TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.2K photos
1.5K videos
211 files
4.1K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#ሳህለወርቅ_ዘውዴ

“ አቅጣጫዬን አሳይቻለሁ፤ በዛ መሠረት ለመስራት ሞክሬአለሁ ” - የቀድሞ የኢትዮጵያ ፕሬዜዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ

በበጎ ፈቃድ የተሰባሰቡ ሴቶችና የሴት መሪ ድርጅቶች በጋራ በመሆን በቅርቡ የሥራ ዘመናቸውን ላጠናቀቁት ለቀድሞዋ ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ በሸራተን አዲስ ሆቴል ዛሬ የምስጋና ፕሮግራም አዘጋጅተው ነበር።

በዚሁ መርሀ ግብር አቶ አባዱላ ገመዳ፣ አምባሳደር ተሾመ ቶጋ፣ ተፅዕኖ ፈጣሪ ሰዎች ፣ የሴቶች ማኀበራት መሪዎችና በሌሎች የሥራ ዘርፎች ላይ የተሰማሩ ጥሪ የተደረገላቸው በርካታ ሴቶች ተገኝተዋል።

ፕሮግራሙ ከተዘጋጀበት ዓላማ አኳያም ለቀድሞ ፕሬዜዳንቷ “ በጣም ውድ ” እና “ ከኢትዮጵያ እንዳይወጣ ” የተባለለት የሀገር ቅርስ ጭምር የተቀረጸበት የስዕል ስጦታ የተበረከተላቸው ሲሆን፣ “ ከሚገባው ቦታ አስቀምጠዋለሁ ” በማለት ስጦታውን ላበረከቱላቸው ምስጋና አቅርበዋል።

በመርሀ ግብሩ ባደረጉት ንግግር ደግሞ፣ “ የዛሬ 6 ዓመት ገደማ ያደረኩት ንግግር የ18 ደቂቃ ነበር። ጥቂት ጊዜ ነው የነበረኝ ለመዘጋጀት። የደረሰብኝም አልገባኝም ነበር ” ሲሉ አስተውሰዋል የቀድሞ ፕሬዜዳንቷ።

“ ሴቶች የሚለውን ቃል 29 ጊዜ፣ ሰላም የሚውን ቃል 30 ጊዜ ተናግሬ ነበር ” ያሉት ሳህለወርቅ፣ “ ለራሴ አልዋሽም፣ ለሌላም አልዋሽም። አቅጣጫዬን አሳይቻለሁ፣ በዛ መሠረት ለመስራት ሞክሬአለሁ ” ሲሉም አክለዋል።

“ ተያይዘን መስራት አለብን። ጡረታ የሚባለውን ነገር አሁን ነው የጀመርኩት ግን እረፍት የለም። ጡረታም ተወጥቶ እንደማይታረፍ የቀደሙኝ እያሳዩኝ ነው። ላደረጋችሁልኝ በጣም ነው የማመሰግነው ” ነው ያሉት።

የቀድሞዋ ፕሬዜዳንት ከዚህ ቀደም፣ “ ‘የሰው ልጅ ሆዱ ሲከፋው ጊዜም እንደ ሰው ሲገፋው፣ መሄጃ መውጫ ሲጠፋው ዝምታ ብቻ ነው ተስፋው’ ይላል ማህሙድ ‘ዝምታ ነው መልሴ’ን ሲያዜም ” ብለው፣ “ አንድ ዓመት ሞከርኩ ” የሚል ፅሑፍ በX (ቲዊተር) ገጻቸው አጋርተው ነበር።

በወቅቱም ከፍተኛ መነጋገሪያ ሆኖ ነበር። ይህንን ምስጢር አዘል የሆነ ፅሑፋቸውን በተመለከተ ግን ዛሬም የሰጡት ማብራሪያ የለም።

የቀድሞዋ ፕሬዜዳንት ሳልለወርቅ ዘውዴ የመጀመሪያዋ ሴት የኢትዮጵያ ፕሬዜዳንት ሆነው ለ6 ዓመታት 4ኛ የኢትዮጵያ ፕሬዜዳንት ሆነው ሲያገለግሉ ቆይተው፣ የሥልጣን ዘመናቸው በመጠናቀቁ ኃላፊነታቸውን ለፕሬዚዳንት አምባሳደር ታዬ አጽቀስላሴ ማስረከባቸው የቅርብ ጊዜ ትውስታ ነው።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
#InfinixEthiopia

