TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.1K photos
1.5K videos
211 files
4.09K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#EOTC

ቅዱስ ፓትርያርኩ " የሃይማኖት አባቶች ከፓለቲካ ገለልተኛ በመሆን ሁሉን በፍቅርና በእኩልነት ማቀራረብ ይገባቸዋል " ሲሉ በ11ኛ ዓመት በዓለ ሢመታቸው ተናገሩ።

ፓለቲከኞቾም ባልዋሉበት እና ባልተፈቀደላቸው ቦታ በቤተክርስቲያን ጉዳይ ጣልቃ ከመግባት እንዲቆጠቡ አሳስበዋል።

ቅዱስነታቸው " የዘመናችን ትውልድ ከተግባር ይልቅ አስመሳይ ሆኖ መታየትን ከቅድስና ይልቅ ነውረ ኃጢአትን፤ ከትሕትና ይልቅ ትዕቢትን የተለማመደ ለሃይማኖትም ሆነ ለማኅበረ ሰብ ጤና ያልተመቸ ትውልድ እንደሆነ በግልጽ ይታያል ሲሉ ተግሳጽ አሰምተዋል።

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቀነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት 11ኛ ዓመት በዓለ ሢመታቸውን አስመልክቶ ምን አሉ ?

- ያለንበት ዘመን ለእግዚአብሔር ክብርን የነሣ፤ ከፍቅርና ከአንድነት የራቀ ራስ ወዳድነትና በቃኝ አለማለትን የወረረው፤ በዘመን አመጣሽ ቴክኖሎጂ የተዋጠ ትውልድ የታየበት ዘመን ነው።

- የዘመናችን ትውልድ ከተግባር ይልቅ አስመሳይ ሆኖ መታየትን ከቅድስና ይልቅ ነውረ ኃጢአትን፤ ከትሕትና ይልቅ ትዕቢትን የተለማመደ ለሃይማኖትም ሆነ ለማኅበረሰብ ጤና ያልተመቸ ትውልድ እንደሆነ በግልጽ የሚታይ ነው፤ ይህን አደገኛ አዝማሚያ በማስተዋል ካልታረመ ሂዶ ሂዶ የእግዚአብሔርን ቁጣ ማስከተሉ አይቀርምና እንደ እግዚአብሔር ጥሪ ወደ እሱ ብንመለስ ይሻላል።

- እኛ የሃይማኖት አባቶችም አልጫ የሆነውን የዘመናችንን ትውልድ በትጋት አስተምረን በቈራጥነት ገሥጸንና መክረን ወደ እግዚአብሔር ካልመለስነው ከቁጣው አንድንም። ቅዱስ መጽሐፍ እንዳስተማረን አስተምረነው የማይመለስ ከሆነ ደሙ በራሱ ላይ ይሆናል! እኛ ባለማስተማራችን የሚጎዳ ትውልድ ካለ ግን እኛ የደሙ ተጠያቂዎች መሆናችንን በማያሻማ ሁኔታ ተገልጾአልና ነው፤ የእኛ ኃላፊነት እስከዚህ ድረስ ከባድ መሆኑን ባንዘነጋውም እንደ ዓለሙ በልዩ ልዩ ደካማ አስተሳሰቦችና ተግባራት እየተሰናከልን መሆናችን የአደባባይ ምሥጢር ከሆነ ውሎ አድሮአል።

- እኛ የሃይማኖት አባቶች ዓለም ሲሳሳት ከመገሠጽ ይልቅ አብሮ ማጨብጨብ ተለማምደናል፤ ባናጨበጭብም ዝምታን መርጠናል ነገር ግን ኃላፊነቱን የተረከብነው ጥፋት ሲፈጸም ዝም ብሎ ለማየት አልነበረም፤ ከዓለሙ ጋር አብሮ ለማጨብጨብ ወይም አድማቂ ለመሆንም አልነበረም፤ ከቅዱስ ወንጌሉ መሠረተ ሐሳብ ፍንክች ሳንል ፦
* የእውነት፥
* የፍትሕ የሰላም፥
* የፍቅር፥
* የዕርቅ የይቅርታ የአንድነት፥
* የስምምነት ጠበቃ መሆናችንን ማሳየት ነበረብን፣ ሰውን ሁሉ በእኩልነት በመቀበልና የሁሉም እኩል አባቶች መሆናችንን በተግባር ማስመስከር ይገባን ነበር፤ የተዛባውን በማረም ትውልዱን ለማዳን ያደረግነው ጥረት የሚያረካ እንዳልሆነ ታዛቢው ሁሉ አይቶብናል፡፡

- ለፈተና የተጋለጡ ልጆቻችን ሁሉ የዜግነት የሃይማኖትና የሰብአዊ መብታቸው እንዲከበር ሰላም ፍቅር፥ ፍትሕ አንድነት በሀገር እንዲነግሥ ሁሉም ድንበሩን ጠብቆ ሕዝቡን የሚያገለግልበት ዓመት እንዲሆን ከመቼውም ጊዜ በላይ በርትተን መሥራት አለብን። ይህንን ብናደርግ በእውነትም ወደ እግዚአብሔር ተመልሰናል ማለት ነው፤ እኛ ከተመለስን እሱም ወደ እኛ መመለሱ አይጠረጠርም፤ ስለዚህ አሁንም ወደእሱ እንመለስ፡፡

(ሙሉ መልዕክታቸው ከላይ ተያይዟል)

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ትግራይ " ' ያንቺ እቃ ብቻዬን ጠላ እየሸጥኩ ያሳደኳቸውን 2 ወንድ ልጆቼን ይመልስልኛል ወይ ? ' ነው ያለችኝ ! " - ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ በታሪካዊቷ ዓድዋ ከተማ በነበረው የዓድዋ ድል በዓል  ላይ እምባ እየተናነቃቸው 😭 ንግግር አድርገው ነበር። እሳቸው በእንባ ንግግር ሲያደርጉ የበዓሉ ታዳሚ ህዝብ ከፍተኛ የሀዘን ስሜቱ ከፊቱ ይነበብ እንደነበር በስፍራው…
#ኢትዮጵያ

" የአንድ ሀገር ልጆች እየተገዳደሉ ናቸው !! "

ፕሬዜዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ በዓድዋ በዓል ላይ የተናገሩት ፦

" ከአንዱ ሳናገገም ሌሎች ችግሮችም በሀገራችን አሉ።

በመካከላችን ድልድይ ሳይሆን ግንብ የመገንባት አካሄድም አለ።

ዛሬ በሌሎች ክልሎች ንፁሃን እየሞቱ ናቸው።

በአማራ ክልል እንደዚሁ ከውጭ የመጣን ጠላት ሳይሆን የአንድ ሀገር ልጆች እየተገዳደሉ ናቸው። ህዝቡም በከፍተኛ አደጋ ላይ እየተጣለ ነው።

በሌሎችም እንደዚሁ ኦሮሚያም የሚሞተው ንፁህ ሰው መሞት የሌለበት ነው።

ይሄ ሁላችንም አያገባኝም ሳይሆን ፤ እኔ ላይ አይደርስም ሳይሆን ፤ የት ይደርሳሉም ሳይሆን ሁላችንም ነቅተን ይሄን ያለንን ጀግኖች አባቶቻችን እናቶቻችን የሰጡንን ነፃነት ፣ አንገታችንን ከፍ እንድናደርግ የረዳንን ባንድነት የመስራትን እንደገና ማደስ ያስፈልጋል፤ ይህ ከታሪካችን ጋር መታረቅ ማለት ነው።

ይሄን አደራ ማለት እፈልጋለሁ። "

@tikvahethiopia
ወጋገን ባንክ !

በማንኛውም ጊዜ እና ቦታ በሞባይል ስልክዎ ወጋገን ሞባይል መተግበሪያን ከፕለይስቶር ወይም ከአፕስቶር በማውረድ ምቾትዎ ተጠብቆ ሂሳብዎን ያንቀሳቅሱ፡፡ አገልግሎቱን ለማግኘት የወጋገን ባንክ ሂሳብ በመክፈት የወጋገን የሞባይል ባንክ አገልግሎት *866# ይመዝገቡ፡፡

ከዚያም ቀጣዩን ሂደት ይከተሉ፤
(ሀ) መተግበሪያውን ከአፕስቶር ወይም ጎግል ፕሌይስቶር በማውረድ ስልክዎ ላይ ይጫኑ፤
(ለ) ወደ *866# በመደወል ተራ ቁጥር 8ኛ ላይ የሚገኘውን “Activate Your Mobile Application” የሚለውን ይምረጡ፤
(ሐ) በአጭር ፅሁፍ መልዕክት አገልግሎቱን ማስጀመሪያ የአንድ ጊዜ የይለፍ ቃል (Activation Code) ሲደርስዎት መተግበሪያው ላይ ይህንኑ ሚስጥራዊ ቁጥር ያስገቡ፤
(መ) የሚስጥር ቁጥር በመቀየር አገልግሎቱን መጠቀም መጀመር ይችላሉ፡፡
ለተጨማሪ መረጃ በ866 ነፃ የስልክ መስመር ወደ ደንበኞች ግንኙነት ማዕከል ይደውሉ፣ ይስተናገዱ፡፡

Download now:
Android:https://play.google.com/store/apps/details?id=com.act.wegagen&hl
IOS:https://apps.apple.com/in/app/wegagen-mobile/id6472656143
TIKVAH-ETHIOPIA
#ኢትዮጵያ ሰለሞን ባረጋ ለኢትዮጵያ የነሃስ ሜዳሊያ አምጥቷል። በግላስኮ ዓለም አትሌቲክስ የቤት ውስጥ ሻምፒዮና በወንዶች 3 ሺህ ሜትር ኢትዮጵያ በአትሌት ሰለሞን ባረጋ አማካኝነት የነሃስ ሜዳሊያ ማግኘት ችላለች። ጌትነት ዋለ 4ኛ ወጥቷል። ኢትዮጵያ በዚህ ርቀት በዓለም የቤት ውስጥ ሻምፒዮና ላይ የወርቅ ሜዳሊያ ሳታሸንፍ ስትቀር ከ3 ተከታታይ ውድድሮች በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው። ሰለሞን ባረጋ…
#ኢትዮጵያ

ኢትዮጵያ ከአፍሪካ 1ኛ ሆና አጠናቀቀች።

በዓለም አትሌቲክስ የቤት ውስጥ ሻምፒዮና ኢትዮጵያ ከአፍሪካ 1ኛ ከዓለም ደግሞ 5 በመሆን አጠናቃለች።

ከማርች 1-3/2024 በእንግሊዝ ግላስጎ ሲካሄድ የ19ኛው የዓለም የቤት ዉስጥ ሲካሄድ ነበር። በሻምፒዮናው ከ130 በላይ አገሮች የተውጣጡ ከ650 በላይ አትሌቶቸ ተሳትፈዋል።

ሀገራችን ኢትዮጵያ በ800 ሜትር፣ በ1500 ሜትር እና በ3000 ሜትር በሴትና በወንድ  በአጠቃላይ በ8 ሴቶች እና በ5 ወንዶች በድምሩ በ13 አትሌቶች ተሳትፋለች።

በዚህም #በሴቶች 800 ሜትር ፅጌ ዱጉማ እና በሴቶች 1500 ሜትር ፍሬወይኒ ሀይሉ #የወርቅ፣ በሴቶች 3000 ሜትር ጉዳፍ ፀጋይ የብር እንዲሁም #በወንዶች 3000 ሜትር ሰለሞን ባረጋ የነሃስ ሜዳሊያ ለኢትዮጵያ አስገኝተዋል።

ይህን ተከትሎ ኢትዮጵያ በሁለት ወርቅ አንድ ነሀስ በአንድ ብር በአጠቃላይ በአራት ሜዳሊያዎች በሜዳልያ ሰንጠረዡ   ከአፍሪካ 1ኛ  ከዓለም 5ኛ ደረጃን በመያዝ ጨርሳለች።

ምንጭ፦ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን

@tikvahethiopia
#ቅሬታ

የፓስፖርት ጉዳይ ...

ከፓስፖርት አሰጣጥ ጋር በተያያዘ ቅሬታ አለን ያሉ ወገኖች አሰፈላጊው ማስተካከያ እንዲደረግ አሳሰቡ።

" የተሰራ ፓስፖርት ለመስጠት ህዝቡ እጅግ በጣም ዘግናኝ በሆነ መልኩ እየተንገላታ ይገኛል። " ያሉት ለቲክቫህ መልዕክታቸውን ያደረሱ ወገኖች ፤ በቀን የሚሰጠው ፓስፖርት ውስን ነው ብለዋል።

" በቀኑ ስለማይሰጥም ባስቀመጡት ቀን ተገልጋዩ እየተመላለሰ መከራ እየበላ ነው። " ሲሉ ሁኔታውን ገልጸውታል።

በተለይ ጎተራ አካባቢ ሌሊት ወረፋ ለመያዝ ብር  የሚጠይቁ እንዳሉ ፤ አንዳንዱ ከፍሎ ወረፋ እንደሚይዝ የሌለው ደግሞ ሌሊት ሂዶ ከገባ በኋላ ሰልፋን ይበትኑና ቀኑን ሙሉ በህዝብ ሲጫወቱ ውለው 10 ሰዓት ላይ በዱላ ደብድበው እንደሚያስወጡ በምሬት ገልጸዋል።

" በቀጣዩ ሳምንትም እንደዛው። " ሲሉ አክለዋል።

" የብዙ ሰው ቪዛ እየተቃጠለበት ለብዙ ወጪ እየተዳረገ " መሆኑን የሚገልፁት እነዚህ ወገኖች " በየወረዳው ቢበትኑ እንዲሁ። በፊደል ተራ በተለቀቀበት ቀን ቢሰጡ/they mix it/  ጥሩ ነው። የህዝብ እንግልት ግድ የሚሰጠው ካለ መፍትሄ ይፈልግ !! " ሲሉ አሳስበዋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ቅሬታ የፓስፖርት ጉዳይ ... ከፓስፖርት አሰጣጥ ጋር በተያያዘ ቅሬታ አለን ያሉ ወገኖች አሰፈላጊው ማስተካከያ እንዲደረግ አሳሰቡ። " የተሰራ ፓስፖርት ለመስጠት ህዝቡ እጅግ በጣም ዘግናኝ በሆነ መልኩ እየተንገላታ ይገኛል። " ያሉት ለቲክቫህ መልዕክታቸውን ያደረሱ ወገኖች ፤ በቀን የሚሰጠው ፓስፖርት ውስን ነው ብለዋል። " በቀኑ ስለማይሰጥም ባስቀመጡት ቀን ተገልጋዩ እየተመላለሰ መከራ እየበላ…
#ፓስፖርት

ፓስፖርት ፈልገው/ በሥራ ምክንያት ኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ጎራ ካሉ ረዥም ሰልፍ እና መጨናነቅ ማየት የተለመደ ነው።

የሰልፍ አሰላፊዎች ዱላም ሊያጋጥም ይችላል።

ወጣት፣ሴት፣ወንድ፣ልጅ ያዘሉ እናቶች እንዲሁም " ፓስፖርት ፈልገው ነው ? " እያሉ እግር በእግር የሚከተሉ ሕገወጥ ደላሎችም በአካባቢው ውር ውር ይላሉ።

አገልግሎቱ 24 ሰዓት የፓስፖርት ህትመትና በበይነ መረብ ምዝገባ አሠራር ዘርግቻለሁ ቢልም አሁንም በርካታ ተገልጋዮችን አገልግሎቱ ደጃፍ ላይ መመልከት አልቀረም።

ተገልጋዮች ዐሻራ ለመስጠት እና ፎቶ ለመነሳት በመ/ቤቱ መገኘት ግዴታቸው በመሆኑ ከተለያዩ አካባቢዎች መጥተው በወረፋው ምክንያት ላልተፈለገ እንግልት ይዳረጋሉ።

እንግልቱ ከሌሊቱ 10 ሰዓት ከእንቅልፍ ተነስቶ ረዥም ሰልፍ ከመሰለፍ ይጀምራል።

በሌቦች መዘረፍም የሚያጋጥም ክስተት መሆኑን ተገልጋዮች በምሬት ይናገራሉ።

ለአላስፈላጊ እንግልት እና ወጪ ተዳርገናል የሚሉ ተገልጋዮች ሃሳባቸውን አዲስ ፓስፖርት ለማውጣት በበይነ መረብ አማካኝነት ከተመዘገቡ ወራት እንዳለፋቸው ይገልጻሉ።

ተገልጋዮቹ አገልግሎቱ አካባቢ ወረፋ ለመያዝ ስንሞክር " እኔ ቅድሚያ ወረፋ ልያዝላችሁ ክፈሉኝ " በሚሉ ደላሎች እንዋከባለን ይላሉ።

እነሱ እንደሚሉት የመሥሪያ ቤቱን ሰልፍ አሰላፊዎች ወከባና ዱላ አልፎ ውስጥ መግባት መቻል መታደል ነው።

ተገልጋዮቹ በሌሊት ለመነሳት ሲሉ በአካባቢው ለአልጋ ኪራይ ከፍለው እንደሚያድሩና ለአላስፈላጊ ወጪም እንደሚዳረጉም ይገልጻሉ።

ሰልፉ ረዝሞ ወረፋ ሳይደርሳቸው ከቀረም ቅጣት እንደማይቀርላቸው ይናገራሉ።

በርካታ አገልግሎት ፈላጊ ሕዝብ በተገቢው መንገድ ከማስተናገድ ይልቅ በዱላ በመደብደብ ሥርዓት ለማስያዝ ሲሞከር ይታያል። ወደ መግቢያ በሩ ተጠግቶ መረጃ ማግኘት የማይታሰብ ነው።

የፓስፖርት አሰጣጥ ሂደቱ ተስተካክሏል ይባል እንጂ አሁንም ችግሮቹ እንደነበሩ ናቸው ይላሉ ተገልጋዮች።

የፓስፖርት አሰጣጥ ሂደቱ ሳይዘምን እንደዘመነ አድርጎ ማስተዋወቅም ፍጹም ተገቢነት እንደሌለውና ሕዝብ በለውጥ እንዳያምን እንደሚያደርግም ያስገነዝባሉ።

ሰሞኑን የፓስፖርት አሰጣጥ ሂደቱን ለመመልከት በመ/ቤቱ የተገኙት የኢፕድ ጋዜጠኞች መረጃ ለመሰብሰብ ያደረጉት ሙከራ በፖሊሶች ክልከላ ተደርጎበታል።

የተቋሙ ኮሙኒኬሽን ዳሬክተር ወ/ሮ ማስተዋል ገዳ ምን ምላሽ ሰጡ ?

- ተገልጋዮች ወደ ተቋሙ በሚመጡበት ወቅት በክብር መስተናገድ እንዳለባቸው እናውቃለን። ተገልጋዮችን በአግባቡ ባለማስተናገድ የዲሲፕሊን ችግር ያለባቸው ሠራተኞች ላይ እርምጃ እየተወሰደ ነው።

- ተገልጋዮች ቅሬታ ሲኖራቸው ቅሬታ ለተቋሙ ማቅረብ አለባቸው።

- አዲስ ፓስፖርት ፈልገው በድረ ገጽ ሲያመለክቱ ፎቶግራፍ የሚነሱበትን እና ዐሻራ የሚሰጡበትን ቀንና ሰዓት የሚያሳውቅ በመሆኑ ተገልጋዮች በሰዓቱ ብቻ ቢመጡ ሰልፉ ሊቀንስ ይችላል። የተቀጠሩ ተገልጋዮች ሳይስተናገዱ አይቀሩም።

- በአካባቢው መጨናነቅ የሚፈጠረው ቀጠሮ ባላቸው ተገልጋዮች ብቻ ሳይሆን " ፓስፖርት ዘግይቶብናል "  ብለው ለመጠየቅ በሚመጡ ተገልጋዮች ነው። አንድ ጉዳይ ለመጨረስ ከአንድ በላይ ሰው ስለሚመጣ ነው።

- የሌሊት ሰልፉ ከአገልግሎቱ እውቅና ውጪ ነው። ለሰልፉ ሰዓት የመገደቡን ጉዳይ በቀጣይ በጋራ የሚታይ ነገር ነው።

- ተገልጋዮች ለአስቸኳይ ፓስፖርት በሕገ ወጥ ደላሎች በኩል ለማስጨረስ ከመሞከር ይልቅ እራሳቸው በጥቂት ቀናት መጨረስ ይችላሉ።

ያንብቡ https://telegra.ph/EPA-03-04

ይህ መረጃ የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ነው።

ፎቶ፦ Tikvah Family

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ፓስፖርት ፓስፖርት ፈልገው/ በሥራ ምክንያት ኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ጎራ ካሉ ረዥም ሰልፍ እና መጨናነቅ ማየት የተለመደ ነው። የሰልፍ አሰላፊዎች ዱላም ሊያጋጥም ይችላል። ወጣት፣ሴት፣ወንድ፣ልጅ ያዘሉ እናቶች እንዲሁም " ፓስፖርት ፈልገው ነው ? " እያሉ እግር በእግር የሚከተሉ ሕገወጥ ደላሎችም በአካባቢው ውር ውር ይላሉ። አገልግሎቱ 24 ሰዓት የፓስፖርት ህትመትና በበይነ መረብ ምዝገባ…
#ፓስፖርት

አዳማ ላይም ፖስፖርት ለመውሰድ አስቸጋሪ መሆኑን ተገልጋዮች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በላኩት ቅሬታ አመላክተዋል።

" ሰው ከመብዛቱ የተነሳ ሰው በየቀኑ ፓስፖርቱን ሳይወስድ ሳምንት ተመለሱ ይባላል። " ያሉት ቅሬታ አቅራቢዎች " ፓስፖርት ለመስጠት የሚጠሩት በአልፋቤት ብሆንም Order የጠበቃ አይደለም። " ብለዋል።

" አንዱ የጠረውን በድጋሚ ሌላም አንስቶ የመጥራት ክስተት እንዳለ " አመላክተዋል።

ከዚሁ ጋር በተያያዘ አንድ ተገልጋይ የቲክቫህ ቤተሰብ አባል ይህንን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አጋርቷል።

N ከአዳማ ፦

" አዲስ ፓስፖርትን ለመውሰድ ያለው እንግልት አለ።

አዲስ ፓስፖርት ካመለከትኩ አሁን ላይ 11 ወራት ሆኖኛል፡፡

በየካቲት ወር 7ኛው (February 15) ቀን በቴሌግራም አካውንት ላይ አዲስ ፓስፖርት የመጣላቸው ስም ዝርዝር ውስጥ ስሜን ስላገኘሁት ልቀበል አውራ ጎዳና በሚገኘው አዳማ ቢሯቸው ሄድኩኝ፡፡

ሆኖም ግን እዛ ስድርስ የመ/ቤቱ ጥበቃዎች በዱላ ጥያቄ ለመጠየቅ ግራ ገብቶት ያለውን ሰው መምታቱትን ተያይዘውታል፡፡

ከዛም ብቸኛ የመረጃ ምንጭ የሆኑት እነርሱ (ጥበቃዎቹ) ስለሆኑ ዱላው ሳያገኘኝ ጥያቄዬን ለመጠየቅ ተጋፍቼ ሳበቃ የአንተ ዛሬ አይደለም የሚቀጥለው ሳምንተ ከሰኞ በኃላ ና አሉኝ የሄድኩት ማክሰኞ እለት ነበር (February 19)፡፡

ወደ መስሪያ ቤቱ የሚያስገባው በር ሁለት ሰው እንኩዋን የማያስገባ ነው እናም መረጃ ለማግኘት ወደ ውስጥ መግባት የማይታሰብ ነው፡፡

ቀጥሎም አርብ እለት (February 23) ሄድኩ እንደምንም ተጋፍቼ ስጠይቅ አንድ ጊዜ ረቡህ አንዴ ሃሙስ አለኝ ጥበቃው፡፡

በቀጣይ ስለተጠራጠርኩ ቀደም ብዬ ማክሰኞ (February 26) ሄድኩ ከዛም በዛ ቀን የነበረው ጥበቃ አርብ እለት ነው አለኝ፡፡አርብ ስሄድ(March 01) ስሄድ ሰልፍ ያዝ ተባልኩ፡፡

ሰልፍ ከያዝኩ በኃላ ተሰላፊዎቹን ስጠይቅ የአንተ እኮ ሀሙስ ነበር አሉኝ(February 29)፡፡

መስሪያ ቤቱ ቅጥር ግቢ ላይ ያለ ማስታወቂያ አሳኙኝ ማስታወቂያውን አነበብኩት የተለጠፈው February 23 ነው፡፡ እናም ጥበቃዎች ቢያንስ ተገልጋይ ማስታወቂያ እንዲያይ ቢያደርጉ የሰውን እንግልት ይቀንሳሉ፡፡

እኔ ቤተሰብ አዳማ ስለሆነ መመላለስ እችላለሁ ነገር ግን ከሩቅ ቦታ ለሚመጡ ምን ያህል ከባድ ነው በዚ ላይ የጥበቃዎቹ ዱላ ተጨምሮበት ?

አመሰግናለሁ፡፡ "

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ፓስፖርት ፓስፖርት ፈልገው/ በሥራ ምክንያት ኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ጎራ ካሉ ረዥም ሰልፍ እና መጨናነቅ ማየት የተለመደ ነው። የሰልፍ አሰላፊዎች ዱላም ሊያጋጥም ይችላል። ወጣት፣ሴት፣ወንድ፣ልጅ ያዘሉ እናቶች እንዲሁም " ፓስፖርት ፈልገው ነው ? " እያሉ እግር በእግር የሚከተሉ ሕገወጥ ደላሎችም በአካባቢው ውር ውር ይላሉ። አገልግሎቱ 24 ሰዓት የፓስፖርት ህትመትና በበይነ መረብ ምዝገባ…
#AddisAbaba

4 ኪሎ አካባቢ የሚገኙ ሁለት የእግረኛ መሸጋገሪያ የብረት ድልድዮች የማንሳት ስራ እየተከናወነ ነው።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ በከተማዋ የተለያዩ አካባቢዎች ዓለም አቀፍ የስማርት ሲቲ ስታንደሰርድን የሚያሟሉ አዳዲስ አራት የመንገድ ኮሪደሮች ግንባታ እንዲከናወን ውሳኔ ማሳለፉን ተከትሎ 4 ኪሎ አካባቢ የሚገኙትን ሁለት የእግኛ መሸጋገሪያ የብረት ድልድዮች የማንሳት ስራ እየተከናወነ እንደሚገኝ የአዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ባለሥልጣን አሳውቋል።

" 4 ኪሎ ዳግማዊ ምኒልክ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት አጠገብ የሚገኘው የእግረኞች መሸጋገሪያ ድልድይ ጉዳት ደርሶበታል " በሚል የማህበራዊ ትስስር ገፆች ላይ የተላለፈው ዘገባ የተሳሳተ መሆኑ ተገልጿል።

የብረት ድልድዮችን የማንሳት ስራ በሁለት ቀናት ውስጥ የሚጠናቀቅ ሲሆን፣  የትራፊክ መጨናነቅ እንዳይፈጠር አሽከርካሪዎች አማራጭ መንገዶችን እንዲጠቀሙ መልዕክት አስተላልፏል።

@tikvahethiopia