምዝገባው ፦
- በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ (አዳማ)
- አዲስ አበባ (በኦንላይን ልክ ማመልከቻው ሲከፈት ይፋ ይደረጋል)
- አምቦ ዩኒቨርሲቲ (አምቦ)
- አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ (አርባ ምንጭ)
- አሶሳ ዩኒቨርሲቲ (አሶሳ)
- ባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ (ባህር ዳር)
- ወሎ ዩኒቨርሲቲ (ደሴ)
- ድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ (ድሬዳዋ)
- ጋምቤላ ዩኒቨርሲቲ ( ጋምቤላ)
- ጎንደር ዩኒቨርሲቲ (ጎንደር)
- ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ (ሀዋሳ)
- ጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ (ጅግጅጋ)
- ጅማ ዩኒቨርሲቲ (ጅማ)
- መቐለ ዩኒቨርሲቲ (መቐለ)
- ወለጋ ዩኒቨርሲቲ (ነቀምቴ)
- መደወላቡ ዩኒቨርሲቲ (ሮቤ)
- ሰመራ ዩኒቨርሲቲ (ሰመራ)
- ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ (ወልቂጤ) ይከናወናል።

ተጨማሪ መረጃዎች ለማግኘት እና ለማመልከት 👇
https://corporate.ethiopianairlines.com/AboutEthiopian/careers/vacancies

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#AddisAbaba " ያለደረሰኝ አትሽጡ አልን እንጂ እቃ እንወርሳለን ያለ አካል የለም " -የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ " በከተማዋ በርካታ ነጋዴዎች በግብር ከፋይነት ተመዝግበው ደረሰኝ የማይሰጡ በመሆናቸው እና ችግሩም በጣም እየሰፋ በመሆኑ ወጥነት ባለው መንገድ ህጉን እንዲያከብሩ እና ወደስርዓት እንዲገቡ ለማድረግ እየሰራው ነው " ሲል ገልጿል። ቢሮው የታክስ ኢንተለጀንስ…
የዛሬው የመርካቶ ገበያ  ውሎ ምን ይመስላል ?

በዛሬው እለት በመርካቶ የሚገኙ የተለያዩ የገበያ ማዕከላት ተዘግተው መዋላቸውን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ባደረገው ቅኝት ማየት ችሏል።

የመርካቶ ገበያም ከዚህ ቀደም ከነበረው የንግድ እንቅስቃሴ ተቀዛቅዞ መዋሉን ነጋዴዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

ተዘግተው ከዋሉት የገበያ ማዕከላት መካከል
ሚሊተሪ ተራ ፤ ዱባይ ተራ ፤ አድማስ እና አመዴ ገበያ አካባቢ የሚገኙ ሱቆች ይገኙበታል።

ነጋዴዎች ሱቆቻቸውን የዘጉት ከደረሰኝ ጋር በተገናኘ ውዝግብ መሆኑ ታውቋል።

ነጋዴዎቹ ዛሬ ጠዋት በርካታ የንግድ ሱቆች ዝግ እንደነበሩ የተናገሩ ሲሆን በከሰአቱ የገበያ ሁኔታ አንዳንድ ሱቆች እንደተከፈቱ ገልፀዋል።

የቲክቫህ ኢትዮጵያ አባላት ከሰዓት በኋላ ባደረጉት ቅኝት የጣና ገበያ ፣ ሲዳሞ ተራ እና ቦምብ ተራ አካባቢ የንግድ እንቅስቃሴዎች እንደታዩበት ታዝበዋል።

በተወሰነ መልኩም ወደ ሸማ ተራ እና መሃል መርካቶ አካባቢዎች መደበኛ የንግድ እንቅስቃሴዎችን መመልከት ተችሏል።

ሆኖም ግን በሸማ ተራ ፣ ድር ተራ እና ሰሀን ተራ አካባቢዎች የነበረው የንግድ እንቅስቃሴ የተቀዛቀዘ መሆኑን ነጋዴዎች ነግረውናል።

በዛሬው እለት በሰሀን ተራ አካባቢ በግምት 8 ሰዓት ገደማ ላይ ነጋዴዎች " አነስተኛ ነው " ያሉት እሳት ተነስቶ እንደነበር ጠቁመዋል። ነገር ግን እሳቱ ሳይስፋፋ ወዲያው በነጋዴው ርብርብ እንደጠፋ ጠቅሰዋል።

በሰሀን ተራ አካባቢ የሚገኙት ሱቆች በአክሲዮን የገበያ ማዕከልን ለመገንባት ሱቆቻቸውን ለቀው እየወጡ እንደሆነም ካነጋገርናቸው ነጋዴዎች ተረድተናል።