የኢንፊኒክስ ስማርት ስልኮች የሆኑትን ሆት 40 ፣ ኖት 40 ፣ ዜሮ 40 እና የኢንፊኒክስ ስማርት TVን ሲገበያዩ የሽልማት ኩፖን ይውሰዱ፡፡ አብሮት ካለ ወዳጅ ዘመድ ወይም ጓደኛ ጋር በመረጡት ስፍራ ፎቶ በመነሳት #InfinixEthiopia የሚለውን ሃሽታግ በመጠቀም የማህበራዊ ገጾት ላይ ይለጥፉ የዛንዚባር የቢዝነስ ክላስ ደርሶ መልስ የአውሮፕላን ቲኬት ፣ የኢንፊኒክስ ስማርት ቲቪ ፣ የኢንፊኒክስ ላፕቶፕ እንዲሁም ሌሎች አጓጊ ሽልማቶችን ያሸንፉ፡፡

መመሪያ

1. የኢንፊኒክስ ኢትዮጵያን ፌስ ቡክ ፣ ኢንስታግራም እና ቲክቶክ ገጾችን ፎሎው ያድርጉ፡፡
2. የተነሱትን ፎቶ በመረጡት ማህበራዊ ሚዲያ ሲለጥፉ የኢንፊኒክስ ኢትዮጵያን ገፅ ከፖስቶት ጋር ታግ ያድርጉ፡፡
3. #InfinixEthiopia የሚለውን ሃሽታግ መጠቀሞን አይርሱ፡፡

Tag ሲያደርጉ ለ Facebook @InfinixMobileEthiopia ፣ ለ Instagram @infinixethiopia ለ TikTok @Infinixet እና ለ Telegram @Infinixeth ሜንሽን ማድረግ እንዳይረሱ።
ሕብር ሞባይል ባንኪንግ- አሁን የበለጠ ዘምኗል! - ቀሏል!


ውድ ደንበኞቻችን! ባንካችን የሕብር ሞባይል ባንኪንግ መተግበሪያ ላይ አዳዲስ አገልግሎቶችን ከጥብቅ የደህንነት ማሻሻያዎች ጋር ይዞላችሁ  ቀርቧል፡፡  እጅግ ዘምኖ የቀረበውን ሕብር የሞባይል መተግበሪያ ሲጠቀሙ  ፡-
•  በቀላሉ ከውጭ ሀገር የአገልግሎት ወይም የንግድ ክፍያን መቀበል
•  ስካን በማድረግ ክፍያ መፈፀም
•  ክፍያ ለመቀበል የራስ QR ኮድ መፍጠር እና ለሌሎች ማጋራት
•  የሞባይል ጥቅል አገልግሎት በቀላሉ መግዛት
•  አንድን ሂሳብ በቋሚነት መምረጥ እና መጠቀም
•  ተጨማሪ ስልክ/ኢሜይል መጠቀም one time password እንዲደርሶ ማድረግ ይችላሉ፡፡

የተሻሻለውን መተግበሪያ ከጉግል ፕሌይ ወይም አፕ ስቶር ያውርዱ! ይጠቀሙ!

https://www.hibretbank.com.et/hibir-mobile-landing-page

ሕብረት ባንክ
በሕብረት እንደግ!

📞  ለበለጠ መረጃ ወደ 995 ነፃ የጥሪ ማዕከል ይደውሉ፡፡
🤳 በቀላሉ አዳዲስ መረጃዎች  እንዲደርስዎ የቴሌግራም ገፃችንን አሁኑኑ ይቀላቀሉ፡፡ https://t.iss.one/HibretBanket
🌐 ሌሎች የማህበራዊ ገፆቻችንን እና ድህረ ገፃችንን linktr.ee/Hibret.Bank ይጎብኙ፡፡

#Hibirmobile #appupdate #Hibretbank
" ወጣቱ ሳይጎዳ በገመድ አስረው በማውረድ በተአምር ህይወቱን ታድገዋል " - የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል

የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ላይ የወጣ ወጣት በተአምር ህይወቱ ተርፏል።

በከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶ ላይ የወጣ ወጣት ኃይል እንዲቋረጥ ማድረጉን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ አስታውቋል፡፡

በዘርፉ የደቡብ ሁለት ሪጅን እንደገለፀው ወጣቱ ዛሬ  ከቀኑ  8:00  ጀምሮ ከወላይታ ሶዶ ወደ ሳውላ በሚሄደው ከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ላይ ወጥቶ " አልወርድም " በማለቱ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በሚገኙ ፦
- ጎፋ ዞን፣
- አሪ ዞን፣
- ባስኬቶ ዞን እና ኦሞ ዞን ሙሉ በሙሉ እንዲሁም ጋሞ ዞን በከፊል ከሦስት ሰዓታት በላይ ኃይል ተቋርጦ ቆይቷል፡፡

በምን ምክንያት የኃይል ማስተላለፊያ መስመሩ ላይ እንደወጣ ያልታወቀው ወጣት በአካባቢው ሽማግሌዎችና የመስተዳድር አካላት ቢለመንም ለመውረድ ግን አስቸግሮ እንደነበር መምሪያው ገልጿል፡፡

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ባለሙያዎች ኃይል በማቋረጥ ወጣቱ ሳይጎዳ በገመድ አስረው በማውረድ በተአምር ህይወቱን ታድገዋል፡፡

የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች የሚያስተላልፉት የቮልቴጅ መጠን ከፍተኛ በመሆኑ ህብረተሰቡ ጥንቃቄ እንዲያደርግ መምሪያው አሳስቧል፡፡

#EthiopianElectricPower

@tikvahethiopia
🔈 #የወጣቶችድምጽ

" በየት በኩል እንስራ ? "

ከሰሞኑን የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት የሆኑ የኮንስትራክሽን እና ሌሎች ስራ ዘርፎች ላይ የተሰማሩ ወጣቶች በምሬት አንድ ሃሳባቸውን አካልፈዋል።

" እንናገረውና ሰው ሰምቶት ይወጣልን ብለን ነው "  ሲሉ ስለደረሰባቸው ነገር አጋርተዋል።

እኚ ወጣቶች በክልል ከተሞች ተንቀሳቅሰው ለመስራት የሚታትሩ ናቸው።

ግን በብሄር፣ በዝምድና በትውውቅ የሚሰሩ ስራዎች ፈተና ሆነውባቸዋል። ተስፋም እያስቆረጣቸው ነው።

በቅርቡ ለአንድ ስራ ይወዳደራሉ ፤ ይህንን ስራ እንደሚያሸንፉ ባለሙሉ ተስፋ ሆነው ስራውን ለማሰራት ማስታወቂያ ወዳወጣው አካባቢና ቢሮ ያመራሉ።

ከአንድ ኃላፊ ተሰጠን ያሉት መልስ ግን " አትልፉ ፤ ይሄንን ስራ ወስዳችሁ ልትሰሩ የምትችሉ አይመስለኝም " የሚል ነው።

ይህ የሆነው ደግሞ " ከሌላ አካባቢ የመጡ ናቸው " በሚልና ከየት አካባቢ እንደመጡ በማጣራት እንደሆነ አስረድተዋል።

በዚህም " ከሌላ አካባቢ " በሚል አደገኛ አመለካከት ብቻ ስራውን ሌላ ሰው እንዲወስደው ስለመደረጉ በምሬት ተናግረዋል።

ድርጊቱ እጅግ እንዳሳዘናቸው ይሄ የብሄር፣ የዝምድና፣ የትውውቅ፣ የአካባቢ መርጦ ስራ ብዙ ወጣቶች አቅም እያላቸው እንዳይሰሩ እያደረገ ያለ እጅግ አደገኛ መርዝ መሆኑን ሳይናገሩ አላሉፍም።

ሌላ ቃላቸውን የተቀበልናቸው ወጣቶች ለስራ ጉዳይ ካለው የተንዛዛ ሂደት ባለፈ የዝምድና የትውውቅ ስራ ተስፋ አስቆርጧቸው ምን እንደሚያደርጉ ግራ እንደገባቸው ተናግረዋል።

በአንድ ሀገር በአንድ ባንዲራ ስር ከአንዱ ክልል ወደ ሌላው ሄዶ ስራ መስራት ፈተና እንደሆነና ስራዎች በዝምድና፣ ለተወላጅ፣ ለአካባቢ ሰው በትውውቅ እንደሚሰጡ ጠቁመዋል።

" ሚዲያውም ሆነ ሌላው አካል እነዚህን መሰል ጉዳዮች ሳይሆን ለራሱ የገቢ ትርፍ እና ተመልካች የሚያስገኝለትን ጉዳይ እየመዘዘ ነው የሚሰራው " በማለትም ወቀሳ አቅርበዋል።

