#Safaricom
💫ከዳር እስከ ዳር አስተማማኙን ኔትወርካችንን እያሰፋን ወደ እናንተ እይቀረብን ነው!🙌👏 ከአስተማማኙ ኔትወርካችን ጋር አሁንም በአብሮነት ወደፊት!
አስተማማኙን ኔትወርክ ዛሬውኑ እንቀላቀል!
የቴሌግራም ቦታችንን https://t.iss.one/official_safaricomet_bot በመጠቀም የአየር ሰዓት ወይንም ልዩ ልዩ ጥቅሎችን እንግዛ!
#SafaricomEthiopia #MPESASafaricom #1Wedefit
#Furtheraheadtogether
💫ከዳር እስከ ዳር አስተማማኙን ኔትወርካችንን እያሰፋን ወደ እናንተ እይቀረብን ነው!🙌👏 ከአስተማማኙ ኔትወርካችን ጋር አሁንም በአብሮነት ወደፊት!
አስተማማኙን ኔትወርክ ዛሬውኑ እንቀላቀል!
የቴሌግራም ቦታችንን https://t.iss.one/official_safaricomet_bot በመጠቀም የአየር ሰዓት ወይንም ልዩ ልዩ ጥቅሎችን እንግዛ!
#SafaricomEthiopia #MPESASafaricom #1Wedefit
#Furtheraheadtogether
#ብርሃን_ባንክ
የብርሃን ጉዞጎ ተጠቃሚዎች ብቻ የሚያገኙትን ልዩ ቅናሾች እና ጥቅሞች ያግኙ፣ ይህም ጉዞዎን የበለጠ ተመጣጣኝ እና አስደሳች ያደርገዋል።
👉ደንበኞች በአካል መሄድ ሳያስፈልጋቸው ከ10 በላይ አለም አቀፍ የአየር መንገዶች የበረራ ትኬቶችን ዋጋ ማወዳደር ያስችላል።
👉ደንበኞች በሚመርጡት አየር መንገድ የበረራ ትኬቶች ላይ ቅናሽ ዋጋዎች እንዲያገኙ ያስችላል።
👉ደንበኞች በሚመርጡት ሰዓት እና ዋጋ አስተማማኝ የበረራ ቡኪንግ ለመያዝ ያስችላል።
👉በሁሉም የባንካችን ቅርንጫፎች፣ በሞባይል ወይንም በኢንተርኔት ባንኪንግ ክፍያዎችን መፈጸም ያስችላል፡፡
👉ያለ ተጨማሪ ክፍያ ሳምንቱን ሙሉ ለ 24 ሰዓታት የባለሙያ ምክር እና እርዳታ እንዲያገኙ ያስችላል። ስለ ብርሃን ጉዞጎ (GuzoGo) አገልግሎት ተጨማሪ መረጃ ለማግኘት በ0116506355 /0116507425 ወይም በነፃ የጥሪ ማዕከል ቁጥር 8292 ላይ ይደውሉ፤
ከታች የሚገኙትን ሊንኮች በመጫን የማህበራዊ ድህረ-ገጾቻችንን ይቀላቀሉ!
Facebook
Telegram
Instagram
Twitter
LinkedIn
YouTube
የብርሃን ጉዞጎ ተጠቃሚዎች ብቻ የሚያገኙትን ልዩ ቅናሾች እና ጥቅሞች ያግኙ፣ ይህም ጉዞዎን የበለጠ ተመጣጣኝ እና አስደሳች ያደርገዋል።
👉ደንበኞች በአካል መሄድ ሳያስፈልጋቸው ከ10 በላይ አለም አቀፍ የአየር መንገዶች የበረራ ትኬቶችን ዋጋ ማወዳደር ያስችላል።
👉ደንበኞች በሚመርጡት አየር መንገድ የበረራ ትኬቶች ላይ ቅናሽ ዋጋዎች እንዲያገኙ ያስችላል።
👉ደንበኞች በሚመርጡት ሰዓት እና ዋጋ አስተማማኝ የበረራ ቡኪንግ ለመያዝ ያስችላል።
👉በሁሉም የባንካችን ቅርንጫፎች፣ በሞባይል ወይንም በኢንተርኔት ባንኪንግ ክፍያዎችን መፈጸም ያስችላል፡፡
👉ያለ ተጨማሪ ክፍያ ሳምንቱን ሙሉ ለ 24 ሰዓታት የባለሙያ ምክር እና እርዳታ እንዲያገኙ ያስችላል። ስለ ብርሃን ጉዞጎ (GuzoGo) አገልግሎት ተጨማሪ መረጃ ለማግኘት በ0116506355 /0116507425 ወይም በነፃ የጥሪ ማዕከል ቁጥር 8292 ላይ ይደውሉ፤
ከታች የሚገኙትን ሊንኮች በመጫን የማህበራዊ ድህረ-ገጾቻችንን ይቀላቀሉ!
Telegram
YouTube
" አባታችንን አፈልጉን " - ቤተሰቦች
ከላይ በፎቶው ላይ የምትመለከቷቸው አቶ አቡበከር ያሲን ኡመር ይባላሉ።
ነዋሪነታቸው በአዲስ አበባ ኮ/ቀ ክፍለ ከተማ ዓለም ባንክ አካባቢ ሲሆን፤ በቀን ጥቅምት 13 ቀን 2017 ዓ.ም ከቤት እንደወጡ አልተመለሱም።
የለበሱት ልብስ እና ጫማ እንዲሁም ደግሞ በወቅቱ የያዙት ሳምሶናይት ከተፍኪ ከተማ ትንሽ አለፍ ብሎ ባለ አካባቢ የተገኘ ቢሆንም ፤ የአካባቢው ፖሊስ እና የአደጋ ግዜ ሰራተኞች በውሀ ውስጥ እና በአካባቢው ፍለጋ አድርገው አቶ አቡበከርን ሊገኙ አልቻሉም።
አቶ አቡበከር እድሜያቸው ከ55 እስከ 60 የሚጠጋ ሲሆን፤ ረጅም ጠቆር ያሉ አባት ናቸው።
በወቅቱ ለብሰውት የነበረው ልብስ ወድቆ በመገኘቱ በአሁኑ ወቅት የአለባበሳቸውን ሁኔታ መለየት አልተቻልም።
በዚህም ምክንያት አባታቸው ከጠፉበት ሰዓት ጀምሮ ቤተሰባቸው በጣም ከፍተኛ ጭንቅ ውስጥ ይገኛሉ።
እኚህን አባት ያያችሁ አሊያም ያሉበትን የምታውቁ ጥቆማ በመስጠት ተባበሩን ሲሉ ቤተሰቦቻቸው ተማጽነዋል።
ፈላጊ ቤተሰብ ስልክ ፦ 0938704092
@tikvahethiopia
ከላይ በፎቶው ላይ የምትመለከቷቸው አቶ አቡበከር ያሲን ኡመር ይባላሉ።
ነዋሪነታቸው በአዲስ አበባ ኮ/ቀ ክፍለ ከተማ ዓለም ባንክ አካባቢ ሲሆን፤ በቀን ጥቅምት 13 ቀን 2017 ዓ.ም ከቤት እንደወጡ አልተመለሱም።
የለበሱት ልብስ እና ጫማ እንዲሁም ደግሞ በወቅቱ የያዙት ሳምሶናይት ከተፍኪ ከተማ ትንሽ አለፍ ብሎ ባለ አካባቢ የተገኘ ቢሆንም ፤ የአካባቢው ፖሊስ እና የአደጋ ግዜ ሰራተኞች በውሀ ውስጥ እና በአካባቢው ፍለጋ አድርገው አቶ አቡበከርን ሊገኙ አልቻሉም።
አቶ አቡበከር እድሜያቸው ከ55 እስከ 60 የሚጠጋ ሲሆን፤ ረጅም ጠቆር ያሉ አባት ናቸው።
በወቅቱ ለብሰውት የነበረው ልብስ ወድቆ በመገኘቱ በአሁኑ ወቅት የአለባበሳቸውን ሁኔታ መለየት አልተቻልም።
በዚህም ምክንያት አባታቸው ከጠፉበት ሰዓት ጀምሮ ቤተሰባቸው በጣም ከፍተኛ ጭንቅ ውስጥ ይገኛሉ።
እኚህን አባት ያያችሁ አሊያም ያሉበትን የምታውቁ ጥቆማ በመስጠት ተባበሩን ሲሉ ቤተሰቦቻቸው ተማጽነዋል።
