ገንዘባችንን ከየትኛውም ባንክ ወደ M-PESA ፤ ከM-PESA ወደ የትኛውም ባንክ በመላክ ቀላል እና የተቀላጠፈ ክፍያ እንፈጽም!
M-PESA ላይ እንመዝገብ፣ በM-PESA እንገበያይ!
🔗 የM-PESA ሳፋሪኮምን መተግበሪያ በዚህ ሊንክ እናውርድ፡ https://bit.ly/M-PESA_SafaricomEthiopia
ስለ አገልግሎታችን ማንኛውንም ጥያቄ ወይም መረጃ በቴሌግራም ቻናላችን https://t.iss.one/Safaricom_Ethiopia_PLC 24/7 ማግኘት ይቻላል!
#MPESASafaricom #TerekBeMPESA #FurtherAheadTogether
M-PESA ላይ እንመዝገብ፣ በM-PESA እንገበያይ!
🔗 የM-PESA ሳፋሪኮምን መተግበሪያ በዚህ ሊንክ እናውርድ፡ https://bit.ly/M-PESA_SafaricomEthiopia
ስለ አገልግሎታችን ማንኛውንም ጥያቄ ወይም መረጃ በቴሌግራም ቻናላችን https://t.iss.one/Safaricom_Ethiopia_PLC 24/7 ማግኘት ይቻላል!
#MPESASafaricom #TerekBeMPESA #FurtherAheadTogether
TIKVAH-ETHIOPIA
#ETHIOPIA🇪🇹 ሀገራችን ኢትዮጵያ በሳዑዲ አረቢያ በማቆያ ጣቢያ የሚገኙ ዜጎቿን ከነገ ጀምሮ በተቀናጀ መንገድ የመመለስ ሥራ እንደምትጀምር የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል። በሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ብርቱካን አያኖ የተመራ የመንግሥት ልዑክ በሳዑዲ አረቢያ ሪያድ የኢትዮጵያ ኢምባሲ እና የጂዳ ቆንስላ ጀነራል ሰራተኞች እና የኮሙኒቲ አስተባባሪዎች ጋር በመወያየት በተመላሾች መለየት እና መመለስ ላይ…
#Update
“ ከሳዑዲ ተመላሾች በመደበኛው የሥራ ዕድል ፈጠራ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ተካተዋል ” - ሴቶች እና ማኀበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር
ኢትዮጵያ ከሳዑዲ አረቢያ ዜጎቿ እየመለሰች እንደምትገኝ የሴቶችና ህፃናት ጉዳይ ሚኒስቴር ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገለጿል።
በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የሕገ ወጥ ሰዎች ዝውውር መካላከልና የተመላሽ ዜጎች ድጋፍና ክትትል ሂደት መሪ ስራ አስፈጻሚ አቶ ደረጀ ተግይበሉ በሰጡት ቃል ፣ " በሳዑዲ አረቢያ የሚገኙ ዜጎችን የመመለሱ ስራ እየተሰራ ነው " ብለዋል።
ዛሬ እና ትላንት ብቻ 1913 ሰዎች ተመልሰዋል።
ምን ያህል ወገኖችን ለመመለስ ታስቧል ? ሲል ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ያቀረበላቸው አቶ ደረጃ “ በአጠቃላይ ለመመለስ የታቀደው ወደ 70 ሺሕ የሚሆኑ ኢትዮጵያውያንን ነው። በሚቀጥሉት 3 እና 4 ወራት ውስጥ በስምንት 3 ወይም 4 ቀናት በሚደረግ በረራ የማስመለስ ዕቅድ ተይዟል ” ሲሉ መልሰዋል።
70 ሺሕ ወገኖችን ከመመለስ ባሻገር ኢትዮጵያ ውስጥ በቋሚነት ለማቋቋም ምን ታቅዷል ? በሚል ላነሳነው ጥያቄ ፥ “ በተለይ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ትኩረት ሰጥቶ የሳዑዲ ተመላሾች በመደበኛው የሥራ ዕድል ፈጠራ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ተካተዋል ” ብለዋል።
በዚህ ወቅት በመደበኛው ሆነ በኢመደበኛው የሄዱ በአጠቃላይ በሳዑዲ አረቢያ ምን ያህል ኢትዮጵያውያን ስደተኞች አሉ ? ለሚለው ጥያቄ፣ “ አብዛኛዎቹ መደበኛ ባልሆነ ስርዓት ስለሆነ የሚሄዱት ይህን ይህል ናቸው ተብለው በመንግሥት አይታወቅም ” ብለዋል።
በሳዑዲ በጣም በርካታ ኢትዮጵያውያን ዜጎች እንዳሉ፣ ነገር ግን ሁሉም መደበኛ ባልሆነ ፍልሰት የሄዱ ናቸው ተብሎ ስለማይጠበቅ ከሳዑዲ መንግሥት ጋር በተደረገ ድርድር እየተመለሱ ያሉት በኢመደበኛ ፍልሰት የሄዱትንና በአስቸጋሪ ሁኔታ ሚገኙትን እንደሆነ አስረድተዋል።
በኢመደበኛ መንገድ የሚሄዱ ዜጎች፦
- የሞት አደጋ፣
- ሴቶች ለፆታዊ ጥቃት፣
- በደላላ ገንዘባቸውን የመበዝዘብ ችግር እንደሚደርስባቸው የገለጹት አቶ ደረጀ፣ “ መደበኛውን የፍልሰት ስርዓት ተከትለው የሚሄዱባቸውን ሁኔታዎች ከመንግሥት አካላት መረጃ ወስደው እንዲጠቀሙ አደራ እንላለን
” ሲሉ አስገንዝበዋል።
#ThikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
“ ከሳዑዲ ተመላሾች በመደበኛው የሥራ ዕድል ፈጠራ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ተካተዋል ” - ሴቶች እና ማኀበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር
ኢትዮጵያ ከሳዑዲ አረቢያ ዜጎቿ እየመለሰች እንደምትገኝ የሴቶችና ህፃናት ጉዳይ ሚኒስቴር ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገለጿል።
በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የሕገ ወጥ ሰዎች ዝውውር መካላከልና የተመላሽ ዜጎች ድጋፍና ክትትል ሂደት መሪ ስራ አስፈጻሚ አቶ ደረጀ ተግይበሉ በሰጡት ቃል ፣ " በሳዑዲ አረቢያ የሚገኙ ዜጎችን የመመለሱ ስራ እየተሰራ ነው " ብለዋል።
ዛሬ እና ትላንት ብቻ 1913 ሰዎች ተመልሰዋል።
ምን ያህል ወገኖችን ለመመለስ ታስቧል ? ሲል ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ያቀረበላቸው አቶ ደረጃ “ በአጠቃላይ ለመመለስ የታቀደው ወደ 70 ሺሕ የሚሆኑ ኢትዮጵያውያንን ነው። በሚቀጥሉት 3 እና 4 ወራት ውስጥ በስምንት 3 ወይም 4 ቀናት በሚደረግ በረራ የማስመለስ ዕቅድ ተይዟል ” ሲሉ መልሰዋል።
70 ሺሕ ወገኖችን ከመመለስ ባሻገር ኢትዮጵያ ውስጥ በቋሚነት ለማቋቋም ምን ታቅዷል ? በሚል ላነሳነው ጥያቄ ፥ “ በተለይ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ትኩረት ሰጥቶ የሳዑዲ ተመላሾች በመደበኛው የሥራ ዕድል ፈጠራ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ተካተዋል ” ብለዋል።
በዚህ ወቅት በመደበኛው ሆነ በኢመደበኛው የሄዱ በአጠቃላይ በሳዑዲ አረቢያ ምን ያህል ኢትዮጵያውያን ስደተኞች አሉ ? ለሚለው ጥያቄ፣ “ አብዛኛዎቹ መደበኛ ባልሆነ ስርዓት ስለሆነ የሚሄዱት ይህን ይህል ናቸው ተብለው በመንግሥት አይታወቅም ” ብለዋል።
በሳዑዲ በጣም በርካታ ኢትዮጵያውያን ዜጎች እንዳሉ፣ ነገር ግን ሁሉም መደበኛ ባልሆነ ፍልሰት የሄዱ ናቸው ተብሎ ስለማይጠበቅ ከሳዑዲ መንግሥት ጋር በተደረገ ድርድር እየተመለሱ ያሉት በኢመደበኛ ፍልሰት የሄዱትንና በአስቸጋሪ ሁኔታ ሚገኙትን እንደሆነ አስረድተዋል።
በኢመደበኛ መንገድ የሚሄዱ ዜጎች፦
- የሞት አደጋ፣
- ሴቶች ለፆታዊ ጥቃት፣
- በደላላ ገንዘባቸውን የመበዝዘብ ችግር እንደሚደርስባቸው የገለጹት አቶ ደረጀ፣ “ መደበኛውን የፍልሰት ስርዓት ተከትለው የሚሄዱባቸውን ሁኔታዎች ከመንግሥት አካላት መረጃ ወስደው እንዲጠቀሙ አደራ እንላለን
” ሲሉ አስገንዝበዋል።
#ThikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
#ስልክአምባ
" 12 ሰዎች ናቸው የተገደሉት፤ .. ቤቶች ተቃጥለዋል፤ ከብቶችም እየተነዱ ተወስደዋል " - ነዋሪዎች
" 11 ሰዎች ስለመገደላቸው መረጃ ደርሶናል መረጃውን የማጣራት ስራ እየሰራን ነው " - ኢሰመኮ
️በኦሮሚያ ክልል ፤ በምዕራብ ሸዋ ዞን ፤ ኖኖ ወረዳ ስልክ አምባ ከተማ ባለፈው ሠኞ ታጣቂዎች በፈጸሙት ጥቃት 12 ሰዎች መገደላቸውን ነዋሪዎች ለቪኦኤ ሬድዮ ጣቢያ በሰጡት ቃል ተናግረዋል።
ነዋሪዎቹ በ5 ቀበሌዎች ጥቃት መፈጸሙን ይህን ያደረጉት ደግመ የሸኔ ታጣቂዎች (የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት) እንደሆኑ ገልጸዋል።
ከሟቾች አብዛኛዎቹ የአማራ ብሔር ተወላጆች መኾናቸውን ተናግረዋል።
ወደ 60 ቤት እህል ጭምር የያዘ መቃጠሉን እና በርካቶች ቤት ንብረታቸውን ጥለው መሸሻቸውን ገልጸዋል። ከ100 በላይ ከብቶችም እየተነዱ ተወስደዋል።
አንድ ነዋሪ በሰጡት ቃል ፥ ጥቃቱ ከተፈፀመ በኃላ ዘግይተው የደረሱት የመንግሥት የጸጥታ ኃይሎች ከታጣቂዎቹ ጋር ተኩስ ገጥመው እንደነበር አስረድተዋል።
ሌላ ነዋሪ ፤ " ኦነግ ሸኔ ነው የሚባለው ቁጥራቸው የበዛና ከባድ መሳሪያ ጭምር የታጠቁ ናቸው በተኛንበት 12 ሰዓት ላይ መጥተው ነው ጉዳት ያደረሱት " ብለዋል።
" እኛ ገበሬዎች ነን ምንም ኃይል የለን አቅም የለን በጣም ነው ጉዳት የደረሰብን " ያሉ ሲሆን ሴቶችን፣ አዛውንቶችን ከብቶችን በማሸሽ ወደጫካ ማስመለጥ እንደተቻለ አቅም የሌላቸው አዛውንቶች ግን መገደላቸውን እነሱንም ሲቀብሩ እንዳመሹ ተናግረዋል።
የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ፥ በአካባቢው በታጣቂዎች ግጭት ተነስቶ 11 ሰዎች ህይወታቸው እንዳለፈ ከአካባቢው መረጃ እንደደረሰው ገልጾ መረጃውን ለማጣራት ጥረት ላይ መሆኑን አመልክቷል።
የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ለቪኦኤ ሬድዮ በሰጠው ቃል በነዋሪዎች የቀረበበትን ክስ አስተባብሎ፤ " እኛ እንዲህ ዓይነት ድርጊት ውስጥ እጃችን የለበትም " ብሏል። " ጉዳዩ በገለልተኛ አካል ምርመራ ሊደረግበት ይገባል " ሲልም ገልጿል።
ክልሉ እስካሁን በይፋ የሰጠው መረጃ የለም።
@tikvahethiopia
" 12 ሰዎች ናቸው የተገደሉት፤ .. ቤቶች ተቃጥለዋል፤ ከብቶችም እየተነዱ ተወስደዋል " - ነዋሪዎች
" 11 ሰዎች ስለመገደላቸው መረጃ ደርሶናል መረጃውን የማጣራት ስራ እየሰራን ነው " - ኢሰመኮ
️በኦሮሚያ ክልል ፤ በምዕራብ ሸዋ ዞን ፤ ኖኖ ወረዳ ስልክ አምባ ከተማ ባለፈው ሠኞ ታጣቂዎች በፈጸሙት ጥቃት 12 ሰዎች መገደላቸውን ነዋሪዎች ለቪኦኤ ሬድዮ ጣቢያ በሰጡት ቃል ተናግረዋል።
ነዋሪዎቹ በ5 ቀበሌዎች ጥቃት መፈጸሙን ይህን ያደረጉት ደግመ የሸኔ ታጣቂዎች (የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት) እንደሆኑ ገልጸዋል።
ከሟቾች አብዛኛዎቹ የአማራ ብሔር ተወላጆች መኾናቸውን ተናግረዋል።
ወደ 60 ቤት እህል ጭምር የያዘ መቃጠሉን እና በርካቶች ቤት ንብረታቸውን ጥለው መሸሻቸውን ገልጸዋል። ከ100 በላይ ከብቶችም እየተነዱ ተወስደዋል።
አንድ ነዋሪ በሰጡት ቃል ፥ ጥቃቱ ከተፈፀመ በኃላ ዘግይተው የደረሱት የመንግሥት የጸጥታ ኃይሎች ከታጣቂዎቹ ጋር ተኩስ ገጥመው እንደነበር አስረድተዋል።
ሌላ ነዋሪ ፤ " ኦነግ ሸኔ ነው የሚባለው ቁጥራቸው የበዛና ከባድ መሳሪያ ጭምር የታጠቁ ናቸው በተኛንበት 12 ሰዓት ላይ መጥተው ነው ጉዳት ያደረሱት " ብለዋል።
" እኛ ገበሬዎች ነን ምንም ኃይል የለን አቅም የለን በጣም ነው ጉዳት የደረሰብን " ያሉ ሲሆን ሴቶችን፣ አዛውንቶችን ከብቶችን በማሸሽ ወደጫካ ማስመለጥ እንደተቻለ አቅም የሌላቸው አዛውንቶች ግን መገደላቸውን እነሱንም ሲቀብሩ እንዳመሹ ተናግረዋል።
የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ፥ በአካባቢው በታጣቂዎች ግጭት ተነስቶ 11 ሰዎች ህይወታቸው እንዳለፈ ከአካባቢው መረጃ እንደደረሰው ገልጾ መረጃውን ለማጣራት ጥረት ላይ መሆኑን አመልክቷል።
የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ለቪኦኤ ሬድዮ በሰጠው ቃል በነዋሪዎች የቀረበበትን ክስ አስተባብሎ፤ " እኛ እንዲህ ዓይነት ድርጊት ውስጥ እጃችን የለበትም " ብሏል። " ጉዳዩ በገለልተኛ አካል ምርመራ ሊደረግበት ይገባል " ሲልም ገልጿል።
ክልሉ እስካሁን በይፋ የሰጠው መረጃ የለም።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Hawassa ➡️ " እህታችንን የጠለፋት ግለሰብ ወደ ፓሊስ እንዳንሄድ በእህታችን ህይወት እያስፈራራን ነው " - የተጠላፊዋ ውድነሽ ማቲዎስ ቤተሰቦች በእንባ የታጀበ መልእከት ➡️ " ቆየት ብዬ ዝርዝር መረጃ ሰጣችኃለሁ " - ፖሊስ ነዋሪነቷ በሀዋሳ ከተማ ነው። ስሟ ውድነሽ ማቲዮስ ይባላል። በቀን 28/07/2016 ቅዳሜ ምሽት ከቤት " ሰው ይጠራሻል " ተብላ እንደወጣች አልተመለሰችም። ቤተሰቦቿ…
#Update
➡️ " እንደተባለዉ ጠለፋ አለመፈጸሙን በማወቃችንና ቤተሰቦቿ ተስማምተዉ ጉዳዩ ከህግ እጅ እንዲወጣ ስለፈለጉ ክትትላችንን አቋርጠናል " - የሀዋሳ ከተማ ፖሊስ
➡️ " ጉዳዩ በሽምግልና መያዙን እንፈልገዋለን ቢሆንም ህግ አይግባ የሚለዉን የልጄ ቃል ከራሷ የመጣ ስለመሆኑ እጠራጠራለሁ " - አባት አቶ ማቲዎስ
ከሰሞኑ ነዋሪነቷ በሀዋሳ ከተማ ታቦር ክ ከተማ የሆነ ወድነሽ ማቲዮስ የተባለች ግለሰብ በድንገት ከቤት ተጠርታ እንደወጣች መቅረቷንና ቆይቶም መጠለፏ መታወቁን ተከትሎ ቤተሰቦች " ፖሊስ አስፈላጊውን ክትትል አድርጎ ልጃችን ይመልስልን " ማለታቸዉን ቲኪቫህ ኢትዮጵያ መዘገቡ ይታወሳል።
ይሁንና ጉዳዩን እየተከታተለ የነበረው የሀዋሳ ከተማ ፖሊስ " ጉዳዩ ጠለፋ ሳይሆን በገዛ ፍላጎቷ ያደረገችዉ መሆኑን ደርሸበታለሁ " በማለት ክትትሉን ማቆሙን የሀዋሳ ከተማ ፖሊስ ለቲኪቫህ ኢትዮጵያ አሳውቋል።
" ቤተሰቦቿ እንደሚሉት ጠለፋ ሳይሆን በፍላጎት የተደረገ መሆኑንና አሁን ላይ ጉዳዩ በሽምግልና እነደተያዘ " የገለጸዉ የከተማዉ ፖሊስ የሽምግልና ሂደቱ ከልጅቱ በተጨማሪ የቤተሰብ ይሁንታ ማግኘቱንም ገልጿል።
የልጅቱ አባት የሆኑት አቶ ማቲዎስ በበኩላቸዉ ሁኔታዉ በሽምግልና መያዙ ቢያስደስታቸዉም ልጃቸዉን በስልክ እንጅ በአካል አለማግኘታቸዉ አሁንም ልባቸዉ ዉስጥ ጥርጣሬ እንደፈጠረ ተናግረዋል።
" ህግ አይግባ የሚለዉን የልጄ ቃል ከራሷ የመጣ ስለመሆኑ እጠራጠራለሁ "ብለዋል።
በመሆኑም በሲዳማ ባህል መሰረት ሚያዚያ 17 የሚደረገው ሽምግልና የተደበቀዉን ሚስጥር እንደሚፈታዉና መፍትሄዉንም ያቀርባል ብለዉ እንደሚያስቡ ገልጸዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyHawassa
@tikvahethiopia
➡️ " እንደተባለዉ ጠለፋ አለመፈጸሙን በማወቃችንና ቤተሰቦቿ ተስማምተዉ ጉዳዩ ከህግ እጅ እንዲወጣ ስለፈለጉ ክትትላችንን አቋርጠናል " - የሀዋሳ ከተማ ፖሊስ
➡️ " ጉዳዩ በሽምግልና መያዙን እንፈልገዋለን ቢሆንም ህግ አይግባ የሚለዉን የልጄ ቃል ከራሷ የመጣ ስለመሆኑ እጠራጠራለሁ " - አባት አቶ ማቲዎስ
ከሰሞኑ ነዋሪነቷ በሀዋሳ ከተማ ታቦር ክ ከተማ የሆነ ወድነሽ ማቲዮስ የተባለች ግለሰብ በድንገት ከቤት ተጠርታ እንደወጣች መቅረቷንና ቆይቶም መጠለፏ መታወቁን ተከትሎ ቤተሰቦች " ፖሊስ አስፈላጊውን ክትትል አድርጎ ልጃችን ይመልስልን " ማለታቸዉን ቲኪቫህ ኢትዮጵያ መዘገቡ ይታወሳል።
ይሁንና ጉዳዩን እየተከታተለ የነበረው የሀዋሳ ከተማ ፖሊስ " ጉዳዩ ጠለፋ ሳይሆን በገዛ ፍላጎቷ ያደረገችዉ መሆኑን ደርሸበታለሁ " በማለት ክትትሉን ማቆሙን የሀዋሳ ከተማ ፖሊስ ለቲኪቫህ ኢትዮጵያ አሳውቋል።
" ቤተሰቦቿ እንደሚሉት ጠለፋ ሳይሆን በፍላጎት የተደረገ መሆኑንና አሁን ላይ ጉዳዩ በሽምግልና እነደተያዘ " የገለጸዉ የከተማዉ ፖሊስ የሽምግልና ሂደቱ ከልጅቱ በተጨማሪ የቤተሰብ ይሁንታ ማግኘቱንም ገልጿል።
የልጅቱ አባት የሆኑት አቶ ማቲዎስ በበኩላቸዉ ሁኔታዉ በሽምግልና መያዙ ቢያስደስታቸዉም ልጃቸዉን በስልክ እንጅ በአካል አለማግኘታቸዉ አሁንም ልባቸዉ ዉስጥ ጥርጣሬ እንደፈጠረ ተናግረዋል።
" ህግ አይግባ የሚለዉን የልጄ ቃል ከራሷ የመጣ ስለመሆኑ እጠራጠራለሁ "ብለዋል።
በመሆኑም በሲዳማ ባህል መሰረት ሚያዚያ 17 የሚደረገው ሽምግልና የተደበቀዉን ሚስጥር እንደሚፈታዉና መፍትሄዉንም ያቀርባል ብለዉ እንደሚያስቡ ገልጸዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyHawassa
@tikvahethiopia
🚨 #ዲላ 🚨
ዛሬ በዲላ ከተማ 10 ሠዓት ገዳማ ንፋስ ቀላቅሎ በዘነበው ከባድ ዝናብ #ሁለት የአንድ ቤተሰብ #ህጻናት ህይወታቸው አልፏል።
2 ሰዎች ከባድ ጉዳት ደርሶባቸዋል። ቀላል ጉዳት የደረሰባቸውም ሰዎች አሉ።
ንብረት ላይም ከፍተኛ የሆነ ጉዳት ደርሷል።
በርካታ ዛፎች እና በርካታ የኤሌክትሪክ ፖሎች ወድቀዋል።
የኤሌክትሪክ ኃይልም ተቋርጧል።
ነዋሪው የኤሌክትሪክ ኃይል ተስተካክሎ ወደ ቦታው እስኪመለስ እንዲታገስና እራሱ ከተለያዩ አደጋዎች እንዲጠብቅ የከተማው አስተዳደር አደራ ብሏል።
@Tikvahethiopia
ዛሬ በዲላ ከተማ 10 ሠዓት ገዳማ ንፋስ ቀላቅሎ በዘነበው ከባድ ዝናብ #ሁለት የአንድ ቤተሰብ #ህጻናት ህይወታቸው አልፏል።
2 ሰዎች ከባድ ጉዳት ደርሶባቸዋል። ቀላል ጉዳት የደረሰባቸውም ሰዎች አሉ።
ንብረት ላይም ከፍተኛ የሆነ ጉዳት ደርሷል።
በርካታ ዛፎች እና በርካታ የኤሌክትሪክ ፖሎች ወድቀዋል።
የኤሌክትሪክ ኃይልም ተቋርጧል።
ነዋሪው የኤሌክትሪክ ኃይል ተስተካክሎ ወደ ቦታው እስኪመለስ እንዲታገስና እራሱ ከተለያዩ አደጋዎች እንዲጠብቅ የከተማው አስተዳደር አደራ ብሏል።
@Tikvahethiopia
🚨BREAKING🚨
ኢራን እስራኤል ላይ የድሮን ጥቃት ከፈተች።
ከዛሬ 12 ቀናት በፊት እስራኤል በሶሪያ የኢራን ቆንስላ ጽ/ቤት ላይ እንደፈፀመችው በተነገረ የአየር ጥቃት ከፍተኛ የኢራን ጄኔራልን ጨምሮ 13 ሰዎች ተገድለዋል።
እስራኤል ለግድያው ኃላፊነቱን ባትወስድም ኢራን እሷ እንደሆነች ነው የምታምነው። ይህን ተከትሎ ኢራን የበቀል እርምጃ እንደምትወስድ ስትዝት ቆይታለች። መዛት ብቻ ሳይሆን ዝግጅትም ስታደርግ ነበር።
እስራኤልም " እኔ እራሴን ለመከላከል ዝግጁ ነኝ " ስትል ከርማለች።
ገና የእስራኤል እና የፍልስጤም ሀማስ ጦርነት ይህ ነው የተባለ መቋጫ ባላገኘበት ሁኔታ ኢራን እና እስራኤል የለየለት ጦርነት ውስጥ ይገባሉ በሚል ፍራቻ ሀገራት ሲያስጨንቃቸው ቆይቷል።
እንደ አሜሪካ ያሉ የእስራኤል እጅግ ጠንካራ ወዳጅ ሀገራት ኢራንን " አርፈሽ ተቀመጪ ጥቃት እንዳትፈጽሚ " ሲሉ ሲያስጠነቅቁ ነበር።
ዛሬ ለሊቱን በተሰማው ዜና ግን ኢራን እንደዛተች አልቀረችም እስራኤልን በድሮን (ሰው አልባ አውሮፕላን) ማጥቃት ጀምራለች። የሚሳኤል ጥቃትም እንደሚኖር ኢራን ገልጻለች።
እስካሁን ድረስ ከ100 በላይ የድሮን ጥቃቶችን እንደሰነዘረች ተሰምቷል።
የእስራኤል ጦርም የኢራን ድሮኖች ወደ እስራኤል እየተላኩ መሆኑን አረጋግጧል። በትንሹ ከ100 በላይ ድሮኖች የእስራኤል አየር ክልል ሳይደርሱ መከላከል እንደተቻለ ገልጿል።
የአሜሪካ ጦርም እስራኤልን እየተከላከለ ሲሆን እስራኤልን ለማጥቃት የተላኩ ድሮኖችን መቶ መጣሉን አመልክቷል። የዩኬ አየር ኃይልም እስራኤልን እንዲያጠቁ የተላኩ ድሮኖችን መቶ ጥሏል።
እስራኤል ለማንኛውም የኢራን ቀጥተኛ ጥቃት ምላሽ ለመስጠት እንደተዘጋጀች አሳውቃለች።
ይህ በእንዲህ እንዳለ ሌባኖስ ያለው ሄዝቦላህ በሰሜናዊ እስራኤል የሚሳኤል ጥቃት እየፈፀመ ሲሆን የየመኑ ሁቲ ደግሞ እስራኤል ላይ የድሮን ጥቃት ከፍቷል።
More⬇️
https://t.iss.one/+LM-bJ8NzZMcxMjA8
@tikvahethiopia
ኢራን እስራኤል ላይ የድሮን ጥቃት ከፈተች።
ከዛሬ 12 ቀናት በፊት እስራኤል በሶሪያ የኢራን ቆንስላ ጽ/ቤት ላይ እንደፈፀመችው በተነገረ የአየር ጥቃት ከፍተኛ የኢራን ጄኔራልን ጨምሮ 13 ሰዎች ተገድለዋል።
እስራኤል ለግድያው ኃላፊነቱን ባትወስድም ኢራን እሷ እንደሆነች ነው የምታምነው። ይህን ተከትሎ ኢራን የበቀል እርምጃ እንደምትወስድ ስትዝት ቆይታለች። መዛት ብቻ ሳይሆን ዝግጅትም ስታደርግ ነበር።
እስራኤልም " እኔ እራሴን ለመከላከል ዝግጁ ነኝ " ስትል ከርማለች።
ገና የእስራኤል እና የፍልስጤም ሀማስ ጦርነት ይህ ነው የተባለ መቋጫ ባላገኘበት ሁኔታ ኢራን እና እስራኤል የለየለት ጦርነት ውስጥ ይገባሉ በሚል ፍራቻ ሀገራት ሲያስጨንቃቸው ቆይቷል።
እንደ አሜሪካ ያሉ የእስራኤል እጅግ ጠንካራ ወዳጅ ሀገራት ኢራንን " አርፈሽ ተቀመጪ ጥቃት እንዳትፈጽሚ " ሲሉ ሲያስጠነቅቁ ነበር።
ዛሬ ለሊቱን በተሰማው ዜና ግን ኢራን እንደዛተች አልቀረችም እስራኤልን በድሮን (ሰው አልባ አውሮፕላን) ማጥቃት ጀምራለች። የሚሳኤል ጥቃትም እንደሚኖር ኢራን ገልጻለች።
እስካሁን ድረስ ከ100 በላይ የድሮን ጥቃቶችን እንደሰነዘረች ተሰምቷል።
የእስራኤል ጦርም የኢራን ድሮኖች ወደ እስራኤል እየተላኩ መሆኑን አረጋግጧል። በትንሹ ከ100 በላይ ድሮኖች የእስራኤል አየር ክልል ሳይደርሱ መከላከል እንደተቻለ ገልጿል።
የአሜሪካ ጦርም እስራኤልን እየተከላከለ ሲሆን እስራኤልን ለማጥቃት የተላኩ ድሮኖችን መቶ መጣሉን አመልክቷል። የዩኬ አየር ኃይልም እስራኤልን እንዲያጠቁ የተላኩ ድሮኖችን መቶ ጥሏል።
እስራኤል ለማንኛውም የኢራን ቀጥተኛ ጥቃት ምላሽ ለመስጠት እንደተዘጋጀች አሳውቃለች።
ይህ በእንዲህ እንዳለ ሌባኖስ ያለው ሄዝቦላህ በሰሜናዊ እስራኤል የሚሳኤል ጥቃት እየፈፀመ ሲሆን የየመኑ ሁቲ ደግሞ እስራኤል ላይ የድሮን ጥቃት ከፍቷል።
More⬇️
https://t.iss.one/+LM-bJ8NzZMcxMjA8
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
🚨BREAKING🚨 ኢራን እስራኤል ላይ የድሮን ጥቃት ከፈተች። ከዛሬ 12 ቀናት በፊት እስራኤል በሶሪያ የኢራን ቆንስላ ጽ/ቤት ላይ እንደፈፀመችው በተነገረ የአየር ጥቃት ከፍተኛ የኢራን ጄኔራልን ጨምሮ 13 ሰዎች ተገድለዋል። እስራኤል ለግድያው ኃላፊነቱን ባትወስድም ኢራን እሷ እንደሆነች ነው የምታምነው። ይህን ተከትሎ ኢራን የበቀል እርምጃ እንደምትወስድ ስትዝት ቆይታለች። መዛት ብቻ ሳይሆን ዝግጅትም…
#UPDATE
ኢራን ለሊቱን እስራኤልን በድሮን ፣ በሚሳኤልና ሮኬቶች ስትደበድብ ከቆየች በኃላ " እስራኤልን የመቅጣቱ ተግባር #ተጠናቋል " ብላለች።
እስራኤል ማንኛውም አፀፋዊ ምላሽ ሰጣለሁ ካለች ግን ከአሁኑ እጅግ በጣም የከፋው ቅጣት ይጠብቃታል ሲትል አስጠንቅቃለች።
ኢራን የትኛውም ህዝባዊ ይሁን ኢኮኖሚያዊ ዒላማዋች እንዳልነበሯት ዒላማዋ የእስራኤል ወታደራዊ ስፍራዎችና አቅም ላይ እንደነበር ገልጻለች።
ኢራን ለመጀመሪያ ጊዜ ነው በእስራኤል ላይ እንዲህ ያለውም ቀጥተኛ መጠነ ሰፊ ጥቃት የከፈተችው።
ከ360 በላይ ሚሳኤል እና ድሮኖች ከኢራን፣ ኢራቅ፣ የመን ወደ እስራኤል መወንጨፋቸውን የእስራኤል ሠራዊት አስታውቋል።
አብዛኞቹ ጉዳት ሳያደርሱ (99%) በእስራኤል እና በወዳጆቿ አማካይነት እንዲከሽፉ መደረጋቸው ተገልጿል።
ያም ሆኑ በጥቃቱ መጠነኛ ጉዳት መድረሱ ተነግሯል።
እስራኤል የለሊቱን ጥቃት ብቻ ለመመከት 1 ቢሊዮን ዶላር ሳታወጣ አልቀረችም ተብሏል።
የአሜሪካ ጦር በርካታ ሚሳኤሎችን እና ድሮኖችን ከአየር ላይ እንዲከሽፉ አድርጓል። ፕሬዜዳንቷም " እስራኤል የኢራንን ጥቃት የመከተችው በአሜሪካ ድጋፍ ነው " ብለዋል።
ዩናይትድ ኪንግደም እና ፈረንሳይም ከጥቃቱ በፊት የአየር ቅኝት በማድረግ እስራኤልን ሲያግዙ አንግተዋል።
ጆርዳን በአየር ክልሏ ሲያልፉ የነበሩ ድሮኖችን እየመታች የጣለች ሲሆን ይህንን " ለህዝቤ ደህንነት ስል ያደረኩት ነው " ብላለች።
ኢራንም ጆርዳንን " አርፈሽ ካልተቀመጥሽ አንቺም ልክ እንደ እስራኤል ትመቻለሽ " ስትል ዝታባታለች።
እስራኤል በቀጣይ የአፀፋ እርምጃ ትወስድ ይሆን ? የሚለው ብዙዎችን ያሳሰበ ጉዳይ ሲሆን " አሜሪካ ተያት አፀፋ አትውሰጂ " ብላታለች።
ቀድሞኑ በእራኤል እና ፍልስጤም ሀማስ ጦርነት የተለያየ አቋም ያላቸው የተለያዩ ሀገራትና ተቋማት በጉዳዩ ላይ ያላቸውን ስጋት ገልጸዋል። ውጥረቱ ይረግብ ዘንድ ጥሪ አቅርበዋል።
ኢራን ፥ እስራኤልን የደበደበችው ከዛሬ 13 ቀን በፊት በሶሪያ የኢራን ቆንስላ ጽ/ቤት ላይ እስራኤል እንደፈፀመችው በምታምነው የአየር ጥቃት ከፍተኛ ጄኔራሏን ጨምሮ አጠቃላይ 13 ሰዎች በመገደላቸው ለሱ አፀፋ ነው።
መረጃው ከዓለም አቀፍ የዜና አውታሮች የተሰባሰበ ነው።
More⬇️
https://t.iss.one/+LM-bJ8NzZMcxMjA8
@tikvahethiopia
ኢራን ለሊቱን እስራኤልን በድሮን ፣ በሚሳኤልና ሮኬቶች ስትደበድብ ከቆየች በኃላ " እስራኤልን የመቅጣቱ ተግባር #ተጠናቋል " ብላለች።
እስራኤል ማንኛውም አፀፋዊ ምላሽ ሰጣለሁ ካለች ግን ከአሁኑ እጅግ በጣም የከፋው ቅጣት ይጠብቃታል ሲትል አስጠንቅቃለች።
ኢራን የትኛውም ህዝባዊ ይሁን ኢኮኖሚያዊ ዒላማዋች እንዳልነበሯት ዒላማዋ የእስራኤል ወታደራዊ ስፍራዎችና አቅም ላይ እንደነበር ገልጻለች።
ኢራን ለመጀመሪያ ጊዜ ነው በእስራኤል ላይ እንዲህ ያለውም ቀጥተኛ መጠነ ሰፊ ጥቃት የከፈተችው።
ከ360 በላይ ሚሳኤል እና ድሮኖች ከኢራን፣ ኢራቅ፣ የመን ወደ እስራኤል መወንጨፋቸውን የእስራኤል ሠራዊት አስታውቋል።
አብዛኞቹ ጉዳት ሳያደርሱ (99%) በእስራኤል እና በወዳጆቿ አማካይነት እንዲከሽፉ መደረጋቸው ተገልጿል።
ያም ሆኑ በጥቃቱ መጠነኛ ጉዳት መድረሱ ተነግሯል።
እስራኤል የለሊቱን ጥቃት ብቻ ለመመከት 1 ቢሊዮን ዶላር ሳታወጣ አልቀረችም ተብሏል።
የአሜሪካ ጦር በርካታ ሚሳኤሎችን እና ድሮኖችን ከአየር ላይ እንዲከሽፉ አድርጓል። ፕሬዜዳንቷም " እስራኤል የኢራንን ጥቃት የመከተችው በአሜሪካ ድጋፍ ነው " ብለዋል።
ዩናይትድ ኪንግደም እና ፈረንሳይም ከጥቃቱ በፊት የአየር ቅኝት በማድረግ እስራኤልን ሲያግዙ አንግተዋል።
ጆርዳን በአየር ክልሏ ሲያልፉ የነበሩ ድሮኖችን እየመታች የጣለች ሲሆን ይህንን " ለህዝቤ ደህንነት ስል ያደረኩት ነው " ብላለች።
ኢራንም ጆርዳንን " አርፈሽ ካልተቀመጥሽ አንቺም ልክ እንደ እስራኤል ትመቻለሽ " ስትል ዝታባታለች።
እስራኤል በቀጣይ የአፀፋ እርምጃ ትወስድ ይሆን ? የሚለው ብዙዎችን ያሳሰበ ጉዳይ ሲሆን " አሜሪካ ተያት አፀፋ አትውሰጂ " ብላታለች።
ቀድሞኑ በእራኤል እና ፍልስጤም ሀማስ ጦርነት የተለያየ አቋም ያላቸው የተለያዩ ሀገራትና ተቋማት በጉዳዩ ላይ ያላቸውን ስጋት ገልጸዋል። ውጥረቱ ይረግብ ዘንድ ጥሪ አቅርበዋል።
ኢራን ፥ እስራኤልን የደበደበችው ከዛሬ 13 ቀን በፊት በሶሪያ የኢራን ቆንስላ ጽ/ቤት ላይ እስራኤል እንደፈፀመችው በምታምነው የአየር ጥቃት ከፍተኛ ጄኔራሏን ጨምሮ አጠቃላይ 13 ሰዎች በመገደላቸው ለሱ አፀፋ ነው።
መረጃው ከዓለም አቀፍ የዜና አውታሮች የተሰባሰበ ነው።
More⬇️
https://t.iss.one/+LM-bJ8NzZMcxMjA8
@tikvahethiopia