TIKVAH-ETHIOPIA
“ ግድያና እገታ የሚፈጸመው መሀል ከተማ ላይ ነው፡፡ ለዛውም ፖሊስ ጣቢያ ባለበት አጠገብ፡፡ ዛሬ ህዝቡ ሰላማዊ ሰልፍ ወጥቷል፡፡ ፖሊስና ሚሊሻ ወደ ህዝቡ ነው የተኮሰው ” - ነዋሪዎች
በአማራ ክልል፣ ጎንደር ከተማ የሚገኙ ነዋሪዎች በተለይ ከሦስት ወራት ወዲህ " በታጠቁ አካላት አማካኝነት ግድያ፣ እገታና ዝርፍያ " በመበራከቱ ሰቆቃ ላይ መሆናቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡
ድርጊቱ የሚፈጸመው በከተማው ምንም አይነት የተኩስ ልውወጥ በማይደረግበትና አገር ሰላም በተባለበት ወቅት እንደሆነ፣ የጸጥታ አካላት ቅሬታው ከነዋሪዎቸ ቢቀርብላቸውም ለጉዳዩ ትኩረት ባለመስጠታቸው ጥቃቱ እንደተባባሰ አስረድተዋል፡፡
ነዋሪዎቹ ምን አሉ ?
- ኧረ የፍትህ ያለህ ! አገራችን ይሄው ሆነ፡፡ ታዲያ አገራችንን ትተን የት እንሂድ ? ሞትና እገታ በቃ እንደ ደና አደርክ ሁሌም የምንሰማው ቃል ሆነብን እኮ፡፡
- የታጠቁ አካላት ሌሊት የተኩስ ሩምታ ይከፍታሉ፡፡ የነዋሪዎችን ቤትም ሰብረው ይገባሉ፡፡ ከዚያ ሰዎቹን በማስፈራራት አግተው ይወስዳሉ፡፡ እንደገና ታጋቾቹን ለመልቀቅ እስከ 3 ሚሊዮን ብር ይጠይቃሉ፡፡ ገንዘቡ ተልኮም ታጋቾቹን ይገድሏቸዋል፡፡
- ሁሌም ሌሊት ላይ በጣም ይተኮሳል፡፡ እናም ተኩስ ከተሰማ የሆነ ሰው እየታገተ እንደሆነ ይታወቃል ከድርጊቱ መደጋገም ተነሳ፡፡
- የ ‘ፋኖ’ ታጣቂዎች በከተማው የሉም። ከተማው ላይ ያለው ሚሊሻ ነው፡፡ ፖሊሶች ራሱ ከተማ ላይ ሲንቀሳቀሱ አይታዩም፡፡
- ጎንደር ላይ ፋኖም፣ መከላከያም የለም፤ ስለዚህ ጦርነት የለም፡፡ እገታ፣ ግድያና ዝርፊያው የሚፈጸመው በከተማው ጦርነት እየተካሄደ ሆኖ እንኳ አይደለም፡፡
- እንዲህ የሚያደርጉትን አካላት ማንነት ሌሊት ስለሚመጡ በደንብ ማወቅ አይቻልም፡፡
- በየቀኑ በመኪና እየመጡ አጥር ዘለው ይገባሉ፡፡ ግቢ ከበው ሌሎች ሙሉ አባበሎቻቸውን አስገብተው ነዋሪዎቹን አግተው ይወስዳሉ፡፡ እንደዚህ መሆን ከጀመረ ሦስት ወራት አስቆጥሯል፡፡
- አጋቾቹ ገንዘብ ሲጠይቁ የታጋች ቤተሰብ በባንክ ነው ገንዘብ የሚልከው፡፡ በባንክ ነው የሚላክላቸው። ስለዚህ እነርሱን ማግኘት ለምን አልተሻለም ? ሙሉ መረጃው ባንክ ላይ አለ።
- የጸጥታ አካላት በቀበሌ ሰብስበውን ነበር፡፡ ሁሉም ሰዎች ‘ እናንተ የምታመጧቸው ሚሊሾች ናቸው እንዲህ የሚያደርጉን፡፡ ' ነው ያሉት።
- ትላንት ከሚሊሻ በተተኮሰ ጥይት አንድ ልጅ ተገድሏል፡፡
- ግድያና እገታ የሚፈጸመው መሀል ከተማ ላይ ነው፡፡ ለዛውም ፖሊስ ጣቢያ ባለበት አጠገብ፡፡ ዛሬ ህዝቡ ሰላመዊ ሰልፍ ሲወጣ ፖሊስና ሚሊሻ ወደ ህዝቡ ተኩሷል ፒያሳ ላይ። ሰዎችም ተጎድተዋል። ተገድለዋል።
- እንዲህ የሚያደረገው የነዋሪው ሥነ ልቦና እንዲጎዳ፣ ተስፋ እንዲቆርጥ ነው፡፡ ፍላጎታቸው ገንዘብ ብቻ አይደለም፤ ምክንያቱም ገንዘብ ከተላከ በኋላም ታጋቾቹን ይገድሏቸዋል፡፡
- ጡት እንኳን ጠብታ ያልጨረሰች ኖላዊት የተባለች ህፃን ልጅ በአጋቾች ታግታ አጋቾቹ 1 ሚሊዮን ተጠየቀባት ፤ አቅም የለንም ሲሉ 500 ሺህ አደረጉ ከዛ 200 ሺህ ብር ከተቀበሉ በኃላገድለዋት አስክሬኗን በር ላይ ጥለዋል። ለማን እንጩህ ፤ የት እንሂድ ?
- በቅርቡ ደግሞ እናት እና ልጅን ለማፈን ብለው ለሊት ቢመጡም አልመች ስላላቸው ገለዋቸው ሂደዋል። የፍትህ ያለህ።
- ባለሃብቱ ከከተማው እየወጣ ነው ፤ ሌላውም ይህን ሽሽት በቻለው አቅም ወደ አዲስ አበባ እየገባ ነው። እዚህ የቀረው መሄጃ ቢያጣ ነው።
- ባለሀብቱ እየወጣ ሲያስቸግራቸው አጋቾቹ ያገኙትን አፍነው ለምናቹ አምጡ ማለት ጀምረዋል። የሚጠይቁት 1 እስከ 3 ሚሊዮን ብር ነው ሚጠይቁ ደሀም ያዙ ሀብታም ይህን ነድ የሚጠይቁት።
ጉዳዩን በተመለከተ ምላሽ ለማግኘት ወደ ከተማው እና የክልሉ ጸጥታ አካላት ሙከራ ብናደርግም ስልክ ላመንሳት ፈቃደበኛ አልሆኑም፡፡
ምላሽ ከሰጡ በድጋሚ የምንጠይቃቸው ይሆናል፡፡
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
TIKVAH-ETHIOPIA
#EthiopianAirlines🇪🇹 " የኤርትራ ሲቪል አቬሽን ውሳኔውን መልሶ እንዲያጤነው እንጠይቃለን ፤ ይህ የማይሆን ከሆነ የሚጎዱት ወደ ኤርትራ የሚጓዙ ተጓዦች ናቸው " - " አቶ መስፍን ጣሰው የኤርትራ ሲቪል አቬሽን ከኢትዮጵያ ወደ ኤርትራ የሚያደርገው በረራ ከመስከረም 30 / 2024 ጀምሮ እንዲቆም የሚያሳውቅ ደብዳቤ መላኩን ተከትሎ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ጣሰው…
#EthiopianAirlines
ወደ አስመራ የሚያደርገው በረራ ከነገ ጀምሮ ይቋረጣል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ኤርትራ ዋና ከተማ አስመራ የሚያደርገውን በረራ ከነገ ጀምሮ እንደሚያቋርጥ አስታውቋል፡፡
አየር መንገዱ በረራውን የሚያቋርጠው በኤርትራ ውስጥ አገልግሎቱን ለመስጠት ባጋጠመው ከአቅም በላይ በሆነ የአሰራር ችግር እንደሆነ ገልጿል።
በኢትዮጵያ አየር መንገድ ለመብረር ትኬት የቆረጡ መንገደኞች ያለምንም ተጨማሪ ወጪ በሌሎች አየር መንገዶች ጉዟቸውን እንዲያደርጉ ጥረት እንደሚያደርግ አሳውቋል።
" የትኬት ገንዘብ ይመለስልን " የሚሉ ካሉም ለቲኬታቸው ሙሉ ገንዘብ ተመላሽ እንደሚያደረግ ገልጿል።
በበረራው መቋረጥ ምክንያት ለሚፈጠረው መጉላላት ይቅርታ ጠይቋል።
@tikvahethiopia
ወደ አስመራ የሚያደርገው በረራ ከነገ ጀምሮ ይቋረጣል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ኤርትራ ዋና ከተማ አስመራ የሚያደርገውን በረራ ከነገ ጀምሮ እንደሚያቋርጥ አስታውቋል፡፡
አየር መንገዱ በረራውን የሚያቋርጠው በኤርትራ ውስጥ አገልግሎቱን ለመስጠት ባጋጠመው ከአቅም በላይ በሆነ የአሰራር ችግር እንደሆነ ገልጿል።
በኢትዮጵያ አየር መንገድ ለመብረር ትኬት የቆረጡ መንገደኞች ያለምንም ተጨማሪ ወጪ በሌሎች አየር መንገዶች ጉዟቸውን እንዲያደርጉ ጥረት እንደሚያደርግ አሳውቋል።
" የትኬት ገንዘብ ይመለስልን " የሚሉ ካሉም ለቲኬታቸው ሙሉ ገንዘብ ተመላሽ እንደሚያደረግ ገልጿል።
በበረራው መቋረጥ ምክንያት ለሚፈጠረው መጉላላት ይቅርታ ጠይቋል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update
" በረራውን ለማቋረጥ የተገደድኩት ገንዘብ እንዳላንቀሳቅስ በመታገዴ ነው " - የኢትዮጵያ አየር መንገድ
የኤርትራ ሲቪል አቬሽን ከኢትዮጵያ ወደ ኤርትራ የሚያደርገው በረራ ከመስከረም 20፣ 2016 ዓ.ም ጀምሮ እንዲቆም የሚያሳውቅ ደብዳቤ ጽፎ እንደነበር ይታወሳል።
ዛሬ አየር መንገዱ በሰጠው መግለጫ ውሳኔው ይሻሻላል በሚል ሲጠብቅ እንደነበር እና የኤርትራ የሲቪል አቪዬሽን ባለሥልጣንን ለማናገር በተደጋጋሚ ያደረገው ሙከራ አለማሳካቱን አስታውቋል።
የአየር መንገዱ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ጣሰው በመግለጫው እንደጠቀሱት በአስመራ የሚገኘው ተወካያቸው ከሽያጭ የተሰበሰበ ገንዘብ ለማስገባት ሲል ገንዘብ ወደ ኢትዮጵያ መላክ እንደማይቻል ተነግሮታል። ይህ የሆነው ሐምሌ 18/2016 ዓ.ም በተጻፈ ደብዳቤ አማካኝነት ነው።
" ' ከነሐሴ 25/ 2016 ዓ.ም በኋላ ሂሳባችሁ ታግዷል ለሀገር ውስጥ ወጪም (oppration fee) መጠቀም አትችሉም ' መባሉን ተከትሎ ከዛሬ ጀምሮ በረራውን ለማቋረጥ ተገደናል። የበረራ ወጪያችንን መሸፈን ባለመቻላችን ተገደን ወጥተናል " ሲሉ ነው የገለጹት።
አየር መንገዱ እንዳያንቀሳቅስ የታገደበት ገንዘብ መጠን ስንት ነው ?
ይህ ጥያቄ ከጋዜጠኞች የቀረበላቸው ዋና ሥራ አስፈጻሚው የገንዘቡን መጠን ከመግለጽ ተቆጥበው ማብራሪያ ሰጥተዋል።
አየር መንገዱ በኤርትራ ሁለት አካውንት እንዳለው የገለጹት አቶ መስፍን፥ አንዱ የናቅፋ አካውንት ሲሆን የቆየ እንዲሁም ወደ ዶላር መቀየር ያልተቻለ የማይንቀሳቀስ የሂሳብ አካውንት መሆኑን ገልጸዋል።
ሌላኛው የባንክ አካውንት ደግሞ የዶላር ሲሆን ባለፉት ጥቂት ዓመታት ትኬት ሲሸጥ የነበረው በውጭ ምንዛሬ መሆኑን ገልጸው ይህንን ገንዘብም እገዳው እስከተላለፈበት ቀን ድረስ በተለያዩ ጊዜዎች ገንዘቡን ሲያንቀሳቅስ እንደነበረ ገልጸዋል።
" የበረራ እገዳውን ካወጡብን በኋላ ነው Block ያደረጉብን " ሲሉ ነው የገለጹት።
አቶ መስፍን አክለውም ፥ "ለእኛ ገንዘቡ ካልተለቀቀልን ከዚህ በኋላ የሁለቱ ሀገራት ጉዳይ ነው የሚሆነው " ሲሉ ጉዳዩን ለኢትዮጵያ ለሲቪል አቬሽን ባለሥልጣን እና ለውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር ማስታወቃቸውን ገልጸዋል።
" አየር መንገዱ ከኤርትራ የወጣው ተገዶ ነው " ያሉት አቶ መስፍን ዋናው ችግሩ ለምን እንደታገድን አለማወቃችን ነው፤ በተጻፈው ደብዳቤም ላይ ምንም የተገለጸ ነገር የለም ብለዋል።
" ከዚህም በተጨማሪ በደብዳቤም በስልክም ለማናገር ያደረግነው ጥረት አልተሳካም " ሲሉ ገልጸዋል።
የአየር ቀጠናውን አስመልክቶ ጥያቄ የቀረበላቸው ዋና ሥራ አስፈጻሚው አሁን ባለው ሁኔታ በኤርትራ የአየር ክልል መብረር እንዳልተከለከሉ ገልጸው የሚያስገድድ ጉዳይ ካለ ግን አማራጭ መጠቀም እንደሚችሉ አንስተዋል።
#ቲክቫህኢትዮጵያ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
" በረራውን ለማቋረጥ የተገደድኩት ገንዘብ እንዳላንቀሳቅስ በመታገዴ ነው " - የኢትዮጵያ አየር መንገድ
የኤርትራ ሲቪል አቬሽን ከኢትዮጵያ ወደ ኤርትራ የሚያደርገው በረራ ከመስከረም 20፣ 2016 ዓ.ም ጀምሮ እንዲቆም የሚያሳውቅ ደብዳቤ ጽፎ እንደነበር ይታወሳል።
ዛሬ አየር መንገዱ በሰጠው መግለጫ ውሳኔው ይሻሻላል በሚል ሲጠብቅ እንደነበር እና የኤርትራ የሲቪል አቪዬሽን ባለሥልጣንን ለማናገር በተደጋጋሚ ያደረገው ሙከራ አለማሳካቱን አስታውቋል።
የአየር መንገዱ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ጣሰው በመግለጫው እንደጠቀሱት በአስመራ የሚገኘው ተወካያቸው ከሽያጭ የተሰበሰበ ገንዘብ ለማስገባት ሲል ገንዘብ ወደ ኢትዮጵያ መላክ እንደማይቻል ተነግሮታል። ይህ የሆነው ሐምሌ 18/2016 ዓ.ም በተጻፈ ደብዳቤ አማካኝነት ነው።
" ' ከነሐሴ 25/ 2016 ዓ.ም በኋላ ሂሳባችሁ ታግዷል ለሀገር ውስጥ ወጪም (oppration fee) መጠቀም አትችሉም ' መባሉን ተከትሎ ከዛሬ ጀምሮ በረራውን ለማቋረጥ ተገደናል። የበረራ ወጪያችንን መሸፈን ባለመቻላችን ተገደን ወጥተናል " ሲሉ ነው የገለጹት።
አየር መንገዱ እንዳያንቀሳቅስ የታገደበት ገንዘብ መጠን ስንት ነው ?
ይህ ጥያቄ ከጋዜጠኞች የቀረበላቸው ዋና ሥራ አስፈጻሚው የገንዘቡን መጠን ከመግለጽ ተቆጥበው ማብራሪያ ሰጥተዋል።
አየር መንገዱ በኤርትራ ሁለት አካውንት እንዳለው የገለጹት አቶ መስፍን፥ አንዱ የናቅፋ አካውንት ሲሆን የቆየ እንዲሁም ወደ ዶላር መቀየር ያልተቻለ የማይንቀሳቀስ የሂሳብ አካውንት መሆኑን ገልጸዋል።
ሌላኛው የባንክ አካውንት ደግሞ የዶላር ሲሆን ባለፉት ጥቂት ዓመታት ትኬት ሲሸጥ የነበረው በውጭ ምንዛሬ መሆኑን ገልጸው ይህንን ገንዘብም እገዳው እስከተላለፈበት ቀን ድረስ በተለያዩ ጊዜዎች ገንዘቡን ሲያንቀሳቅስ እንደነበረ ገልጸዋል።
" የበረራ እገዳውን ካወጡብን በኋላ ነው Block ያደረጉብን " ሲሉ ነው የገለጹት።
አቶ መስፍን አክለውም ፥ "ለእኛ ገንዘቡ ካልተለቀቀልን ከዚህ በኋላ የሁለቱ ሀገራት ጉዳይ ነው የሚሆነው " ሲሉ ጉዳዩን ለኢትዮጵያ ለሲቪል አቬሽን ባለሥልጣን እና ለውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር ማስታወቃቸውን ገልጸዋል።
" አየር መንገዱ ከኤርትራ የወጣው ተገዶ ነው " ያሉት አቶ መስፍን ዋናው ችግሩ ለምን እንደታገድን አለማወቃችን ነው፤ በተጻፈው ደብዳቤም ላይ ምንም የተገለጸ ነገር የለም ብለዋል።
" ከዚህም በተጨማሪ በደብዳቤም በስልክም ለማናገር ያደረግነው ጥረት አልተሳካም " ሲሉ ገልጸዋል።
የአየር ቀጠናውን አስመልክቶ ጥያቄ የቀረበላቸው ዋና ሥራ አስፈጻሚው አሁን ባለው ሁኔታ በኤርትራ የአየር ክልል መብረር እንዳልተከለከሉ ገልጸው የሚያስገድድ ጉዳይ ካለ ግን አማራጭ መጠቀም እንደሚችሉ አንስተዋል።
#ቲክቫህኢትዮጵያ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ መግለጫ
TIKVAH-MAGAZINE
" የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ኤርትራ አስመራ የሚደረገውን መደበኛ በረራ ከዛሬ ሴፕቴምበር 3/2024 ጀምሮ አቋርጧል። " - የኢትዮጵያ አየር መንገድ
(ሙሉ መግለጫውን ከድምጽ ቅጂው ያዳምጡ)
@tikvahethiopia
(ሙሉ መግለጫውን ከድምጽ ቅጂው ያዳምጡ)
@tikvahethiopia
🌟 ዓለም አቀፍ የበረራ ትኬትን ጨምሮ በትላልቅ ሽልማቶች ይንበሽበሹ!!
መጪውን አዲስ ዓመት አስመልክቶ ከባህርማዶ በቴሌብር ሬሚት እና በአጋሮቻችን በኩል በቴሌብር ዓለም አቀፍ ሐዋላ የተላከልዎን ገንዘብ ሲቀበሉ 5% የገንዘብ ስጦታ ያገኛሉ፡፡
በተጨማሪም 5 ሺህ ብር እና ከዛ በላይ ሲቀበሉ አጓጊ ለሆነው ልዩ የዕድል ጨዋታ ብቁ ይሆናሉ!
✈️ ደርሶ መልስ የበረራ ትኬት - እያንዳንዳቸው 480,000 ብር
🏞 ኩሪፍቱ ወተር ፓርክ ቤተሰብ ፓኬጅ - እያንዳንዳቸው 44,000 ብር
🐏 የበግ ስጦታ - እያንዳንዳቸው 20,000 ብር
💰 5 ሺህ ብር - 450 ስጦታዎች
🌐 ወርኃዊ ያልተገደበ ዳታ + ድምጽ - 300 ስጦታዎች
🗓 እስከ መስከረም 22 ቀን 2017 ዓ.ም ብቻ
#Ethiotelecom #telebirr #telebirrSupperApp #DigitalEthiopia #DigitalAfrica #RealizingDigitalEthiopia
መጪውን አዲስ ዓመት አስመልክቶ ከባህርማዶ በቴሌብር ሬሚት እና በአጋሮቻችን በኩል በቴሌብር ዓለም አቀፍ ሐዋላ የተላከልዎን ገንዘብ ሲቀበሉ 5% የገንዘብ ስጦታ ያገኛሉ፡፡
በተጨማሪም 5 ሺህ ብር እና ከዛ በላይ ሲቀበሉ አጓጊ ለሆነው ልዩ የዕድል ጨዋታ ብቁ ይሆናሉ!
✈️ ደርሶ መልስ የበረራ ትኬት - እያንዳንዳቸው 480,000 ብር
🏞 ኩሪፍቱ ወተር ፓርክ ቤተሰብ ፓኬጅ - እያንዳንዳቸው 44,000 ብር
🐏 የበግ ስጦታ - እያንዳንዳቸው 20,000 ብር
💰 5 ሺህ ብር - 450 ስጦታዎች
🌐 ወርኃዊ ያልተገደበ ዳታ + ድምጽ - 300 ስጦታዎች
🗓 እስከ መስከረም 22 ቀን 2017 ዓ.ም ብቻ
#Ethiotelecom #telebirr #telebirrSupperApp #DigitalEthiopia #DigitalAfrica #RealizingDigitalEthiopia
ኢትዮጵያ ውስጥ የጊግ ኢኮኖሚን ጥቅም ማወቅ ይፈልጋሉ?
በቢዝነስ፣ በህግ እና በፋይናንስ ዙርያ የሚሰጠውን የጊግ ኢኮኖሚ ስልጠና በቴሌግራም ቦት በኩል ይውሰዱ!
🔗 በ https://t.iss.one/mesirat_academy_bot ተመዝግበው ስልጠናውን ይጀምሩ!
ስልጠናውን ሲጨርሱ ሰርተፍኬቶን እንዳይረሱ!
#MesiratEthiopia #Entrepreneurship #BusinessGrowth #GigEconomy #Workshops #Mesirat
በቢዝነስ፣ በህግ እና በፋይናንስ ዙርያ የሚሰጠውን የጊግ ኢኮኖሚ ስልጠና በቴሌግራም ቦት በኩል ይውሰዱ!
🔗 በ https://t.iss.one/mesirat_academy_bot ተመዝግበው ስልጠናውን ይጀምሩ!
ስልጠናውን ሲጨርሱ ሰርተፍኬቶን እንዳይረሱ!
#MesiratEthiopia #Entrepreneurship #BusinessGrowth #GigEconomy #Workshops #Mesirat
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#TIGRAY
የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት ጌታቸው ረዳ በዓዲግራት ምን አሉ ?
የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ ዛሬ በትግራይ ምስራቃዊ ዞን ዋና ከተማ ዓዲግራት ህዝባዊ ውይይት አካሂደዋል።
" ህዝቡ ስጋት ላይ የሚጥል ሁኔታ ለመቅረፍ ከናንተ መሃል ተገናኝተናል " ብለዋል።
" የትግራይ መልሶ ግንባታ ጋሃድ እንዲሆን በመደጋገፍ መስራት ይገባናል " ሲሉ አስገንዝበዋል።
" በውስጣች በተፈጠረው መፎካከር መስራት የሚገቡን አልሰራንም " ያሉት አቶ ጌታቸው " አብዛኛው ጊዚያችን በጭቅጭቅና በጎሪጥ በመተያየት ነው ያሳለፍነው " ሲሉ ተደምጠዋል።
" ከፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት በኋላ በማህበራዊ አገልግሎት መልሶ ግንባታ ጥሩ እንቅስቃሴ አድርገናል ፤ ጅምሮቻችን ይበልጥ ተጠናክረው እንዲቀጥሉ በውስጣችን የታዩ ድክመቶችን ማረምና የጋራ መፍትሄ ለመሻት መስራት ይጠበቅብናል " ብለዋል።
" በፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት መሰረት ሁሉም በጠላት ስር የሚገኙ አከባቢዎች ወደ ነባር አስተዳደራቸው መመለስ አለባቸው ብለን እየሰራን ነው " ያሉት አቶ ጌታቸው " የሰላም ስምምነቱ በተሟላ መልኩ እንዲተገበር እንደ መንግስት ጠንክረን እንሰራለን " ሲሉ ተናግረዋል።
" የህዝባችን ሰላም በማረጋገጥ በኩል ዓለም ከኛ ጋር ናት ይህንን እንዲቀጥል ግን ውስጣዊ አንድነታችን እንዳይላላ ያለማቋረጥ መስራት አለብንም " ብለዋል።
በፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ የሚመሩ የጊዚያዊ አስተዳደሩ ከፍተኛ አመራሮች ዓዲግራት ሲደርሱ በልዩ አጀብ በፈረሰኞች የተደገፈ አቀባበል ነበር የተደረገላቸው።
በአቀባበሉ የተገኙ የዓዲግራት ከተማ ወጣቶች ፦
👉 የጥይት ድምፅ እንጠየፍ !!
👉 መሰረታዊ ለውጥ እንፈልጋለን !!"
👉 ተፈናቃዮች ይመለሱ ግዛታዊ አንድነት ይከበር !!
👉 ትግራይ በሳይንስና ጥበብ እንጂ በጥይት አፈሙዝ አትመራም !!
👉 ጊዚያዊ አስተዳደሩ እንደግፋለን !!
የሚሉና ልሎች መፈክሮች በመያዝ ድምጻቸውን አሰምተዋል።
በፕሬዜዳንት ጌታቸው ረዳ በተመራ የጊዚያዊ አስተዳደሩ አመራሮች ቡድን ምክትል ፕሬዜዳንት ጄነራል ጻድቃን ገብረትንሳኤ ነበሩበት።
#TikvahEthiopiaMekelle
@tikvahethiopia
የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት ጌታቸው ረዳ በዓዲግራት ምን አሉ ?
የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ ዛሬ በትግራይ ምስራቃዊ ዞን ዋና ከተማ ዓዲግራት ህዝባዊ ውይይት አካሂደዋል።
" ህዝቡ ስጋት ላይ የሚጥል ሁኔታ ለመቅረፍ ከናንተ መሃል ተገናኝተናል " ብለዋል።
" የትግራይ መልሶ ግንባታ ጋሃድ እንዲሆን በመደጋገፍ መስራት ይገባናል " ሲሉ አስገንዝበዋል።
" በውስጣች በተፈጠረው መፎካከር መስራት የሚገቡን አልሰራንም " ያሉት አቶ ጌታቸው " አብዛኛው ጊዚያችን በጭቅጭቅና በጎሪጥ በመተያየት ነው ያሳለፍነው " ሲሉ ተደምጠዋል።
" ከፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት በኋላ በማህበራዊ አገልግሎት መልሶ ግንባታ ጥሩ እንቅስቃሴ አድርገናል ፤ ጅምሮቻችን ይበልጥ ተጠናክረው እንዲቀጥሉ በውስጣችን የታዩ ድክመቶችን ማረምና የጋራ መፍትሄ ለመሻት መስራት ይጠበቅብናል " ብለዋል።
" በፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት መሰረት ሁሉም በጠላት ስር የሚገኙ አከባቢዎች ወደ ነባር አስተዳደራቸው መመለስ አለባቸው ብለን እየሰራን ነው " ያሉት አቶ ጌታቸው " የሰላም ስምምነቱ በተሟላ መልኩ እንዲተገበር እንደ መንግስት ጠንክረን እንሰራለን " ሲሉ ተናግረዋል።
" የህዝባችን ሰላም በማረጋገጥ በኩል ዓለም ከኛ ጋር ናት ይህንን እንዲቀጥል ግን ውስጣዊ አንድነታችን እንዳይላላ ያለማቋረጥ መስራት አለብንም " ብለዋል።
በፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ የሚመሩ የጊዚያዊ አስተዳደሩ ከፍተኛ አመራሮች ዓዲግራት ሲደርሱ በልዩ አጀብ በፈረሰኞች የተደገፈ አቀባበል ነበር የተደረገላቸው።
በአቀባበሉ የተገኙ የዓዲግራት ከተማ ወጣቶች ፦
👉 የጥይት ድምፅ እንጠየፍ !!
👉 መሰረታዊ ለውጥ እንፈልጋለን !!"
👉 ተፈናቃዮች ይመለሱ ግዛታዊ አንድነት ይከበር !!
👉 ትግራይ በሳይንስና ጥበብ እንጂ በጥይት አፈሙዝ አትመራም !!
👉 ጊዚያዊ አስተዳደሩ እንደግፋለን !!
የሚሉና ልሎች መፈክሮች በመያዝ ድምጻቸውን አሰምተዋል።
በፕሬዜዳንት ጌታቸው ረዳ በተመራ የጊዚያዊ አስተዳደሩ አመራሮች ቡድን ምክትል ፕሬዜዳንት ጄነራል ጻድቃን ገብረትንሳኤ ነበሩበት።
#TikvahEthiopiaMekelle
@tikvahethiopia