TIKVAH-ETHIOPIA
#አዲስአበባ #ነዳጅ የኢትዮጵያ ነዳጅ አዳዮች ማህበር ፥ በአዲስ አበባ ከተማ የነዳጅ ዕጥረት መከሰቱንና ምክንያቱ ደግሞ ጅቡቲ ላይ የዘነበ ከባድ ዝናብን ተከትሎ የመንገድ መቆራረጥ በመፈጠሩ መሆኑን ገልጿል። በተጨማሪም አስቀድሞም ከቦታዉ በበቂ ሁኔታ ነዳጅ እየተጫነ ባለመሆኑ መሆኑን አመልክቷል። የማህበሩ የቦርድ አባል አቶ ደሳለኝ አበባየሁ ፥ እነዚህ ምክንያቶች ከነዳጅ አቅራቢ ኩባንያዎች የተነገራቸዉ…
#ነዳጅ
" እስከ ነገ ጠዋት ድረስ ችግሩ ይቀረፋል " - የኢትዮጵያ ነዳጅ አቅራቢ ድርጅት
የኢትዮጵያ ነዳጅ አቅራቢ ድርጅት ፥ በአዲስ አበባ የነዳጅ እጥረት የተፈጠረው ጅቡቲ ላይ የዘነበውን ከባድ ዝናብ ተከትሎ ድልድይ በመሰበሩ ነው ብሏል።
በተጨማሪም ነዳጅ የጫነ አንድ የነዳጅ ቦቴ ተገልብጦ መንገድ መዘጋጋት በማስከተሉ የነዳጅ እጥረት መከሰቱን ገልጿል።
ችግሩን ለመቅረፍ ነዳጅ የጫኑ ቦቴዎች በድሬደዋ በኩል እንዲገቡ መደረጉን የገለጸው ድርጅቱ ይሄንኑ ተከትሎ ትናንት ከሰአት ጀምሮ ነዳጅ የጫኑ ቦቴዎች መግባት መጀመራቸውን አሳውቋል።
#ዛሬ እና #ነገ ነዳጅ የጫኑ ተጨማሪ ቦቴዎች እንደሚገቡና ችግሩ እስከ ነገ ጠዋት ድረስ እንደሚቀረፍ ለብሄራዊ የቴሌቪዥን ጣቢያ በሰጠው ቃል ገልጿል።
ከሰሞኑን በአዲስ አበባ ነዳጅ ማግኘት አስቸጋሪ ሆኗል። አሽከርካሪዎች ነዳጅ ለማግኘት እጅግ ረጅም ሰልፍ ለመጠበቅ እየተገደዱ ሲሆን በዚህ ምክንያት ስራቸውም እየተስተጓጎለ ነው።
@tikvahethiopia
" እስከ ነገ ጠዋት ድረስ ችግሩ ይቀረፋል " - የኢትዮጵያ ነዳጅ አቅራቢ ድርጅት
የኢትዮጵያ ነዳጅ አቅራቢ ድርጅት ፥ በአዲስ አበባ የነዳጅ እጥረት የተፈጠረው ጅቡቲ ላይ የዘነበውን ከባድ ዝናብ ተከትሎ ድልድይ በመሰበሩ ነው ብሏል።
በተጨማሪም ነዳጅ የጫነ አንድ የነዳጅ ቦቴ ተገልብጦ መንገድ መዘጋጋት በማስከተሉ የነዳጅ እጥረት መከሰቱን ገልጿል።
ችግሩን ለመቅረፍ ነዳጅ የጫኑ ቦቴዎች በድሬደዋ በኩል እንዲገቡ መደረጉን የገለጸው ድርጅቱ ይሄንኑ ተከትሎ ትናንት ከሰአት ጀምሮ ነዳጅ የጫኑ ቦቴዎች መግባት መጀመራቸውን አሳውቋል።
#ዛሬ እና #ነገ ነዳጅ የጫኑ ተጨማሪ ቦቴዎች እንደሚገቡና ችግሩ እስከ ነገ ጠዋት ድረስ እንደሚቀረፍ ለብሄራዊ የቴሌቪዥን ጣቢያ በሰጠው ቃል ገልጿል።
ከሰሞኑን በአዲስ አበባ ነዳጅ ማግኘት አስቸጋሪ ሆኗል። አሽከርካሪዎች ነዳጅ ለማግኘት እጅግ ረጅም ሰልፍ ለመጠበቅ እየተገደዱ ሲሆን በዚህ ምክንያት ስራቸውም እየተስተጓጎለ ነው።
@tikvahethiopia
ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) እና ብልፅግና ፓርቲ በፕሪቶሪያ ውል መሰረት ፓለቲካዊ ውይይት ለመጀመር መስማማታቸው ተገለጸ።
ህወሓት በይፋዊ የማህበራዊ የትስስር ገፁ ባሰራጨው መረጃ ፥ በብልፅግና ምክትል ፕረዚደንት አቶ አደም ፋራህ የሚመራ ቡድን ዛሬ መጋቢት 24/2017 ዓ.ም በመቐለ ከህወሓት ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ጋር ተወያይቷል።
የሁለቱም ፓለቲካዊ ፓርቲዎች የፓለቲካ ውይይት በፕሪቶሪያው ስምምነት መሰረት ቀደም ብሎ መጀመር እንደነበረበት በመተማመን በአጭር ጊዜ ውስጥ ውይይት እንዲጀምሩ ስምምነት ላይ መድረሳቸውን ህወሓት ገልጿል።
@tikvahethiopia
ህወሓት በይፋዊ የማህበራዊ የትስስር ገፁ ባሰራጨው መረጃ ፥ በብልፅግና ምክትል ፕረዚደንት አቶ አደም ፋራህ የሚመራ ቡድን ዛሬ መጋቢት 24/2017 ዓ.ም በመቐለ ከህወሓት ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ጋር ተወያይቷል።
የሁለቱም ፓለቲካዊ ፓርቲዎች የፓለቲካ ውይይት በፕሪቶሪያው ስምምነት መሰረት ቀደም ብሎ መጀመር እንደነበረበት በመተማመን በአጭር ጊዜ ውስጥ ውይይት እንዲጀምሩ ስምምነት ላይ መድረሳቸውን ህወሓት ገልጿል።
@tikvahethiopia
በቢዝነስ ኤክሴል ንግድዎን ያዘምኑ!
ሥራዎን የሚያቀሉ ቴምፕሌቶች እና ስለንግዱ ዓለም ወሳኝ መረጃዎችን ያገኛሉ።
በተጨማሪ ይህን መድረክ በመጠቀም በሳምንታዊ ጥያቄና መልስ ውድድር በመሳተፍ በየሳምንቱ 50,000 ብር ተሸላሚ መሆን ይችላሉ።
ለመመዝገብ ok ብለው ወደ 6424 ይላኩ
በቀን 2ብር ብቻ፤ ለ3 ቀናት በነፃ
ለተጨማሪ https://www.businessexcel.et ይጎብኙ
#Ethiotelecom #telebirr #RealizingDigitalEthiopia
ሥራዎን የሚያቀሉ ቴምፕሌቶች እና ስለንግዱ ዓለም ወሳኝ መረጃዎችን ያገኛሉ።
በተጨማሪ ይህን መድረክ በመጠቀም በሳምንታዊ ጥያቄና መልስ ውድድር በመሳተፍ በየሳምንቱ 50,000 ብር ተሸላሚ መሆን ይችላሉ።
ለመመዝገብ ok ብለው ወደ 6424 ይላኩ
በቀን 2ብር ብቻ፤ ለ3 ቀናት በነፃ
ለተጨማሪ https://www.businessexcel.et ይጎብኙ
#Ethiotelecom #telebirr #RealizingDigitalEthiopia
ወ/ሮ አያንቱ ሙስጠፋ ላይ የተፈፀመው ምንድነው ?
➡ ወ/ሮ አያንቱ ሙስጠፋ ነዋሪነቷ በምስራቅ ሀረጌ ዞን ኮምቦልቻ ወረዳ ቀበሌ 02 ነው።
➡ በ2008 ዓ/ም ነው ከባለቤቷ አቶ አሪፍ አልዬ ጋር በጋብቻ የተሳሰረችው።
➡ ላለፉት 8 ዓመታት በትዳር ስትቆይ 2 ወንድ ልጆችን አፍርተዋል።
ጥር 15 ቀን 2016 ዓ/ም ፍፁም ባልጠበቀችው ሁኔታ በገዛ ባለቤቷ እና የልጆቿ አባት ዘግናኝ በሆነ መንገድ በአሲድ ተቃጥላለች። አንድ አይኗንም አጥታለች።
ከባለቤቷ ጋር በተደጋጋሚ አለመግባባቶች ቢፈጠሩም ይህን ያደርግብኛል ብላ በፍፁም አልጠበቀችም።
ወ/ሮ አያንቱ ሙስጠፋ ፦
" በዕለቱ (ጥር 15 ቀን 2016) ቀን ስራ ውዬ ልጆቼን ከቤተሰቦቼ ጋር ይዤ ወደ ቤት ገባሁ።
ማታ ተሰብስበን እራታችንን በላን እጅግ ደክሞኝ ስለነበር ልጆቼን በግራ እና በቀኝ አስተኝቼ እኔም ተኛው።
በዛ ቀን ምን ክፉ ደግ አልተነገርንም። ከለሊቱ 9 ሰዓት ተኩል አካባቢ #አሲድ በማስታጠቢያ አድርጎ በተኛሁበት በጭንቅላቴ አፈሰሰብኝ።
ወይኔ ጭንቅላቴን ተቃጠልኩ ! ብዬ ከተኛሁበት ተነስቼ እጁን ልይዘው ስሞክር ' ገና መቼ ተቃጠልሽ ' ብሎ አሲዱን አይኔ ውስጥ ጨመረው።
ያኔ አንዱ አይኔን ለማትረፍ በእጄ ሸፍኜ በሩን ለመክፈት ስሞክር የተረፈውን አሲድ ጀርባዬ ላይ ረጨብኝ።
ለረጅም ጊዜ #በቅናት ምክንያት ያስቸግረኝ ነበር። ከዛሬ ነገ ይሻለዋል እያልኩኝ አብሬው ቆየሁ። በዚህ ውስጥ ነው 2 ልጆች የወለድነው።
በተደጋጋሚ ይዝትብኝ የነበረ ቢሆንም እንዲህ ይጨክናል ብዬ አላሰብኩም። "
እንደ ሀረማያ የሕይወት ፋና ሆስፒታል መረጃ ከሆነ በወ/ሮ አያንቱ ላይ የደረሰው ቃጠሎ 3ኛ ደረጃ የሚባለው ነው። የአሲድ ጥቃቱ በአይኗ፣ በጭንቅላቷ፣ ፊቷ ላይ ፣ ደረቷ ፊት ፣ እጇ ላይ ጉዳት ደርሷል።
የቀኝ አይኗ ላይ በአሲድ ቃጠሎው ምክንያት የብሌን ጉዳት ስላጋጠመ ማየት አትችልም። የግራውን ግን በህክምና ማትረፍ ተችሏል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ለመረጃው ባለቤት የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቴሌቪዥን ጣቢያ (ጋዜጠኛ ቴዎድሮስ ታደሰ) እውቅና ይሰጣል።
@tikvahethiopia
➡ ወ/ሮ አያንቱ ሙስጠፋ ነዋሪነቷ በምስራቅ ሀረጌ ዞን ኮምቦልቻ ወረዳ ቀበሌ 02 ነው።
➡ በ2008 ዓ/ም ነው ከባለቤቷ አቶ አሪፍ አልዬ ጋር በጋብቻ የተሳሰረችው።
➡ ላለፉት 8 ዓመታት በትዳር ስትቆይ 2 ወንድ ልጆችን አፍርተዋል።
ጥር 15 ቀን 2016 ዓ/ም ፍፁም ባልጠበቀችው ሁኔታ በገዛ ባለቤቷ እና የልጆቿ አባት ዘግናኝ በሆነ መንገድ በአሲድ ተቃጥላለች። አንድ አይኗንም አጥታለች።
ከባለቤቷ ጋር በተደጋጋሚ አለመግባባቶች ቢፈጠሩም ይህን ያደርግብኛል ብላ በፍፁም አልጠበቀችም።
ወ/ሮ አያንቱ ሙስጠፋ ፦
" በዕለቱ (ጥር 15 ቀን 2016) ቀን ስራ ውዬ ልጆቼን ከቤተሰቦቼ ጋር ይዤ ወደ ቤት ገባሁ።
ማታ ተሰብስበን እራታችንን በላን እጅግ ደክሞኝ ስለነበር ልጆቼን በግራ እና በቀኝ አስተኝቼ እኔም ተኛው።
በዛ ቀን ምን ክፉ ደግ አልተነገርንም። ከለሊቱ 9 ሰዓት ተኩል አካባቢ #አሲድ በማስታጠቢያ አድርጎ በተኛሁበት በጭንቅላቴ አፈሰሰብኝ።
ወይኔ ጭንቅላቴን ተቃጠልኩ ! ብዬ ከተኛሁበት ተነስቼ እጁን ልይዘው ስሞክር ' ገና መቼ ተቃጠልሽ ' ብሎ አሲዱን አይኔ ውስጥ ጨመረው።
ያኔ አንዱ አይኔን ለማትረፍ በእጄ ሸፍኜ በሩን ለመክፈት ስሞክር የተረፈውን አሲድ ጀርባዬ ላይ ረጨብኝ።
ለረጅም ጊዜ #በቅናት ምክንያት ያስቸግረኝ ነበር። ከዛሬ ነገ ይሻለዋል እያልኩኝ አብሬው ቆየሁ። በዚህ ውስጥ ነው 2 ልጆች የወለድነው።
በተደጋጋሚ ይዝትብኝ የነበረ ቢሆንም እንዲህ ይጨክናል ብዬ አላሰብኩም። "
እንደ ሀረማያ የሕይወት ፋና ሆስፒታል መረጃ ከሆነ በወ/ሮ አያንቱ ላይ የደረሰው ቃጠሎ 3ኛ ደረጃ የሚባለው ነው። የአሲድ ጥቃቱ በአይኗ፣ በጭንቅላቷ፣ ፊቷ ላይ ፣ ደረቷ ፊት ፣ እጇ ላይ ጉዳት ደርሷል።
የቀኝ አይኗ ላይ በአሲድ ቃጠሎው ምክንያት የብሌን ጉዳት ስላጋጠመ ማየት አትችልም። የግራውን ግን በህክምና ማትረፍ ተችሏል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ለመረጃው ባለቤት የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቴሌቪዥን ጣቢያ (ጋዜጠኛ ቴዎድሮስ ታደሰ) እውቅና ይሰጣል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#ፎቶ
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከ121 ሺህ እስከ 95 ሺህ ገንዘብ ያለአግባብ የወሰዱና እስካሁን ያልመለሱ ግለሰቦችን ፎቶግራፍ አሰራጨ።
በትላንትናው ዕለት 108 ሺህ እስከ 305 ሺህ ገንዘብ ወስደው ያልመለሱ ግለሰቦችን ፎቶግራፍ ማሰራጨቱ ይታወሳል።
@tikvahethiopia
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከ121 ሺህ እስከ 95 ሺህ ገንዘብ ያለአግባብ የወሰዱና እስካሁን ያልመለሱ ግለሰቦችን ፎቶግራፍ አሰራጨ።
በትላንትናው ዕለት 108 ሺህ እስከ 305 ሺህ ገንዘብ ወስደው ያልመለሱ ግለሰቦችን ፎቶግራፍ ማሰራጨቱ ይታወሳል።
@tikvahethiopia