" ጨረታ፣ ውድድር በሚኖር ሰዓት እንኳን ዘመድ ያለው፣ ገንዘብ ያለው በእጅ አዙር ስራውን ያገኛል ይሄ ምንም የሚደበቅ አይደለም " ብለዋል።

ወጣቶች በፈለጉት ቦታ ተንቀሳቅሰው መስራት ካልቻሉ ሀገር ውስጥ እንዴት ይቀመጣሉ ? ቆይ በገፍ ቢሰደዱስ ምን ይገርማል ? ሲሉም ጠይቀዋል።

በዙሪያቸው ያለ እጅግ ብዙ ወጣት ባለው አሰራር ምክንያት ተማሮ ከሀገር ለመውጣት ብዙ እንደሚጥር ጠቁመዋል።

" አሁን ላይ ያለው ነገር ሁሉ ብሶበት ቁጭ ብሏል። የወጣቱን፣ የህዝቡን ድምጽ ሰምቶ ችግር ከማስተካከል ይልቅ ህዝብን ዝቅ ብለው እንዲያገለግሉ የተቀመጡ አካላት ሌላ ስም መስጠት እና መፈረጅ ስራቸው ሆኗል " ሲሉ አክለዋል።

ከአንድ ክልል፣  ዞን ፣ ወረዳ ሌላ ቦታ ሄዶ ለመስራት ችግር ከሆነና ስራው ሁሉ ብቃት ላለው ሳይሆን በብሄር፣ ትውውቅ፣ ዝምድና፣ በሙስና እየተመረጠ የሚሰጥ ከሆነ እንዴት ለውጥ ሊመጣ ይችላል ? ወደኃላ መጓዝ ማለትስ ይህ አይደለም ? ይህ የበርካታ ወጣቶች ጥያቄና ድምጽ ነው።

#TikvahEthiopia
#የወጣቶችድምጽ

@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
TIKVAH-ETHIOPIA
የአቶ በቴ ኡርጌሳ ምርመራ ከምን ደረሰ ? “ ... ምርመራው ተጀምሯል ፤ እየቀጠለ ነው ” - ኢሰመኮ በኦሮሚያ ክልል፣ መቂ ከተማ ተገደሉትን የኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ) ከፍተኛ አመራር አቶ በቴ ኡርጌሳን ጉዳይ በተመለከተ በርካታ መረጃዎች አድርሰናችሁ ነበር።  ሰሞኑን ደግሞ ፦ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በአቶ በቴ ኡርጌሳ ግድያ ላይ የጀመረውን ምርመራ በደረሰበት ጫና ማቆሙን…
" በቴ ምን ያህል ለህዝቡ አስፈላጊ እንደነበር በህዝቡ ሁኔታ፣ በህዝቡ ለቅሶ ተመልክቻለሁ ! " - የፖለቲከኛ አቶ በቴ ኡርጌሳ ባለቤት

ከወራት በፊት መቂ ላይ በግፍ የተገደሉት የኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ) ከፍተኛ አመራር ፖለቲከኛው አቶ በቴ ኡርጌሳ ባለቤት ከልጆቻቸው ጋር ከሀገር ወጥተው አሜሪካ መግባታቸው ተሰምቷል።

ባለቤታቸው ወ/ሮ ስንታየሁ አንበሴ በአጭር ቪድዮ ባሰራጩት ቃላቸው ፥ አሁን ላይ ከልጆቻቸው ጋር አሜሪካ ሀገር እንደሚገኙ ገልጸዋል።

" ባለቤቴ በቴ ኡርጌሳ ከሞተ 7ኛ ወር ሊሞላ ነው። " ብለዋል።

" በዓለም ላይ ያላችሁ ሃዘናችንን የተካፈላችሁ ፣ የኦሮሞ ኮሚውኒቲ ፤ በቴ ምን ያህል ለህዝቡ አስፈላጊ እንዳሆነ በሃዘናችሁ ፤ ባለው ነገር ሁሉ አይተናል " ሲሉ ገልጸዋል።

" እሱ ካረፈበት ቀን ጀምሮ በሀዘናችን ያለቀሳችሁ፣ ከኛ ጋር ያዘናችሁ ፣ በገንዘባችሁ በሃሳባችሁ በጸሎታችሁ የረዳችሁን እግዚአብሔር ይስጥልን ፤ እናመሰግናለን " ብለዋል።

