TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.2K photos
1.5K videos
211 files
4.1K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
" በየቤቱ የቁም እንስሳት ማረድ / በየአካባቢው ቅርጫ አድርጎ መከፋፈል አልተከለከለም " - የአዲስ አበባ የሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ

የአዲስ አበባ ከተማ የሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ ፥ ከትንሳዔ በዓል ጋር በተያያዘ " ህብረተሰቡ በየቤቱ የቁም እንስሳት እርድ በማካሄድ ወይም በየአካባቢው ቅርጫ በማድረግ የሚከፋፈልበት አሰራር ተከልክሏል " በሚል በማህበራዊ ሚዲያ እየተሰራጨ ያለው መረጃ #ሐሰተኛ ነው ሲል አሳወቀ።

ከዚህም ጋር በተያያዘ #ምንም_ዓይነት_ክልከላ ያልተደረገ መሆኑን አረጋግጧል።

ነገር ግን በየአካባቢው #በሕገወጥ_መንገድ እርድ በመፈፀም ለሆቴሎች እና ለስጋ ቤቶች በማከፋፈል ተግባር ላይ የተሰማሩ አካላት የቁም እንስሳቱ ጤንነት ባልተረጋገጠበት ሁኔታ ድርጊቱ በከተማው ነዋሪዎች ጤንነት ላይ ጉዳት የሚያደርስ በመሆኑ ጥብቅ ቁጥጥር ይደረጋል ብሏል።

የከተማዋ ነዋሪዎችም ትብብር እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርቧል።

@tikvahethiopia
#DV2025

የአሜሪካ ዲቪ ሎተሪ (Diversity Visa) 2025 አሸናፊዎች ነገ ይፋ ይደረጋሉ።

ለዲቪ (Diversity Visa) 2025 ማመልከቻ የሞሉ በ dvprogram.state.gov/ESC/ ብቻ የማረጋገጫ ቁጥራቸውን በማስገባት ውጤቱን ወይም ማሸነፍ አለማሸነፋቸውን መመልከት ይችላሉ።

NB. የማረጋገጫ ቁጥር ማመልከቻው ሲሞላ የተሰጠ ነው። ይህ ቁጥር የጠፋበት Forgot Confirmation Number በማለት አስፈለጊ መረጃ በመሙላት በኢሜል አዲስ ቁጥር ማግኘት ይቻላል።

ውጤቱ በኢትዮጵያ ሰዓት አቆጣጠር ከምሽት 1 ሰዓት ጀምሮ ይፋ ይሆናል።

የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር " የዲቪ (DV) ሎተሪ አሸንፋችኋል ፣ ከአሜሪካ ኤምባሲ ነው ምንደውለው / ይህን ኢሜል / ቴክስት የምንልከው " በማለት #የሚያጭበረብሩ_አካላት ስለሚኖሩ አመልካቾች እንዲጠነቀቁ አሳስቧል።

አንድ አመልካች ዲቪ 2025 ደርሶት እንደሆነ እና እንዳልሆነ ማወቅ የሚችልበት ብቸኛው መንገድ ከላይ የተጠቀሰው ድረገጽ መሆኑን አስገንዝቧል።

አሜሪካ በየዓመቱ ከአፍሪካ (ኢትዮጵያ ጨምሮ) ፣ እስያ ፣ አውሮፓ፣ ሰሜን አሜሪካ፣ ደቡብ አሜሪካ እና አውስትራሊያ 55 ሺህ ሰዎችን በዲቪ (DV) ሎተሪ ወደ ሀገሯ ታስገባለች።

@tikvahethiopia
#LionInternationalBank

አንበሳ ኢንተርናሽናል ባንክ መጪውን የፋሲካ በዓል ምክንያት በማድረግ ልዩ ልዩ ሽልማቶችን የሚያስገኙ የጥያቄና መልስ ውድድር ይዞላችሁ መጥቷል፡፡
እርስዎም የሽልማቱ ተሳታፊ ለመሆን ከታች ያሉትን የባንኩን ይፋዊ የቴሌግራም እና የፌስቡክ ገፆች በመቀላቀል እና ጥያቄውን ቀድመው በመመለስ ሽልማቶችን የራስዎ ያድርጉl
ጥያቄው የሚካሄዳው እሁድ ሚያዚያ 27 ከቀኑ 5:00 ሰዓት ሲሆን ጥያቄውን ቀድመው ለመለሱ 3 ሰዎች ሊሸልም ዝግጅቱን ጨርሷል።

1ኛ ለሚወጣ ተሸላሚ የበግ ሽልማት
2ኛ ለሚወጣ  የ5000 ብር ሽልማት 
3ኛ ለሚወጣ የ3000 ብር ሽልማት      ያበረክትላችኋል።

እርስዎም ለወዳጅ ዘመድዎ በማጋራት የውድድሩ ተሳታፊ ይሁኑ!!

አንበሳ ኢንተርናሽናል ባንክ     
    የስኬትዎ አጋር!   

[Telegram]  [Facebook]

https://t.iss.one/LionBankSC

#LIB #lioninternationalbank #anbesabank #keytosuccess
#ለጥንቃቄ

በአዲስ አበባ ከተማ ቂርቆስ ክ/ከተማ በተለያየ ቦታ እየተንቀሳቀሱ የመኪና ስፖኪዮ በመስረቅ ወንጀል የተጠረጠሩ 4 ግለሰቦች (ታዳጊ ልጆች) በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የቂርቆስ ክ/ከተማ ፖሊስ መምሪያ ገልጿል።

ተጠርጣሪዎቹ ሚያዚያ 23 እና 24/ 2016 ዓ.ም ወረዳ 2 ጋዜቦ አደባባይ እና ወረዳ 9 አካባቢ ነው የተያዙት ተብሏል።

ተጠርጣሪዎቹ #ከመስቀል፣አደባባይ ወደ #ቦሌ በሚወስደው መንገድ ላይ የትራፊክ መብራቶችና ተሽከርካሪ በሚቆምባቸው ሌሎች ቦታዎች ላይ በመንቀሳቀስ ስፖኪዮ ሲሰርቁ እንደነበር ፖሊስ አመልክቷል።

በዚህ የወንጀል ድርጊት ለይ ተሳትፈው የተገኙት ህፃናቶች መሆናቸውን ገልጿል።

በዚህ መነሻ በተደረገ ምርመራ ለህፃናቱ ስምሪት የሚሰጡ የተደራጁ ወንጀለኞች መኖራቸውን ፖሊስ ማረጋገጡን አሳውቋል።

" አንዳንድ ህፃናት መኪና የሚጠብቁ እንዲሁም ደግሞ እርዳታ የሚፈልጉ መስለው በመቅረብ የወንጀል ተግባራት እንደሚፈፅሙ አሽከርካሪዎች ተገንዝበው በትራፊክ መብራቶችም ሆነ የትራፊክ ፍሰት በሚበዛባቸው ሌሎች ቦታዎች ላይ ሲቆሙ እና በዝግታ ሲያሽከረክሩ ተገቢውን ጥንቃቄ ሊያደርጉ ይገባል " ሲል ፖሊስ መልዕክት አስተላልፏል።

#AddisAbabaPolice

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና የሚሰጥበት ቀን ይፋ ሆነ። የ2016 የትምህርት ዘመን የኢትዮጵያ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ (12ኛ ክፍል) ፈተና የሚሰጥበት ቀን ይፋ ሆኗል። የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ከሐምሌ 3 እስከ ሐምሌ 5 ለማህበራዊ ሳይንስ ፤ ከሐምሌ  9 እስከ ሐምሌ 11/2016 ዓ/ም ለተፈጥሮ ሳይንስ ተፈታኞች በበይነ መረብ (Online) እና በዩኒቨርሲቲ ውስጥ በወረቀት…
" የኦንላይን ፈተናው በተመረጡ 25 ከተሞች ይሰጣል " - ትምህርት ሚኒስቴር

ትምህርት ሚኒስቴር የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በተመረጡ 25 ከተሞች በኦንላይን እንደሚሰጥ ገልጿል።

ተፈታኝ ተማሪዎች በኦንላይን ለሚሰጠው ፈተና እንዲዘጋጁ ማሳሰቢያ ተላልፏል።

የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ አየለች እሸቴ የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተናን ከሁሉም ክልሎች በተመረጡ 25 ከተሞች በኦንላይን ለመስጠት ዝግጅት እየተደረገ ነው ብለዋል።

በወረቀት ከሚሰጠው ፈተና ጎን ለጎን የሚሰጠው የኦንላይን ፈተና ተማሪዎች ከቦታ ቦታ ሳይጓጓዙ በየአካባቢያቸው #ቤተሰቦቻቸው_ጋር_እያደሩ ፈተናውን ይወስዳሉ ሲሉ አሳውቀዋል።

ወ/ሮ አየለች ፤ ተማሪዎች ለፈተናው እንዲዘጋጁ፣ ባለድርሻ አካላት ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ፣ ወላጆችንም ልጆቻቸውን እንዲደግፉ ጥሪ አቅርበዋል።

ትምህርት ሚኒስቴር እስካሁን ፈተናው በኦንላይን የሚሰጥባቸውን 25 ከተሞች በዝርዝር ይፋ አላደረገም።

የኦንላይን ተፈታኞች ፈተናውን ከመውሰዳቸው በፊት ደጋግመው እንዲለማመዱ ቅድመ ዝግጅት እየተደረገ ነው ተብሏል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update የአብን አባሉ አቶ ጣሂር መሐመድ " በግል ምክንያት " ከአማራ ክልል ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ኃላፊነት መልቀቃቸውን ለቢቢሲ አማርኛው አገልግሎት ተናግረዋል። " ከባለፉት ሶስት፣ አራት ወራት ወዲህ አንስቶ ከኃላፊነት የመልቀቅ ጉዳይ ላይ ከክልሉ አመራሮች ጋር በዝርዝር ንግግር አድርጌያለሁ " ያለቱ አቶ ጣሂር " የክልሉ መንግሥት ጥያቄውን ተቀብሏል " ብለዋል። " ትንሽ የቤተሰብ ጉዳይ ስለነበረብኝ…
“ ...  ተገምግመው ተነሱ እንጅ አመልክተው አልተነሱም ” - አየለ አናውጤ (ዶ/ር)

የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) አባሉ አቶ ጣሂር መሐመድ " በግል ምክንያት" ከአማራ ክልል ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ኃላፊነት መልቀቃቸውን፤ በእሳቸው ምትክ ሌላኛው የፓርቲው አባል አቶ መልካሙ ፀጋዬ መሾማቸውን መረጃ አድርሰናችሁ ነበር።

አቶ ጣሂር ለቢቢሲ አማርኛው ክፍል በሰጡት ቃል፣ " ከባለፉት ሶስት፣ አራት ወራት ወዲህ አንስቶ ከኃላፊነት የመልቀቅ ጉዳይ ላይ ከክልሉ አመራሮች ጋር በዝርዝር ንግግር አድርጌያለሁ። የክልሉ መንግሥት ጥያቄውን ተቀብሏል " ነበር ያሉት።

ይሁን እንጂ አቶ ጣሂር ከኃላፊነት የተነሱት “ በግል ምክንያት ” እንደሆነ ቃላቸውን ከሰጡ በኋላ፣ የአማራ ክልል ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ም/ ኃላፊ ዶክተር  አየለ አናውጤ በፌስቡክ ገጻቸው ባሰራጩት መልዕክት፣ “ ተገምግመው ተነሱ እንጂ አመልክተው አልተነሱም ” ብለዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ በበኩሉ፣ የተነሱት በምን ምክንያት እንደሆነ ተጨማሪ ማብራሪያ እንዲሰጡ ለአየለ አናውጤ (ዶ/ር) ጥያቄ ያቀረበ ሲሆን፣ “ በፌስቡክ ገፄ በዝርዝር ፅፌዋለሁ። ለጊዜው ከዚህ የተለየ ነገር የለኝም ” ብለው ለዘገባ ያንኑ ፅሑፍ መጠቀም እንደሚቻል ገልጸዋል።

በፌስቡክ ገጻቸው ባሰራጩት ፅሑፍ “ ላለፈው አንድ አመት ተቋሙ በአንድ በኩል በአግባቡ እየተሰራ ባለመሆኑ፣ በሌላ በኩል ከፍተኛ የሀብት ብክነት አለ ብለን በማመናችን ተደጋጋሚ ግምገማዎች አድርገናል ” ብለዋል።

“ ለ2 ዓመት ከ8 ወራት አዲስ አበባ ተቀምጠው በ3 ወር አንዴ እየመጡ፣ ለዛውም ተደብቀው ገብተው ሕገ ወጥ ድርጊት ፈጽመው ይሄዳሉ ” ሲሉም ገልጸዋል።

“ በመሆኑም በቢሮው ማኔጅመንት ፣ በዘርፉ ማኔጅመንት ፣ በክልል ም/ቤት ቋሚ ኮሚቴ፣ በከተማ ክላስተር ደረጃ በርካታ ግምገማዎች አድርገናል ” ያሉት ዶ/ር አየለ “ በመጨረሻ ከኃላፊነት እንደተነሱ ከተገለጸልን ቆይቷል፤ ደብዳቤው በእርሳቸው ጥያቄ ቢዘገይም ” ብለዋል።

“ ይህ ብቻ ሳይሆን ከወር በፊት የክልሉ መንግስት ልዩ የኦዲት ምርመራ አድርጎ እርምጃ እንዲወስድ ለርዕሰ መስተዳደሩ በደብዳቤ አሳውቄአለሁ ” የሚለውንና ሌሎች ማብራሪያዎች ሰጥተው፣ “ ተገምግመው ተነሱ እንጂ በግል ምክንያት በእሳቸው ጠያቂነት አልተነሱም ” ነው ያሉት። (ሙሉ ፅሑፋቸው ከላይ ተያይዟል)

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
#ለጥንቃቄ🚨

" በከፍተኛ ሁኔታ የሚንቀሳቀስ #የጅብ_መንጋ ተከስቷል ማህበረሰቡ ሊጠነቀቅ ይገባል " - የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሠላምና ጸጥታ ቢሮ

ከሰሞኑ በማዕከላዊ ኢትዮጵያዊ ክልል በምሽት አንዳንዴም በቀን ጅቦች በሰው ላይ በተለይ በህጻናት እና ሴቶች እንዲሁም በአቅመደካሞች ላይ ጥቃት እያደረሱ ተነግሯል።

በደረሰን መረጃ በስልጤ ዞን 2 ሰዎች ሲሞቱ በሀዲያ ዞን እንዲሁም በሀላባ አካባቢ ሌሎች 2 የአካል ጉድለት ያደረሱ ጉዳቶች ተመዝግበዋል።

ከሟቾች አንዷ የ3 ዓመት ህጻን ናት። በስልጤ ዞን ላንፉሮ ወረዳ ነዋሪ የሆነችው ይህች ህጻን በእናቷ ጀርባ ላይ ታዝላ (እናትየው ከወፍጮ ቤት እህል አስፈጭታ ስትመለስ) በነበረበት ወቅት አድፍጦ ይጠብቅ በነበረ የተራበ ጅብ ተወስዳ ጉዳት ከደረሰባት በኃላ ህይወቷ አልፏል።

በአጠቃላይ ያለውን ሁኔታ በተመለከተ ቲክቫህ ኢትዮጵያ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሰላምና ጸጥታ ጉዳይ ኃላፊ የሆኑትን አቶ ተመስገን ካሳን አነጋግሯቸዋል።

አቶ ተመስገን ፤ በዚህ አመት ከፍተኛ የጅብ መንጋ መፈጠሩን አመልከተዋል። መንጋው ሲበዛ ለረሀብ በመጋለጡ ወደ ሰዎች እንደሚሄድ ገልጸዋል።

እስካሁን በክልሉ የሁለት ሞትና በርካታ ለሞት ያላበቁ ጉዳቶች ሪፖርት እንደደረሳቸዉ ጠቅሰዉ ጉዳቱ በህጻናት ላይ የበረታ መሆኑን ተናግረዋል።

አሁን ላይ ባካሄዱት ግምገማ መንጋዉ ከፍተኛ ቁጥር ያለው እንደሆነ ገልጸዋል። ይህን ለማጥፋት ከሚመለከተዉ አካል ጋር እየተነጋገሩ መሆኑን ጠቅሰዋል።

ማህበረሰቡ ግን የራሱን ጥንቃቄ እንዲያደርግ አሳስበዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyHawassa

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#DV2025 የአሜሪካ ዲቪ ሎተሪ (Diversity Visa) 2025 አሸናፊዎች ነገ ይፋ ይደረጋሉ። ለዲቪ (Diversity Visa) 2025 ማመልከቻ የሞሉ በ dvprogram.state.gov/ESC/ ብቻ የማረጋገጫ ቁጥራቸውን በማስገባት ውጤቱን ወይም ማሸነፍ አለማሸነፋቸውን መመልከት ይችላሉ። NB. የማረጋገጫ ቁጥር ማመልከቻው ሲሞላ የተሰጠ ነው። ይህ ቁጥር የጠፋበት Forgot Confirmation…
ዲቪ 2025 ዛሬ ምሽት ይፋ ሆኗል።

የአሜሪካ ዲቪ (Diversity Visa) ሎተሪ 2025 ዛሬ ምሽት ይፋ መደረጉን የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መ/ቤት አሳውቋል።

መ/ቤቱ፥ አመልካቾች መመረጥ አለመመረጣቸውን / ደርሷቸው እንደሆነ እና እንዳልሆነ ማየት የሚችሉት በ dvprogram.state.gov/ESC/ ላይ የማረጋገጫ ቁጥራቸውን በማስገባት #ብቻ መሆኑን አሳስቧል።

ከዚህ ውጭ የዲቪ ውጤት የሚታይበት ምንም አይነት መንገድ የለም።

N.B. ዲቪ የሚደርሳቸው ሰዎች የሚስጥር ቁጥሩን እስከ ቀጣይ አመት መስከረም መጨረሻ ቀናት መያዝ አለባቸው።

ምናልባትም  " ዲቪ ደርሷችኃል ከአሜሪካ ኤምባሲ ነው የምንደውለው፣ ኢሜል / ቴክስት መልዕክት የሚንልከው " የሚሉ አጭበርባሪ ስለሚኖሩ ጥንቃቄ አድርጉ ተብሏል።

እንደ አሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ፥ የዲቪ ተመራጭ መሆን ለቪዛ ወይም ለቃለመጠይቅ ዋስትና አይሆንም።

የዲቪ ሎተሪ ተመራጭ መሆን የቪዛ ጥያቄ ለማቅረብ የመጀመሪያው መስፈርት ሲሆን በቀጥታ ለቪዛ ወይም ለቃለመጠይቅ ዋስትና አይሰጥም።

@tikvahethiopia
#ትንሣኤሎተሪ

የ2016 የትንሳኤ ሎተሪ ዕጣ የወጣ ሲሆን 10 ሚሊዮን ብር ባለዕድለኛ የሚያደርገው የአንደኛ ዕጣ ቁጥር 1407747 ሆኖ ወጥቷል።

5 ሚሊዮን ብር የሚያስገኘው የሁለተኛው የዕጣ ቁጥር ደግሞ 0179265 ሆኖ ወጥቷል።

የ2.5 ሚሊዮን ብሩ የሶስተኛው ዕጣ ቁጥር 2160591 እንዲሁም የ1.5 ሚሊዮን ብር የ4ኛ ዕጣ ቁጥር 0165786 ሆኖ ወጥቷል።

(ተጨማሪ ዝርዝር የዕጣ ማውጫው ከላይ ተያይዟል)

#NationalLottery

@tikvahethiopia
#ትንሣኤ

ለመላው #የክርስትና_እምነት_ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለብርሃነ ትንሣኤው በሰላም አደረሳችሁ !

" በዚህ የለም ፤ እርሱ እንደተናገረው ተነሥቶአል "  


በማቴዎስ ወንጌል ፥ " እነሆ ታላቅ የምድር መናወጥ ሆነ፤ የእግዚአብሔር መልአክ ከሰማይ ወርዶአልና ፤ ቀርቦም በመቃብሩ አፍ ላይ ድንጋይዋን አንከባሎ በላይዋ ተቀመጠ፡፡

መልኩም እንደ መብረቅ ፤ ልብሱም እንደ በረዶ ነጭ ነበር፡፡

እርሱንም ከመፍራት የተነሣ መቃብሩን የሚጠብቁ ታወኩ ፤ እንደ በድንም ሆኑ፡፡

መልአኩ መልሶ ሴቶቹን እንዲህ አላቸው፥ ' እናንተስ #አትፍሩ ፤ የተሰቀለውን #ኢየሱስን_እንደምትሹ አውቃለሁና፡፡ በዚህ የለም ፤ እርሱ እንደ ተናገረው ተነሥቶአል ' " ተብሎ እንደተጻፈው #መድኃኒዓለም ብርሃንን ተጎናጽፎ በታላቅ ኃይልና ሥልጣን በክብር #ተነሥቶአል፡፡

መልካም የትንሣኤ በዓል !
በዓሉ የሰላምና የፍቅር ይሆን ዘንድ እንመኛለን !


#TikvahEthiopiaFamily❤️

@tikvahethiopia
#ለጥንቃቄ🚨

“ በጀኔተር ላይ በተነሳ የእሳት አደጋ የ1 ሰው ሕይወት አልፏል ” - አቶ ንጋቱ ማሞ

ትላንት ምሽት 3:03 ሰዓት ላይ በአዲስ አበባ ቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 12 ማርያም ማዞሪያ እየተባለ በሚጠራው አካባቢ በእሳት አደጋ የ1 ሰው ሕይወት ማለፉን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የእሳትና ሥራ አመራር ኮሚሽን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።

የኮሚሽኑ የሕዝብ ግንኙነት ባለሙያው አቶ ንጋቱ ማሞ በሰጡት ቃል፣ “ ኤሌክትሪክ በመቋረጡ ጀነሬተር ለማስነሳት ነዳጅ በመጨመር ላይ የነበረ የ26 ዓመት የሆቴል ሠራተኛ በጀነሬተሩ ላይ በተነሳ የእሳት አደጋ ወዲያው ሕይወቱ አልፏል ” ብለዋል።

“ የአደጋ ጊዜ ሠራተኞች በስፍራው ፈጥነው ቢደርሱም በጀነሬተሩ ላይ በተፈጠረው ከፍተኛ እሳት አስቀድሞ ሕይወቱ  አልፏል ” ነው ያሉት።

አቶ ንጋቱ፣ “ በጄኔሬተር የነዳጅ ታንከር ውስጥ ነዳጅ ከተጨመረ በኋላ #ቫልቩ በአግባቡ መዘጋቱን ማረጋገጥ ፣ እንዲሁም ጄነሬተሩ አስቀድሞ አገልግሎት ሲሰጥ ከቆየና ግለት ካለ ነዳጅ ከመጨመር መቆጠብ ያስፈልጋል ” ሲሉ አስገንዝበዋል።

በሌላ በኩል ፥ የበዓል ስራዎች እንቅስቃሴዎች አሁንም ድረስ ያልጠተናቀቁ በመሆኑ ህብረተሰቡ ከኮሚሽን መስሪያ ቤቱ እየተላለፉ ያሉ የጥንቃቄ መልዕክቶች እንዲተገብር አሳስበዋል።

የእሳትና ሌሎች ድንገተኛ አደጋዎች ሲያጋጥሙ ፣ እንዲሁም ለአንቡላንስ አገልግሎት ማህበረሰቡ በኮሚሽኑ ስልክ #በ939 ላይ ፈጥኖ ደውሎ እንዲያሳውቅ ጥሪ አቅርበዋል።

በተጨማሪ መረጃ ፤ የአዲስ አበባ ፖሊስ በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ በስሊንደር ፍንዳታ ምክንያት የ1 ሰው ህይወት ማለፉን ገልጿል።

የድሮው ቄራ አካባቢ ትላንት ቀን 9:30 በአነስተኛ መጠጥ ቤት ውስጥ ድስት ተጥዶበት በነበረ ስሊንደር ላይ በተፈጠረው ፍንዳታ ዕድሜው 30 ዓመት የሚገመት 1 ሰው ህይወቱ ያለፈ ሲሆን በ3 ሰዎች ላይ ከባድና ቀላል ጉዳት ደርሶባቸው ወደ ህክምና ተወስደዋል።

ፖሊስ በበዓል ወቅት የምንጠቀማቸውን ምግቦች ስናበስል #ከሲልንደር_አጠቃቀም ጋር በተያያዘ አስፈላጊውን ጥንቃቄ እንዲደረግ አሳስቧል።

#TikvahEthiopiaFamilyAddisAbaba

@tikvahethiopia
" የ2 ሰዎችን አስክሬን እየፈለግን ነው " - የዞኑ የሰላምና ጸጥታ ቢሮ

በሀላባ ዞን ንፋስ እና በረዶ ቀላቅሎ የጣለዉ ከባድ ዝናብ ባስከተለው ጎርፍ የሰዎች ህይወት ጠፍቷል።

ከሰው ህይወት መጥፋት ባለፈ በአዝእርትና በብረት ላይ ጉዳት አድርሷል።

ይህ ሁሉ ጉዳት የደረሰው በአጭር ጊዜ ውስጥ ሲሆን ከዝናቡ ጋር በተያያዘ የተከሰተው የመሬት መሰንጠቅ በህብረተሰቡ ዘንድ ድንጋጤ  መፍጠሩ ተነግሯል።

በጉዳዩ ላይ ቃላቸውን ለቲኪቫህ ኢትዮጵያ የሰጡት የሀላባ ዞን ሰላምና ጸጥታ መምሪያ ሀላፊው አቶ ሸምሰዲን ጉታጎ ፥ " ሁኔታዉ እጅግ አስደንጋጭ ነው " ብለዋል።

በጎርፍ አደጋው የ5 ሰዎች ህይወት ጠፍቷል ሲሉ ገልጸዋል።

" አሁንም በጎርፍ ተወስደዉ ከሞቱት 5 ወገኖች መካከል የሁለቱን  አስክሬን ማግኘት አልቻልንም " ብለዋል።

የአስከሬን ፍለጋው ሻላ ሀይቅ ውስጥ እየተካሄደ መሆኑን እና የኦሮሚያ የጸጥታ ኃይሎች በተለይ ዋናተኞች እያገዟቸዉ መሆኑን አስረድተዋል።

በተጨማሪም አደጋው በርካታ የግለሰብ ቤቶችን እንዲሁም ዌራ ወረዳ ያለን ሆስፒታልን ሙሉ በሙሉ ከስራ ዉጭ እንዳደረገው ገልጸዋል።

በዞኑ በበርካታ ቦታዎች ላይ የተፈጠረው የመሬት መሰንጠቅም በህብረተሰቡ ዘንድ ድንጋጤ መፍጠሩን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyHawassa

@tikvahethiopia
#Hawassa

" እንደሚወራው አይደለም ፤ ከአንድ ቤት በላይ የከፋ ጉዳት አላደረሰም " - የሀዋሳ ከተማ ሰላምና ጸጥታ ቢሮ

በሀዋሳ ከተማ የተነሳ የእሳት አደጋ አንድ መዝናኛ ቤት አውድሞ በቁጥጥር ስር መዋሉ ተሰምቷል።

ዛሬ ረፋድ 4 ሰዓት አካባቢ በከተማው በተለምዶ 05 በመባል በሚታውቀዉ ሰፈር (አደባባይ አለፍ ብሎ ወይም ከመድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን ፊት ለፊት/አስፓልት ተሻግሮ) የተነሳው የእሳት አደጋ አንድ መዝናኛ ቤትን በከፋ ሁኔታ አውድሞ በቁጥጥር ስር ውሏል።

እሳት አደጋው የደረሰው በማህበር ተደራጅተዉ በምግብና መጠጥ ሽያጭ የሚተዳደሩ ወጣቶች ውስጥ በአንደኛው ቤት ነው።

የእሳት አደጋው መፈጠሩን ተከትሎ በአካባቢው ግርግር ቢፈጠርም ከሰአት በኋላ ሁሉም ተረጋግቶ ወደተለመደው እንቅስቃሴ ተመልሷል።

ቃላቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የሰጡት የከተማው ሰላምና ጸጥታ መምሪያ ሀላፊ አቶ ወንድሙ ቶርባ ፤ " ችግሩ እንደተፈጠረ የሀዋሳ ከተማ ማዘጋጃ ቤት እና የኢንዱስትሪው መንደር የእሳት ብርጌድ በፍጥነት ደርሶ ተቆጣጥሮታል " ብለዋል።

" ከፍተኛ አደጋ በደረሰበት መዝናኛ ቤት ውስጥ በነበረ የኤሌክትሪክ ገመድ ላይ በተፈጠረ እሳት ነው አደጋው የተፈጠረው " ሲሉ ገልጸዋል።

በአደጋው በመዝናኛ ቤቱ ላይ ውድመት መድረሱን ጠቁመዋል።

አደጋው በደረሰበት ወቅት በአካባቢው ወደነበሩ ቤቶች እሳቱ እንዳይስፋፋ ሌሎች ሰዎች እቃቸዉን ቢያወጡም ቆይተው ወደቤቶቻቸዉ ተመልሰዋል ብለዋል።

" ከሁኔታው ጋር በተያያዘ ግርግር ቢፈጠርም ሰዎች ተመልሰው ወደ ስራቸዉ ገብተዋል " ሲሉ አክለዋል።

" አደጋው እንደሚወራዉ #እጅግ የከፋ አይደለም " ያሉ ሲሆን ከአንድ ቤት በላይ የከፋ ጉዳት አላደረሰም ብለዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyHawassa

@tikvahethiopia