በዚህ አካባቢ የሚገኙት ነጋዴዎች ሱቃቸውን የለቀቁት በስምምንነት መሆኑንም ተናግረዋል።

የተለቀቁትም ሱቆች ከወረዳው የመሬት የልማት አስተዳደር ጽ/ቤት ማህተም የተደረገበት " ታሽጓል " የሚል ጽሑፍ ተለጥፎባቸዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ያነጋገራቸው የተለያዩ የመርካቶ ነጋዴዎች በሸማ ተራ ከተከሰተው የእሳት አደጋ በኋላ " ስራ የለም " ሲሉ ገልፀዋል።

በተጨማሪም ያለ ደረሰኝ ሲነግዱ የተገኙ ነጋዴዎች ላይ ይጣላል የተባለው ቅጣት የተጋነነ መሆኑን ጠቅሰዋል።

ሱቆቹ የተዘጉት " ግብይቶች ሁሉ በደረሰኝ ይካሄዱ " የሚለው ተቃውሞ እንዳልሆነ አንድ ስሙ እንዳይገለፅ የጠየቀ የመረጃ ምንጭ ገልጿል።

የመረጃ ምንጩ " ግብይቶች በደረሰኝ የሚደረጉ ቢሆንም ተቆጣጣሪ አካላት የተሸጡ እቃዎችን የሚያሳይ ደረሰኝ በሚጠይቁበት እና በምናሳያቸው ወቅት ከሚገባው በታች ነው የቆረጣችሁት በማለት በ6 ወር ሰርተነው የማናቀውን 100 ሺህ ቅጣት ጥለውብን ይሄዳሉ " በማለት አማረዋል።

በአንፃሩ አንድ ሌላ ነጋዴ እንደገለፁት ከንግድ ስራ መንግስት ማግኘት የሚገባው ገቢ ቢኖርም ይህ አሰራር የማይመቻቸው እና ደረሰኝ የማይቆርጡ ነጋዴዎች እንዳሉ ጠቁመዋል።

ከዚህ ቀደም ቃላቸውን ለቲክቫህ የሰጡት የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ የታክስ ኢንተለጀንስ እና የምርመራ ዳይሬክተር አቶ ተስፋዬ ነጋሽ  " መርካቶ በባህሪው ብዙ የክልል ግብር ከፋዮች የሚያለቅሱበት ቦታ ነው የሌሎች ክፍለ ከተሞች ግብር ከፋዮችም ቅሬታ ያቀርባሉ ደረሰኝ አይሰጡም በሚል ትልቅ ችግር ስላለበት ትኩረት ተደርጎበት ያለ ነው እንጂ አዲስ አይደለም " የሚል ምላሽ ሰጥተው ነበር።

ዳይሬክተሩ አክለውም " ቦታው በልዩ ሁኔታ (በግብር አሰባሰብ) በመንግስት ትኩረት ተደርጎበት ሊሰራበት የሚፈለግ አካባቢ ነው ነገር ግን ከአሰራር አንጻር በሚፈለገው ልክ ማሳካት አልተቻለም " ማለታቸው ይታወሳል።

#TikvahEthiopiaFamilyAddisAbaba

@tikvahethiopia
#Ethiopia #USA

የአሜሪካ ከፍተኛ ባለስልጣናት ኢትዮጵያ ይገኛሉ።

በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ማሲንጋን ጨምሮ፣ የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ምክትል ረዳት ሚኒስትር ስፔራ፣ የአሜሪካ መከላከያ ሚኒስቴር ምክትል ረዳት ፀሀፊ ፋሬል እና ሌሎችም የተካተቱበት ልዑክ ከሀገር መከላከያ ሚኒስትር ኢንጂነር አይሻ መሐመድ ጋር መክረዋል።

በወቅቱም ኢንጂነር አይሻ ፤ ኢትዮጵያ ከአሜሪካ ጋር ላላት የረዥም ጊዜ ወታደራዊ ግንኙነት ትልቅ ዋጋ እንደምትሰጥ እንደገለጹና ይህንኑ ትብብር የበለጠ ለማጠናከር ኢትዮጵያ ፍላጎት እንዳለት መናገራቸውን ሀገር መከላከያ ሰራዊት ገልጿል።

የአሜሪካ ኤምባሲ እንዳለው ከሆነ ደግሞ በምክክሩ ላይ #በአማራ እና #ኦሮሚያ ያለው ግጭት ጉዳይ ተነስቷል።

ሌላው የቀድሞ ተዋጊዎችን ዲሞብላይዝ በማድረግ ወደ ማህበረሰቡ መልሶ ለመቀላቀልና ለማቋቋም ስለሚደረገው ስራ (DDR) ውይይት ተደርጓል።

በኢትዮጵያ እና በአሜሪካ መካከል ያለውን ወታደራዊ ትብብር በማጠናከር ላይም ትኩርት ያደረገ ምክክር መደረጉን ከኤምባሲው የተገኘ መረጃ ያሳያል።

#USA #USEmbassy

@tikvahethiopia