" የኛን ሰላም መሆን ለተጨነቃችሁ ፤ ድምጻችን ሲጠፋ ለተጨነቃችሁ ' ምን ሆናችሁ ነው ? ' ላላችሁን ያለንበትን ለመግለፅ ነው  ፤ አሁን ያለነው አሜሪካ ነው ፤ በሰላም ደርሰናል " ሲሉ ገልጸዋል።

" ኤምባሲዎች በጣም እናመሰግናለን ፤ ያለንበት ቦታ ድምጻችን የጠፋባችሁ ስልካችን እንቢ ያላችሁ ፣ ቤታችን ድረስ ሄዳችሁ ያጣችሁን ምን ሆናችሁ ነው ? ላለችሁን ላደረጋችሁልን ነገር ሁሉ እናመሰግናለን " ብለዋል።

" በቴ ምን ያህል ለህዝቡ አስፈላጊ እንደነበር በህዝቡ ሁኔታ፣ ለቅሶ ተመልክቻለሁ " ያሉት ወ/ሮ ስንታየሁ " እኔ እውነት ለመናገር በቴ ከሞተ በኃላ ነው ህዝቡ እንዴት በቴን ያውቅ እንደነበር የተረዳሁት ምክንያቱም በቴን እንደዚህ አላውቀውም ነበር እውነቱን ለመናገር ከጫፍ ጫፍ ነው ህዝቡ ያዘነው " ሲሉ በእምባ ታጅበው ስሜታቸውን ገልጸዋል።

እምባቸውን 😭 እያፈሰሱ የተናገሩት የበቴ ባለቤት " እሱ የኢትዮጵያ ብቻ አይደለም የዓለም ሰው እንደሆነ አውቃለሁ " ብለዋል።

አሁንም ከጎናቸው ሆነው በብዙ ነገር እየረዷቸው ላሉ በተለይ ለኦሮሞ ኮሚውኒቲ ፣ በውጭ ሆነው በስልክ እየደወሉ እያፅናኗቸው ያሉ፣ በፀሎታቸው ፣ በገንዘብ እየደገፏቸው ላሉ  ሁሉ " እግዚአብሔር ይስጥልን " ሲሉ አመስግነዋል።

ወ/ሮ ስንታየው አንበሴ ፤ ልጆቻቸው ደህንነታቸው የተጠበቀ ቦታ ላይ እንዳሉና ትምህርትም እንደጀመሩ ገልጸዋል።

ወደፊት ጊዜው ሲደርስ ደግሞ ስላሳለፉት ነገር እንደሚገልጹ ቃል ገብተዋል።

ለተደረገላቸው ነገር ሁሉ እያነቡ በልጆቻቸው ስም ምስጋና አቅርበዋል።

የአምስት ልጆች አባቱ ፖለቲከኛው በቴ ኡርጌሳ ከወራት በፊት መቂ ላይ በግፍ መገደላቸው ይታወሳል። ከዛ በኃላ " ማጣራት ተደርጎ ስለ ግድያው ዝርዝር ማብራሪያ ለህዝቡ ይሰጣል " ተብሎ ቃል ቢገባም እስከ ዛሬ ስለ ግድያው ሁኔታ ፣ ከግድያው ጋር በተያያዘ ተጠያቂ ስለሆነ አካል በይፋ አንድም የተባለ ነገር የለም።

የፖለቲከኛ አቶ በቴ ኡርጌሳ ጉዳይ " ቄሱም ዝም መፅሃፉም ዝም " እንዲሉ ሆኖ ቀጥሏል።

#TikvahEthiopia

@tikvahethiopia
#InfinixEthiopia

የዛንዚባር የቢዝነስ ክላስ ደርሶ መልስ የአውሮፕላን ቲኬት፣ የኢንፊኒክስ ስማርት ቲቪ፣ የኢንፊኒክስ ላፕቶፕ እንዲሁም ሌሎች አጓጊ ሽልማቶችን ኢንፊኒክስ ስማርት ስልኮች የሆኑትን ሆት 40 ፣ ኖት 40 ፣ ዜሮ 40 እና የኢንፊኒክስ ስማርት TVን ሲገበያዩ ኩፖን በመውሰድ አብሮት ካለ ወዳጅ ዘመድ ወይም ጓደኛ ጋር በመረጡት ስፍራ ፎቶ በመነሳት #InfinixEthiopia የሚለውን ሃሽ ታግ በመጠቀም እና ማህበራዊ ሚዲያ ላይ በመለጠፍ ማሸነፍ ይችላሉ ይፍጠኑ የዚህ ልዩ የሽልማት ፕሮግራም አካል ይሁኑ፡፡

መመሪያ

1. የኢንፊኒክስ ኢትዮጵያን ፌስ ቡክ ፣ ኢንስታግራም እና ቲክቶክ ገጾችን ፎሎው ያድርጉ፡፡
2. የተነሱትን ፎቶ በመረጡት ማህበራዊ ሚዲያ ሲለጥፉ የኢንፊኒክስ ኢትዮጵያን ገፅ ከፖስቶት ጋር ታግ ያድርጉ፡፡
3. #InfinixEthiopia የሚለውን ሃሽታግ መጠቀሞን አይርሱ፡፡

Tag ሲያደርጉ ለ Facebook @InfinixMobileEthiopia ፣ ለ Instagram @infinixethiopia ለ TikTok @Infinixet እና ለ Telegram @Infinixeth ሜንሽን ማድረግ እንዳይረሱ።
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#ንጉስማልት

ደስስስስስስ ደስስስስስስ የሚለዉን የንጉስ ጠርሙስን ያሽከርክሩ ፈገግታን ይላበሱ !! ምን ደረስዎ ? ይሄ 🥰 ? ይሄኛው 🤩 ? ወይስ ሌላ ? ደስ የሚል ግዜ ይሁንልዎ !!

#ደስደስበንጉስ #nonalcoholic #ከአልኮልነፃ
#MPESASafaricom

የሀገር ዉስጥ በረራ ትኬታችንን በM-PESA እንቁረጥ ፤ 5% ተመላሽ አሁኑኑ እናግኝ !

የM-PESA ሳፋሪኮም መተግበሪያን በዚህ ሊንክ እናውርድ ፡ https://play.google.com/store/apps/details?id=et.safaricom.mpesa.lifestyle

የቴሌግራም ቻናላችንን እዚህ እንቀላቀል 👉https://t.iss.one/Safaricom_Ethiopia_PLC

ስለ አገልግሎታችን ማንኛውንም ጥያቄ ወይም መረጃ  በቴሌግራም   ቻናላችን https://t.iss.one/Safaricom_Ethiopia_PLC 24/7 ማግኘት ይቻላል!

 #FurtherAheadTogether
🔈 #የጤናባለሞያዎችድምጽ

በአማራ ክልል፣ ደቡብ ወሎ ዞን ቃሉ ወረዳ በዘጠኝ ጤና ጣቢያ ውስጥ የሚሰሩ የጤና ባለሞያዎች ከግንቦት 2016 ዓ/ም ጀምሮ ያልተከፈላቸው  የተጠራቀመ የትርፍ ሰዓት ስራ (ዲዩቲ) ክፍያቸው ሳይከፈላቸው እንደቆየ ተናግረዋል።

ክፍያቸው እንዲፈጸምላቸው ተደጋጋሚ የሆነ ጥያቄ ለወረዳው እና ለጤና ጽ/ቤቱ ሲጠይቁ የቆዩ ሲሆን የወረዳው ጤና ጽ/ቤት ከ6 ወር ክፍያው ውስጥ የ2 ወሩን እንደከፈላቸው ቅሬታቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ያቀረቡ የጤና ባለሞያዎች ተናግረዋል።

ቅሬታ አቅራቢዎች የቀረውን የ4 ወር ክፍያ ለመፈጸም ግን ከወረዳው " በጀት የለንም " የሚል ምላሽ እንደተሰጣቸው ተናግረዋል።

ያነጋገርናቸው የጤና ባለሞያዎች " ወረዳው በክልሉ ካሉ የሰላም ወረዳ (ቀጠና) አንዱ ነው የመንግስት ስራ በሁሉም ሴክተር እየተሰራ ነው ያለው የግብር እና የታክስ መሰብሰብ ስራም በአግባቡ እየተሰራ ነው የበጀት እጥረት አጋጠመን የሚባለው በጭራሽ ከእውነት የራቀ ነው " ብለዋል።

" በዞኑ የሚገኙ አጎራባች ወረዳዎችን፣ ኮምቦልቻ ከተማ አስተዳደር፣ ባቲ ወረዳ፣ አርጎባ ልዩ ወረዳ እና ሌሎችም ወረዳዎች ለባለሙያዎቻቸው የሰሩበትን የትርፍ ሰዓት ክፍያ ከፍለዋል የእኛ በምን ተለይቶ ዘገየ " የሚል ጥያቄን አንስተዋል።

