TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
58.9K photos
1.5K videos
211 files
4.07K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
#ኢትዮቴሌኮም : ዛሬ የኢትዮ ቴሌኮም 10 በመቶ የአክሲዮን ሽያጭ ይፋ ሆኗል። ጠ/ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት በተካሄደ ሥነ-ስርዓት የኢትዮ ቴሌኮም 10 በመቶ የአክሲዮን ሽያጭ ይፋ ተደርጓል። የአክሲዮን ሽያጭ ጊዜው ከዛሬ ጥቅምት 6 ጀምሮ እስከ ታኅሣስ 25 ቀን 2017 ዓ.ም ድረስ ይቆያል ተብሏል፡፡ ዝርዝር መረጃ ፦ - በ2016 በወጣው የሂሳብ ሪፖርት የድርጅቱ ካፒታል ➡️ 100…
አንድ ሰው ከኢትዮ ቴሌኮም የገዛውን አክሲዮን ድርሻ ማዘዋወር፤ አትርፎ መሸጥ ፤ እንደ ማሲያዣ መጠቀም ቢፈልግ ይችላል ወይ ?

አትዮ ቴሌኮም አሁን የሚጀመረው የአክሲዮን ሺያጭ የመጀመሪያው ምዕራፍ እንደሆነ አስታውቋል።

በዚህ ምዕራፍ ዜጎች የአክሲዮን ድርሻ ብቻ መግዛት የሚችሉ ይሆናል።

ዜጎች ድርሻቸውን ማዘዋወር ፤ አትርፎ መሸጥ ፤ እንደ ማሲያዣ መጠቀም የሚችሉት ኢትዮ ቴሌኮም ሁለተኛ ምዕራፍ ብሎ ባስቀመጠው ሲሆን ይህም ገና በሂደት ላይ እንዳለ ተጠቅሷል።

የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ሥራ አስፈጻሚ ፍሬህይወት ታምሩ ቴሌኮም በ " listing " ሂደት ላይ እንደሚገኝ እና ይህም በአጭር ጊዜ እንደሚጠናቀቅ የጠቀሱ ሲሆን ይፋዊ ቀን ግን አልተቆረጠለትም።

የሁለተኛው ዙር አክሲዮን ሽያጭ ሲጀመር ደግሞ ዜጎች ድርሻ ማዘዋወር ፣ አትርፎ መሸጥ ፤ እንደ ማሲያዣ መጠቀም ያስችላቸዋል።

እንዴት ነው አክሲዮን የሚገዛው ?

በቴሌብር ላይ ነው መግዛት የሚቻለው። ቴሌብር ላይ ሲገቡ አክሲዎን ለመግዛት የሚል አማራጭ ይገናኛል (ልክ ላውንች ሲደረግ) በዛ አማካኝነት ነው መግዛት የሚቻለው። በዛ ዝርዝር መረጃ ይገኛል፤ የደብንበኝነት ውልን ስለሚኖር አንብቦ መቀጠል ይችላል ከተስማሙ።

(እስካሁን ድረስ ቴሌብር ላይ ይህ የአክሲዎችን ሽያጭ አማራጭ አልመጣም ልክ ሲመጣ እናሳውቃችኃለን)

ፎርሙን በ48 ሰዓት ውስጥ ማስተካከል  ይቻላል ፤ በተመሳሳይ ክፍያም በ48 ሰዓት ውስጥ መከፈል አለበት። ከ48 ሰዓት በኃላ ፎርሙን ማስተካከል አይቻልም።

ፎርሙን መጀመሪያ በመደበኛ መታወቂያ፣ መንጃ ፍቃድ ፣ ፓስፖርት መሙላት የሚቻል ሲሆን መጨረሻ ላይ የሼር ባለቤት ለመሆን የናሽናል አይዲ (ፋይዳ) ያስፈልጋል።

ሼር ገዢ ተመዝጋቢዎች ቁጥር ለሽያጭ ከቀረበው ሼር በላይ ከመጣ ከዛ ውስጥ እነማን የሼሩ ባለቤት ይሆናሉ የሚለውን ለመለየት የሚያስችል አሰራር ተቀምጧል። (በቀጣይ በዚህ ላይ መረጃ እናቀርባለን)

➡️ ሼር መግዛት ማመልከይ የሚችለው ኢትዮጵያዊ ዜጋ እና እዚሁ ሀገር ውስጥ በአካል ያለ ነው።

2016 ዓ/ም በወጣ የሂሳብ ሪፖርት የድርጅቱ የካፒታል 100 ቢሊዮን ብር ሲሆን በዓለም አቀፍ የ3ተኛ ወገን የገበያ ተመን መሰረት ድርጅቱ የሚያወጣው ዋጋ 300 ቢሊዮን ብር ነው።

በመጀመሪያ ዙር መደበኛ የአክሲዮን ሽያጭ የቀረበው ደግሞ 100 ሚሊዮን ሼር ነው። የአንድ ሼር ዋጋም 300 ብር ነው። ዝቅተኛ መግዛት የሚቻለው የሼር መጠን  33 ሼር ሲሆን ይህን በገንዘብ ሲቀመጥ 9,900 ብር ይሆናል። ከፍተኛው መግዛት የሚቻለው የሼር መጠን 3,333 ሲሆን ይህን በገንዘብ ሲቀመጥ 999,900 ብር ይሆናል።

#TikvahEthiopiaAddisAbaba

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" ለመሬት መንቀጥቀጡ ምክንያት የሆነው ቅልጥ አለት መሬት ውስጥ መምጣቱ ነው " - ኤልያስ ሌዊ (ዶ/ር) ዛሬ ጠዋት 1 ሰዓት ከ37 ደቂቃ ከ50 ሴኮንድ ላይ የመሬት መንቀጥቀጥ ተከስቷል። ቦታው  ባለፈው በተከሰተበት አዋሽ ፈንታሌ አካባቢ ሲሆን በሬክተር ስኬል 4.6 አካባቢ እነደሆነ ተገልጿል። የዛሬው የመሬት መንቀጥቀጥ ንዝረት አዲስ አበባ ድረስ በደንብ ተሰምቷል። በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጂኦፊዚክስና…
#Alert🚨

ከደቂቃዎች በፊት በአዲስ አበባ የተለያዩ አካባቢዎች የመሬት መንቀጥቀጥ ንዘረት እንደሰሙ ነዋሪዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ጠቁመዋል።

" በተለይም ፎቅ ላይ በደንብ ይታወቅ ነበር " ብለዋል።

ጎተራ፣ አያት ፣ ባልደራስ ፣ ሰሚት ፣ መካኒሳ ፣ ጀሞ ፣ ኮዬ ፣ ጣፎ ፣ ቱሉ ዲምቱ ፣ ጦር ኃይሎች ፣ ቀጨኔ፣ ጎፋ ... እንዲሁም ከሌሎች በርካታ አካባቢዎች ቲክቫህ ኢትዮጵያ ንዝረቱ መሰማቱን የሚመለከቱ መልዕክቶችን ተቀብሏል።

ይህ የመሬት መንቀጥቀጥ ንዝረት በቀናት ውስጥ ለሶስተኛ ጊዜ ነው።

ሰሞኑን በአዋሽ ፈንታሌ አካባቢ የመሬት መንቀጥቀጥ እየተከሰተ መሆኑ ይታወቃል።

ይህም የመሬት መንቀጥቀጥ ንዝረቱ አዲስ አበባ እና ሌሎች ከተሞች ድረስ እየተሰማ ነው።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Alert🚨 ከደቂቃዎች በፊት በአዲስ አበባ የተለያዩ አካባቢዎች የመሬት መንቀጥቀጥ ንዘረት እንደሰሙ ነዋሪዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ጠቁመዋል። " በተለይም ፎቅ ላይ በደንብ ይታወቅ ነበር " ብለዋል። ጎተራ፣ አያት ፣ ባልደራስ ፣ ሰሚት ፣ መካኒሳ ፣ ጀሞ ፣ ኮዬ ፣ ጣፎ ፣ ቱሉ ዲምቱ ፣ ጦር ኃይሎች ፣ ቀጨኔ፣ ጎፋ ... እንዲሁም ከሌሎች በርካታ አካባቢዎች ቲክቫህ ኢትዮጵያ ንዝረቱ መሰማቱን የሚመለከቱ…
#Update

እንደ ' አሜሪካ የጂኦሎጂካል ሰርቬይ ድረገጽ ' ዛሬ ምሽት ልክ 5:11 ላይ የመሬት መንቀጥቀጥ ተከስቶ ነበር።

የመሬት መንቀጥቀጡ ከአዋሽ በሰሜን በኩል 17 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ነው።

በሬክተር ስኬል 4.6 የተመዘገበ እንደሆነ ጠቁሟል።

የመሬት መንቀጥቀጡ ንዝረት በአዲስ አበባ የተለያዩ አካባቢዎች እና በተለያዩ የክልል ከተሞች ተሰምቷል።

አዋሽ አካባቢ ባለፉት ሳምንታት ተደጋጋሚ የመሬት መንቀጥቀጥ እየተከሰተ ሲሆን አዲስ አበባ ድረስ የዘለቀ ንዝረት ሲሰማ ይህ በቀናት ልዩነት ለ3ኛ ጊዜ ነው።

ከቀናት በፊት አዋሽ ፈንታሌ አካባቢ በሬክተር ስኬል 4.6 የሆነ የመሬት መንቀጥቀጥ ከዛ በፊት ደግሞ በሬክተር ስኬል 4.9 የሆነ የመሬት መንቀጥቀጥ ተከስቶ ንዝረቱ አዲስ አበባና ሌሎች ከተሞች ላይ መሰማቱ ይታወሳል።

@tikvahethiopia
" የታይ-ታይ ከረሜላ በህጋዊ መንገድ የተመዘገበ እና የተረጋገጠ ጤናማ እና ደህንነቱ የተጠበቀ ነው " -ቪታ ፉድ ኢንዱስትሪ ኃ.የተ.የግ.ማ

መሰረቱን በቱርክ ያደረገው እና እ.ኤ.አ ከ 2019 ጀምሮ በኢትዮጵያ ታይ ታይ የተሰኙ ከረሜላዎችን በማምረት ለተጠቃሚዎች እያደረሰ የሚገኘው ቪታ ፉድ ኢንዱስትሪ ኃ.የተ.የግ.ማ ምርቶቼ በህጋዊ መንገድ በኢትዮጵያ በአምራችነት የተመዘገቡ እና ጥራታቸውን የጠበቁ መሆናቸውን ሊሰመርበት ይገባል ሲል ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በላከው መግለጫ ገልጿል።

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በገበያ ላይ በመንግስት ያልተመዘገቡና የምስክር ወረቀት የሌላቸው ተመሳስለው የተሰሩ ምርቶች መኖራቸውን አስተውለናል ያለው ድርጅቱ እነዚህ ምርቶች በህገ ወጥ መንገድ ስለሚመረቱ ምንም አይነት የአምራች መረጃም ሆነ አድራሻ የላቸውም ብሏል።

ተቋሙ ጉዳዩን ለአዲስ አበባ ጤና ቢሮ እና ለኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለሥልጣን በተደጋጋሚ ማሳወቁን በመግለጫው ገልጿል።

የአዲስ አበባ ጤና ቢሮም እነዚህን ህገወጥ ምርቶች የመለየት ስራ የሰራ ሲሆን የኢትዮጵያ ምግብ እና መድኃኒት ቁጥጥር ባለሥልጣንም ምርቶቹን በመገናኛ ብዙሃን በማሳወቅ ከገበያ አግዷቸዋል።

ሆኖም እኚህ የታገዱ፣ በህገወጥ መንገድ የተመረቱ እና ተመሳስለው የተሰሩ ምርቶች የእኛን ምርቶች አመሳስለው ስለሚገለብጡ ደንበኞቻችን ምርቶቹን ከእኛ(ከህጋዊ ምርቶች)መለየት ባለመቻላቸው ምርቶቻችን ታግደዋል የሚል ብዥታ እንደተፈጠረ ተናግሯል።

ድርጅቱ የታይ-ታይ ከረሜላ በህጋዊ መንገድ የተመዘገበ እና የተረጋገጠ ጤናማ እና ደህንነቱ የተጠበቀ እንዲሁም በህጋዊ መንገድ በኢትዮጵያ በአምራችነት የተመዘገበ መሆኑን ሊሰመርበት ይገባል ብሏል።

እነዚህ ምርቶች (ከረሜላዎች) በተለይም ልጆች የሚጠቀሟቸው በመሆኑ ሁሉም ሰው ከመግዛቱ በፊት የምርቶቹን ደህንነት ግምት ውስጥ ማስገባት እንደሚኖርበት አሳስቧል።

@tikvahethiopia
🔈 #የሰራተኞችድምጽ

" ኑሮን መቋቋም አቃተን ! " - ሰራተኞች

በተለይ በተለይ አዲስ አበባ ከተማ ነዋሪነታቸውን ያደረጉና ቃላቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የሰጡ በተለያዩ የመንግሥት እና የግል ተቋማት ውስጥ ተቀጥረው የሚሰሩ ሰራተኞች ኑሮን መቋቋም ፈተና እንደሆነባቸው ገልጸዋል።

ቃላቸውን ከሰጡት ውስጥ የልጆች እናት መሆናቸውን የገለጹ አንዲት እናት " መሃል ከተማ ያለውን የማይቀመስ የቤት ኪራይ ሽሽት ከከተማ ጥግ ብገባም በየጊዜው በእያንዳንዱ ነገር ላይ በሚታየው ጭማሪ ኑሮን መቋቋም አልቻልኩም " ብለዋል።

" እኔ የዛሬ አመት ይከፈለኝ የነበረ ደመወዝ ዛሬም እዛው ነው ትምህርት ቤት፣ የምግብ ግብዓት፣ አልባሳት፣ ትራንስፖርት ሌሎችም ነገሮች ጨምረዋል ፤ ነገር ሁሉ ነው ግራ ያጋባኝ " ሲሉ በሃዘን ስሜት ያሉበትን ሁኔታ ገልጸዋል።

ሌላኛዋ ወጣት በአንድ የግል ድርጅት ውስጥ ተቀጥራ የምትሰራ ፥ " ከተመረቅኩ ይኸው 5 ዓመቴ ነው ፤ ደህና ደመወዝ የለኝም። የምሰራው ቀን ሙሉ ነው ደመወዜ እዛው ሆኖ ያልጨመረ ነገር የለም " ብላለች።

" ቤት ኪራይ ብቻዬን መክፈል ስለማልችል ከጓደኛዬ ጋር ነው የምኖረው ፤ እንደዛም ሆኖ የወር ጊቢዬን ምኑን ከምን እንደማደረገው አላውቅም ይኸው ልክ እንደ ዩኒቨርሲቲ ተማሪ አንዳንዴ ቤተሰቦቼ ገንዘብ ይልኩልኛል ፤ ሁኔታዎች እንዲህ ከሆኑ እዛው ቤተሰቤ ጋር ሄጅ ሻይ ቡናም ቢሆን እየሰራው ብኖር ይሻለኛል " ስትል ተናግራለች።

ሌላ ቃላቸውን የሰጡ አንድ አባት ፤ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በየአገልግሎቱ ላይ የሚታዩት ጭማሪዎች እሳቸውና ሌሎችም ሰራተኛ ዜጎች ቼይ ከፍተኛ ጫና እንደሚያሳድር ገልጸዋል።

" አንዳንድ የመንግሥት ተቋማት ሳይቀሩ ለአገልግሎት የሚያስከፍሉትን ጭማሪ አድርገዋል ፤ ትራንስፖርት ዋጋው ጨምሯል እኔም ሆንኩኝ ሌላው ሰራተኛ ወርሃዊ ደመወዙ እዚህ ግባ የማይባል ነው ፤ ታዲያ ኑሮ የሚኖረው  ፤ ልጆችን ማሳደግ የሚቻለው እንዴት ነው ? " ሰሉ ጠይቀዋል።

አዲስ አበባ ከተማ በርካታ ዜጎች የሚኖሩባት ሲሆን የቤት ኪራይ ዋጋ የማይቀመስባት በመሆኑ በርካቶች ከሚሰሩበት ርቀው ከከተማ ዳር ዳር ተከራይተው ለመኖር ይገደዳሉ።

በርካቶች ጥዋት ማታ ለፍተው ተንከራተው የሚያገኙት ገቢም እዚህ ግባ የማይባል ፤ ያሰቡትን ለማሳካት ይቅርና ኑሮን ለመግፋት የማያስችል ነው።

በተለይ ወርሃዊ ደመወዝ የሚያገኙ ዜጎች በኑሮ ውድነቱ እጅግ በጣም ነው የሚፈተኑት።

ቃላቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የሰጡ ወጣቶች በክልል ከተሞች ያለው ብሔር እየመረጡ ፣ በትውውቅ በሙስና ሰዎችን ስራ መቅጠር ፣  አስተማማኝ የሆነ ሰላምና ደህንነት ሁኔታ አለመኖር ፣ ብዙ ድርጅት እና ተቋማት አለመኖር ፣ የሰፋ የስራ እድል አለመኖር ፣ በአንዳንድ ከተሞችም ያለውን እንቅስቃሴ እጅጉን መዳከም ሳቢያ በአንጻራዊነት አዲስ አበባን ለኑሮና ስራ እንዲመርጧት እንዳደረጋቸው ጠቁመዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update እንደ ' አሜሪካ የጂኦሎጂካል ሰርቬይ ድረገጽ ' ዛሬ ምሽት ልክ 5:11 ላይ የመሬት መንቀጥቀጥ ተከስቶ ነበር። የመሬት መንቀጥቀጡ ከአዋሽ በሰሜን በኩል 17 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ነው። በሬክተር ስኬል 4.6 የተመዘገበ እንደሆነ ጠቁሟል። የመሬት መንቀጥቀጡ ንዝረት በአዲስ አበባ የተለያዩ አካባቢዎች እና በተለያዩ የክልል ከተሞች ተሰምቷል። አዋሽ አካባቢ ባለፉት ሳምንታት ተደጋጋሚ የመሬት…
" የቅልጥ ዓለቱ እንቅስቀሴ እስከቀጠለ ድረስ የመሬት መንቀጥቀጥ ክስተቱ የመቀጠል እድል አለው " - ኤልያስ ሌዊ (ዶ/ር)

በዛሬው ዕለት ከቀኑ 6 ሰዓት አከባቢ በ 'አዋሽ ፈንታሌ' የመሬት መንቀጥቀጥ ተከስቷል።

ንዝረቱ በአዲስ አበባ ከተማ የተለያዩ አካባቢዎች ተሰምቷል፡፡

ትናንት ምሽት የመሬት መንቀጥቀጥ ንዝረት መሰማቱ ይታወሳል።

አሁንም ዳግም የመሬት መንቀጥቀጥ ንዝረቱ መከሰቱ ታውቋል።

በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጂኦፊዚክስና ስፔስ ሳይንስ ዳይሬክተር ዶ/ር ኤሊያስ ሌዊ ለብሔራዊ ቴሌቪዥን ጣቢያ በሰጡት ቃል፥ " ከቀኑ 6 ሰዓት ከ10 ደቂቃ ከ9 ሰኮንድ በአዋሽ ፈንታሌ የመሬት መንቀጥቀጥ ተከስቷል በሬክተር ስኬል 4.6 አካባቢ ነው " ብለዋል።

የዛሬው የመሬት መንቀጥቀጥ የተከሰተው ባለፈው በተከሰተበት አዋሽ ፈንታሌ አካባቢ ሲሆን በአካባቢው ያለው የመሬት መንቀጥቀጥ እንቅስቃሴ አሁንም እንዳልቆመ ተናግረዋል።

" አሁን የተከሰተው የመሬት መንቀጥቀጥ የንዝረት መጠኑ አነስተኛ ነው " ሲሉ ገልጸው " በአዋሽ ፈንታሌ እና ሳቡሬ ከተማ መካከል ላይ ያለው የቅልጥ ዓለት እንቅስቀሴ እስከቀጠለ ድረስ የመሬት መንቀጥቀጥ ክስተቱ የመቀጠል እድል አለው "  በማለት ለብሔራዊ ቴሌቪዥን ጣቢያ አስረድተዋል።

@tikvahethiopia
#ትኩረት🚨

ከሰሞኑን በርካታ ሰዎች በተለይ ትንንሽ ህጻናት በጉንፋን እና በጉንፋን መሰል የመተንፈሻ አካላት ህመም እየተያዙ ይገኛሉ።

ይህንን ወቅታዊ ሁኔታ አስመክቶ ጤና ሚኒስቴር እና የኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና እንስቲትዩት ያጋራ መግለጫ ልከዋል።

ምን አሉ ?

➡️ የጉንፋን ሕመም በተፈጥሮ የላይኛውን የመተንፈሻ የሰውነት ክፍሎች ማለትም አፍንጫን፣ ጎሮሮን እና የአየር መተላለፊያ ባንቧን የሚያጠቃ ተላላፊ ሕመም ነዉ።

➡️ ሪኖ ቫይረስ ለጉንፉን መከሰት ዋና ምክንያት ሲሆን፣ ኮሮና፣ ኢንፍሉዌንዛ፣ ፓራ ኢንፍሉዌንዛ፣ አር ኤስ ቪ(RSV) ቫይረሶች ደግሞ ለጉንፉን መሰል ህመሞች መከሰት ዋና ዋና ምክንያቶች ናቸዉ። ከተጠቀሱት ቫይረሶችም ለጉንፋን ሕመም መከሰት 50 በመቶ ድርሻውን የሚይዘው ሪኖ ቫይረስ ነው፡፡ በደረቅ ነፋሳማ ወቅት የአፍንጫ የውስጠኛው ስስ ሽፋን “ ሙከስ መምብሬን ” ስለሚደርቅ የጉንፋን ሕመም እና ተላላፊነቱ ይጨምራል፡፡

➡️ የክረምት ወራት ወይም የዝናብ ወቅት ማብቃቱን ተከትሎ መስከረምን ጨምሮ በጥቅምትና ህዳር ወራት እንደዚህ አይነት ጉንፋን መሰል ህመም የሚጠበቅ ነው፡፡

➡️ ሕመሙ ከሰው ወደ ሰው የሚተላለፈው በቫይረሱ የተጠቃ ሰው በሚያስልበት ወይም በሚያስነጥስበት ጊዜ እንደሆነና በተጨማሪም ሰዎች ቫይረሱ ያረፈበትን የበር እጀታ፣ ጠረጴዛ ወይም በሕመምተኛው የተነካካንን ሰው እጅ ከነኩ በኋላ አፋቸውንና አፍንጫቸውን ሲነካኩ ቫይረሱ ለመተላለፍ በሚፈጠርለት ምቹ ሁኔታ ነው።

➡️ የጉንፋን ሕመም የመጀመሪያ ምልክቱ ከመጀመሩ አንድ ቀን በፊት ተላላፊ ሊሆን ይችላል፤ ሕመሙ ከጀመረ ከ 5 እስከ 10 ባሉት ቀናት ደግሞ ሕመምተኛው ቫይረሱን ያስተላልፋል።

➡️ ህመሙ አብዛኛዉን ጊዜ እስከ 2 ሳምንት ሊቆይ ይችላል። ምልክቶቹም እንደ ፦
° የአፍንጫ ፈሳሽ መብዛት፣
° ሳል፣
° ትኩሳት፣
° ራስ ምታትና ጉሮሮን መከርከር፣
° ማስነጠስ፣
° አይን ማሳከክ እና መቅላት፣
° ማስታወክ፣
° ከፍ ሲልም የትንፋሽ ማጠር፣
° ከፍተኛ ድካምና የምግብ ፍላጎት መቀነስ ዋና ዋናዎቹ ናቸዉ።

➡️ ከመስከረም ወር ጀምሮ መሰል ህመም ተሰምቷቸው ወደ ጤና ተቋማት በመሄድ ናሙና ከሰጡት ታካሚዎች ውስጥ አር ኤስ ቪ የተገኘባቸዉ ቁጥር የመጨመር ሁኔታ ያሳያል፡፡ በዚሁ ወቅት የተከሰተው ጉንፋን መሰል ህመም (አር ኤስ ቪ) በተለይ በህጻናት ላይ በብዛት የተከሰተ ሲሆን ለዚህም ወቅቱ ትምህርት ቤት የተከፈተበት በመሆኑ ለበሽታው መስፋፋት አስተዋጽኦ አድርጓል፡፡

➡️ ባለፈዉ 1 ወር ዉስጥ ተመርምረዉ አር ኤስ ቪ ከተገኘባቸዉ ታካሚዎች መካከል 84% ያክሉ እድሜያቸዉ ከ5 አመት በታች ነዉ። እንደዚሁም ባለፈዉ ሳምንት ለአር ኤስ ቪ ከተመረመሩት 81 ናሙናዎች 49 (60.5%) ያህሉ ቫይረሱ ተገኝቶባቸዋል።

➡️ አስፈላጊው ጥንቃቄ ካልተደረገ በሽታው የመዛመት እድሉ ከፍ ሊል እንደሚችል፤ በተለይ ቀዳሚ ተጎጅ ሊሆኑ የሚችሉ እንደ ህጻናትና አረጋውያን ያሉ የህብረተሰብ ክፍሎች አና ተጓዳኝ የጤና ችግር እንደነ አስም፣ የስኳር በሽታ፣ ካንሰር እና ሌሎች ሥር የሰደዱ በሽታዎች ያሉባቸው ሕሙማን ከፍተኛ ጥንቃቄ ልናደርግላቸው እና ወደ ጤና ተቋማት በመሄድ አስፈላጊዉን ምርመራና ህክምና ሊያደርጉ ይገባል።

➡️ የጉንፋን ሕመም የጆሮ ኢንፌክሽን እና የሳንባ ምች ሕመምን ጨምሮ ለተለያዩ ሕመሞች ተጋላጭ ሊያደርግ ይችላል፡፡

ጉንፋን መሰል በሽታን የምንከላከልባቸው መንገዶች ምንድናቸው ?
° የእጅ ንጽህናን መጠበቅ፣
° ሰዎች በተሰበሰቡበት ቦታ የአፍና አፍንጫ ጭምብል(ማስክ) ማድረግ
° በዕለት ኑሯችን የምንጠቀምባቸውን በከባቢዎቻችን የሚገኙ ቁሳቁሶችን ማጽዳት
° የብዙሃን ማጓጓዣ ትራንስፖርት ላይ መስኮቶችን በመክፈት በቂ የአየር ዝዉዉር እንዲኖር በማድረግ የበሽታዉን የመተላለፍ ዕድል መቀነስ ይቻላል፡፡


#ማሳሰቢያ ፦ ህብረተሰቡ አስፈላጊውን የጥንቃቄ እርምጃዎችን እንዲወስድና ጠንከር ያለ የበሽታው ምልክት የሚታይበት ሰው በፍጥነት በአቅራቢያው ወደሚገኝ የጤና ተቋም በመሄድ አስፈላጊውን የህክምና ምክር አና ዕርዳታ ማግኘት አለበት፡፡

#MoH #EPHI

@tikvahethiopia
#DStvEthiopia

⚽️አጓጊው የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ስምንተኛ ሳምንት ጨዋታዎች!
👉 ጨዋታዎችን ከትንታኔ ፣ ከተጫዋች ብቃት እስከ ቡድን ወኔ በሱፐርስፖርት ለመከታተል ዛሬውኑ ደንበኝነትዎን ያራዝሙ!

ደንብና ሁኔታዎች ተፈፀሚነት አላቸው! ለበለጠ መረጃ
👇
www.dstv.com/en-et
👉 የዲኤስቲቪን ዲኮደር በ1,999 ብር ከ1 ወር ነፃ የሜዳ ፓኬጅ ጋር ያገኛሉ።

የMyDStv Telegram bot ሊንክ ይጫኑ!
👇
https://bit.ly/2WDuBLk

#PremierLeagueAllonDStv #ሁሉምያለውእኛጋርነው #DStvSelfServiceET
#MesiratEthiopia

ድሬዳዋና ሃዋሳ ቢዝነሱን ማሳደግ ለሚፈልግ ⬇️
- በፋይናንስ፣
- በማርኬቲንግ፣
- ችሎታን በማዳበር፣
- በቴክኖሎጂ፣
- በኔትወርኪንግ፣
- የባለሙያ አማካሪዎችን በማግኘት፣
- በፖሊሲ፣
- በአገልግሎት ሰጪነት እና
- በአማካሪነት ድጋፍ ለማግኘት https://bit.ly/3BGeH75 ላይ ተመዝገቡ።

የመስራት ስራ ፈጠራ ፕሮግራም አባል ይሁኑና ቢዝነስዎ እንዲያድግ አጠቃላይ ድጋፍን ያግኙ።

ሴቶች እና አካል ጉዳተኞች እንዲያመለክቱ ይበረታታሉ!
#Tigray

" ጠቅላይ ሚንስትሩ ያስቀመጡት የመፍትሄ አቅጣጫ ተግባራዊ አልሆነም " - የትግራይ የንግድ ማህበረሰብ ግብረ ሃይል ተወካዮች

የትግራይ የንግድ ማህበረሰብ ግብረ ሃይል ተወካዮች ከሰሞኑን ውይይት ተቀምጠው ነበር።

በዚህም ወቅት ፤ " ጠ/ሚ ዶ/ር ዐብይ አህመድ በትግራይ ከነበረው ጦርነት ጋር በተያያዘ የተከማች የብድር ወለድና ቅጣት መልክ እንዲይዝ ባለፈው ዓመት የሰየሙት የመፍትሄ አፈላላጊ ቡድን እስካሁን ያስቀመጠው ተጨባጭ ነገር የለም " ብለዋል።

" ጠቅላይ ሚንስትሩ በሰጡት የአመራር አቅጣጫ የገንዘብ ሚንስቴር ፣ የብሄራዊ ባንክና ልሎች ከፍተኛ የፌደራል መንግስት የስራ ሃላፊዎች ያካተተ መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ ቢቋቋምም እስከ አሁን የሚዳሰሰ የሚጨበጥ ለውጥ አልመጣም " ሲሉ ገልጸዋል።

ተወካዮቹ ፥ " ከ7 ወራት በፊት በ2016 ዓ.ም ጠቅላይ ሚንስትሩ ወደ አዲስ አበባ ከጋበዟቸው የንግድ ማህበረሰብ ያካተተ ልኡክ ጋር ባካሄዱት ውይይት ማጠቃለያ በጦርነቱ ጊዜ የተከማቸው የብድር ወለድና ቅጣት ተሰልቶ ፓለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ መፍትሄ እንዲሰጠው አቅጣጫ ቢያስቀምጡም እስከ አሁን ጠብ የሚል መፍትሄ አለመጣም ይህም በጣም አሳዝኖናል " ብለዋል።

አበዳሪ የፋይናንስ ተቋማት የሰጡት የብድር ወለድ ከነቅጣቱ እንዲመለስ የንግድ ማህበረሰቡ ማስጨነቅ እንደጀመሩ በዚሁ ውይይት ወቅት ተነግሯል።

ተግባሩ በጦርነት ምክንያት የደቀቀው የክልሉ ኢኮኖሚያዊ አቅም ይበልጥ ጉልበት የሚያሳጣ መሆኑ በመገንዘብ አገራዊ የፓሊሲና የፓለቲካ መፍትሄ ሊሰጠው ይገባል ተብሏል።

ጉዳዩ ጊዜ የሚሰጥ አይደለምና " አስቸኳይ ትኩረት እና መፍትሄ " እንደሚያሻው አፅንኦት ተሰጥቷል።

የውይይቱ ተሳታፊዎች የፌደራል መንግስት የትግራይ የንግድ ማህበረሰብ የሚታደግ የመፍትሄ እርምጃ እንዲያስቀመጥ ተጠይቋል።

#TikvahEthiopiaMekelleFamily

@tikvahethiopia
#AddisAbaba

ትናንት ምሽት 5 ሰዓት ተኩል ገደማ በአቃቂ ቃሊቲ ክ/ ከተማ ወረዳ 7 ኢንዱስትሪ መንደር እየተባለ በሚጠራው አካባቢ አንድ ግለሰብ በማሽን ተይዞ በአሰቃቂ ሁኔታ ህይወቱ አልፏል።

እንደ አዲስ አበባ እሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን መረጃ ፤ ከሜድሮክ ድርጅቶች በአንዱ ውስጥ ሰራተኛ የሆነው ሟቹ ትናንት ምሽት አሸዋ በሚፈጭ ማሽን ላይ ስራውን እያከወነ በነበረበት ወቅት በማሽኑ ተይዞ ወዲያው ህይወቱ አልፏል።

አስከሬኑን ከማሽኑ ለማላቀቅ አልተቻለም ነበር፡፡

የአደጋ ጊዜ ሰራተኞች አስከሬኑን ከማሽኑ አላቀው ማውጣት የቻሉት ለ2 ሰዓት ከፈጀ ጥረት በኋላ ነው።

የትናንቱ በማሽን ላይ የደረሰው አደጋ ጉዳይ በህግ ተይዟል ተብሏል።

በሌላ በኩል ፤ ትላንት በሸገር ከተማ አሸዋ ሜዳ እየተባለ በሚጠራው አካባቢ ተቆፍሮ ክፍቱን በተተወና ወሀ ባቆረ ጉድጓድ ውስጥ ሁለት ወጣቶች ህይወታቸው አልፏል።

ሟቾቹ ዕድሜያቸዉ 19 እና 23 ነው።

የአደጋ ጊዜ ሰራተኞች አንደኛውን ወጣት አስክሬን አውጥተዉ ለፖሊስ ያስረከቡ ሲሆን እድሜው 19 ዓመት የሆነው ወጣት አስክሬን የአካባቢው ህብረተሰብ አስቀድሞ አውጥተውታል።

ክፍት የተተወው ጉድጓድ ውሃ ያለበት በመሆኑ አንደኛው ግለሰብ ለመታጠብ ብሎ ገብቶ ተንሸራትቶ ወደ ውሃው ውስጥ ይገባል ፤ የዚህን ሰው መግባት የተመለከተው ሌላው ግለሰብ ደግሞ እርሱን ለማውጣት ሲል ወደ ጉድጓዱ በመግባቱ የሁለቱም ህይወት ወዲያው አልፏል፡፡

#ShegerFM102.1

@tikvahethiopia
" ታፍኖ ከተወሰደ ከ5 ቀናት በኋላ ተገድሎ አስክሬኑ ወንዝ ተጥሎ ተገኝቷል " - የትግራይ ነፃነት ፓርቲ

የትግራይ ነፃነት ፓርቲ የአመራር አባሉ ታፍኖ ከተወሰደ በኃላ ተገድሎ አስከሬኑ ወንዝ ተጥሎ እንደተገኘ ገለፀ።  

ፓርቲው ታፍኖ የተወሰደውን የአመራር አባሉን ላለፉት ከ5 ቀናት ሲፈልግ የቆየ ቢሆን ተገድሎ አስክሬኑ ወንዝ ተጥሎ ማግኘቱ አሳውቋል።

የፓርቲው ሊቀ-መንበር ዶ/ር ደጀን መዝገበ " አሰቃቂ ድርጊቱ የተፈፀመው በትግራይ ሰሜናዊ ምዕራብ ዞን አስገደ ወረዳ ነው " ብለዋል።

ተገድሎ የተገኘው የፓርቲው አመራር አባል በወረዳው የፓርቲው አስተባባሪ መሆኑን ገልጸው ፥ " ታፍኖ ከተወሰደ ከ5 ቀናት በኋላ ተገድሎ ሬሳው በወንዝ ተጥሎ ተገኝቷል ይህ ጭካኔ የተሞላበት አረመንያዊ ድርጊት ነው " ሲሉ አውግዘውታል። 

ሊቀ-መንበሩ በዞኑ የሚገኙ አባላቱ " ' ፓርቲው መደገፍ ህወሓት መቃወም አቁሙ አለበለዚያ ትገደላላችሁ ' የሚል ማስፈራርያ ደርሶዋቸዋል " ሲሉ ' ህወሓትን ክሰዋል።

ህወሓት ለቀረበበት ክስ እስካሁን የሰጠው መልስ የለም። 

" ተግባሩን የህወሓት አባላት ነው እየፈፀሙ የሚገኙት " በማለት ያቀረቡትን ክስ ያጠነከሩት የፓርቲው ሊቀመንበር " በ19 የፓርቲው አባላት አፈና ፣ ደብደባና ግድያ ደርሷል " ማለታቸው ቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ ዘግቧል።

#TikvahEthiopiaFamilyMekelle

@tikvahethiopia            
TIKVAH-ETHIOPIA
አንድ ሰው ከኢትዮ ቴሌኮም የገዛውን አክሲዮን ድርሻ ማዘዋወር፤ አትርፎ መሸጥ ፤ እንደ ማሲያዣ መጠቀም ቢፈልግ ይችላል ወይ ? አትዮ ቴሌኮም አሁን የሚጀመረው የአክሲዮን ሺያጭ የመጀመሪያው ምዕራፍ እንደሆነ አስታውቋል። በዚህ ምዕራፍ ዜጎች የአክሲዮን ድርሻ ብቻ መግዛት የሚችሉ ይሆናል። ዜጎች ድርሻቸውን ማዘዋወር ፤ አትርፎ መሸጥ ፤ እንደ ማሲያዣ መጠቀም የሚችሉት ኢትዮ ቴሌኮም ሁለተኛ ምዕራፍ ብሎ…
#ኢትዮቴሌኮም #የሼርሽያጭ

ኢትዮ ቴሌኮም አክሲዮን ማኅበር (Ethio Telecom S.c) 10% በመቶ ድርሻውን መሸጥ የሚያስችለውን ሥርዓት (Mini App) በቴሌብር ሱፐር አፕ መተግበሪያው ላይ አካቷል።

ዜጎች ይህንን ሼር ከመግዛታቸው አስቀድሞ ስለ አጠቃላይ የሼር ሽያጭ የቀረበ ዝርዝር መረጃ (prospectus) አንብበው መስማማታቸውን መግለጽ ይኖርባቸዋል።

ይህ ዶክመንት ምን ይላል ?

ዶክመንቱ ፥ የሼር መጠን ፤ መግዛት ስለሚቻለው የሼር ብዛት፤ ስለ አክሲዮን ማኅበሩ ዳራ፤ የሂሳብ ሪፖርት መረጃዎችን፤ ቀነ ገደቦችን፤ ስጋቶችን፤ ለማመልከት የሚያስፈልጉ ዝርዝር ሂደቶችን፤ የሼር አከፋፈል ሥርዓቶችን በዝርዝር ያስቀመጠ ነው።

ሂደቶቹ ምን ይመስላሉ ?

ዜጎች በ prospectus ዶክመንቱ እንዲሁም ውል እና ሁኔታዎች (Terms and conditions) ከተስማሙ በኃላ መግዛት የሚፈልጉትን የሼር መጠን በመምረጥ ያመለክታሉ።

የመኖሪያ አድራሻ ፣ መታወቂያ ፣ ፎቶ ፣ ስልክ ቁጥር ጨምሮ ዝርዝር መረጃዎችን ከተሞላ በኋላ ሼር ለመግዛት ማመልከት ይቻላል። እነዚህን መረጃዎች ለማስተካከል እና ክፍያ ለመፈጸም 48 ሰዓት ተሰጥቷል።

ሼር ለመግዛት ካመለከቱ በኋላ ኢትዮ ቴሌኮም የክፍያ ሂደቱን እንዲሁም ያስገቡት ዝርዝር መረጃ የማጣራት ሂደት የሚያካሂድ ሲሆን ሂደቱን ካለፉ የተሳካ ማመልከቻ ዝርዝር ውስጥ ይካተታሉ። ሂደቱን ካላለፉ መሰረዞን የሚገልጽ መልዕክት ይደርሶታል።

(የአገልግሎት ጊዜው ያላለፈበት መታወቂያ እንዲሁም ፎቶ ሲያነሱት በሚታይ መልኩ እንዲሆን ይመከራል)

ኢትዮ ቴሌኮም አክሲዮን ማኅበር ካቀረበው በላይ ግዢ ከተፈጸመ ምን ይደረጋል ?

መሸጥ ከሚታሰበው በታች ሼር ከተሸጠ ሼር ለመግዛት ያመለከቱ በሙሉ የጠየቁትን የሼር መጠን የሚያገኙ ይሆናል።

ሆኖም የሼር ግዢ ጥያቄው ከተቀመጠው በላይ ከሆነ በprospectus ዶክመንቱ መሰረት የአክሲዮን ድልድል (Allotment of Shares) ይካሄዳል።

ይህም ሼር መሸጥ ከሚያበቃበት ታኅሣሥ 25 ጀምሮ የሚደረግ ይሆናል።

ይህ ድልድል በተመጣጣኝ ድርሻ ስሌት (Pro-rata Algorithm) የሚካሄድ ሲሆን ሙሉ ለሙሉ በዲጂታል የሚከናወን ነው። ይህም እያንዳንዱ አመልካች ተመጣጣኝ ድርሻ እንዲደርሰው የሚያስችል ነው።

ለምሳሌ ፦  አንድ ሰው 100 ሼር ግዢ ለመፈጸም ጥያቄ አቀረበ። የተመጣጣኝ ድርሻ ስሌቱ (Pro-rata Algorithm) ሁሉም 70% እንዲደርሳቸው ቢወስን 100 ሼር ለመግዛት ጥያቄ ያቀረበው ሰው የሚደርሰው 70 ሼር ይሆናል ማለት ነው።

በጊዜ ሰሌዳው መሰረት ድልድሉ ጥር 23/2017 ዓ.ም በይፋ ለህዝብ በይፋ ይገለጻል።

ተመላሽ ክፍያ በተመለከተ ?

አመልካቾች ድልድል ከተደረገ በኋላ የደረሳቸው የሼር መጠን ያክል ክፍያ ተቆርጦለት ቀሪው ገንዘብ ከአገልግሎት ክፍያው ጋር ተደምሮ ተመላሽ የሚደረግ ይሆናል።

ገንዘቡ ድልድሉ ይፋ በሆነ በ10 የስራ ቀናት ውስጥ ተመላሽ ይደረጋል። ዜጎች ሼር ለመግዛት ካመለከቱ እና ክፍያ ከፈጸሙ በኋላ ድልድሉን አለመቀበል አይችሉም።

የኢትዮ ቴሌኮም አክሲዮን ማኅበር 10% ድርሻ ለኢትዮጵያውያን ብቻ የቀረበ ሲሆን በኢትዮጵያ ውስጥ ብቻ ሽያጭ የሚደረግበት ይሆናል። በተጨማሪም ዜጎች ለራሳቸው እና ህጋዊ ውክልና ላላቸው ዜጋ ግዢውን መፈጸም ይችላሉ።

ከዚህ የሼር ሽያጭ ኢትዮ ቴሌኮም 30 ቢሊዮን ብር ገቢ የሚያገኝ ሲሆን። ከአገልግሎት ክፍያ ደግሞ 450 ሚሊዮን ብር ተጨማሪ ገቢ ያገኛል። መንግሥት ሙሉ ለሙሉ የቀረበው ሼር ተሸጦ ካለቀ ከተጨማሪ እሴት ታክስ (VAT) ብቻ 67.5 ሚሊዮን ብር ያገኛል።

አክሲዮን ማኅበሩ፥ በኢትዮጵያ ካፒታል ማርኬት ገበያ ዝርዝር ውስጥ ለመካተት (Listing) የሚያስችለውን ዝግጅት የሼር ሽያጩ ካበቃ በ12 ወራት ውስጥ ለማጠናቀቅ ማቀዱን በዶክመንቱ ተገልጿል።

(ቲክቫህ ኢትዮጵያ)

@tikvahethiopia