#Tigray
" በፓለቲካ አመራሮች መካከል የተፈጠረው ልዩነት ወደ ፀጥታ ሃይሉ እንዲጋባ የሚያደርግ ቅስቀሳና ነጭ ውሸት አልታገስም " - የትግራይ ክልል የፀጥታ እና የሰላም ቢሮ
የትግራይ ክልል ፀጥታ እና ሰላም ቢሮ ባወጣው መግለጫ ፤ " የህዝብ እና የሰራዊት አንድነት በማላላት የአርስ በርስ ግጭት እንዲከሰት የሚሰሩት ግለሰቦች እና አካላት አንታገስም " ብሏል።
እንዲህ ያለው ተግባር ላይ ስለተሰማሩት ግለሰቦችና አካላት በግልጽ ስም ጠቅሶ ያለው ነገር የለም።
ቢሮው ፥ " በአገር ውስጥ እና በውጭ በመሆን በተለያዩ የማህበራዊ የትስስር ገፆች በመጠቀም በሬ ወለደ ውሸት በመንዛት በክልሉ የፀጥታ ሃይልና ህዝብ መካከል ያለው አንድነት እንዲላላ እየተሰራ እያየን በትእግስት ለማለፍ መርጠናል " ብሏል።
" ከአሁን በኋላ ህግ እንዲከበር በጥብቅ ይሰራል " ሲል አስታውቀዋል ።
" በፀጥታ ሃይሉ ጉድለት አለ የሚል አካል ተጨባጭ አሳማኝ መረጃ በማቅረብ ህጋዊ በሆነ መልኩ ጥያቄ ማቅረብ ይቻላል " ያለው ቢሮው " ይሁን እንጂ ፓለቲካ አስታኮ የሚነዛ የማህበራዊ ሚዲያ ገፅ ውሸት በግለሰብም ሆነ በየትኛውም አካል አያሰጠይቅም ማለት እንዳልሆነ ሊታወቅ ይገባል " ሲል አስጠንቅቀዋል።
" በፓለቲካ አመራሮች መካከል የተፈጠረውም ልዩነት ወደ ፀጥታ ሃይሉ እንዲጋባ የሚያደርግ ቅስቀሳና ነጭ ውሸት አልታገስም " ሲልም ገልጿል።
ቢሮው ፤ " የፀጥታ ሃይል የማንም የፓለቲካ ቡድን መሳሪያ አይደለም " ሲልም አክሏል።
የፀጥታ ኃይሉ በክልሉ ባለው የፓለቲካ መከፋፈል መካከል ገብቶ የአንዱ ደጋፊ የሌላው ተቃዋሚ እንዲሆን ታልሞ የማህበራዊ ሚዲያ እንቅስቃሴ መሆኑን የገለጸው ቢሮው " ይህ አይሳካም ፍፁም ተቀባይነት የለውም፤ ይህንን ተላልፎ የሚገኝ ግለስብና አካል በህግ እንዲጠየቅ በማድረግ የህግ ልእልና እንዲከበርና የህዝቡ ሰላምና ፀጥታ እንዲከበር እንሰራለን " ብሏል።
#TikvahEthiopiaMekelleFamily
@tikvahethiopia
" በፓለቲካ አመራሮች መካከል የተፈጠረው ልዩነት ወደ ፀጥታ ሃይሉ እንዲጋባ የሚያደርግ ቅስቀሳና ነጭ ውሸት አልታገስም " - የትግራይ ክልል የፀጥታ እና የሰላም ቢሮ
የትግራይ ክልል ፀጥታ እና ሰላም ቢሮ ባወጣው መግለጫ ፤ " የህዝብ እና የሰራዊት አንድነት በማላላት የአርስ በርስ ግጭት እንዲከሰት የሚሰሩት ግለሰቦች እና አካላት አንታገስም " ብሏል።
እንዲህ ያለው ተግባር ላይ ስለተሰማሩት ግለሰቦችና አካላት በግልጽ ስም ጠቅሶ ያለው ነገር የለም።
ቢሮው ፥ " በአገር ውስጥ እና በውጭ በመሆን በተለያዩ የማህበራዊ የትስስር ገፆች በመጠቀም በሬ ወለደ ውሸት በመንዛት በክልሉ የፀጥታ ሃይልና ህዝብ መካከል ያለው አንድነት እንዲላላ እየተሰራ እያየን በትእግስት ለማለፍ መርጠናል " ብሏል።
" ከአሁን በኋላ ህግ እንዲከበር በጥብቅ ይሰራል " ሲል አስታውቀዋል ።
" በፀጥታ ሃይሉ ጉድለት አለ የሚል አካል ተጨባጭ አሳማኝ መረጃ በማቅረብ ህጋዊ በሆነ መልኩ ጥያቄ ማቅረብ ይቻላል " ያለው ቢሮው " ይሁን እንጂ ፓለቲካ አስታኮ የሚነዛ የማህበራዊ ሚዲያ ገፅ ውሸት በግለሰብም ሆነ በየትኛውም አካል አያሰጠይቅም ማለት እንዳልሆነ ሊታወቅ ይገባል " ሲል አስጠንቅቀዋል።
" በፓለቲካ አመራሮች መካከል የተፈጠረውም ልዩነት ወደ ፀጥታ ሃይሉ እንዲጋባ የሚያደርግ ቅስቀሳና ነጭ ውሸት አልታገስም " ሲልም ገልጿል።
ቢሮው ፤ " የፀጥታ ሃይል የማንም የፓለቲካ ቡድን መሳሪያ አይደለም " ሲልም አክሏል።
የፀጥታ ኃይሉ በክልሉ ባለው የፓለቲካ መከፋፈል መካከል ገብቶ የአንዱ ደጋፊ የሌላው ተቃዋሚ እንዲሆን ታልሞ የማህበራዊ ሚዲያ እንቅስቃሴ መሆኑን የገለጸው ቢሮው " ይህ አይሳካም ፍፁም ተቀባይነት የለውም፤ ይህንን ተላልፎ የሚገኝ ግለስብና አካል በህግ እንዲጠየቅ በማድረግ የህግ ልእልና እንዲከበርና የህዝቡ ሰላምና ፀጥታ እንዲከበር እንሰራለን " ብሏል።
#TikvahEthiopiaMekelleFamily
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ካዛን ፦ ከ16ኛው የ #BRICS+ የመሪዎች ጉባኤ ጎን ለጎን የሀገራት መሪዎች የተናጠል ውይይት እያደረጉ ይገኛሉ። የኢትዮጵያ ጠ/ሚ ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) እና የሩስያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን የሁለትዮሽ ውይይት አድርገዋል። በተጨማሪም ጠ/ሚ ዐቢይ (ዶ/ር) ፦ ° ከተባበሩት አረብ ኤሜሬትስ (UAE) ፕሬዜዳንት ሼክ መሃመድ ቢን ዛይድ አል ናህንያን ፣ ° ከደቡብ አፍሪካ ፕሬዜዳንት ሲሪል ራማፎሳ…
#BRICS+
በሩስያ፣ ካዛን ሲካሄድ የቆየው የBRICS+ አባል ሀገራት መሪዎች ጉባኤ ዛሬ ተጠናቋል።
ስብስቡ 13 ሀገራትን በአጋር (ፓርትነር) አድርጎ ተቀብሏል።
ሀገራቱን የBRICS አጋር (ፓርትነር) አድርጎ የተቀበለው በ2024 ምንም አይነት አዲስ ሙሉ አባል ሀገር ላለመቀበል በመወሰኑ ነው።
13ቱ ሀገራት ወደፊት የስብሰቡ ሙሉ አባል ሀገር ለመሆን እንደሚሰሩ ነው የተነገረው።
የBRICS+ ሙሉ አባል ሀገራት እነማን ናቸው ?
🇧🇷 ብራዚል
🇷🇺 ሩስያ
🇮🇳 ሕንድ
🇨🇳 ቻይና
🇿🇦 ደቡብ አፍሪካ
🇪🇹 ኢትዮጵያ
🇦🇪 የተባበሩት አረብ ኤሜሬትስ
🇮🇷 ኢራን
🇪🇬 ግብፅ ናቸው።
አሁን BRICS+ን በአጋርነት (ፓርትነር) ሆነው የተቀላቀሉት እነማን ናቸው ?
🇩🇿 አልጄሪያ
🇧🇾 ቤላሩስ
🇧🇴 ቦሊቪያ
🇨🇺 ኩባ
🇮🇩 ኢንዶኔዥያ
🇰🇿 ካዛኪስታን
🇲🇾 ማሌዢያ
🇳🇬 ናይጄሪያ
🇹🇭 ታይላንድ
🇹🇷 ቱርክ
🇺🇬 ዩጋንዳ
🇺🇿 ኡዝቤኪስታን
🇻🇳 ቬዬትናም ናቸው።
በካዛኑ የBRICS+ የመሪዎች ጉባኤ የቱርክ ፕሬዝዳንት ሬሲፕ ጣይብ ኤርዶጋን ፣ የቬንዝዌላው ፕሬዜዳንት ኒኮላስ ማዱሮ ተገኝተው ነበር።
የሳዑዲ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትርም ካዛን ተገኝተው ነበር። ሳዑዲ ምንም እንኳን በይፋ የBRICS ስብስብን ባትቀላቀልም በተጋባዥ ሀገርነት ትሳተፋለች።
የሌሎች ሀገራት መሪዎችና ተወካዮችም በካዛን ተገኝተው ነበር።
#BRICSSummit #Russia
@tikvahethiopia
በሩስያ፣ ካዛን ሲካሄድ የቆየው የBRICS+ አባል ሀገራት መሪዎች ጉባኤ ዛሬ ተጠናቋል።
ስብስቡ 13 ሀገራትን በአጋር (ፓርትነር) አድርጎ ተቀብሏል።
ሀገራቱን የBRICS አጋር (ፓርትነር) አድርጎ የተቀበለው በ2024 ምንም አይነት አዲስ ሙሉ አባል ሀገር ላለመቀበል በመወሰኑ ነው።
13ቱ ሀገራት ወደፊት የስብሰቡ ሙሉ አባል ሀገር ለመሆን እንደሚሰሩ ነው የተነገረው።
የBRICS+ ሙሉ አባል ሀገራት እነማን ናቸው ?
🇧🇷 ብራዚል
🇷🇺 ሩስያ
🇮🇳 ሕንድ
🇨🇳 ቻይና
🇿🇦 ደቡብ አፍሪካ
🇪🇹 ኢትዮጵያ
🇦🇪 የተባበሩት አረብ ኤሜሬትስ
🇮🇷 ኢራን
🇪🇬 ግብፅ ናቸው።
አሁን BRICS+ን በአጋርነት (ፓርትነር) ሆነው የተቀላቀሉት እነማን ናቸው ?
🇩🇿 አልጄሪያ
🇧🇾 ቤላሩስ
🇧🇴 ቦሊቪያ
🇨🇺 ኩባ
🇮🇩 ኢንዶኔዥያ
🇰🇿 ካዛኪስታን
🇲🇾 ማሌዢያ
🇳🇬 ናይጄሪያ
🇹🇭 ታይላንድ
🇹🇷 ቱርክ
🇺🇬 ዩጋንዳ
🇺🇿 ኡዝቤኪስታን
🇻🇳 ቬዬትናም ናቸው።
በካዛኑ የBRICS+ የመሪዎች ጉባኤ የቱርክ ፕሬዝዳንት ሬሲፕ ጣይብ ኤርዶጋን ፣ የቬንዝዌላው ፕሬዜዳንት ኒኮላስ ማዱሮ ተገኝተው ነበር።
የሳዑዲ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትርም ካዛን ተገኝተው ነበር። ሳዑዲ ምንም እንኳን በይፋ የBRICS ስብስብን ባትቀላቀልም በተጋባዥ ሀገርነት ትሳተፋለች።
የሌሎች ሀገራት መሪዎችና ተወካዮችም በካዛን ተገኝተው ነበር።
#BRICSSummit #Russia
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
“ አንድ እንጀራ 30 ብር በገባበት ወቅት 450 ብር ለምን ይጠቅማል ? ለቤት ኪራይ፣ ወይስ ለቀለብ ነው የሚሆነው? ” - የኢትዮጵያ መምህራን ማኀበር። የመምህራን የስልጠና ክፍያ እጅግ አነስተኛ መሆን ከኑሮ ውደነት ጋር ተያይዞ ፣ ዩኒቨርሲቲዎች ሲሰጡት የነበረውን የሙያ ስልጠና አለመስጠታቸው የትምህርት ጥራት ቀውስ ውስጥ እንዲገባ እያደረገ በመሆኑ ትኩረት እንዲሰጠው የኢትዮጵያ መምህራን ማኀበር በቲክቫህ…
“ የመምህራን ደመወዝ በዘመቻ በሚባል መልኩ ይቆረጣል ” - ማኀበሩ
“ በተለይ ደቡብ ኢትዮጵያ፣ ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ፣ ጋምቤላ፣ ቤንሻንጉል ክልሎች የመምህራን ደመወዝ በዘመቻ በሚባል መልኩ ይቆረጣል ” ሲል የኢትዮጵያ መምህራን ማኀበር ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።
ማኅበሩ 37ኛ መደበኛ የምክር ቤት ስብሰባ በአዳማ ከተማ ከጥቅምት 7 እስከ ጥቅምት 9 ቀን 2017 ዓ/ም አካሂዶ የነበረ ሲሆን፣ የመምህራን ቅሬታዎች ትምህርት ሚኒስቴር በተገኘት መቅረባቸውን ገልጿል።
መምህራን እየገጠሟቸው ያሉ በርካታ ችግሮች መኖራቸውን የገለጹት የማኀበሩ ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ ሽመልስ አበበ ችግሩ በወቅቱ እንዲፈታ አሳስበዋል።
ማኀበሩ በዝርዝር ምን አለ ?
“ ክልሎችና ዩኒቨርሲቲዎች በተገኙበት የተለያዩ አጀንዳዎች ተነስተዋል። የተነሱት አጀንዳዎችም እንደ ክልል የመልካም አስተዳደር ችግሮች አሉ የሚሉ ናቸው።
በየክልሎች የተለያዩ የመልካም አስተዳደር ችግሮች አሉ፡፡ ከመልካም አስተዳደር ችግር ደግሞ የጸዱ አካባቢዎች አሉ፡፡ በተለይ አዲስ አበባ፣ ድሬዳዋ፣ ሀረር አካባቢ የከፋ የመልካም አስተዳደር ችግር የለም።
ጦርነቱ በአማራ ክልል መምህራን ተረጋግተው እንዲሰሩ፣ ተማሪዎቹም ተረጋግተው እንዲማሩ እያደረገ አይደለም፡፡ ወደ 3,000 የሚሆኑ ት/ቤቶች ከሥራ ውጪ ናቸው፡፡
በዛው ልክ ደግሞ በእነዚህ ት/ቤቶች ሲማሩ የነበሩ ተማሪዎችና መምህራን ከሥራ ውጪ እንደሆኑ ተገጿል።
እንደ ኦሮሚያ ክልልም ብዙ ቃል የተገቡ ነገሮች ነበሩ ነገር ግን አልተተገበሩም (በተለይም ከመኖሪያ ቤት አንጻር)፤ ይሄ መስተካከል አለበት፡፡ የተሻለ ነበረ ኦሮሚያ አፈጻጸሙ ግን በዚህ ዓመት ብዙ ርቀት አልሄደም።
ከእነዚህ ክልሎች ውጪ ያሉት ደግሞ በተለይ ደቡብ ኢትዮጵያ፣ ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ፣ ጋምቤላ፣ ቤንሻንጉል ክልሎች የመምህራን ደመወዝ በዘመቻ በሚባል መልኩ ይቆረጣል።
ይሄ በጣም የከፋ የመልካም አስተዳደር ችግር ሆኖ ነው የተነሳው።
በአፋር ክልልም ለረዥም ጊዜ የደረጃ እድገት፣ የትምህርት ማሻሻያ ያልተከፈለበት ሁኔታ አለ።
በትግራይ ክልል የ17 ወራት የመምህራን ደመወዝ አልተከፈለም። የአምስት ወሩን ክልሉ እከፍላለሁ ብሎ ነበር እስካሁን አልከፈለም።
የክልሉ መምህራን ማኀበር ጠበቃ ቀጥሮ ክስ መስርቷል። በሕግ ሂደት ላይ ነው ” የሚሉ ቅሬታዎች ተነስተው መፍትሄ እንዲሰጥ መጠየቁን ገልጿል።
ከትምህርት ሚኒስቴር ባለድርሻ አካላት ባሉበት ለተነሳው ቅሬታ ታዲያ ምን የመፍትሄ አቅጣጫ ተቀመጠ ? ለሚለው የቲክቫህ ኢትዮጵያ ጥያቄ ፣ የትምህርት ሚኒስቴር ጉዳዩን እንዳዳመጠ፣ በቀጣይ ለመፍትሄ እንደሚሰራ መጠቆሙን ማኅበሩ አስረድቷል።
ማኀበሩ በመጨረሻም የተነሱት ቅሬታዎች ምላሽ እንዲያገኙ በአንክሮ ጠይቋል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
“ በተለይ ደቡብ ኢትዮጵያ፣ ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ፣ ጋምቤላ፣ ቤንሻንጉል ክልሎች የመምህራን ደመወዝ በዘመቻ በሚባል መልኩ ይቆረጣል ” ሲል የኢትዮጵያ መምህራን ማኀበር ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።
ማኅበሩ 37ኛ መደበኛ የምክር ቤት ስብሰባ በአዳማ ከተማ ከጥቅምት 7 እስከ ጥቅምት 9 ቀን 2017 ዓ/ም አካሂዶ የነበረ ሲሆን፣ የመምህራን ቅሬታዎች ትምህርት ሚኒስቴር በተገኘት መቅረባቸውን ገልጿል።
መምህራን እየገጠሟቸው ያሉ በርካታ ችግሮች መኖራቸውን የገለጹት የማኀበሩ ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ ሽመልስ አበበ ችግሩ በወቅቱ እንዲፈታ አሳስበዋል።
ማኀበሩ በዝርዝር ምን አለ ?
“ ክልሎችና ዩኒቨርሲቲዎች በተገኙበት የተለያዩ አጀንዳዎች ተነስተዋል። የተነሱት አጀንዳዎችም እንደ ክልል የመልካም አስተዳደር ችግሮች አሉ የሚሉ ናቸው።
በየክልሎች የተለያዩ የመልካም አስተዳደር ችግሮች አሉ፡፡ ከመልካም አስተዳደር ችግር ደግሞ የጸዱ አካባቢዎች አሉ፡፡ በተለይ አዲስ አበባ፣ ድሬዳዋ፣ ሀረር አካባቢ የከፋ የመልካም አስተዳደር ችግር የለም።
ጦርነቱ በአማራ ክልል መምህራን ተረጋግተው እንዲሰሩ፣ ተማሪዎቹም ተረጋግተው እንዲማሩ እያደረገ አይደለም፡፡ ወደ 3,000 የሚሆኑ ት/ቤቶች ከሥራ ውጪ ናቸው፡፡
በዛው ልክ ደግሞ በእነዚህ ት/ቤቶች ሲማሩ የነበሩ ተማሪዎችና መምህራን ከሥራ ውጪ እንደሆኑ ተገጿል።
እንደ ኦሮሚያ ክልልም ብዙ ቃል የተገቡ ነገሮች ነበሩ ነገር ግን አልተተገበሩም (በተለይም ከመኖሪያ ቤት አንጻር)፤ ይሄ መስተካከል አለበት፡፡ የተሻለ ነበረ ኦሮሚያ አፈጻጸሙ ግን በዚህ ዓመት ብዙ ርቀት አልሄደም።
ከእነዚህ ክልሎች ውጪ ያሉት ደግሞ በተለይ ደቡብ ኢትዮጵያ፣ ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ፣ ጋምቤላ፣ ቤንሻንጉል ክልሎች የመምህራን ደመወዝ በዘመቻ በሚባል መልኩ ይቆረጣል።
ይሄ በጣም የከፋ የመልካም አስተዳደር ችግር ሆኖ ነው የተነሳው።
በአፋር ክልልም ለረዥም ጊዜ የደረጃ እድገት፣ የትምህርት ማሻሻያ ያልተከፈለበት ሁኔታ አለ።
በትግራይ ክልል የ17 ወራት የመምህራን ደመወዝ አልተከፈለም። የአምስት ወሩን ክልሉ እከፍላለሁ ብሎ ነበር እስካሁን አልከፈለም።
የክልሉ መምህራን ማኀበር ጠበቃ ቀጥሮ ክስ መስርቷል። በሕግ ሂደት ላይ ነው ” የሚሉ ቅሬታዎች ተነስተው መፍትሄ እንዲሰጥ መጠየቁን ገልጿል።
ከትምህርት ሚኒስቴር ባለድርሻ አካላት ባሉበት ለተነሳው ቅሬታ ታዲያ ምን የመፍትሄ አቅጣጫ ተቀመጠ ? ለሚለው የቲክቫህ ኢትዮጵያ ጥያቄ ፣ የትምህርት ሚኒስቴር ጉዳዩን እንዳዳመጠ፣ በቀጣይ ለመፍትሄ እንደሚሰራ መጠቆሙን ማኅበሩ አስረድቷል።
ማኀበሩ በመጨረሻም የተነሱት ቅሬታዎች ምላሽ እንዲያገኙ በአንክሮ ጠይቋል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
ጁመዓ ሙባረክ!
ሕብረት ባንክ ሕብር ሀቅ በተሰኘው ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎቱ ስር የሚገኙትን በርካታ አገልግሎቶች ተጠቃሚ እንዲሆኑ ይጋብዝዎታል፡፡
ሕብረት ባንክ
በሕብረት እንደግ!
📞 ለበለጠ መረጃ ወደ 995 ነፃ የጥሪ ማዕከል ይደውሉ፡፡
🤳 በቀላሉ አዳዲስ መረጃዎች እንዲደርስዎ የቴሌግራም ገፃችንን አሁኑኑ ይቀላቀሉ፡፡ https://t.iss.one/HibretBanket
🌐 ሌሎች የማህበራዊ ገፆቻችንን እና ድህረ ገፃችንን linktr.ee/Hibret.Bank ይጎብኙ፡፡
#HibirHaq #IslamicBanking #ShariaCompliant #HibretBank
ሕብረት ባንክ ሕብር ሀቅ በተሰኘው ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎቱ ስር የሚገኙትን በርካታ አገልግሎቶች ተጠቃሚ እንዲሆኑ ይጋብዝዎታል፡፡
ሕብረት ባንክ
በሕብረት እንደግ!
📞 ለበለጠ መረጃ ወደ 995 ነፃ የጥሪ ማዕከል ይደውሉ፡፡
🤳 በቀላሉ አዳዲስ መረጃዎች እንዲደርስዎ የቴሌግራም ገፃችንን አሁኑኑ ይቀላቀሉ፡፡ https://t.iss.one/HibretBanket
🌐 ሌሎች የማህበራዊ ገፆቻችንን እና ድህረ ገፃችንን linktr.ee/Hibret.Bank ይጎብኙ፡፡
#HibirHaq #IslamicBanking #ShariaCompliant #HibretBank
#ጤናባለሙያዎች
" ቀን ፣ ምሽት ፣ ቅዳሜ እና እሁድ እንዲሁም በበዓል ወቅት ጭምር እየገባን ሰርተን ክፈሉን ስንል የሚሰጠን ምላሽ ማስፈራሪያ ነው " - ጤና ባለሙያዎች
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የዲዩቲ ክፍያ አልተከፈለንም ያሉ ከ 80 በላይ የጤና ባለሞያዎች ስራ ማቆማቸው ተሰምቷል።
በከምባታ ዞን ፤ አንጋጫ ወረዳ ውስጥ የሚገኘው የአንጋጫ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል የሚሰሩ የጤና ባለሞያዎች የ6 ወር የዲዩቲ (የትርፍ ሰዓት ስራ ክፍያ) ስላልተከፈላቸው ከማክሰኞ 12/02/17 ዓ/ም ጀምሮ ስራ ማቆማቸው ተሰምቷል።
በአመት ከ120 ሺ በላይ ለሚሆኑ ሰዎች የህክምና አገልግሎት የሚሰጠው የአንጋጫ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ውስጥ የሚሰሩ በቁጥር ከ80 በላይ ይሆናሉ የተባሉት የጤና ባለሞያዎች ከማክሰኞ ጀምሮ ስራ ያቆሙ ሲሆን የሆስፒታሉ አስተዳደር በበኩሉ እስከ ትላንት ድረስ ወደ ስራቸው ካልተመለሱ አስተዳደራዊ እርምጃ እንደሚወስድባቸው በደብዳቤ አሳውቋቸዋል።
ይሁን እንጂ እስከ ዛሬ ወደስራ ገበታው የተመለሰ ባለሞያ አለመኖሩን ሰምተናል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ያነጋገራቸው በሆስፒታሉ የሚሰሩ ባለሞያዎች " ከዚህ በፊትም በስራ ላይ ሆናችሁ ጥያቄያችሁን አቅርቡ ተብለን ተስማምተን ጀምረን ተታለናል ሳይከፈለን የመጀመር ፍላጎት የለንም " ሲሉ ገልጸዋል።
ክፍያው ያልተከፈለው የ2015 ዓ/ም የግንቦት ወር የ2016 ዓም የመስከረም፣ ጥቅምት፣ ጥር እና የነሀሴ ወር የ2017 ዓ/ም የመስከረም ወር በአጠቃላይ የ6 ወር የዲዩቲ ክፍያ ነው።
" ከዚህ በፊት የ4 ወር ክፍያ ባልተከፈለን ወቅት በወረቀት በዞን እና በክልል ደረጃ ለሚመለከታቸው አካላት አሳውቀን ነበር ነገር ግን ችግራችን አልተፈታም ከዚህ በላይ በትዕግስት መጠበቅ አልቻልንም ለተለያዩ ማህበራዊ ቀውሶች እየተዳረግን ነው " ብለዋል።
አክለው " ቀን ፣ምሽት ፣ቅዳሜ እና እሁድ እንዲሁም በበዓል ወቅት ጭምር እየገባን ሰርተን ክፈሉን ስንል የሚሰጠን ምላሽ ማስፈራሪያ በመሆኑ እና ' እየሰራችሁ ጠይቁ እንጂ ሥራ ማቆም አትችሉም ' በማለት እንዲሁም የሚያስተባብሩትን አካላት ' በህግ እንጠይቃለን ' የሚል ማስፈራሪያ ከወረዳ አስተዳዳሪዎች እየደረሰን ነው " ብለዋል።
ባለሙያዎቹ " አምና ጥር ወር ላይ በተመሳሳይ ስራ አቁመን የነበረ ሲሆን የክልሉ ጤና ቢሮ እና የብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ጭምር አመልክተው ' እናንተ በስራ ላይ ተገኙ እንጂ እንዲከፈል እንነግራለን ' በማለታቸእ ወደ ስራ ተመልሰን ነበር ፤ ምንም ምላሽ ሳይሰጠን ቆይቶ በኋላ የአንድ ወር እንዲከፈለን ተደርጓል ፤ ከዚያ በኋላ ግን በተለመደው መቆራረጥ ነው የቀጠለው " ሲሉ ገልጸዋል።
ክፍያው እየተቆራረጠ ነው የሚገባው ወደ ኋላ ተመልሶ ያልተከፈለንን ክፍያ የመክፈል ምንም ፍላጎት የለም ነው ያሉት።
" የፊቱን እንከፍላለን ወደ ኋላ ተመልሶ ለመክፈል ግን ዞኑ በጀት የሌለው በመሆኑ በጀት ሲለቀቅልን ነው የምንከፍለው " የሚል ምላሽ እንደሚሰጣቸው ተናግረዋል።
ሆስፒታሉ ዝግ ሆኖ በቆየባቸው ቀናት ሁለት ነብሰ ጡር እናቶች ምጥ ይዟቸው ወደ ሆስፒታል መጥተው የነበረ ሲሆን ባለሞያ በሆስፒታሉ ባለመኖሩ ወደሌላ ሆስፒታል በግል ትራንስፖርት በሚጓዙበት ወቅት የህፃናቱ ህይወት እንዳለፈ አክለዋል።
ሀኪሞች ሥራ በማቆማቸው ታካሚዎችም ከሆስፒታል በር እየተመለሱ መሆኑም ተነግሯል።
ባለፈው ዓመት ጥር ወር ላይ በተመሳሳይ የስራ ማቆም አድማ ባደረጉበት ወቅት ሆስፒታሉ የወሰደው እርምጃ ያለምንም የቅጥር ማስታወቂያ 17 ሰዎችን መቅጠሩን የተናገሩት ጤና ባለሙያዎቹ " አሁንም ችግራችንን ከመፍታት ይልቅ ከሌሎች ቦታዎች ባለሞያ አምጥተን እንቀጥራለን በሚል እያስፈራሩ ነው " ብለዋል።
" ' ባለሞያ እንቀጥራለን እንደለቀቃቹ ቁጠሩት መጥታቹ ቁልፍ አስረክቡ ንብረት ላይ ቆልፋቹሃል ' በሚል ከፖሊስ ማዘዣ በማውጣት ማስፈራሪያ እየተደረገ ነው ፤ እኛ ሥራ እንለቃለን እላልንም እንሰራለን ግን ክፈሉን ነው ያልነው ተርበናል፣ ገንዘብ አጥተናል፣ ልጆቻችንን ማስተማር አልቻልንም የወተት እና የቤት ኪራይ መክፈል ከአቅማችን በላይ እየሆነ ነው " ሲሉ ገልጸዋል።
ቲክቫህ የባለሞያዎቹን ቅሬታ ይዞ የሆስፒታሉን ሥራ አስኪያጅ አቶ ተሰማ አበራን ትላንት ቢያነጋግርም ስብሰባ ላይ መሆናቸውን በመግለጽ ለጊዜው ምላሽ አልሰጡም።
ምላሻቸውን እንዳገኘን የምናካትት ይሆናል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
" ቀን ፣ ምሽት ፣ ቅዳሜ እና እሁድ እንዲሁም በበዓል ወቅት ጭምር እየገባን ሰርተን ክፈሉን ስንል የሚሰጠን ምላሽ ማስፈራሪያ ነው " - ጤና ባለሙያዎች
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የዲዩቲ ክፍያ አልተከፈለንም ያሉ ከ 80 በላይ የጤና ባለሞያዎች ስራ ማቆማቸው ተሰምቷል።
በከምባታ ዞን ፤ አንጋጫ ወረዳ ውስጥ የሚገኘው የአንጋጫ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል የሚሰሩ የጤና ባለሞያዎች የ6 ወር የዲዩቲ (የትርፍ ሰዓት ስራ ክፍያ) ስላልተከፈላቸው ከማክሰኞ 12/02/17 ዓ/ም ጀምሮ ስራ ማቆማቸው ተሰምቷል።
በአመት ከ120 ሺ በላይ ለሚሆኑ ሰዎች የህክምና አገልግሎት የሚሰጠው የአንጋጫ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ውስጥ የሚሰሩ በቁጥር ከ80 በላይ ይሆናሉ የተባሉት የጤና ባለሞያዎች ከማክሰኞ ጀምሮ ስራ ያቆሙ ሲሆን የሆስፒታሉ አስተዳደር በበኩሉ እስከ ትላንት ድረስ ወደ ስራቸው ካልተመለሱ አስተዳደራዊ እርምጃ እንደሚወስድባቸው በደብዳቤ አሳውቋቸዋል።
ይሁን እንጂ እስከ ዛሬ ወደስራ ገበታው የተመለሰ ባለሞያ አለመኖሩን ሰምተናል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ያነጋገራቸው በሆስፒታሉ የሚሰሩ ባለሞያዎች " ከዚህ በፊትም በስራ ላይ ሆናችሁ ጥያቄያችሁን አቅርቡ ተብለን ተስማምተን ጀምረን ተታለናል ሳይከፈለን የመጀመር ፍላጎት የለንም " ሲሉ ገልጸዋል።
ክፍያው ያልተከፈለው የ2015 ዓ/ም የግንቦት ወር የ2016 ዓም የመስከረም፣ ጥቅምት፣ ጥር እና የነሀሴ ወር የ2017 ዓ/ም የመስከረም ወር በአጠቃላይ የ6 ወር የዲዩቲ ክፍያ ነው።
" ከዚህ በፊት የ4 ወር ክፍያ ባልተከፈለን ወቅት በወረቀት በዞን እና በክልል ደረጃ ለሚመለከታቸው አካላት አሳውቀን ነበር ነገር ግን ችግራችን አልተፈታም ከዚህ በላይ በትዕግስት መጠበቅ አልቻልንም ለተለያዩ ማህበራዊ ቀውሶች እየተዳረግን ነው " ብለዋል።
አክለው " ቀን ፣ምሽት ፣ቅዳሜ እና እሁድ እንዲሁም በበዓል ወቅት ጭምር እየገባን ሰርተን ክፈሉን ስንል የሚሰጠን ምላሽ ማስፈራሪያ በመሆኑ እና ' እየሰራችሁ ጠይቁ እንጂ ሥራ ማቆም አትችሉም ' በማለት እንዲሁም የሚያስተባብሩትን አካላት ' በህግ እንጠይቃለን ' የሚል ማስፈራሪያ ከወረዳ አስተዳዳሪዎች እየደረሰን ነው " ብለዋል።
ባለሙያዎቹ " አምና ጥር ወር ላይ በተመሳሳይ ስራ አቁመን የነበረ ሲሆን የክልሉ ጤና ቢሮ እና የብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ጭምር አመልክተው ' እናንተ በስራ ላይ ተገኙ እንጂ እንዲከፈል እንነግራለን ' በማለታቸእ ወደ ስራ ተመልሰን ነበር ፤ ምንም ምላሽ ሳይሰጠን ቆይቶ በኋላ የአንድ ወር እንዲከፈለን ተደርጓል ፤ ከዚያ በኋላ ግን በተለመደው መቆራረጥ ነው የቀጠለው " ሲሉ ገልጸዋል።
ክፍያው እየተቆራረጠ ነው የሚገባው ወደ ኋላ ተመልሶ ያልተከፈለንን ክፍያ የመክፈል ምንም ፍላጎት የለም ነው ያሉት።
" የፊቱን እንከፍላለን ወደ ኋላ ተመልሶ ለመክፈል ግን ዞኑ በጀት የሌለው በመሆኑ በጀት ሲለቀቅልን ነው የምንከፍለው " የሚል ምላሽ እንደሚሰጣቸው ተናግረዋል።
ሆስፒታሉ ዝግ ሆኖ በቆየባቸው ቀናት ሁለት ነብሰ ጡር እናቶች ምጥ ይዟቸው ወደ ሆስፒታል መጥተው የነበረ ሲሆን ባለሞያ በሆስፒታሉ ባለመኖሩ ወደሌላ ሆስፒታል በግል ትራንስፖርት በሚጓዙበት ወቅት የህፃናቱ ህይወት እንዳለፈ አክለዋል።
ሀኪሞች ሥራ በማቆማቸው ታካሚዎችም ከሆስፒታል በር እየተመለሱ መሆኑም ተነግሯል።
ባለፈው ዓመት ጥር ወር ላይ በተመሳሳይ የስራ ማቆም አድማ ባደረጉበት ወቅት ሆስፒታሉ የወሰደው እርምጃ ያለምንም የቅጥር ማስታወቂያ 17 ሰዎችን መቅጠሩን የተናገሩት ጤና ባለሙያዎቹ " አሁንም ችግራችንን ከመፍታት ይልቅ ከሌሎች ቦታዎች ባለሞያ አምጥተን እንቀጥራለን በሚል እያስፈራሩ ነው " ብለዋል።
" ' ባለሞያ እንቀጥራለን እንደለቀቃቹ ቁጠሩት መጥታቹ ቁልፍ አስረክቡ ንብረት ላይ ቆልፋቹሃል ' በሚል ከፖሊስ ማዘዣ በማውጣት ማስፈራሪያ እየተደረገ ነው ፤ እኛ ሥራ እንለቃለን እላልንም እንሰራለን ግን ክፈሉን ነው ያልነው ተርበናል፣ ገንዘብ አጥተናል፣ ልጆቻችንን ማስተማር አልቻልንም የወተት እና የቤት ኪራይ መክፈል ከአቅማችን በላይ እየሆነ ነው " ሲሉ ገልጸዋል።
ቲክቫህ የባለሞያዎቹን ቅሬታ ይዞ የሆስፒታሉን ሥራ አስኪያጅ አቶ ተሰማ አበራን ትላንት ቢያነጋግርም ስብሰባ ላይ መሆናቸውን በመግለጽ ለጊዜው ምላሽ አልሰጡም።
ምላሻቸውን እንዳገኘን የምናካትት ይሆናል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
#ነዳጅ
ዛሬ በአዲስ አበባ የምትንቀሳቀሱ አሽከርካሪዎች ነዳጅ ያለባቸውን ማደያዎች ከያዙት የነዳጅ መጠን ጨምሮ ከላይ በምስሉ መመልከት ትችላላችሁ።
#AddisAbabaTradeBureau
@tikvahethiopia
ዛሬ በአዲስ አበባ የምትንቀሳቀሱ አሽከርካሪዎች ነዳጅ ያለባቸውን ማደያዎች ከያዙት የነዳጅ መጠን ጨምሮ ከላይ በምስሉ መመልከት ትችላላችሁ።
#AddisAbabaTradeBureau
@tikvahethiopia
" ከ2017 የትምህርት ዘመን ጀምሮ የሪሚዲያል ተማሪዎች የማጠቃለያ ምዘና ከ100% የሚሰጠው ከማዕከል ነው " - ትምህርት ሚኒስቴር
ትምህርት ሚኒስቴር በአቅም ማካካሻ (Remedial) ፕሮግራም ውጤት አያያዝ ላይ ማሻሻያ አደረገ፡፡
ከ2015 ዓ.ም ጀምሮ ከ50 በመቶ በታች ውጤት ካገኙ የ12ኛ ክፍል የመልቀቂያ ፈተና ተፈታኝ ተማሪዎች መካከል የተሻለ ውጤት ያላቸውን በመምረጥ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በማካካሻ (Remedial) ፕሮግራም ተመድበው የማካካሻ ትምህርት እንዲከታተሉ መደረጉ ይታወቃል።
በዚህ መሠረት ተማሪዎቹ 70% በማዕከል እና 30% በተቋማት የሚዘጋጁ ምዘናዎችን ተፈትነው ሲያልፉ የፍሬሽማን ፕሮግራም ተማሪዎች ሆነው እንዲቀጥሉ እየተደረገ ይገኛል።
ይሁን እንጂ ከ30% በተቋማት የሚሰጠው ውጤት አሰጣጥ ላይ ወጥነት የሌለ መሆኑን የትምህርት ሚኒስትሩ ለሁሉም የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች እና የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በፃፉት ሰርኩላር ገልፀዋል፡፡
በዚህም ዘንድሮ / ከ2017 የትምህርት ዘመን ጀምሮ የሪሚዲያል ተማሪዎች የማጠቃለያ ምዘና ፈተና ከ100% የሚሰጠው ከማዕከል እንዲሆን ተወስኗል፡፡
Via @tikvahuniversity
ትምህርት ሚኒስቴር በአቅም ማካካሻ (Remedial) ፕሮግራም ውጤት አያያዝ ላይ ማሻሻያ አደረገ፡፡
ከ2015 ዓ.ም ጀምሮ ከ50 በመቶ በታች ውጤት ካገኙ የ12ኛ ክፍል የመልቀቂያ ፈተና ተፈታኝ ተማሪዎች መካከል የተሻለ ውጤት ያላቸውን በመምረጥ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በማካካሻ (Remedial) ፕሮግራም ተመድበው የማካካሻ ትምህርት እንዲከታተሉ መደረጉ ይታወቃል።
በዚህ መሠረት ተማሪዎቹ 70% በማዕከል እና 30% በተቋማት የሚዘጋጁ ምዘናዎችን ተፈትነው ሲያልፉ የፍሬሽማን ፕሮግራም ተማሪዎች ሆነው እንዲቀጥሉ እየተደረገ ይገኛል።
ይሁን እንጂ ከ30% በተቋማት የሚሰጠው ውጤት አሰጣጥ ላይ ወጥነት የሌለ መሆኑን የትምህርት ሚኒስትሩ ለሁሉም የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች እና የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በፃፉት ሰርኩላር ገልፀዋል፡፡
በዚህም ዘንድሮ / ከ2017 የትምህርት ዘመን ጀምሮ የሪሚዲያል ተማሪዎች የማጠቃለያ ምዘና ፈተና ከ100% የሚሰጠው ከማዕከል እንዲሆን ተወስኗል፡፡
Via @tikvahuniversity
#ኢትዮቴሌኮም
ጂ.ኤስ.ኤም.ኤ ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር በአጋርነት የኢትዮጵያን ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ለማፋጠን ያዘጋጀውን በአይነቱ የመጀመሪያ የሆነውን የኢትዮጵያ ዲጂታላይዜሽን ሪፖርት ትላንት በአዲስ አበባ ይፋ አድርጓል።
ሪፖርቱ የኢትዮጵያ ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ጥረት በማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ እድገት፣ በፈጠራ በማጎልበት እና ዘላቂ ልማትን በማምጣት ረገድ እያስመዘገበ ያለውን ውጤት እንዲሁም የሀገሪቱን ዲጂታል ስነ-ምህዳር ከማሳደግ አንጻር እየተደረገ ያለውን ጥረት ዳስሷል።
የጂ.ኤስ.ኤም.ኤ ዘገባ እንደሚያመለክተው የቴሌኮም ዘርፍ በኢትዮጵያ ቁልፍ የኢኮኖሚ አንቀሳቃሽ ሆኖ በመቀጠል እ.ኤ.አ በ2023 በቀጥታ እና በተዘዋዋሪ ያበረከተው ተጨምሮ ከአጠቃላይ የሀገር ውስጥ ምርት (GDP) 8% ደርሷል።
በሪፖርቱ የተዳሰሱ ግኝቶች ኢትዮጵያ በዲጂታል ትራንስፎርሜሽን እያከናወነቻቸው ለሚገኙ ተግባራት ዓለም አቀፋዊ ዕውቅናን የሚፈጥርላት ሲሆን በተለይም ለዜጎች አካታች ዲጂታል ኢኮኖሚን ለመገንባት ያላትን ቁርጠኝነት እንደሚያጎለብት ይታመናል፡፡
ኢንጅነር ባልቻ ሬባ የኢትዮጵያ ኮሙዩኒኬሽን ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ጂ.ኤስ.ኤም.ኤ እና ኢትዮ ቴሌኮም የዘርፉ ባለድርሻ አካላትን ያሰባሰበውን መርሃ ግብር በማዘጋጀታቸው ያላቸውን አድናቆት በመግለጽ ለቴሌኮም ኦፕሬተሮች የሚያደርጉትን ድጋፍ አጠናክረው እንደሚቀጥሉ አረጋግጠዋል።
የኢትዮጵያን ቀጣይ የዲጂታል ጉዞ ለማፋጠን ጠቃሚ ግብዓት ለሚሆነው የ ጂ.ኤስ.ኤም.ኤ አድናቆታችንን ለመግለጽ እንወዳለን።
ሪፖርቱን ያንብቡ፡ https://bit.ly/3NCN7Kx
(ኢትዮ ቴሌኮም)
ጂ.ኤስ.ኤም.ኤ ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር በአጋርነት የኢትዮጵያን ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ለማፋጠን ያዘጋጀውን በአይነቱ የመጀመሪያ የሆነውን የኢትዮጵያ ዲጂታላይዜሽን ሪፖርት ትላንት በአዲስ አበባ ይፋ አድርጓል።
ሪፖርቱ የኢትዮጵያ ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ጥረት በማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ እድገት፣ በፈጠራ በማጎልበት እና ዘላቂ ልማትን በማምጣት ረገድ እያስመዘገበ ያለውን ውጤት እንዲሁም የሀገሪቱን ዲጂታል ስነ-ምህዳር ከማሳደግ አንጻር እየተደረገ ያለውን ጥረት ዳስሷል።
የጂ.ኤስ.ኤም.ኤ ዘገባ እንደሚያመለክተው የቴሌኮም ዘርፍ በኢትዮጵያ ቁልፍ የኢኮኖሚ አንቀሳቃሽ ሆኖ በመቀጠል እ.ኤ.አ በ2023 በቀጥታ እና በተዘዋዋሪ ያበረከተው ተጨምሮ ከአጠቃላይ የሀገር ውስጥ ምርት (GDP) 8% ደርሷል።
በሪፖርቱ የተዳሰሱ ግኝቶች ኢትዮጵያ በዲጂታል ትራንስፎርሜሽን እያከናወነቻቸው ለሚገኙ ተግባራት ዓለም አቀፋዊ ዕውቅናን የሚፈጥርላት ሲሆን በተለይም ለዜጎች አካታች ዲጂታል ኢኮኖሚን ለመገንባት ያላትን ቁርጠኝነት እንደሚያጎለብት ይታመናል፡፡
ኢንጅነር ባልቻ ሬባ የኢትዮጵያ ኮሙዩኒኬሽን ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ጂ.ኤስ.ኤም.ኤ እና ኢትዮ ቴሌኮም የዘርፉ ባለድርሻ አካላትን ያሰባሰበውን መርሃ ግብር በማዘጋጀታቸው ያላቸውን አድናቆት በመግለጽ ለቴሌኮም ኦፕሬተሮች የሚያደርጉትን ድጋፍ አጠናክረው እንደሚቀጥሉ አረጋግጠዋል።
የኢትዮጵያን ቀጣይ የዲጂታል ጉዞ ለማፋጠን ጠቃሚ ግብዓት ለሚሆነው የ ጂ.ኤስ.ኤም.ኤ አድናቆታችንን ለመግለጽ እንወዳለን።
ሪፖርቱን ያንብቡ፡ https://bit.ly/3NCN7Kx
(ኢትዮ ቴሌኮም)