በወረዳው ከሚገኙ ጤና ጣቢያዎች አንዱ ከሆነው " ደጋን " ጤና ጣቢያ ሁለት የጤና ባለሞያዎች ማክሰኞ 03/03/17 ዓም በጸጥታ አካላት ተወስደዋል።

የጤና ባለሞያዎች ለእስር የተዳረጉት ካልተከፈላቸው ክፍያ ጋር በተገናኘ የሰሩበትን የትርፍ ሰዓት ክፍያ እንዲከፈላቸው የሚጠይቅ ጽሁፍ " በሶሻል ሚዲያ አጋርታቹሃል " በሚል ሳይሆን እንዳልቀረ ተነግሯል።

ባለሞያዎቹ ከ4 ቀናት እስር በኋላ ትላንት ምሽት ተፈተዋል።

የቃሉ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ ሙህዲን አህመድ ለጤና ባለሞያዎቹ ክፍያው በእርግጥም አለመፈጸሙን አረጋግጠው ያልተከፈላቸው ግን በበጀት እጥረት ምክንያት አለመሆኑን ተናግረዋል።

" ክፍያው የዘገየው በየጤና ጣቢያዎቹ የሚሰጠው አገልግሎት እና የሥራ ጫና የሚለያይ በመሆኑ የሚያድረው የጤና ባለሞያ ቁጥርም ይለያያል በዛ ምክንያት ደረጃ ይውጣለትና በሚሰጡት አገልግሎት እና ባለባቸው የስራ ጫና ልክ ይከፈላቸው ተብሎ ይህንን የሚያጣራ ኮሚቴ ተቋቁሞ በወረዳው በሚገኙ በዘጠኙም ጤና ጣቢያዎች እያጣራ ነው ሪፖርቱን እንዳቀረበ ይከፈላቸዋል " ብለዋል።

በሌሎች ትይዩ ወረዳዎች ላይ ከክፍያ ጋር በተያያዘ ተመሳሳይ ችግር የለም ይህ በቃሉ ወረዳ ለምን ተፈጠረ ለሚለው የቲክቫህ ጥያቄ " የእኛ ወረዳ ከሌሎች የጎንዮሽ ወረዳዎች ጋር ለማነጻጸሪያ ቢቀርብ የተሻለ ከፋይ ነው " ብለዋል።

ታሰሩ ስለተባሉት ባለሞያዎች መረጃው እንደሌላቸው ተናግረው በሌላ ጉዳይ ተጠርጥረው ካልታሰሩ በቀር በክፍያው ጉዳይ አይታሰሩም ብለዋል።

" ከተያዙም ሌላ የጸጥታ ስራ ስላለ በዛ ምክንያት ተጠርጥረው ነው የሚሆነው በተባለው ምክንያት ከሆነ ግን አጣርቼ ልጆቹን ትሪት አደርጋለው " የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።

#TikvahEthiopia

@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
🔈#የዜጎችድምጽ

ችግሩ ቢነገር ቢነገር መፍትሄ ያልተገኘለት በክልሎች ያለው የቤንዚን ጉዳይ !

በክልል ከተሞች ነዳጅ በተለይም ቤንዚን ማግኘት ፈተና እንደሆነ ቀጥሏል።

በርካታ በትራንስፖርት ስራ ላይ የተሰማሩ ወጣቶች ባለው ችግር ምክንያት ሰርቶ መግባት ቤተሰብ ማስተዳደር ከባድ ሆኖባቸዋል።

ከክልል ከተሞች አንዷ የሲዳማ መዲናዋ ሀዋሳ ናት።

በዚህች ከተማ ነዳጅ እንደልብ ማግኘት ከቆመ ዓመታት አልፈዋል።

ያለው ችግር በተደጋጋሚ ቢነገርም በክልል መዲናይቱ ምንም የተቀየረ ነገር የለም። አሁንም ችግሩ እንደቀጠለ ነው። እንደልብ ነዳጅ ማግኘት አይቻልም።

አሽከርካሪዎች " ነዳጅ ማግኘት ከፍተኛ መከራ ሆኖብናል " ሲሉ ድምጻቸውን በቲክቫህ ኢትዮጵያ በኩል አሰምተዋል።

" ብላክ በኃይላድ እየተሞላ እንደሸቀጥ ዕቃ በየሱቁ አንድ ሊትር  ከ160 እስከ 180 ከዛም በላይ እየተሸጠ ነው " ሲሉ ገልጸዋል።

በከተማው በርካታ ማደያዎች ቢኖሩም ነዳጅ ማግኘት ስቃይ ነው።

ነዳጅ በፕሮግራም ማሸጥ ከተጀመረም በርካታ ወራት አልፈዋል።

ምንም እንኳን በየማደያው ቤንዚን የለም ይባል እንጂ ባጥቁር ገቢያ ነጋዴዎች በከፍተኛ ብር እንደጉድ ይቸበቸባል።

ቤንዚን ከከተማ እስከ ገጠር ድረስ ከጥቁር ገበያው ጠፍቶ አያውቅም።

ጉዳዩ ይመለከታቸዋል የሚባሉት የሥራ ኃላፊዎች " ችግሩ ይቀረፋል እየሰራን ነው " እያሉ ተደጋጋሚ ቃል ከመስጠት ውጪ ያመጡት መሬት ላይ የሚታይ ለውጥ እንደሌለ ነዋሪዎቹ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

ባለው ሁኔታ ምክንያት " ሰርቶ መኖር በጣም ችግር ሆኖብናል " ብለዋል።

ወደ ደቡብ ኢትዮጵያ እና ሌሎች ክልሎችም ብንመለከት የቤንዚን ችግር እንደዚሁ ነው።

በየማደያው የለም የሚባለው ቤንዚን ከጥቁር ከገበያ እንደልብ ሲገኝ ይታያል።

ቃላቸውን የሰጡን ነዋሪዎች " ቤንዚን በየሱቁ ፤ በየመንደሩ እንደጉድ ይቸበቸሻል ነዳጅ ማደያ ሲኬድ የለም ነው መልሳቸው " ብለዋል።

" ህዝብ እየተሰቃየ ነው። በተለይ የትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጡ ዜጎች መከራቸውን እያዩ ነው። ችግሩ በርካታ ጊዜ ቢያልፈውም ለምን ማስተካከል እንዳልተቻለ ሊገባን አልቻለም " ሲሉ አክለዋል።

ከነዳጅ ማደያዎች ሌሊት በሲኖትራክ ሳይቀር ነዳጅ ተጭኖ እንደሚወጣ ፤ በዚህ የጥቁር ገበያና የነዳጅ ሽያጭ ሰንሰለት እጃቸው የረዘመ በመዋቅር ውስጥ ያሉ አካላት ሊኖሩ እንደሚችላ ጠቁመዋል።

በየመዋቅሩ ተጠቃሚ ሰዎች ባይኖሩ እንዴት ይሄን ያህል ጊዜ ችግሩ ይቀጥላል ? ሲሉም ጠይቀዋል።

ለአብነት ወላይታ ሶዶ ከተማ ውስጥ ቤንዚን ማግኘት አይታሰብም።

በጥቁር ገበያ እስከ 200 ብር ድረስ ይቸበቸድረስ

ከዚህ ባለፈ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከነዋሪዎች እንደሰማው አንዳንድ ከከተማ የወጡ ማደያዎች ሳይቀሩ ነዳጅ በድብቅ ይሸጣሉ።

አንድ ሊትር ቤንዚን 92 ብር መሸጥ ሲገባው ከጀርባ በትውውቅ እስከ 220 ብር ድረስ ለመሸጥ የሚደራደሩ አሉ።

ይህ ሁሉ ሲሆን ግን የመፍትሄ እርምጃ ሲወሰድ እና ማስተካከያ ሲደረግ አይታይም።

በአጠቃላይ በክልል ከተሞች በቤንዚን ምክንያት ስራ መስራት ፈተና እንደሆነ ነው። ከከተማ ወጥቶ ለመስራትም እየተቻለ አይደለም።

የዚህ ሁሉ ችግር መጨረሻ የሚወርደው ህዝብ ላይ ነው። " ነዳጅ የለም ተወዷል " በሚል በትራንስፖርት ተገልጋዩ ዜጋ ላይ የሚጨመረው ዋጋ ከፍተኛ ነው ፤ ካለው የኑሮ ውድነት ጋር ይሄ ተጨምሮ የሚያሳድረው ተፅእኖ እንዲሁ በቃላት የሚገለጽ አይደለም።

#TikvahEthiopia

@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM