TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.3K photos
1.51K videos
214 files
4.11K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
www.tridal.org

ለማኑፋክቸረሮች፣ ሆስፒታሎች፣ ሆቴሎች፣ ሪልስቴት እና የግንባታ ኢንዱስትሪ መስኮች የልዩ የስራ ሂደታቸውን ባገናዘበ መሰረት የመዝገብ አያያዝ፣ የስራ ሂደት እና የክፈያ አቀባበልን የሚያዘምን የሶፍትዌር ሲስተም ለሀገር ወስጥ እና አለም አቀፍ ደንበኞች ትራይዳል ቴክኖሎጂስ ኃ፡የተ፡የግ፡ማ በጥራት ገንብቶ በማቅረብ ይታወቃል።

የድርጅቶን የስራ ሂደትን ለማዘመንና ለቁጥጥር ምቹ ለማረግ ካሰብ በፍላጎቶ መሰረትና በተመጣጣኘ ዋጋ የሶፍትዌር ሶሉሽን ገንብተን ለማስረከብ ዝግጁ ነን።

ለበለጠ መረጃ : www.tridal.org/custom
ስልክ : 0901357160
አድራሻ : አዲስ አበባ፣ ብሪቲሽ ኢምባሲ፣ ፍቅር ቢውልዲንግ
#SafaricomEthiopia

ሊያልቅ ነው!  የ#1ወደፊት የሙዚቃ ውድድራችን ዛሬ ይጠናቀቃል! የወደዳችሁትን ተወዳዳሪ ቪዲዮ ላይክ ማድረጋችሁን እንዳትረሱ! ❤️

የዲጂታል ሙዚቃ ውድድርን ለመቀላቀል፡
🎥 የአንድ ደቂቃ የራሳችን ሙዚቃ ቪዲዮ በTikTok ላይ እንፖስት
🏷 #1Wedefit እና #የምትኖሩበትከተማ አድራሻ ማስገባት እንዳንረሳ
📲የTikTok ደረገጽ @Safaricomet ታግ እናድርግ

እንዝፈን! እንፖስት! እናሸንፍ!

መልካም ዕድል!

#1Wedefit #FurtherAheadTogether #DigitalMusicChallenge
TIKVAH-ETHIOPIA
#ሪልስቴት #Update " ቤት ገብተው የሚኖሩ ሰዎች አሉ በጣም ነው የሚያሳዝኑት መብራትና ውሃ ስለሌለ እንጀራ ጋግረው አያውቁም እሱን እያየን ለመግባት ተቸግረል " - የኖህ ሪልስቴት ቤት ገዢዎች "...ለፕሬስ መግለጫ አልሰጥም  " - ኖህ ሪልስቴት የኖህ ሪልስቴት ሀያት ግሪን ቤት ገዢዎች ድርጅቱ በውሉ መሠረት የቤቱን መሠረተ ልማት እንዳላሟላላቸው በድጋሚ በቲክቫህ ኢትዮጵያ በኩል ቅሬታ አቀረቡ፡፡…
#Update

" በድጋሚ ቢሮ ሂደን ጠየቅናቸው ግን የተስፋ ቃል ከመስጠት ውጪ መሬት ላይ ምንም ተጨባጭ ነገር አይሰሩም  " - ቤት ገዢዎች

ከ600 በላይ የሚሆኑ የአያት ግሪን ኖህ ሪልስቴት ቤት ገዢዎች፣ በውላቸው መሠረት ድርጅቱ የመብራት፣ የውሃ፣ የታንከር መሠረተ ልማቶችን ባለሟማላቱ በሚሊዮን የሚቆጠር ገንዘብ ከፍለው ከገዙት ቤታቸው መግባት እንዳልቻሉ በቲክቫህ ኢትዮጵያ በኩል እሮሮ ማቅረባቸው ይታወሳል፡፡

በወቅቱ ለጉዳዩ ምላሽ የጠየቅነው ኖህ ሪልስቴት በበኩሉ፣ አንድ ጊዜ በሰጠን ምላሽ የመብራት፣ ውሃ፣ የታንከር ችግር እንዳለና መሠረተ ልማቶቹን ለማሟላት የዘገየው ችግር ገጥሞት እንደሆነ ገልጾ፣ " በጣም በአጠረ ጊዜ ውስጥ ለመስራት እየሞከርን ነው " ሲል ቃል ገብቶ ነበር፡፡

ይሁን እንጅ ቅሬታቸው ባለመፈታቱ ገዢዎቹ ከወራት በኋላ በድጋሚ ቅሬታ አቅርበዋል፡፡

ድርጅቱን በድጋሚ ጥያቄ ስናቀርብለት ግን፣ " በጠበቃቸው አማካኝነት እየተከታተሉ ስለሆነና ጉዳዩ ወደ ፍርድ ቤት የመሄድ እድል ስላለው የድርጅቱን የመከራከር መብት የሚያጣብብ ስለሚሆን ለፕሬስ መግለጫ አልሰጥም " ከማለት ውጪ ማብራሪያ ከመስጠት ተቆጠቧል፡፡

ገዢዎቹ አሁንስ ዝርዝር ምን አሉ ?

" ምን ማድረግ እንዳለብን ጨነቀን፡፡ በገንዘባችን ቤት ገዝተን መሠረተ ልማቱ እንዲሟላ ለዓመታት እየለመንን እንገኛለን፡፡ እኛ ዋናው ጥያቄያችን ቤታችን ተጠናቆልን እንድንገባ ነው፡፡

በድጋሚ ቢሮ ሂደን ጠየቅናቸው ግን የተስፋ ቃል ከመስጠት ውጪ መሬት ላይ ምንም ተጨባጭ ነገር አይሰሩም፡፡ ማጭበርብር ማታለል ነው የተያያዙት፡፡ የሚነግሩን ነገር በብዙ ውሸት ታጀበ ነው፡፡

እየሄድን ስንጠይቅ በቃ መጫወቻ ነው የሚያደርጉን ንቀት ያለበት ቃላት ከመስጠት ውጪ ምንም የሚሰሩልን ነገር የለም፡፡

20፣ 30 እየሆንን እየተሰበሰብን እየሄድን ስድስት፣ ሰባት ጊዜ በአካል ቢሯቸው ሂደን ጠየቅናቸው ግን ቃል ከመግባት ውጪ የሚያደርጉት ነገር የለም፡፡

ስለዚህ ጠበቃ ወክለን በጠበቃችን አማካኝነት ያለበትን ፕሮጀክት ሂደት ስጡን፣ መቼ ትጨርሳላችሁ? ብለን ጠየቅናቸው፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ መስተዳድርም ተሰብስብን ሂደን ጠየቅን ግን ይህንን የሚከታተል አካል የለም፡፡ ሌላው የሚገርመው ነገር ደግሞ ይሄ ነው፡፡

በሌላ በኩል ግን ቤቱ ሳይጠናቀቅ የከተማዋ ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ ራሱ ሳይቱን ሂዳ መርቃለች፡፡

እኛን ብቻ ሳይሆን እሷንም ሸውደዋታል፡፡ ኤሌክትሪክ ጠልፈው፣ ኤሊቬተሩን አሰርተው፣ ፊኒሽንጉን የጨረሰ አንድ የቤት ባለቤት አለ እርሱን ለምነው ያንን ቤት ነው ያሳዩዋት (ለከንቲባዋ ማለታቸው ነው)፡፡

ከተማ አስተዳደሩም ያለውን እውነታ እንዲያውቅልን እንወዳለን፡፡ ቤቱ ተጠናቀቀ ብለው እኛ ላይ ዜና፤ ፕሮሞሽን ሰርተውብናል፡፡ ቤቱ ግን የውሃና የጋራ መሠረተ ልማቱ ምንም አላለቀም፡፡

አሁንም በውላችን መሠረት የውሃ፣ መብራት፣ ኢሊቬተር መሠረተ ልማቶች እንደሚሟሉልን እንጠይልን " ብለዋል፡፡

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Tigray

በምክትል ሊቀ-መንበር አቶ ጌታቸው ረዳ የሚመራው ህወሓት " አስቸኳይ " ያለውን ሰብሰባ ዛሬ ማካሄድ ጀምሯል።

ዛሬ መሰከረም 20 ቀን 2017 ዓ.ም በመቐለ በክልሉ ጊዚያዊ አስተዳደር ፅ/ቤት አዳራሽ መካሄድ በጀመረው ስብሰባ በሊቀመንበር ዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል የሚመራውን ህወሓት በይፋ የተቃወሙ የማእከላዊ ኮሚቴ አባላት ከፍተኛ ካድሬዎች ተገኝተዋል። 

አቶ ጌታቸው በሰብሰባው መክፈቻ " ፓለቲካዊና ሰላማዊ ትግል በማጠንከር በብቃት በመምራት ወደፊት የሚያራምድ አመራር መፍጠር ልዩ ትኩረት  ያሻዋል " ብለዋል። 

ህወሓት ያጋጠመው ችግርና መፍትሄዎቹ አልሞ መካሄድ በጀመረው ስብሰባ በድርጅቱ ወስጥ የተፈጠረው ችግር ተገንዝቦ ውስብስቡን በማቅለል ተገቢ የፓለቲካ መፍትሄና አቅጣጫ የሚሰጥ አመራር የሚያስፈልግበት ወቅት አሁን ነው ተብሏል። 

" የፕሪቶሪ ስምምነት ህዝብን ከተጨማሪ እልቂት የታደገ ነው " ያሉት አቶ ጌታቸው " ስምምነቱ ያሰገኘው ሰላም ማስቀጠል ቁልፍ ጉዳይ ነው " ብለዋል።

" በምክትል ሊቀመንበር የተመራው ማእከላይ ኮሚቴና የከፍተኛ ካድሬዎች ስበሰባ ውሳኔዎችን ያስተላልፋል ተብሎ ይጠበቃል " ሲል ድምፂ ወያነ ጠቅሶ ቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ ዘግቧል።

@tikvahethiopia
#VisitAmhara

ግሸን ደብረ ከርቤ !

ግሸን ደብረ ከርቤ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ እምነት ተከታዮች ዘንድ በአንጋፋነታቸው ከሚታወቁት ቅዱሳን ሥፍራዎች አንዷ ናት፡፡

የእምነቱ ተከታዮች እንዲሁም ሌሎች የገዳሟን ታሪክ ማወቅ የሚፈልጉ ሰዎች በየጊዜው ወደ ግሸን ይጓዛሉ፡፡

በተለይ ከመስቀል በዓል እስከ መስከረም 21፣ ጥር 21 እንዲሁም መጋቢት 10 ወደ ግሸን የሚጓዘው ሕዝብ በመቶ ሽዎች ይቆጠራል፡፡

በረከት ለማግኘት፣ ታሪክ ለማወቅ እና ለመፈወስ ግሸን ለእምነቱ ተከታዮች ቀዳሚ መዳረሻ ናት፡፡

በኢትዮጵያ የሀይማኖት ቱሪዝም ታሪክ ብዙ እንግዶችን በማስተናገድ ግሸን ከቀዳሚዎች መካከል ትገኛለች፡፡

ነገ መስከረም 21 ታላቁ የግሸን ደብረ ከርቤ ቅድስት ማርያም ክብረ በዓል ይከበራል፡፡

እንኳን አደረሳችሁ !

(Vist Amhara)

#TourismAndPeace  #GishenDebreKerbe #SouthWollo #ReligiousFestival #Ethiopia #LandOfOrigins

@tikvahethiopia
" ከዛሬ ጀምሮ እስከ ጥምቅት 30/2017 ወደ ቤታችሁ ግቡ ፤ ይህ ካልሆነ የሽያጭ ውሉ እንዲቋረጥ ተደርጎ ቤቱን ለሌላ ዕድለኛ እናስተላልፋለን " - የቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የጋራ መኖሪያ ቤቶችን እየገነባ ለቤት ተጠቃሚዎች በዕጣና በጨረታ የሚያስተላልፈው የቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን " በሽያጭ ከተላለፉና ውል ከተፈጸመባቸው ቤቶች መካከል የቤት ባለቤቶች ወደ ቤታቸው ገብተው እየኖሩ አለመሆኑን አረጋግጫለሁ " ብሏል።

" በህጋዊ መንገድ ውል የተያዘባቸው ቤቶች ለህገወጥ ተግባር እየዋሉ ነው " ያለው ኮርፖሬሽኑ ፥ የቤት ባለቤቶች ከኮርፖሬሽኑ ጋር በያዙት የሽያጭ ውል ከዛሬ ጀምሮ እስከ ጥቅምት 30 ቀን 2017 ዓ.ም ድረስ ወደ ቤታቸው እንዲገቡ አስጠንቅቋል።

" በተባለው ጊዜ ውስጥ ወደ ቤቱ የማይገባ የቤት ባለቤት የሽያጭ ውሉ በህግ አግባብ እንዲቋረጥ ተደርጎ ቤቱን ለሌላ ዕድለኛ እናስተላልፋለን " ሲልም ገልጿል።

#AddisAbaba

@tikvahethiopia
#CBE🚨

በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የአገልግሎት ክፍያ ላይ የተጨማሪ እሴት ታክስ ታሪፍ ተጨመረ።

መንግስት በቅርቡ ባወጣው አዲስ የተጨማሪ እሴት ታክስ ሕግ መስረት የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በሚያቀርባቸው ምርት እና አገልግሎቶች ላይ በነበረው የአገልግሎት ክፍያ ላይ ተጨማሪ እሴት ታክስ እንዲከፈልባቸው መወሰኑን ገልጿል።

በዚህም ከነገ መስከረም 21 ቀን 2017 ዓ. ም ጀምሮ የባንኩ ምርትና የአገልግሎት ዓይነቶች ላይ በሚከፈል የአገልግሎት ክፍያ ላይ የተጨማሪ እሴት ታክስ ታሪፍ የተጨመረባቸው መሆኑን ባንኩ አሳውቋል።

@tikvahethiopia
ዋሪት ፈርኒቸር !

የቤትዎን ምቾትና ውበት የሚያስናፍቁ  የዋሪት ምርቶች በሁሉም ማሳያ ሱቆቻችን ያገኛሉ ። ከእርሶ ሚጠበቀው ጎራ ማለት ብቻ ነው። በሚወዱት የቀለም  ምርጫ ይሸምቱ!!
ዋሪት ፈርኒቸር
ትክክለኛ ምርጫ!!
* 22- ዋሪት ህንፃ
* ጉርድ ሾላ- ሴንቸሪ ሞል
* ለቡ- ቫርኔሮ ፊት ለፊት
* ፒያሳ- ፍርዱ ኮሜርሻል
* ቡልቡላ- ልዑል ህንፃ ፊት ለፊት
* አዳማ- ሶረቲ ሞል
📞0911210706 | 07
www.warytze.com
ፌስቡክ፡ www.fb.com/WARYTZE
ቴሌግራም፡ https://t.iss.one/warytfurniture
ኢንስታግራም፡ https://www.instagram.com/warytfurniture/
ቲክቶክ፡ https://www.tiktok.com/@warytzefurniture
🇪🇹በኢትዮጵያ የተመረተ 🇪🇹
ስለ ሲፒ ጉዳተኛ ህጻናት ይመለከተኛል !!

' እዝነት አካል ጉዳተኛ ህፃናትና ወላጆች መርጃ ድርጅት ' የዓለም አቀፍ የሲፒ ጉዳተኞች ቀን አስመልክቶ የእግር ጉዞ ማዘጋጀቱን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።

ድርጅቱ  የእግር ጉዞውን አዘጋጅቶ ነበረው በኢትዮጵያ መስረም 26 / 2017 የነበረ ቢሆን በዚህ ሰሞን ከሚከበረው ባህላዊ፣ ሃይማኖታዊ እንዲሁም በምልእተ ህዝብ የሚከበር አመታዊ ክብረ በአል (ኢሬቻ) ጋር ስለተገጣጠመበት መርሃግብሩን እንደቀየረ አመልክቷል።

የእግር ጉዞው የሚያረደርግበት ቀንም ጥቅምት 03 / 2017 መሆኑን ገልጿል።

ድርጅቱ  በሃገራችን ያለው የሲፒ ጉዳተኞች ስርጭት ከፍተኛ መሆኑን በማመልከት የድጋፍ ስራው ማህበረሰቡን ያሳተፈ እንዲሆን፣ ግንዛቤ ለማስጨበጥና የድርጅቱን ተደራሽነት ከፍ እንዲል ለማድረግ ነው የዓለም አቀፍ የሲፒ ጉዳተኞች ቀን በማሰብ ይህን መርሃ ግብር ያዘጋጀው፡፡

የድርጅቱ መሰራች እና ስራ አስኪያጅ ወ/ሮ ዘቢባ አህመድ " ቀን ለውጡን ያረግንበት ዋና አላማ የህዝቡን ትኩረት እና ድጋፍ በይበልጥ ለማግኘት ፣ እንደ እቅዳችን ብዙ ህዝብ ያካተተ ሆኖ ተደራሽነቱ ከፍ እንዲል ነው " ብለዋል።

ድርጅቱ ቀኑን የቀየረው አምኖበት ቢሆንም ቀደመው ቲሸርት ለገዙ ተሳታፊዎች ይቅርታ ጠይቋል።

በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚከበረውን የዓለም የሰረብራል ፓልሲ ጉዳተኞች ቀንን ተንተርሶ የሚዘጋጀው መርሃግብር በአዲስ አበባ ከተማ ጥቅምት 03 / 2017 ከጠዋቱ 2፡00 እስከ 7፡00 ድረስ መነሻውን አድዋ ዐዐ መዳረሻውን ኩባ ፓርክ ያደርጋል።

@tikvahethiopia