TIKVAH-ETHIOPIA
" ለአንድ ዓመት ሞከርኩት " ዛሬ በይፋዊ የፕሬዜዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ የX ገጽ ላይ የወጣው ፅሁፍ ብዙዎችን እያነጋገረ ነው። ፅሁፉ " እነ ጥላሁን ገሠሠ : ቴዲ አፍሮ : አሊ ቢራ : ማህሙድ አህመድ ... ድንቅ ድምጻውያን መካከል ናቸው " ይላል። ቀጥል አድርጎ ፥ " ' የሰው ልጅ ሆዱ ሲከፋው ጊዜም እንደ ሰው ሲገፋው : መሄጃ መውጫ ሲጠፋው ዝምታ ብቻ ነው ተስፋው ' ማህሙድ ' ዝምታ ነው መልሴ'…
#ኢትዮጵያ
ዛሬ በኢትዮጵያ የማህበራዊ ትስስር ገጾች ትልቅ መነጋገሪያ የሆነው በፕሬዜዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ X ኦፊሻል ገጽ ላይ የሰፈረው ፅሁፍ ነው።
ፅሁፉ ላይ የማህሙድን ዘፈን ' ዝምታ ነው መልሴ 'ን በማንሳት " የሰው ልጅ ሆዱ ሲከፋው ጊዜም እንደ ሰው ሲገፋው: መሄጃ መውጫ ሲጠፋው ዝምታ ብቻ ነው ተስፋው " የሚለው ግጥም ተጋርቷል። መጨረሻ ላይ " ለአንድ አመት ሞከርኩ " የሚልም ሰፍሯል።
ፅሁፉ ስለምን ጉዳይ እንደሆነ ፤ ለምንስ ይህንን ግጥም ነጥሎ እንደተጻፈ በግልጽ የሚያብራራው ነገር የለም።
ያም ሆኖ ግን ፅሁፉን ላይ በርካቶች የየራሳቸውን አስተያየት እየሰጡ ይገኛሉ።
አንዳንዶች ፤ " አሁን ባለው ስርዓት በከፍተኛ ጫና ውስጥ ወድቀው ነው እየሰሩ ያሉት ፤ በተለያዩ ጉዳዮች አለመግባባት ውስጥም እንደነበሩ ብዙ ጊዜ በሚዲያ ይሰማ ነበር ፤ ለመናገር እንኳን እድል የላቸውም ፤ ባገኙት አጋጣሚ ግን በገደምዳሜው ስሜታቸውን ስለ ሀገራቸው ይናገሩ ነበር ፤ አሁንም ቦታውን ሲለቁ ስለዚህ ስርዓት ብዙ የሚናገሩት ይኖር ይሆናል " የሚል አስተያየት ሰጥተዋል።
አንዳንዶች፤ " በዚህ ልክ ትልቅ የስልጣን እርከን ይዘው ህዝብን ግራ የሚያጋባ ድፍንፍን ያለ ፅሁፍ በገጻቸው መጋራቱ ሳያንስ እውነትም እሳቸው መሆናቸውን በግልጽ አለማብራራታቸው ትክክል አይደለም ፤ ችግር ካለም እውነታውን ለህዝብ ማሳወቅ አለባቸው እንዲህ የዘፈን ግጥም ከሚያስቀምጡ " ብለዋል።
ሌሎች አስተያየት ሰጪዎች ደግሞ " የ6 ዓመት የስልጣን ዘመናቸው ሲያበቃ ይህን አይነት ነገር በገጻቸው መፃፋቸው የህዝብ ተቀባይነት ለማግኘት ነው እስከዛሬ በሀገሪቱ ብዙ ነገር ብዙ ግፍ ሲፈጠር ባላየ ሲያልፉ ነበር ፤ አንዳንዱን ደግሞ እየመረጡ ሲናገሩ ነበር ፤ ለምን አሁን ? በዚህ ስልጣን እንደማይቀጥሉ ስለሚያውቁ ነው ፤ ስልጣንም መልቀቅ ከነበረባቸው ቀድሞ ተናግሮ እንጂ አሁን ላይ ይህን አጀንዳ ለህዝብ መስጠት ትክክል አይደለም ፤ ጊዜያቸው አብቅቷል ይሰናበታሉ ፤ እሱንም ስለሚያውቁ ነው " ሲሉ ፅፈዋል።
በኢትዮጵያ የፕሬዜዳንት ስልጣን ዘመን 6 ዓመት ሲሆን ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ወደ ስልጣን የመጡት ጥቅምት 15 ቀን 2011 ዓ/ም ላይ ነበር።
ሌሎች ደግሞ " እንዲያው በደፈናው ድምዳሜ ላይ ከመድረስ የእሳቸውን ሙሉ ሀሳብ በትዕግስት ጠብቆ መስማት ይገባል " ብለዋል።
ከዚህ ባለፈ ግን ለመሆኑ ኢትዮጵያ ውስጥ የፕሬዝዳንትነት የስልጣን ድርሻው ምንድነው ? ፕሬዝዳንት የሚኮነው እንዴት ነው ? ምን ምን ይሰራል በዝርዝር ? ሲሉ የጠየቁ አሉ።
ለዚህ ምላሽ ይሆን ዘንድ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ህገ መንግስቱ ስለ ፕሬዜዳንቱ የሚለውን ከዚህ በታች አቅርቧል።
የኢፌዲሪ ህገ መንግስት ስለ ሪፐብሊኩ ፕሬዝዳንት ስልጣንና ተግባር ምን ይላል ?
(የኢፌዴሪ ህገ መንግስት)
ምዕራፍ ሰባት
ስለ ሪፐብሊኩ ኘሬዚዳንት
አንቀጽ 69
ስለ ኘሬዚዳንቱ
ኘሬዚዳንቱ የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ርዕሰ ብሔር ነው፡፡
አንቀጽ 70
የፕሬዜዳንቱ አሰያየም
1. ለፕሬዜዳንትነት ዕጩ የማቅረብ ሥልጣን የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ነው።
2. የቀረበው ዕጩ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እና በፌዴሬሽን ምክር ቤት የጋራ ስብሰባ በሁለት ሦስተኛ ድምጽ ከተደገፈ ፕሬዜዳንት ይሆናል።
3. የምክር ቤት አባል ፕሬዜዳንት ሆኖ ከተመረጠ የተወከለበትን ምክር ቤት ወንበር ይለቃል።
4. የፕሬዜዳንቱ የሥራ ዘመን 6 ዓመት ነው። አንድ ሰው ከሁለት ጊዜ በላይ ለፕሬዜዳንትነት ሊመረጥ አይችልም።
አንቀጽ 71
የኘሬዚዳንቱ ሥልጣንና ተግባር
1. የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤትና የፌዴሬሽኑን ምክር ቤት ዓመታዊ የጋራ ስብሰበባ ይከፍታል፡፡
2. በዚህ ሕገ መንግሥት መሰረት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ያጸደቃቸው ሕጐችና ዓለምአቀፍ ስምምነቶች በነጋሪት ጋዜጣ ያውጀል፡፡
3. ሀገሪቷን በውጭ ሀገሮች የሚወክሉትን አምባሳደሮችና ሌሎች መልክተኞች በጠቅላይ ሚኒስትሩ አቅራቢነት ይሾማል፡፡
4. የውጭ ሀገር አምሳደሮችንና የልዩ መልዕክተኞችን የሹመት ደብዳቤ ይቀበላል፡፡
5. በሕግ መሰረት ኒሻኖች እና ሽልማቶችን ይሰጣል፡፡
6. በጠቅላይ ሚኒስትሩ አቅራቢነት በሕግ በተወሰነው መሰረት ከፍተኛ የውትድርና ማዕረጐችን ይሰጣል፡፡
7. በሕግ መሰረት ይቅርታ ያደርጋል፡፡
#TikvahEthiopia
@tikvahethiopia
ዛሬ በኢትዮጵያ የማህበራዊ ትስስር ገጾች ትልቅ መነጋገሪያ የሆነው በፕሬዜዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ X ኦፊሻል ገጽ ላይ የሰፈረው ፅሁፍ ነው።
ፅሁፉ ላይ የማህሙድን ዘፈን ' ዝምታ ነው መልሴ 'ን በማንሳት " የሰው ልጅ ሆዱ ሲከፋው ጊዜም እንደ ሰው ሲገፋው: መሄጃ መውጫ ሲጠፋው ዝምታ ብቻ ነው ተስፋው " የሚለው ግጥም ተጋርቷል። መጨረሻ ላይ " ለአንድ አመት ሞከርኩ " የሚልም ሰፍሯል።
ፅሁፉ ስለምን ጉዳይ እንደሆነ ፤ ለምንስ ይህንን ግጥም ነጥሎ እንደተጻፈ በግልጽ የሚያብራራው ነገር የለም።
ያም ሆኖ ግን ፅሁፉን ላይ በርካቶች የየራሳቸውን አስተያየት እየሰጡ ይገኛሉ።
አንዳንዶች ፤ " አሁን ባለው ስርዓት በከፍተኛ ጫና ውስጥ ወድቀው ነው እየሰሩ ያሉት ፤ በተለያዩ ጉዳዮች አለመግባባት ውስጥም እንደነበሩ ብዙ ጊዜ በሚዲያ ይሰማ ነበር ፤ ለመናገር እንኳን እድል የላቸውም ፤ ባገኙት አጋጣሚ ግን በገደምዳሜው ስሜታቸውን ስለ ሀገራቸው ይናገሩ ነበር ፤ አሁንም ቦታውን ሲለቁ ስለዚህ ስርዓት ብዙ የሚናገሩት ይኖር ይሆናል " የሚል አስተያየት ሰጥተዋል።
አንዳንዶች፤ " በዚህ ልክ ትልቅ የስልጣን እርከን ይዘው ህዝብን ግራ የሚያጋባ ድፍንፍን ያለ ፅሁፍ በገጻቸው መጋራቱ ሳያንስ እውነትም እሳቸው መሆናቸውን በግልጽ አለማብራራታቸው ትክክል አይደለም ፤ ችግር ካለም እውነታውን ለህዝብ ማሳወቅ አለባቸው እንዲህ የዘፈን ግጥም ከሚያስቀምጡ " ብለዋል።
ሌሎች አስተያየት ሰጪዎች ደግሞ " የ6 ዓመት የስልጣን ዘመናቸው ሲያበቃ ይህን አይነት ነገር በገጻቸው መፃፋቸው የህዝብ ተቀባይነት ለማግኘት ነው እስከዛሬ በሀገሪቱ ብዙ ነገር ብዙ ግፍ ሲፈጠር ባላየ ሲያልፉ ነበር ፤ አንዳንዱን ደግሞ እየመረጡ ሲናገሩ ነበር ፤ ለምን አሁን ? በዚህ ስልጣን እንደማይቀጥሉ ስለሚያውቁ ነው ፤ ስልጣንም መልቀቅ ከነበረባቸው ቀድሞ ተናግሮ እንጂ አሁን ላይ ይህን አጀንዳ ለህዝብ መስጠት ትክክል አይደለም ፤ ጊዜያቸው አብቅቷል ይሰናበታሉ ፤ እሱንም ስለሚያውቁ ነው " ሲሉ ፅፈዋል።
በኢትዮጵያ የፕሬዜዳንት ስልጣን ዘመን 6 ዓመት ሲሆን ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ወደ ስልጣን የመጡት ጥቅምት 15 ቀን 2011 ዓ/ም ላይ ነበር።
ሌሎች ደግሞ " እንዲያው በደፈናው ድምዳሜ ላይ ከመድረስ የእሳቸውን ሙሉ ሀሳብ በትዕግስት ጠብቆ መስማት ይገባል " ብለዋል።
ከዚህ ባለፈ ግን ለመሆኑ ኢትዮጵያ ውስጥ የፕሬዝዳንትነት የስልጣን ድርሻው ምንድነው ? ፕሬዝዳንት የሚኮነው እንዴት ነው ? ምን ምን ይሰራል በዝርዝር ? ሲሉ የጠየቁ አሉ።
ለዚህ ምላሽ ይሆን ዘንድ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ህገ መንግስቱ ስለ ፕሬዜዳንቱ የሚለውን ከዚህ በታች አቅርቧል።
የኢፌዲሪ ህገ መንግስት ስለ ሪፐብሊኩ ፕሬዝዳንት ስልጣንና ተግባር ምን ይላል ?
(የኢፌዴሪ ህገ መንግስት)
ምዕራፍ ሰባት
ስለ ሪፐብሊኩ ኘሬዚዳንት
አንቀጽ 69
ስለ ኘሬዚዳንቱ
ኘሬዚዳንቱ የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ርዕሰ ብሔር ነው፡፡
አንቀጽ 70
የፕሬዜዳንቱ አሰያየም
1. ለፕሬዜዳንትነት ዕጩ የማቅረብ ሥልጣን የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ነው።
2. የቀረበው ዕጩ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እና በፌዴሬሽን ምክር ቤት የጋራ ስብሰባ በሁለት ሦስተኛ ድምጽ ከተደገፈ ፕሬዜዳንት ይሆናል።
3. የምክር ቤት አባል ፕሬዜዳንት ሆኖ ከተመረጠ የተወከለበትን ምክር ቤት ወንበር ይለቃል።
4. የፕሬዜዳንቱ የሥራ ዘመን 6 ዓመት ነው። አንድ ሰው ከሁለት ጊዜ በላይ ለፕሬዜዳንትነት ሊመረጥ አይችልም።
አንቀጽ 71
የኘሬዚዳንቱ ሥልጣንና ተግባር
1. የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤትና የፌዴሬሽኑን ምክር ቤት ዓመታዊ የጋራ ስብሰበባ ይከፍታል፡፡
2. በዚህ ሕገ መንግሥት መሰረት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ያጸደቃቸው ሕጐችና ዓለምአቀፍ ስምምነቶች በነጋሪት ጋዜጣ ያውጀል፡፡
3. ሀገሪቷን በውጭ ሀገሮች የሚወክሉትን አምባሳደሮችና ሌሎች መልክተኞች በጠቅላይ ሚኒስትሩ አቅራቢነት ይሾማል፡፡
4. የውጭ ሀገር አምሳደሮችንና የልዩ መልዕክተኞችን የሹመት ደብዳቤ ይቀበላል፡፡
5. በሕግ መሰረት ኒሻኖች እና ሽልማቶችን ይሰጣል፡፡
6. በጠቅላይ ሚኒስትሩ አቅራቢነት በሕግ በተወሰነው መሰረት ከፍተኛ የውትድርና ማዕረጐችን ይሰጣል፡፡
7. በሕግ መሰረት ይቅርታ ያደርጋል፡፡
#TikvahEthiopia
@tikvahethiopia
ፎቶ ፦ የ2017 ዓ/ም የኢሬቻ ሆራ አርሰዲ በዓል ዋዜማ በቢሾፍቱ ከተማ #Irreechaa2017 #HoraaHarsadee
Photo Credit - Visit Oromia
@tikvahethiopia
Photo Credit - Visit Oromia
@tikvahethiopia
#ዓለምአቀፍ #ሀንጋሪ
ሀንጋሪያዊያን የመንግስት ሚዲያን ' ፕሮፓጋንዳ ' ለመቃወም ሰልፍ መውጣታቸው ተሰማ።
በሀንጋሪ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች በአደባባይ በመውጣት በመንግስት ስር በሚተዳደረው የ ' MTVA ' ቴሌቪዥን ጣቢያ ዋና መሥሪያ ቤት አከባቢ በመገኘት መንግስት ቴሌቪዥኑን ለፕሮፓጋንዳ መጠቀሙን እንዲያቆም እና ጣቢያው ገለልተኛ የህዝብ ሚዲያ እንዲሆን ጠይቀዋል።
የተቃውሞ ሰልፉን ያስተባበረው ' TISZA ' የተሰኘው የተቃዋሚ ፓርቲ ሲሆን በሰልፉ ላይ የተገኙ ተቃዋሚዎች " ፕሮፓጋንዳ ይቁም !! " በሚል የሀገሪቱን ባንዲራ በመያዝ ድምጻቸውን አሰምተዋል።
የተቃዋሚ ፖርቲው መሪ የሆኑት ፒተር ማጂር ለተቃውሞ ለወጣው ተሳታፊ ንግግር ሲያደርጉ፥ " ክፋት፣ ውሸት፣ ፕሮፓጋንዳን ከበቂ በላይ ሰምተናል፤ ትዕግሥታችን አብቅቷል፣ አሁን በሀንጋሪ ያለው የመንግስት ሚዲያ በዓለም አቀፍ ደረጃ የተዋረድንበት ነው " ሲሉ ገልጸዋል።
ጣቢያው ሰልፉን ያለምንም መቆራረጥ እንዲያስተላልፈውም ጠይቀዋል።
የሀገሪቱ ገዢ ፖርቲ መሪ የሆኑት ቪክቶር ኦርባን መንግስትን የሚደግፉ ሚዲያዎችን ለማብዛት ከመንግስት ጋር ቅርበት ባላቸው #ባለሀብቶች ሚዲያዎች እንዲገዙ አድርገዋል በሚል ቅሬታ ይቀርብባቸዋል።
ድንበር የለሽ የሪፖርተሮች ቡድን ግምት እንደሚያሳየው 80 በመቶ የሚሆነው የሃንጋሪ የሚዲያ ገበያ በዚሁ መንገድ በገዢው መንግስት ቁጥጥር ሥር ወድቋል።
በዚህ የተነሳ እ.ኤ.አ በ2021 ቡድኑ ቪክቶር ኦርባንን " ሚዲያ አዳኝ " ዝርዝር ውስጥ ያስቀመጠው ሲሆን ይህንን ስያሜ የተቀበለ የመጀመሪያው የአውሮፓ ህብረት መሪ አድርጎታል።
ባላዝ ቶምፔ የተባሉ አንድ ተቃዋሚ በሰልፉ ላይ ለመሳተፍ ለብዙ ሰዓታት መጓዛቸውን ጠቅሰው ጣቢያውን " የውሸት ፋብሪካ " ሲሉ አጥላልተውታል።
አግነስ ጌራ የተባሉ ጡረታ የወጡ መምህር በበኩላቸው ፥ " የሚዲያ ሥርዓቱ በዚህ መንገድ መሆኑ ህዝቡ ከአንድ ወገን ብቻ ያለውን እንዲሰማ እና ስለሌላኛው ወገን እንኳን በማያውቅበት መንገድ መስራቱ በጣም ከባድ እና አሳዛኝ ነው" ብለዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ መረጃውን ከሮይተርስ እና ኤፒ ማሰስባሰቡን ይገልጻል።
@tikvahethmagazine @tikvahethiopia
ሀንጋሪያዊያን የመንግስት ሚዲያን ' ፕሮፓጋንዳ ' ለመቃወም ሰልፍ መውጣታቸው ተሰማ።
በሀንጋሪ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች በአደባባይ በመውጣት በመንግስት ስር በሚተዳደረው የ ' MTVA ' ቴሌቪዥን ጣቢያ ዋና መሥሪያ ቤት አከባቢ በመገኘት መንግስት ቴሌቪዥኑን ለፕሮፓጋንዳ መጠቀሙን እንዲያቆም እና ጣቢያው ገለልተኛ የህዝብ ሚዲያ እንዲሆን ጠይቀዋል።
የተቃውሞ ሰልፉን ያስተባበረው ' TISZA ' የተሰኘው የተቃዋሚ ፓርቲ ሲሆን በሰልፉ ላይ የተገኙ ተቃዋሚዎች " ፕሮፓጋንዳ ይቁም !! " በሚል የሀገሪቱን ባንዲራ በመያዝ ድምጻቸውን አሰምተዋል።
የተቃዋሚ ፖርቲው መሪ የሆኑት ፒተር ማጂር ለተቃውሞ ለወጣው ተሳታፊ ንግግር ሲያደርጉ፥ " ክፋት፣ ውሸት፣ ፕሮፓጋንዳን ከበቂ በላይ ሰምተናል፤ ትዕግሥታችን አብቅቷል፣ አሁን በሀንጋሪ ያለው የመንግስት ሚዲያ በዓለም አቀፍ ደረጃ የተዋረድንበት ነው " ሲሉ ገልጸዋል።
ጣቢያው ሰልፉን ያለምንም መቆራረጥ እንዲያስተላልፈውም ጠይቀዋል።
የሀገሪቱ ገዢ ፖርቲ መሪ የሆኑት ቪክቶር ኦርባን መንግስትን የሚደግፉ ሚዲያዎችን ለማብዛት ከመንግስት ጋር ቅርበት ባላቸው #ባለሀብቶች ሚዲያዎች እንዲገዙ አድርገዋል በሚል ቅሬታ ይቀርብባቸዋል።
ድንበር የለሽ የሪፖርተሮች ቡድን ግምት እንደሚያሳየው 80 በመቶ የሚሆነው የሃንጋሪ የሚዲያ ገበያ በዚሁ መንገድ በገዢው መንግስት ቁጥጥር ሥር ወድቋል።
በዚህ የተነሳ እ.ኤ.አ በ2021 ቡድኑ ቪክቶር ኦርባንን " ሚዲያ አዳኝ " ዝርዝር ውስጥ ያስቀመጠው ሲሆን ይህንን ስያሜ የተቀበለ የመጀመሪያው የአውሮፓ ህብረት መሪ አድርጎታል።
ባላዝ ቶምፔ የተባሉ አንድ ተቃዋሚ በሰልፉ ላይ ለመሳተፍ ለብዙ ሰዓታት መጓዛቸውን ጠቅሰው ጣቢያውን " የውሸት ፋብሪካ " ሲሉ አጥላልተውታል።
አግነስ ጌራ የተባሉ ጡረታ የወጡ መምህር በበኩላቸው ፥ " የሚዲያ ሥርዓቱ በዚህ መንገድ መሆኑ ህዝቡ ከአንድ ወገን ብቻ ያለውን እንዲሰማ እና ስለሌላኛው ወገን እንኳን በማያውቅበት መንገድ መስራቱ በጣም ከባድ እና አሳዛኝ ነው" ብለዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ መረጃውን ከሮይተርስ እና ኤፒ ማሰስባሰቡን ይገልጻል።
@tikvahethmagazine @tikvahethiopia
ሕብር የሴቶች የቁጠባ ሒሳብ - ለአንቺ የሚገባሽ!
ሕብር የሴቶች የቁጠባ ሒሳብ ከመደበኛው የቁጠባ ሒሳብ ላቅ ያለ ወለድ የምታገኚበት!
ሕብረት ባንክ
በሕብረት እንደግ!
ለበለጠ መረጃ ወደ 995 ነፃ የጥሪ ማዕከል ይደውሉ፡፡ አዳዲስ መረጃዎች እንዲደርስዎ የሚከተሉትን የማህበራዊ ገፆቻችንን ይቀላቀሉ፡፡
ቴሌግራም- https://t.iss.one/HibretBanket
linktr.ee/Hibret.Bank
#Hibretbank
ሕብር የሴቶች የቁጠባ ሒሳብ ከመደበኛው የቁጠባ ሒሳብ ላቅ ያለ ወለድ የምታገኚበት!
ሕብረት ባንክ
በሕብረት እንደግ!
ለበለጠ መረጃ ወደ 995 ነፃ የጥሪ ማዕከል ይደውሉ፡፡ አዳዲስ መረጃዎች እንዲደርስዎ የሚከተሉትን የማህበራዊ ገፆቻችንን ይቀላቀሉ፡፡
ቴሌግራም- https://t.iss.one/HibretBanket
linktr.ee/Hibret.Bank
#Hibretbank
#DStvEthiopia
🔥 ማን ዩናይትድ ከ አውሮፓ ሊግ ጨዋታ በኋላ ወደ ሜዳ ተመልሷል! በአስቶን ቪላ ሜዳ ማን ዩናይትድ ድል ማድረግ ይችላል ?
ዛሬ ከሰዓት 10፡00 የሚያደርጉትን ፍልሚያ በቀጥታ ይከታተሉ🔥 🤔 ማን ዩናይትድ ወደ አሸናፊነት መንገድ መመለስ ይችላል?
እንዳያመልጥዎ…
👉 ይህንን ድንቅ ፍልሚያ ጨምሮ ሌሎች የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታዎችን በቀጥታ በዲኤስቲቪ ሱፐርስፖርት ይመልከቱ።
👉 ዛሬውኑ ፓኬጅዎን ያሳድጉ። ጨዋታዎችን ከትንታኔ ፣ ከተጫዋች ብቃት እስከ ቡድን ወኔ በሱፐርስፖርት በቀጥታ ይከታተሉ!
ደንብና ሁኔታዎች ተፈፀሚነት አላቸው! ለበለጠ መረጃ
👇www.dstv.com/en-et
የዲኤስቲቪ ያስገቡ ፣ ደንበኝነትዎን ያራዝሙ!
👇https://bit.ly/3RFtEvh
#ሁሉምያለውእኛጋርነው
🔥 ማን ዩናይትድ ከ አውሮፓ ሊግ ጨዋታ በኋላ ወደ ሜዳ ተመልሷል! በአስቶን ቪላ ሜዳ ማን ዩናይትድ ድል ማድረግ ይችላል ?
ዛሬ ከሰዓት 10፡00 የሚያደርጉትን ፍልሚያ በቀጥታ ይከታተሉ🔥 🤔 ማን ዩናይትድ ወደ አሸናፊነት መንገድ መመለስ ይችላል?
እንዳያመልጥዎ…
👉 ይህንን ድንቅ ፍልሚያ ጨምሮ ሌሎች የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታዎችን በቀጥታ በዲኤስቲቪ ሱፐርስፖርት ይመልከቱ።
👉 ዛሬውኑ ፓኬጅዎን ያሳድጉ። ጨዋታዎችን ከትንታኔ ፣ ከተጫዋች ብቃት እስከ ቡድን ወኔ በሱፐርስፖርት በቀጥታ ይከታተሉ!
ደንብና ሁኔታዎች ተፈፀሚነት አላቸው! ለበለጠ መረጃ
👇www.dstv.com/en-et
የዲኤስቲቪ ያስገቡ ፣ ደንበኝነትዎን ያራዝሙ!
👇https://bit.ly/3RFtEvh
#ሁሉምያለውእኛጋርነው
TIKVAH-ETHIOPIA
ፎቶ ፦ የ2017 ዓ/ም የኢሬቻ ሆራ አርሰዲ በዓል ዋዜማ በቢሾፍቱ ከተማ #Irreechaa2017 #HoraaHarsadee Photo Credit - Visit Oromia @tikvahethiopia
ፎቶ ፦ የ2017 ዓ/ም የኢሬቻ ' ሆራ አርሰዲ ' በዓል በቢሾፍቱ ከተማ #Irreechaa2017 #HoraaHarsadee
Baga Ayyaanaa #Irreechaa geessan !
Ayyaana Gaari !
Photo Credit - EBC & Visit Oromia
@tikvahethiopia
Baga Ayyaanaa #Irreechaa geessan !
Ayyaana Gaari !
Photo Credit - EBC & Visit Oromia
@tikvahethiopia
#Mekelle
° " መንግስት ቃሉና መመሪያው ማክበር አለበት " - የ70 ካሬ የቤት ግንባታ ማህበር አመራሮች
° " ወደ ላይ እንጂ ወደ ጎን የሚሰጥ የቤት መስሪያ ቦታ የለም " - የትግራይ የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ
በመላ ትግራይ በተለይ በመቐለ የሚገኙ የ70 ካሬ የቤት ግንባታ ማህበር አመራሮች ከቤት መስሪያ ቦታ ጋር በተያያዘ ከአንድ ሳምንት በላይ ወደ ክልሉ ጊዚያዊ አስተዳደር ፅ/ቤት ምላሽ ለማግኘት ቢመላለሱም ሰሚ እንዳላገኙ ገልጸዋል።
ትላንት በጊዚያዊ አስተዳደሩ ፅ/ቤት የተሰባሰቡት የ 3043 የ70 ካሬ የቤት ግንባታ ማህበር አመራሮች ለጥያቄያቸው ምላሽ ለማግኘት ያደረጉት ሙከራ ሳይሳካ ቀርተዋል።
በቦታው የተገኘው የቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ አባል የ70 ካሬ የቤት ግንባታ ማህበር አመራሮችና ጥያቄና የክልሉ መንግስት ምላሽ ተመልክቷል።
60,860 አባላት ያቀፉት 3,043 የ70 ካሬ የቤት ግንባታ ማህበራት ከጦርነቱ በፊት ተደራጅተው ህጋዊ እውቅና በማግኘት ለቤት መስሪያ የሚሆን ገንዘብ በባንክ ሲቆጥቡ መቆየታቸው ይናገራሉ።
ማህበራቱ ቢያንስ በአንድ ቤተሰብ 5 አባላት ቢኖሩ መንግሰት ቃሉ እንዲጠብቅ እየቀረበለት ያለው ጥያቄ የ300 ሺህ ሰዎች መሆኑን ጠቁመዋል።
ተወካዮቹ ፤ " እኛ በሦስተኛ ዙር የ70 ካሬ የቤት ግንባታ ማህበር ስንደራጅ በክልሉ መመሪያ 4/2011 መሰረት ከኛ በፊት በሁለት ዙር እንደተስተናገዱት 70 ካሬ ለቤት መስሪያ ቦታ እንዲሰጠን ተሰማምተን ነው " ብለዋል።
የክልሉ አስተዳደር ግን ከጦርነቱ በኋላ ጥያቄያቸውን ላለመለስ ጀሮ ዳባ ልበስ ማለቱ እንዳሰዘናቸው በአደባባይ ወጥተው ገልፀዋል።
" የክልሉ አስተዳደር በመመሪያ 4/2011 የገባው ቃል ይተግብር " ተወካዮቹ ፥ በሚሰጣቸው 70 ካሬ ቦታ ቤት ለመስራት እንጂ ኮንደሚንየም ማለትም የጋራ መኖሪያ ቤት ለመስራት ቃል እንዳልፈፀሙ አስረድተዋል።
የማህበራቱ አመራሮች ከቀናት በፊት ለጥያቄያቸው ተገቢ ምላሽ ለማግኘት ለክልሉ ምክትል ጊዚያዊ አስተዳደር ሌተናል ጀነራል ፃድቃን ገ/ትንሳኤ ጥያቄ አቅርበው ከክልሉ ፕሬዜዳንት ጌታቸው ረዳ በመነጋገር መልስ እንደሚሰጣቸው የተነገራቸው ቢሆንም አስከ አሁን የተሰጣቸው ምላሽ እንደሌለ ተናግረዋል።
ከአንድ ሳምንት በፊት የክልሉ የከተማ ልማት እና ኮንስትራክሽን ቢሮ ሃላፊ ወ/ሮ አልማዝ ገ/ፃድቕ ለድምፂ ወያነ ትግራይ ጉዳዩ በማስመልከት በሰጡት ማብራርያ ፤ ማህበራቱ ከጦርነቱ በፊት ለእንያንዳንዱ አባል 70 ካሬ መሬት ለቤት መገንብያ እንዲሰጥ በሚፈቅደው መመሪያ መደራጀታቸው አምነዋል።
"ይሁን እንጂ ከአሁን በኋላ ወደ ላይ እንጂ ወደ ጎን የሚሰጥ የቤት መስሪያ ቦታ የለም ፤ ስለሆነም ማህበራቱ የሚሰጣቸው ቦታ G+4 ወደ ላይ የሚገነባ የጋራ መኖሪያ አፓርታማ ነው " ብለዋል።
የማህበራቱ ተወካዮች በቢሮ ሃላፊዋ መልስ እንደማይስማሙ ገልጸዋል።
ለፍትሃዊ ጥያቄያቸው ፍትሃዊ ምላሽ ለማግኘት በማለምም ትላንት ቅዳሜ ቀኑን ሙሉ በጊዚያዊ አስተዳደሩ ፅ/ቤት ጠብቀው የሚያናግራቸው የመንግስት የስራ ሃላፊ ባለመገኘቱ ነገ ሰኞ ጥያቄቸውን በሰላማዊ ሁኔታ ማቅረብ እንደሚቀጥሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ ተናግረዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia
° " መንግስት ቃሉና መመሪያው ማክበር አለበት " - የ70 ካሬ የቤት ግንባታ ማህበር አመራሮች
° " ወደ ላይ እንጂ ወደ ጎን የሚሰጥ የቤት መስሪያ ቦታ የለም " - የትግራይ የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ
በመላ ትግራይ በተለይ በመቐለ የሚገኙ የ70 ካሬ የቤት ግንባታ ማህበር አመራሮች ከቤት መስሪያ ቦታ ጋር በተያያዘ ከአንድ ሳምንት በላይ ወደ ክልሉ ጊዚያዊ አስተዳደር ፅ/ቤት ምላሽ ለማግኘት ቢመላለሱም ሰሚ እንዳላገኙ ገልጸዋል።
ትላንት በጊዚያዊ አስተዳደሩ ፅ/ቤት የተሰባሰቡት የ 3043 የ70 ካሬ የቤት ግንባታ ማህበር አመራሮች ለጥያቄያቸው ምላሽ ለማግኘት ያደረጉት ሙከራ ሳይሳካ ቀርተዋል።
በቦታው የተገኘው የቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ አባል የ70 ካሬ የቤት ግንባታ ማህበር አመራሮችና ጥያቄና የክልሉ መንግስት ምላሽ ተመልክቷል።
60,860 አባላት ያቀፉት 3,043 የ70 ካሬ የቤት ግንባታ ማህበራት ከጦርነቱ በፊት ተደራጅተው ህጋዊ እውቅና በማግኘት ለቤት መስሪያ የሚሆን ገንዘብ በባንክ ሲቆጥቡ መቆየታቸው ይናገራሉ።
ማህበራቱ ቢያንስ በአንድ ቤተሰብ 5 አባላት ቢኖሩ መንግሰት ቃሉ እንዲጠብቅ እየቀረበለት ያለው ጥያቄ የ300 ሺህ ሰዎች መሆኑን ጠቁመዋል።
ተወካዮቹ ፤ " እኛ በሦስተኛ ዙር የ70 ካሬ የቤት ግንባታ ማህበር ስንደራጅ በክልሉ መመሪያ 4/2011 መሰረት ከኛ በፊት በሁለት ዙር እንደተስተናገዱት 70 ካሬ ለቤት መስሪያ ቦታ እንዲሰጠን ተሰማምተን ነው " ብለዋል።
የክልሉ አስተዳደር ግን ከጦርነቱ በኋላ ጥያቄያቸውን ላለመለስ ጀሮ ዳባ ልበስ ማለቱ እንዳሰዘናቸው በአደባባይ ወጥተው ገልፀዋል።
" የክልሉ አስተዳደር በመመሪያ 4/2011 የገባው ቃል ይተግብር " ተወካዮቹ ፥ በሚሰጣቸው 70 ካሬ ቦታ ቤት ለመስራት እንጂ ኮንደሚንየም ማለትም የጋራ መኖሪያ ቤት ለመስራት ቃል እንዳልፈፀሙ አስረድተዋል።
የማህበራቱ አመራሮች ከቀናት በፊት ለጥያቄያቸው ተገቢ ምላሽ ለማግኘት ለክልሉ ምክትል ጊዚያዊ አስተዳደር ሌተናል ጀነራል ፃድቃን ገ/ትንሳኤ ጥያቄ አቅርበው ከክልሉ ፕሬዜዳንት ጌታቸው ረዳ በመነጋገር መልስ እንደሚሰጣቸው የተነገራቸው ቢሆንም አስከ አሁን የተሰጣቸው ምላሽ እንደሌለ ተናግረዋል።
ከአንድ ሳምንት በፊት የክልሉ የከተማ ልማት እና ኮንስትራክሽን ቢሮ ሃላፊ ወ/ሮ አልማዝ ገ/ፃድቕ ለድምፂ ወያነ ትግራይ ጉዳዩ በማስመልከት በሰጡት ማብራርያ ፤ ማህበራቱ ከጦርነቱ በፊት ለእንያንዳንዱ አባል 70 ካሬ መሬት ለቤት መገንብያ እንዲሰጥ በሚፈቅደው መመሪያ መደራጀታቸው አምነዋል።
"ይሁን እንጂ ከአሁን በኋላ ወደ ላይ እንጂ ወደ ጎን የሚሰጥ የቤት መስሪያ ቦታ የለም ፤ ስለሆነም ማህበራቱ የሚሰጣቸው ቦታ G+4 ወደ ላይ የሚገነባ የጋራ መኖሪያ አፓርታማ ነው " ብለዋል።
የማህበራቱ ተወካዮች በቢሮ ሃላፊዋ መልስ እንደማይስማሙ ገልጸዋል።
ለፍትሃዊ ጥያቄያቸው ፍትሃዊ ምላሽ ለማግኘት በማለምም ትላንት ቅዳሜ ቀኑን ሙሉ በጊዚያዊ አስተዳደሩ ፅ/ቤት ጠብቀው የሚያናግራቸው የመንግስት የስራ ሃላፊ ባለመገኘቱ ነገ ሰኞ ጥያቄቸውን በሰላማዊ ሁኔታ ማቅረብ እንደሚቀጥሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ ተናግረዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia