#AddisAbaba
በአዲስ አበባ ከተማ ከፖሊስ አባላት ጋር ቶክስ በመክፈታቸው የተነገረላቸው የፋኖ መሪዎችና አባላት መገደላቸውን ፖሊስ ገልጿል።
የአዲስ አበባ ፖሊስ ባወጣው መግለጫ ፤
- ናሁሰናይ አንድአርጌ ታረቀኝ ፣
- አቤኔዜር ጋሻው አባተ
- ሀብታሙ አንድአርጌ ተሰማ የተባሉት " ፋኖ " ቡድን አባላት በከተማው " የሽበር ጥቃት ለመፈፀም እየተንቃሰቀሱ " መሆኑን የፀጥታ አካላት ባደረጉ ክትትል እንደደረሱባቸው ገልጿል።
ዛሬ " ሚሊኒየም አዳራሽ " አካባቢ ግለሰቦቹ በቁጥጥር ስር ለማዋል የፖሊስ አባላት እንቅስቃሴ እያደረጉ ባለበት ሁኔታ " እጃቸውን እንዲሰጡ ቢጠየቁም ፍቃደኛ ባለመሆን በሰሌዳ ቁጥር ኮድ 2C 14373 አ/አ አይነቷ ሱዙኪ ዲዛዬር መኪናን በመጠቀም ተኩስ መክፈታቸውን " አመልክቷል።
በዚም ናሁሰናይ አንዳርጌ ታረቀኝ ቆስሎ ወደ ህክምና ከተላከ በኋላ ሲሞት አቤነዘር ጋሻው በተኩስ ልውውጡ መሃል መገደሉን ገልጿል።
ሀብታሙ አንዳርጌ ተሰማ ሳይቆስል በቁጥጥር ስር መዋሉን አዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል፡፡
በነበረው የተኩስ ልውውጥ ሳጅን አራርሳ ተሾመ እና ኮንስታብል ማቲያስ ጴጥሮስ ቆስለዋል።
ከዚህ በተጨማሪ የፈኖ አባለቱ አቶ እንዳሻው ጌትነት የተባሉ ግለሰብ በመኪናቸው እንዲጭኗቸው ቢያስገድዷቸውም ግለሰቡ አልተባበርም በማለታቸው እንደገደሏቸው አመልክቷል።
አቶ እንደሻው ሲያሽከርክሯት የነበረቸው የሰሌዳ ቁጥር ኮድ 2 አ/አ 80457 በጥይት ጉዳት እንደረሰባት አዲስ አበባ ፖሊስ ገልጿል።
@tikvahethiopia
በአዲስ አበባ ከተማ ከፖሊስ አባላት ጋር ቶክስ በመክፈታቸው የተነገረላቸው የፋኖ መሪዎችና አባላት መገደላቸውን ፖሊስ ገልጿል።
የአዲስ አበባ ፖሊስ ባወጣው መግለጫ ፤
- ናሁሰናይ አንድአርጌ ታረቀኝ ፣
- አቤኔዜር ጋሻው አባተ
- ሀብታሙ አንድአርጌ ተሰማ የተባሉት " ፋኖ " ቡድን አባላት በከተማው " የሽበር ጥቃት ለመፈፀም እየተንቃሰቀሱ " መሆኑን የፀጥታ አካላት ባደረጉ ክትትል እንደደረሱባቸው ገልጿል።
ዛሬ " ሚሊኒየም አዳራሽ " አካባቢ ግለሰቦቹ በቁጥጥር ስር ለማዋል የፖሊስ አባላት እንቅስቃሴ እያደረጉ ባለበት ሁኔታ " እጃቸውን እንዲሰጡ ቢጠየቁም ፍቃደኛ ባለመሆን በሰሌዳ ቁጥር ኮድ 2C 14373 አ/አ አይነቷ ሱዙኪ ዲዛዬር መኪናን በመጠቀም ተኩስ መክፈታቸውን " አመልክቷል።
በዚም ናሁሰናይ አንዳርጌ ታረቀኝ ቆስሎ ወደ ህክምና ከተላከ በኋላ ሲሞት አቤነዘር ጋሻው በተኩስ ልውውጡ መሃል መገደሉን ገልጿል።
ሀብታሙ አንዳርጌ ተሰማ ሳይቆስል በቁጥጥር ስር መዋሉን አዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል፡፡
በነበረው የተኩስ ልውውጥ ሳጅን አራርሳ ተሾመ እና ኮንስታብል ማቲያስ ጴጥሮስ ቆስለዋል።
ከዚህ በተጨማሪ የፈኖ አባለቱ አቶ እንዳሻው ጌትነት የተባሉ ግለሰብ በመኪናቸው እንዲጭኗቸው ቢያስገድዷቸውም ግለሰቡ አልተባበርም በማለታቸው እንደገደሏቸው አመልክቷል።
አቶ እንደሻው ሲያሽከርክሯት የነበረቸው የሰሌዳ ቁጥር ኮድ 2 አ/አ 80457 በጥይት ጉዳት እንደረሰባት አዲስ አበባ ፖሊስ ገልጿል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#AddisAbaba በአዲስ አበባ ከተማ ከፖሊስ አባላት ጋር ቶክስ በመክፈታቸው የተነገረላቸው የፋኖ መሪዎችና አባላት መገደላቸውን ፖሊስ ገልጿል። የአዲስ አበባ ፖሊስ ባወጣው መግለጫ ፤ - ናሁሰናይ አንድአርጌ ታረቀኝ ፣ - አቤኔዜር ጋሻው አባተ - ሀብታሙ አንድአርጌ ተሰማ የተባሉት " ፋኖ " ቡድን አባላት በከተማው " የሽበር ጥቃት ለመፈፀም እየተንቃሰቀሱ " መሆኑን የፀጥታ አካላት ባደረጉ ክትትል…
“ በፀጥታ ጉዳይ ምንም አይነት ድርድር የለም ” - አዲስ አበባ ፓሊስ
በአዲስ አበባ ከተማ በፋኖና በፓሊስ በተደረገ የተኩስ ልውውጥ አንድ ሲቪልና ሁለት ታጣቂዎች ሲገደሉ፣ በሁለት የፓሊስ አባላት ላይ ከባድ ጉዳት መድረሱ ተገልጿል።
የ“ፋኖ” አመራርና አባላት በአዲስ አበባ ከተማ ቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 3 ሚሊኒየም አዳራሽ አጠገብ ከፀጥታ አካላት ተኩስ እንደከፈቱ፣ በ “ፋኖ” በኩል ሁለት ታጣቂዎች ሲገደሉ አንድ በቁጥጥር ስር እንደዋለ፣ በመንግሥት በኩል ሁለት የፓሊስ አባላት ላይ ጉዳት እንደደረሰ፣ በንጹሐን በኩል ደግሞ አንድ አሽከርካራ እንደተገደለ፣ የአዲስ አበባ ፓሊስ ኮሚሽን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አረጋግጧል።
የኮሚሽኑ የሕዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር ምክትል ኮማንደር ማርቆስ ታደሰ በሰጡት ቃል፣ “ የተገደሉት የ “ፋኖ” ቡድን አመራርና አባላት ናቸው። አመራሩ ናሁሰናይ አንዳርጌ ነው። ሌላው አቤኔዘር ጋሻው የተባለው ነው፣ እዛው ቦታው ላይ በተደረገ የተኩስ ልውውጥ ሂወቱ አልፏል። ሀብታሙ አንዳርጌ ግን ምንም አልሆነም በቁጥጥር ስር ውሏል ” ብለዋል።
የ “ፋኖ” አመራርና አባላት የነበራቸውን እንቅስቃሴ ሲያስረዱም ኮማንደሩ፣ “ በከተማው ውስጥ ነው የሚንቀሳቀሱት የነበረው። በከተማው ውስጥ ደግሞ የተለያዩ ጥፋቶች ለማጥፋት ነው እንቅስቃሴ ሲያደርጉ የነበረው ” ነው ያሉት።
አክለውም፣ “ እነርሱን ለመያዝ በተደረገው ሂደት ቦሌ ወረዳ 3 ሳጅን አራርሳ ተሾመና ኮንስታብል ማቲያስ ጴጥሮስ የሚባሉ ሁለት የፓሊስ አባላት ከባድ ጉዳት ደርሶባቸዋል ከእነርሱ (“ፋኖ”) በተተኮሰ ጥይት ” ሲሉ ተናግረዋል።
“ እሱም ብቻ አይደለም አንድ አሽከርካሪ እንዲጭናቸው ሲያስገድዱት ‘አልተባበርም’ ስላለ መኪና ውስጥ በጥይት መትተውት ሞቷል። የአንድ ግለሰብ ተሽከርካሪ መስታውት በጥይት መትተውታል። ሙሉ ለሙሉ ጉዳት ደርሶበታል። ሰውየው ግን ምንም የሆነው ነገር የለም ” ነው ያሉት።
“ ማኀበረሰቡ ከፓሊስና ከፀጥታ አካላት የሚተላለፉ መረጃዎችን በቁም ነገር ማዳመጥ፣ አካባቢውን ማዬት መቻል አለበት። በሰላምና በፀጥታ ጉዳይ ምንም አይነት ድርድር የለም። እነዚህ ሰዎች መካከላችን አሉ። ይሄ አንዱ ማሳያ ነው። ቦሌ መሀል ከተማው ላይ እንግዲህ እየኖሩ ነው የነበረው ” ብለዋል ኮማንደር ማርቆስ።
“ እነዚህ ሰዎች መንፈስ አይደሉም። በተሽከርካሪያቸው ሲወጡ ሲገቡ ይታያሉ። ግን ፓሊስ በራሱ ነው ሲከታተተል የነበረው ” ያሉት ኮማንደር ማርቆስ፤ አሁንም ማህበረሰቡ አካባቢውን መጠበቅ አለበት ብለዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
በአዲስ አበባ ከተማ በፋኖና በፓሊስ በተደረገ የተኩስ ልውውጥ አንድ ሲቪልና ሁለት ታጣቂዎች ሲገደሉ፣ በሁለት የፓሊስ አባላት ላይ ከባድ ጉዳት መድረሱ ተገልጿል።
የ“ፋኖ” አመራርና አባላት በአዲስ አበባ ከተማ ቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 3 ሚሊኒየም አዳራሽ አጠገብ ከፀጥታ አካላት ተኩስ እንደከፈቱ፣ በ “ፋኖ” በኩል ሁለት ታጣቂዎች ሲገደሉ አንድ በቁጥጥር ስር እንደዋለ፣ በመንግሥት በኩል ሁለት የፓሊስ አባላት ላይ ጉዳት እንደደረሰ፣ በንጹሐን በኩል ደግሞ አንድ አሽከርካራ እንደተገደለ፣ የአዲስ አበባ ፓሊስ ኮሚሽን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አረጋግጧል።
የኮሚሽኑ የሕዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር ምክትል ኮማንደር ማርቆስ ታደሰ በሰጡት ቃል፣ “ የተገደሉት የ “ፋኖ” ቡድን አመራርና አባላት ናቸው። አመራሩ ናሁሰናይ አንዳርጌ ነው። ሌላው አቤኔዘር ጋሻው የተባለው ነው፣ እዛው ቦታው ላይ በተደረገ የተኩስ ልውውጥ ሂወቱ አልፏል። ሀብታሙ አንዳርጌ ግን ምንም አልሆነም በቁጥጥር ስር ውሏል ” ብለዋል።
የ “ፋኖ” አመራርና አባላት የነበራቸውን እንቅስቃሴ ሲያስረዱም ኮማንደሩ፣ “ በከተማው ውስጥ ነው የሚንቀሳቀሱት የነበረው። በከተማው ውስጥ ደግሞ የተለያዩ ጥፋቶች ለማጥፋት ነው እንቅስቃሴ ሲያደርጉ የነበረው ” ነው ያሉት።
አክለውም፣ “ እነርሱን ለመያዝ በተደረገው ሂደት ቦሌ ወረዳ 3 ሳጅን አራርሳ ተሾመና ኮንስታብል ማቲያስ ጴጥሮስ የሚባሉ ሁለት የፓሊስ አባላት ከባድ ጉዳት ደርሶባቸዋል ከእነርሱ (“ፋኖ”) በተተኮሰ ጥይት ” ሲሉ ተናግረዋል።
“ እሱም ብቻ አይደለም አንድ አሽከርካሪ እንዲጭናቸው ሲያስገድዱት ‘አልተባበርም’ ስላለ መኪና ውስጥ በጥይት መትተውት ሞቷል። የአንድ ግለሰብ ተሽከርካሪ መስታውት በጥይት መትተውታል። ሙሉ ለሙሉ ጉዳት ደርሶበታል። ሰውየው ግን ምንም የሆነው ነገር የለም ” ነው ያሉት።
“ ማኀበረሰቡ ከፓሊስና ከፀጥታ አካላት የሚተላለፉ መረጃዎችን በቁም ነገር ማዳመጥ፣ አካባቢውን ማዬት መቻል አለበት። በሰላምና በፀጥታ ጉዳይ ምንም አይነት ድርድር የለም። እነዚህ ሰዎች መካከላችን አሉ። ይሄ አንዱ ማሳያ ነው። ቦሌ መሀል ከተማው ላይ እንግዲህ እየኖሩ ነው የነበረው ” ብለዋል ኮማንደር ማርቆስ።
“ እነዚህ ሰዎች መንፈስ አይደሉም። በተሽከርካሪያቸው ሲወጡ ሲገቡ ይታያሉ። ግን ፓሊስ በራሱ ነው ሲከታተተል የነበረው ” ያሉት ኮማንደር ማርቆስ፤ አሁንም ማህበረሰቡ አካባቢውን መጠበቅ አለበት ብለዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
ባህር ማዶ ከሚኖር ወዳጅ ዘመድ በአጋሮቻችን በኩል የተላከልዎትን ገንዘብ በቴሌብር ዓለም አቀፍ ሃዋላ በኩል እስከ ሰኔ 23 ቀን 2016 ዓ.ም ሲቀበሉ 20% የገንዘብ ስጦታ ያገኛሉ፤ የዕድል ጨዋታ በመጫወት የአየር ሰዓት ይሸለማሉ!
ለተጨማሪ መረጃ ማስፈንጠሪያውን bit.ly/3ArwoEO ይጫኑ
#Ethiotelecom #telebirr #DigitalAfrica #DigitalEthiopia #RealizingDigitalEthiopia
ለተጨማሪ መረጃ ማስፈንጠሪያውን bit.ly/3ArwoEO ይጫኑ
#Ethiotelecom #telebirr #DigitalAfrica #DigitalEthiopia #RealizingDigitalEthiopia
የኤርትራ መንግሥት 46 እስረኞችን ለቀቀ።
በትግራይ ክልል ጦርነት ወቅት ከክልሉ የተለያዩ አካባቢዎች ወደ #ኤርትራ ተወስደው በኤርትራ መንግሥት ታስረው ከነበሩ የትግራይ ተወላጆች ውስጥ 46ቱ በዛሬው ዕለት ተለቀው ሽራሮ ከተማ ገብተዋል።
የሽራሮ ከንቲባ አቶ ሙሉ ብርሃነ ለ " ኢትዮጵያ ኢንሳይደር " ድርገጽ በሰጡት ቃል ፥ እስረኞቹ በኤርትራ የጋሽ ባርካ ዞን መቀመጫ በሆነችው የባረንቱ ከተማ ታስረው የቆዩ መሆናቸውን ጠቁመዋል።
ዛሬ ጠዋት በ”አይሱዙ” ተሽከርካሪ ተጭነው ሽራሮ እንደገቡ ተናግረዋል።
በእስር ላይ የቆዩት የትግራይ ተወላጆች “ ምህረት ተደርጎላቸው ” የተለቀቁ ሲሆን ይህም በኢፌዲሪ የመከላከያ ሰራዊት እና በኤርትራ ሰራዊት መካከል ሲካሄድ በቆየ ንግግር መሆኑን ከንቲባው ገልጸዋል።
እስረኞቹ ተለቅቀው ወደ ሀገራቸው እንዲመለሱ የተደረገው፤ በጦርነቱ ጊዜ “ ከባድ የሆነ ወንጀል ያልፈጸሙ ናቸው ” በሚል ምክንያት ነው።
በኤርትራ እስር ላይ ከሚገኙ የትግራይ ተወላጆች መካከል አሁንም ያልተፈቱ አሉ።
የዛሬው እርምጃ የቀሩትም እንደሚለቀቁ “ ተስፋ ሰጪ ነው ” ሲሉ የሽራሮ ከተማ ከንቲባ ለድረገፁ በሰጡት ቃል ተናግረዋል።
@tikvahethiopia
በትግራይ ክልል ጦርነት ወቅት ከክልሉ የተለያዩ አካባቢዎች ወደ #ኤርትራ ተወስደው በኤርትራ መንግሥት ታስረው ከነበሩ የትግራይ ተወላጆች ውስጥ 46ቱ በዛሬው ዕለት ተለቀው ሽራሮ ከተማ ገብተዋል።
የሽራሮ ከንቲባ አቶ ሙሉ ብርሃነ ለ " ኢትዮጵያ ኢንሳይደር " ድርገጽ በሰጡት ቃል ፥ እስረኞቹ በኤርትራ የጋሽ ባርካ ዞን መቀመጫ በሆነችው የባረንቱ ከተማ ታስረው የቆዩ መሆናቸውን ጠቁመዋል።
ዛሬ ጠዋት በ”አይሱዙ” ተሽከርካሪ ተጭነው ሽራሮ እንደገቡ ተናግረዋል።
በእስር ላይ የቆዩት የትግራይ ተወላጆች “ ምህረት ተደርጎላቸው ” የተለቀቁ ሲሆን ይህም በኢፌዲሪ የመከላከያ ሰራዊት እና በኤርትራ ሰራዊት መካከል ሲካሄድ በቆየ ንግግር መሆኑን ከንቲባው ገልጸዋል።
እስረኞቹ ተለቅቀው ወደ ሀገራቸው እንዲመለሱ የተደረገው፤ በጦርነቱ ጊዜ “ ከባድ የሆነ ወንጀል ያልፈጸሙ ናቸው ” በሚል ምክንያት ነው።
በኤርትራ እስር ላይ ከሚገኙ የትግራይ ተወላጆች መካከል አሁንም ያልተፈቱ አሉ።
የዛሬው እርምጃ የቀሩትም እንደሚለቀቁ “ ተስፋ ሰጪ ነው ” ሲሉ የሽራሮ ከተማ ከንቲባ ለድረገፁ በሰጡት ቃል ተናግረዋል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#AddisAbaba
" ... የተኩስ ልውውጡ የነበረው ከሚሊኒየም አዳራች በሰንሻይን በኩል ወደ ቦሌ መድኃኒዓለም በሚያስወጣው መንገድ ነበር " - የአካባቢው ነዋሪዎች
ዛሬ በአዲስ አበባ ከተማ ፤ ቦሌ በፖሊስ እና ፋኖ አባላት መካከል የነበረው የተኩስ ልውውጥ ከሚሊኒየም አዳራሽ ጎን በሰንሸይን ቪላ ቤቶች አድርጎ ወደ ቦሌ መድኃኒያለም ቤተክርስቲያን ወደ ሚያስወጣው መንገድ ላይ እንደነበር በአካባቢው የነበሩ ሰዎች ለቢቢሲ አማርኛ አገልግሎት ገልጸዋል።
በተኩስ ልውውጡ ሁለት የፋኖ አባላት እና አንድ መንገደኛ ህይወታቸው ጠፍቷል። ሁለት የፖሊስ አባላት ከባድ ጉዳት ደርሶባቸዋል።
የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ምክትል ኮማንደር ማርቆስ ታደሰ ለቢቢሲ አማርኛ በሰጡት ቃል ፥ " ናሁሰናይ አንዳርጌ የሚባለው በፖሊስ ቁጥጥር ስር ለማዋል በሚደረገው እንቅስቃሴ ወቅት እጅ ላለመስጠት ከፍተኛ የሆነ ትግል ነው ያደረገው " ብለዋል።
" ከዚያም አልፎ በዚያ አካባቢ የሚሄድ አንድ ግለሰብ ሕይወት እንዲያልፍ ምክንያት ሆኗል። ሁለት የፖሊስ አባላት ላይ ተኩስ ከፍቶ ከባድ ጉዳት እንዲደርስባቸው ምክንያት ሆኗል " ሲሉ ተናግረዋል።
ምክትል ኮማንደር ማርቆስ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃላቸው ፥ ቦሌ በነበረው የፋኖ አባላቱና እና የፖሊስ ተኩስ ልውውጥ ፦
- ናሁሰናይ አንዳርጌ ቆስሎ ወደ ህክምና ከተላከ በኋላ #ሞቷል፤
- አቤኔዘር ጋሻው በተኩስ ልውውጡ መሃል ተገድሏል፤
- ሀብታሙ አንዳርጌ የተባለ የፋኖ አባል ሳይቆስል በቁጥጥር ስር ውሏል።
ከዚህ ባለፈ ፦
° አቶ እንዳሻው ጌትነት የተባሉ ባለመኪና ‘#አልተባበርም’ ስላሉ መኪና ውስጥ በጥይት መትተውት ገድለውታል።
° የአንድ ግለሰብ ተሽከርካሪ መስታወት በጥይት መተውታል " ሲሉ ተናግረዋል።
በነበረው የተኩስ ልውውጥ ከፖሊስ በኩል ሳጅን አራርሳ ተሾመ እና ኮንስታብል ማቲያስ ጴጥሮስ ቆስለው ከባድ ጉዳት ደርሶባቸዋል።
@tikvahethiopia
" ... የተኩስ ልውውጡ የነበረው ከሚሊኒየም አዳራች በሰንሻይን በኩል ወደ ቦሌ መድኃኒዓለም በሚያስወጣው መንገድ ነበር " - የአካባቢው ነዋሪዎች
ዛሬ በአዲስ አበባ ከተማ ፤ ቦሌ በፖሊስ እና ፋኖ አባላት መካከል የነበረው የተኩስ ልውውጥ ከሚሊኒየም አዳራሽ ጎን በሰንሸይን ቪላ ቤቶች አድርጎ ወደ ቦሌ መድኃኒያለም ቤተክርስቲያን ወደ ሚያስወጣው መንገድ ላይ እንደነበር በአካባቢው የነበሩ ሰዎች ለቢቢሲ አማርኛ አገልግሎት ገልጸዋል።
በተኩስ ልውውጡ ሁለት የፋኖ አባላት እና አንድ መንገደኛ ህይወታቸው ጠፍቷል። ሁለት የፖሊስ አባላት ከባድ ጉዳት ደርሶባቸዋል።
የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ምክትል ኮማንደር ማርቆስ ታደሰ ለቢቢሲ አማርኛ በሰጡት ቃል ፥ " ናሁሰናይ አንዳርጌ የሚባለው በፖሊስ ቁጥጥር ስር ለማዋል በሚደረገው እንቅስቃሴ ወቅት እጅ ላለመስጠት ከፍተኛ የሆነ ትግል ነው ያደረገው " ብለዋል።
" ከዚያም አልፎ በዚያ አካባቢ የሚሄድ አንድ ግለሰብ ሕይወት እንዲያልፍ ምክንያት ሆኗል። ሁለት የፖሊስ አባላት ላይ ተኩስ ከፍቶ ከባድ ጉዳት እንዲደርስባቸው ምክንያት ሆኗል " ሲሉ ተናግረዋል።
ምክትል ኮማንደር ማርቆስ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃላቸው ፥ ቦሌ በነበረው የፋኖ አባላቱና እና የፖሊስ ተኩስ ልውውጥ ፦
- ናሁሰናይ አንዳርጌ ቆስሎ ወደ ህክምና ከተላከ በኋላ #ሞቷል፤
- አቤኔዘር ጋሻው በተኩስ ልውውጡ መሃል ተገድሏል፤
- ሀብታሙ አንዳርጌ የተባለ የፋኖ አባል ሳይቆስል በቁጥጥር ስር ውሏል።
ከዚህ ባለፈ ፦
° አቶ እንዳሻው ጌትነት የተባሉ ባለመኪና ‘#አልተባበርም’ ስላሉ መኪና ውስጥ በጥይት መትተውት ገድለውታል።
° የአንድ ግለሰብ ተሽከርካሪ መስታወት በጥይት መተውታል " ሲሉ ተናግረዋል።
በነበረው የተኩስ ልውውጥ ከፖሊስ በኩል ሳጅን አራርሳ ተሾመ እና ኮንስታብል ማቲያስ ጴጥሮስ ቆስለው ከባድ ጉዳት ደርሶባቸዋል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update ታግታ ከተወሰደች በኃላ ለማስለቀቂያ 3 ሚሊዮን ብር የተጠየቀባት ታጋዲዋ ተማሪ ማህሌት ተኽላይ ታግታ ከተወሰደች 20 ቀናት ሆኗታል። ቤተሰቦቿ " ልጃችንን አፋልጉን " ሲሉ በፈጣሪ ስም ተማጽነዋል። መላው ኢትዮጵያ ህዝብ እና የፀጥታ ኃይል ልጃቸውን እንዲፈልግላቸው ጥሪ አቅርበዋል። የታዳጊ ተማሪ ማህሌት ቤተሰቦች ከትግራይ ዓድዋ ከተማ ያስተላለፉት የአፋልጉን የተማፅኖ ጥሪ ምን ይላል ?…
#Update
"...ታጋችዋን ታዳጊ ለማስለቀቅ ከከተማ እስከ ክልል የተቀናጀ የክትትልና ምርመራ ስራ እየሰራን ነው። በቁጥጥር ስር የዋሉ ተጠርጣሪዎችም አሉ " - የዓድዋ ከተማ ፓሊስ
የዓድዋ ከተማ ፓሊስ በታጋቿ ታዳጊ ተማሪ ማህሌት ተኽላይ ጉዳይ ለመጀመሪያ ጊዜ ማብራሪያ ሰጥቷል።
መጋቢት 10/2016 ዓ.ም በዓድዋ ከተማ ልዩ ቦታ ዓዲ ማሕለኻ ማንነታቸው ባልታወቁ ሰዎች ታግታ የተሰወረችው ታዳጊ ተማሪ ማህሌት ተኽላይ ከታገተች 24 ቀናት ተቆጥሯል።
የዓድዋ ከተማ ፓሊስ ዋና አዛዥ ተስፋይ ኣማረ ለ104.4 የመቐለ ኤፍኤም በስልክ በሰጡት መረጃ ፥ ማንነታቸው ባልታወቁ ሰዎች ታግታ ለማስለቀቂያ 3 ሚሊዮን ብር የተጠየቀባትን የተማሪ ማህሌት ተኽላይ አጋቾችን በቁጥጥር ስር ለመዋል ፓሊስ ጥረት እንያደረገ እንደሆነ ተናግረዋል።
የታዳጊዋ መታገት በማስመልከት በተሰቦችዋ መጋቢት 10/2016 ዓ.ም ሪፓርት ካደረጉበት ቀንና ሰዓት ጀምሮ ፓሊስ ጉዳዩ ለደቂቃ ያህል ችላ እንዳላለው የገለፁት የፓሊስ ዋና አዛዡ ፥ " ' ፓሊስ ለእገታው ትኩረት አልሰጠውም ' ተብሎ በማህበራዊ የትስስር ገፆችና በሚድያዎች የሚሰራጨው መረጃ ልክ አይደለም " ብለዋል።
" ይህን ያህል ከባድ የውንብድና ወንጀል ተፈፅሞ ፓሊስ እንዴት ችላ ይለዋል ? " ሲሉ የጠየቁት ዋና አዛዡ ተስፋይ አማረ ፥ ከከተማው እስከ ክልል ፓሊስ ኮሚሽን በመቀናጀት ተጠርጣሪ ወንጀለኞች ለመያዝ ሌት ተቀን እየተሰራ ነው ብለዋል።
" ታዳጊዋን ያገቱ ሰዎች ከእገታው በፊት ለረጅም ጊዜ ሲከታተሉዋት የቆዩ መሆናቸው ከቤተሰቦችዋ የተገኘ መረጃ ይጠቁማል " ያሉት ዋና አዛዡ ፥ " የተወሰኑት ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር አውለናል። ለሚድያ መግለጫ ስላልሰጠን ብቻ ስራችን እየሰራን እንዳልሆነ ተደርጎ መውሰድ አግባብነት የለውም " ብለዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ በታዳጊዋ ተማሪ ማህሌት ተኽላይ ጉዳይ በተደጋጋሚ መረጃ ያደረሰ ሲሆን ከቀናት በፊት ቤተሰቦቿ በሰጡት ቃል ፥ አጋቾች ለማስለቀቅያ 3 ሚሊዮን ብር እንዲከፈላቸው በጠየቁበት ዕለት ድምጿን ከሰሙ በኃላ ዳግም እንዳላገኟት እነሱም እንዳልደወሉ ፣በምን ሁኔታ ላይ እንዳለች እንኳን እንደማያውቁ ፤ በዚህም መላው ቤተሰብ በከፍተኛ ጭንቅና ሃዘን ውስጥ እንደሚገኝ ተናግረው ነበር።
#TikvahEthiopiaMekelleFamily
@tikvahethiopia
"...ታጋችዋን ታዳጊ ለማስለቀቅ ከከተማ እስከ ክልል የተቀናጀ የክትትልና ምርመራ ስራ እየሰራን ነው። በቁጥጥር ስር የዋሉ ተጠርጣሪዎችም አሉ " - የዓድዋ ከተማ ፓሊስ
የዓድዋ ከተማ ፓሊስ በታጋቿ ታዳጊ ተማሪ ማህሌት ተኽላይ ጉዳይ ለመጀመሪያ ጊዜ ማብራሪያ ሰጥቷል።
መጋቢት 10/2016 ዓ.ም በዓድዋ ከተማ ልዩ ቦታ ዓዲ ማሕለኻ ማንነታቸው ባልታወቁ ሰዎች ታግታ የተሰወረችው ታዳጊ ተማሪ ማህሌት ተኽላይ ከታገተች 24 ቀናት ተቆጥሯል።
የዓድዋ ከተማ ፓሊስ ዋና አዛዥ ተስፋይ ኣማረ ለ104.4 የመቐለ ኤፍኤም በስልክ በሰጡት መረጃ ፥ ማንነታቸው ባልታወቁ ሰዎች ታግታ ለማስለቀቂያ 3 ሚሊዮን ብር የተጠየቀባትን የተማሪ ማህሌት ተኽላይ አጋቾችን በቁጥጥር ስር ለመዋል ፓሊስ ጥረት እንያደረገ እንደሆነ ተናግረዋል።
የታዳጊዋ መታገት በማስመልከት በተሰቦችዋ መጋቢት 10/2016 ዓ.ም ሪፓርት ካደረጉበት ቀንና ሰዓት ጀምሮ ፓሊስ ጉዳዩ ለደቂቃ ያህል ችላ እንዳላለው የገለፁት የፓሊስ ዋና አዛዡ ፥ " ' ፓሊስ ለእገታው ትኩረት አልሰጠውም ' ተብሎ በማህበራዊ የትስስር ገፆችና በሚድያዎች የሚሰራጨው መረጃ ልክ አይደለም " ብለዋል።
" ይህን ያህል ከባድ የውንብድና ወንጀል ተፈፅሞ ፓሊስ እንዴት ችላ ይለዋል ? " ሲሉ የጠየቁት ዋና አዛዡ ተስፋይ አማረ ፥ ከከተማው እስከ ክልል ፓሊስ ኮሚሽን በመቀናጀት ተጠርጣሪ ወንጀለኞች ለመያዝ ሌት ተቀን እየተሰራ ነው ብለዋል።
" ታዳጊዋን ያገቱ ሰዎች ከእገታው በፊት ለረጅም ጊዜ ሲከታተሉዋት የቆዩ መሆናቸው ከቤተሰቦችዋ የተገኘ መረጃ ይጠቁማል " ያሉት ዋና አዛዡ ፥ " የተወሰኑት ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር አውለናል። ለሚድያ መግለጫ ስላልሰጠን ብቻ ስራችን እየሰራን እንዳልሆነ ተደርጎ መውሰድ አግባብነት የለውም " ብለዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ በታዳጊዋ ተማሪ ማህሌት ተኽላይ ጉዳይ በተደጋጋሚ መረጃ ያደረሰ ሲሆን ከቀናት በፊት ቤተሰቦቿ በሰጡት ቃል ፥ አጋቾች ለማስለቀቅያ 3 ሚሊዮን ብር እንዲከፈላቸው በጠየቁበት ዕለት ድምጿን ከሰሙ በኃላ ዳግም እንዳላገኟት እነሱም እንዳልደወሉ ፣በምን ሁኔታ ላይ እንዳለች እንኳን እንደማያውቁ ፤ በዚህም መላው ቤተሰብ በከፍተኛ ጭንቅና ሃዘን ውስጥ እንደሚገኝ ተናግረው ነበር።
#TikvahEthiopiaMekelleFamily
@tikvahethiopia
" በህገ-መንግስቱ መሰረት የትግራይ ግዛታዊ አንድነት ይከበር ወደ ቤታችን መልሱን " - የራያ አለማጣ ተፈናቃዮች
ከትግራይ ደቡባዊ ዞን ወረዳ ራያ አላማጣና አለማጣ ከተማ ተፈናቅለው በመኾኒ ከተማ የመጠለያ ጣብያ የሚኖሩ ተፈናቃዮች ሰላማዊ ሰልፍ አካሂደዋል።
ዛሬ ቅዳሜ ሚያዝያ 5 /2016 ዓ.ም በተካሄደውና ከመኾኒ ከተማ እስከ ኩኩፍቶ ፣ በሪ ተኽላይ የተባለ ቦታ በሸፈነው የተፈናቃዮቹ ሰላማዊ ሰልፍ ፦
- የፕሪቶሪያ ስምምነት ሙሉ በሙሉ ይተግበር!!
- የትግራይ ግዛታዊ አንድነት ይከበር !!
- ወደ ቄያችን መልሱን !!
... የሚሉና ሌሎች መፈክሮች መሰማታቸውን የቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ አባል ቦታው ድረስ በመደወል ለማረጋገጥ ችሏል።
@tikvahethiopia
ከትግራይ ደቡባዊ ዞን ወረዳ ራያ አላማጣና አለማጣ ከተማ ተፈናቅለው በመኾኒ ከተማ የመጠለያ ጣብያ የሚኖሩ ተፈናቃዮች ሰላማዊ ሰልፍ አካሂደዋል።
ዛሬ ቅዳሜ ሚያዝያ 5 /2016 ዓ.ም በተካሄደውና ከመኾኒ ከተማ እስከ ኩኩፍቶ ፣ በሪ ተኽላይ የተባለ ቦታ በሸፈነው የተፈናቃዮቹ ሰላማዊ ሰልፍ ፦
- የፕሪቶሪያ ስምምነት ሙሉ በሙሉ ይተግበር!!
- የትግራይ ግዛታዊ አንድነት ይከበር !!
- ወደ ቄያችን መልሱን !!
... የሚሉና ሌሎች መፈክሮች መሰማታቸውን የቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ አባል ቦታው ድረስ በመደወል ለማረጋገጥ ችሏል።
@tikvahethiopia