#ጋምቤላ
አዲስ አመራር ከመጣ በኃላ በጋምቤላ መሻሻል ታይቷል ?
በጋምቤላ ክልል ካለፈው ነሐሴ 2016 ዓ/ም ወዲህ የአመራር ለውጥ ከተደረገ ወዲህ በክልሉ የነበረው የሠላም ሁኔታ እየተሻሻለ መምጣቱን አዲሱ አስተዳደር፣ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች እንዲሁም ነዋሪዎች ተናግረዋል።
ባለፈው ዓመት በጋምቤላ ክልል በተለያዩ አካባቢዎችና ጊዜዎች ግጭቶች እየተከሰቱ በሰው ህይዎት ላይ ጉዳት ሲደርስ ቆይቷል።
ከሰብዓዊ ጉዳቱ ባሻገር በክልሉ ነዋሪዎች መካክል የነበሩ ማህበራዊ እንቅስቃሴዎች በአንዳንድ ቦታዎች እስከመገደብ ደርሰውም ነበር።
የክልሉ ልማትና ሰላምም በእጅጉ ተጎደቶ ነበር።
በተለይ ቀደም ባሉት ጊዜዎች የአኙዋክ ተውላጆች ወደ ኑዌር ሰፈር አይሄዱም፣ ኑዌሮችም በተመሳሳይ ወደ አኙዋክ ሰፈር ይሻገሩ አልነበረም።
አሁን ላይ ግን ሁኔታዎች እየተሻሻሉ መምጣታቸውን የጋምቤላ ነዋሪዎች ተናግረዋል።
የጋምቤላ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ዶ/ር ጋትሏክ ሮን ምን አሉ ?
- ችግሮችን ለማስተካክልና በክልሉ ሠላም ለማስፈንና ህዝቡን ወደልማት ለማምጣት በክልሉ ከነሐሴ 2016 ዓ/ም መጀመሪያ ሳምንት ላይ የአመራር ለውጥ በመደረጉ በሁሉም የክልሉ አካባቢዎች ሠላም ሰፍኗል።
- በክልሉ በነበረው የሠላም እጦት ምክንያት የጋምቤላ ከተማ የአኙዋክና የኑዌር በሚል ተከፍሎ አኙዋኮች ወደ ኑዌር ሰፈር፣ ኑዌሮችም ወደ አኙዋክ መንደር ለመሻገር ችግሮች ነበሩ። አሁን ያ ሁሉ ቀርቶ አዲሱ አመራር ወደ ሥራ ከገባና ህዝባዊ ውይይቶች ከተደረጉ በኋላ ሁሉም በሠላም በሁሉም ሥፍራ ይንቀሳቀሳል።
🔵 ማሉት ዴቪድ የተባሉ የጋምቤላ ከተማ ነዋሪ የምክትል ርዕሰ መስተዳድሩን ሀሳብ ይጋሩታል፣ አሁን አንዱ ወደ ሌላው ያለስጋት እንደሚንቀሳቀስ ነው ያረጋገጡት። ከተማውም ሠላም እንደሆን አመልክተዋል።
- አዳዲስ ሹመቶችና ምደባዎች ተሰጥተዋል። ይህም የትምህርት ዝግጅትንና የሥራ ልምድን መሠረት ያደረገ ነው።
- ለውጥ ያመጣሉ ተብሎ የታመነባቸው ቀደም ሲል ስልጣን ላይ የነበሩና ህዝባዊ አመለካከት ያላቸው በርከት ያሉ አመራሮችም በአዲሱ ሹመትና ምደባ እንደገና ተካተዋል።
- " ሠላም ወርዶ ህዝቡ በልማት መካስ አለበት " በሚል እሳቤ እውቀት፣ ልምድና የተሻል አመለካክትና እይታ ያላችው ሠዎች ወደ አመራሩ ተካተዋል።
- በኮታ መታሰር ቀርቷል። ቀደም ሲል በነበረው አሰራር ወንጀል ያልሰሩ ሰዎች በኮታ ጭምር ይታሰሩ ነበር። አሁን ግን በወንጀል የተጠረጠሩትን ብቻ ተጠያቂ የሚያደርግ አሰራር ተዘርግቷል።
- በፊት አንድ ኑዌር ቢያጠፋና ቢታሰር ሌላ አኙዋክ አብሮ እንዲታሰር ይደረግ ነበር፣ ሌላ አኙዋክ አጥፍቶ ቢታሰር የኑዌር ተወላጅ ተደርቦ እንዲታሰር ይደረግ ነበር ፤ አሁን ግን ጠፋተኛው ከየትኛውም ወገን ይሁን ጠፋተኛ ከሆን ተጠርጣሪው ብቻ ተለይቶ ተጠያቂ ይሆናል። የኮታ እስር ቀርቷል።
" ከአዲሱ አመራር ጋር ለመስራት ዝግጁ ነኝ " - ጋብዴን
የጋምቤላ ብሔራዊ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ(ጋብዴን) ሊቀመንበር አቶ ኡባንግ ኡሞድ ቀደም ሲል የነበረው አመራር ህዝቡን መምራት እንዳልቻለና ለውጥ እንዲመጣ ሲታግሉ እንደንበር ገልጠዋል።
ችግሩ የአመራሩ ሆኖ ሳለ ህዝቡን በከፍተኛ የሠላም እጦት ውስጥ ከትቶት ነበር ነው ያሉት።
በክልሉ የነበረውን ችግር እስከ የተፎካካሪ ፓርቲ የጋራ ምክር ቤት በማድረስ የነበረው የሠላም እጦት እንዲታወቅ መደረጉንና ለውጥ እንዲደረግ በግልም በጋራም ትግል ሲደረግ እንደነበር አስረድተዋል።
አዲሶቹ አመራሮች በሕዝቡ ተቀባይነት ማግኘታቸውንና ፓርቲያቸውም በአዲሱ አመራር ደስተኛ መሆኑን አቶ ኡባንግ ተናግረዋል።
ከአዲሱ አመራር ጋርም በጋራ ለመስራት ዝግጁ እንደሆኑም ነው የገለጡት።
የጋምቤላ ክልል ምክር ቤት ነሐሴ 9/2016 ዓ ም ባደረገው አስቸኳይ ስብሰባ ወ/ሮ ዓለሚቱ ኡመድን የመጀመሪያዋ የክልል ሴት ርዕሰ መስተዳድር፣ ዶ/ር ጋትሏክ ሮንን ደግሞ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አድርጎ መሾሙ ይታወሳል።
ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የዶቼ ቨለ ሬድዮ ጣቢያ ነው።
@tikvahethiopia
አዲስ አመራር ከመጣ በኃላ በጋምቤላ መሻሻል ታይቷል ?
በጋምቤላ ክልል ካለፈው ነሐሴ 2016 ዓ/ም ወዲህ የአመራር ለውጥ ከተደረገ ወዲህ በክልሉ የነበረው የሠላም ሁኔታ እየተሻሻለ መምጣቱን አዲሱ አስተዳደር፣ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች እንዲሁም ነዋሪዎች ተናግረዋል።
ባለፈው ዓመት በጋምቤላ ክልል በተለያዩ አካባቢዎችና ጊዜዎች ግጭቶች እየተከሰቱ በሰው ህይዎት ላይ ጉዳት ሲደርስ ቆይቷል።
ከሰብዓዊ ጉዳቱ ባሻገር በክልሉ ነዋሪዎች መካክል የነበሩ ማህበራዊ እንቅስቃሴዎች በአንዳንድ ቦታዎች እስከመገደብ ደርሰውም ነበር።
የክልሉ ልማትና ሰላምም በእጅጉ ተጎደቶ ነበር።
በተለይ ቀደም ባሉት ጊዜዎች የአኙዋክ ተውላጆች ወደ ኑዌር ሰፈር አይሄዱም፣ ኑዌሮችም በተመሳሳይ ወደ አኙዋክ ሰፈር ይሻገሩ አልነበረም።
አሁን ላይ ግን ሁኔታዎች እየተሻሻሉ መምጣታቸውን የጋምቤላ ነዋሪዎች ተናግረዋል።
የጋምቤላ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ዶ/ር ጋትሏክ ሮን ምን አሉ ?
- ችግሮችን ለማስተካክልና በክልሉ ሠላም ለማስፈንና ህዝቡን ወደልማት ለማምጣት በክልሉ ከነሐሴ 2016 ዓ/ም መጀመሪያ ሳምንት ላይ የአመራር ለውጥ በመደረጉ በሁሉም የክልሉ አካባቢዎች ሠላም ሰፍኗል።
- በክልሉ በነበረው የሠላም እጦት ምክንያት የጋምቤላ ከተማ የአኙዋክና የኑዌር በሚል ተከፍሎ አኙዋኮች ወደ ኑዌር ሰፈር፣ ኑዌሮችም ወደ አኙዋክ መንደር ለመሻገር ችግሮች ነበሩ። አሁን ያ ሁሉ ቀርቶ አዲሱ አመራር ወደ ሥራ ከገባና ህዝባዊ ውይይቶች ከተደረጉ በኋላ ሁሉም በሠላም በሁሉም ሥፍራ ይንቀሳቀሳል።
🔵 ማሉት ዴቪድ የተባሉ የጋምቤላ ከተማ ነዋሪ የምክትል ርዕሰ መስተዳድሩን ሀሳብ ይጋሩታል፣ አሁን አንዱ ወደ ሌላው ያለስጋት እንደሚንቀሳቀስ ነው ያረጋገጡት። ከተማውም ሠላም እንደሆን አመልክተዋል።
- አዳዲስ ሹመቶችና ምደባዎች ተሰጥተዋል። ይህም የትምህርት ዝግጅትንና የሥራ ልምድን መሠረት ያደረገ ነው።
- ለውጥ ያመጣሉ ተብሎ የታመነባቸው ቀደም ሲል ስልጣን ላይ የነበሩና ህዝባዊ አመለካከት ያላቸው በርከት ያሉ አመራሮችም በአዲሱ ሹመትና ምደባ እንደገና ተካተዋል።
- " ሠላም ወርዶ ህዝቡ በልማት መካስ አለበት " በሚል እሳቤ እውቀት፣ ልምድና የተሻል አመለካክትና እይታ ያላችው ሠዎች ወደ አመራሩ ተካተዋል።
- በኮታ መታሰር ቀርቷል። ቀደም ሲል በነበረው አሰራር ወንጀል ያልሰሩ ሰዎች በኮታ ጭምር ይታሰሩ ነበር። አሁን ግን በወንጀል የተጠረጠሩትን ብቻ ተጠያቂ የሚያደርግ አሰራር ተዘርግቷል።
- በፊት አንድ ኑዌር ቢያጠፋና ቢታሰር ሌላ አኙዋክ አብሮ እንዲታሰር ይደረግ ነበር፣ ሌላ አኙዋክ አጥፍቶ ቢታሰር የኑዌር ተወላጅ ተደርቦ እንዲታሰር ይደረግ ነበር ፤ አሁን ግን ጠፋተኛው ከየትኛውም ወገን ይሁን ጠፋተኛ ከሆን ተጠርጣሪው ብቻ ተለይቶ ተጠያቂ ይሆናል። የኮታ እስር ቀርቷል።
" ከአዲሱ አመራር ጋር ለመስራት ዝግጁ ነኝ " - ጋብዴን
የጋምቤላ ብሔራዊ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ(ጋብዴን) ሊቀመንበር አቶ ኡባንግ ኡሞድ ቀደም ሲል የነበረው አመራር ህዝቡን መምራት እንዳልቻለና ለውጥ እንዲመጣ ሲታግሉ እንደንበር ገልጠዋል።
ችግሩ የአመራሩ ሆኖ ሳለ ህዝቡን በከፍተኛ የሠላም እጦት ውስጥ ከትቶት ነበር ነው ያሉት።
በክልሉ የነበረውን ችግር እስከ የተፎካካሪ ፓርቲ የጋራ ምክር ቤት በማድረስ የነበረው የሠላም እጦት እንዲታወቅ መደረጉንና ለውጥ እንዲደረግ በግልም በጋራም ትግል ሲደረግ እንደነበር አስረድተዋል።
አዲሶቹ አመራሮች በሕዝቡ ተቀባይነት ማግኘታቸውንና ፓርቲያቸውም በአዲሱ አመራር ደስተኛ መሆኑን አቶ ኡባንግ ተናግረዋል።
ከአዲሱ አመራር ጋርም በጋራ ለመስራት ዝግጁ እንደሆኑም ነው የገለጡት።
የጋምቤላ ክልል ምክር ቤት ነሐሴ 9/2016 ዓ ም ባደረገው አስቸኳይ ስብሰባ ወ/ሮ ዓለሚቱ ኡመድን የመጀመሪያዋ የክልል ሴት ርዕሰ መስተዳድር፣ ዶ/ር ጋትሏክ ሮንን ደግሞ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አድርጎ መሾሙ ይታወሳል።
ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የዶቼ ቨለ ሬድዮ ጣቢያ ነው።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update " ዘግተው የወጡትን ሰዎች በህግ እንዲፈለጉ እያደረግን ነው " -የሆስፒታሉ ስራ አስኪያጅ ከክፍያ ጋር በተያያዘ የአንጋጫ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታልን ዘግተው ስለወጡና ስራ ስላቆሙ ጤና ባለሞያዎች በተመለከተ የሆስፒታሉ ስራ አስኪያጅ አቶ ተሰማ አበራ ዝርዝር ምላሽ ሰጥተዋል። " እኔ እንደ ተቋሙ ስራ አስኪያጅ ይከፈላቸው ብዬ እየጠየኩ ነው በዕለቱም ይህንን ጉዳይ ከሚመለከተው አካል ጋር…
#Update
" ጥያቄያችን ፖለቲካዊ ይዘት እንዲኖረው ተደርጓል " - ቅሬታ አቅራቢ የጤና ባለሙያዎች
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል፣ የአንጋጫ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ውስጥ የሚሰሩ ከ80 በላይ የጤና ባለሞያዎች ለ6 ወራት የሰሩበት የተጠራቀመ የዲዩቲ ክፍያ ስላልተከፈላቸው ከ12/02/17 ዓ/ም ጀምሮ ስራ ማቆማቸውን መግለጻችን ይታወሳል።
የሆስፒታሉ ሰራተኞች ከተጠቀሰው ቀን ጀምሮ ለስድስት ቀናት ማለትም 12/02/17 እስከ 18/02/17 ድረስ ስራ ሳይገቡ ቆይተው ማክሰኞ በ19/02/2017 ዓ.ም ከአካባቢው ሽማግሌዎች ጋር የወረዳው ባለሥልጣናት በተገኙበት በተደረገ ውይይት ሽማግሌዎች ከወረዳው ሃላፊዎች ጋር ለማደራደር በመስማማታቸው ወደ ስራ ገበታቸው ተመልሰዋል።
ይሁን እንጂ ከስብሰባው ማብቃት በኋላ " አድማውን አስተባብራቹሃል " በሚል 14 የሚሆኑ ባለሞያዎች ለእስር ተዳርገዋል።
በተለያየ ቀናት ለእስር የተዳረጉት እነዚህ ባለሞያዎች ከ 2 እስከ 6 ቀናት ለሚሆን ጊዜ ታስረው በዋስ ከእስር ተፈተው ወደ ስራ ገበታቸው ተመልሰዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ለእስር ከተዳረጉት ባለሞያዎች መካከል የተወሰኑትን አነጋግሯል።
ባለሙያዎቹ " ጥያቄያችን ፓለቲካዊ ይዘት እንዲኖረው ተደርጓል " ብለውናል።
" የጠየቅነው የሰራንበትን ክፍያ ሆኖ ሳለ ፍርድ ቤት ስንቀርብ ' ህዝብ በመንግስት ላይ እንዲነሳ አድርጋቹሃል፣ ሰዎችን ወደ ሥራ እንዳይጋቡ አስፈራርታቹሃል ' የሚል ክስ ተነቦልናል " ነው ያሉት።
በተጨማሪም ባለሞያዎች ወደ ሆስፒታል ሲመለሱ ከአሁን በኋላ ተመሳሳይ የሆነ የስራ ማቆም አድማ ውስጥ ቢገቡ አስፈላጊውን አስተዳደራዊ እርምጃ እንደሚወሰድባቸው የሚገልጽ ደብዳቤ ላይ እንዲፈርሙ ተደርጓል ብከዋክ።
ሰራተኞቹ ከተመለሱ በኋላ BPR የተሰኘ በየስምንት ሰዓቱ በሺፍት የሚቀያየሩበት አሰራር እንዲዘረጋ መደረጉን ተናግረዋል።
በአዲሱ አሰራር መሰረት ጠዋት 12 ሰዓት ወደ ስራ የገባ ሰራተኛ 8 ሰዓት ከስራ የሚወጣ ሲሆን 8 ሰዓት የገባው ምሽት 4 ሰዓት ከስራ ይወጣል።
ይሁን እንጂ ይህ አሰራር " ሆስፒታሉ ለሰራተኞች ሰርቪስ የሌለው በመሆኑ እና በምሽት ሺፍት ከስራ ስንወጣ እና ስንገባ ለጅብ እየተጋለጥን ነው " በሚል ቅሬታ አቅርበዋል።
" ይህ አይነቱ አሰራር የተዘረጋው የወረዳው አስተዳደር ለመቀጣጫ እንዲሆን በሚል ነው " ያሉት ቅሬታ አቅራቢዎቹ " የትርፍ ሰዓት ሥራ ለማስቀረት የተደረገ ነው " ብለዋል።
ቲክቫህ ጉዳዩ በዋናነት የሚመለከታቸውን የአንጋጫ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ እና የሆስፒታሉ ምክትል ቦርድ ሰብሳቢ የሆኑትን አቶ ማርቆስ ማሞን ቅሬታውን ከተቀበለበት ቀን ጀምሮ ለማናገር ተደጋጋሚ የሆነ የስልክ ሙከራ ቢያደርግም ስልካቸውን ለማንሳት ፈቃደኛ አልሆኑም።
የሆስፒታሉ አስተዳዳሪ አቶ ተሰማ አበራ አዲሱ አሰራር ለአደጋ አጋልጦናል የሚለውን የሆስፒታሉን ባለሞያዎች ቅሬታ አይቀበሉም።
" የትርፍ ሰዓት ስራ ሲሰሩ ያልነበረ ጅብ ዛሬ ከየት መጣ " የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።
ይህ አይነቱ አሰራር ያልነበረና አዲስ ተደርጎ መወሰድ የለበትም ብለዋል።
አክለውም " ይህን ጭቅጭቅ የሚያመጣው ወረዳው የመክፈል አቅም የሌለው በመሆኑ ነው በቀጣይም መጋጨት የለብንም " በማለት አሰራሩ በገንዘብ እጥረት ምክንያት የተዘረጋ መሆኑን ጠቁመዋል።
ባለሞያዎቹ የሰሩበት ገንዘባቸው ሳይከፈላቸው ወደ ስራ እንዲመለሱ ተደርጓል መቼ ክፍያቸው ይፈጸማል ስንል በድጋሚ ላነሳንላቸው ጥያቄም "አሁንም እየተነጋገርን ነው ከወረዳ መንግሥት ጋር የገንዘብ ክፍተት ስላጋጠመ እንጂ መከፈል እንዳለበት ተግባብተናል" የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።
#TikvahEthiopia
@tikvahethiopia
" ጥያቄያችን ፖለቲካዊ ይዘት እንዲኖረው ተደርጓል " - ቅሬታ አቅራቢ የጤና ባለሙያዎች
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል፣ የአንጋጫ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ውስጥ የሚሰሩ ከ80 በላይ የጤና ባለሞያዎች ለ6 ወራት የሰሩበት የተጠራቀመ የዲዩቲ ክፍያ ስላልተከፈላቸው ከ12/02/17 ዓ/ም ጀምሮ ስራ ማቆማቸውን መግለጻችን ይታወሳል።
የሆስፒታሉ ሰራተኞች ከተጠቀሰው ቀን ጀምሮ ለስድስት ቀናት ማለትም 12/02/17 እስከ 18/02/17 ድረስ ስራ ሳይገቡ ቆይተው ማክሰኞ በ19/02/2017 ዓ.ም ከአካባቢው ሽማግሌዎች ጋር የወረዳው ባለሥልጣናት በተገኙበት በተደረገ ውይይት ሽማግሌዎች ከወረዳው ሃላፊዎች ጋር ለማደራደር በመስማማታቸው ወደ ስራ ገበታቸው ተመልሰዋል።
ይሁን እንጂ ከስብሰባው ማብቃት በኋላ " አድማውን አስተባብራቹሃል " በሚል 14 የሚሆኑ ባለሞያዎች ለእስር ተዳርገዋል።
በተለያየ ቀናት ለእስር የተዳረጉት እነዚህ ባለሞያዎች ከ 2 እስከ 6 ቀናት ለሚሆን ጊዜ ታስረው በዋስ ከእስር ተፈተው ወደ ስራ ገበታቸው ተመልሰዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ለእስር ከተዳረጉት ባለሞያዎች መካከል የተወሰኑትን አነጋግሯል።
ባለሙያዎቹ " ጥያቄያችን ፓለቲካዊ ይዘት እንዲኖረው ተደርጓል " ብለውናል።
" የጠየቅነው የሰራንበትን ክፍያ ሆኖ ሳለ ፍርድ ቤት ስንቀርብ ' ህዝብ በመንግስት ላይ እንዲነሳ አድርጋቹሃል፣ ሰዎችን ወደ ሥራ እንዳይጋቡ አስፈራርታቹሃል ' የሚል ክስ ተነቦልናል " ነው ያሉት።
በተጨማሪም ባለሞያዎች ወደ ሆስፒታል ሲመለሱ ከአሁን በኋላ ተመሳሳይ የሆነ የስራ ማቆም አድማ ውስጥ ቢገቡ አስፈላጊውን አስተዳደራዊ እርምጃ እንደሚወሰድባቸው የሚገልጽ ደብዳቤ ላይ እንዲፈርሙ ተደርጓል ብከዋክ።
ሰራተኞቹ ከተመለሱ በኋላ BPR የተሰኘ በየስምንት ሰዓቱ በሺፍት የሚቀያየሩበት አሰራር እንዲዘረጋ መደረጉን ተናግረዋል።
በአዲሱ አሰራር መሰረት ጠዋት 12 ሰዓት ወደ ስራ የገባ ሰራተኛ 8 ሰዓት ከስራ የሚወጣ ሲሆን 8 ሰዓት የገባው ምሽት 4 ሰዓት ከስራ ይወጣል።
ይሁን እንጂ ይህ አሰራር " ሆስፒታሉ ለሰራተኞች ሰርቪስ የሌለው በመሆኑ እና በምሽት ሺፍት ከስራ ስንወጣ እና ስንገባ ለጅብ እየተጋለጥን ነው " በሚል ቅሬታ አቅርበዋል።
" ይህ አይነቱ አሰራር የተዘረጋው የወረዳው አስተዳደር ለመቀጣጫ እንዲሆን በሚል ነው " ያሉት ቅሬታ አቅራቢዎቹ " የትርፍ ሰዓት ሥራ ለማስቀረት የተደረገ ነው " ብለዋል።
ቲክቫህ ጉዳዩ በዋናነት የሚመለከታቸውን የአንጋጫ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ እና የሆስፒታሉ ምክትል ቦርድ ሰብሳቢ የሆኑትን አቶ ማርቆስ ማሞን ቅሬታውን ከተቀበለበት ቀን ጀምሮ ለማናገር ተደጋጋሚ የሆነ የስልክ ሙከራ ቢያደርግም ስልካቸውን ለማንሳት ፈቃደኛ አልሆኑም።
የሆስፒታሉ አስተዳዳሪ አቶ ተሰማ አበራ አዲሱ አሰራር ለአደጋ አጋልጦናል የሚለውን የሆስፒታሉን ባለሞያዎች ቅሬታ አይቀበሉም።
" የትርፍ ሰዓት ስራ ሲሰሩ ያልነበረ ጅብ ዛሬ ከየት መጣ " የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።
ይህ አይነቱ አሰራር ያልነበረና አዲስ ተደርጎ መወሰድ የለበትም ብለዋል።
አክለውም " ይህን ጭቅጭቅ የሚያመጣው ወረዳው የመክፈል አቅም የሌለው በመሆኑ ነው በቀጣይም መጋጨት የለብንም " በማለት አሰራሩ በገንዘብ እጥረት ምክንያት የተዘረጋ መሆኑን ጠቁመዋል።
ባለሞያዎቹ የሰሩበት ገንዘባቸው ሳይከፈላቸው ወደ ስራ እንዲመለሱ ተደርጓል መቼ ክፍያቸው ይፈጸማል ስንል በድጋሚ ላነሳንላቸው ጥያቄም "አሁንም እየተነጋገርን ነው ከወረዳ መንግሥት ጋር የገንዘብ ክፍተት ስላጋጠመ እንጂ መከፈል እንዳለበት ተግባብተናል" የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።
#TikvahEthiopia
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" ፍራንኮ ቫሉታን በሚመለከት በቅርብ ማስተካከያ ይደረጋል " - ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከፓርላማ አባላት ለተነሱ የኢኮኖሚ ጥያቄዎች ማብራሪያ እና ምላሽ እየሰጡ ናቸው። በዚሁ ወቅት በቅርቡ ፍራንኮ ቫሉታን በሚመለከት ማስተካከያ እንደሚደረግ ጠቁመዋል። ጠ/ሚ ዐቢይ (ዶ/ር) " ባለፉት ጥቂት ወራት ከሪፎርሙ ጋር ተያይዞ ከወሰናቸው አብሮ ከማይሄዱ ውሳኔዎች ውስጥ አንዱ…
#ኢትዮጵያ
የገንዘብ ሚኒስቴር ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ እና ለጉምሩክ ኮሚሽን በፃፈው ደብዳቤ ፍራንኮ ቫሉታ ከዛሬ ጀምሮ መከልከሉን አሳውቋል።
የብር የመግዛት አቅም በገበያው እንዲወሰን ከተደረገ በኋላ ለተወሰነ ጊዜ የነዳጅ ተሽከርካሪዎችን እና የፀጥታ ተቋማት መሳሪያዎችን ሳይጨምር ሌሎች ምርቶችን በፍራንኮ ቫሉታ ወደ ሀገር ማስገባት ተፈቅዶ እንደነበር ይታወሳል፡፡
ይሁንና ከሳምንት በፊት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) በፓርላማ ተገኝተው ማብራሪያ ሲሰጡ የተፈቀደው ፍራንኮ ቫሉታ ሀብት ከሀገር እንዲሸሽ ምክንያት እየሆነ በመሆኑ ሊታገድ እንደሚችል ፍንጭ ሰጥተው እንደነበር ይታወሳል፡፡
የገንዘብ ሚኒስቴር ዛሬ በፃፈው ደብዳቤም ከዚህ ቀደም በፍራንኮ ቫሉታ ሸቀጦችን ከውጪ ያዘዙ ካሉ ከዛሬ ጀምሮ በ2 ሳምንት ጊዜ ውስጥ ግዢ የተፈፀመባቸው ህጋዊ ሰነዶችን ለጉምሩክ ኮሚሽን በማቅረብ ተቀባይነት አቅርበው የንግድ ሸቀጦቹ ወደ ሀገር እንዲገቡ ይደረጋል ብሏል።
የፍራንኮ ቫሉታ ፍቃድ ከጥቅምት 28/2017 ዓ/ም ጀምሮ ተግባራዊ የማይደረግ መሆኑ ተመላክቷል።
የመረጃው ባለቤት ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 ሬድዮ ነው።
@tikvahethiopia
የገንዘብ ሚኒስቴር ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ እና ለጉምሩክ ኮሚሽን በፃፈው ደብዳቤ ፍራንኮ ቫሉታ ከዛሬ ጀምሮ መከልከሉን አሳውቋል።
የብር የመግዛት አቅም በገበያው እንዲወሰን ከተደረገ በኋላ ለተወሰነ ጊዜ የነዳጅ ተሽከርካሪዎችን እና የፀጥታ ተቋማት መሳሪያዎችን ሳይጨምር ሌሎች ምርቶችን በፍራንኮ ቫሉታ ወደ ሀገር ማስገባት ተፈቅዶ እንደነበር ይታወሳል፡፡
ይሁንና ከሳምንት በፊት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) በፓርላማ ተገኝተው ማብራሪያ ሲሰጡ የተፈቀደው ፍራንኮ ቫሉታ ሀብት ከሀገር እንዲሸሽ ምክንያት እየሆነ በመሆኑ ሊታገድ እንደሚችል ፍንጭ ሰጥተው እንደነበር ይታወሳል፡፡
የገንዘብ ሚኒስቴር ዛሬ በፃፈው ደብዳቤም ከዚህ ቀደም በፍራንኮ ቫሉታ ሸቀጦችን ከውጪ ያዘዙ ካሉ ከዛሬ ጀምሮ በ2 ሳምንት ጊዜ ውስጥ ግዢ የተፈፀመባቸው ህጋዊ ሰነዶችን ለጉምሩክ ኮሚሽን በማቅረብ ተቀባይነት አቅርበው የንግድ ሸቀጦቹ ወደ ሀገር እንዲገቡ ይደረጋል ብሏል።
የፍራንኮ ቫሉታ ፍቃድ ከጥቅምት 28/2017 ዓ/ም ጀምሮ ተግባራዊ የማይደረግ መሆኑ ተመላክቷል።
የመረጃው ባለቤት ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 ሬድዮ ነው።
@tikvahethiopia
#መቐለ
መቐለ ውስጥ ባለፉት 3 ወራት ብቻ 1,088 ወንጀሎች መፈፀማቸው የመቐለ ከተማ ፓሊስ አስታውቋል።
ከተፈፀሙት ወንጀሎች መካከል ፦
➡️ 16 የግድያ
➡️ 47 የግድያ ሙከራ
➡️ 16 የሴቶች አስገድዶ መድፈር ይገኙበታል።
በሩብ አመቱ የተመዘገበው የወንጀል ተግባር አሳሳቢና ህዝብ ያሳተፈ የመከላከል ስራ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት አመላካች ነው ብሏል።
ፖሊስ የወንጀል ተግባራቱ ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ 3 ወራት ሲነፃፃር የቀነሰ ቢሆንም አሁንም ቢሆን ህዝቡ ከወንጀልና የወንጀል ስጋት ነፃ እንዳልሆነ አመላካች ነው ሲል አሳውቋል።
@tikvahethiopia
መቐለ ውስጥ ባለፉት 3 ወራት ብቻ 1,088 ወንጀሎች መፈፀማቸው የመቐለ ከተማ ፓሊስ አስታውቋል።
ከተፈፀሙት ወንጀሎች መካከል ፦
➡️ 16 የግድያ
➡️ 47 የግድያ ሙከራ
➡️ 16 የሴቶች አስገድዶ መድፈር ይገኙበታል።
በሩብ አመቱ የተመዘገበው የወንጀል ተግባር አሳሳቢና ህዝብ ያሳተፈ የመከላከል ስራ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት አመላካች ነው ብሏል።
ፖሊስ የወንጀል ተግባራቱ ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ 3 ወራት ሲነፃፃር የቀነሰ ቢሆንም አሁንም ቢሆን ህዝቡ ከወንጀልና የወንጀል ስጋት ነፃ እንዳልሆነ አመላካች ነው ሲል አሳውቋል።
@tikvahethiopia
#ሲሚንቶ
" ከዛሬ ጀምሮ በሚኒስትር መ/ቤቱ በኩል ይደረግ የነበረዉ የሲሚንቶ ግብይት ትስስር ሥራ ቀርቷል " - ዶ/ር ካሳሁን ጎፌ
የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ዶ/ር ካሳሁን ጎፌ ከሲሚንቶ አምራቾች ጋር መወያየታቸው ተሰምቷል።
በዚህም ወቅት " ከዚህ ቀደም በሚኒስትር መስሪያ ቤቱ በኩል ይደረግ የነበረዉ የሲሚንቶ ግብይት ትስስር ሥራ ከዛሬ ጀምሮ ቀርቷል " ብለዋል።
አምራቾች በራሳቸዉ ኃላፊነት በሚመርጧቸዉ አከፋፋዮችና ቸርቻሪዎች በኩል ለተጠቃሚዎች በተመጣጣኝ ዋጋ እንዲያቀርቡ አሳስበዋል፡፡
የሲሚንቶ ገበያዉን ለማረጋጋት ጥብቅ ቁጥጥርና ክትትል ይደረጋል ያሉ ሲሆን የአፈጻጸም ሪፖርት ለሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ በማያቀርቡ በማናቸዉም የሲሚንቶ አምራች ላይ " የማያዳግም እርምጃ ይወስዳል " ሲሉ አስጠንቅቀዋል።
ሚኒስትሩ " አዲሱን ዉሳኔና አቅጣጫ ተከትሎ በግብይት ሰንሰለቱ የደላላ ጣልቃ ገብነት የከሰመ፣ ለመንግስት ፕሮጀክቶችና ለተጠቃሚዉ ህብረተሰብ አስተማማኝ የሲሚንቶ አቅርቦት የተረጋገጠ፣ አምራቾችም ተገቢዉን ትርፍ እያገኙ የከምፓኒዎቻቸዉን ዘላቂ ዕድገት የሚያስቀጥሉበት እንዲሆን " ብለዋል።
የግብይት ሥርዓቱ ሙሉ በሙሉ ከካሽ ክፍያ ነጻ ሆኖ በዲጂታል ክፍያ ሥርዓት እንዲፈጸም አቅጣጫ አስቀምጠዋል።
በውይይት መድረኩ ወቅት አምራቾች የምርት አቅማቸውን እንዲያሳድጉ ተብሏል።
ሲሚንቶ አምራቾች አዲሱን ውሳኔ በማክበር እንደሚተገብሩ ተናግረው ነገር ግን የማምረቻ ግብዓት ፣ የኃይል አቅርቦትና ተያያዥ ችግሮች እንዲፈቱላቸዉ ጠይቀዋል፡፡
@tikvahethiopia
" ከዛሬ ጀምሮ በሚኒስትር መ/ቤቱ በኩል ይደረግ የነበረዉ የሲሚንቶ ግብይት ትስስር ሥራ ቀርቷል " - ዶ/ር ካሳሁን ጎፌ
የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ዶ/ር ካሳሁን ጎፌ ከሲሚንቶ አምራቾች ጋር መወያየታቸው ተሰምቷል።
በዚህም ወቅት " ከዚህ ቀደም በሚኒስትር መስሪያ ቤቱ በኩል ይደረግ የነበረዉ የሲሚንቶ ግብይት ትስስር ሥራ ከዛሬ ጀምሮ ቀርቷል " ብለዋል።
አምራቾች በራሳቸዉ ኃላፊነት በሚመርጧቸዉ አከፋፋዮችና ቸርቻሪዎች በኩል ለተጠቃሚዎች በተመጣጣኝ ዋጋ እንዲያቀርቡ አሳስበዋል፡፡
የሲሚንቶ ገበያዉን ለማረጋጋት ጥብቅ ቁጥጥርና ክትትል ይደረጋል ያሉ ሲሆን የአፈጻጸም ሪፖርት ለሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ በማያቀርቡ በማናቸዉም የሲሚንቶ አምራች ላይ " የማያዳግም እርምጃ ይወስዳል " ሲሉ አስጠንቅቀዋል።
ሚኒስትሩ " አዲሱን ዉሳኔና አቅጣጫ ተከትሎ በግብይት ሰንሰለቱ የደላላ ጣልቃ ገብነት የከሰመ፣ ለመንግስት ፕሮጀክቶችና ለተጠቃሚዉ ህብረተሰብ አስተማማኝ የሲሚንቶ አቅርቦት የተረጋገጠ፣ አምራቾችም ተገቢዉን ትርፍ እያገኙ የከምፓኒዎቻቸዉን ዘላቂ ዕድገት የሚያስቀጥሉበት እንዲሆን " ብለዋል።
የግብይት ሥርዓቱ ሙሉ በሙሉ ከካሽ ክፍያ ነጻ ሆኖ በዲጂታል ክፍያ ሥርዓት እንዲፈጸም አቅጣጫ አስቀምጠዋል።
በውይይት መድረኩ ወቅት አምራቾች የምርት አቅማቸውን እንዲያሳድጉ ተብሏል።
ሲሚንቶ አምራቾች አዲሱን ውሳኔ በማክበር እንደሚተገብሩ ተናግረው ነገር ግን የማምረቻ ግብዓት ፣ የኃይል አቅርቦትና ተያያዥ ችግሮች እንዲፈቱላቸዉ ጠይቀዋል፡፡
@tikvahethiopia
#ጥቆማ #የኢትዮጵያአየርመንገድ
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ በTRAINEE CABIN CREW ፣ በSENIOR ACCOUNTANT I እንዲሁም በሌሎች ዘርፎች ማስታወቂያ አውጥቷል።
ለTRAINEE CABIN CREW በኢትዮጵያ ሀገር አቀፍ የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና ቢያንስ (ዝቅተኛው) 200 ነጥብ ያስመዘገበ ለማመልከት ብቁ ነው።
የዕድሜ ገደቡ ከ19 እስከ 30 ዓመት ነው።
ቁመት ቢያንስ 1.58 ሜትር እና 212 ሴ.ሜ የሆነ ክንድ ለሴት እንዲሁም ለወንድ ቢያንስ 1.70 ሜትር ቁመት መሆን አለበት።
የምዝገባ ጊዜው ከህዳር 08/2017 ዓ/ም እስከ ህዳር 12/2017 ዓ/ም ነው።
ምዝገባው ፦
- በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ (አዳማ)
- አዲስ አበባ (በኦንላይን ልክ ማመልከቻው ሲከፈት ይፋ ይደረጋል)
- አምቦ ዩኒቨርሲቲ (አምቦ)
- አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ (አርባ ምንጭ)
- አሶሳ ዩኒቨርሲቲ (አሶሳ)
- ባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ (ባህር ዳር)
- ወሎ ዩኒቨርሲቲ (ደሴ)
- ድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ (ድሬዳዋ)
- ጋምቤላ ዩኒቨርሲቲ ( ጋምቤላ)
- ጎንደር ዩኒቨርሲቲ (ጎንደር)
- ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ (ሀዋሳ)
- ጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ (ጅግጅጋ)
- ጅማ ዩኒቨርሲቲ (ጅማ)
- መቐለ ዩኒቨርሲቲ (መቐለ)
- ወለጋ ዩኒቨርሲቲ (ነቀምቴ)
- መደወላቡ ዩኒቨርሲቲ (ሮቤ)
- ሰመራ ዩኒቨርሲቲ (ሰመራ)
- ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ (ወልቂጤ) ይከናወናል።
ተጨማሪ መረጃዎች፣ የሚያስፈልጉ መስፈርቶች፣ ዝርዝር ጉዳዮች እንዲሁም ሌሎችም የወጡ ማስታወቂያዎች በዚህ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ድረገጽ ላይ ሰፍሮ ይገኛል ይመልከቱ 👇
https://corporate.ethiopianairlines.com/AboutEthiopian/careers/vacancies
@tikvahethiopia
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ በTRAINEE CABIN CREW ፣ በSENIOR ACCOUNTANT I እንዲሁም በሌሎች ዘርፎች ማስታወቂያ አውጥቷል።
ለTRAINEE CABIN CREW በኢትዮጵያ ሀገር አቀፍ የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና ቢያንስ (ዝቅተኛው) 200 ነጥብ ያስመዘገበ ለማመልከት ብቁ ነው።
የዕድሜ ገደቡ ከ19 እስከ 30 ዓመት ነው።
ቁመት ቢያንስ 1.58 ሜትር እና 212 ሴ.ሜ የሆነ ክንድ ለሴት እንዲሁም ለወንድ ቢያንስ 1.70 ሜትር ቁመት መሆን አለበት።
የምዝገባ ጊዜው ከህዳር 08/2017 ዓ/ም እስከ ህዳር 12/2017 ዓ/ም ነው።
ምዝገባው ፦
- በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ (አዳማ)
- አዲስ አበባ (በኦንላይን ልክ ማመልከቻው ሲከፈት ይፋ ይደረጋል)
- አምቦ ዩኒቨርሲቲ (አምቦ)
- አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ (አርባ ምንጭ)
- አሶሳ ዩኒቨርሲቲ (አሶሳ)
- ባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ (ባህር ዳር)
- ወሎ ዩኒቨርሲቲ (ደሴ)
- ድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ (ድሬዳዋ)
- ጋምቤላ ዩኒቨርሲቲ ( ጋምቤላ)
- ጎንደር ዩኒቨርሲቲ (ጎንደር)
- ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ (ሀዋሳ)
- ጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ (ጅግጅጋ)
- ጅማ ዩኒቨርሲቲ (ጅማ)
- መቐለ ዩኒቨርሲቲ (መቐለ)
- ወለጋ ዩኒቨርሲቲ (ነቀምቴ)
- መደወላቡ ዩኒቨርሲቲ (ሮቤ)
- ሰመራ ዩኒቨርሲቲ (ሰመራ)
- ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ (ወልቂጤ) ይከናወናል።
ተጨማሪ መረጃዎች፣ የሚያስፈልጉ መስፈርቶች፣ ዝርዝር ጉዳዮች እንዲሁም ሌሎችም የወጡ ማስታወቂያዎች በዚህ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ድረገጽ ላይ ሰፍሮ ይገኛል ይመልከቱ 👇
https://corporate.ethiopianairlines.com/AboutEthiopian/careers/vacancies
@tikvahethiopia
#Infinix_HOT50_Pro+
አዲሱ የኢንፊኒክስ HOT 50 Pro+ ስልክ 7 ነጥብ 8 ሚሊሜትር ያህል ቀጭን ዲዛይን ይዞ የመጣ ሲሆን ይህም ስልኩን ለአያያዝ ምቹ ከማድረጉም በላይ እጅዎት ላይ እጅግ ያምራል፡፡
@Infinix_Et|@Infinixet
#Infinix #InfinixHOT50Pro+ #WOOOWNewHOT #InfinixHOT50Series
አዲሱ የኢንፊኒክስ HOT 50 Pro+ ስልክ 7 ነጥብ 8 ሚሊሜትር ያህል ቀጭን ዲዛይን ይዞ የመጣ ሲሆን ይህም ስልኩን ለአያያዝ ምቹ ከማድረጉም በላይ እጅዎት ላይ እጅግ ያምራል፡፡
@Infinix_Et|@Infinixet
#Infinix #InfinixHOT50Pro+ #WOOOWNewHOT #InfinixHOT50Series
#MPESASafaricom
ይህን የመሰለ ቅናሽ ሲገኝ የምን አይን ማሸት፤ ለዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ወደ ግቢ ጉዞ የሃገር ዉስጥ በረራ ትኬታችንን በM-PESA ስንቆርጥ 5% ተመላሽ በልዩ ሁኔታ ተዘጋጅቶ ይጠብቀናል ፤ እየሄዱ ማፈስ ነው እንግዲህ!
የM-PESA ሳፋሪኮም መተግበሪያን በዚህ ሊንክ እናውርድ ፡https://play.google.com/store/apps/details?id=et.safaricom.mpesa.lifestyle
የቴሌግራም ቻናላችንን እዚህ እንቀላቀል 👉https://t.iss.one/Safaricom_Ethiopia_PLC
ስለ አገልግሎታችን ማንኛውንም ጥያቄ ወይም መረጃ በቴሌግራም ቻናላችን https://t.iss.one/Safaricom_Ethiopia_PLC 24/7 ማግኘት ይቻላል!
#FurtherAheadTogether
ይህን የመሰለ ቅናሽ ሲገኝ የምን አይን ማሸት፤ ለዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ወደ ግቢ ጉዞ የሃገር ዉስጥ በረራ ትኬታችንን በM-PESA ስንቆርጥ 5% ተመላሽ በልዩ ሁኔታ ተዘጋጅቶ ይጠብቀናል ፤ እየሄዱ ማፈስ ነው እንግዲህ!
የM-PESA ሳፋሪኮም መተግበሪያን በዚህ ሊንክ እናውርድ ፡https://play.google.com/store/apps/details?id=et.safaricom.mpesa.lifestyle
የቴሌግራም ቻናላችንን እዚህ እንቀላቀል 👉https://t.iss.one/Safaricom_Ethiopia_PLC
ስለ አገልግሎታችን ማንኛውንም ጥያቄ ወይም መረጃ በቴሌግራም ቻናላችን https://t.iss.one/Safaricom_Ethiopia_PLC 24/7 ማግኘት ይቻላል!
#FurtherAheadTogether
#Amhara
🔴 “ ስለፓለቲካ ምንም የማያውቁ፣ ሮጠው የማያመልጡና ሰርተው የማይበሉ አረጋዊያን ላይ መድፍ መወርወር ሊወገዝ ይገባል ” - ነዋሪዎች
🔵 “ ፈቃደኝነት እንዲኖራቸው የሚፈለጉ ኃይሎች ቢያንስ ድርድር እንደሚፈልጉ በመግለጫ የተደገፈ ሀሳብ ቢሰጡ ህዝቡ ከስቃይ እፎይ ይል ነበር ” - ካውንስሉ
ከአንድ ዓመት በላይ ባስቆጠረውና ልጓም ባጣው በአማራ ክልል በመንግሥት የጸጥታ ኃይሎች እና በፋኖ መካከል በሚደረገው የተኩስ ልውውጥ ሳቢያ የንጹሐ ስቃይ ተባብሶ መቀጠሉን አሁንም የገፈቱ ቀማሾችና የዓይን እማኞች ገልጸውልናል።
ንጻሃን ዜጎች እየተጎዱ ያሉት በምድር በሚደረግ የተኩስ ልውውጥ ከዚህም አለፍ ሲል በአየር ላይ በሚካሄድ ጥቃትም ጭምር ነው።
ሰሞኑን በክልሉ በከባድ መሳሪያ ጨምር የታገዘ የተኩስ ልውውጥ ከተካሄደባቸው አካባቢዎች መካከል አንዱ በሆነው አዊ ዞን በንጹሐን ላይ ከባድ የአካል ጉዳት፣ የንብረት ውድመት መድረሱ ታውቋል፡፡
በዞኑ ጓጉሳ ሽኩዳድ ወረዳ ቲሊሊ ከተማ ዙሪያ በ ‘ፋኖ’ እና መከላከያ መካከል የሚደረገው የተኩስ ልውውጥ በንጹሐን ላይ የከፋ ጉዳት እየደረሰ በመሆኑ ዓለም አቀፍ ተቋማት ለጉዳዩ ትኩረት እንዲሰጡ የተጎጂ ቤተሰቦችና ነዋሪዎች በቲክቫህ ኢትዮጵያ በኩል ተማጽነዋል።
ከቀናት በፊት ከእንጅባራ አቅጣጫ ተተኩሶ ቲሊሊ ከተማ ወጣ ብሎ ከአንድ የገጠር ቤት ላይ ያረፈ መድፍ በቤተሰብ አባላት ላይ ከባድ የአካል ጉዳት፣ በንብረት ላይም የከፋ ውድመት ማድረሱን ነዋሪዎቹ ተናግረዋል።
“ ሰሞኑን ወደ ቲሊሊ መድፍ ተወርውሮ በንጹሐን ቤት ላይ አርፏል። አንዲት ሴት እግሯ ተቆርጧል። ህጻን ልጅም ተጎድታለች። ስድስት ከብቶች ተገድለዋል። ቤቱ ሙሉ ለሙሉ ወድሟል ” ሲሉ አንድ የዓይን እማኝ ገልጸዋል።
ሌላኛው የተጎጂ ቤተሰብ፣ “ ከቲሊሊ ከተማ ወጣ ብሎ ነው የተወረወረው መድፍ ጉዳት ያደረሰው ” ሲሉ ተናግረዋል።
“ በወቅቱ በመከላከያና በፋኖ መካከል የተኩስ ልውውጥ ተደርጎ ነበር። መድፉ የተተኮሰው ግን ከእንጅባራ አቅጣጫ ነው። እሳቱ አልበርድ ብሎ የሰፈር ሰው በልቅሶ፣ በከፍተኛ ሀዘን ውስጥ ነው ያለው ” ብለዋል።
“ የሞተ የለም። ከሁለቱ ሰዎች ውጪ ሌላ የተጎዳም የለም። ከብቶች ግን ሁሉም አልቀዋል ” ነው ያሉት።
ስለፓለቲካ ምንም የማያውቁ፣ ሮጠው የማያመልጡና ሰርተው የማይበሉ አረጋዊያን ላይ መድፍ መወርወር ሊወገዝ ይገባል ሲሉም ነዋሪዎች ተናግረዋል።
ድርጊቱ የተፈጸመው ማክሰኞ ጥቅምት 26 ቀን 2017 ዓ/ም ከቀኑ 7: 30 ገደማ መሆኑን አስረድተዋል።
በአካባቢው ባለው ሁኔታ የመንግስት የጸጥታ ኃይሎች ንጹሐንን ይደበድባሉ ሲሉም ቅሬታቸውን አቅርበዋል።
" ያለው ድባብም የሚመች አይደለም " ሲሉም ገልጸዋል።
በምዕራብና ሰሜን ጎጃም፣ በጎንደር፣ በሰሜን ወሎ የተለያዩ አከባቢዎች ሰሞኑን ተፈጸመ በተባለ በድሮንና ከባድ መሳሪያ ጭምር የታገዘ የተኩስ ልውውጥ ቁጥራቸው ገና በውል የማይታወቅ ንጹሐን ሰዎች ግድያና የአካል ጉዳት እንደደረሰባቸው ነዋሪዎች በሀዘን ስሜት አስረድተዋል።
የመንግስት የጸጥታ ኃይሎች ‘ የፋኖ ኃይሎችን ትደግፋላችሁ ’ በማለት ንጹሃን ላይ ከሚያደርሱት ግድያና ድብደባ በተጨማሪ ፥ ታጣቂዎችም ‘ መንግስትን ትደፋላችሁ ’ በሚል በንጹሐን ላይ ግድያ መፈጸማቸው ከተጎጂ ቤተሰቦች የደረሱን መረጃዎች ያመለክታሉ።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ በክልሉ ባለው የጸጥታ ችግር የንጹሐን ግድያ ፣ የአካል ጉዳት ፣ እገታ ፣ የትምህርትና የግብርና ሥራ መስተጓጎል እንዳስከተለ ይታወቃል ፤ እየደረሰ ያለው ዘርፈ ብዙ ጉዳትም ሊቀለበስ አልቻለም። ሁለቱንም ተዋጊ ኃይሎች ለድርድር እንዲቀራረቡ ከማድረግ አንፃር ተስፋ ይኖር ይሆን ? ሲል የአማራ ክልል የሰላም ካውንስልን ጠይቋል።
ካውንስሉ ምን ምላሽ ሰጠ ?
" በሁለቱም ወገኖች በኩል ድርድርና ምክክር መደረግ አለበት ብለን ነው የተነሳበውና ይሄንኑ ወደ ተግባር ለማሸጋገር በመንግስት በኩል ፈቃደኝነት እንዳለ ገልጸናል፡፡
ፈቃደኝነት እንዲኖራቸው የሚፈለጉ ኃይሎች ቢያንስ ድርድር እንደሚፈልጉ በመግለጫ የተደገፈ ሀሳብ ቢሰጡ ህዝቡ ከስቃይ እፎይ ይል ነበር፡፡
' የገበያ ግርግር ለሌባ ያመቻል ' እንዲሉ በተፈጠረው ጦርነት ምክንያት ሌሎች አክተሮችም ስላሉ ግድያው፣ ሌብነቱ፣ እገታው ከዚሁ የመነጨ ነው፡፡
የእርስ በእርስ ጦርነት ከባድ ችግር ነው የሚያስከትከለው፡፡ ወደፊትም እንዲህ አይነቱ ነገር እጅግ በጣም ዘግናኝ የሆነ መጥፎ ነገር ሁሉ ያመጣል።
ይሄ እንዳይመጣ ወደ ድርድር እንዲመጡ ነው ለሁሉም አካላት ጥሪ ያደረግነው፡፡ የሆነው ሆነና እንደ ጠቅላላ ጉባዔ የምንለው ነገር አለና ያኔ ለሁሉም ጥያቄዎች ዝርዝር ማብራሪያ እንሰጣለን፡፡
ይህንኑ ጉዳይ በሚመለከት ሰሞኑን ስብሰብ እንደርጋለን፡፡ የሰላም ካውንስሉ የራሱን ጠቅላላ ጉባዔ ጠርቷል፡፡ ከእሁድ በኋላ ጠቅላላ መግለጫ የምንሰጥ ነው የሚሆነው በዚያን ጊዜ ጠቅላላ ህዝቡ እንዲያውቀው የምናደርገው ጉዳይ አለ " ብሏል።
(የካውንስሉን የጉባዔ ውጤትና ለሚቀርቡት እሮሮዎች የተሻለ የሚለውን ጉዳይ በተመለከተ በቀጣይ መረጃ የምናደርሳችሁ ይሆናል)
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
🔴 “ ስለፓለቲካ ምንም የማያውቁ፣ ሮጠው የማያመልጡና ሰርተው የማይበሉ አረጋዊያን ላይ መድፍ መወርወር ሊወገዝ ይገባል ” - ነዋሪዎች
🔵 “ ፈቃደኝነት እንዲኖራቸው የሚፈለጉ ኃይሎች ቢያንስ ድርድር እንደሚፈልጉ በመግለጫ የተደገፈ ሀሳብ ቢሰጡ ህዝቡ ከስቃይ እፎይ ይል ነበር ” - ካውንስሉ
ከአንድ ዓመት በላይ ባስቆጠረውና ልጓም ባጣው በአማራ ክልል በመንግሥት የጸጥታ ኃይሎች እና በፋኖ መካከል በሚደረገው የተኩስ ልውውጥ ሳቢያ የንጹሐ ስቃይ ተባብሶ መቀጠሉን አሁንም የገፈቱ ቀማሾችና የዓይን እማኞች ገልጸውልናል።
ንጻሃን ዜጎች እየተጎዱ ያሉት በምድር በሚደረግ የተኩስ ልውውጥ ከዚህም አለፍ ሲል በአየር ላይ በሚካሄድ ጥቃትም ጭምር ነው።
ሰሞኑን በክልሉ በከባድ መሳሪያ ጨምር የታገዘ የተኩስ ልውውጥ ከተካሄደባቸው አካባቢዎች መካከል አንዱ በሆነው አዊ ዞን በንጹሐን ላይ ከባድ የአካል ጉዳት፣ የንብረት ውድመት መድረሱ ታውቋል፡፡
በዞኑ ጓጉሳ ሽኩዳድ ወረዳ ቲሊሊ ከተማ ዙሪያ በ ‘ፋኖ’ እና መከላከያ መካከል የሚደረገው የተኩስ ልውውጥ በንጹሐን ላይ የከፋ ጉዳት እየደረሰ በመሆኑ ዓለም አቀፍ ተቋማት ለጉዳዩ ትኩረት እንዲሰጡ የተጎጂ ቤተሰቦችና ነዋሪዎች በቲክቫህ ኢትዮጵያ በኩል ተማጽነዋል።
ከቀናት በፊት ከእንጅባራ አቅጣጫ ተተኩሶ ቲሊሊ ከተማ ወጣ ብሎ ከአንድ የገጠር ቤት ላይ ያረፈ መድፍ በቤተሰብ አባላት ላይ ከባድ የአካል ጉዳት፣ በንብረት ላይም የከፋ ውድመት ማድረሱን ነዋሪዎቹ ተናግረዋል።
“ ሰሞኑን ወደ ቲሊሊ መድፍ ተወርውሮ በንጹሐን ቤት ላይ አርፏል። አንዲት ሴት እግሯ ተቆርጧል። ህጻን ልጅም ተጎድታለች። ስድስት ከብቶች ተገድለዋል። ቤቱ ሙሉ ለሙሉ ወድሟል ” ሲሉ አንድ የዓይን እማኝ ገልጸዋል።
ሌላኛው የተጎጂ ቤተሰብ፣ “ ከቲሊሊ ከተማ ወጣ ብሎ ነው የተወረወረው መድፍ ጉዳት ያደረሰው ” ሲሉ ተናግረዋል።
“ በወቅቱ በመከላከያና በፋኖ መካከል የተኩስ ልውውጥ ተደርጎ ነበር። መድፉ የተተኮሰው ግን ከእንጅባራ አቅጣጫ ነው። እሳቱ አልበርድ ብሎ የሰፈር ሰው በልቅሶ፣ በከፍተኛ ሀዘን ውስጥ ነው ያለው ” ብለዋል።
“ የሞተ የለም። ከሁለቱ ሰዎች ውጪ ሌላ የተጎዳም የለም። ከብቶች ግን ሁሉም አልቀዋል ” ነው ያሉት።
ስለፓለቲካ ምንም የማያውቁ፣ ሮጠው የማያመልጡና ሰርተው የማይበሉ አረጋዊያን ላይ መድፍ መወርወር ሊወገዝ ይገባል ሲሉም ነዋሪዎች ተናግረዋል።
ድርጊቱ የተፈጸመው ማክሰኞ ጥቅምት 26 ቀን 2017 ዓ/ም ከቀኑ 7: 30 ገደማ መሆኑን አስረድተዋል።
በአካባቢው ባለው ሁኔታ የመንግስት የጸጥታ ኃይሎች ንጹሐንን ይደበድባሉ ሲሉም ቅሬታቸውን አቅርበዋል።
" ያለው ድባብም የሚመች አይደለም " ሲሉም ገልጸዋል።
በምዕራብና ሰሜን ጎጃም፣ በጎንደር፣ በሰሜን ወሎ የተለያዩ አከባቢዎች ሰሞኑን ተፈጸመ በተባለ በድሮንና ከባድ መሳሪያ ጭምር የታገዘ የተኩስ ልውውጥ ቁጥራቸው ገና በውል የማይታወቅ ንጹሐን ሰዎች ግድያና የአካል ጉዳት እንደደረሰባቸው ነዋሪዎች በሀዘን ስሜት አስረድተዋል።
የመንግስት የጸጥታ ኃይሎች ‘ የፋኖ ኃይሎችን ትደግፋላችሁ ’ በማለት ንጹሃን ላይ ከሚያደርሱት ግድያና ድብደባ በተጨማሪ ፥ ታጣቂዎችም ‘ መንግስትን ትደፋላችሁ ’ በሚል በንጹሐን ላይ ግድያ መፈጸማቸው ከተጎጂ ቤተሰቦች የደረሱን መረጃዎች ያመለክታሉ።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ በክልሉ ባለው የጸጥታ ችግር የንጹሐን ግድያ ፣ የአካል ጉዳት ፣ እገታ ፣ የትምህርትና የግብርና ሥራ መስተጓጎል እንዳስከተለ ይታወቃል ፤ እየደረሰ ያለው ዘርፈ ብዙ ጉዳትም ሊቀለበስ አልቻለም። ሁለቱንም ተዋጊ ኃይሎች ለድርድር እንዲቀራረቡ ከማድረግ አንፃር ተስፋ ይኖር ይሆን ? ሲል የአማራ ክልል የሰላም ካውንስልን ጠይቋል።
ካውንስሉ ምን ምላሽ ሰጠ ?
" በሁለቱም ወገኖች በኩል ድርድርና ምክክር መደረግ አለበት ብለን ነው የተነሳበውና ይሄንኑ ወደ ተግባር ለማሸጋገር በመንግስት በኩል ፈቃደኝነት እንዳለ ገልጸናል፡፡
ፈቃደኝነት እንዲኖራቸው የሚፈለጉ ኃይሎች ቢያንስ ድርድር እንደሚፈልጉ በመግለጫ የተደገፈ ሀሳብ ቢሰጡ ህዝቡ ከስቃይ እፎይ ይል ነበር፡፡
' የገበያ ግርግር ለሌባ ያመቻል ' እንዲሉ በተፈጠረው ጦርነት ምክንያት ሌሎች አክተሮችም ስላሉ ግድያው፣ ሌብነቱ፣ እገታው ከዚሁ የመነጨ ነው፡፡
የእርስ በእርስ ጦርነት ከባድ ችግር ነው የሚያስከትከለው፡፡ ወደፊትም እንዲህ አይነቱ ነገር እጅግ በጣም ዘግናኝ የሆነ መጥፎ ነገር ሁሉ ያመጣል።
ይሄ እንዳይመጣ ወደ ድርድር እንዲመጡ ነው ለሁሉም አካላት ጥሪ ያደረግነው፡፡ የሆነው ሆነና እንደ ጠቅላላ ጉባዔ የምንለው ነገር አለና ያኔ ለሁሉም ጥያቄዎች ዝርዝር ማብራሪያ እንሰጣለን፡፡
ይህንኑ ጉዳይ በሚመለከት ሰሞኑን ስብሰብ እንደርጋለን፡፡ የሰላም ካውንስሉ የራሱን ጠቅላላ ጉባዔ ጠርቷል፡፡ ከእሁድ በኋላ ጠቅላላ መግለጫ የምንሰጥ ነው የሚሆነው በዚያን ጊዜ ጠቅላላ ህዝቡ እንዲያውቀው የምናደርገው ጉዳይ አለ " ብሏል።
(የካውንስሉን የጉባዔ ውጤትና ለሚቀርቡት እሮሮዎች የተሻለ የሚለውን ጉዳይ በተመለከተ በቀጣይ መረጃ የምናደርሳችሁ ይሆናል)
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ደመወዝ : የደመወዝ ጭማሪ ተፈቅዶና በጀቱም ጸድቆ ክፍያው ከጥቅምት ወር 2017 ዓ.ም. ጀምሮ ተግባራዊ እንደሚደረግ የሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ዛሬ አሳውቋል። ከገንዘብ ሚኒስቴር የተፈቀደው በጀት፣ የአፈጻጸም መመሪያውንና የክፍያ ትዕዛዙን ለ12ቱ ክልሎች፣ ለሁለቱ የከተማ አስተዳደሮችና ለፌደራል ተቋማት ዛሬ መተላለፉም ተገልጿል። (ከጥቅምት ወር 2017 ዓ/ም ጀምሮ ተግባራዊ የሚደረገው ይፋዊ የደመወዝ…
#ደመወዝ
" በእኛ መስሪያ ቤት በኩል የተስተካከለው የጥቅምት ወር ደመወዝ ተከፍሏል " - መኩሪያ ኃይሌ (ዶ/ር)
የሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ኮሚሽነር የሆኑት መኩሪያ ኃይሌ (ዶ/ር) ፥ የመንግሥት ሠራተኞች የደመወዝ ማስተካከያን በተመለከተ ባሰራጩት ፅሁፍ፣ የገንዘብ ሚኒስቴር የተጨማሪ ክፍያ በጀቱን ለሚመለከታቸው ተቋማት ፈቅዷል። በእኛ መስሪያ ቤትም በኩል የተስተካከለውን የጥቅምት ወር ደመወዝ ተከፍሏል " ብለዋል።
" ሌሎችም እንደዚሁ የከፈሉ አሉ። የቀሩት ደግሞ የማጥራት ሥራ እየሰሩ ሊሆን ይችላል። " ሲሉ ገልጸዋል።
" እነዚያም ዝግጅታቸውን ሲያጠናቅቁ የተስተካከለው የጥቅምት ወር ክፍያ ታሳቢ በማድረግ የሚከፍሉ ይሆናል " ሲሉ አስረድተዋል።
" የተፈቀደው የመንግስት ሠራተኞች የደመወዝ ማስተካከያ ክፍያ ዘግይቷል፥ ቀርቷል የሚሉ ሃሳቦች እየተራመዱ ነው " ያሉት ኮሚሽነሩ " በሲቪል ሰርቪስ በኩል የሚለቀቁ መረጃዎች ኦፊሴላዊና የሚተገበሩ መሆኑን መተማመን ጥሩ ነው " ሲሉ ገልጸዋል።
" ከሠራተኞች ደመወዝ ስኬል ጋር በተገናኘ በማህበራዊ ሚዲያ የሚሰራጩ አሳሳች ወሬዎችን እንዳታምኗቸው መልዕክት አስተላልፌ ነበር " ሲሉም አክለዋል።
ከሰሞኑን ከሠራተኞች ደመወዝ ጋር በተገናኘ በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያዎች መረጃዎችን ተዘዋውረዋል።
ከነዚህም አንዱ ጭማሪው እንዳልተከፈለ የሚገልጽ ነው።
ነገር ግን በአንዳንድ መ/ቤቶች ጭማሪው መከፈሉ ታውቋል። ጭማሪው ያልተከፈለባቸውም መ/ቤቶችም ግን አሉ ፤ እነዚህ ናቸው ' እያጣሩ ናቸው " የተባሉት።
" ተጨምሯል የተባለው ገንዘብ ያን ያህል አይደለም " - ሠራተኞች
" የደመወዝ ጭማሪ ይደረጋል " የሚለውን መረጃ የሰሙ ሠራተኞች ከፍተኛ ጭማሪ ጠብቀው እንደነበር ነገር ግን እጃቸው ላይ የደረሰው እዚህ ግባ የማይባል እንደሆነ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
አንድ ቃላቸውን የሰጡ ሠራተኛ ፥ " ምንኑን ከምኑን ልናደርገው ይሄ ብቻ እንደተጨመረ አልገባኝም " ብለዋል።
ጭማሪው አነስተኛ እንደሆነ የገለጹ አንዲት ሠራተኛ በበኩላቸው " ከሚጨመረው ብር በላይ ወሬው በዝቶ ይበልጥ ኑሮውን እንዳያስወድደው " ሲሉ ስጋታቸውን ገልጸዋል።
" አይደለም ደመወዝ ተጨመረ ተብሎ ሳይባል እንኳን ነጋዴው ሁሉን ነገር አምጥቶ የሚጭነው እኛው ድሃው ዜጎች ላይ ነው አሁን ተጨምሯል የተባለው ገንዘብ ከኑሮው ውድነቱ አንጻር ያን ያህል አይደለም፤ ጭራሽ ነጋዴዎቹ ዋጋ ጨምረው አሁንም አልገፋ ያለውን ኑሮን እንዳያከብዱብን " ብለዋል።
ያነጋገርናቸው ሌሎችም ሠራተኞች " ደመወዝ ተጨመረ " የተባለው አነስተኛ እንደሆነ፣ የቁጥጥር ስራ እንዲሰራ ፣ ሌሎች የሠራተኞችን ህይወት የሚያቀሉ መፍትሄዎች እንዲፈለጉ ጥሪ አቅርበዋል።
#TikvahEthiopia
@tikvahethiopia
" በእኛ መስሪያ ቤት በኩል የተስተካከለው የጥቅምት ወር ደመወዝ ተከፍሏል " - መኩሪያ ኃይሌ (ዶ/ር)
የሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ኮሚሽነር የሆኑት መኩሪያ ኃይሌ (ዶ/ር) ፥ የመንግሥት ሠራተኞች የደመወዝ ማስተካከያን በተመለከተ ባሰራጩት ፅሁፍ፣ የገንዘብ ሚኒስቴር የተጨማሪ ክፍያ በጀቱን ለሚመለከታቸው ተቋማት ፈቅዷል። በእኛ መስሪያ ቤትም በኩል የተስተካከለውን የጥቅምት ወር ደመወዝ ተከፍሏል " ብለዋል።
" ሌሎችም እንደዚሁ የከፈሉ አሉ። የቀሩት ደግሞ የማጥራት ሥራ እየሰሩ ሊሆን ይችላል። " ሲሉ ገልጸዋል።
" እነዚያም ዝግጅታቸውን ሲያጠናቅቁ የተስተካከለው የጥቅምት ወር ክፍያ ታሳቢ በማድረግ የሚከፍሉ ይሆናል " ሲሉ አስረድተዋል።
" የተፈቀደው የመንግስት ሠራተኞች የደመወዝ ማስተካከያ ክፍያ ዘግይቷል፥ ቀርቷል የሚሉ ሃሳቦች እየተራመዱ ነው " ያሉት ኮሚሽነሩ " በሲቪል ሰርቪስ በኩል የሚለቀቁ መረጃዎች ኦፊሴላዊና የሚተገበሩ መሆኑን መተማመን ጥሩ ነው " ሲሉ ገልጸዋል።
" ከሠራተኞች ደመወዝ ስኬል ጋር በተገናኘ በማህበራዊ ሚዲያ የሚሰራጩ አሳሳች ወሬዎችን እንዳታምኗቸው መልዕክት አስተላልፌ ነበር " ሲሉም አክለዋል።
ከሰሞኑን ከሠራተኞች ደመወዝ ጋር በተገናኘ በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያዎች መረጃዎችን ተዘዋውረዋል።
ከነዚህም አንዱ ጭማሪው እንዳልተከፈለ የሚገልጽ ነው።
ነገር ግን በአንዳንድ መ/ቤቶች ጭማሪው መከፈሉ ታውቋል። ጭማሪው ያልተከፈለባቸውም መ/ቤቶችም ግን አሉ ፤ እነዚህ ናቸው ' እያጣሩ ናቸው " የተባሉት።
" ተጨምሯል የተባለው ገንዘብ ያን ያህል አይደለም " - ሠራተኞች
" የደመወዝ ጭማሪ ይደረጋል " የሚለውን መረጃ የሰሙ ሠራተኞች ከፍተኛ ጭማሪ ጠብቀው እንደነበር ነገር ግን እጃቸው ላይ የደረሰው እዚህ ግባ የማይባል እንደሆነ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
አንድ ቃላቸውን የሰጡ ሠራተኛ ፥ " ምንኑን ከምኑን ልናደርገው ይሄ ብቻ እንደተጨመረ አልገባኝም " ብለዋል።
ጭማሪው አነስተኛ እንደሆነ የገለጹ አንዲት ሠራተኛ በበኩላቸው " ከሚጨመረው ብር በላይ ወሬው በዝቶ ይበልጥ ኑሮውን እንዳያስወድደው " ሲሉ ስጋታቸውን ገልጸዋል።
" አይደለም ደመወዝ ተጨመረ ተብሎ ሳይባል እንኳን ነጋዴው ሁሉን ነገር አምጥቶ የሚጭነው እኛው ድሃው ዜጎች ላይ ነው አሁን ተጨምሯል የተባለው ገንዘብ ከኑሮው ውድነቱ አንጻር ያን ያህል አይደለም፤ ጭራሽ ነጋዴዎቹ ዋጋ ጨምረው አሁንም አልገፋ ያለውን ኑሮን እንዳያከብዱብን " ብለዋል።
ያነጋገርናቸው ሌሎችም ሠራተኞች " ደመወዝ ተጨመረ " የተባለው አነስተኛ እንደሆነ፣ የቁጥጥር ስራ እንዲሰራ ፣ ሌሎች የሠራተኞችን ህይወት የሚያቀሉ መፍትሄዎች እንዲፈለጉ ጥሪ አቅርበዋል።
#TikvahEthiopia
@tikvahethiopia