ፈላጊ ቤተሰብ ስልክ ፦ 0938704092
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#መቐለ " የጊዚያዊ አስተዳደሩን የሚፃረር አቋም በመያዝ በጊዚያዊ አስተዳደሩ ስር ያለን መዋቅር መምራት አትችሉም " - አቶ ጌታቸው ረዳ የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ አዲሱን የመቐለ ከንቲባ ከስራ አገዱ። ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ " ለዶ/ር ረዳኢ በርሀ " በማለት ጥቅምት 15/2017 ዓ.ም በፃፉት ደብዳቤ ፤ አዲሱ የመቐለ ከተማ ከንቲባ ዶ/ር ረዳኢ በርሀ ህጋዊ ያልሆነ…
#Tigray
" እስከ በጀት መገደብ የሚደርስ ቅጣት ሊጣል ይችላል " - የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር
የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር በፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ ፊርማ ተፈርሞ ባሰራጨው መመሪያ ፤ " የጊዚያዊ አስተዳደሩ እቅዶች ማደናቀፍ እና በዘፈቀደ ህጋዊ ያልሆነ ሹመት መስጠትና መንሳት የበጀት ቅጣትና የህግ ተጠያቂነት ያስከትላል " ሲል አሳስቧል።
መመሪያ ደ/18/8/84 እንደሚለው " በህወሓት አመራሮች የተፈጠረ የፓለቲካ ልዩነት ምክንያት በማድረግ መንግስታዊ ስልጣን እና ሃላፊነት የሌለው ' ቡድን ' በማለት የተጠቀሰው በዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል የሚመራው ህወሓት የሚሰጠው ሹመት የመሻርና ሹመት የመስጠት ተግባር ፍፁም ተቀባይነት የለውም " ብሏል።
በመሆኑም ፦
1. ቡድኑ የሚያካሄዳቸውን ህጋዊ ያልሆኑ ተግባራት እንዲቆም ፤ ይህንን የጊዚያዊ መንግስቱ መመሪያ በመቀበል ፍርድ ቤት ጨምሮ የዞን እና የወረዳ የመንግስት መዋቅሮች ህጋዊ አሰራር እንዲከተሉና ህግ በሚጥስ ላይ ህጋዊ እርምጃ እንዲወስዱ፤
2. በክልሉ በየመዋቅሩ ያሉ ምክር ቤቶች ጊዚያቸው ያለፈ እና ህጋዊ መሰረታቸው ያበቃ መሆኑን በመቀበል ሹመት ከመስጠትና ከመሻር እንዲቆጠቡ፤
... ሲል ማስጠንቀቅያ ሰጥቷል።
ከዚህ ባለፈ የጊዚያዊ አስተዳደሩን እቅዶች የሚፃረር የከተማና የገጠር ወረዳ የአስተዳደር መዋቅር በጀት እስከመገደብ የሚደርስ ቅጣት እንደሚጣልበት በአፅንኦት አሳስቧል።
#TikvahEthiopiaFamilyMeklle
@tikvahethiopia
" እስከ በጀት መገደብ የሚደርስ ቅጣት ሊጣል ይችላል " - የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር
የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር በፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ ፊርማ ተፈርሞ ባሰራጨው መመሪያ ፤ " የጊዚያዊ አስተዳደሩ እቅዶች ማደናቀፍ እና በዘፈቀደ ህጋዊ ያልሆነ ሹመት መስጠትና መንሳት የበጀት ቅጣትና የህግ ተጠያቂነት ያስከትላል " ሲል አሳስቧል።
መመሪያ ደ/18/8/84 እንደሚለው " በህወሓት አመራሮች የተፈጠረ የፓለቲካ ልዩነት ምክንያት በማድረግ መንግስታዊ ስልጣን እና ሃላፊነት የሌለው ' ቡድን ' በማለት የተጠቀሰው በዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል የሚመራው ህወሓት የሚሰጠው ሹመት የመሻርና ሹመት የመስጠት ተግባር ፍፁም ተቀባይነት የለውም " ብሏል።
በመሆኑም ፦
1. ቡድኑ የሚያካሄዳቸውን ህጋዊ ያልሆኑ ተግባራት እንዲቆም ፤ ይህንን የጊዚያዊ መንግስቱ መመሪያ በመቀበል ፍርድ ቤት ጨምሮ የዞን እና የወረዳ የመንግስት መዋቅሮች ህጋዊ አሰራር እንዲከተሉና ህግ በሚጥስ ላይ ህጋዊ እርምጃ እንዲወስዱ፤
2. በክልሉ በየመዋቅሩ ያሉ ምክር ቤቶች ጊዚያቸው ያለፈ እና ህጋዊ መሰረታቸው ያበቃ መሆኑን በመቀበል ሹመት ከመስጠትና ከመሻር እንዲቆጠቡ፤
... ሲል ማስጠንቀቅያ ሰጥቷል።
ከዚህ ባለፈ የጊዚያዊ አስተዳደሩን እቅዶች የሚፃረር የከተማና የገጠር ወረዳ የአስተዳደር መዋቅር በጀት እስከመገደብ የሚደርስ ቅጣት እንደሚጣልበት በአፅንኦት አሳስቧል።
#TikvahEthiopiaFamilyMeklle
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update
🔵 “ መምህራኑን ስምንት ቀናት አስረው ነው የፈቷቸው። በሕግ አምላክ አሁንም ደመወዛችን ይከፈለን ” - የወላይታ ዞን መምህራን
🔴 “ ከ10,500 በላይ መምህራን ደመወዝ አልተፈጸመላቸውም ” - የዞኑ መምህራን ማኀበር
በወላይታ ዞን የሚገኙ መምህራን ያልተከፈላቸውን ደመወዝ በተመለከተ ለኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) አቤቱታ ለማስገባት እንቅስቃሴ ሲያደርጉ “ በፓሊስ መታሰራቸው ” ተሰምቶ ነበር።
የደመወዝ ቅሬታቸው ባለመፈታቱ የመብት ጥያቄ ለማንሳት ባደረጉት ፒቲሽን የማሰባሰብ እንቅስቃሴ ነበር ፓሊስ “ አመጽ ለመቀስቀስ ተንቀሳቅሰዋል። የዞኑን ገጽታ አጥፍተዋል ” በሚል ያሰራቸው።
ቲክቫህ ኢትዮጵያም የታሰሩት መምህራን ተፈቱ ? የደመወዝ ቅሬታችሁስ መፍትሄ አገኘ ? ሲል ዛሬ ቅሬታ ያላቸው መምህራንን ጠይቋል።
ምን መለሱ ?
“ ምህራኑን ስምንት ቀናት አስረው ነው የፈቷቸው። ሦስቱም መምህራን ተፈትተዋል። በሕግ አምላክ አሁንም ደመወዛችን ይከፈለን።
‘ መንግስትን ከሕዝብ አጣልታችኋል ’ የሚለው ክስ በፍርድ ቤት ሲቀርብ ምንም መረጃ የላቸውም። ከዚያ ጋር ተያይዞ ነው ፍርድ ቤት በዋስ የለቀቃቸው።
የመማር ማስተማር ሥራ ተጀምሯል።
አሁንም ደመወዝ እንዲከፈለን እንፈልጋለን።
መምህራን ከአዕምሮ ጋር የተያያዘ ሥራ ስለሚሰሩ የመማር ማስተማር ሂደቱን በትክክል እንዲተገብሩ ደመወዝ መከፈል አለበት።
የሐምሌ ደመወዝ እስካሁን አልተከፈለም። ለመምህራንና ለጤና ባለሙያ 40 በመቶ፣ ለፓሊስ 20 በመቶ እንጂ ከዚህ ውጪ ደመወዝ አልተከፈለም።
አሁን እንደገና አጠቃላይ የትምህርት ባለሙያም ወደታች ወርዶ ‘የሐምሌን ደመወዝ እንከፍላለን’ በማለት አመራርም በአጠቃላይ ተረባርቦ መምህራን ወደ ስራ አስገብተዋል።
ፍርድ ቤትም ገና የራሱን ቀጠሮ እየሰጠ ነው የሐምሌ ደመወዝ ባለመከፈሉ ምክንያት ” ብለዋል።
ደመወዛቸው በወቅቱ አለመፈጸሙ ትልቅ ጥፋት ሆኖ እያለ ይህንኑ ቅሬታ መምህራን ታስረው መቆዬታቸው ግፍ መሆኑን ያስረዱ ሲሆን፣ ቲክቫህ ኢትዮጵያም በዚሁ ቅሬታ ላይ ምን እየሰሩ እንደሆነ የክልሉና የዞኑን መምህራን ማኀበር ጠይቋል።
የክልሉ መምህራን ማኀበር የመምህራንን መታሰር በተመለከተ እስካሁን ሪፓርት እንዳልተደረገለት/ቅሬታ ያደረሰው አካል እንደሌለ ገልጾ፣ በይበልጥ የዞኑ መምህራን ማኀበር እንዲጠየቅ አሳስቧል።
ተመሳሳይ ጥያቄ ያቀረብንላቸው የወላይታ ዞን መምህራን ማኀበር ሊቀ መንበር መምህርት ባዩሽ ዘውዴ፣ “ በቅርቡ ታስረዋል ስለተባሉት መምህራን ለኛ ኦፊሻሊ የቀረበልን ምንም መረጃ የለም ” የሚል ምላሽ ሰጥተውናል።
“ ያመለከተልን አካል የለም። ከውጪ ወሬ ነው እየሰማን ያለነው። ወደ አክሽን እንዳንገባ የመጣልን መረጃ የለም ” ያሉት ሊቀመንበሯ፣ “ እንነጋገርበት ወደኛ መምጣት ይችላሉ ” ብለዋል።
የደመወዝ ክፍያን ቅሬታ በተመለከተም በሰጡን ምላሽም፣ ከ10 ሺህ 500 በላይ መምህራን ደመመወዝ እንዳልተፈጸመላቸው ገልጸው፣ ማኀበሩ ለሚመለከታቸው አካላት ሁሉ እንዳሳወቀ አስረድተዋል።
የክፍያ አለመፈጸምን በተለመከተ ምላሽ እንዲሰጡ ከዚህ ቀደም የጠየቅናቸው የወላይታ ዞን ትምህርት መምሪያ ኃላፊ አቶ ጎበዜ ጎደና፣ “ አራት ወረዳዎች ላይ መሉ ደመወዝም ሳይሆን የተወሰነ እየተከፈለ ነው። የሐምሌ ወር ክፍያ ላልተፈጸመላቸውም ወረዳዎች ገቢ ሰብስበው እንዲከፍሉ እየተደረገ ነው ” ብለው ነበር።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
🔵 “ መምህራኑን ስምንት ቀናት አስረው ነው የፈቷቸው። በሕግ አምላክ አሁንም ደመወዛችን ይከፈለን ” - የወላይታ ዞን መምህራን
🔴 “ ከ10,500 በላይ መምህራን ደመወዝ አልተፈጸመላቸውም ” - የዞኑ መምህራን ማኀበር
በወላይታ ዞን የሚገኙ መምህራን ያልተከፈላቸውን ደመወዝ በተመለከተ ለኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) አቤቱታ ለማስገባት እንቅስቃሴ ሲያደርጉ “ በፓሊስ መታሰራቸው ” ተሰምቶ ነበር።
የደመወዝ ቅሬታቸው ባለመፈታቱ የመብት ጥያቄ ለማንሳት ባደረጉት ፒቲሽን የማሰባሰብ እንቅስቃሴ ነበር ፓሊስ “ አመጽ ለመቀስቀስ ተንቀሳቅሰዋል። የዞኑን ገጽታ አጥፍተዋል ” በሚል ያሰራቸው።
ቲክቫህ ኢትዮጵያም የታሰሩት መምህራን ተፈቱ ? የደመወዝ ቅሬታችሁስ መፍትሄ አገኘ ? ሲል ዛሬ ቅሬታ ያላቸው መምህራንን ጠይቋል።
ምን መለሱ ?
“ ምህራኑን ስምንት ቀናት አስረው ነው የፈቷቸው። ሦስቱም መምህራን ተፈትተዋል። በሕግ አምላክ አሁንም ደመወዛችን ይከፈለን።
‘ መንግስትን ከሕዝብ አጣልታችኋል ’ የሚለው ክስ በፍርድ ቤት ሲቀርብ ምንም መረጃ የላቸውም። ከዚያ ጋር ተያይዞ ነው ፍርድ ቤት በዋስ የለቀቃቸው።
የመማር ማስተማር ሥራ ተጀምሯል።
አሁንም ደመወዝ እንዲከፈለን እንፈልጋለን።
መምህራን ከአዕምሮ ጋር የተያያዘ ሥራ ስለሚሰሩ የመማር ማስተማር ሂደቱን በትክክል እንዲተገብሩ ደመወዝ መከፈል አለበት።
የሐምሌ ደመወዝ እስካሁን አልተከፈለም። ለመምህራንና ለጤና ባለሙያ 40 በመቶ፣ ለፓሊስ 20 በመቶ እንጂ ከዚህ ውጪ ደመወዝ አልተከፈለም።
አሁን እንደገና አጠቃላይ የትምህርት ባለሙያም ወደታች ወርዶ ‘የሐምሌን ደመወዝ እንከፍላለን’ በማለት አመራርም በአጠቃላይ ተረባርቦ መምህራን ወደ ስራ አስገብተዋል።
ፍርድ ቤትም ገና የራሱን ቀጠሮ እየሰጠ ነው የሐምሌ ደመወዝ ባለመከፈሉ ምክንያት ” ብለዋል።
ደመወዛቸው በወቅቱ አለመፈጸሙ ትልቅ ጥፋት ሆኖ እያለ ይህንኑ ቅሬታ መምህራን ታስረው መቆዬታቸው ግፍ መሆኑን ያስረዱ ሲሆን፣ ቲክቫህ ኢትዮጵያም በዚሁ ቅሬታ ላይ ምን እየሰሩ እንደሆነ የክልሉና የዞኑን መምህራን ማኀበር ጠይቋል።
የክልሉ መምህራን ማኀበር የመምህራንን መታሰር በተመለከተ እስካሁን ሪፓርት እንዳልተደረገለት/ቅሬታ ያደረሰው አካል እንደሌለ ገልጾ፣ በይበልጥ የዞኑ መምህራን ማኀበር እንዲጠየቅ አሳስቧል።
ተመሳሳይ ጥያቄ ያቀረብንላቸው የወላይታ ዞን መምህራን ማኀበር ሊቀ መንበር መምህርት ባዩሽ ዘውዴ፣ “ በቅርቡ ታስረዋል ስለተባሉት መምህራን ለኛ ኦፊሻሊ የቀረበልን ምንም መረጃ የለም ” የሚል ምላሽ ሰጥተውናል።
“ ያመለከተልን አካል የለም። ከውጪ ወሬ ነው እየሰማን ያለነው። ወደ አክሽን እንዳንገባ የመጣልን መረጃ የለም ” ያሉት ሊቀመንበሯ፣ “ እንነጋገርበት ወደኛ መምጣት ይችላሉ ” ብለዋል።
የደመወዝ ክፍያን ቅሬታ በተመለከተም በሰጡን ምላሽም፣ ከ10 ሺህ 500 በላይ መምህራን ደመመወዝ እንዳልተፈጸመላቸው ገልጸው፣ ማኀበሩ ለሚመለከታቸው አካላት ሁሉ እንዳሳወቀ አስረድተዋል።
የክፍያ አለመፈጸምን በተለመከተ ምላሽ እንዲሰጡ ከዚህ ቀደም የጠየቅናቸው የወላይታ ዞን ትምህርት መምሪያ ኃላፊ አቶ ጎበዜ ጎደና፣ “ አራት ወረዳዎች ላይ መሉ ደመወዝም ሳይሆን የተወሰነ እየተከፈለ ነው። የሐምሌ ወር ክፍያ ላልተፈጸመላቸውም ወረዳዎች ገቢ ሰብስበው እንዲከፍሉ እየተደረገ ነው ” ብለው ነበር።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
የሴቶች_እና_የሕፃናት_ሰብአዊ_መብቶች_ሁኔታ_ዓመታዊ_ሪፖርት_ከሰኔ_ወር_2015_ዓ_ም_እስከ_ሰኔ_ወር.pdf
2.7 MB
#EHRC
ሰሞኑን የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን የሴቶች እና የሕፃናት ሰብአዊ መብቶች ሁኔታ ዓመታዊ ሪፖርት ይፋ አድርጎ ነበር።
ይህ ሪፖርት ከሰኔ 2015 ዓ/ም እስከ ሰኔ 2016 ዓ/ም ያለውን ጊዜ የሚሸፍን ነው።
በዚሁ የዓመታዊ ሪፖርት ፥ በግጭት ውስጥ ባሉ እና በትጥቅ ግጭት ውስጥ በቆዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች በመንግሥት የጸጥታ ኃይሎች እና በታጣቂ ቡድኖች በተለያየ ጊዜ በሚፈጸሙ ጥቃቶች ሴቶችና ሕፃናትን ፦
🔴 ለሞት ፣ ለአካል ጉዳት እንዲሁም ለወሲባዊ እና ጾታዊ ጥቃቶች መጋለጣቸው፤
🔴 በግጭት ዐውድ ውስጥ በቆዩት፦
° አፋር፣
° ቤኒሻንጉል ጉሙዝ
° ትግራይ ክልሎች በቂ መልሶ የማቋቋም ሥራ ባለመከናወኑ በሕክምና ተቋማት የውሃና ኤሌክትሪክ ፣ የሕክምና ቁሳቁስ ፣ የአምቡላንስ ፣ የመድኃኒት ፣ የክትባትና የምግብ አቅርቦት ውስንነት ምክንያት እናቶችና ጨቅላ ሕፃናት በቅድመ ወሊድ ፣ በወሊድ ፣ ድኅረ ወሊድ ፣ በድንገተኛ ወሊድ ወቅት ሊያገኙት የሚገባቸውን መሠረታዊ አገልግሎቶች እያገኙ ባለመሆኑ የእናቶችና ሕፃናት ሞት እየጨመረ መምጣቱ፣
🔴 በሀገሪቱ በቀጠሉ ግጭቶች እና በተፈጠረው የደኅንነት ሥጋት በተለያዩ ክልሎች የሚገኙ በሺህዎች የሚቆጠሩ ትምህርት ቤቶች መዘጋታቸው በአሳሳቢነት ተጠቅሰዋል፡፡
(ሙሉ ሪፖርቱ ከላይ ተያይዟል)
@tikvahethiopia
ሰሞኑን የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን የሴቶች እና የሕፃናት ሰብአዊ መብቶች ሁኔታ ዓመታዊ ሪፖርት ይፋ አድርጎ ነበር።
ይህ ሪፖርት ከሰኔ 2015 ዓ/ም እስከ ሰኔ 2016 ዓ/ም ያለውን ጊዜ የሚሸፍን ነው።
በዚሁ የዓመታዊ ሪፖርት ፥ በግጭት ውስጥ ባሉ እና በትጥቅ ግጭት ውስጥ በቆዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች በመንግሥት የጸጥታ ኃይሎች እና በታጣቂ ቡድኖች በተለያየ ጊዜ በሚፈጸሙ ጥቃቶች ሴቶችና ሕፃናትን ፦
🔴 ለሞት ፣ ለአካል ጉዳት እንዲሁም ለወሲባዊ እና ጾታዊ ጥቃቶች መጋለጣቸው፤
🔴 በግጭት ዐውድ ውስጥ በቆዩት፦
° አፋር፣
° ቤኒሻንጉል ጉሙዝ
° ትግራይ ክልሎች በቂ መልሶ የማቋቋም ሥራ ባለመከናወኑ በሕክምና ተቋማት የውሃና ኤሌክትሪክ ፣ የሕክምና ቁሳቁስ ፣ የአምቡላንስ ፣ የመድኃኒት ፣ የክትባትና የምግብ አቅርቦት ውስንነት ምክንያት እናቶችና ጨቅላ ሕፃናት በቅድመ ወሊድ ፣ በወሊድ ፣ ድኅረ ወሊድ ፣ በድንገተኛ ወሊድ ወቅት ሊያገኙት የሚገባቸውን መሠረታዊ አገልግሎቶች እያገኙ ባለመሆኑ የእናቶችና ሕፃናት ሞት እየጨመረ መምጣቱ፣
🔴 በሀገሪቱ በቀጠሉ ግጭቶች እና በተፈጠረው የደኅንነት ሥጋት በተለያዩ ክልሎች የሚገኙ በሺህዎች የሚቆጠሩ ትምህርት ቤቶች መዘጋታቸው በአሳሳቢነት ተጠቅሰዋል፡፡
(ሙሉ ሪፖርቱ ከላይ ተያይዟል)
@tikvahethiopia
የሀገር_ውስጥ_ተፈናቃዮች_የሰብአዊ_መብቶች_ሁኔታ_ዓመታዊ_ሪፖርት_ከሰኔ_ወር_2015_ዓ_ም_እስከ_ሰኔ.pdf
2.6 MB
#EHRC
የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች የሰብአዊ መብቶች ሁኔታ ዓመታዊ ሪፖርት ይፋ አድርጓል።
በዚህም ሪፖርቱ ለሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች የሰብአዊ ድጋፍ በአግባቡ ሊቀርብ እንዲሁም ደግሞ የሰብአዊ መብቶች መርሖችን ፣ የተፈናቃዮችን ክብር ፣ ደኅንነት እና ፍላጎት ያከበረ ዘላቂ መፍትሔ ሊመቻች እንደሚገባ አሳስቧል።
የኢሰመኮ ተጠባባቂ ዋና ኮሚሽነር ራኬብ መሰለ ምን አሉ ?
" ኢትዮጵያ ውስጥ መፈናቀል በአብዛኛው እየተከሰተ ያለው በግጭቶች ምክንያት በመሆኑ ግጭቶችን በአፋጣኝ ሁኔታ በሰላማዊ መንገድ መፍታትና እንዳይባባሱ አስፈላጊውን እርምጃ መውሰድ፤ መፈናቀልን ለመከላከል እና በዘላቂነት መፍትሔ ለመስጠት ወሳኝ በመሆናቸው ትኩረት ሰጥቶ መተግበር ያስፈልጋል።
በተፈጥሮ አደጋም የሚከሰት መፈናቀል ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተስፋፋ በመምጣቱ ለቅድመ አደጋ መከላከል እና ለአደጋ ጊዜ ምላሽ አሰጣጥ ትኩረት ሊሰጠው ይገባል።
የሰብአዊ መብቶች መርሖችን መሠረት ያደረገ ዘላቂ መፍትሔ ለመስጠት እንዲሁም የሽግግር ፍትሕ እና የሀገራዊ ምክክር ሂደቶች የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮችን መብቶችና ተሳትፎ በሚያረጋገጥ ሁኔታ እንዲተገበሩ ሁሉም ባለድርሻ አካላት ኃላፊነታቸውን ሊወጡ ይገባል። "
(ሙሉ ሪፖርቱ ከላይ ተያይዟል)
@tikvahethiopia
የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች የሰብአዊ መብቶች ሁኔታ ዓመታዊ ሪፖርት ይፋ አድርጓል።
በዚህም ሪፖርቱ ለሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች የሰብአዊ ድጋፍ በአግባቡ ሊቀርብ እንዲሁም ደግሞ የሰብአዊ መብቶች መርሖችን ፣ የተፈናቃዮችን ክብር ፣ ደኅንነት እና ፍላጎት ያከበረ ዘላቂ መፍትሔ ሊመቻች እንደሚገባ አሳስቧል።
የኢሰመኮ ተጠባባቂ ዋና ኮሚሽነር ራኬብ መሰለ ምን አሉ ?
" ኢትዮጵያ ውስጥ መፈናቀል በአብዛኛው እየተከሰተ ያለው በግጭቶች ምክንያት በመሆኑ ግጭቶችን በአፋጣኝ ሁኔታ በሰላማዊ መንገድ መፍታትና እንዳይባባሱ አስፈላጊውን እርምጃ መውሰድ፤ መፈናቀልን ለመከላከል እና በዘላቂነት መፍትሔ ለመስጠት ወሳኝ በመሆናቸው ትኩረት ሰጥቶ መተግበር ያስፈልጋል።
በተፈጥሮ አደጋም የሚከሰት መፈናቀል ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተስፋፋ በመምጣቱ ለቅድመ አደጋ መከላከል እና ለአደጋ ጊዜ ምላሽ አሰጣጥ ትኩረት ሊሰጠው ይገባል።
የሰብአዊ መብቶች መርሖችን መሠረት ያደረገ ዘላቂ መፍትሔ ለመስጠት እንዲሁም የሽግግር ፍትሕ እና የሀገራዊ ምክክር ሂደቶች የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮችን መብቶችና ተሳትፎ በሚያረጋገጥ ሁኔታ እንዲተገበሩ ሁሉም ባለድርሻ አካላት ኃላፊነታቸውን ሊወጡ ይገባል። "
(ሙሉ ሪፖርቱ ከላይ ተያይዟል)
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
" የከንቲባዋ ቃል አሳዝኖናል " - የ97 ተመዝጋቢዎች
" የ1997 ኮንዶሚኒየም ተመዝጋቢዎች 20 አመት ሙሉ የጠበቅነዉን ተስፋ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ' 97 ሰጥተን ጨርሰናል ' ማለታቸዉ በጣም አሳዝኖናል " ሲሉ ገልጸዋል።
" ቁጠባችንን በአግባቡ እየቆጠብን የነበርን በሺዎች የምንቆጠር ዜጎች አለን " ብለዋል።
" እኛም ዜጎች ነን በኪራይ ቤት እድሜችን አለቀ " ሲሉ አክለዋል።
ነዋሪዎቹ ፥ " ለሕዝብ ዕንባ ጠበቂ ተቋም ደብዳቤ አስገብተናል አዲስ አበባ ቤቶች ኤጀንሲ ግን መልስ አልሰጣቸውም " ሲሉ አስታውሰዋል።
" ከዚህ ባለፈ የጠቅላይ ሚኒስቴር ቢሮም መፍትሄ እንዲፈልግልን ብለን ነበር ጋር ግን ምላሽ ተነፍጎናል " ብለዋል።
" ወዴት እንደምንሄድ ጨንቆናል ፍትህ ተጓሎብናል ፤ አሁን ካለው የኑሮ ጫና አንጻር የቤት ኪራይ ትልቁ ፈተና ነው እባካችሁ መፍትሄ ፈልጉልን " ሲሉ ድምጻቸውን አሰምተዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
TIKVAH-ETHIOPIA
#የ97ተመዝጋቢዎች
" ምላሽ ካልተሰጠበት በ15 ቀናት ውስጥ ለሕዝብ ተ/ም/ቤት እናቀርባለን " - የሕዝብ ዕንባ ጠባቂ ተቋም
የጋራ መኖሪያ (ኮንዶሚኒየም) ቤት ለማግኝት ተመዝግበው ገንዘብ በባንክ ሲቆጥቡ የነበሩና እስካሁን ቤቱን ያላገኙ የ1997 ዓ.ም. ተመዝጋቢዎች አቤቱታ፣ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምላሽ ካልሰጠበት፣ በ15 ቀናት ውስጥ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንደሚያቀርበው የሕዝብ ዕንባ ጠባቂ ተቋም አስታወቀ፡፡
ተቋሙ ፤ ለ20 ዓመታት ያህል " ቤት ይደርሰናል " ብለው እየጠበቁ ቢሆንም መንግሥት ምላሽ አልሰጠንም ያሉ ቢያንስ 67 ሰዎችን አቤቱታ ተቀብሎ እየመረመረ መሆኑን ጠቁሟል።
አቤቱታውን ተከትሎም የከተማ አስተዳደሩን ማብራሪያ ጠይቋል።
ምላሽ ካልመጣ ተቋሙ የሚወስደው ዕርምጃ እንደሚኖ ገልጿል።
" በ1997 ዓ.ም. ተመዝግበን ቤት ሳይደርሰን ለሌሎች ተሰጥቷል ፤ በሚል ተደራጅተው ጠይቀዋል፣ እኛም ጥያቄ አቅርበናል፡፡ ነገር ግን የከተማ አስተዳደሩ እስካሁን መልስ አልሰጠንም " ብሏል።
የአዲስ አበባ ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ በቅርቡ በነበረ የውይይት መድረክ ፤ ከዚህ በፊት በ2015 ዓ/ም በተላለፉት ቤቶች የ1997 ዓ/ም ቆጣቢዎች ሁሉም ዕጣ እንዲወጣላቸው መደረጉንና ለተመዘገቡት ሁሉ ቤት ተሰጥቶ መጠናቀቁን ገልጸው ነበር፡፡
ይሁን እንጂ የሕዝብ ዋና ዕንባ ጠባቂ ተቋም በዚህ ሁኔታ ከከተማ አስተዳደሩ የደረሰው ምላሽ እንደሌለ አመልክቷል።
ለረዥም ጊዜ ጠብቀው ምላሽ ያልተሰጣቸውን ሰዎች አቤቱታ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በማቅረብ የመጨረሻ ዕልባት እንዲያገኝ ይደረጋልም ብሏል።
በ1997 ዓ.ም. የቤት ምዝገባ በርካቶች ተመዝግበው ለ20 ዓመታት ሲቆጥቡ መቆየታቸውን የገለጸው ተቋሙ ፤ " መንግሥት የተሠሩትን ቤቶችን ለአርሶ አደር ልጆች ፣ ለፖለቲካ ሹመኞች እና ለተለያዩ ግለሰቦች እየሰጠ ነው " በማለት ቅሬታ ሲያቀርቡ ነበር ብሏል።
ከዚህ ቀደም በአዲስ አበባና በሸገር ከተማ ቤታቸው የፈረሰባቸው ነዋሪዎች ባቀረቡት አቤቱታ ካሳና ተለዋጭ ቦታ እንዲሰጥ በተደጋጋሚ ጥያቄ ሲቀርብ እንደነበር መረጃ የደረሰው ዕንባ ጠባቂ ተቋም፣ አሁን በመሀል አዲስ አበባ ከሚከናወነው የኮሪደር ልማት ጋር በተገናኘ የደረሰው የሕዝብ አቤቱታ እንደሌለ አመልክቷል።
በአሁኑ ወቅት ወደ ሕዝብ ዕንባ ጠባቂ ተቋም በብዛት እየቀረቡ ያሉ አቤቱታዎች ፦
° የሥራ ስንብት፣
° የመሬት አገልግሎት፣
° የጡረታ መብት
° የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን የተመለከቱ መሆናቸውን አመልክቷል።
ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የሪፖርተር ጋዜጣ ነው።
@tikvahethiopia
" ምላሽ ካልተሰጠበት በ15 ቀናት ውስጥ ለሕዝብ ተ/ም/ቤት እናቀርባለን " - የሕዝብ ዕንባ ጠባቂ ተቋም
የጋራ መኖሪያ (ኮንዶሚኒየም) ቤት ለማግኝት ተመዝግበው ገንዘብ በባንክ ሲቆጥቡ የነበሩና እስካሁን ቤቱን ያላገኙ የ1997 ዓ.ም. ተመዝጋቢዎች አቤቱታ፣ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምላሽ ካልሰጠበት፣ በ15 ቀናት ውስጥ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንደሚያቀርበው የሕዝብ ዕንባ ጠባቂ ተቋም አስታወቀ፡፡
ተቋሙ ፤ ለ20 ዓመታት ያህል " ቤት ይደርሰናል " ብለው እየጠበቁ ቢሆንም መንግሥት ምላሽ አልሰጠንም ያሉ ቢያንስ 67 ሰዎችን አቤቱታ ተቀብሎ እየመረመረ መሆኑን ጠቁሟል።
አቤቱታውን ተከትሎም የከተማ አስተዳደሩን ማብራሪያ ጠይቋል።
ምላሽ ካልመጣ ተቋሙ የሚወስደው ዕርምጃ እንደሚኖ ገልጿል።
" በ1997 ዓ.ም. ተመዝግበን ቤት ሳይደርሰን ለሌሎች ተሰጥቷል ፤ በሚል ተደራጅተው ጠይቀዋል፣ እኛም ጥያቄ አቅርበናል፡፡ ነገር ግን የከተማ አስተዳደሩ እስካሁን መልስ አልሰጠንም " ብሏል።
የአዲስ አበባ ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ በቅርቡ በነበረ የውይይት መድረክ ፤ ከዚህ በፊት በ2015 ዓ/ም በተላለፉት ቤቶች የ1997 ዓ/ም ቆጣቢዎች ሁሉም ዕጣ እንዲወጣላቸው መደረጉንና ለተመዘገቡት ሁሉ ቤት ተሰጥቶ መጠናቀቁን ገልጸው ነበር፡፡
ይሁን እንጂ የሕዝብ ዋና ዕንባ ጠባቂ ተቋም በዚህ ሁኔታ ከከተማ አስተዳደሩ የደረሰው ምላሽ እንደሌለ አመልክቷል።
ለረዥም ጊዜ ጠብቀው ምላሽ ያልተሰጣቸውን ሰዎች አቤቱታ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በማቅረብ የመጨረሻ ዕልባት እንዲያገኝ ይደረጋልም ብሏል።
በ1997 ዓ.ም. የቤት ምዝገባ በርካቶች ተመዝግበው ለ20 ዓመታት ሲቆጥቡ መቆየታቸውን የገለጸው ተቋሙ ፤ " መንግሥት የተሠሩትን ቤቶችን ለአርሶ አደር ልጆች ፣ ለፖለቲካ ሹመኞች እና ለተለያዩ ግለሰቦች እየሰጠ ነው " በማለት ቅሬታ ሲያቀርቡ ነበር ብሏል።
ከዚህ ቀደም በአዲስ አበባና በሸገር ከተማ ቤታቸው የፈረሰባቸው ነዋሪዎች ባቀረቡት አቤቱታ ካሳና ተለዋጭ ቦታ እንዲሰጥ በተደጋጋሚ ጥያቄ ሲቀርብ እንደነበር መረጃ የደረሰው ዕንባ ጠባቂ ተቋም፣ አሁን በመሀል አዲስ አበባ ከሚከናወነው የኮሪደር ልማት ጋር በተገናኘ የደረሰው የሕዝብ አቤቱታ እንደሌለ አመልክቷል።
በአሁኑ ወቅት ወደ ሕዝብ ዕንባ ጠባቂ ተቋም በብዛት እየቀረቡ ያሉ አቤቱታዎች ፦
° የሥራ ስንብት፣
° የመሬት አገልግሎት፣
° የጡረታ መብት
° የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን የተመለከቱ መሆናቸውን አመልክቷል።
ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የሪፖርተር ጋዜጣ ነው።
@tikvahethiopia
ፎቶ ፦ በድሬደዋ እና ሱማሌ ክልል ሲቲ ዞን መካከል አሁን በተከሰተ የሰደድ እሳት ምክንያት ለግዜው የባቡር እንቅስቃሴ መቆሙን ኢንጂነር ታከለ ኡማ አሳውቀዋል።
" እሳቱን ለመቆጣጠር እና አገልግሎቱን ለማስጀመር የድሬደዋ የእሳት አደጋ እና የሽንሌ ዞን ሀላፊዎች ከጣቢያው ሰራተኞች ጋር በመሆን ባደረጉት ርብርብ እሳቱን ማጥፋት ተችሏል " ሲሉ ገልጸዋል።
@tikvahethiopia
" እሳቱን ለመቆጣጠር እና አገልግሎቱን ለማስጀመር የድሬደዋ የእሳት አደጋ እና የሽንሌ ዞን ሀላፊዎች ከጣቢያው ሰራተኞች ጋር በመሆን ባደረጉት ርብርብ እሳቱን ማጥፋት ተችሏል " ሲሉ ገልጸዋል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update
ከ1997 የጋራ መኖሪያ ቤት ተመዝጋቢዎች ጉዳይ ጋር በተያያዘ የአዲስ አበባ ቤቶች ልማት እና አስተዳደር ቢሮ ከደቂቃዎች በፊት ማብራሪያ ሰጥቷል።
ቢሮው እየተሰራጨ ያለው መረጃ ከአውድ ውጪ በተተረጎመ መንገድ እንደሆነ ጠቁሟል።
" የ1997 የጋራ መኖርያ ቤት ተመዝጋቢዎችን በተመለከተ ሰሞኑን በተለያዩ ሚዲያዎች እየተሰራጨ ያለው የተሳሳተ መረጃ ትክክል ባልሆነ መልኩ ከአውድ ውጪ ተተርጉሞ የቀረበ ነው " ብሏል።
ቢሮው በሰጠው ማብራሪያ ምን አለ ?
" ከተማ አስተዳደሩ የጋራ መኖሪያ እና ንግድ ቤቶች ለማስተላለፍ ባወጣው መመሪያ ቁጥር 3/2011 መሰረት ክፍል 3 አንቀፅ 13 ንኡስ አንቀፅ 1 እና 2 መሰረት ብቁ እና ንቁ ማለትም ' የቤት ፈላጊዎች በገቡት ግዴታ መሰረት የቁጠባ መጠን በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በትክክል ተቀማጭ ማድረጋቸውን ከእጣ በፊት ያረጋግጣል ' ይላል።
ስለሆነም የ1997 ተመዝጋቢዎች በወቅቱ በመረጃ ቋት ውስጥ ንቁ እና ብቁ የነበሩ ተመዝጋቢዎችን ከተማ አስተዳደሩ ሙሉ በሙሉ አስተናግዶ ያጠናቀቀ ሲሆን ነገር ግን በወቅቱ ብቁ ያልነበሩትን የ1997 ተመዝጋቢዎች እና ሌሎች የ2005 እጣ ያልደረሳቸው የቤት ፈላጊዎች እየተተገበሩ ባሉ የተለያዩ የቤት ልማት አማራጮች እያስተናገደ ይገኛል፡፡
ስለሆነም በወቅቱ ብቁ እና ንቁ ያልነበሩ የ1997 ተመዝጋቢዎች ከየትኛውም የቤት ልማት መርሃ ግብር ውጪ እንደተደረጉ ተደርጎ የተሰራጨው የሀሰት መረጃ ተገቢ እንዳልሆነ ህብረተሰቡ እንዲገነዘብ እና ይህንን ሀሰተኛ መረጃ የሚያሰራጩትን ከተማ አስተዳደሩ በህግ የሚጠይቅ ይሆናል።
ከተማ አስተዳደሩ ተመዝግበው የሚጠባበቁትን ሆነ ሌሎች የከተማችዋን የቤት ፈላጊዎች ቤት ተደራሽ ለማድረግ የተለያዩ አዳዲስ የቤት ልማት አማራጮችን በመቀየስ እየተገበረ ይገኛል " ብሏል።
NB. ቢሮው ስለ 1997 ተመዝጋቢዎች የትኛው ሚዲያ ከአውድ ውጭ የተተረጎመ ሀሰተኛ መረጃ እንዳሰራጨ በግልጽ ያለው ነገር የለም። ነገር ግን መረጃውን የሚያሰራጩትን በህግ እጠይቃለሁ የሚል ማስጠንቀቂያ አስተላልፏል።
#AddisAbabaHousingDevelopmentandAdministrationBureau
@tikvahethiopia
ከ1997 የጋራ መኖሪያ ቤት ተመዝጋቢዎች ጉዳይ ጋር በተያያዘ የአዲስ አበባ ቤቶች ልማት እና አስተዳደር ቢሮ ከደቂቃዎች በፊት ማብራሪያ ሰጥቷል።
ቢሮው እየተሰራጨ ያለው መረጃ ከአውድ ውጪ በተተረጎመ መንገድ እንደሆነ ጠቁሟል።
" የ1997 የጋራ መኖርያ ቤት ተመዝጋቢዎችን በተመለከተ ሰሞኑን በተለያዩ ሚዲያዎች እየተሰራጨ ያለው የተሳሳተ መረጃ ትክክል ባልሆነ መልኩ ከአውድ ውጪ ተተርጉሞ የቀረበ ነው " ብሏል።
ቢሮው በሰጠው ማብራሪያ ምን አለ ?
" ከተማ አስተዳደሩ የጋራ መኖሪያ እና ንግድ ቤቶች ለማስተላለፍ ባወጣው መመሪያ ቁጥር 3/2011 መሰረት ክፍል 3 አንቀፅ 13 ንኡስ አንቀፅ 1 እና 2 መሰረት ብቁ እና ንቁ ማለትም ' የቤት ፈላጊዎች በገቡት ግዴታ መሰረት የቁጠባ መጠን በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በትክክል ተቀማጭ ማድረጋቸውን ከእጣ በፊት ያረጋግጣል ' ይላል።
ስለሆነም የ1997 ተመዝጋቢዎች በወቅቱ በመረጃ ቋት ውስጥ ንቁ እና ብቁ የነበሩ ተመዝጋቢዎችን ከተማ አስተዳደሩ ሙሉ በሙሉ አስተናግዶ ያጠናቀቀ ሲሆን ነገር ግን በወቅቱ ብቁ ያልነበሩትን የ1997 ተመዝጋቢዎች እና ሌሎች የ2005 እጣ ያልደረሳቸው የቤት ፈላጊዎች እየተተገበሩ ባሉ የተለያዩ የቤት ልማት አማራጮች እያስተናገደ ይገኛል፡፡
ስለሆነም በወቅቱ ብቁ እና ንቁ ያልነበሩ የ1997 ተመዝጋቢዎች ከየትኛውም የቤት ልማት መርሃ ግብር ውጪ እንደተደረጉ ተደርጎ የተሰራጨው የሀሰት መረጃ ተገቢ እንዳልሆነ ህብረተሰቡ እንዲገነዘብ እና ይህንን ሀሰተኛ መረጃ የሚያሰራጩትን ከተማ አስተዳደሩ በህግ የሚጠይቅ ይሆናል።
ከተማ አስተዳደሩ ተመዝግበው የሚጠባበቁትን ሆነ ሌሎች የከተማችዋን የቤት ፈላጊዎች ቤት ተደራሽ ለማድረግ የተለያዩ አዳዲስ የቤት ልማት አማራጮችን በመቀየስ እየተገበረ ይገኛል " ብሏል።
NB. ቢሮው ስለ 1997 ተመዝጋቢዎች የትኛው ሚዲያ ከአውድ ውጭ የተተረጎመ ሀሰተኛ መረጃ እንዳሰራጨ በግልጽ ያለው ነገር የለም። ነገር ግን መረጃውን የሚያሰራጩትን በህግ እጠይቃለሁ የሚል ማስጠንቀቂያ አስተላልፏል።
#AddisAbabaHousingDevelopmentandAdministrationBureau
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#EthiopianInstitutionoftheOmbudsman
የኢትዮጵያ ሕዝብ ዕንባ ጠባቂ ተቋም ስለ 1997 ተመዝጋቢዎች ምን አለ ?
" ለ20 ዓመታት ያህል ' ቤት ይደርሰናል ' ብለው እየጠበቁ ቢሆንም መንግሥት ምላሽ አልሰጠንም ያሉ ቢያንስ 67 ሰዎችን አቤቱታ ተቀለን እየመረመርን ነው።
' በ1997 ተመዝግበን ቤት ሳይደርሰን ለሌሎች ተሰጥቷል ' ፤ በሚል ተደራጅተው ጠይቀዋል፣ እኛም ጥያቄ አቅርበናል፡፡ ነገር ግን የከተማ አስተዳደሩ እስካሁን መልስ አልሰጠንም።
መልስ የማይሰጠን ከሆነ ለረዥም ጊዜ ጠብቀው ምላሽ ያልተሰጣቸውን ሰዎች አቤቱታ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በማቅረብ የመጨረሻ ዕልባት እንዲያገኝ እናደርጋለን። "
ይህ ቃል ከሪፖርተር ጋዜጣ የተወሰደ ነው።
@tikvahethiopia
የኢትዮጵያ ሕዝብ ዕንባ ጠባቂ ተቋም ስለ 1997 ተመዝጋቢዎች ምን አለ ?
" ለ20 ዓመታት ያህል ' ቤት ይደርሰናል ' ብለው እየጠበቁ ቢሆንም መንግሥት ምላሽ አልሰጠንም ያሉ ቢያንስ 67 ሰዎችን አቤቱታ ተቀለን እየመረመርን ነው።
' በ1997 ተመዝግበን ቤት ሳይደርሰን ለሌሎች ተሰጥቷል ' ፤ በሚል ተደራጅተው ጠይቀዋል፣ እኛም ጥያቄ አቅርበናል፡፡ ነገር ግን የከተማ አስተዳደሩ እስካሁን መልስ አልሰጠንም።
መልስ የማይሰጠን ከሆነ ለረዥም ጊዜ ጠብቀው ምላሽ ያልተሰጣቸውን ሰዎች አቤቱታ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በማቅረብ የመጨረሻ ዕልባት እንዲያገኝ እናደርጋለን። "
ይህ ቃል ከሪፖርተር ጋዜጣ የተወሰደ ነው።
@tikvahethiopia
#ዶክተርነቢያትተስፋዬ 👏 #ኢትዮጵያ
ከስፓይና ቢፊዳ የጤና እከል ጋር የተወለዱት ግለሰብ በማሌንዢያ የስፓይና ቢፊዳ ዓለም አቀፍ ኮንግረንስ የሕይወት ዘመን ተሸላሚ ሆኑ።
ከ30 ዓመታት በፊት ከህመሙ ጋር የተወለዱት ዶ/ር ነቢያት ተስፋዬ ፣ በማሊዥያ የስፓይና ቢፊዳ ዓለም አቀፍ ኮንግረስ የሕይወት ዘመን ተሸላሚ መሆናቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።
የሕይወት ዘመን ተሸላሚ የሆኑት፣ ያሳለፉትን የሕይወት ውጣ ውረድ ሌሎች ልጆች እንዳያልፉ በሕይወት ልምዳቸውና በሙያቸው ኢትዮጵያውያንን ለማገልገል በሚያደርጉት ጥረት ነው።
ለኢትዮጵያውያን የሚሰጡትን አግልግሎት አድማስ ለማስፋት “ አለያንስ ፎር በርዝ ዲፌክት ” የተሰኘ በስማቸው ሀገር በቀል ግብረሰናይ ድርጅት በመመስረት አገልግሎት መስጠት እንደጀመሩም ተናግረዋል።
ድርጅታቸው ከሀገር ውስጥና ውጭ ካሉ ድርጅቶች ጋር በመተባበር በስፓይና ቢፊዳ እና ተያያዥ የጤና ችግር ውስጥ ለሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች የተሟላ ድጋፍ ለማድረግ ሽልማታቸውን ከተቀበሉ በኋላ ቃል ገብተዋል።
በዓለም አቀፍ ደረጃ ወደ ግማሽ ሚሊዮን የሚጠጉ ሕፃናት በዓመት ከስፓይና ቢፊዳና ተያያዥ የጤና እክሎች ጋር አብረው የሚወለዱ ሲሆን፣ በኢትዮጵያም በርካታ ሕፃናት ከዚህ ችግር ጋር አብረው ከሚወለድባቸው ሀገሮች ግንባር ቀደም መሆኗን አስረድተዋል።
በመሆኑም ከጤና ሚንስቴር ፣ ከሆስፒታሎችና ከሌሎች አጋሮች ጋር በመተባበር በዚህ ችግር የተጠቁ የህብረተሰብ ክፍሎች የክትትልና የማገገም አገልግሎት እንዲያገኙ በትጋት እየሰሩ መሆናቸው ተገልጿል።
የተሸላሚው የሕይወት ጉዞ ምን ይመስላል ?
ከ30 ዓመታት በፊት ከዚህ የጤና ችግር ጋር ተወልደዋል። ከዚህ ችግር ጋር አብረው በመወለዳቸው በሕይወታቸው ውስጥ ብዙ ውጣውረዶች አሳልፈዋል።
የተለያዩ ቀዶ ጥገና ሕክምናዎችንም አድርገዋል።
በልጅነት ጊዜያቸው በዚሁ በሽታ ሳቢያ ትምህርታቸውን ቤት ተቀምጠው እስከመከታተል ተገደዋል። በተለያዩ የጤና ችግሮች ውስጥም አልፈዋል።
እነዚህን ሁሉ ችግሮች በትጋትና በጥንካሬ ከቤተሰቦቼ ጋር በመሆን አልፈው የህክምና ትምህርት መማር ችለዋል።
ለአምስት አመታት የህክምና ትምህርታቸውን ተከታትለው ከጨረኩበት ማግስት ጀምረው እንደሳቸው ሁሉ ከዚህ የጤና ችግር ጋር ለሚወለዱ ሕፃናት የተለያዩ ድጋፎችና የህክምና አገልግሎቶች እንዲያገኙ በማድረግ በሺዎች ለሚቆጠሩ ቤተሰቦች ተስፋ ለመሆን በቅተዋል።
ልጆች ከዚህ ከባድ የጤና ችግር ጋር አብረው እንዳይወለዱና መከላከል እንዲቻል ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር ፎሊክ አሲድ በምግብ እንዲበለፅግ የማስተማርና የማስተዋውቅ ሥራ እየሰሩ ይገኛሉ።
ለሁለት አመታት Reachanother foundation በሚባል ግብረሰናይ ድርጅት ውስጥ የአገልግሎት ዳይሬክተር በመሆን በአገራችን በተለያዩ ክልሎች በሚገኙ 8 ሆስፒታሎች ሕፃናት ጥራት ያለው የቀዶ ሕክምና አገልግሎት እንዲያገኙ ባለሙያዎች ማስልጠን እና ግብቶችን የሟሟላት ሥራ በመስራት ላይም ይገኛሉ።
ስለ ስፓይና ቢፊዳ ይወቁ ፦ https://t.iss.one/tikvahethiopia/74429?single
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
ከስፓይና ቢፊዳ የጤና እከል ጋር የተወለዱት ግለሰብ በማሌንዢያ የስፓይና ቢፊዳ ዓለም አቀፍ ኮንግረንስ የሕይወት ዘመን ተሸላሚ ሆኑ።
ከ30 ዓመታት በፊት ከህመሙ ጋር የተወለዱት ዶ/ር ነቢያት ተስፋዬ ፣ በማሊዥያ የስፓይና ቢፊዳ ዓለም አቀፍ ኮንግረስ የሕይወት ዘመን ተሸላሚ መሆናቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።
የሕይወት ዘመን ተሸላሚ የሆኑት፣ ያሳለፉትን የሕይወት ውጣ ውረድ ሌሎች ልጆች እንዳያልፉ በሕይወት ልምዳቸውና በሙያቸው ኢትዮጵያውያንን ለማገልገል በሚያደርጉት ጥረት ነው።
ለኢትዮጵያውያን የሚሰጡትን አግልግሎት አድማስ ለማስፋት “ አለያንስ ፎር በርዝ ዲፌክት ” የተሰኘ በስማቸው ሀገር በቀል ግብረሰናይ ድርጅት በመመስረት አገልግሎት መስጠት እንደጀመሩም ተናግረዋል።
ድርጅታቸው ከሀገር ውስጥና ውጭ ካሉ ድርጅቶች ጋር በመተባበር በስፓይና ቢፊዳ እና ተያያዥ የጤና ችግር ውስጥ ለሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች የተሟላ ድጋፍ ለማድረግ ሽልማታቸውን ከተቀበሉ በኋላ ቃል ገብተዋል።
በዓለም አቀፍ ደረጃ ወደ ግማሽ ሚሊዮን የሚጠጉ ሕፃናት በዓመት ከስፓይና ቢፊዳና ተያያዥ የጤና እክሎች ጋር አብረው የሚወለዱ ሲሆን፣ በኢትዮጵያም በርካታ ሕፃናት ከዚህ ችግር ጋር አብረው ከሚወለድባቸው ሀገሮች ግንባር ቀደም መሆኗን አስረድተዋል።
በመሆኑም ከጤና ሚንስቴር ፣ ከሆስፒታሎችና ከሌሎች አጋሮች ጋር በመተባበር በዚህ ችግር የተጠቁ የህብረተሰብ ክፍሎች የክትትልና የማገገም አገልግሎት እንዲያገኙ በትጋት እየሰሩ መሆናቸው ተገልጿል።
የተሸላሚው የሕይወት ጉዞ ምን ይመስላል ?
ከ30 ዓመታት በፊት ከዚህ የጤና ችግር ጋር ተወልደዋል። ከዚህ ችግር ጋር አብረው በመወለዳቸው በሕይወታቸው ውስጥ ብዙ ውጣውረዶች አሳልፈዋል።
የተለያዩ ቀዶ ጥገና ሕክምናዎችንም አድርገዋል።
በልጅነት ጊዜያቸው በዚሁ በሽታ ሳቢያ ትምህርታቸውን ቤት ተቀምጠው እስከመከታተል ተገደዋል። በተለያዩ የጤና ችግሮች ውስጥም አልፈዋል።
እነዚህን ሁሉ ችግሮች በትጋትና በጥንካሬ ከቤተሰቦቼ ጋር በመሆን አልፈው የህክምና ትምህርት መማር ችለዋል።
ለአምስት አመታት የህክምና ትምህርታቸውን ተከታትለው ከጨረኩበት ማግስት ጀምረው እንደሳቸው ሁሉ ከዚህ የጤና ችግር ጋር ለሚወለዱ ሕፃናት የተለያዩ ድጋፎችና የህክምና አገልግሎቶች እንዲያገኙ በማድረግ በሺዎች ለሚቆጠሩ ቤተሰቦች ተስፋ ለመሆን በቅተዋል።
ልጆች ከዚህ ከባድ የጤና ችግር ጋር አብረው እንዳይወለዱና መከላከል እንዲቻል ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር ፎሊክ አሲድ በምግብ እንዲበለፅግ የማስተማርና የማስተዋውቅ ሥራ እየሰሩ ይገኛሉ።
ለሁለት አመታት Reachanother foundation በሚባል ግብረሰናይ ድርጅት ውስጥ የአገልግሎት ዳይሬክተር በመሆን በአገራችን በተለያዩ ክልሎች በሚገኙ 8 ሆስፒታሎች ሕፃናት ጥራት ያለው የቀዶ ሕክምና አገልግሎት እንዲያገኙ ባለሙያዎች ማስልጠን እና ግብቶችን የሟሟላት ሥራ በመስራት ላይም ይገኛሉ።
ስለ ስፓይና ቢፊዳ ይወቁ ፦ https://t.iss.one/tikvahethiopia/74429?single
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM