TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Mekelle
የኮሚሽነር ግርማይ ከበደ (ግርማይ ማንጁስ) ስርዓተ ቀብር ተፈጸመ።
የቀድሞ የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ወንጀል መከላከል ዘርፍ ኃላፊ እና የትግራይ ክልል ፖሊስ ኮሚሽነር ኮሚሽነር ግርማይ ከበደ (ግርማይ ማንጁስ) ስርዓተ ቀብር ዛሬ በመቐለ ተፈጽሟል።
የቀብር ስነስርዓቱ በመቐለ ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስትያን የአርበኞች የመቃብር ቦታ ነው የተፈጸመው።
በቀብር ስነስርዓቱ የሟች ቤተሰቦች፣ የመቐለ ነዋሪዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ የፌዴራል ፖሊስ፣ የክልሉ ጊዚያዊ አስተዳደር አመራሮች ፣ የህወሓትን ጨምሮ የተለያዩ የፓለቲካ ፓርቲ አመራሮች እንዲሁም የትግል ጓዶቻቸው ተገኝተው ነበር።
የ3 ሴት ልጆች አባት የሆኑት ኮሚሽነር ግርማይ ከበደ (ግርማይ ማንጁስ) ባደረባቸዉ ህመም ምክንያት ህክምናቸውን ሲከታተሉ ቆይተው መስከረም 24 / 2017 ዓ.ም በተወለዱ በ60 ዓመታቸው ነው ከዚህ ዓለም በሞት የተለዩት።
Photo Credit - Tigrai Communication & Demtsi Woyane
@tikvahethiopia
የኮሚሽነር ግርማይ ከበደ (ግርማይ ማንጁስ) ስርዓተ ቀብር ተፈጸመ።
የቀድሞ የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ወንጀል መከላከል ዘርፍ ኃላፊ እና የትግራይ ክልል ፖሊስ ኮሚሽነር ኮሚሽነር ግርማይ ከበደ (ግርማይ ማንጁስ) ስርዓተ ቀብር ዛሬ በመቐለ ተፈጽሟል።
የቀብር ስነስርዓቱ በመቐለ ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስትያን የአርበኞች የመቃብር ቦታ ነው የተፈጸመው።
በቀብር ስነስርዓቱ የሟች ቤተሰቦች፣ የመቐለ ነዋሪዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ የፌዴራል ፖሊስ፣ የክልሉ ጊዚያዊ አስተዳደር አመራሮች ፣ የህወሓትን ጨምሮ የተለያዩ የፓለቲካ ፓርቲ አመራሮች እንዲሁም የትግል ጓዶቻቸው ተገኝተው ነበር።
የ3 ሴት ልጆች አባት የሆኑት ኮሚሽነር ግርማይ ከበደ (ግርማይ ማንጁስ) ባደረባቸዉ ህመም ምክንያት ህክምናቸውን ሲከታተሉ ቆይተው መስከረም 24 / 2017 ዓ.ም በተወለዱ በ60 ዓመታቸው ነው ከዚህ ዓለም በሞት የተለዩት።
Photo Credit - Tigrai Communication & Demtsi Woyane
@tikvahethiopia
#AddisAbaba
በአዲስ አበባ ከተማ የተለያዩ አካባቢዎች የመሬት መንቀጥቀጥ ንዝረት እንደነበር ነዋሪዎች ገልጸዋል።
ይህ የሆነው አሁን ከመሸ ከ2:00 በኃላ ነው።
በአንዳንድ ቦታዎችም ህንጻዎችን አንቀጥቅጧል።
የጋራ መኖሪያ ቤቶች የሚኖሩ ነዋሪዎች በስጋት ወደ መሬት ወርደው ተሰብስበዋል።
ተጨማሪ መረጃዎች ከባለሙያዎች ለማግኘት ጥረት እያደረግን ነው።
@tikvahethiopia
በአዲስ አበባ ከተማ የተለያዩ አካባቢዎች የመሬት መንቀጥቀጥ ንዝረት እንደነበር ነዋሪዎች ገልጸዋል።
ይህ የሆነው አሁን ከመሸ ከ2:00 በኃላ ነው።
በአንዳንድ ቦታዎችም ህንጻዎችን አንቀጥቅጧል።
የጋራ መኖሪያ ቤቶች የሚኖሩ ነዋሪዎች በስጋት ወደ መሬት ወርደው ተሰብስበዋል።
ተጨማሪ መረጃዎች ከባለሙያዎች ለማግኘት ጥረት እያደረግን ነው።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#AddisAbaba በአዲስ አበባ ከተማ የተለያዩ አካባቢዎች የመሬት መንቀጥቀጥ ንዝረት እንደነበር ነዋሪዎች ገልጸዋል። ይህ የሆነው አሁን ከመሸ ከ2:00 በኃላ ነው። በአንዳንድ ቦታዎችም ህንጻዎችን አንቀጥቅጧል። የጋራ መኖሪያ ቤቶች የሚኖሩ ነዋሪዎች በስጋት ወደ መሬት ወርደው ተሰብስበዋል። ተጨማሪ መረጃዎች ከባለሙያዎች ለማግኘት ጥረት እያደረግን ነው። @tikvahethiopia
#Update : በአዲስ አበባ ከተማ በበርካታ ቦታዎች ላይ የመሬት መንቀጥቀጥ ንዝረት ተሰምቷል።
ከምሽት 2 ሰዓት በኃላ በርካታ ቦታዎች ላይ የመሬት መንቀጥቀጥ ንዝረት ነበር።
ህፃዎች ላይ የነበሩ ሰዎችም በደንብ ንዝረቱ የተሰማቸው ሲሆን በተለይ በጋራ መኖሪያ ቤቶች ያሉ ነዋሪዎች ከስጋት አንጻር ወደ መሬት ወርደው ተሰባስበው ነው የሚገኙት።
ከአዲስ አበባ ውጭም በሌሎች አንዳንድ ከተማዎች / ቦታዎች መሰል ሁኔታ እንደነበር ከቤተሰቦቻችን በሚላኩ መልዕክቶች ተረድተናል።
በጉዳዩ ላይ የዘርፉ ባለሙያዎች የሚሰጡትን አስተያየት እናቀርባለን።
@tikvahethiopia
ከምሽት 2 ሰዓት በኃላ በርካታ ቦታዎች ላይ የመሬት መንቀጥቀጥ ንዝረት ነበር።
ህፃዎች ላይ የነበሩ ሰዎችም በደንብ ንዝረቱ የተሰማቸው ሲሆን በተለይ በጋራ መኖሪያ ቤቶች ያሉ ነዋሪዎች ከስጋት አንጻር ወደ መሬት ወርደው ተሰባስበው ነው የሚገኙት።
ከአዲስ አበባ ውጭም በሌሎች አንዳንድ ከተማዎች / ቦታዎች መሰል ሁኔታ እንደነበር ከቤተሰቦቻችን በሚላኩ መልዕክቶች ተረድተናል።
በጉዳዩ ላይ የዘርፉ ባለሙያዎች የሚሰጡትን አስተያየት እናቀርባለን።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update : በአዲስ አበባ ከተማ በበርካታ ቦታዎች ላይ የመሬት መንቀጥቀጥ ንዝረት ተሰምቷል። ከምሽት 2 ሰዓት በኃላ በርካታ ቦታዎች ላይ የመሬት መንቀጥቀጥ ንዝረት ነበር። ህፃዎች ላይ የነበሩ ሰዎችም በደንብ ንዝረቱ የተሰማቸው ሲሆን በተለይ በጋራ መኖሪያ ቤቶች ያሉ ነዋሪዎች ከስጋት አንጻር ወደ መሬት ወርደው ተሰባስበው ነው የሚገኙት። ከአዲስ አበባ ውጭም በሌሎች አንዳንድ ከተማዎች / ቦታዎች…
#Update
" እዚህ አዲስ አበባ የተከሰተ የመሬት መንቀጥቀጥ የለም፤ ሞገዱ በመሬት ውስጥ ተጉዞ መጥቶ ነው ፤ አዋሽ አካባቢ ነው የተከሰተው በሬክተር ስኬል 4.9 ነው " - ዶክተር ኤልያስ ሌዊ
በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጂኦ ፊዚክስና ስፔስ ሳይንስ ዳይሬክተር ዶክተር ኤልያስ ሌዊ ለብሔራዊ ቴሌቪዥን በሰጡት ቃል ምን አሉ ?
" እስካሁን ባለው መረጃ እዚህ የመሬት መንቀጥቀጡ እዚህ አዲስ አባባ የተከሰተ ሳይሆን አዋሽ አካባቢ የተከሰተ ነው።
ግን በመሬት ውስጥ አልፎ እዚህ አዲስ አበባ ውስጥ ልዩ ልዩ ቦታዎች ተሰምቷል።
ይሄን ግልጽ ማድረግ እንፈልጋለን እዚህ አዲስ አበባ የተከሰተ አይደለም። ግን በመሬት ውስጥ ተጉዞ መጥቶ እዚህ ያሉ ህንጻዎችን አንቀጥቅጧል።
በሪክተር ስኬል 4.9 ነው ያገኘነው። ይሄም ከፈንታሌ የሚባል ተራራ አለ ወደ መተሃራ አካባቢ ነው የተከሰተው። እስካሁን ያለው መረጃ ይሄ ነው።
ሰውም ይረጋጋ እዚህ አዲስ አበባ የተከሰተ የመሬት መንቀጥቀጥ ሳይሆን ከሩቅ የተከሰተ የመሬት መንቀጥቀጥ ሞገዱ በመሬት ውስጥ ተጉዞ መጥቶ በተለይ እዚህ ሰሜን እና ሰሜን ምስራቅ ያሉ የአዲስ አበባ ነዋሪዎች በጣም ተረብሸዋል። ልክ ነው ከዛም ሊሰማ ይችላል።
በሬክተር ስኬል 4.9 ነው ይሄ ነው ያለው መረጃ።
ተጨማሪ መረጃ እንዳገኘን በግልጽ እንነግራለን። " ብለዋል።
ዛሬ ምሽት በአዲስ አበባ በነበረው የመሬት መንቀጥቀጥ ንዝረት ምክንያት በተለይ የጋራ መኖሪያ ቤቶች የሚኖሩ ነዋሪዎች ህንጻቸው ሲንቀጠቀጥ እንደነበር ገልጸውልናል። በዚህ ምክንያት ከቤታቸው ወጥተው መሬት ላይ ወርደው ተሰባስበዋል።
#Ethiopia
@tikvahethiopia
" እዚህ አዲስ አበባ የተከሰተ የመሬት መንቀጥቀጥ የለም፤ ሞገዱ በመሬት ውስጥ ተጉዞ መጥቶ ነው ፤ አዋሽ አካባቢ ነው የተከሰተው በሬክተር ስኬል 4.9 ነው " - ዶክተር ኤልያስ ሌዊ
በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጂኦ ፊዚክስና ስፔስ ሳይንስ ዳይሬክተር ዶክተር ኤልያስ ሌዊ ለብሔራዊ ቴሌቪዥን በሰጡት ቃል ምን አሉ ?
" እስካሁን ባለው መረጃ እዚህ የመሬት መንቀጥቀጡ እዚህ አዲስ አባባ የተከሰተ ሳይሆን አዋሽ አካባቢ የተከሰተ ነው።
ግን በመሬት ውስጥ አልፎ እዚህ አዲስ አበባ ውስጥ ልዩ ልዩ ቦታዎች ተሰምቷል።
ይሄን ግልጽ ማድረግ እንፈልጋለን እዚህ አዲስ አበባ የተከሰተ አይደለም። ግን በመሬት ውስጥ ተጉዞ መጥቶ እዚህ ያሉ ህንጻዎችን አንቀጥቅጧል።
በሪክተር ስኬል 4.9 ነው ያገኘነው። ይሄም ከፈንታሌ የሚባል ተራራ አለ ወደ መተሃራ አካባቢ ነው የተከሰተው። እስካሁን ያለው መረጃ ይሄ ነው።
ሰውም ይረጋጋ እዚህ አዲስ አበባ የተከሰተ የመሬት መንቀጥቀጥ ሳይሆን ከሩቅ የተከሰተ የመሬት መንቀጥቀጥ ሞገዱ በመሬት ውስጥ ተጉዞ መጥቶ በተለይ እዚህ ሰሜን እና ሰሜን ምስራቅ ያሉ የአዲስ አበባ ነዋሪዎች በጣም ተረብሸዋል። ልክ ነው ከዛም ሊሰማ ይችላል።
በሬክተር ስኬል 4.9 ነው ይሄ ነው ያለው መረጃ።
ተጨማሪ መረጃ እንዳገኘን በግልጽ እንነግራለን። " ብለዋል።
ዛሬ ምሽት በአዲስ አበባ በነበረው የመሬት መንቀጥቀጥ ንዝረት ምክንያት በተለይ የጋራ መኖሪያ ቤቶች የሚኖሩ ነዋሪዎች ህንጻቸው ሲንቀጠቀጥ እንደነበር ገልጸውልናል። በዚህ ምክንያት ከቤታቸው ወጥተው መሬት ላይ ወርደው ተሰባስበዋል።
#Ethiopia
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update " እዚህ አዲስ አበባ የተከሰተ የመሬት መንቀጥቀጥ የለም፤ ሞገዱ በመሬት ውስጥ ተጉዞ መጥቶ ነው ፤ አዋሽ አካባቢ ነው የተከሰተው በሬክተር ስኬል 4.9 ነው " - ዶክተር ኤልያስ ሌዊ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጂኦ ፊዚክስና ስፔስ ሳይንስ ዳይሬክተር ዶክተር ኤልያስ ሌዊ ለብሔራዊ ቴሌቪዥን በሰጡት ቃል ምን አሉ ? " እስካሁን ባለው መረጃ እዚህ የመሬት መንቀጥቀጡ እዚህ አዲስ አባባ የተከሰተ…
#Attention🚨
በአዋሽ ፣ መተሀራ ፈንታሌ ተራራ አካባቢ የመሬት መንቀጥቀጥ መድረሱን የመንግሥት ኮሚኒኬሽን አሳውቋል።
" በሬክተር ስኬል 4.9 ነው። 150 ኪሎሜትር አካባቢ ርቀት ላይ የተፈፀመ ነው። ንዝረቱ አዲስ አበባ ድረስ ተሰምቷል " ብሏል።
" በስምጥ ሸለቆች ውስጥ ንዝራቱ ከማሰማት በሻገር የመሬት መንቀጥቀጥ ከፈንታሌ ተራሮች ውጭ የደረሰ ስለመኖሩ አልተረጋገጠም " ሲል አክሏል።
" በደሴ መስመር እስከ ኮምቦልቻ የተየውም ንዝራቱ ነው። ክስተቱ ከሰሞኑ ጀምሮ በፈንታሌ ተራራ እና አዋሽ አካባቢዎች የነበረ ስሜት ነው " ብሏል።
@tikvahethiopia
በአዋሽ ፣ መተሀራ ፈንታሌ ተራራ አካባቢ የመሬት መንቀጥቀጥ መድረሱን የመንግሥት ኮሚኒኬሽን አሳውቋል።
" በሬክተር ስኬል 4.9 ነው። 150 ኪሎሜትር አካባቢ ርቀት ላይ የተፈፀመ ነው። ንዝረቱ አዲስ አበባ ድረስ ተሰምቷል " ብሏል።
" በስምጥ ሸለቆች ውስጥ ንዝራቱ ከማሰማት በሻገር የመሬት መንቀጥቀጥ ከፈንታሌ ተራሮች ውጭ የደረሰ ስለመኖሩ አልተረጋገጠም " ሲል አክሏል።
" በደሴ መስመር እስከ ኮምቦልቻ የተየውም ንዝራቱ ነው። ክስተቱ ከሰሞኑ ጀምሮ በፈንታሌ ተራራ እና አዋሽ አካባቢዎች የነበረ ስሜት ነው " ብሏል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update " እዚህ አዲስ አበባ የተከሰተ የመሬት መንቀጥቀጥ የለም፤ ሞገዱ በመሬት ውስጥ ተጉዞ መጥቶ ነው ፤ አዋሽ አካባቢ ነው የተከሰተው በሬክተር ስኬል 4.9 ነው " - ዶክተር ኤልያስ ሌዊ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጂኦ ፊዚክስና ስፔስ ሳይንስ ዳይሬክተር ዶክተር ኤልያስ ሌዊ ለብሔራዊ ቴሌቪዥን በሰጡት ቃል ምን አሉ ? " እስካሁን ባለው መረጃ እዚህ የመሬት መንቀጥቀጡ እዚህ አዲስ አባባ የተከሰተ…
#ATTENTION🚨
ድጋሚ ሊከሰት ይችላል ? መደረግ ያለበት ጥንቃቄስ ምንድነው ?
በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጂኦ ፊዚክስና ስፔስ ሳይንስ ዳይሬክተር ዶክተር ኤልያስ ሌዊ ምን አሉ ?
" ድጋሚ ሊከሰት ይችላል ወይ ? የሚባለው ሰሞኑን በሙሉ ይሄን አይነት ንዝረቶች ነበሩ።
መሬት መንቀጥቀጥ መተንበይ የሚባል ነገር የለም ፤ የት አካባቢ እንደሆነ እንጂ መቼ ይከሰታል የሚባለውን መተንበይ አይቻልም።
ስለዚህ ሊከሰት ይችላል ሊመጣ ይችላል። ይሄ ሁል ጊዜ በተለይ አዲስ አበባ የምንኖር ሰዎች ነቅተን የምንጠብቀው ነገር መሆን አለበት።
ስምጥ ሸለቆና የስምጥ ሸለቆ አካባቢ የሚኖሩ ሰዎች ሁሉ ነቅተን የምንጠብቀው ነገር ነው መሆን ያለበት።
ለጊዜው መናገር የምችለው ከበድ ያለ ነገር ከመጣ አይመጣም ብለን ነው የምንገምተው ከመጣ ግን ምን መደረግ ስለለበት ጥንቃቄ ነው።
➡️ የቤት ቋሚዎች በተለይ ኮንዶሚኒየም ህንጻ ላይ ያሉ ሰዎች ኮለኖች አካባቢ መጠጋት ለምን መውረድ ሊከብድ ይችላል ቁልፍ ማክፈትም ሊከብድ ይችላል። ስለዚህ ኮለኖች አካባቢ መጠጋት።
➡️ ከተቻለ ጠረጴዛ ስር መግባት።
➡️ ሊፍት አትጠቀሙ። ማንም ሰው በሊፍት ለመውረድ እንዳይሞክር። ያን እንዳትጠቀሙ።
ይሄን ይሄን ጥንቃቄ ማደርግ ያስፈልጋል። ነገር ግን አሁን ባለው እዚህ ደረጃ የሚያደርስ ከባድ ነገር አለ ብለን አንገምትም። "
#Ethiopia #AddisAbaba
@tikvahethiopia
ድጋሚ ሊከሰት ይችላል ? መደረግ ያለበት ጥንቃቄስ ምንድነው ?
በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጂኦ ፊዚክስና ስፔስ ሳይንስ ዳይሬክተር ዶክተር ኤልያስ ሌዊ ምን አሉ ?
" ድጋሚ ሊከሰት ይችላል ወይ ? የሚባለው ሰሞኑን በሙሉ ይሄን አይነት ንዝረቶች ነበሩ።
መሬት መንቀጥቀጥ መተንበይ የሚባል ነገር የለም ፤ የት አካባቢ እንደሆነ እንጂ መቼ ይከሰታል የሚባለውን መተንበይ አይቻልም።
ስለዚህ ሊከሰት ይችላል ሊመጣ ይችላል። ይሄ ሁል ጊዜ በተለይ አዲስ አበባ የምንኖር ሰዎች ነቅተን የምንጠብቀው ነገር መሆን አለበት።
ስምጥ ሸለቆና የስምጥ ሸለቆ አካባቢ የሚኖሩ ሰዎች ሁሉ ነቅተን የምንጠብቀው ነገር ነው መሆን ያለበት።
ለጊዜው መናገር የምችለው ከበድ ያለ ነገር ከመጣ አይመጣም ብለን ነው የምንገምተው ከመጣ ግን ምን መደረግ ስለለበት ጥንቃቄ ነው።
➡️ የቤት ቋሚዎች በተለይ ኮንዶሚኒየም ህንጻ ላይ ያሉ ሰዎች ኮለኖች አካባቢ መጠጋት ለምን መውረድ ሊከብድ ይችላል ቁልፍ ማክፈትም ሊከብድ ይችላል። ስለዚህ ኮለኖች አካባቢ መጠጋት።
➡️ ከተቻለ ጠረጴዛ ስር መግባት።
➡️ ሊፍት አትጠቀሙ። ማንም ሰው በሊፍት ለመውረድ እንዳይሞክር። ያን እንዳትጠቀሙ።
ይሄን ይሄን ጥንቃቄ ማደርግ ያስፈልጋል። ነገር ግን አሁን ባለው እዚህ ደረጃ የሚያደርስ ከባድ ነገር አለ ብለን አንገምትም። "
#Ethiopia #AddisAbaba
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#ለጥንቃቄ🚨
የመሬት መንቀጥቀጥ ሲከሰት ምን ማድረግ አለብን ?
➡️ ከቤት ውጭ ከሆኑ ፦ ከዛፎች ፣ ከሕንፃዎች ፣ ከኤሌትሪክ ምሶሶዎች እና ሌሎች ወድቀው ጉዳት ሊያደርሱ ከሚችሉ ነገሮች መራቅ እና ገላጣ ሜዳ አካባቢ መቆየት።
➡️ በቤት ውስጥ ከሆኑ ፦ በበር መቃኖች ፣ ኮርነሮች እና ኮሪደሮች ተጠግቶ ማሳለፍ። ከእሳት ምድጃዎች፣ ከተሰቀሉ ፍሬሞች እና የግድግዳ ጌጦች፣ ከመጽሐፍ መደርደሪያዎች እንዲሁም ከመስኮት አካባቢ መራቅ። የጋዝ ምድጃዎችን በተቻለ ፍጥነት ማጥፋት ካልሆነም ከአካባቢው መራቅ።
➡️ በትልልቅ ሕንጻዎች ውስጥ ከሆኑ ፦ ከሕንጻዎቹ ለመውጣት አለመሞከር ፣ አሳንሰር (ሊፍት) በፍፁም አለመጠቀም። ከደረጃዎች አካባቢ መራቅ።
➡️ መኪና እያሽከረከሩ ከሆኑ ፦ የኤሌትሪክ መተላለፊያ ምሶሶዎችን፣ ዛፎችና ሽቦዎች አካባቢ አለመቆም፣ የኤሌትሪክ መስመር ምሶሶዎች እና ሽቦዎች ተሽርካሪው ላይ ከወደቁ ከመኪናው ለመውጣት አለመሞከር፣ በተቻለ ፍጥነት ገላጣ ወደሆነ አካባቢ መኪናን ማቆም።
#Ethiopia #AddisAbaba #የእሳትናአደጋስራአመራር
@tikvahethiopia
የመሬት መንቀጥቀጥ ሲከሰት ምን ማድረግ አለብን ?
➡️ ከቤት ውጭ ከሆኑ ፦ ከዛፎች ፣ ከሕንፃዎች ፣ ከኤሌትሪክ ምሶሶዎች እና ሌሎች ወድቀው ጉዳት ሊያደርሱ ከሚችሉ ነገሮች መራቅ እና ገላጣ ሜዳ አካባቢ መቆየት።
➡️ በቤት ውስጥ ከሆኑ ፦ በበር መቃኖች ፣ ኮርነሮች እና ኮሪደሮች ተጠግቶ ማሳለፍ። ከእሳት ምድጃዎች፣ ከተሰቀሉ ፍሬሞች እና የግድግዳ ጌጦች፣ ከመጽሐፍ መደርደሪያዎች እንዲሁም ከመስኮት አካባቢ መራቅ። የጋዝ ምድጃዎችን በተቻለ ፍጥነት ማጥፋት ካልሆነም ከአካባቢው መራቅ።
➡️ በትልልቅ ሕንጻዎች ውስጥ ከሆኑ ፦ ከሕንጻዎቹ ለመውጣት አለመሞከር ፣ አሳንሰር (ሊፍት) በፍፁም አለመጠቀም። ከደረጃዎች አካባቢ መራቅ።
➡️ መኪና እያሽከረከሩ ከሆኑ ፦ የኤሌትሪክ መተላለፊያ ምሶሶዎችን፣ ዛፎችና ሽቦዎች አካባቢ አለመቆም፣ የኤሌትሪክ መስመር ምሶሶዎች እና ሽቦዎች ተሽርካሪው ላይ ከወደቁ ከመኪናው ለመውጣት አለመሞከር፣ በተቻለ ፍጥነት ገላጣ ወደሆነ አካባቢ መኪናን ማቆም።
#Ethiopia #AddisAbaba #የእሳትናአደጋስራአመራር
@tikvahethiopia
#MPESASafaricom
💫ከዳር እስከ ዳር በፈጣኑ የሳፋሪኮም ኢንተርኔት አሁንም አንድ ወደፊት! ባለው የሳፋሪኮም ኔትወርክ አሁንም አንድ ወደፊት እያልን እንገናኝ!✨ የተመቸንን ሼር እናድርግ!👍ከወደድነው ❤️ጋር እንደልብ እንገናኝ!
አስተማማኙን ኔትወርክ ዛሬውኑ እንቀላቀል!
የቴሌግራም ቦታችንን https://t.iss.one/official_safaricomet_bot በመጠቀም የአየር ሰዓት ወይንም ልዩ ልዩ ጥቅሎችን እንግዛ!
#SafaricomEthiopia #1Wedefit
#Furtheraheadtogether
💫ከዳር እስከ ዳር በፈጣኑ የሳፋሪኮም ኢንተርኔት አሁንም አንድ ወደፊት! ባለው የሳፋሪኮም ኔትወርክ አሁንም አንድ ወደፊት እያልን እንገናኝ!✨ የተመቸንን ሼር እናድርግ!👍ከወደድነው ❤️ጋር እንደልብ እንገናኝ!
አስተማማኙን ኔትወርክ ዛሬውኑ እንቀላቀል!
የቴሌግራም ቦታችንን https://t.iss.one/official_safaricomet_bot በመጠቀም የአየር ሰዓት ወይንም ልዩ ልዩ ጥቅሎችን እንግዛ!
#SafaricomEthiopia #1Wedefit
#Furtheraheadtogether
ፎቶ ፦ የአልነጃሺ መስጂድ መልሶ የመጠገን ስራ በመከናወን ላይ እንደሆነ ተገልጿል።
ከትግራይ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ በተገኘው መረጃ ፥ በትግራይ ጦርነት ከባድ ጉዳት ከደረሰባቸው ቅርሶች አንዱ የሆነው ቅዱሱ መስጂድ አልነጃሺን መልሶ የመጠገን እና የማልማት ስራ ከያዝነው ወር መጀመሪያ ጀምሮ እየተካሄደ ይገኛል።
ጥገናው የመስጂዱን ሃይማኖታዊና ታሪካዊ ይዘት በጠበቀ መልኩ በመከናወን ላይ ነው ተብሏል።
በሚቀጥሉት 8 ወራት ጥገናው ተጠናቅቆ ክፍት እንደሚደረግ ተመላክቷል።
የትግራይ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ የአልነጃሺ ቅዱስ መስጂድን መልሶ ለመጠገን ከቱርክ ልማት ኤጀንሲ (ቲካ) ጋር መፈራረሙ ቢሮው አስታውሷል።
@tikvahethiopia
ከትግራይ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ በተገኘው መረጃ ፥ በትግራይ ጦርነት ከባድ ጉዳት ከደረሰባቸው ቅርሶች አንዱ የሆነው ቅዱሱ መስጂድ አልነጃሺን መልሶ የመጠገን እና የማልማት ስራ ከያዝነው ወር መጀመሪያ ጀምሮ እየተካሄደ ይገኛል።
ጥገናው የመስጂዱን ሃይማኖታዊና ታሪካዊ ይዘት በጠበቀ መልኩ በመከናወን ላይ ነው ተብሏል።
በሚቀጥሉት 8 ወራት ጥገናው ተጠናቅቆ ክፍት እንደሚደረግ ተመላክቷል።
የትግራይ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ የአልነጃሺ ቅዱስ መስጂድን መልሶ ለመጠገን ከቱርክ ልማት ኤጀንሲ (ቲካ) ጋር መፈራረሙ ቢሮው አስታውሷል።
@tikvahethiopia