TIKVAH-ETHIOPIA
#Afar #Tigray የትግራይ እና ዓፋር ክልሎች በፕሬዜዳንቶቻቸው የተደገፈ ይፋዊ ምክክር አደረጉ። ዛሬ በዓፋርዋ ሰመራ ከተማ የተሳለጠው ግንኙነት በትግራይ ክልል ጊዚያዊ አስተዳደር ጌታቸው ረዳ እና በዓፋር ክልል ፕሬዜዳንት አወል አርባ የተመራ ነው። በአቶ ጌታቸው ረዳ የተመራ ልኡክ ሰመራ ከተማ አውሮፕላን ማረፍያ ሲደርስ ፕሬዜዳንት አወል አርባ እና ካቢኔያቸው አቀባበል አደርገውለታል። የሁለቱ…
#Afar #Tigray
ትግራይ እና ዓፋር ክልሎች በፕሬዜዳንቶቻቸው በኩል ባደረጉት ይፋዊ ግንኙነት የሁለቱም ህዝቦች አብሮነት የሚጎዱ ወንጀለኞች ተላለፈው እንዲሰጣጡ ተሰማሙ።
በትግራይ ክልል ጊዚያዊ አስተዳደር አቶ ጌታቸው ረዳ የተመራ ልኡክ በዓፋር ክልል ሰመራ ከተማ ያደረገው የአንድ ቀን ምክክር አድርጓል።
ምክክሩ ውጤታማ እንደነበር ተገልጿል።
የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ልኡክ አባል የዓፋር ክልል አጎራባች ደቡባዊ ምስራቅ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ጸጋይ ገብረተኽለ ፥ " ውይይቱ የሁለቱ ክልል ህዝቦች ጉርብትና ሰላማዊ ሆኖ እንዲቀጥል የሚያግዝ ውጤታማ ውይይት ነው " ብሎውታል።
" በትግራይ እና ዓፋር ክልሎች የህዝብ ለህዝብ ግንኙነት እንዲጀመር ፣ የተዘጉ መንገዶች እንዲከፈቱ ፣ ነፃ የሆነ ግንኙነት እንዲኖር ፣ ተፈናቃዮች ወደ ቄያቸው እንዲመለሱ እና የቆየው የሰላም እና የልማት ግንኙነት እንዲቀጥል በውይይቱ ስምምነት ላይ ተደርሷል " ብለዋል።
" ሁለቱ ክልሎች በሚያዋስኑ አከባቢዎች ተደጋጋሚ ግጭቶች እንደሚከሰቱ " የገለፁት ዋና አስተዳዳሪው " ግጭት ጠማቂዎችና ወንጀለኞች ተላልፈው እንዲሰጣጡ ፣ የጋራ የሰላም እና የፀጥታ እቅድ እንዲኖርና በየወሩ እየተገመገመ እንዲመራ ትግራይ እና ዓፋር ተስማምተዋል " ሲሉ አሳውቀዋል።
በፕሬዜዳንት ጌታቸው ረዳ የተመራ ልኡክ በዓፋር ክልል የነበረው የአንድ ቀን ቆይታ አጠናቅቆ ወደ መቐለ መመለሱ የጊዚያዊ አስተዳደሩ ፕሬዜዳንት ፅህፈት ቤት በመጥቀስ ቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ ዘግቧል።
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia
ትግራይ እና ዓፋር ክልሎች በፕሬዜዳንቶቻቸው በኩል ባደረጉት ይፋዊ ግንኙነት የሁለቱም ህዝቦች አብሮነት የሚጎዱ ወንጀለኞች ተላለፈው እንዲሰጣጡ ተሰማሙ።
በትግራይ ክልል ጊዚያዊ አስተዳደር አቶ ጌታቸው ረዳ የተመራ ልኡክ በዓፋር ክልል ሰመራ ከተማ ያደረገው የአንድ ቀን ምክክር አድርጓል።
ምክክሩ ውጤታማ እንደነበር ተገልጿል።
የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ልኡክ አባል የዓፋር ክልል አጎራባች ደቡባዊ ምስራቅ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ጸጋይ ገብረተኽለ ፥ " ውይይቱ የሁለቱ ክልል ህዝቦች ጉርብትና ሰላማዊ ሆኖ እንዲቀጥል የሚያግዝ ውጤታማ ውይይት ነው " ብሎውታል።
" በትግራይ እና ዓፋር ክልሎች የህዝብ ለህዝብ ግንኙነት እንዲጀመር ፣ የተዘጉ መንገዶች እንዲከፈቱ ፣ ነፃ የሆነ ግንኙነት እንዲኖር ፣ ተፈናቃዮች ወደ ቄያቸው እንዲመለሱ እና የቆየው የሰላም እና የልማት ግንኙነት እንዲቀጥል በውይይቱ ስምምነት ላይ ተደርሷል " ብለዋል።
" ሁለቱ ክልሎች በሚያዋስኑ አከባቢዎች ተደጋጋሚ ግጭቶች እንደሚከሰቱ " የገለፁት ዋና አስተዳዳሪው " ግጭት ጠማቂዎችና ወንጀለኞች ተላልፈው እንዲሰጣጡ ፣ የጋራ የሰላም እና የፀጥታ እቅድ እንዲኖርና በየወሩ እየተገመገመ እንዲመራ ትግራይ እና ዓፋር ተስማምተዋል " ሲሉ አሳውቀዋል።
በፕሬዜዳንት ጌታቸው ረዳ የተመራ ልኡክ በዓፋር ክልል የነበረው የአንድ ቀን ቆይታ አጠናቅቆ ወደ መቐለ መመለሱ የጊዚያዊ አስተዳደሩ ፕሬዜዳንት ፅህፈት ቤት በመጥቀስ ቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ ዘግቧል።
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Ethiopia የውጪ ምንዛሪ ቢሮ ፍቃድ መስጠት የሚያስችለውን ሂደት መጨረሱን የብሔራዊ ባንክ አሳውቋል። ብሔራዊ ባንክ ከዚህ ቀደም መደበኛ ባልሆነ መንገድ የውጪ ምንዛሪ ላይ የሚሳተፉ አካላትን ህጋዊ ሆነዉ ፍቃድ አውጥተዉ መስራት እንዲችሉ መፍቀዱን ተከትሎ ከወዲሁ ብዙ ሰዎችና ኩባንያዎችን እየተቀበለ እንደሚገኝ ገልጿል። የውጪ ምንዛሪ ገበያ ውስጥ የሚሳተፉ በፊት ባንኮች ብቻ የነበሩ ቢሆንም አሁን…
#NBE : የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ለአምስት ባንክ ላልሆኑ የውጭ ምንዛሪ ቢሮዎች የስራ ፈቃድ ሰጠ።
የስራ ፍቃድ የተሰጣቸው ፦
1. Dugda Fidelity Investment PLC
2. Ethio Independent Foreign Exchange Bureau
3. Global Independent Foreign Exchange Bureau
4. Robust Independent Foreign Exchange Bureau
5. Yoga Forex Bureau ናቸው።
" እነዚህ የውጭ ምንዛሪ ቢሮዎች በሙሉ ተቀባይነት ያላቸው " ናቸው ያለው ብሔራዊ ባንክ " የውጭ ሀገር ጥሬ ገንዘቦችን በመግዛትና በመሸጥ እንዲሁም ከባንኮች ጋር በመቀናጀት ለወጪና ገቢ ንግድ የሚውል የውጭ ምንዛሪ በማመቻቸት የሀገሪቱን የውጭ ምንዛሪ ገበያ ለማስፋፋትና ለማዳበር የሚረዳ ሚና ይኖራቸዋል " ብሏል።
የውጭ ምንዛሪ ቢሮዎቹ በዋናነት የሚያካሂዱት የውጭ ምንዛሪ ሽያጭም ሆነ ግዥ ወዲያውኑ የሚፈጸም (spot transaction) ብቻ ይሆናል ተብሏል።
የውጭ ምንዛሪ ቢሮዎች ያለ ጉምሩክ ዴክላራሲዮን ከደንበኞች እስከ 10 ሺህ የአሜሪካን ዶላር፣ የጉምሩክ ፈቃድ ከሚያቀርቡት ደግሞ ከዚያ በላይ የውጭ ምንዛሪ በጥሬ ገንዘብ መግዛት ይችላሉ፡፡
እንዲሁም ተፈላጊ የጉዞ መረጃ ላላቸው የግል ተጓዦች እስከ 5 ሺህ የአሜሪካን ዶላር፣ ለንግድ ሥራ ተጓዦች ደግሞ እስከ 10 ሺህ የአሜሪካን ዶላር በጥሬ ገንዘብ መሸጥ ይችላሉ፡፡
@tikvahethiopia
የስራ ፍቃድ የተሰጣቸው ፦
1. Dugda Fidelity Investment PLC
2. Ethio Independent Foreign Exchange Bureau
3. Global Independent Foreign Exchange Bureau
4. Robust Independent Foreign Exchange Bureau
5. Yoga Forex Bureau ናቸው።
" እነዚህ የውጭ ምንዛሪ ቢሮዎች በሙሉ ተቀባይነት ያላቸው " ናቸው ያለው ብሔራዊ ባንክ " የውጭ ሀገር ጥሬ ገንዘቦችን በመግዛትና በመሸጥ እንዲሁም ከባንኮች ጋር በመቀናጀት ለወጪና ገቢ ንግድ የሚውል የውጭ ምንዛሪ በማመቻቸት የሀገሪቱን የውጭ ምንዛሪ ገበያ ለማስፋፋትና ለማዳበር የሚረዳ ሚና ይኖራቸዋል " ብሏል።
የውጭ ምንዛሪ ቢሮዎቹ በዋናነት የሚያካሂዱት የውጭ ምንዛሪ ሽያጭም ሆነ ግዥ ወዲያውኑ የሚፈጸም (spot transaction) ብቻ ይሆናል ተብሏል።
የውጭ ምንዛሪ ቢሮዎች ያለ ጉምሩክ ዴክላራሲዮን ከደንበኞች እስከ 10 ሺህ የአሜሪካን ዶላር፣ የጉምሩክ ፈቃድ ከሚያቀርቡት ደግሞ ከዚያ በላይ የውጭ ምንዛሪ በጥሬ ገንዘብ መግዛት ይችላሉ፡፡
እንዲሁም ተፈላጊ የጉዞ መረጃ ላላቸው የግል ተጓዦች እስከ 5 ሺህ የአሜሪካን ዶላር፣ ለንግድ ሥራ ተጓዦች ደግሞ እስከ 10 ሺህ የአሜሪካን ዶላር በጥሬ ገንዘብ መሸጥ ይችላሉ፡፡
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ተማሪዎች እስከ መቼ ማመልከት ይችላሉ ? የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጠው መረጃ የማመልከቻው ቀን ከዚህ ቀደም በነበረው ማስታወቂያ ዛሬ መስከረም 08/2017 እንደሚያበቃ ቢገለጽም እስከ ነገ መስከረም 09/2017 ድረስ መራዘሙን አስታውቋል። በዚህም በዩኒቨርሲቲው ድረ ገጾች ፦ ➡️ www.aau.edu.et ➡️ https://portal.aau.edu.et ላይ የተመለከቱትን ዝርዝር…
#AAU
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ራስ ገዝ ዩኒቨርሲቲ መሆኑን ተከትሎ ተማሪዎችን ለማስተማር በራሱ መስፈርት አወዳድሮ እንደሚቀበል የምልመላ ፖሊሲ መዘርጋቱን ከዚህ ቀደም መግለጹ ይታወሳል፡፡
ለማስተማር የተቀባላቸውን ተማሪዎች በተመለከተም ዛሬ መግለጫ ሰጥቷል፡፡
የዩኒቨርሲቲው የአካዳሚክ ምክትል ፕሬዚደንት ዩኒቨርሲቲ ጀይል ዑመር (ዶ/ር) ፣ “ ዩኒቨርሲቲው በቅድመ ምረቃም ሆነ በድህረ ምረቃ ፕሮግራሞች የሚከታተሉትን ብቃትና አቅም ለመመልመል የሚያስችል የቅበላ ፖሊሲ በማዘጋጀት ምልመላውን አዘጋጂቷል ” ብለዋል፡፡
“ ለምልመላው ትልቁ መስፈርት በሀገራችን ለቅድመ መረቃ ፕሮግራሞች በአገሪቷ የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ወደ ዩኒቨርሲቲ መግባት የሚያስችል ውጤት ያላቸው ተማሪዎች እንዲወዳደሩ ነው የተደረገው ” ነው ያሉት፡፡
ለምልመላው በጥቅሉ፣ ዩኒቨርሲቲው የሰጠው የአድሚሽን ፈተና ከ50 ፐርሰንት፣ የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ውጤት ከ50 ፐርሰንት መያዙ ተነግሯል፡፡
“ በዚህ ዓመት ለከፍተኛ ትምህርት ብቁ ናቸው ተብለው ትምህርት ሚኒስቴር ካረጋገጠላቸው መካካል 11 ሺሕ 939 ተማሪዎች ለአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ለመመረጥ ለፈተና ቀርበዋል፡፡ የቅበላ ፈተናው የሚለካው ተማሪዎቹ ወደ ዩኒቨርሲቲው ቢገቡ ያለ ምንም እንከን የቅድሞ ምረቃውን ፕሮግራም ዝግጁነት ኑሯቸው የሚችሉ መሆኑን የሚያረጋግጡ ናቸው ” ሲሉ ተናግረዋል፡፡
የክሪቲካል ቲንኪንግ፣ የቋንቋ ዝግጁነትን፣ የስሌት ብቃቶችን ሊያረጋግጡ የሚችሉ ጉዳዮችን የቅበላ ፈተናው ማካተቱንም ገልጸዋል፡፡
“ ከ11 ሺሕ 939 ለፈተናው የተቀመጡትን ስናይ፣ በቅድመ ምረቃ ፕሮግራም የመጀመሪያው ነው፡፡ የፍሬሽማን ፕሮግራም ዘርፍ አለው፡፡ በተፈጥሮ ሳይንስና በማህበራዊ ሳይንስ ተብሎ ይከፈላል ” ነው ያሉት።
“ በተፈጥሮ ሳይንስ ያመለከቱትና ለፈተና የተቀመጡት 7,589 ሲሆኑ፣ በሶሻል ሳይንስ ደግሞ 4,350 ተማሪዎች ናቸው ” ነው የተባለው።
በዚህም በመንግስት ስኮላርሽፕ የሚማሩት 4,402፣ በራሳቸው ከፍለው የሚማሩት ደግሞ 7,537 ተማሪዎች ለፈተና እንደተቀመጡ ተገልጿል፡፡
በዬፕሮግራሞቹ የማስተናገድ አቅምም አንዱ ታሳቢ የሆነ መስፈርት እንደሆነ የገለጸው ዩኒቨርሲቲው፣ “ በዚህ ስሌት በመንግስት ስፖንሰርነት የተመለመሉት 2,660፣ በግል አመልካችነት (ከፍሎ ለመማር) 2,640፣ በአጠቃላይ ዩኒቨርሲቲው በቅድመ ምረቃ ፕሮግራም 5300 ተማሪዎችን ቅበላ አድርጓል ” ነው ያሉት፡፡
በሚቀጥሉት ጥቂት ቀናት ውስጥ ተመዝግበው ትምህርትቸውን እንደሚቀጥሉም ተመላክቷል፡፡
በተለይ የጸጥታ ችግር ባለባቸው አካባቢዎች ያሉ ተማሪዎች ወደ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ መጥተው ለመማር የሚፈልጉ ከመሆናቸው አንጻር ዩኒቨርሲቲው ምልመላውን በምን መልኩ እንደዳሰሰው ለቀረበለት ጥያቄ በሰጠው ምላሽ፣ “ ከየትኛውም የአገሪቷ ኮርነር ላሉት እድሉ ተሰጥቷል፡፡ ዩኒቨርሲቲው በዚህ በኩል ነፍጓል የምንለው ነገር የለም ” ብሏል፡፡
ክፍያው ስንት እንደሆነ ከጋዜጠኞች ለቀረበው ጥያቄም፣ ክፍያው የተለያዬ እንደሆነ፣ መንግስት ስፖንሰር ያደረጋቸው የምግብ፣ የመኝታ፣ የትምህርታና ሌሎች ወጪዎው በመንግስት እንደሚሸፈኑ ዪኒቨርሲቲው ምላሽ ሰጥቶበታል፡፡
“ ከፍለው የሚማሩ ደግሞ ምግብም፣ መኝታ ቤትም ያስፈልገኛል ለሚል ኮስት ያደርጋል፡፡ የትምህርት ወጪ የምንለው ስሌቱ በኢሲቲኤስ ነው፡፡
እንደዬየፕሮግራሞቹ ይለያያል፡፡ ለምሳሌ ዝቅተኛ በአንድ ኢሲቲኤስ 600 ብር፣ በኢሲቲኤስ ከፍተኛው እስከ 2000 ብር የሚሄድ ነው ” ብሏል፡፡
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ራስ ገዝ ዩኒቨርሲቲ መሆኑን ተከትሎ ተማሪዎችን ለማስተማር በራሱ መስፈርት አወዳድሮ እንደሚቀበል የምልመላ ፖሊሲ መዘርጋቱን ከዚህ ቀደም መግለጹ ይታወሳል፡፡
ለማስተማር የተቀባላቸውን ተማሪዎች በተመለከተም ዛሬ መግለጫ ሰጥቷል፡፡
የዩኒቨርሲቲው የአካዳሚክ ምክትል ፕሬዚደንት ዩኒቨርሲቲ ጀይል ዑመር (ዶ/ር) ፣ “ ዩኒቨርሲቲው በቅድመ ምረቃም ሆነ በድህረ ምረቃ ፕሮግራሞች የሚከታተሉትን ብቃትና አቅም ለመመልመል የሚያስችል የቅበላ ፖሊሲ በማዘጋጀት ምልመላውን አዘጋጂቷል ” ብለዋል፡፡
“ ለምልመላው ትልቁ መስፈርት በሀገራችን ለቅድመ መረቃ ፕሮግራሞች በአገሪቷ የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ወደ ዩኒቨርሲቲ መግባት የሚያስችል ውጤት ያላቸው ተማሪዎች እንዲወዳደሩ ነው የተደረገው ” ነው ያሉት፡፡
ለምልመላው በጥቅሉ፣ ዩኒቨርሲቲው የሰጠው የአድሚሽን ፈተና ከ50 ፐርሰንት፣ የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ውጤት ከ50 ፐርሰንት መያዙ ተነግሯል፡፡
“ በዚህ ዓመት ለከፍተኛ ትምህርት ብቁ ናቸው ተብለው ትምህርት ሚኒስቴር ካረጋገጠላቸው መካካል 11 ሺሕ 939 ተማሪዎች ለአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ለመመረጥ ለፈተና ቀርበዋል፡፡ የቅበላ ፈተናው የሚለካው ተማሪዎቹ ወደ ዩኒቨርሲቲው ቢገቡ ያለ ምንም እንከን የቅድሞ ምረቃውን ፕሮግራም ዝግጁነት ኑሯቸው የሚችሉ መሆኑን የሚያረጋግጡ ናቸው ” ሲሉ ተናግረዋል፡፡
የክሪቲካል ቲንኪንግ፣ የቋንቋ ዝግጁነትን፣ የስሌት ብቃቶችን ሊያረጋግጡ የሚችሉ ጉዳዮችን የቅበላ ፈተናው ማካተቱንም ገልጸዋል፡፡
“ ከ11 ሺሕ 939 ለፈተናው የተቀመጡትን ስናይ፣ በቅድመ ምረቃ ፕሮግራም የመጀመሪያው ነው፡፡ የፍሬሽማን ፕሮግራም ዘርፍ አለው፡፡ በተፈጥሮ ሳይንስና በማህበራዊ ሳይንስ ተብሎ ይከፈላል ” ነው ያሉት።
“ በተፈጥሮ ሳይንስ ያመለከቱትና ለፈተና የተቀመጡት 7,589 ሲሆኑ፣ በሶሻል ሳይንስ ደግሞ 4,350 ተማሪዎች ናቸው ” ነው የተባለው።
በዚህም በመንግስት ስኮላርሽፕ የሚማሩት 4,402፣ በራሳቸው ከፍለው የሚማሩት ደግሞ 7,537 ተማሪዎች ለፈተና እንደተቀመጡ ተገልጿል፡፡
በዬፕሮግራሞቹ የማስተናገድ አቅምም አንዱ ታሳቢ የሆነ መስፈርት እንደሆነ የገለጸው ዩኒቨርሲቲው፣ “ በዚህ ስሌት በመንግስት ስፖንሰርነት የተመለመሉት 2,660፣ በግል አመልካችነት (ከፍሎ ለመማር) 2,640፣ በአጠቃላይ ዩኒቨርሲቲው በቅድመ ምረቃ ፕሮግራም 5300 ተማሪዎችን ቅበላ አድርጓል ” ነው ያሉት፡፡
በሚቀጥሉት ጥቂት ቀናት ውስጥ ተመዝግበው ትምህርትቸውን እንደሚቀጥሉም ተመላክቷል፡፡
በተለይ የጸጥታ ችግር ባለባቸው አካባቢዎች ያሉ ተማሪዎች ወደ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ መጥተው ለመማር የሚፈልጉ ከመሆናቸው አንጻር ዩኒቨርሲቲው ምልመላውን በምን መልኩ እንደዳሰሰው ለቀረበለት ጥያቄ በሰጠው ምላሽ፣ “ ከየትኛውም የአገሪቷ ኮርነር ላሉት እድሉ ተሰጥቷል፡፡ ዩኒቨርሲቲው በዚህ በኩል ነፍጓል የምንለው ነገር የለም ” ብሏል፡፡
ክፍያው ስንት እንደሆነ ከጋዜጠኞች ለቀረበው ጥያቄም፣ ክፍያው የተለያዬ እንደሆነ፣ መንግስት ስፖንሰር ያደረጋቸው የምግብ፣ የመኝታ፣ የትምህርታና ሌሎች ወጪዎው በመንግስት እንደሚሸፈኑ ዪኒቨርሲቲው ምላሽ ሰጥቶበታል፡፡
“ ከፍለው የሚማሩ ደግሞ ምግብም፣ መኝታ ቤትም ያስፈልገኛል ለሚል ኮስት ያደርጋል፡፡ የትምህርት ወጪ የምንለው ስሌቱ በኢሲቲኤስ ነው፡፡
እንደዬየፕሮግራሞቹ ይለያያል፡፡ ለምሳሌ ዝቅተኛ በአንድ ኢሲቲኤስ 600 ብር፣ በኢሲቲኤስ ከፍተኛው እስከ 2000 ብር የሚሄድ ነው ” ብሏል፡፡
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Afar #Tigray ትግራይ እና ዓፋር ክልሎች በፕሬዜዳንቶቻቸው በኩል ባደረጉት ይፋዊ ግንኙነት የሁለቱም ህዝቦች አብሮነት የሚጎዱ ወንጀለኞች ተላለፈው እንዲሰጣጡ ተሰማሙ። በትግራይ ክልል ጊዚያዊ አስተዳደር አቶ ጌታቸው ረዳ የተመራ ልኡክ በዓፋር ክልል ሰመራ ከተማ ያደረገው የአንድ ቀን ምክክር አድርጓል። ምክክሩ ውጤታማ እንደነበር ተገልጿል። የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ልኡክ አባል የዓፋር ክልል…
#Afar #Tigray
" የትግራይ ክልል ሰላም ለክልላችን ሰላም ወሳኝ ነው " - ሀጂ አወል አርባ
የአፋር ክልል ፕሬዜዳንት ሀጂ አወል አርባ ለትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ እና ከፍተኛ አመራርን ላካተተዉ ሉዑካን ቡድን ምን አሉ ?
" የአፋርና ትግራይ ህዝቦች መካከል የሰላምና ፀጥታ ችግሮችን መፍታት እና የህዝብ ለህዝብ ግንኙነቶችን ማጠናከር አስፈላጊ ነው።
በሁለቱ ክልሎች መካከል ዘላቂ ሰላምን ማስፈን አስፈላጊ ነው።
የትግራይ ክልል ሰላም ለክልላችን ሰላም ወሳኝ በመሆኑ በክልሉ መረጋጋትን ለመፍጠር የሁሉንም ተሳትፎ ይጠይቃል።
ለክልሉ ሰላምና መረጋገት የድርሻችንን እንወጣለን " ብለዋል።
@tikvahethiopia
" የትግራይ ክልል ሰላም ለክልላችን ሰላም ወሳኝ ነው " - ሀጂ አወል አርባ
የአፋር ክልል ፕሬዜዳንት ሀጂ አወል አርባ ለትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ እና ከፍተኛ አመራርን ላካተተዉ ሉዑካን ቡድን ምን አሉ ?
" የአፋርና ትግራይ ህዝቦች መካከል የሰላምና ፀጥታ ችግሮችን መፍታት እና የህዝብ ለህዝብ ግንኙነቶችን ማጠናከር አስፈላጊ ነው።
በሁለቱ ክልሎች መካከል ዘላቂ ሰላምን ማስፈን አስፈላጊ ነው።
የትግራይ ክልል ሰላም ለክልላችን ሰላም ወሳኝ በመሆኑ በክልሉ መረጋጋትን ለመፍጠር የሁሉንም ተሳትፎ ይጠይቃል።
ለክልሉ ሰላምና መረጋገት የድርሻችንን እንወጣለን " ብለዋል።
@tikvahethiopia
" የጥገና ሥራው ከ20 ቀን ያላነሰ ጊዜ ሊወስድ ይችላል " - የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል
ከቆቃ-ሁርሶ ባለ 230 ኪሎ ቮልት ጥምር የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ላይ በተፈፀመ ስርቆት ኃይል መቋረጡን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አሳውቋል።
ኃይል የተቋረጠው በአፋር ክልል አዋሽ ፈንታሌ ወረዳ በንቲ ቀበሌ ልዩ ስሙ አዋሽ ፓርክ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ በአንድ የኃይል ተሸካሚ ምሰሶ ላይ በተፈፀመ ስርቆት ምክንያት ነው።
የኃይል ማስተላለፊያ መስመሩ ፦
- በምስራቅ የሃገሪቱ ክፍል ለሚገኙ ከተሞችና አካባቢዎች፣
- ለአዲስ አበባ- ጅቡቲ የባቡር መስመር
- ለጅቡቲ የኤሌክትሪክ ኃይል እያቀረበ ነበር።
በደረሰው ጉዳት ምክንያት በተጠቀሱት ቦታዎች የኃይል አቅርቦት መቋረጡ ተገልጿል።
በስርቆት ምክንያት ከወደቀው አንድ ምሰሶ በተጨማሪ ሰባት የኃይል ተሸካሚ ምሰሶዎች በአስጊ ሁኔታ ላይ ይገኛሉ ተብሏል።
ጉዳት የደረሰበትን የኃይል ተሸካሚ ምሰሶ ለመቀየር የቴክኒክ ባለሙያዎች ቡድን ተዋቅሮ ወደ ሥራ መግባቱ ተገልጿል።
ስርቆት የተፈፀመበት የኃይል ተሸካሚ ምሰሶ ጥምር የኤሌክትሪክ መስመሮችን የያዘ በመሆኑ የጥገና ሥራው ከ20 ቀን ያላነሰ ጊዜ ሊወስድ እንደሚችል ተመላክቷል።
የጥገና ሥራው ሙሉ በሙሉ እስከሚጠናቀቅ ድረስም ከመስመሩ ኃይል ሲያገኙ ለነበሩ ከተሞችና አካባቢዎች በፈረቃ ኤሌክትሪክ እንዲያገኙ ለማድረግ ጥረቶች ይደረጋሉ ተብሏል።
ህብረተሰቡ የተፈጠረውን ችግር ተረድቶ በትዕግስት እንዲጠብቅ ተቋሙ መልዕክት አስተላልፏል።
በሌላ በኩል ፥ ከመተሃራ - አዋሽ ባለ 132 ኪሎ ቮልት የባቡር መስመር ላይ በሚገኙ 9 የኃይል ተሸካሚ ምሰሶዎች ላይ ጉዳት መድረሱ ተገልጿል።
የጥገና ሥራዎችን ለማከናወን ርብርብ እየተደረገ ነው ተብሏል።
በአዋሽ ፈንታሌ ወረዳ በኃይል ማስተላለፊያ ተሸካሚ ምሰሶ አካላት ላይ እየተፈፀሙ የሚገኙ የስርቆት ወንጀሎች መበራከታቸው የገለጸው ተቋሙ ፦
- የአካባቢው ማህበረሰብ፣
- የመስተዳድር
- የፀጥታ አካላት ለኃይል መሰረተ ልማቶቹ ተገቢውን ጥበቃና ትኩረት እንዲሰጡ ጥሪ አቅርቧል።
@tikvahethiopia
ከቆቃ-ሁርሶ ባለ 230 ኪሎ ቮልት ጥምር የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ላይ በተፈፀመ ስርቆት ኃይል መቋረጡን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አሳውቋል።
ኃይል የተቋረጠው በአፋር ክልል አዋሽ ፈንታሌ ወረዳ በንቲ ቀበሌ ልዩ ስሙ አዋሽ ፓርክ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ በአንድ የኃይል ተሸካሚ ምሰሶ ላይ በተፈፀመ ስርቆት ምክንያት ነው።
የኃይል ማስተላለፊያ መስመሩ ፦
- በምስራቅ የሃገሪቱ ክፍል ለሚገኙ ከተሞችና አካባቢዎች፣
- ለአዲስ አበባ- ጅቡቲ የባቡር መስመር
- ለጅቡቲ የኤሌክትሪክ ኃይል እያቀረበ ነበር።
በደረሰው ጉዳት ምክንያት በተጠቀሱት ቦታዎች የኃይል አቅርቦት መቋረጡ ተገልጿል።
በስርቆት ምክንያት ከወደቀው አንድ ምሰሶ በተጨማሪ ሰባት የኃይል ተሸካሚ ምሰሶዎች በአስጊ ሁኔታ ላይ ይገኛሉ ተብሏል።
ጉዳት የደረሰበትን የኃይል ተሸካሚ ምሰሶ ለመቀየር የቴክኒክ ባለሙያዎች ቡድን ተዋቅሮ ወደ ሥራ መግባቱ ተገልጿል።
ስርቆት የተፈፀመበት የኃይል ተሸካሚ ምሰሶ ጥምር የኤሌክትሪክ መስመሮችን የያዘ በመሆኑ የጥገና ሥራው ከ20 ቀን ያላነሰ ጊዜ ሊወስድ እንደሚችል ተመላክቷል።
የጥገና ሥራው ሙሉ በሙሉ እስከሚጠናቀቅ ድረስም ከመስመሩ ኃይል ሲያገኙ ለነበሩ ከተሞችና አካባቢዎች በፈረቃ ኤሌክትሪክ እንዲያገኙ ለማድረግ ጥረቶች ይደረጋሉ ተብሏል።
ህብረተሰቡ የተፈጠረውን ችግር ተረድቶ በትዕግስት እንዲጠብቅ ተቋሙ መልዕክት አስተላልፏል።
በሌላ በኩል ፥ ከመተሃራ - አዋሽ ባለ 132 ኪሎ ቮልት የባቡር መስመር ላይ በሚገኙ 9 የኃይል ተሸካሚ ምሰሶዎች ላይ ጉዳት መድረሱ ተገልጿል።
የጥገና ሥራዎችን ለማከናወን ርብርብ እየተደረገ ነው ተብሏል።
በአዋሽ ፈንታሌ ወረዳ በኃይል ማስተላለፊያ ተሸካሚ ምሰሶ አካላት ላይ እየተፈፀሙ የሚገኙ የስርቆት ወንጀሎች መበራከታቸው የገለጸው ተቋሙ ፦
- የአካባቢው ማህበረሰብ፣
- የመስተዳድር
- የፀጥታ አካላት ለኃይል መሰረተ ልማቶቹ ተገቢውን ጥበቃና ትኩረት እንዲሰጡ ጥሪ አቅርቧል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#DV2026 የ2026 የአሜሪካ ዳይቨርሲቲ ቪዛ (DV) ማመልከቻ ከነገ ጀምሮ ክፍት ይደረጋል። ለ2026 የፊስካል ዓመት እስከ 55,000 የዳይቨርሲቲ ቪዛ (DV) አዘጋጅታለች። ለማመልከት ምንም አይነት ክፍያ አያስፈልግም። አሜሪካ በየዓመቱ ከኢትዮጵያ ጨምሮ ከተለያዩ ሀገራት በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎችን በዳይቨርሲቲ ቪዛ (DV) አማካኝነት እንደምትቀበል ይታወቃል። በነገው ዕለት ዝርዝር መረጃ የምንልክላችሁ…
#DV2026
የ2026 የአሜሪካ ዳይቨርሲቲ ቪዛ (DV) ማመልከቻ ከዛሬ ጀምሮ ክፍት ተደርጓል።
ለ2026 DV ለማመልከት https://dvprogram.state.gov/ ይጠቀሙ።
ለማመልከት ምንም አይነት ክፍያ አያስፈልግም።
ማመልከቻው እስከ ህዳር 5 /2024 ድረስ ክፍት ሆኖ ይቆያል።
ከፍተኛ የመሙላት ፍላጎቶች ድረገጹ ላይ መዘግየቶችን ሊያስከትል ስለሚችል ለመሙላት እስከ የምዝገባው ጊዜ የመጨረሻ ሳምንት ድረስ ባይጠብቁ ይመከራል።
ዘግይተው የሚገቡ ማመልከቻዎች ተቀባይነት አይኖራቸውም።
ህጉ ለአንድ ሰው አንድ ጊዜ ብቻ እንዲያመለክት ነው የሚፈቅደው። የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት የሚጠቀመው የተራቀቀ ቴክኖሎጂ ደጋግሞ የሚገቡ ማመልከቻዎችን የሚለይ ነው። ከአንድ ጊዜ በላይ አንድ ሰው ካመለከተ ሁሉንም የዛን ሰዎች ማመልከቻዎች ይሰርዛል።
ያልተሟላ ማመልከቻም ተቀባይነት የለውም።
ዳይቨርሲቲ ቪዛ (DV) ከቪዛ አማካሪዎች ፣ ' እንሞላለን ' ከሚሉ ወኪሎችና ከሌሎች አካላት እገዛ ሳይጠይቁ ራስዎ እንዲሞሉ ይመከራል።
ማመልከቻውን እንዲሞላሎት የሰው እርዳታ ካስፈለገ ጥያቄዎችን በትክክል ለመመለስ በሚሞላበት ስፍራ መገኘት ያስፈልጋል። ከዚህ በተጨማሪም የ ' ልዩ ማረጋገጫ ቁጥሩ ' ን ለመያዝ በስፍራው መገኝት ያስፈልጋል።
አንዳንድ የሚሞሉ ሰዎች ይህን ቁጥር ይዘው በመቀየር ተጨማሪ ብር የሚጠይቁ ስላሉ እንዳይታለሉ መጠንቀቅ ያስፈልጋል።
የማረጋገጫ ቁጥሩ እጅግ ወሳኝ በመሆኑ በጥንቃቄ መያዝ አለበት።
ለ2026 የፊስካል ዓመት እስከ 55,000 የሚደርስ የዳይቨርሲቲ ቪዛ (DV) ተዘጋጅቷል። ይህ ቁጥር ብቁ የሆኑ ሀገራት ሁሉ የሚጠቃልል ነው።
ኢትዮጵያውያንም ለማመልከት ብቁ ናቸው።
አሜሪካ በየዓመቱ ከኢትዮጵያ ጨምሮ ከተለያዩ ሀገራት በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎችን በዳይቨርሲቲ ቪዛ (DV) አማካኝነት እንደምትቀበል ይታወቃል።
🇺🇸 ለአሜሪካ ዳይቨርሲቲ ቪዛ 2026 ለማመልከት ይህንን dvprogram.state.gov ሊንክ ይጠቀሙ !🇺🇸
(ተጨማሪ ማብራሪያ እና እንዴት መሙላት እንደሚቻል የሚገልጽ መመሪያ በቀጣይ እናያይዛለን)
#TikvahEthiopia
@tikvahethiopia
የ2026 የአሜሪካ ዳይቨርሲቲ ቪዛ (DV) ማመልከቻ ከዛሬ ጀምሮ ክፍት ተደርጓል።
ለ2026 DV ለማመልከት https://dvprogram.state.gov/ ይጠቀሙ።
ለማመልከት ምንም አይነት ክፍያ አያስፈልግም።
ማመልከቻው እስከ ህዳር 5 /2024 ድረስ ክፍት ሆኖ ይቆያል።
ከፍተኛ የመሙላት ፍላጎቶች ድረገጹ ላይ መዘግየቶችን ሊያስከትል ስለሚችል ለመሙላት እስከ የምዝገባው ጊዜ የመጨረሻ ሳምንት ድረስ ባይጠብቁ ይመከራል።
ዘግይተው የሚገቡ ማመልከቻዎች ተቀባይነት አይኖራቸውም።
ህጉ ለአንድ ሰው አንድ ጊዜ ብቻ እንዲያመለክት ነው የሚፈቅደው። የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት የሚጠቀመው የተራቀቀ ቴክኖሎጂ ደጋግሞ የሚገቡ ማመልከቻዎችን የሚለይ ነው። ከአንድ ጊዜ በላይ አንድ ሰው ካመለከተ ሁሉንም የዛን ሰዎች ማመልከቻዎች ይሰርዛል።
ያልተሟላ ማመልከቻም ተቀባይነት የለውም።
ዳይቨርሲቲ ቪዛ (DV) ከቪዛ አማካሪዎች ፣ ' እንሞላለን ' ከሚሉ ወኪሎችና ከሌሎች አካላት እገዛ ሳይጠይቁ ራስዎ እንዲሞሉ ይመከራል።
ማመልከቻውን እንዲሞላሎት የሰው እርዳታ ካስፈለገ ጥያቄዎችን በትክክል ለመመለስ በሚሞላበት ስፍራ መገኘት ያስፈልጋል። ከዚህ በተጨማሪም የ ' ልዩ ማረጋገጫ ቁጥሩ ' ን ለመያዝ በስፍራው መገኝት ያስፈልጋል።
አንዳንድ የሚሞሉ ሰዎች ይህን ቁጥር ይዘው በመቀየር ተጨማሪ ብር የሚጠይቁ ስላሉ እንዳይታለሉ መጠንቀቅ ያስፈልጋል።
የማረጋገጫ ቁጥሩ እጅግ ወሳኝ በመሆኑ በጥንቃቄ መያዝ አለበት።
ለ2026 የፊስካል ዓመት እስከ 55,000 የሚደርስ የዳይቨርሲቲ ቪዛ (DV) ተዘጋጅቷል። ይህ ቁጥር ብቁ የሆኑ ሀገራት ሁሉ የሚጠቃልል ነው።
ኢትዮጵያውያንም ለማመልከት ብቁ ናቸው።
አሜሪካ በየዓመቱ ከኢትዮጵያ ጨምሮ ከተለያዩ ሀገራት በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎችን በዳይቨርሲቲ ቪዛ (DV) አማካኝነት እንደምትቀበል ይታወቃል።
🇺🇸 ለአሜሪካ ዳይቨርሲቲ ቪዛ 2026 ለማመልከት ይህንን dvprogram.state.gov ሊንክ ይጠቀሙ !🇺🇸
(ተጨማሪ ማብራሪያ እና እንዴት መሙላት እንደሚቻል የሚገልጽ መመሪያ በቀጣይ እናያይዛለን)
#TikvahEthiopia
@tikvahethiopia
#MesiratEthiopia
📢 በሐዋሳ እና በድሬዳዋ ለምትገኙ ወጣቶች በሙሉ!
የመስራት የወጣቶች መማክርት ቡድን (M-YAG) አባል በመሆን ለለውጥ ድምጽ ሁኑ !
M-YAG ከቡድን በላይ ነው፤ በመስራት ፕሮግራም ውስጥ የወጣቶችን ድምጽ ለማሰማት የተዘጋጀ እንቅስቃሴ ነው።
ከ 15 እስከ 35 እድሜ የሆኑ ለመምራት፣ ለማነሳሳት እና በማህበረሰቦቻቸው ላይ አዎንታዊ ተፅዕኖ ለማሳደር ዝግጁ የሆኑ ወጣቶችን እየፈለግን ነው። በM-YAG በኩል በዋጋ ሊተመን የማይችል የግል እና ሙያዊ ክህሎቶችን ታገኛላችሁ፣ ጠንካራ አመራር ላይ ቁርጠኛ የሆነ ቡድን አካል ትሆናላችሁ።
ተጽዕኖ ለማሳደር ዝግጁ ከሆናችሁ እዚህ ተመዝገቡ፥ https://forms.gle/pd3JLtHM1u1fDD4D6
#MYAG #መስራት #Hawassa #ሐዋሳ #DireDawa #ድሬዳዋ
📢 በሐዋሳ እና በድሬዳዋ ለምትገኙ ወጣቶች በሙሉ!
የመስራት የወጣቶች መማክርት ቡድን (M-YAG) አባል በመሆን ለለውጥ ድምጽ ሁኑ !
M-YAG ከቡድን በላይ ነው፤ በመስራት ፕሮግራም ውስጥ የወጣቶችን ድምጽ ለማሰማት የተዘጋጀ እንቅስቃሴ ነው።
ከ 15 እስከ 35 እድሜ የሆኑ ለመምራት፣ ለማነሳሳት እና በማህበረሰቦቻቸው ላይ አዎንታዊ ተፅዕኖ ለማሳደር ዝግጁ የሆኑ ወጣቶችን እየፈለግን ነው። በM-YAG በኩል በዋጋ ሊተመን የማይችል የግል እና ሙያዊ ክህሎቶችን ታገኛላችሁ፣ ጠንካራ አመራር ላይ ቁርጠኛ የሆነ ቡድን አካል ትሆናላችሁ።
ተጽዕኖ ለማሳደር ዝግጁ ከሆናችሁ እዚህ ተመዝገቡ፥ https://forms.gle/pd3JLtHM1u1fDD4D6
#MYAG #መስራት #Hawassa #ሐዋሳ #DireDawa #ድሬዳዋ
#ባይቶና
" በትግራይ ያጋጠመው ፓለቲካዊ ብልሽት የሚያጠራ ብሄራዊ እርቅ ያስፈልጋል " - ባይቶና ፓርቲ
ብሄራዊ ባይቶ ዓባይ ትግራይ (ባይቶና) የፓለቲካ ፓርቲ በክልሉ ወቅታዊ የፓለቲካ ሁኔታ አስመልክቶ በሰጠው መግለጫ " በትግራይ ያጋጠመው ፓለቲካዊ ብልሽት የሚፈታ ብሄራዊ የእርቅ ምክር ቤት ያስፈልጋል " ብሏል።
ብሄራዊ የዕርቅ ምክር ቤት በአስቸኳይ እንዲቋቋም የጠየቁት የባይቶና ፓርቲ ሊቀመንበር ክብሮም በርሀ ፥ ምክር ቤቱን የማቋቋም ሃላፊነት ለጊዚያዊ አስተዳደሩ ይሰጥ ብሏል።
የትግራይ ጥቅም የሚያረጋግጥ ብሄራዊ ዕርቅ ማካሄድ እጅግ አስፈላጊ መሆኑ የገለፁት ሊቀመንበሩ እርቅ ሲባል በልሂቃን መካከል የሚፈፀም እንደሆነ አብራርተዋል።
" የተፈጠረው መገፋፋት የትግራይ ብሄራዊ ጥቅም ወደ አደጋ እያስገባው ነው " ያሉት አቶ ክብሮም " ከመጠፋፋት ፓለቲካ ወጥተን የሰለጠነ ፓለቲካ ማራመድ አለብን " በማለት ተናግረዋል።
" ጊዚያዊ አስተዳደሩ የአንድ ቡድን ሳይሆን የጀግኖች ደም ባረጋገጠው የፕሪቶሪያ ስምምነት እውቅና ያለው ነው " ያሉት አቶ ክብሮም " ጊዚያዊ አስተዳደሩ እንዳሻን የምንገነባውና የምናፈርሰው ሳይሆን ፀጋዎቹን አሟጠን በመጠቀም የህዝባችን ድህንነት ማረጋገጠረ አለብን ' ማለታቸው ቲክሻህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ ዘግቧል።
@tikvahethiopia
" በትግራይ ያጋጠመው ፓለቲካዊ ብልሽት የሚያጠራ ብሄራዊ እርቅ ያስፈልጋል " - ባይቶና ፓርቲ
ብሄራዊ ባይቶ ዓባይ ትግራይ (ባይቶና) የፓለቲካ ፓርቲ በክልሉ ወቅታዊ የፓለቲካ ሁኔታ አስመልክቶ በሰጠው መግለጫ " በትግራይ ያጋጠመው ፓለቲካዊ ብልሽት የሚፈታ ብሄራዊ የእርቅ ምክር ቤት ያስፈልጋል " ብሏል።
ብሄራዊ የዕርቅ ምክር ቤት በአስቸኳይ እንዲቋቋም የጠየቁት የባይቶና ፓርቲ ሊቀመንበር ክብሮም በርሀ ፥ ምክር ቤቱን የማቋቋም ሃላፊነት ለጊዚያዊ አስተዳደሩ ይሰጥ ብሏል።
የትግራይ ጥቅም የሚያረጋግጥ ብሄራዊ ዕርቅ ማካሄድ እጅግ አስፈላጊ መሆኑ የገለፁት ሊቀመንበሩ እርቅ ሲባል በልሂቃን መካከል የሚፈፀም እንደሆነ አብራርተዋል።
" የተፈጠረው መገፋፋት የትግራይ ብሄራዊ ጥቅም ወደ አደጋ እያስገባው ነው " ያሉት አቶ ክብሮም " ከመጠፋፋት ፓለቲካ ወጥተን የሰለጠነ ፓለቲካ ማራመድ አለብን " በማለት ተናግረዋል።
" ጊዚያዊ አስተዳደሩ የአንድ ቡድን ሳይሆን የጀግኖች ደም ባረጋገጠው የፕሪቶሪያ ስምምነት እውቅና ያለው ነው " ያሉት አቶ ክብሮም " ጊዚያዊ አስተዳደሩ እንዳሻን የምንገነባውና የምናፈርሰው ሳይሆን ፀጋዎቹን አሟጠን በመጠቀም የህዝባችን ድህንነት ማረጋገጠረ አለብን ' ማለታቸው ቲክሻህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ ዘግቧል።
@tikvahethiopia
#እንድታውቁት
በአዲስ አበባ ከነገ ጀምሮ የሚዘጉ መንገዶች ይፋ ሆነዋል።
ከኢሬቻ ሆራ ፊንፊኔ በዓል ጋር በተያያዘ ለተሽከርካሪ ዝግ የሚሆኑ መንገዶችን የአዲስ አበባ ፖሊስ ይፋ አድርጓል።
የኢሬቻ ሆራ ፊንፊኔ በዓል መስከረም 25/ 2017 ዓ/ም በአዲስ አበባ ይከበራል ፤ ይህን ተከትሎ የሚከተሉት መንገዶች ይዘጋሉ።
- ከቅዱስ ኡራኤል አደባባይ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ቅዱስ ኡራኤል አደባባይ ላይ፤
- ከቦሌ አቅጣጫ ወደ መስቀል አደባባይ ለሚመጡ ተሽከርካሪዎች ኦሎምፒያ አደባባይ ላይና ታች እንዲሁም ግራና ቀኝ፤
- ከመስቀል ፍላወር ወደ ኦሎምፒያ የሚወስደው መንገድ ጋዜቦ አደባባይ ላይ፤
- ከአጎና ሲኒማ ወደ መስቀል አደባባይ ለከባድ ተሽከርካሪ አጎና ሲኒማ አጠገብ እንዲሁም ለቀላል ተሽከርካሪ ጥላሁን አደባባይ (አራተኛ ክፍለ ጦር ላይ)፤
- ከለገሀር መብራት ወደ መስቀል አደባባይ ለገሀር መብራት ላይ፤
- ከቴሌ ማቋረጫ ወደ ስታድዮም ለሚጓዙ ቴሌ ማቋረጫ፤
- ከራስ ሆቴል ወደ ስታድዮም ለሚመጡ ተሽከርካሪዎች ራስ ሆቴል ላይ፤
- ከሃራምቤ መብራት ወይም ከአምባሳደር ሲኒማ ወደ መስቀል አደባባይ ሃራምቤ መብራት ላይ፤
- ከብሔራዊ ቤተ መንግስት ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ብሔራዊ ቤተ መንግስት አጠገብ፤
- ከካዛንቺስ ሼል ወደ ባምቢስ የሚወስደው መንገድ ካዛንቺስ ሼል አጠገብ፤
- ከጁፒተር ሆቴል ወደ ECA የሚወስደው መንገድ ባምቢስ ሳልኮት ህንፃ አጠገብ፤
ከመስከረም 24/ 2017 ዓ/ም ከቀኑ 6፡00 ሰዓት ጀምሮ ፕሮግራሙ እስከሚጠናቀቅ ድረስ መንገዶቹ ለተሽከርካሪ ዝግ እንደሚሆኑ ተገልጿል።
በዓሉ በሚከበርበት ዙሪያና በአካባቢው በግራና በቀኝ ለረጅምም ሆነ ለአጭር ጊዜ ተሽከርካሪ አቁሞ መሄድ ፍፁም የተከለከለ ነው ተብሏል።
ህብረተሰቡ ለፀጥታ ስጋት የሆኑ አጠራጣሪ ነገሮች ሲያጋጥሙት በ011-1-11-01-11 እንዲሁም በ991 ነፃ የስልክ መስመር ጥቆማ መስጠት ይችላል።
#AddisAbabaPolice
@tikvahethiopia
በአዲስ አበባ ከነገ ጀምሮ የሚዘጉ መንገዶች ይፋ ሆነዋል።
ከኢሬቻ ሆራ ፊንፊኔ በዓል ጋር በተያያዘ ለተሽከርካሪ ዝግ የሚሆኑ መንገዶችን የአዲስ አበባ ፖሊስ ይፋ አድርጓል።
የኢሬቻ ሆራ ፊንፊኔ በዓል መስከረም 25/ 2017 ዓ/ም በአዲስ አበባ ይከበራል ፤ ይህን ተከትሎ የሚከተሉት መንገዶች ይዘጋሉ።
- ከቅዱስ ኡራኤል አደባባይ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ቅዱስ ኡራኤል አደባባይ ላይ፤
- ከቦሌ አቅጣጫ ወደ መስቀል አደባባይ ለሚመጡ ተሽከርካሪዎች ኦሎምፒያ አደባባይ ላይና ታች እንዲሁም ግራና ቀኝ፤
- ከመስቀል ፍላወር ወደ ኦሎምፒያ የሚወስደው መንገድ ጋዜቦ አደባባይ ላይ፤
- ከአጎና ሲኒማ ወደ መስቀል አደባባይ ለከባድ ተሽከርካሪ አጎና ሲኒማ አጠገብ እንዲሁም ለቀላል ተሽከርካሪ ጥላሁን አደባባይ (አራተኛ ክፍለ ጦር ላይ)፤
- ከለገሀር መብራት ወደ መስቀል አደባባይ ለገሀር መብራት ላይ፤
- ከቴሌ ማቋረጫ ወደ ስታድዮም ለሚጓዙ ቴሌ ማቋረጫ፤
- ከራስ ሆቴል ወደ ስታድዮም ለሚመጡ ተሽከርካሪዎች ራስ ሆቴል ላይ፤
- ከሃራምቤ መብራት ወይም ከአምባሳደር ሲኒማ ወደ መስቀል አደባባይ ሃራምቤ መብራት ላይ፤
- ከብሔራዊ ቤተ መንግስት ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ብሔራዊ ቤተ መንግስት አጠገብ፤
- ከካዛንቺስ ሼል ወደ ባምቢስ የሚወስደው መንገድ ካዛንቺስ ሼል አጠገብ፤
- ከጁፒተር ሆቴል ወደ ECA የሚወስደው መንገድ ባምቢስ ሳልኮት ህንፃ አጠገብ፤
ከመስከረም 24/ 2017 ዓ/ም ከቀኑ 6፡00 ሰዓት ጀምሮ ፕሮግራሙ እስከሚጠናቀቅ ድረስ መንገዶቹ ለተሽከርካሪ ዝግ እንደሚሆኑ ተገልጿል።
በዓሉ በሚከበርበት ዙሪያና በአካባቢው በግራና በቀኝ ለረጅምም ሆነ ለአጭር ጊዜ ተሽከርካሪ አቁሞ መሄድ ፍፁም የተከለከለ ነው ተብሏል።
ህብረተሰቡ ለፀጥታ ስጋት የሆኑ አጠራጣሪ ነገሮች ሲያጋጥሙት በ011-1-11-01-11 እንዲሁም በ991 ነፃ የስልክ መስመር ጥቆማ መስጠት ይችላል።
#AddisAbabaPolice
@tikvahethiopia
#DStvEthiopia
💥ማን ዩናይትድ ከ ቶተንሃም 0-3 ሸንፈት በኋካ ዛሬ ምሽት ወደ ፖርቹጋል ተጉዞ ከፖርቶ ጋር ይጫወታል!
ዩናይትድ ወደ አሸናፊነት መንገድ ይመለሳል?
👉 ዛሬውኑ ፓኬጅዎን ያሳድጉ ጨዋታዎችን ከትንታኔ ፣ ከተጫዋች ብቃት እስከ ቡድን ወኔ በሜዳ ፕላስ ፓኬጅ ይከታተሉ!
ደንብና ሁኔታዎች ተፈፀሚነት አላቸው! ለበለጠ መረጃ
👇
www.dstv.com/en-et
ዲኤስቲቪ ያስገቡ ፣ ደንበኝነትዎን ያራዝሙ!
👇
https://bit.ly/3RFtEvh
#ChampionsLeagueAllonDStv #ሁሉምያለውእኛጋርነው #DStvSelfServiceET
💥ማን ዩናይትድ ከ ቶተንሃም 0-3 ሸንፈት በኋካ ዛሬ ምሽት ወደ ፖርቹጋል ተጉዞ ከፖርቶ ጋር ይጫወታል!
ዩናይትድ ወደ አሸናፊነት መንገድ ይመለሳል?
👉 ዛሬውኑ ፓኬጅዎን ያሳድጉ ጨዋታዎችን ከትንታኔ ፣ ከተጫዋች ብቃት እስከ ቡድን ወኔ በሜዳ ፕላስ ፓኬጅ ይከታተሉ!
ደንብና ሁኔታዎች ተፈፀሚነት አላቸው! ለበለጠ መረጃ
👇
www.dstv.com/en-et
ዲኤስቲቪ ያስገቡ ፣ ደንበኝነትዎን ያራዝሙ!
👇
https://bit.ly/3RFtEvh
#ChampionsLeagueAllonDStv #ሁሉምያለውእኛጋርነው #DStvSelfServiceET
“ለፒኤችዲ የሚመጡት ተማሪዎች የኑሮ ሁኔታ ዩኒቨርሲቲው ለብቻው ሶልቭ የሚያደርገው አይደለም፡፡ አጠቃላይ የአገሪቷ ችግር ነው ” - አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ
በአንጋፋውና ራስ ገዙ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የፒኤችዲ ትምህርታቸውን የሚማሩ ቤተሰብ ጭምር የሚያስተዳድሩ ተማሪዎች ኑሮው እጅግ ፈታኝ እንደሆነባቸው በምሬት ሲገልጹ ተስትውለዋል፡፡
ትምህርትቻውን የሚከታተሉት ለዛውም ሲያገኙ ሻይ በዳቦ እየተመገቡ፣ መቀየሪያ አጥተው ለበርካታ ጊዜ አንድ ልብስ ለብሰውና አንድ ጫማ ተጫምተው እንደሆነ ያነሳሉ።
በዚህም ሃፍረትና የዝቅተኝነት ስሜት አሸማቋቸው የሚያውቋቸውን ሰዎች ሲያዩ መንገድ ቀይሰው ለመሄድ፣ ቤተሰብ ላለመጠየቅ እንደተገደዱ በተሰበረ ድምጽ እሮሮ እያቀረቡ ነው፡፡
ይህንኑ ቅሬታ በተመለከተ ቲክቫህ ኢትዮጵያ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ምን አስተያየት እንዳለው ተጠይቆ ምላሽ ሰጥቷል፡፡
ምን አለ ?
“ ችግሩ ለአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ብቻ አይደለም፡፡ አጠቃላይ ችግር ነው፡፡
ነገር ግን የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በተለይ ለድኀረ ምረቃ ፕሮግራም በተቻለ አቅም ለመፍታት ካደረጋቸው አንዱ ጥረት በአነስተኛ ኪራይ የመኖሪያ ክፍሎችን (ዶርሚተሪ) ማዘጋጀት ነው፡፡
በግል በከተማ ውስጥ እንከራይ ቢባል ክራይስ እንደሚያመጣ ማንም ሰው መገመት የሚያቅተው አይደለምና አንዱ የዩቨርሲቲው ኮንትሪቢሽን በቀላሉ የፒኤችዲ ተማሪዎች ዶርም እንዲይዙ ማድረግ ነው፡፡
በዩኒቨርሲቲ ውስጥ በሚኖሩት የጥናትና ምርምር ሥራዎችም እንዲሳተፉ እያደረገም ነው ያደርጋልም፡፡
የፒኤችዲ ተማሪዎች በዩኒቨርሲቲው ፕሮግራም ውስጥ መማር ማስተማር በተወሰነ ደረጃ እስከ 3 ክሬዲት ሊሆን የሚችል ሎድ እንዲይዝ ነው የተደረገው፡፡ ይሄም ከመደገፍ አንጻር ሊታይ ይገባል፡፡
እንደ አጠቃላይ ለፒኤችዲ የሚመጡት ተማሪዎች የኑሮ ሁኔታ ዩኒቨርሲቲው ለብቻው ሶልቭ የሚያደርገው አይደለም፡፡ አጠቃላይ የአገሪቷ ችግር ነው፡፡
ከዛ ውጪ ዩኒቨርሲቲው ባለው አቅም ለመደገፍና ሁኔታዎችን ለማመቻቸት ፋላጎትና አቅም ኖሮት የያዘው አይደለም። ማድረግ የሚችለውን እያጣረ፣ መደገፍ የሚችለውን እያደገ ነው ያለው” ብሏል፡፡
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
በአንጋፋውና ራስ ገዙ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የፒኤችዲ ትምህርታቸውን የሚማሩ ቤተሰብ ጭምር የሚያስተዳድሩ ተማሪዎች ኑሮው እጅግ ፈታኝ እንደሆነባቸው በምሬት ሲገልጹ ተስትውለዋል፡፡
ትምህርትቻውን የሚከታተሉት ለዛውም ሲያገኙ ሻይ በዳቦ እየተመገቡ፣ መቀየሪያ አጥተው ለበርካታ ጊዜ አንድ ልብስ ለብሰውና አንድ ጫማ ተጫምተው እንደሆነ ያነሳሉ።
በዚህም ሃፍረትና የዝቅተኝነት ስሜት አሸማቋቸው የሚያውቋቸውን ሰዎች ሲያዩ መንገድ ቀይሰው ለመሄድ፣ ቤተሰብ ላለመጠየቅ እንደተገደዱ በተሰበረ ድምጽ እሮሮ እያቀረቡ ነው፡፡
ይህንኑ ቅሬታ በተመለከተ ቲክቫህ ኢትዮጵያ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ምን አስተያየት እንዳለው ተጠይቆ ምላሽ ሰጥቷል፡፡
ምን አለ ?
“ ችግሩ ለአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ብቻ አይደለም፡፡ አጠቃላይ ችግር ነው፡፡
ነገር ግን የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በተለይ ለድኀረ ምረቃ ፕሮግራም በተቻለ አቅም ለመፍታት ካደረጋቸው አንዱ ጥረት በአነስተኛ ኪራይ የመኖሪያ ክፍሎችን (ዶርሚተሪ) ማዘጋጀት ነው፡፡
በግል በከተማ ውስጥ እንከራይ ቢባል ክራይስ እንደሚያመጣ ማንም ሰው መገመት የሚያቅተው አይደለምና አንዱ የዩቨርሲቲው ኮንትሪቢሽን በቀላሉ የፒኤችዲ ተማሪዎች ዶርም እንዲይዙ ማድረግ ነው፡፡
በዩኒቨርሲቲ ውስጥ በሚኖሩት የጥናትና ምርምር ሥራዎችም እንዲሳተፉ እያደረገም ነው ያደርጋልም፡፡
የፒኤችዲ ተማሪዎች በዩኒቨርሲቲው ፕሮግራም ውስጥ መማር ማስተማር በተወሰነ ደረጃ እስከ 3 ክሬዲት ሊሆን የሚችል ሎድ እንዲይዝ ነው የተደረገው፡፡ ይሄም ከመደገፍ አንጻር ሊታይ ይገባል፡፡
እንደ አጠቃላይ ለፒኤችዲ የሚመጡት ተማሪዎች የኑሮ ሁኔታ ዩኒቨርሲቲው ለብቻው ሶልቭ የሚያደርገው አይደለም፡፡ አጠቃላይ የአገሪቷ ችግር ነው፡፡
ከዛ ውጪ ዩኒቨርሲቲው ባለው አቅም ለመደገፍና ሁኔታዎችን ለማመቻቸት ፋላጎትና አቅም ኖሮት የያዘው አይደለም። ማድረግ የሚችለውን እያጣረ፣ መደገፍ የሚችለውን እያደገ ነው ያለው” ብሏል፡፡
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Djibouti 45 ስደተኞች ህይወታቸው ማለፉ ተሰማ። ከየመን 310 ስደተኞችን በመጫን በጉዞ ላይ የነበሩ ሁለት ጀልባዎች ሰጥመው እስካሁን ባለው 45 ሰዎች መሞታቸውን ዓለም አቀፉ የስደተኞች ድርጅት (IOM) አስታውቋል። የጅቡቲ የባህር ጠረፍ ጠባቂ እንዳስታወቀው አደጋው በሰሜናዊ ምዕራብ ሖር አንጋር አካባቢ ካለው የባህር ዳርቻ 150 ሜትሮች ርቆ ነው የተከሰተው። ከሰኞ ጀምሮ በተደረገው ፍለጋ…
" የሞቱት ሁሉም ኢትዮጵያውያን ናቸው " - በጅቡቲ የሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ
ሰሞኑን በጅቡቲ የባህር ዳርቻ በደረሰው የጀልባ መስጠም አደጋ በአደጋው የሞቱት ዜጎች በሙሉ ኢትዮጵያውያን መሆናቸው መረጋጋገጡን በጅቡቲ የኢትዮጵያ ኤምባሲ አስታውቋል፡፡
መስከረም 21 ቀን 2017 ዓ.ም ማምሻውን ከየመን ወደ ጅቡቲ 320 መደበኛ ያልሆኑ ፍልሰተኞች ይዘው የተነሱት ሁለት የስደተኞች ጀልባዎች በጅቡቲ ባህር ዳርቻ አከባቢ ሲደርሱ በደረሰው አደጋ የበርካቶች ህይወት ማለፉ ይታወሳል።
አደጋውን ተከትሎ 48 ፍልሰተኞች ህይወታቸው ሲያልፍ፣ 197 ፍልሰተኞች ከአደጋው ተርፈው ኦቦክ የሚገኘው ዓለም አቀፉ የስደተኞች ካምፕ መድረሳቸው ተጠቅሷል።
የተቀሩት 75 ፍልሰተኞችን አካል የማፈላለጉ ስራ በነፍስ አድን ሠራተኞች መቀጠሉ ተጠቁሟል።
እስከአሁን በስፍራው በተደረገው የዜጎች ማጣራት ሂደት ሁሉም ፍልሰተኞች ኢትዮጵያውያን መሆናቸውን ከሚመለከተው አካላት በተገኘው መረጃ ማወቅ መቻሉን በጅቡቲ የኢትዮጵያ ኤምባሲ ገልጿል።
@tikvahethiopia
ሰሞኑን በጅቡቲ የባህር ዳርቻ በደረሰው የጀልባ መስጠም አደጋ በአደጋው የሞቱት ዜጎች በሙሉ ኢትዮጵያውያን መሆናቸው መረጋጋገጡን በጅቡቲ የኢትዮጵያ ኤምባሲ አስታውቋል፡፡
መስከረም 21 ቀን 2017 ዓ.ም ማምሻውን ከየመን ወደ ጅቡቲ 320 መደበኛ ያልሆኑ ፍልሰተኞች ይዘው የተነሱት ሁለት የስደተኞች ጀልባዎች በጅቡቲ ባህር ዳርቻ አከባቢ ሲደርሱ በደረሰው አደጋ የበርካቶች ህይወት ማለፉ ይታወሳል።
አደጋውን ተከትሎ 48 ፍልሰተኞች ህይወታቸው ሲያልፍ፣ 197 ፍልሰተኞች ከአደጋው ተርፈው ኦቦክ የሚገኘው ዓለም አቀፉ የስደተኞች ካምፕ መድረሳቸው ተጠቅሷል።
የተቀሩት 75 ፍልሰተኞችን አካል የማፈላለጉ ስራ በነፍስ አድን ሠራተኞች መቀጠሉ ተጠቁሟል።
እስከአሁን በስፍራው በተደረገው የዜጎች ማጣራት ሂደት ሁሉም ፍልሰተኞች ኢትዮጵያውያን መሆናቸውን ከሚመለከተው አካላት በተገኘው መረጃ ማወቅ መቻሉን በጅቡቲ የኢትዮጵያ ኤምባሲ ገልጿል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Ethiopia " ማንኛውም ማሻሻያ ወይም የደመወዝ ስኬል ለውጥ ካለ ሕጋዊ ሰውነት ባላቸው እና በሚመለከታቸው አካላት ይፋ ይደረጋል " ሲል የሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን አሳውቋል። ውሳኔዎቹ ሲኖሩ በዝርዝር ጥናቶችና የበጀት አጸዳደቅ ሥርዓትን ተከትለው የሚካሄዱ እንደሆኑ ገልጿል። የትኛውንም አይነት መረጃ ሁልጊዜም በቀጥታ ጉዳዩ ከሚመለከታቸው አካላት ማጣራት እና ማገናዘብ ከስህተት ይታደጋልም ብሏል። የትላንትናው…
የመንግሥት_ሰራተኞች_የደመወዝ_ጭማሪ_1.pdf
14.9 MB
#ደመወዝ ፦ ይህ ስለ መንግሥት ሰራተኞች ደመወዝ ጭማሪ የሚያትት ዶክመንት ባለፈው ዓመት ነሃሴ ወር ላይ ሲዘዋወር የነበር ነው።
ዶክመንቱ ከየትኛው አካል የወጣ እንደሆነ በግልጽ አይታወቅም።
በእርግጥም ከዚህ ወር ጀምሮ ወደ ትግበራ የሚገባው የመንግሥት ሰራተኞች ደመወዝ ጭማሪ ይኸው ይሁን ወይስ ሌላ ስለሚለው ጉዳይ ወይም ደግሞ ስለዚህ ዶክመንት ትክክለኝነት ወይም ትክክል አለመሆን በግልጽ ወጥቶ ምላሽ የሰጠ አንድም አካል የለም።
ይህ ዶክመንት ወጥቶ ከመሰራጨቱ በፊት አንድ ስለ ደመወዝ ጭማሪ የሚያትት ምስል ተሰራጭቶ የሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ' ሀሰት ' ነው ማለቱ አይዘነጋም።
ስለዚህ የደመወዝ ጭማሪ ዶክመንት ግን ወጥቶ ያስተባበለ ሆነ ማረጋገጫ የሰጠ አካል የለም።
ይህ ጉዳይ በቀጥታ ይመለከታቸዋል የተባሉ አካላትን በማነጋገር ምላሽ ለማግኘት ጥረት ብናደርግም አልተሳካም።
NB. ከላይ በፋይል የተያያዘው ስለ ደመወዝ ጭማሪ የሚያትተው ዶክመት በቀጥታ ጉዳዩ በሚመላከታቸው የትኛውም አካላት ያልተረጋገጠ ነገር ግን ደግሞ በይፋ ትክክል አይደለም ተብሎ ማስተባበያ ሆነ አስተያየት ያልተሰጠበት ነው።
#Ethiopia
@tikvahethiopia
ዶክመንቱ ከየትኛው አካል የወጣ እንደሆነ በግልጽ አይታወቅም።
በእርግጥም ከዚህ ወር ጀምሮ ወደ ትግበራ የሚገባው የመንግሥት ሰራተኞች ደመወዝ ጭማሪ ይኸው ይሁን ወይስ ሌላ ስለሚለው ጉዳይ ወይም ደግሞ ስለዚህ ዶክመንት ትክክለኝነት ወይም ትክክል አለመሆን በግልጽ ወጥቶ ምላሽ የሰጠ አንድም አካል የለም።
ይህ ዶክመንት ወጥቶ ከመሰራጨቱ በፊት አንድ ስለ ደመወዝ ጭማሪ የሚያትት ምስል ተሰራጭቶ የሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ' ሀሰት ' ነው ማለቱ አይዘነጋም።
ስለዚህ የደመወዝ ጭማሪ ዶክመንት ግን ወጥቶ ያስተባበለ ሆነ ማረጋገጫ የሰጠ አካል የለም።
ይህ ጉዳይ በቀጥታ ይመለከታቸዋል የተባሉ አካላትን በማነጋገር ምላሽ ለማግኘት ጥረት ብናደርግም አልተሳካም።
NB. ከላይ በፋይል የተያያዘው ስለ ደመወዝ ጭማሪ የሚያትተው ዶክመት በቀጥታ ጉዳዩ በሚመላከታቸው የትኛውም አካላት ያልተረጋገጠ ነገር ግን ደግሞ በይፋ ትክክል አይደለም ተብሎ ማስተባበያ ሆነ አስተያየት ያልተሰጠበት ነው።
#Ethiopia
@tikvahethiopia
#ደመወዝ
" የደመወዝ ጭማሪ ዝርዝሩ በቅርቡ በሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን በኩል ይፋ ይደረጋል " - የገንዘብ ሚኒስቴር
የገንዘብ ሚኒስቴር ሚኒስትር አህመድ ሽዴ ፤ ከመስከረም ወር 2017 ጀምሮ የሚጨመር ደመወዝ በካቢኔ መፅደቁን አሳውቀዋል።
ዝቅተኛ ገቢ ያላቸውን ትኩረት ያደረገ የተወሰነ የደመወዝ ጭማሪ መደረጉን አመልክተዋል።
አቶ አህመድ " የተወሰነ የደመወዝ ጭማሪ ለኑሮ ድጎማ ጭምር እንዲሆን ታሳቢ ተደርጎ በካቢኔ ፀድቋል ከመስከረም ወር ጀምሮ ታሳቢ ይደረጋል። የደመወዝ ጭማሪው ከ91 እስከ 92 ቢሊዮን ብር መካከል ተጨማሪ በጀት የሚጠይቅ ይሆናል " ብለዋል።
በነባሩ በጀት የተወሰነ መግባቱን ፤ በተጨማሪ በጀትነትም የሚታወጅ መኖሩን ጠቁመዋል።
" ሲቪል ሰርቫንቱ አጠቃላይ የመንግሥት ሰራተኛው በሁሉም መስክ በፀጥታም በሌሎችም ዘርፍ ያሉትን የኑሮ ጫና ለመቋቋም የሚያስችለውን ድጋፍ ለማድረግ መንግሥት በከፍተኛ ቁርጠኝነት ተገባበት ነው " ሲሉ አቶ አህመድ ተናግረዋል።
" የባለፉት ሁለት ወራት የኢንፍሌሽን አፈጻጸም በሚታይበት ጊዜ እንደተሰጋው አይደለም። የተረጋጋ የዋጋ ሁኔታ ነው ያለው። የተወስነ ጭማሪ በአንዳንድ እቃዎች ላይ እንጂ በአብዛኛው የተረጋጋ ሁኔታ ነው ያለው። " ብለዋል።
" እንደዛም ሆኖ የደመወዝ ጭማሪው እጅግ አስፈላጊ ስለሆነ የሰራተኛውን ቋሚ ደመወዝተኛ ገቢ ያለውን ዝቅተኛውን ትኩረት አድርገን የዝቅተኛውን በጣም ከፍተኛ ጭማሪ አድርገናል የላይኛውን ዝቅተኛ ጭማሪ አድርገን ነው የተሰራው ዝርዝሩ በቅርቡ በሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን በኩል ይፋ ይደረጋል " ሲሉ ተደምጠዋል።
@tikvahethiopia
" የደመወዝ ጭማሪ ዝርዝሩ በቅርቡ በሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን በኩል ይፋ ይደረጋል " - የገንዘብ ሚኒስቴር
የገንዘብ ሚኒስቴር ሚኒስትር አህመድ ሽዴ ፤ ከመስከረም ወር 2017 ጀምሮ የሚጨመር ደመወዝ በካቢኔ መፅደቁን አሳውቀዋል።
ዝቅተኛ ገቢ ያላቸውን ትኩረት ያደረገ የተወሰነ የደመወዝ ጭማሪ መደረጉን አመልክተዋል።
አቶ አህመድ " የተወሰነ የደመወዝ ጭማሪ ለኑሮ ድጎማ ጭምር እንዲሆን ታሳቢ ተደርጎ በካቢኔ ፀድቋል ከመስከረም ወር ጀምሮ ታሳቢ ይደረጋል። የደመወዝ ጭማሪው ከ91 እስከ 92 ቢሊዮን ብር መካከል ተጨማሪ በጀት የሚጠይቅ ይሆናል " ብለዋል።
በነባሩ በጀት የተወሰነ መግባቱን ፤ በተጨማሪ በጀትነትም የሚታወጅ መኖሩን ጠቁመዋል።
" ሲቪል ሰርቫንቱ አጠቃላይ የመንግሥት ሰራተኛው በሁሉም መስክ በፀጥታም በሌሎችም ዘርፍ ያሉትን የኑሮ ጫና ለመቋቋም የሚያስችለውን ድጋፍ ለማድረግ መንግሥት በከፍተኛ ቁርጠኝነት ተገባበት ነው " ሲሉ አቶ አህመድ ተናግረዋል።
" የባለፉት ሁለት ወራት የኢንፍሌሽን አፈጻጸም በሚታይበት ጊዜ እንደተሰጋው አይደለም። የተረጋጋ የዋጋ ሁኔታ ነው ያለው። የተወስነ ጭማሪ በአንዳንድ እቃዎች ላይ እንጂ በአብዛኛው የተረጋጋ ሁኔታ ነው ያለው። " ብለዋል።
" እንደዛም ሆኖ የደመወዝ ጭማሪው እጅግ አስፈላጊ ስለሆነ የሰራተኛውን ቋሚ ደመወዝተኛ ገቢ ያለውን ዝቅተኛውን ትኩረት አድርገን የዝቅተኛውን በጣም ከፍተኛ ጭማሪ አድርገናል የላይኛውን ዝቅተኛ ጭማሪ አድርገን ነው የተሰራው ዝርዝሩ በቅርቡ በሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን በኩል ይፋ ይደረጋል " ሲሉ ተደምጠዋል።
@tikvahethiopia