TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.4K photos
1.51K videos
215 files
4.12K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
" ውሎ ማደር፣ ወጥቶ መግባት በአንዳንድ የሀገራችን አካባቢዎች ስጋት ከሆነ ሰነባብቷል ! " - ቋሚ ሲኖዶስ ቋሚ ሲኖዶስ ፥ ከሐምሌ 22 እስከ ሐምሌ 28 ቀን 2016 ዓ/ም ድረስ በሁሉም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ገዳማት የምሕላ ጸሎት እንዲፈጸም አወጀ። በሀገር አስተማማኝ ሰላም ሲጠፋ በጾም በጸሎት በመወሰን ፣ ምሕላ ይታወጃል። ምሕላ የሚታወጀው ልባዊ በሆነ ተማሕጽኖ ሁሉን ማድረግ…
🔈#መልዕክት

" ሁሉም የቤተክርስቲያናችን አገልጋዮችና ምእመናን ሀገራዊ ፦
- ሰላምን፣ 
- መረጋጋትን
- ፍቅርን
- አንድነትን ለማስፈን ጾም እና ጸሎት በታወጀበት የምሕላ ሳምንት ለገዳማውያኑ ፀጥታ ሲባል ወደ ገዳማት የምታደርጉትን ጉዞ ለጊዜው እንዲቆይ አድርጋችሁ መደበኛ ሥራችሁን በያላችሁበት ቦታ እየሠራችሁ እግዚአብሔር የገዳማውያኑን ጸሎት ሰምቶ ለሀገራችንና ለሕዝባችን ምሕረትን እንዲሰጥ በኅሊና ዝግጅት፣ በሐሳብ አንድነት ሆናችሁ በጾም በጸሎት እንድተጉ ቋሚ ሲኖዶስ መንፈሳዊ ጥሪውን ያስተላልፋል፡፡ " - የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ


#ኢትዮጵያ🙏

@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
🌍Join Africa’s Largest Hackathon in Addis Ababa!🔥

Dear university and high school students,

A2SV is hosting Africa's largest hackathon, and it's happening here in Addis Ababa! Last year, 3,709 students from 47 countries across Africa created digital solutions using AI. Now it's your turn! 🫵🏽

Register for the hackathon to enhance your skills and receive guidance from top tech mentors at companies such as Google, Meta, TikTok, Nvidia, and more.

Compete for a share of $30,000 USD and make a real impact. Don’t miss your chance to shine and win!

REGISTER NOW at hackathon.a2sv.org

Let us show the world what Africa can do! 💪🏽
🔈#የነዋሪዎችድምጽ

" የምንኖረው በኮንሶና አካባቢው ነው።

የመብራት ለቀናት መጥፋት እና መቆራረጥ ከፍተኛ ችግር በስራችን እና በህይወታችን ላይ እያደረሰ ነው።

ለቀናት ሲጠፋ ችግሩን ለመንግስት እንዳንናገር ድንገት ይመጣል መጣ ስንል ደግሞ በአንድ ሰአት ውስጥ ሁለት ሶስቴ ይቆራረጣል።

አሁን ላይ ስራ መስራት አስቸጋሪ ሆኗል።

በመብራት የሚሰሩ ስራዎች በተለይም ጸጉር ቤቶች ፣ ብየዳና የማሽነሪ ስራዎች እንዲሁም የእንጨት ቤቶች ላይ የሚሰሩ ሰዎች ተስፋ ቆርጠዋል።

እባካችሁ የሚመለከታችሁ አካላት ድምጻችንን ሰሙንና ችግሩን ፍቱልን።

ሌላው መንግስት በዚህ ሀኔታ እያለን እና አቅማችን በተዳከመበት ወቅት የግብር ማሰባሰብ እንቅስቃሴ ላይ መሆኑ አሳስቦናል። ነባራዊዉ ሁኔታ ካልተገናዘበና ሁኔታዎች በዚህ ከቀጠሉ ሙሉ በሙሉ ከስራ ውጭ ልንሆን እንችላለን " -
የኮንሶና አካባቢው ማህበረሰብ

#TikvahEthiopiaFamilyKonso

@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
#ትግራይ

ባለፉት 3 ወራት በዘራፊዎች ጥቃት ለደረሰባቸው 482 ሰዎች የህክምና አገልግሎት መስጠቱን መቐለ የሚገኘው የዓይደር ሰፔሻላይዝድ ሪፈራል ሆስፒታል አስታወቀ።

በሆስፒታሉ የህዝብ ግንኙነት ባለሙያው ብርሃነ ገ/ሚካኤል ለትግራይ ሬድዮ በሰጡት ቃል፥ ከሚያዝያ እሰከ ሰኔ 2016 ዓ.ም ባሉት ወራት በቢላዋ ሌሎች መሳሪዎች በዘራፊዎች ጥቃት የደረሰባቸው 482 ሰዎች በሆስፒታሉ የድንገተኛ የህክምና ክፍል ታክመዋል።

የጥቃቱ ሰለባዎች የ9 ዓመት ዕድሜ ካለው ህፃን አስከ የ70 አመት አዛውንት የሚያካትት እንደሆነ  ተናግረዋል።

ከነዚሁ ተጠቂዎች 69ኙ ሴቶች ናቸው።

የሆስፒታሉ የህክምና ተገልጋዮች የመቀበያ ሰነድ እንደሚያመላክተው፦

- በሚያዝያ 183 ሰዎች
- በግንቦት 136 ሰዎች
- በሰኔ 163 ሰዎች በዘራፊዎች ጥቃት ደርሶባቸው ታክመዋል።

ሆስፒታሉ ያለው ውስን የመድሃኒት ፣ የህክምና ቁሳቁስና ባለሙያ ለእርጉዝና የሚወልዱ እናቶች እንዲሁም ለሌሎች የቆየ ህመም ላለባቸው ተገልጋዮች የቅድምያ አገልግሎት ከመስጠት ፈንታ የዘራፊዎች የጥቃት ሰለባዎች ለሆኑ ድንገተኛ ታካሚዎች የህክምና አገልግሎት በመስጠት መጠመዱ ሌላ ጫና እንደፈጠረበት ተገልፀዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
#TigrayRadio

@tikvahethiopia            
#SafaricomEthiopia

ከተመረጡ ባንኮች ወደ M-PESA ገንዘብ በማስተላልፍ በቀላሉ ክፍያዎችን እንፈፅም ፤ እስከ 50 ብር ተመላሽ ስጦታ እናግኝ።

M-PESA ላይ እንመዝገብ፣ በM-PESA እንገበያይ!
🔗የM-PESAን ሳፋሪኮም መተግበሪያ በዚህ ሊንክ እናውርድ ፡ https://play.google.com/store/apps/details?id=et.safaricom.mpesa.lifestyle

የቴሌግራም ቻናላችንን እዚህ እንቀላቀል 👉https://t.iss.one/Safaricom_Ethiopia_PLC
ስለ አገልግሎታችን ማንኛውንም ጥያቄ ወይም መረጃ  በቴሌግራም   ቻናላችን https://t.iss.one/Safaricom_Ethiopia_PLC 24/7 ማግኘት ይቻላል!

#MPESASafaricom  #FurtherAheadTogether
TIKVAH-ETHIOPIA
" ፍትህን እስከምናገኝ ድረስ የሚከፈለውን መስዋዕትነት እንከፍላለን " - ካውንስሉ በኢትዮጵያ ቃለ ሕይወት ቤተ ከርስቲያን ኩሪፍቱ ማዕከል ላይ የቢሾፍቱ ከተማ አስተዳደር ኢ-ህገ መንግስታዊ ጥሰት እየፈጸመ እንደሆነ የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስትያናት ካውንስል አሳወቀ። ድርጊቱን በመቃወምም መግለጫ አውጥቷል። ካውንስሉ ፤ የኩሪፍቱ ማዕከል በህጋዊ መንገድ ለቃለ ሕይወት ቤተ ክርስቲያን የተሰጠ…
🔈#የኢትዮጵያ_ቃለ_ሕይወት_ቤተክርስቲያን

በኢትዮጵያ ቃለ ሕይወት ቤተ ክርስቲያን የኩሪፍቱ ማዕከል ይዞታ ላይ በቢሾፍቱ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ጽ/ቤት እየተወሰደ ነው ያለችው ሕገወጥ እርምጃ እንዲቆም የኢትዮጵያ ቃለ ሕይወት ቤተ ክርስቲያን ጥሪ አቅርባለች።

ቤተክርስቲያኗ በዛሬው ዕለት ስለጉዳዩ ሰፋ ያለ ዝርዝር መግለጫ ልካልናለች።

ከመግለጫው መካከል ፦

" በቢሾፍቱ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ እየተካሄደ ያለው ሕገወጥ አካሄድ፣ የፍርድ ቤትን ውሳኔን እና ከጠቅላይ ሚኒስትር ቢሮ ጉዳዩን ለማጣራት የመጣ ቡድን ግኝቱን ይዞ ሄዶ የበላይ ውሳኔ ባልተሠጠበት ሁኔታ የኮርደር ልማትን ሰበብ በማድረግ ከቤተ ክርስቲያን ይዞታ ላይ #መሬት_በጉልበት_ቀምቶ ለሁለት ግለሠቦች ለመሥጠት የሚደረገው ሥራ በወንጌላውያን አምነት ተከታዮች ላይ የተቃጣ የተቀነባበረ የግለሰቦችን ፍላጎት ለማሟላት ቤተ ከርስቲያናችን ላይ በተደጋጋሚ እየተሰነዘረ ያለ ጥቃት ነው።

ይህ መላው የወንጌል አማኞችን የሚመለከት ኢ-ሕገመንግሥታዊ አካሄድ ስለሆነ፣ ጉዳዩን ለመንግሥትና ለፍትህ አካላት ማቅረባችን ይቀጥላል።

ጉዳዩ የሚመለከታቸው የኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ከፍተኛ አመራሮች እና የፌዴራል መንግስት አካላት ይህ ጉዳይ ጥቂት ግለሠቦችን ጠቅሞ ሚሊየኖችን የሚያስከፋ ሕገ ወጥ ድርጊት በመሆኑ አንድታስቆሙልን እና አስቸኳይ ምላሸ እንድትሰጡን በታላቅ አክብሮት እንጠይቃለን።

በቤተ ክርስቲያናችን ላይ እየደረሰባት ያለውን ሕገ ወጥ እርምጃ አጥብቀን የምንቃወምና የምናወግዝ መሆኑን እንገልጻለን።

መላው የኢትዮጵያ ቃለ ሕይወት ቤተ ክርስቲያን እና የወንጌል አማኙ ማሕበረሰብ በአጠቃላይ ይህንን ህገመንግስታዊ መብታችንን የሚጋፋ ተግባር እስኪቆም ድረስ በያለንበት በጸሎት እንድንተጋ፣ በተለያየ መንገድ ፍጹም ሰላማዊ በሆነ መንገድ ድምጻችንን እንድናሰማ፣ ጉዳዩ በዚህ የማይገታ ከሆነ ከወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል ጋር በመምከር ሌሎች ሊወሰዱ የሚገባቸውን እርምጃዎች እናሳውቃለን። "

(ሙሉ መግለጫው ከላይ ተያይዟል)

@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
TIKVAH-ETHIOPIA
" እንደ ባሪያ ነው የምንታየው ፤ እባካችሁ ጭሁልን !! " - በማይናማር የሚገኙ ወጣቶች ማይናማር እና ታይላንድ ድንበር ላይ ከሚገኙ የተለያዩ ዓለም አቀፍ የበየነ መረብ ማጭበርበር (Online Scam) ተግባራት ከሚፈጸምባቸው አንዳንድ ቦታዎች ቲክቫህ ኢትዮጵያ መልዕክቶችን በቴሌግራም እየተቀበለ ይገኛል። እነዚህ ቦታዎች ላይ በርካታ የሀገራችን ወጣቶች ያሉ ሲሆን " ታይላንድ እንልካችኋለን " በሚል…
🔈 #ተጠንቀቁ

ወደ ተለያዩ ውጭ ሀገራት " ስራ ነው " በሚል ፕሮሰስ እያደረጋችሁ ያላችሁ ወጣቶቻችን የትም ሀገር ይሁን የምትሄዱት ስራው ምን እንደሆነ እና ለደህንነታችሁም አስተማማኝ መሆኑን አረጋግጡ።

" ለስራ ውጭ እንላካችሁ " የሚሉትን ደላሎችንም ሆነ ኤጀንሲዎች ፦
- ስራው ምንድነው ?
- በትክክል ድርጅቱ ያለበት ሀገር የት ነው ?
- የድርጅቱን ህጋዊነት የሚያሳይ ማስረጃ አሳዩን !
- ባለበት ሀገር ሕጋዊ ስርዓት የተመዘገበበትን ፋይል አሳዩን ! ብላችሁ ጠይቋቸው።

ከዚህ ውጭ በተድበሰበሰ ሁኔታ " ጠቀም ያለ ገንዘብ ነው የምታገኙት " በሚል ብቻ መረጃ ፤ ማስረጃ በሌለበት ሁኔታ የሚደረግ የውጭ ሂደት ብታቋርጡ መልካም ነው።

አንዳንድ ስለ ገንዘብ እንጂ ፍጹም ስለ ሰው ህይወት የማያሳስባቸው ደላሎች እና ኤጀንሲዎች በርካታ ወጣቶችን እያታለሉ መጀመሪያ ወዳሉት ሳይሆን ወደ ሌላ ምንም ደህንነቱ ወዳልተረጋገጠ ሀገር እየላኩ ሰዎችን በማጭበርበር ላይ ወደ ተሰማሩ ድርጅቶች እያስገቧቸው ነው።

በነዚህ ድርጅቶች ውስጥ በሚቆዩበት ወቅት በርካታ ኢ-ሰብዓዊ ድርጊቶች ይፈጸምባቸዋል።

የወጣትነት ጊዜያችሁ ሳያልፍ ህይወታችሁን ለማሻሻል ብላችሁ እጅግ ተቸግራችሁ ፤ ቤተሰብም አስቸግራችሁ ብዙ ብር ከፍላችሁ ወደ ውጭ ሀገር የምትሄዱ ልጆች ስለምትሄዱበት ሀገር እና ስራ በደንብ አጣሩ አንብቡ።

ዘመኑ  የቴክኖሎጂ  ነውና በስልካችሁ ላይ ገብታችሁ የምትሄዱበት ሀገር ስላለው ደህነት፣  ስላለው የስራ ሁኔታ ፣ እናተም ትስሩታላችሁ ስለሚባለው ስራ በደንብ አረጋግጡ።

በኦንላይን የማያታውቁት ሰው ወይም በማስታወቂያ " ለስራ ወጣቶችን እንፈልጋለን " ሲሉ አትመልሱላቸው።

⚠️ በቀጣይ " ጠቀም ያለ ገቢ የሚያስገኝ ስራ ነው ! " እየተባለ ከተለያዩ የዓለም ሀገራት በብዛት ወጣቶችን በማዘዋወር አንዳንድ ድርጅቶች እያስገቡ ወጣቶችን የሚያሰሯቸውን የኦንላይን ማጭበርበር  / Online Scam / ድርጊት አይነቶችን በዝርዝር እንዳስሳለን።

#TikvahEthiopiaFamily

@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
🌍Join Africa’s Largest Hackathon in Addis Ababa!🔥

Dear university and high school students,

A2SV is hosting Africa's largest hackathon, and it's happening here in Addis Ababa! Last year, 3,709 students from 47 countries across Africa created digital solutions using AI. Now it's your turn! 🫵🏽

Register for the hackathon to enhance your skills and receive guidance from top tech mentors at companies such as Google, Meta, TikTok, Nvidia, and more.

Compete for a share of $30,000 USD and make a real impact. Don’t miss your chance to shine and win!

REGISTER NOW at hackathon.a2sv.org

Let us show the world what Africa can do! 💪🏽
#USA

ከግድያ የተረፉት የቀድሞው ፕሬዜዳንት ትረምፕ !

የቀድሞ የአሜሪካ ፕሬዜዳንት ዶናልድ ትረምፕ ለቀጣዩ ምርጫ ፔንሰልቬኒያ፣ ባትለር ውስጥ ቅስቀሳ በማካሄድ ላይ እያሉ ከሕዝቡ መካከል በተተኮሰ ጥይት ደም በደም ሆነው ከመድረኩ ሲወርዱ ታይተዋል።

ትረምፕ የድንበር አቋራጮች ቁጥር ምን ያህል እንደደረሰ ለማሳየት ሲጋብዙ እና የቁጥር ማሳያ ደውል መደወል ሲጀምር ከሕዝቡ መካከል የተኩስ ድምጽ የተሰማው።

ከዚያም ትረምፕ ቀኝ እጃቸውን ወደ አንገታቸው ሲልኩ ታይተዋል።

ወዲያውኑ ፊታቸው ላይ ደም ሲወርድ ታይቷል።

ትረምፕ ተኩሱ ከተሰማበት አቅጣጫ በኩል ራሳቸውን ለመከለል ወደ ታች ሲሸሹ እና የደኅንነት ሠራተኞች በፍጥነት ወደ መድረኩ ሲሮጡ ታይተዋል።

በዚህ ሰዓትም የሕዝቡ ጩኸት ይሰማ ነበር።

ትረምፕ ቀና ብለው እጃቸውን ወደላይ ሲያነሱ በምርጫ ቅስቀሳው ላይ የነበረው ሕዝብ ጩኸት ከፍ ብሎ ተሰምቷል።

የ "ሴክሬት ሰርቪስ " የሕግ አስከባሪዎች ትራምፕ በፍጥነት ከመድረክ እንዲወርዱ አድርገዋል።

ትራምፕ የግድያ ሙከራው ከተደረገባቸው በኃላ ወደ ሆስፒታል ተወስደው እርዳታ ከተደረገላቸው በኃላ ኒው ጀርዚ ተመልሰዋል።

ያለ ምንም የሰው ድጋፍ እራሳቸው እየተራመዱ ከአውሮፕላን ሲወርዱ ታይተዋል።

" ደህና " መሆናቸውም ታውቋል።

የግድያ ሙከራውን የፈጸመው ግለሰብ በአሜሪካ ሴክሬት ሰርቪስ ደኅንነት አባላት መገደሉን ተሰምቷል።

ከተጠርጣሪው በተጨማሪ ሁለት ሰዎች በተኩስ ልውውጡ መገደላቸውን እና ሌሎች ሁለት ሰዎች ደግሞ በከፍተኛ ሁኔታ መቁሰላቸው ተገልጿል። #VOA #CNN

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Video
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#ቪድዮ : የቀድሞ የአሜሪካ ፕ/ት ዶናልድ ትራምፕ የግድያው ሙከራ በተደረገባቸው ወቅት እሳቸው ቅስቀሳ ከሚያደርጉበት ስፍራ በቅርብ ርቀት በሚገኝ ጣሪያ ላይ የነበሩ የ " ሴክሬት ሰርቪስ " የስናይፐር ተኳሾች የግድያ ሙከራውን ባደረገው ሰው ላይ ምላሽ ሲሰጡ ታይተዋል።

አንድ ተቀርጾ በማህበራዊ ሚዲያ የተሰራጨ ቪድዮ ሁለት የሴክሬት ሰርቪስ ስናይፐር ተኳሾች በፍጥነት ኢላማ አድርገው የግድያ ሙከራ ባደረገው ግለሰብ ላይ የተኩስ መልስ ሲሰጡ ተስተውሏል።

ግለሰቡ የግድያ ሙከራ ባደረገ በሰከንዶች ውስጥ መተገው ገድለውታል።

የግድያ ሙከራውን ያደረገው ማነው ?

- FBI የግድያ ሙከራውን ያደረገው ቶማስ ማቲው የተባለ #የ20_ዓመት_ወጣት እንደሆነ ገልጿል።

- ነዋሪነቱ ምርጫ ቅስቀሳውና የግድያ ሙከራው ከተደረገበት ስፍራ የአንድ ሰዓት ጉዞ የሚፈጅ ቦታ ነው።

- በ2022 ነው ቤተል ፓርክ ከተባለ ሀይስኩል የተመረቀው።

- ወጣቱ በብሔራዊ የሒሳብ እና ሳይንስ ኢኒሼቲቭ ተሸላሚም ነበር።

- የሪፐብሊካን ደጋፊም ጭምር እንደሆነ ተመዝግቧል (የዶናልድ ትራምፕ ፓርቲ ማለት ነው)።

- ቅስቀሳው ከሚደረግበት ቅርብ ርቀት በሚገኝ ጣራ ላይ ሆኖ ነው ዶላንድ ትራምፕን ለመግደል የሞከረው።

- ለምን ይህን ለማድረግ እንደፈለገ FBI ምርመራ እያደረገ ነው።

#USElection #FBI

@tikvahEthiopia
#Internet

ትላንት ምሽት በተካሄደ የኢንተርኔት የመመለስ ስራ ለበርካታ ወራት ኢንተርኔት ተቋርጦባቸው የነበሩ ከተሞች የኢንተርኔት አገልግሎት ማግኛታቸው ተሰምቷል።

ከሁነኛ ምንጭ በተገኘ መረጃ ኢንተርኔት ተቋርጦ በነበረባቸው 19 ከተሞች አገልግሎት ተመልሷል ተብሏል።

የትኞቹ ከተሞች ናቸው ?
- ባህር ዳር
- ጎንደር
- ደሴ
- ኮምቦልቻ
- ወልዲያ
- ሰቆጣ
- ደብረ ብርሃን
- ደብረ ማርቆስ
- ደብረ ታቦር
- ፍኖተ ሰላም
- ገንደውሃ
- ከሚሴ
- ጋሸና
- ቡሬ
- ባቲ
- ደጀን
- ደባርቅ
- ኢንጅባራ
- ሁመራ ናቸው።

በተለያዩ ከተሞች የሚገኙ ነዋሪዎችን ስለ ተለቀቀው የኢንተርኔት አገልግሎት በተመለከተ ጠይቀናቸው ፍጥነቱ ያን ያህል እንደሆነ እንዲሁም መጨናነቅም እንደሚታይ ነገር ግን እንደተለቀቀ አመልክተዋል።

#TikvahEthiopia

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Raya እንደ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት (UN) የሰብዓዊ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ሪፖርት መሰረት ከራያ አላማጣ ገጠራማ አካባቢዎች የተፈናቀሉ ሰዎች ቁጥር ከ50 ሺህ በልጧል። 42 ሺህ ዜጎች ቆቦ ፤ 8,300 ሰዎች ሰቆጣ ይገኛሉ። የተፈናቀሉት ከራያ አላማጣ፣ ዛታ፣ ኦፍላ ነው። አብዛኞቹ ህጻናት ፣ ሴቶች ፣ ወጣቶች እና በእድሜ የገፉ አዛውንቶች ናቸው። #UNOCHA @tikvahethiopia
🔈 #የተፈናቃዮችድምጽ

ሚያዚያ ወር በተቀሰቀሰው ግጭት ከኮረም፣ ኦፍላ፣ ዛታ ወረዳዎች የተፈናቀሉ ዜጎች ዋግ ኽምራ እና ሰሜን ወሎ ዞን ይገኛሉ።

እነዚህ ወገኖች ላለፉት ሶስት ወራት ያለ በቂ ሰብዓዊ ድጋፍ በመቆየታቸው የከፋ ችግር ላይ እንደሚገኙ አመልክተዋል።

አጠቃላይ ተፈናቃዮች ከ22 ሺህ ይልቃሉ።

ተፈናቃዮች ምን አሉ ?

- አሳሳቢ የምግብ እና የመጠለያ ችግር አለ።
- እያንዳንዱ በሰው ቤት ተጠግቶ ነው ያለው።
- ቤተዘመድ እያገዛቸው እንጂ ለ3 ወር የከፋ ችግር ላይ ወድቀው ነው የሚገኙት።
- በ3 ወር ምንም የተደረገ ድጋፍ የለም።
- ዋግኽምራ ዞን የተቻለውን ቢያደርግም ከአቅሙ በላይ ነው። ብዙ ሰው ነው ያለው።
- አብዛኛው በረዳ ወቅዷል።
- ዘመድ ያለውም ዘመዱ ጋር ተቸግሮ ነው የሚኖረው።
- እየለመ የሚበላ አለ፣ ጉልበት ያለውም ተቀጥሮ የሚሰራ አለ።
- አንዳንድ እናቶች መጠለያ ተሰጥቷቸው ነበር ግን ልጆቻቸው ሲታመሙ ቤት ተከራይተው ወጥትተዋል። በዚህ ኑሮ ውድነት መኖር አልቻሉም።
- ተፈናቃዮቹ በቄያቸው ቤት እና ስራ ነበራቸው።

የዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን አደጋ መከላከል እና ምግብ ዋስትና ምን አለ ?

° ከ11 ሺህ ተፈናቃዮች ነው ያሉት።
° አሁን ባለንበት ሁኔታ መጠለያ ማዘጋጀት አንችልም። ድንኳንም የለንም።
° የምንመግበውን ተቸግረን በመጡ ጊዜ ለአንድ ሰው 25 ኪ/ግ ነው  የሰጠነው። ከመጠባበቂያ !
° የሰላሙ ሁኔታ አለ፣ መንገድ ዝግትግት ያለ ነው ሌላ አካል ድጋፍ ላምጣ ቢል እንኳን።
° አካባቢው ዝናብ አጠር ነው። በድርቅ ይጠቃል። የዓምናው ድርቅም ጉዳቱ እንዳለ ነው። ብዙ ሰው ተጎድቷል። አሁን ተፈናቃይ ተጨምሮ ይቅርና በፊትም ብዙ ችግር አለ።
° በህጻናት አድን ድርጅት ካሽ 14 ሺህ በሁለት ዙር ለመስጠት ልየታ እየተደረገ ነው።
° ያሉት ተፈናቃዮች ከኦሮሚያ፣ ከመተማ፣ በሰሜን ጦርነትም ተፈናቅለው ያልሄዱ አሉ።

በአሁኑ ወቅት እርሳቸውም ተፈናቃይ መሆናቸውን የገለጹትና ኮረም ከተማን ለሁለት ዓመት በከንቲባነት የመሩት አቶ ብርሃኑ ኀይሉ፣  የተፈናቀለው ሕዝብ ብዛት ከ22 ሺሕ እንደሚበልጥ ገልጸው ፥ የምግብ አቅርቦቱ እጥረት አሳሳቢ መሆኑን አመልክተዋል፡፡

" እርዳታ ጠይቀናል። ለ3 ወራት ተከታታይ እርዳታ የለም።  ክልሉ የሰጠን ነገር የለም፤ ጭራሽ አላነገረንም " ብለዋል።

የአማራ ክልል አደጋ መከላከል እና ምግብ ዋስትና ኮሚሽን " መረጃ አለን ፤ ለተፈናቃዮቹ የምግብ አቅርቦት ጥያቄ በቅርቡ ምላሽ ይሰጣል ፤ እርዳታም ይጓጓዛልም " ሲል ገልጸዋል። #ቪኦኤ

@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
#DStvEthiopia

የአውሮፓ ዋንጫ ፍፃሜ ደረሰ !

ከከባድ ትንቅንቅ በኋላ ስፔን እና እንግሊዝ ለፍፃሜ በጀርመን ኦሎምፒያስታዲዮን ይገናኛሉ!
እንግሊዝ ለመጀመሪያ ጊዜ ዋንጫውን ታነሳ ይሆን? ስፔንስ የአሸናፊነት መንገዷን ትቀጥል ይሆን? 

⚽️ Spain vs England ሐምሌ 7 ከምሽቱ 4፡00 ሰዓት | 10፡00 PM

👉SS Football ቻናል 225 በጎጆ ፓኬጅ
👉SS Euro2024 ቻናል 222 በሜዳ  ፓኬጅ

ዛሬውኑ ደንበኝነትዎን ያራዝሙ ጨዋታዎችን ከትንታኔ ፣ ከተጫዋች ብቃት እስከ ቡድን ወኔ በሱፐርስፖርት ልዩ በቀጥታ ይከታተሉ!
የዲኤስቲቪ አገልግሎቶችን ለማግኘት ከታች ያለውን የMyDStv Telegram bot ሊንክ ይጫኑ!
👇
https://bit.ly/3RFtEvh

#Euro2024onDStv #ሁሉምያለውእኛጋርነው #DStvEthiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ቪድዮ : የቀድሞ የአሜሪካ ፕ/ት ዶናልድ ትራምፕ የግድያው ሙከራ በተደረገባቸው ወቅት እሳቸው ቅስቀሳ ከሚያደርጉበት ስፍራ በቅርብ ርቀት በሚገኝ ጣሪያ ላይ የነበሩ የ " ሴክሬት ሰርቪስ " የስናይፐር ተኳሾች የግድያ ሙከራውን ባደረገው ሰው ላይ ምላሽ ሲሰጡ ታይተዋል። አንድ ተቀርጾ በማህበራዊ ሚዲያ የተሰራጨ ቪድዮ ሁለት የሴክሬት ሰርቪስ ስናይፐር ተኳሾች በፍጥነት ኢላማ አድርገው የግድያ ሙከራ ባደረገው…
#USA

በትራምፕ ላይ የግድያ ሙከራ ሲደረግ የሚያሳዩ ቪድዮዎች ወጥተዋል።

የግድያ ሙከራ ያደረገው ቶማስ ማቲው ክሮክስ የተባለው የ20 ዓመት ወጣት ትራምፕ የምርጫ ቅስቀሳ ከሚደረጉበት ስፍራ ውጭ ላይ ካለ አንድ ጣራ ላይ ተኝቶ ትራምፕን ለመግደል በተደጋጋሚ ሲተኩስ ታይቷል።

ብዙ ሳይቆይ በሴክሬት ሰርቪስ የስናይፐር ተኳሾች ተመቶ ተገድሏል።

የተለያዩ የአይን እማኞች ለቴሌቪዥን ጣቢያዎች በሰጠቱ ቃል ፥ የግድያ ሙከራ ያደረገው ወጣት ጣራ ላይ ሲወጣና ከአንዱ ጣራ ወደሌላኛው ጣራ ሲሄድ በኋላም ተኝቶ ትራምፕ ላይ ሲተኩስ መመልከታቸውን ተናግረዋል።

ድርጊቱ ከመፈጸሙ በፊት ጣራ ላይ መሳሪያ የያዘ ሰው እንዳለ ለፖሊስ አባላት ጥቆማ ሰጥተው እንደነበር ጠቁመዋል።

የግድያ ሙከራው እስኪደረግ ድረስ ጥቆማቸው ለምን ችላ እንደተባለ ግራ እንዳጋባቸው ተናግረዋል።

አንዳንድ የደህንነት ባለሞያዎች ሁሉም ጣራዎች ላይ ለምን የሴክሬት ሰርቪስ ሰዎች እንዳልነበሩ እና በሰዓቱ የነበረው የደህንነት ስራው ምርመራ እንዳሚፈልግ ጠይቀዋል።

የአሜሪካ " ሴክሬት ሰርቪስ " ዋነኛ ስራው የአሁን እና ቀድሞ ፕሬዜዳንቶችን ደህንነት ማስጠበቅ ነው።

በሀገሪቱ በአሁን ወይም በቀድሞ ፕሬዜዳንቶች ላይ የግድያ ሙከራ ሲደረግ የአሁኑ ከ43 ዓመታት በኋላ ነው።

ከ43 ዓመታት በፊት ሮናልድ ሬገን በተሞከረባቸው ግድያ ክፉኛ ተጎድተው ለጥቂት ነበር ከሞት ያመለጡት።

#USA
#DonaldTrump

@tikvahethiopia