TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.3K photos
1.51K videos
212 files
4.11K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#ተጠንቀቁ⚠️

በምስሉ የተያያዙት በኦንላይን " ቀላል በሆነ ስራ ብዙ ትርፍ ታገኛላችሁ " በሚል #የማጭበርበር ስራ ተታለው ገንዘባቸውን የላኩ ሰዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የላኩት ማስረጃ እና ያጨብረበሯቸውን አካላት የቴሌግራምና የዋትአፕ አድራሻ የሚያሳይ ነው።

" ቀላል ስራ፣ ብዙ ትርፍ የሚያስገኝ ስራ " በሚል ከ65 ሺህ ብር እስከ 600 ሺህ ብር የተበሉ አሉ።

ምንም እንኳን አጨብረባሪዎቹ በውጭ ሀገር ስልክ የሚያጭበረብሩትን ሰው ቢያናግሩም የገንዘብ ልውውጡ እንዲደረግ የሚያደርጉት እዚሁ ኢትዮጵያ ውስጥ ባለ አካውንት ነው።

ገንዘብ የሚያስልኩትም የሚልኩትም እጅግ በጣም በበዙ አካውንቶች ነው። (ይህም በኦንላንይ የክሪፕቶ ግብይት ሊሆን እንደሚችል አንድ ባለሞያ ለቲክቫህ ጠቁመዋል)

ማሳሰቢያ ፦ በተለያዩ የማጭበርበሪያ ግሩፕ ውስጥ ያሉት ሰዎች ለማጭበርበር የተሰማሩ አልያም በሆነ ቡድን የሚመሩ ሲሆን ፕሮፋይል ምስላቸው የታወቂ ሰዎች / ዝም ብሎ ከኢንተርኔት የተገኙ የሴቶች / የወንዶች ፎቶ ናቸው።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ተጠንቀቁ⚠️ በምስሉ የተያያዙት በኦንላይን " ቀላል በሆነ ስራ ብዙ ትርፍ ታገኛላችሁ " በሚል #የማጭበርበር ስራ ተታለው ገንዘባቸውን የላኩ ሰዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የላኩት ማስረጃ እና ያጨብረበሯቸውን አካላት የቴሌግራምና የዋትአፕ አድራሻ የሚያሳይ ነው። " ቀላል ስራ፣ ብዙ ትርፍ የሚያስገኝ ስራ " በሚል ከ65 ሺህ ብር እስከ 600 ሺህ ብር የተበሉ አሉ። ምንም እንኳን አጨብረባሪዎቹ በውጭ ሀገር…
#ተጠንቀቁ ⚠️

ከኦንላይ ዘራፊና አጭበርባሪዎች እራሳችሁን ጠብቁ።

ነገሩ እንዲህ ነው ...

ገንዘባቸውን ኦንላይን ተጭበርብረው የተበሉ ግለሰቦች መጀመሪያ በማያወቁት የውጭ ሀገር ስልክ ቁጥር በ #ዋትስአፕ / በ #ቴሌግራም መልዕክት ይደርሳቸዋል። ስልካቸውን / username እንዴት እንደሚያገኙት ባይታወቅም።

የሚደርሳቸው መልዕክት " ጥሩ የስራ እድል እንደሆነ ፣ በትንሽ ስራም ብዙ ትርፍ እንደሚያገኙ ፣ ይህ እድል ለነሱ የተመቻቸ " እንደሆነ የሚገልጽ ነው።

ቅድመ ክፍያ እንደሌለው ፤ ከ100 ብር አንስቶ እስከ 50 ሺህ ብር በቀን የሚያስገኝ እንደሆነም መልዕክቱ ይገልጻል።

እነዚህ አጭበርባሪዎች የሚያጭበረብሯቸው ሰዎች የሚያናግሩበት መንገድ ፍፁም ትህትና የተሞላበትና ፕሮፌሽናል በሆነ መንገድ ስለሆነ በተበዳይ ዘንድ ጥርጣሬ እንዳይጫር ያደርጋሉ።

ልክ የማግባባት ስራቸውን ከሰሩ በኃላ ትንሽ ተልዕኮ ሊሰጧቸው እንደሆነ በመግለፅ ወደ " ጎግል ማፕ/ ሎኬሽን " ገብተው ኢትዮጵያ ውስጥ ባሉ የተለያዩ አገልግሎት ሰጪ ተቋማት አድራሻ ስር ጥሩ አስተያየት እንዲሰጡ ያዟቸዋል። (ይህ ከማጭበርበሪያ መንገድ አንዱ እንጂ ብቸኛው አይደለም)

የሚጭበረበረውም ሰው እጅግ በጣም ቀለል ያለ ስራ ስለሆነ የተሰጠውን ተልዕኮ መወጣቱን የሚገልጽ screenshot ለአጭበርባሪዎቹ  ይልካል። እነሱም አካውንቱን ይጠይቃሉ።

ከዚህ በኃላ ነው ዋናው ጨዋታ የሚጀመረው።

ሰዎቹ ለተሰራው ስራ ክፍያ በሚል ከ300 - 1,000 ብር ከዚህም ከፍ ያለ ገንዘብ ያስገባሉ። ይህ ሰዎችን የማሳመኛና እንዳይጠራጠሩ ማድረጊያ መንገዳቸው ነው።

ይቀጥሉና ታስክ ይሰጣችኋል ስሩ ይላሉ። በተሰራው ስራ ልክም የተወሰነ ገንዘብ ይልካሉ። ይህ እንደ ሰውየው የመክፈል አቅም እየተገመገመ የሚደረግ ነው።

በዚህ መኃል ላይ " ኮሜርሻል ቤኔፊት " የሚል ነገር ያመጣሉ ይኸውም ከ1,000 ብር እስከ 1,000,000 ብር ሰዎች እንዲያስገቡ የሚጠይቅ ነው። ሰዎች ባስገቡት ብር ልክም በሰሩት ቀላል ስራ በፐርሰንት ትርፍ እንዳለው ይነገራቸዋል።

ለምሳሌ ፦ የሚጭበረበረው ሰው በዚህ ማታለያ ተታሎ 1000 ብር ቢያስገባ ሰዎቹ መልሰው በደቂቃ ውስጥ 1500 ብር አድርገው ያስገባሉ። (ይህ አንዱ የማሳመኛ መንገዳቸው ነው)

በዚህም የሚጭበረበረው ሰው ብሩን ከፍ በማድረግ ብዙ ትርፍ ለማግኘት ሲል በዛ እያደረገ ብር ይልካላቸዋል።

የተጭበርባሪውን ሰው የመክፍል አቅም ገምግመው አጭበርባሪዎቹ የተላከው ብር ላይ 500ም ይሁን 5000 ብር ጨምረውበት መልሰው ይልካሉ። (ይህን እድታምኗቸውና ብዙ ብር እንድታስገቡ ማሳመኛ ነው)

ድጋሚ ሌሎች ስራዎዥ ይላሉ በዚህም ከፍ ያለ ብር እንድታስገቡ ያደርጋሉ። የላካችሁትን ብር እንዳታጡ የሚሳጣችሁን ስራ እንድትወጡ ይጠየቃል። እናተም ብራችሁ ተበልቶ እንዳይቀር የብሩን መጠን ከፍ ወደማድረግ ትሄዳላችሁ። (በዚህ ሁሉ ሂደት ግን ሰዎቹ የምክፈል አቅማችሁን እያጠኑና ከፍ ያለ ብር ከቻሉ እስከ #ሚሊዮን ለመቀበል ጥረት ያደርጋሉ ስለሆነም በመሃል በመሃል የሰራችሁበትን እያሉ ያራሳችሁን ብር መልሰው ይልኩላችኃል)

የመክፈል አቅማችሁንም አይተው ለዚህ ማጭበርበር ስራ ታልሞ ብቻ ወደ ተከፈተው ግሩፕ እንድትገቡ ይደረጋል። (ሁሉም ግሩፑ ውስጥ ያለው አካውንት የአጭበርባሪዎቹ ነው)

እንዲህ እንዲህ እያለ በዛ ያለ ብር ከፈፀማችሁ በኃላ ስህተት ሰርታችኋልና እሱን ለማረም ስራችሁን ቀጥሉ ይላሉ። እናተም ብራችሁን ላለማጣት ውስብሰብ ችግር ውስጥ ትወድቃላችሁ።

በመጨረሻም እየተጭበረበራችሁ እንደሆነ ስታውቁ ታቆማላችሁ። ብራችሁም መና ሆኖ ይቀራል። ሰዎቹ ግን ብር አስገቡ ያኛውን ብር ለማስመለስ ማለታቸውን ይቀጥላሉ።

ብር የሚያስልኩት ኢትዮጵያ ባለ ሰው አካውንት ነው። 

በዚህ መንገድ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ባጣራው ብቻ ከ150 ሺህ ብር እስከ 600 ሺህ ብር የተበሉ አሉ። ይህም የሰዎችን ህይወት አመሰቃቅሏል።

ለምሳሌ ፦ የቲክቫህ ቤተሰብ አባል ሆነው ስማቸውን በይፋ መግለፅ የሚያስፈልግ ሰዎች #የተጭበረበሩት የገንዘብ መጠን እንደሚከተለው ቀርቧል ፦
1. 600 ሺህ ብር
2. 470 ሺህ ብር
3. 300 ሺህ ብር
4. 300 ሺህ ብር
5. 150 ሺህ ብር
6. 150 ሺህ ብር
7. 100 ሺህ ብር
8. 80 ሺህ ብር
9. 80 ሺህ ብር
10. 65 ሺህ ብር

ይህ እጅግ በጣም ጥቂቱ ነው።

በመሆኑንም ፦

1ኛ. ማንኛውም የቴሌግራም ሆነ የዋትስአፕ የውጭ የማይታወቅ መልዕክት አትመልሱ።

2ኛ. በምንም ተአምር በትንሽ ብር ኢንቨስት አድርጉና ትርፍ አግኙ የሚሉ ሰዎችን አታናግሩ አትመኑ ተጠራጠሩ።

3ኛ. አሁንም በዚህ ውስብስብ ነገር ውስጥ ያላችሁ ተጨማሪ ብር እንዳትበሉ አቁሙ።

በቀጣይ በዘርፉ ያለ የባለሞያ አስተያየት እናቀርባለን።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ

@tikvahethiopia
#ቲክቶክ

የአሜሪካ የህዝብ ተወካዮች ም/ቤት " ቲክቶክ " የተሰኘውን መተግበሪያ በመላው ሀገሪቱ ሊያግድ የሚችል አዋጅ አጸደቀ።

አዋጁ የቻይናው #ባይትዳንስ_ኩባንያ ንብረት የሆነው " ቲክቶክ " በስድስት (6) ወራት ውስጥ አክሲዮኖችን #ለአሜሪካውያን ካልሸጠ በመላው አሜሪካ ይታገዳል ብሏል።

ይህ አዋጅ በሴኔቱ ጸድቆ በፕሬዝዳንት ጆ ባይደን ካልተፈረመበት ህግ ሆኖ ተፈጻሚ አይሆንም ተብሏል።

ፕሬዝዳንት ባይደን ግን የህግ መወሰኛ ምክርቤቱ (ሴኔቱ) አዋጁን ካጸደቀው ሳይውሉ ሳያድሩ ፊርማቸውን እንደሚያኖሩበት ከዚህ ቀደም መግለፃቸው ተነግሯል።

ባይትዳንስ በአሜሪካ የህዝብ ተወካዮች ም/ቤት የጸደቀውን አዋጅ ተፈጻሚ ለማድረግ የቻይና ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴርን ይሁንታ ማግኘት አለበት።

በዓለማቀፍ ደረጃ በወር ውስጥ ከ1 ቢሊየን በላይ ተጠቃሚዎችን ያፈራው " ቲክቶክ " በአሜሪካም ከ150 ሚሊየን በላይ ተጠቃሚዎች አሉት።

መተግበሪያው የግለሰቦችን ምስጢር ለቻይና መንግሥት አሳልፎ ሊሰጥ ይችላል በሚል በአሜሪካ በመንግስት ተቋማት ውስጥ ጥቅም ላይ እንዳይውል ታግዷል።

በአንዳንድ ግዛቶች ትምህርት ተቋማት እንዲሁ ወጣቶችን ወዳልተፈለገ አቅጣጫ እየመራ ነው በሚልም ታግዷል።

አሁን ደግሞ በመላው ሀገሪቲ ቲክቶክ ሊታገድ ይችላል በሚል በቲክቶክ ገንዘብ የሚሰሩ በርካታ አሜሪካውያን የአዋጁን መጽደቅ ተቃውመው አደባባይ መውጣታቸውን አል አይን ኒውስ ሮይተርስ እና ቢቢሲን ዋቢ በማደርግ አስነብቧል።

" ቲክቶክ " ምንም እንኳን አሜሪካ ውስጥ ከቻይና ጋር ተገናኝቶ በይበልጥ ከደህንነት ጋር በተያያዘ እንዲታገድ ግፊት ቢደረግም እንደ ኔፓል፣ ኪርጊስታን በመሳሰሉ ሀገራት ፦
- " የማህበራዊ ህይወትን እያወከ ነው "
- " ለወጣቶች እና ለልጆች አእምሮ ጠንቅ ነው "
- " ጎጂ የሆኑን ከሀገር ባህል እና እምነት ያፈነገጡ ተግባራት ይሰራጩበታል "
- " ሱስ በሚያሲዝ ይዘቱ ወጣቱ ትውልድ ላይ አሉታዊ ተፅእኖ እያደረሰ ነው " በሚሉና በሌሎች ምክንያቶች ታግዷል።

በተቃራኒው የ" ቲክቶክ " መተግበሪያ ባለቤት የሆነው ባይትዳንስ ድርጅት በመረጃና ደህንነር ጉዳይ ከቻይና ጋር ምንም የሚያያዘው ነገር እንደሌለ በተደጋጋሚ የገለጸ ሲሆን እገዳውን የሚቃወሙ በርካታቾች ደግሞ ለወጣቶች እየስራ እድል እየፈጠረ ነው ፤ ብዙ ሰዎች ያለ ብዙ ድካም ተደራሽ እንዲሆኑ እያደረገ ነው ፣ የሰዎችን ህይወት እየለወጠ ነው በሚል እገዳውን ይቃወሙታል።

@tikvahethiopia
የነዳጅ ክፍያዎን በሲቢኢ ብር በቀላሉ ይፈፅሙ!
**********
አዲስ በተሻሻለው የሲቢኢ ብር መተግበሪያ የነዳጅ ክፍያን መፈፀም እጅግ ቀሏል፡፡

የነዳጅ ቀጂውን ስልክ ቁጥር፣ የሚገዙትን የነዳጅ መጠን እና አይነት እንዲሁም ታርጋ ቁጥርዎን በማስገባት ብቻ ክፍያውን በቀላሉ መፈፀም ይችላሉ!
**********
የሲቢኢ ብር መተግበሪያን ለማውረድ/ለማዘመን፡

• ለአንድሮይድ ስልኮች፡ https://play.google.com/store/apps/details?id=prod.cbe.birr
• ለአፕል ስልኮች፡ https://apps.apple.com/us/app/cbebirr/id1600841787

#CBE #cbebirr #fuel #payment
TIKVAH-ETHIOPIA
#DrDessalegnChane በ2013 ዓ/ም በተካሄደው ሀገር አቀፍ ምርጫ በባህርዳር ከተማ የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) ፓርቲን ወክለው ተወዳድረው የተመረጡት እና የህዝብ ተወካዮች ም/ ቤት አባል የሆኑት ደሳለኝ ጫኔ (ዶ/ር) መታሰራቸውን ቤተሰባቸውን ዋቢ በማድረግ አል አይን አማርኛው አገልግሎት ዘግቧል። ስማቸው እንዳይጠቀስ የፈለጉ የዶ/ር ደሳለኝ ጫኔ ቤተሰብ አባል ፤ " ትናንት ጥር 22 ቀን…
#NewsAlert

ዶክተር ደሳለኝ ጫኔ በመታወቂያ ዋስትና ከእስር እንዲፈቱ እንደተወሰነላቸው ጠበቃቸው ተናግሩ።

በ2013 በተካሄደው 6ኛው ሀገር አቀፍ ምርጫ በባህርዳር ከተማ የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) ፓርቲን ወክለው ተወዳድረው የተመረጡት እና የህዝብ ተወካዮች ም/ቤት አባል የሆኑት ዶ/ር ደሳለኝ ጫኔ ጥር 22 ቀን 2016 ዓ/ም ምሽት በጸጥታ ኃይሎች ከቤታቸው ከተወሰዱ በኋላ ታስረው ቆይተዋል።

ጠበቃቸው ሰለሞን ገዛኸኝ ፤ ደንበኛቸው ዶ/ር ደሳለኝ ጫኔ በዛሬው ዕለት በመታወቂያ ዋስትና ከእስር እንዲለቀቁ እንደተነገራቸው ለአል አይን ኒውስ ተናግረዋል።

ይሁንና እስካሁን ድረስ ከእስር ስለመለቀቃቸው የሚያውቁት ነገር እንደሌለው ገልጸዋል።

በሌላ በኩል ፤ ዶ/ር ደሳለኝ ጫኔ ዛሬ ከሰዓት ከእስር መለቀቃቸውን የዓይን እማኞችን ዋቢ በማድረግ  ኢትዮጵያ ኢንሳይደር ዘግቧል።

ከዚህ ባለፈው ድርገፁ የቀድሞው የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አብዲ መሐመድ ዑመር (አብዲ ኢሌ)፣ የቀድሞው የብረታ ብረት እና ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን (ሜቴክ) ዋና ዳይሬክተር ሜጀር ጄነራል ክንፈ ዳኘው " በምህረት " ከእስር እንደሚፈቱ ከታመኑ ምንጮች መስማቱን ዘግቧል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የአል ዓይን ኒውስ እና የኢትዮጵያ ኢንሳይደር መሆኑን ያሳውቃል።

@tikvahethiopia
#EthiopianAirlines

" የአየር መንገዳችንን ሰራተኛ ተግባር ህገወጥ አስመስሎ ለማቅረብ መሞከሩ አሳዝኖናል " - የኢትዮጵያ አየር መንገድ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከትናንት ጀምሮ የአየር መንገዱን ዩኒፎርም የለበሰ ሰራተኛን የራሱን ሻንጣ በማስተካከል ላይ ሳለ የሚያሳይ ምስል ከተሳሳተ መረጃ ጋር በተለያዩ የማህበራዊ ትስስር ገፆች ላይ በመዘዋወር ላይ እንዳለ ገለጸ።

ይህን ተከትሎ ፦
* በምስሉ ላይ የሚታየው ግለሰብ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የአውሮፕላን ጥገና ክፍል ባልደረባ (Ethiopian Aircraft Technician) መሆኑን

* የአየር መንገዱ ዓርማ የታተመበት ሻንጣም የሰራተኛው መሆኑን፤

* በምስሉ ላይ የሚታየው ቦታ የአውሮፕላን ጥገና ክፍል ሰራተኞች የግል ንብረቶቻቸውን እና ለስራ የሚገለገሉባቸውን ቁሳቁሶች የሚያስተካክሉበት አካባቢ መሆኑን ግልጿል።

ሌሎቹ ቦርሳዎችም በምስሉ ላይ ያልተካተቱ የሌሎች ሰራተኞች ቦርሳዎች ናቸው ብሏክ።

" ይህ ስፍራ የመንገደኞች ሻንጣ ሊገኝበት የማይችል ለሰራተኞቻችን ብቻ የተከለለ ቦታ ነው " ያለው አየር መንገዱ በተጨማሪም ሳምንቱን ሙሉ ለ24 ሰዓት በደህንነት የካሜራ ዕይታ ውስጥ የሚገኝ እንደሆነ አመላክቷል።

በስራ ገበታው ላይ የሚገኝ የአየር መንገዱን ሰራተኛ ተግባር ህገወጥ አስመስሎ ለማቅረብ መሞከሩ አሳዝኖኛል ያለው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ፤ በምስሉ ላይ የሚታየው የአየር መንገዱ ሰራተኛ የአየር መንገዱ ባልደረባና የሚያስተካክለው ሻንጣም የራሱ መሆኑን አስገንዝቧል።

ደንበኞቹም ከሚዘዋወረው ምስል ጋር ተያይዞ ምንም ስጋት እንዳያድርባቸው አሳስቧል።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ለመንገደኞች ሆነ ለንብረቶቻቸው ደህንነት ከፍተኛ ጥንቃቄ እንደሚያደርግ ገልጿል።

ሰራኞቻችንም ደረጃውን የጠበቀ የደንበኛ አገልግሎት ለመስጠት ትጉህ መሆናቸውን አመልክቷል።

በተሳሳተ መረጃ የብሔራዊ አየር መንገዱን ስም ለማጥፋት ሆን ተብሎ ኃላፊነት በጎደላቸው ግለሰቦች ማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ ከሚሰራጩ የሀሰት መረጃዎች እንድትጠበቁ ሲልም መክሯል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#NewsAlert ዶክተር ደሳለኝ ጫኔ በመታወቂያ ዋስትና ከእስር እንዲፈቱ እንደተወሰነላቸው ጠበቃቸው ተናግሩ። በ2013 በተካሄደው 6ኛው ሀገር አቀፍ ምርጫ በባህርዳር ከተማ የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) ፓርቲን ወክለው ተወዳድረው የተመረጡት እና የህዝብ ተወካዮች ም/ቤት አባል የሆኑት ዶ/ር ደሳለኝ ጫኔ ጥር 22 ቀን 2016 ዓ/ም ምሽት በጸጥታ ኃይሎች ከቤታቸው ከተወሰዱ በኋላ ታስረው ቆይተዋል።…
አብዲ ኢሌ ከእስር ተፈቱ።

የቀድሞው የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አብዲ መሐመድ ኡመር (አብዲ ኢሌ) ከእስር መፈታታቸውን ጠበቃቸው ተናገሩ።

ከ6 ዓመት በፊት ነሐሴ 21/2010 ዓ.ም. አዲስ አበባ ውስጥ በቁጥጥር ስር ውለው አስካሁን በእስር ላይ የቆዩት አቶ አብዲ መሐመድ ኡመር ከእስር የተለቀቁት ዐቃቤ ሕግ ክሱን በማንሳቱ መሆኑን ጠበቃቸው ገልጸዋል።

ጠበቃ እና የሕግ አማካሪው እስክንድር ገዛኸኝ ፤ የቀድሞው የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳደር ክሳቸው ተነስቶ የተለቀቁት ዛሬ መጋቢት 5/2016 ዓ.ም. መሆኑን አመልክተዋል።

ከአቶ አብዲ በተጨማሪም በተመሳሳይ በእሳቸው የክስ መዝገብ ጉዳያቸው ሲታይ የነበሩ የሌሎችም ተከሳሾች ክስ ተቋርጦ መለቀቃቸውን ጠበቃው ተናግረዋል።

ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ ወደ ሥልጣን ከመምጣታቸው ከዓመታት በፊት ጀምሮ የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳደር ሆነው ሲመሩ የነበሩት አቶ አብዲ፣ በክልሉ ውስጥ ከተፈጸሙ በርካታ የሰብአዊ መብት ጥሰቶች፣ ግድያዎች እና የመንግሥት ሀብት ብክነት ጋር በተያያዘ ክስ ይቀርብባቸዋል።

በቀድሞው ርዕሰ መስተዳደር ላይ ከቀረቡባቸው ክሶች መካከልም በ2010 ሰኔ እና ሐምሌ ወራት ውስጥ “በሶማሌ ክልል የእርስ በርስ ግጭት እንዲፈጠር ለማድረግ በማሰብ ‘ሄጎ’ በሚል ስያሜ የሚታወቅ ወጣቶች ቡድን አደራጅተዋል” የሚል ይገኝበታል።

በወቅቱ ሶማሌ ክልል ጅግጅጋ ከተማ በተፈጸመ ጥቃት በርካታ ሰዎች መገደላቸው፣ ንብረት እና አብያተ ክርስቲያናት ላይ ጉዳት መድረሱ ይታወቃል።

ዐቃቤ ሕግም ባቀረበው የክስ ዝርዝር በተከሰተው ግጭት ምክንያት ፦
* 59 ሰዎች #መገደላቸውን
* ከ250 በላይ መቁሰላቸውን
* በመንግሥት፣ በግል እና በሃይማኖት ተቋማት ንብረት ላይ ውድመት መድረሱን ገልጾ ነበር።

ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የቢቢሲ አማርኛው አገልግሎት ነው።

ፎቶ፦ ፋይል

@tikvahethiopia