TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59K photos
1.5K videos
211 files
4.07K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
#Ethiopia የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ የሆኑት ዶ/ር ኢዮብ ተካልኝ የኢትዮጵያ መንግሥት " በገበያ ላይ የተመሰረተ የውጭ ምንዛሬ ተመን ስርዓት " ማስተዋወቁን ይፋ አድርገዋል። ገበያ ላይ የተመሰረተ የውጭ ምንዛሬ ተመን ስርዓትን ጨምሮ ሌሎቹንም የኢኮኖሚ ሪፎርምን በተመለከተ ዝርዝር ጉዳዮች በገንዘብ ሚኒስቴር እና በብሔራዊ ባንክ በኩል በየጊዜው ይገለጣሉ ተብሎ ይጠበቃል። @tikvahethiopia
#IMF : የዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) ሥራ አስፈፃሚ ቦርድ ኢትዮጵያ በጠየቀችው ብድር ላይ ለመወያየት ነገ ሰኞ ሐምሌ 22 / 2016 ይሰበሰባል ተብሎ እንደሚጠበቅ ብሎምበርግ ድረገጽ ስማቸውን መግለጽ ያልፈለጉ የመረጃ ምንጮችን ዋቢ አድርጎ ዘግቧል።

ኢትዮጵያ ከዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት እና ከዓለም ባንክ ጋር የምታደርገው ድርድር ከተሳካ በቀጣይ አመታት 10.5 ቢሊዮን ዶላር ልታገኝ እንደምትችል ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐብይ አህመድ በፓርላማ ቀርበው በነበረበት ወቅት መናገራቸው ይታወሳል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Ethiopia

(የባንክ ጉዳዮች ባለሞያው ሙሼ ሰሙ)

" የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ፕሮግራም የፖሊሲ መግለጫውን ተመልክቺያለሁ። መግለጫው በአጭሩ ሲቃኝና ሲጨመቅ ይህንን ይመስላል። እጠቅሳለሁ።

' የውጭ ምንዛሬ ግብይት በገበያ አማካኝነት እንዲበየን የማድረግ ሂደት ነው። '

ይህንን ውሳኔ ተከትሉ የሚከሰቱ መጠነ ሰፊ ኢኮኖሚያዊ ተግዳሮቶች ( Derivates & Consequence ) እንደሚኖሩ ግልጽ ነው።

ተግዳሮቶቹን ለመከላከል የታቀዱ በአጭር፣ በመካከለኛና በረጅም ጊዜ የሚወሰዱ እርምጃዎች በመግለጫው ላይ ተዘርዝረዋል።

የመካከለኛና የረጅም ጊዜ የመፍትሔ አቅጣጫዎች ዝርዝርና ግልጽነት የሚጎድላቸው እንዲሁም በርካታ አማላይ ምኞቶች የታጨቁበት ከመሆናቸው አኳያ ዝርዝር የአፈጻጸም ትንታኔ የሚፈልጉ ናቸው።

በመርህ ደረጃ ፓሊሲው የሚያተኩርበትን ዓላማ ለግንዛቤ ከመግለጫው  እጠቅሳለሁ።

' የፊስካል ፖሊሲ ማሻሻያው ዋና ትኩረቱ የመንግስት ገቢን ማሳደግ፤ የመንግሥት ወጪንና የድጎማ ሥርዓትን ውጤታማ ማድረግ ነው ' ይላል።

ዓላማው ከአጭር ጊዜ መፍትሔዎች ጋር  የሚጣረስ ነው።

በአንድ በኩል በከፍተኛ ደረጃ ድጎማ እንደሚኖር የሚጠቅስ ሲሆን በሌላ በኩል በከፍተኛ ደረጃ የመንግስት ገቢን ማሳደግን ያመላክታል። ድጎማና ገቢ ግንኙነታቸው ተቃርኗዊ ነው። የመካከለኛና የረጅም ጊዜ የፓሊሲ ዝርዝሩን በሚመለከት ወደፊት የምናየው ስለሆነ አመላካች አንቀጹን ከሰነዱ ጠቅሼ ልለፈው።

የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርሙን በተመለከተ ሌሎች ዝርዝር ጉዳዮች በገንዘብ ሚኒስቴርና በብሔራዊ ባንክ በኩል በየጊዜው የሚገለጹ ይሆናል።

ወደ አጭር ጊዜ መፍትሔዎቹ እንምጣ።

ፓሊሲው በአብዛኛው እንደ መፍትሔ ያቀረበው ድጎማና አስተዳደራዊ እርምጃዎችን ነው።

አስተዳደራዊ አቅምና ብቃቱን ከየት እንደሚገኝና መጠነ ሰፊ ድጎማው ምንጩን ከምን እንደሚሆኑ ዝርዝሩን ወደፊት የምናየው ይሆናል። 

የአጭር ጊዜ ኢኮኖሚያዊ የመፍትሔ ዝርዝሮች ከመግለጫው እጠቅሳለሁ።

1) የነዳጅ ዋጋ ጭማሪውን መንግስት በከፊል የሚደጉም ይሆናል (ድጎማ)

2) የመልካም አስተዳደር ብልሹነት እና ሕገ ወጥነት መከላከል (አስተዳደራዊ)

3) የማኅበራዊ ሴፍቲኔት ፕሮግራሞችን መደጎም ( ድጎማ)

4) ዝቅተኛ ባለ ደሞዝ የመንግሥት ሠራተኞችን መደጎም (ድጎማ)

4) ለማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ፕሮግራሙ ድጋፍን ያሰባስባል (ድጎማ)

5) እንደ ብሔራዊ ባንክ፣ የገንዘብ ሚኒስቴር እና የፕላንና ልማት ሚኒስቴር ላሉ ተቋማት ድጋፍ ያደርጋል ( ድጎማ)

6) ማሻሻያው የዜጎቻችን ተጠቃሚነት በሚያረጋግጥ መልኩ ከፍተኛ የክትትልና ድጋፍ ይደረጋል ( ድጎማና አስተዳደራዊ) .. ወዘተ

በዚህ መሰረት ፦

ድጎማው የመንግስት ዝቅተኛ ደሞዝ ተከፋዮችና የሴፍቲ ኔት ተጠቃሚዎች ላይ ያነጣጠረ ነው። ፓሊሲው ከኢኮኖሚያዊ ቀውሱ ለመታደግ ያቀደው ከ10% የማይበልጠውን ማህበረሰብን ነው ።

መጠነ ሰፊ ድጎማው ከበጀት ውጭ የተለየ ገቢን የሚጠይቅ ነው። ድጎማውን እንዴት ለመሸፈን ታቅዷል። በብድር፣ በእርዳታ ከባለ ሐብቶች በማሰባሰብ፣ ገንዘብ በማተም ? ትልልቅ ፕሮጀክቶችን በማጠፍ ?!

ድጎማ በዓለም አቀፍ የገንዘብ ተቋማት ዘንድ ተቀባይነት የሌለውና የተወገዘ ተግባር ነው። የሚጠበቀውን ብድር በውጭ ምንዛሪ ማግኘትና ድጎማን ካልታወቀ ምንጭ መደጎም እንዴት ይጣጣማል?! በዓለም አቀፍ የገንዘብ ተቋማት ዘንድ ተቀባይነቱስ ምን ያህል ነው ?!

የሰላም እጦት፣ ግጭትና የምርታማነት መዳከም፣ አምራች ኋይል( ወጣቱ) በግጭት መጠመዱ በኢኮኖሚው ላይ ከፍተኛ ተጽእኖ አለው። ተጽእኖው ከፓሊሲው ጋር የሚኖረው ተቃርኖ አልተወሳም?! ለምን

ሙስና፣ የፍትሕና የመልካም አሰተዳደር እጦትን በአስተዳደራዊ መንገድ ብቻ እስከ አሁን መፍታት አልተቻለም። ወደፊትም በአጭር ጊዜ መፍታት ከባድ ነው። አስተዳደራዊ መፍትሔ እንደ አጭር ጊዜ መፍትሔ ሆኖ መቅረቡ ከምን አመክንዮ የተነሳ ነው?!

የውጭ ምንዛሪ አቅርቦትና የዋጋ ንረት አንዱና ዋነኛ ተግዳሮት የአቅርቦትና የፍላጎት አለመጣጣም ነው። ይህንን ችግር ለመፍታት አቅርቦቱን ስለማሳደግ የቀረበው አማራጭ የብድር፣ የእርዳታና የደጋፍ አማራጭ ብቻ ነው። ምን ያህል ዘላቄታ አለው ?!

ድጎማ ለአቅመ ደካሞች መፍትሔ ሊሆን ይችላል። ከዚህ ይልቅ ለተገቢው ስራ ተገቢውን ክፍያ መክፈል ወይም ደሞዝን ማሳደግ አማራጭ ሆኖ አለመቅረቡ ውጤታማነቱ  ጥያቄ ላይ የሚጥል ነው።

መካከለኛ ገቢ ወይም ቋሚ ገቢ ( ደሞዝ) ያለው ዜጋ (Disposable income) ካላደገ ገበያው እና ኢኮኖሚው መቀጨጭና አለመነቃቃቱ የሚጠበቅ ነው። ቋሚ ተከፋዮን ማህበረሰብ (የተደራጀው ብቻ ከ4 ሚሊየን በላይ ነው) ገቢውን ማሳደግ ቢቻል ፍላጎት በመጨመር ምርትንና አቅርቦትን ማሳደግ ይቻላል። ይህ ትኩረት ለምን አላገኝም?!

[ ይሄ በጣም የአጭር ጊዜ ግምገማ ነው። ሰፊ ትንተና የሚፈልግ በመሆኑ በቀጣይ ውሳኔና ሂደቱን ተከትዬ በስፋት እመለስበታለሁ ]

(ሙሼ ሰሙ)

@tikvahethiopia
#ስሃላሰየምት🕯

የስሃላ ሰየምት ወረዳ ዋና  አሥተዳዳሪ ሲሳይ ብሩ ፦

" ትናንት ከቀኑ 6፡00 ገዳማ ከስሃላ ሰየምት ወረዳ ወደ ዝቋላ ወረዳ በተከዜ ወንዝ በጀልባ ሲጎዙ ከነበሩት በግምት 26 ሰዎች ውስጥ 19 የሚደርሱ ሰዎች ሕይወታቸው አልፏል።

ከ26ቱ አንድ ሕጻንን ጨምሮ 7 ሰዎች በአስቸጋሪ ሁኔታ ሕይወታቸው ተርፏል።

አደጋው ከደረሰ በኋላ የሟቾችን አስከሬን ለመፈለግ በተደረገው ጥረት እስከ ዛሬ ድረስ 2 ሰዎች ብቻ አስከሬን ተገኝቷል።

ሕይወቱ የተረፈው ሕጻን ከፍተኛ ጉዳት ስላስተናገደ ወደ ሰቆጣ ተፈራ ኃይሉ መታሰብያ ጠቅላላ ሆስፒታል ሲላክ የተቀሩት ስድስቱ መሸሀ ጤና ጣብያ ገብተው የህክምና ክትትል እየተደረገላቸው ነው።

ከአራት ዓመታት በላይ ከጥቅም ውጭ ሆኖ የቆየው እና እስከ ሰኔ ወር መጨረሻዎች ድረስ ይጠናቀቃል ተብሎ የነበረው ከስሃላ - ዝቋላ የሚያገናኘው የተከዜ የብረት ድልድይ በተያዘለት ጊዜ አለመጠናቀቁ የሰው ሕይወት መቅጠፉን እንዲቀጥል ምክንያት ሆኗል። "
#AMC

@tikvahethiopia
#ATTENTION🔈

" ከሕጋዊው አካዉንት ውጭ በመጠቀም ድጋፍ የምታሰባስቡ አካላት ከድርጊታችሁ ተቆጠቡ !! " - የጎፋ ዞን አስተዳዳሪ

በጎፋ ዞን፣ በገዜ ጎፋ ወረዳ የመሬት ናዳ ከተከሰተ ዛሬ 6ኛ ቀኑን ይዟል።

በዚህ የመሬት ናዳ አደጋ የበርካታ ወገኖቻችን ህይወት ማለፉ ይታወሳል።

የጠፉ ሰዎችን ፍለጋና አስከሬን በቁፋሮ የማውጣቱ ስራ አሁንም የቀጠለ መሆኑን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ተረድቷል።

እስካሁንም ድረስ ያልተገኙ በርካታ የቤተሰብ አካላት በመኖራቸዉ የሟቾችን ቁጥር ቀድሞ ከተገለጸው ሊጨምር ይችላል።

ከጉዳቱ የተረፉ ሰዎችን ወደ አንድ አካባቢ አድርጎ ድጋፍ ለማድረግ ጥረት እየተደረገ ነው።

ከአራቱም የሀገሪቱ አካባቢዎች የሚደረገው ድጋፍ የሚበረታታ ነው ተብሏል።

ግን ከተፈቀደው የንግድ ባንክ አካውንት እና የአጭር መልዕክት ድጋፍ ማድረጊያ ቁጥር ውጭ " ድጋፍ እናሰባስባለን " በሚል አንዳንድ እንቅስቃሴዎች እንዳሉ ለማወቅ ተችሏል።

ይህን ጉዳይ በተመለከተ የጎፋ ዞን አስተዳዳሪ ኢ/ር ዳግማዊ አየለ ፥ " ከተፈቀደዉ የገንዘብ ማሰባሰቢያ ቁጥሮች ወጭ ጥቅም ላይ የዋሉ የንግድ ባንክ አካውንቶች በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች እየተዘዋወሩ በመሆኑ በዚህ ድርጊት ላይ የምትሳተፉ አካላት ከድርጊታችሁ  እንድትቆጠቡ "  ሲሉ አስጠንቅቀዋል።

የዞኑ አስተዳዳሪ ፥ " አሁን ላይ ህጋዊ ሆኖ ገንዘብ የሚሰበሰብበት የንግድ ባንክ አካውንት ቁጥር 1000511561276 እንዲሁም በአጭር መልእክት ድጋፍ ለማድረግ ደግሞ 8991 ብቻ መሆኑን ገልጸዋል።

ማህበረሰቡ ከዚህ ዉጭ በሚዘዋወሩ አካውንቶችን እንዳይጠቀም ገልጸዋል።

በመጨረሻም ከመላው ኢትዮጵያ እየመጣ ያለው ድጋፍ እንዲቀጥል ጠይቀዋል።

ከጉዳት የተረፉ ወገኖችን ስነልቦና የማከሙ ስራ የቀጣይ ዋና ተግባር እንደሚሆንና ይህም የሁሉም ተግባር ሊሆን እንደሚገባ ገልጸዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyHW

@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
TIKVAH-ETHIOPIA
#Ethiopia : የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የውጭ ምንዛሪ አስተዳደር ሥርዓት ላይ ማሻሻያ ማድረጉን አሳውቋል። (ሙሉ መግላጫው ከላይ ተያይዟል) @tikvahethiopia
የዛሬው የምንዛሬ ዋጋ ስንት ነው ?

💵 US Dollar
#CASH
Buying ➡️ 74.7364
Selling ➡️ 76.2311

#TRANSACTION
Buying ➡️ 74.7364
Selling ➡️ 76.2311

💷 Pound Sterling
#CASH
Buying ➡️ 91.8787
Selling ➡️ 93.7162

#TRANSACTION
Buying ➡️ 96.2081
Selling ➡️ 98.1322

💶 Euro
#CASH
Buying ➡️ 81.0367
Selling ➡️ 82.6574

#TRANSACTION
Buying ➡️ 81.0366
Selling ➡️ 82.6574

ተጨማሪ ከላይ ይመልከቱ።

@tikvahethiopia
#Sidama

በመሬት መንሸራተት አደጋ የ6 ሰዎች ሕይወት አለፈ።

በሲዳማ ክልል ማዕከላዊ ሲዳማ ዞን ፣ ወንሾ ወረዳ ግሽሬ ጉዱ ሞና ሆሞ በሚባለው አካባቢ ትላንት የጣለው ከባድ ዝናብ ባስከተለው የመሬት መንሸራተት አደጋ የ6 ሰዎች ሕይወት ማለፉ ተሰምቷል፡፡

በመሬት መንሸራተት አደጋ ህይወታቸውን ካጡ ሰዎች በተጨማሪ በ6 ሰዎች ላይ የአካል ጉዳት መድረሱ ተገልጿል፡፡

#SidamaRegionCommunication

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
የዛሬው የምንዛሬ ዋጋ ስንት ነው ? 💵 US Dollar #CASH Buying ➡️ 74.7364 Selling ➡️ 76.2311 #TRANSACTION Buying ➡️ 74.7364 Selling ➡️ 76.2311 💷 Pound Sterling #CASH Buying ➡️ 91.8787 Selling ➡️ 93.7162 #TRANSACTION Buying ➡️ 96.2081 Selling ➡️ 98.1322 💶 Euro #CASH…
በባንክ የምዛሬ ዋጋ በስንት ጨመረ ?

የውጭ ምንዛሪ አስተዳደር ሥርዓት ላይ ማሻሻያ ከመደረጉ ከ3 ቀናት በፊት የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አንድ የአሜሪካ ዶላር መግዣ ዋጋ 57 ብር ከ4895 ሳንቲም ነበር ፤ መሸጫው 58 ብር ከ6393 ሳንቲም ነበር።

አሁን ማሻሻያውን ተከትሎ በዛሬው የምናዛሬው ተመን አንድ የአሜሪካ ዶላር መግዣ 74 ብር ከ7364 ሳንቲም ሲሆን መሸጫው 76 ብር ከ2311 ሳንቲም ሆኗል።

የአንድ ፓውንድ መግዣ ዋጋ 70 ብር ከ6759 ሳንቲም ፤ መሸጫው 72 ብር ከ0894 ሳንቲም የነበረ ሲሆን በዛሬው የባንክ ምንዛሬ መግዣው 91 ብር 8787 ሳንቲም ፤ መሸጫው 93 ብር ከ7162 ሳንቲም ሆኗል።

አንድ ዩሮ በ62 ከ3359 ሳንቲም ይገዛ ፤ በ63 ብር ከ5856 ሳንቲም ይሸጥ የነበረ ሲሆን በዛሬው የባንክ ምንዛሬ መግዣው 81 ብር ከ0367 ሳንቲም ፤ መሸጫው 82 ብር ከ6574 ሳንቲም ሆኗል።

#ETHIOPIA

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Ethiopia : የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የውጭ ምንዛሪ አስተዳደር ሥርዓት ላይ ማሻሻያ ማድረጉን አሳውቋል። (ሙሉ መግላጫው ከላይ ተያይዟል) @tikvahethiopia
" 10.7 ቢሊዮን ዶላር ድጋፍ ተገኝቷል " - ብሔራዊ ባንክ

ብሔራዊ ባንክ ፥ 10.7 ቢሊዮን ዶላር የገንዘብ ድጋፍ ከውጭ አጋሮች መገኘቱን አሳውቋል።

ባንኩ " የሽግግር ወቅት ወጪዎችንና የውጭ ምንዛሪ ማሻሻያ የሚያስከትላቸውን ጫናዎችን ለመቀነስ የሚረዳ 10.7 ቢሊዮን ዶላር የሚገመት ትልቅ የገንዘብ ድጋፍ ከውጭ አጋሮች ተገኝቷል " ብሏል።

የገንዘብ ድጋፉ ከዓለም የገንዘብ ድርጅት (#IMF) ፣ ከዓለም ባንክ (WB) እና ከአበዳሪዎች የሚገኘውን እንደሚጨምር አመልክቷል።

ነገር ግን፣ በሁለትዮሽ የማዕከላዊ ባንክ ተቀማጭ (central bank deposits) እና በከረንሲ ልውውጥ (currency swap) መልክ የሚመጣውን 2.8 ቢሊዮን የአሜሪካን ዶላር እንዲሁም ከዓለም ባንክ፣ ከዓለም አቀፍ ፋይናንስ ኮርፖሬሽን (IFC) እና ከሌሎች ባለብዙ ወገኖች (multilaterals) ይገኛል ተብሎ የሚጠበቀውንና በሃደት ጉዳዩ በሚመለከታቸው አካላት ይፋ የሚደረገውን ተጨማሪ የገንዘብ ድጋፍ አያካትትም ብሏል።

ብሔራዊ ባንክ " በዓለም የገንዘብ ድርጅት እና የዓለም ባንክ የሚለገሰው ልዩ የገንዘብ እርዳታ የመንግሥትን የሪፎርም ሥራዎችን ጥንካሬ ያገናዘበና በአፍሪካ አህጉር ትልቁ ከሚባሉት የገንዘብ እርዳታዎች አንዱ ነው " ብሎታል።

#NBE #Ethiopia

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" 10.7 ቢሊዮን ዶላር ድጋፍ ተገኝቷል " - ብሔራዊ ባንክ ብሔራዊ ባንክ ፥ 10.7 ቢሊዮን ዶላር የገንዘብ ድጋፍ ከውጭ አጋሮች መገኘቱን አሳውቋል። ባንኩ " የሽግግር ወቅት ወጪዎችንና የውጭ ምንዛሪ ማሻሻያ የሚያስከትላቸውን ጫናዎችን ለመቀነስ የሚረዳ 10.7 ቢሊዮን ዶላር የሚገመት ትልቅ የገንዘብ ድጋፍ ከውጭ አጋሮች ተገኝቷል " ብሏል። የገንዘብ ድጋፉ ከዓለም የገንዘብ ድርጅት (#IMF) ፣ ከዓለም…
#Ethiopia : ከዛሬ ጀምሮ ተግባራዊ የተደረገው የውጭ ምንዛሪ ማሻሻያ ምን ለውጦችን አካቷል ?

1ኛ. የውጭ ምንዛሪ አስተዳደር ሥርዓቱ የውጭ ምንዛሪ ተመን በባንኮችና በደንበኞቻቸው መካከል ወደሚወሰንበት የገበያ ሥርዓት ተሸጋግሯል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ሚና፣ ገበያውን በማረጋጋት ላይ ያተኩራል።

2ኛ. የውጭ ምንዛሪን ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የማስተላለፍ ግዴታ ቀሪ ሆኗል፡፡ ላኪዎች እና ንግድ ባንኮች ያፈሩትን የውጭ ምንዛሪ ለራሳቸው ማስቀረት ይችላሉ። ይህ ለግሉ ዘርፍ የሚሰጠውን የውጭ ምንዛሪ አቅርቦት በእጅጉ እንደሚያሻሽል ይጠበቃል።

3ኛ. ቀደም ሲል በ38 የገቢ ንግድ ሸቀጦች ላይ ተጥሎ የነበረው እግድ ተነሥቷል፡፡ ወደ ውጭ የሚደረግ የካፒታል ሂሳብ ፍስት እንደ በፊቱ የተገደበ ቢሆንም፣ የውጭ ምንዛሪ ገበያው ለገቢ ሸቀጦችና አገልግሎቶች ነጻ ሆኗል፡፡

4ኛ. ምርቶችን ወደ ውጭ የሚልኩ ነጋዴዎች ካፈሩት የውጭ ምንዛሪ ገቢ ለራሳቸው ያስቀሩት የነበረው 40 በመቶ ወደ 50 በመቶ ብሏል፡፡ በሂደት የውጭ ምንዛሬ ገቢያቸውን ሙሉ በሙሉ ለራሳቸው የሚያስቀሩበት አሰራር ይዘረጋል።

5ኛ. ቀደም ሲል ባንኮች ለተለያዩ ገቢ ሸቀጦች የሚጠቀሙበት የውጭ ምንዛሪ አሠራርና አደላደል ደንቦች ቀሪ ሆነዋል፡፡

6ኛ. አሁን በሥራ ካሉና በባንኮች ከተቋቋሙ የውጭ ምንዛሪ ቢሮዎች (Forex Bureaus) በተጨማሪ ባንክ ያልሆኑ የግል የውጭ ምንዛሪ ቢሮዎች ይቋቋማሉ፡፡ ለእነዚህ ባንክ ላልሆኑ የውጭ ምንዛሪ ቢሮዎችም በገበያ ዋጋ የውጭ ምንዛሪ ጥሬ ገንዘብ እንዲገዙና እንዲሸጡ የሥራ ፈቃድ ይሰጣቸዋል፡፡

7ኛ. ሸቀጦችን በፍራንኮ ቫሉታ ወደ ሀገር ውስጥ በማስገባት ረገድ የተጣሉ ክልከላዎች ተነስተዋል።

8ኛ. በውጭ ተቋማት፣ በውጭ ኢንቨስተሮች እና በትውልደ ኢትዮጵያውያን (በዳያስፖራዎች) የተከፈቱ የውጭ ምንዛሪ ሂሳቦችን አስተዳደር የሚመለከቱ በርካታ ሕጎች እንዲላሉ ተደርጓል፡፡

9ኛ. በኢትዮጵያ ውስጥ ነዋሪ የሆኑ ስዎች ከውጭ የሚላክላቸውን ሐዋላ፣ በውጭ ምንዛሪ የሚከፈል ደሞዝን/የኪራይ ገቢን እና ሌሎች ገቢዎችን የሚያስቀምጡባቸውን የውጭ ምንዛሪ ሃሳቦች እንዲከፍቱ፣ እንዲሁም እነዚህን የውጭ ምንዛሪ ሂሳቦች ተጠቅመው የውጭ አገልግሎት ክፍያዎችን እንዲፈጽሙ ተፈቅዷል፡፡

10ኛ. ቀደም ሲል የግል ኩባንያዎች ወይም ባንኮች በሚወስዷቸው የውጭ ብድሮች ላይ ይከፍሉት የነበረው የወለድ ተመን ጣሪያ ተነሥቷል።

11ኛ. መመዘኛውን የሚያሟሉ የውጭ ኢንቨስተሮች በኢትዮጵያ ሰነደ ሙዓለ ንዋይ ገበያ (Ethiopian Securities Exchange) እንዲሳተፉ ተፈቅዷል፡፡

12ኛ. በልዩ የኢኮኖሚ ዞኖች ውስጥ የሚሠሩ ኩባንያዎች የውጭ ምንዛሪ ገቢያቸውን ሙሉ በሙሉ ለራሳቸው መያዝን ጨምሮ ልዩ የውጭ ምንዛሪ አጠቃቀም መብት ተሰጥቷቸዋል፡፡

13ኛ. ከኢትዮጵያ ወደ ውጭ ሀገራት የሚጓዙ ወይም ወደ ኢትዮጵያ የሚገቡ መንገደኞች ሊይዙ በሚገባ የውጭ ምንዛሪ ጥሬ ገንዘብ መጠን ላይ ተጥለው የነበሩ የተለያዩ ጥብቅ ደንቦች እንዲላሉ ተደርጓል፡፡

#NationalBankofEthiopia

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Ethiopia : ከዛሬ ጀምሮ ተግባራዊ የተደረገው የውጭ ምንዛሪ ማሻሻያ ምን ለውጦችን አካቷል ? 1ኛ. የውጭ ምንዛሪ አስተዳደር ሥርዓቱ የውጭ ምንዛሪ ተመን በባንኮችና በደንበኞቻቸው መካከል ወደሚወሰንበት የገበያ ሥርዓት ተሸጋግሯል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ሚና፣ ገበያውን በማረጋጋት ላይ ያተኩራል። 2ኛ. የውጭ ምንዛሪን ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የማስተላለፍ ግዴታ ቀሪ ሆኗል፡፡ ላኪዎች እና ንግድ…
#Ethiopia

በአዲሱ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ መመሪያ ባንኮች እና ፍቃድ የሚሰጣቸው የውጭ ምንዛሪ ላይ የሚሰሩ አካላት በራሳቸው መካከል እና ከደንበኞቻቸው ጋር በዋጋው ላይ ነጻ ድርድር በማድረግ የውጭ ምንዛሪ መግዛት እና መሸጥ እንዲችሉ ተፈቅዶላቸዋል።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ሚና ገበያውን በማረጋጋት ላይ ያተኮረ እንሰሚሆን ተነግሯል።

ባንኮች በየዕለቱ ለሚያደርጉት የውጭ ምንዛሪ ግብይት የሚያውሉትን የምንዛሪ ዋጋ በቀኑ መጨረሻ ለብሔራዊ ባንክ ማሳወቅ ይጠበቅባቸዋል።

በኢትዮጵያ ከዛሬ ጀምሮ " በገበያ ላይ የተመሰረተ የውጭ ምንዛሬ ተመን ስርዓት ወይም Floating exchange rate " ወደ ስራ ገብቷል።

ማሻሻያውን ተከትሎ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አንድ የአሜሪካ ዶላር በ74 ብር ከ7364 ሳንቲም እየገዛ በ76 ብር ከ2311 ሳንቲም በመሸጥ ላይ ነው።

@tikvahethiopia
#Ethiopia

" 7.02 ቢሊዮን ዶላር ገቢ (Revenue) ተገኝቷል " - የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዛሬ መግለጫ ሰጥቶ ነበር።

በመግለጫው ባለፈው በጀት ዓመት በአጠቃላይ 7.02 ቢሊዮን ዶላር ገቢ (Revenue) ማግኘቱንና ካለፈው በጀት ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር 14 በመቶ ጭማሪ እንዳሳየ ገልጿል።

ይህ ገቢ በኢትዮጵያ ብር ሲቀመጥ 402 ቢሊዮን ብር በላይ እንደሆነ ተመላክቷል።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ጣሰው ምን አሉ ?

አየር መንገድ 577,746 የበረራ ሰዓቶችን እንደበረረና ይህም ቀደም ሲል ካለው 19 በመቶ እድገት እንዳሳየ ገልጸዋል።

በበጀት ዓመቱ አየር መንገዱ 17.1 ሚሊየን ተጓዧችን እንዳስተናገደ ተናግረዋል።

ከዚህ ውስጥ 13.4 ሚሊዮን የሚሆነው አለም አቀፍ ተጓዦች እንደሆኑ 3.7 ሚሊዮን የሚሆኑት ደግሞ የሀገር ውስጥ መንገደኞች እንደሆኑ ጠቁመዋል።

" የሀገር ውስጥ በረራ ፍላጎት በከፍተኛ ሁኔታ አድጓል " ያሉት ዋና ስራ አስኪያጁ " ያለፈው በጀት ዓመት ማስተናገድ የተቻለው 2.7 ሚሊዮን የሀገር ተጓዦች ነበር " ብለዋል።

ከካርጎ ጋር ተያይዞ በዚህ ዓመት ካለፉት ተመሳሳይ ወቅቶች ጋር ሲነጻጸር ቅናሽ እንዳሳየ ተሰምቷል።

በዚህ በጀት ዓመት አየር መንገዱ ያጓጓዘው ጭነት መጠን ከ754, 681 ቶን ጭነት እንደሆነ ተናግረዋል።

" አየር መንገዱ ከካርጎ ያገኘው ገቢ 1.65 ቢሊዮን ዶላር ሲሆን ይህም ካለፈው በጀት ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር 8 በመቶ ቅናሽ አሳይቷል " ብለዋል።

በሌላ በኩል ፥ " ቀደም ተብለው ከታዘዙ 20 የሚሆኑ አውሮፕላኖች ጋር ተደምሮ 125 የሚሆን አውሮፕላኖች እንደታዘዙ " ዋና ስራ አስኪያጁ ጠቁመዋል።

ከቦይንግ የታዘዙ አውሮፕላኖች አለመገኘታቸውን ተከትሎ የአውሮፕላን እጥረት እንዳጋጠመ ተናግረዋል።

#TikvahEthiopia

@tikvahethiopia