TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.2K photos
1.5K videos
211 files
4.1K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#እንድታውቁት

የሞተር እንቅስቃሴ ላይ ክልከላ ተጣለ።

በአዲስ አበባ የሚገኙ የሞተር ብስክሌተኞች በሙሉ ከአርብ የካቲት 08/2016 ዓ.ም ከጠዋቱ 12:00 ጀምሮ እስከ ሰኞ የካቲት 11/2016 ዓ.ም እስከ ጠዋት 2:00 ሰአት ድረስ በከተማዋ ውስጥ ሞተር ብስክሌት በፍጹም ማሽከርከር እንደማይችሉ የትራንስፖርት ቢሮ ክልከላ ጥሏል።

ክልከላው የፀጥታ እና የትራፊክ ቁጥጥር የሚሰሩ አካላትን አይመለከትም ተብሏል።

" የሞተር ብስክሌት ባለንብረቶችም ሆኑ አሽከርካሪዎች እስከ ተጠቀሰው ቀን ድረስ በትዕግስት እንዲጠብቁ " ያለው ቢሮው " ይህንን መልእክት በሚተላለፉ አካላት ላይ ጥብቅ እርምጃ ይወሰዳል " ሲል አስጠንቅቋል።

@tikvahethiopia
8118 ይደውሉ!

የግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ ከክፍያ ነፃ የጥሪ ማዕከል ባንኩን የሚመለከቱ ማንኛውንም ጥያቄዎች በተለያዩ አማራጮች ለመመለስ ዝግጁ ሆነው ይጠብቅዎታል፡፡

በሚቀርብዎ አማራጮች ያግኙን፡ https://bit.ly/3TkrrXD

ግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ
ለጋራ ስኬታችን!

#GlobalBankEthiopia #OurSharedSuccess #BankInEthiopia #GBE
ቆይ አንዴ.....

አዲሱን እለታዊ ኮምቦ ጥቅላችንን ሞክራቹታል?

ለመግዛት *777*3# እንደውል::

የሳፋሪኮም ኢትዮጵያን ትክክለኛ መረጃዎችን በቀላሉ ለማግኘት ቀጥሎ በሚገኙት ይፋዊ የማህበራዊ ሚዲያዎች እንዲከታተሉ እንጋብዛለን።

👉Facebook: https://www.facebook.com/SafaricomET
👉Telegram: https://t.iss.one/Safaricom_Ethiopia_PLC
👉LinkedIn: https://www.linkedin.com/company/safaricom-ethiopia
👉Twitter:
https://x.com/SafaricomET?t=y2XAHAhPNvFeZqXa2YE6aQ&s=08
👉 Instagram: https://www.instagram.com/safaricomet?igsh=MWJtcjJrMzNhMzVsNg==
YouTube: https://youtube.com/@safaricomethiopia2751?si=w2o8uz61oHeZM9gm
TIKVAH-ETHIOPIA
" ከፍተኛ ጥረት እየተደረገ ቢሆንም ውጤት አልተገኘም " ደቡብ ወሎ ዞን ፣ ደላንታ ወረዳ የኦፓል ማዕድን በማውጣት ላይ ሳሉ ዋሻ የተደረመሰባቸውን በርካታ ሰዎች ለማውጣት የሚደረገው ጥረት 4 ቀኑን እንደያዘ ተነግሯል። የአካባቢው ባለሥልጣናት እና የከበረ ማዕድን አውጪዎች ማኅበር በሰጡት ቃል  ፤ በቁጥር ከ8 እስከ 30 የሚገመቱትን ሰዎች ለማውጣት የአካባቢው ማኅበረሰብ ጥረት እያደረገ ቢሆንም እስካሁን…
“ በተጨማሪ ማሽነሪ/ቴክኖሎጂ የታገዘ ሥራ ለማከናወን አልተቻለም ” - የደቡብ ወሎ ዞን ኮሚዩኒኬሽን

በአማራ ክልል ደቡብ ወሎ ዞን ደላንታ ወረዳ "018 አለኋት" ቀበሌ በተለምዶ ቆቅ ውኃ እየተባለ በሚጠራ አካባቢ ጥር 30 ቀን 2016 ዓ/ም ሌሊት የኦፓል ማዕድን በቁፋሮ ለማውጣት ሲሞክሩ የነበሩ ከ20 በላይ ወጣቶች የቆፈሩት አለት በመናዱ ያሉበትን አልታወቀም ስለተባሉት ወጣቶች ሁኔታ ቲክቫህ ኢትዮጵያ የዞኑን ኮሚዩኒኬሽን ዛሬ (ጥር 6 ቀን 2016 ዓ/ም) ጠይቋል።

የዞኑ ኮሚዩኒኬሽን ኃላፊ አቶ ኢያሱ ዮሐንስ በሰጡት ቃል፣ “በተጨማሪ ማሽነሪ/ቴክኖሎጂ የታገዘ ሥራ ለማከናወን አልተቻለም። ቁፋሮው ግን አሁንም እንደቀጠለ ነው” ብለዋል።

ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ተሁኖ በትብብር ቁፋሮ እየተደረገ መሆኑን ገልጸው፣ እካሁን (ይህ ዘገባ እስከተጠናቀረበት ጊዜ ድረስ) “ከ50 ሜትር በላይ ቁፋሮ ተከናውኗል” ሲሉ ተናግረዋል።

ቁጥሩ በማኀበራዊ ሚዲያዎች ከፍና ዝቅ እያለ ነው፣ በትክክል ስንት ወጣቶች ናቸው የጠፉት? ተብሎ ለቀረበላቸው ጥያቄም፣ “ቁጥራቸው ከ20 ያላነሰ እንደሆነ ነው ያሉን መረጃዎች የሚያመላክቱት። አካባቢው ላይ ወጣቶቹ ስለሚታወቁ እንደዛ የሚል ነው የተሰጠን መረጃ” ብለዋል።

እስካሁን ምን የተገኘ ፍንጭ አለ? ተብሎ ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ለቀረበላቸው ጥያቄ አቶ ኢያሱ፣ “የተገኘ ነገር የለም። በመግቢያነት የሚጠቀሙበትን የዋሻውን ክፍል መሠረት አድርገው ነው የአካባቢው አስተዳደሮች ቁፋሮ ለማድረግ እየሞከሩ ያሉት” የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።

አክለውም፣ “ተስፋ ተደርጎም እየተሰራ ያለው ከሁለትና ከሦስት ዓመታት በፊት ተመሳሳይ ችግር አጋጥሞ ከ11 ቀናት ቆይታ በኋላ አራት ወጣቶች በሕይወት ተገኝተዋል። አሁንም እንደዚህ አይነት ዕድል ቢገኝ ተብሎ ነው እየተሰራ ያለው። ጥረቱ አሁንም ተጠናክሮ ቀጥሏል” ነው ያሉት።

ከሦስት ዓመታት በፊት በነቀረው ክስተት ጠፍተው የነበሩ ወጣቶች በሕይወት ሊገኙ የቻሉት በምን ሁኔታ እንነበር ማብራሪያ እንዲሰጡ ተጠይቀው በሰጡት ምላሽም፣ “ተመሳሳይ ነው፣ ሲቆፍሩ ዋሻው ተንዶ ነው እነዛም አደጋው አጋጥሟቸው የነበረው” ብለው፣ “ሁኔታው ከተሰማ በኋላ የአካባቢው ማኀበረሰብ እንዳሁኑ የቁፋሮ ስራ በማከናወን ነው ሕይወታቸውን ለማትረፍ የሞከረው” ሲሉ አውስተዋል።

አክለውም፣ “ሕይወታቸውንም ያጡ ወጣቶች ነበሩ። ነገር ግን በጊዜው ወደ አራት የሚደርሱ ወጣቶች ሕይወት ማግኘት ተችሎ ነበር” ሲሉ በአሁኑ ክስተት የጠፉ ወጣቶች ይገኛሉ የሚል ተስፋ ሰጪ ያሉትን የቀድሞ ክስተት አስታውሰዋል።

ዘገባውን የላከው የአ/አ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ሲሆን፣ ሁኔታውን በመከታተል የምናሳውቅ ይሆናል።

@tikvahethiopia
ፎቶ ፦ በአዲስ አበባ ከተማ ፤ አጎና (የጎተራ ኮንዶሚኒየም መግቢያ) በሚገኝ ህንፃ ላይ ምሽቱን የእሳት አደጋ መነሳቱን የአካባቢው የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት ጠቁመዋል።

የእሳት ደጋው ከተነሳ ከአንድ ሰዓት በላይ እንዳለፈውና የእሳት አደጋ ተቆጣጣሪዎች እሳቱ ተጨማሪ ጥፋት እንዳያደርስ በቁጥጥር ስር ለማዋል ርብርብ እያደረጉ ይገኛሉ።

እስካሁን በህንፃውን አንደኛው ጎን ውስጥ የነበሩ ንብረቶች እየወደሙ ይገኛሉ።

ተጨማሪ መረጃዎችን ተከታትለን እናሳውቃለን።

#TikvahFamilyAA

@tikvahethiopia
" በተለያየ ሶሻል ሚዲያ ' አስቸኳይ ፓስፖርት እናወጣለን ' ከሚሉ ህገወጦች ራሳችሁን ጠብቁ ፤ ... በኦንላይ ምንም አይነት አስቸኳይ ፓስፖርት አይሰጥም " - የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት

የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት አስቸኳይ ፓስፖርት ለማውጣት ምን ያስፈልጋል / ለምን ምን ጉዳዮች ይሰጣል አለ ?

- የህክምና ማስረጃ
- የትምህርት ዕድል ማስረጃ
- ለመንግስት ስራ ጉዳይ ለስብሰባ፣ ለወርክሾኘ
- ጊዜው ያላለፈ የመኖሪያ ፈቃድ ያለው ለባል/ለሚስት/ለልጅ
- ለአስመጭና ላኪ /ከፍተኛ ግብር ከፋይ/
- ፓስፖርት ላይ ጊዜው ያላለፈ የተመታ ቪዛ ካለ /ለማሳደስ/

ከእነዚህ ሰነዶች በአንዱ ዋናው ቢሮ በአካል በመገኘት ብቻ የተሟላ ማስረጃ በመያዝ በአስቸኳይ መስተናገድ ይቻላል ሲል አሳውቋል።

ክፍያ የሚከፈለው በቢሮ ብቻ መሆኑን አስገንዝቧል።

ዜጎች በተለያየ ሶሻል ሚዲያ " አስቸኳይ ፓስፖርት እናወጣለን " ከሚሉ ህገወጦች ራሳቸውን እንዲጠብቁ አሳስቧል።

በኦን ላይን ምንም አይነት አስቸኳይ ፓስፖርት የማይሰጥ መሆኑንም ገልጾ ዜጎች ጥንቃቄ እንዲያደርጉ ብሏል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
የመውጫ ፈተና ከየካቲት 6 እስከ የካቲት 11 ቀን 2016 ድረስ ይሰጣል። የ2016 ዓ/ም የአመቱ አጋማሽ የሀገር አቀፍ የመውጫ ፈተና ከነገ ረቡዕ የካቲት 6 ጀምሮ መሰጠት ይጀምራል። ቲክቫህ ኢትዮጵያ ፤ ዩኒቨርሲቲዎች ከትምህርት ሚኒስቴር ተልኮልናል ብለው ያጋሩትን የተሻሻለ የፈተና መርሃ ግብር የተመለከተ ሲሆን በዚህ መርሀ ግብር ሀገር አቀፉ የመውጫ ፈተና እስካ የካቲት 11 /2016 ዓ/ም ድረስ ይሰጣል።…
የመውጫ ፈተና ዛሬ በጤና ትምህርት ፕሮግራሞች  መሰጠት ጀምሯል።

ትምህርት ሚኒስቴር የሁለተኛው ዙር የመውጫ ፈተና ከዛሬ ካቲት 6/2016 ዓ.ም ጀምሮ መሰጠት እንደተጀመረ ገልጿል።

በዛሬው እለት በጤና ፕሮግራሞች በተጀመረው ፈተና ጠዋት 15,440 ተማሪዎች በ23 የጤና ፕሮግራሞች የተፈተኑ ሲሆን ከሰዓት 14,807 ተማሪዎች በ13 ፕሮግራሞች ተፈትነዋል።

ፈተናው በሁሉም የፈተና ማዕከላት ከተማ እየተሰጠ ሲሆን የመውጫ ፈተና አሰጣጡ ፍትሃዊነትና ተአማኒነት ለማስጠበቅና አስፈላጊውን ድጋፍ ለማድረግ የተመደቡ ታዛቢዎች በየተመደቡበት ተቋማት በመገኘት ስራ መጀመራቸውን ሚኒስቴሩ አሳውቋል።

የሁለተኛ ዙር ፈተናው ፦
- በ47 የመንግስት ተቋማት
- በ84 የፈተና ማዕከላት የሚሰጥ ሲሆን በመንግስትና ግል ተቋማት ለመጀመሪያ ጊዜ የሚፈተኑትን ጨምሮ 149,145  ተፈታኞች በ204 የፈተና ፕሮግራሞች ይፈተናሉ።

ፈተናው የካቲት 11/2016 ዓ.ም ይጠናቀቃል ሲል ትምህርት ሚኒስቴር አመላክቷል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update

በአዱስ አበባ አጎና የተነሳው እሳት መጀመሪያ ላይ ከነበረበት የወደ መጥፋት ደረጃ ቢቀንስም እሳቱ ሙሉ በሙሉ አልጠፋም።

በስፍራው የአዲስ አበባ እሳት አደጋ ተቆጣጣሪዎች እና ተሽከርካሪዎች የሚገኙ ሲሆን የፌዴራል ፖሊስም አጋዥ ተሽከርካሪዎችን ወደ ስፍራው በመላክ እሳቱን ሙሉ በሙሉ ለማጥፋት ርብርብ እየተደረገ ይገኛል።

የእሳት አደጋ በተነሳበት ህንፃ ላይ የተለያዩ አገልግሎት ሰጪ ድርጅቶች የሚገኙበት ነው።

የአደጋው መንስኤ እና ሰው ላይ የደረሰ ጉዳት ይኖር እንደሆነ እስካሁን በውል አልታወቀም።

መረጃውን የላኩት በስፍራው የሚገኙ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት ናቸው።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#መርዓዊ

" መከላከያ ሠራዊት ራሱን ነው የተከላከለው ፤ ... የመከላከያ ኃይል የትኛውንም ዐይነት ሲቪል ዒላማ አላደረግም " - መንግሥት

መንግሥት በመርዓዊ የሰላማዊ ሰዎች ግድያ ጉዳይ ምን አለ ?

የኢትዮጵያ መንግሥት በመርዓዊ ከተማ ተፈጽሟል የተባለውን የ45 (ቁጥሩ ከዚህም ከፍ ይላል) ሰላማዊ ሰዎች ግድያ አስተባብሏል።

የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ቢያንስ 45 ሲቪሎች በመንግሥት የፀጥታ ኃይል መገደላቸውን ፤  " የፋኖ አባላት ናቸው " በሚል ተጠርጥረው የተያዙ እና ለጊዜው ብዛታቸውን ለማረጋገጥ ያልተቻለ ሰዎች በተመሳሳይ በመንግሥት የጸጥታ ኃይሎች ከሕግ ውጭ መገደላቸውን ማሳወቁ ይታወሳል።

የንፁሃን ግድያን እንዲሁም የኢሰመኮን ሪፖርት በተመለከተ ለዶቼ ቨለ ሬድዮ ቃላቸውን የሰጡት የመንግሥት ኮሚኒኬሽን ሚኒስትር ዶ/ር ለገሰ ቱሉ ድርጊቱን አስተባብለዋል።

ዶ/ር ለገሰ ቱሉ ፤ በመርዓዊ በመከላከያ ሠራዊት እና በፋኖ ታጣቂዎች መካከል ግጭት እንደነበር አረጋግጠዋል።

" ታጣቂዎቹ በተለያዩ አቅጣጫዎች መከላከያ ሠራዊቱ የሰፈረበትን ካምፕ በአራት አቅጣጫ በማፈን መሣሪያ እና ሎጂስቲኩን ለመዝረፍ በመንቀሳቀሳቸው ራሱን የመከላከል መብቱን ተጠቅሞ ነው እርምጃ ወስዷል " ሲሉ ተናግረዋል።  

" መከላከያ ሠራዊት ራሱን የመከላከል መብቱን ተጠቅሞ እርምጃ ሲወስድ እነዚህ ኃይሎች ተመልሰው ወደ ግለሰቦች ቤት ነው የገቡት " ያሉት ዶ/ር ለገሰ " ወደ ግለሰቦች ቤት በሚገቡበት ጊዜ በሕጉ በተሰጠው ሥልጣን መሠረት አሰሳ ሲያደርግ መልሰው ተኩስ ከፈቱበት " ብለዋል።

" መከላከያ ሠራዊት ራሱን ነው የተከላከለው " ያሉት ዶ/ር ለገሰ ፤ " የመከላከያ ኃይል የትኛውንም ዐይነት ሲቪል ዒላማ አላደረግም " ብለዋል።

የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽንን ጨምሮ ሌሎች መግለጫ ያወጡ የሰብዓዊ መብት ድርጅቶች በመንግሥት የፀጥታ ኃይላት እርምጃ ከተወሰደባቸው ሰዎች መካከል ከቤት እየተወሰዱ የተገደሉ መኖራቸውን መግለፃቸው ይታወቃል።

ይህንን በተመለከተ የተጠየቁት ሚኒስትሩ ፤ " እንደዚያ አይነት እርምጃ ስለመወሰዱ ተረጋግጦ የመጣ መረጃ የለም " ብለዋል።

አክለውም " ሲቪል ይቅርና ታጣቂ እንኳን ለማጥቃት ሄዶ እጅ እስከሰጠ ድረስ የሚገደልበት ሥርዓት የለም። ሊሆንም አይችልም " ሲሉ ተናግረዋል።

" እንዲህ ሆኖ ከሆነም ራሱ መከላከያ ተቋሙ እርምጃ ይወስዳል" ሲሉ አሳውቀዋል።

በሌላ በኩል ፤ የመርዓዊን ግድያ በተመለከተ በኢትዮጵያ የካናዳ ኤምባሲ " እጅግ ያሳስበኛል " ብሏል።

ተፈጽሟል የተባለውን ግድያ " የሚረብሽ ነው " ያለው በኢትዮጵያ የዩናይትድ ኪንግደም ኤምባሲ በበኩሉ ሙሉ ምርመራ እንዲደረግ ጥሪ አቅርቧል።

የአውሮፓ ኅብረት እና የአሜሪካ መንግሥት በበኩላቸው ገለልተኛ ምርመራ እንዲደረግ ጥሪ አስተላልፈዋል።

ዶ/ር ለገሰ ቱሉ ይህ ጉዳይ የሚመለከተው በአማራ ክልል የተደነገገው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መርማሪ ቦርድ እንደሆነ አሳውቀዋል።

" በጉዳዩ ላይ ምርመራ የሚያደርግ ሌላ አካል አይኖርም " ሲሉ ገልጸዋል።

ዶ/ር ለገሰ ጥሪውን ያቀረቡት የአውሮፓ ኅብረት እና የአሜሪካ መንግሥት " ስለ ኢትዮጵያ ሁሌ እንዳሳሰባቸው ነው። ነገር ግን ይኸ ነው የሚባል የሚደረግ ነገር የለም " ሲሉ ምላሽ ሰጥተዋል። 

" የራሳችን ተቋሞች አሉ። ተቋሞቻችን ለሕዝብ ተጠያቂ ናቸው የትኛውም አካል ጥፋት ካጠፋ፤ የትኛውም አካል ጉዳት ካደረሰ ሕጉ እና አሠራሩ በሚፈቅደው መሠረት እርምጃ ይወሰዳል " ብለዋል።

ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የዶቼ ቨለ ሬድዮ ጣቢያ ነው።

@tikvahethiopia
#እንድታውቁት

ከ37ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ እና 44ኛው የሚኒስትሮች ስራ አስፈፃሚ ም/ቤት ስብሰባ ጋር በተያያዘ አሽከርካሪዎች ሌሎች ተለዋጭ መንገዶችን እንዲጠቀሙ የአዲስ አበባ ፖሊስ ጥሪ አቅርቧል።

ጉባኤው ተጀምሮ እስከሚጠናቀ ፦

ከፓርላማ መብራት-በውጭ ጉዳይ ሚ/ር - መስቀል አደባባይ ፍላሚንጎ - ኦምሎፒያ - ወሎ ሰፈር - ጃፓን ኤምባሲ - ፍሬንድ ሺፕ -ቦሌ ቀለበት መንገድ - ኤርፖርት

ከፓርላማ መብራት በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር -በብሔራዊ ቤተ - መንግስት -በፍልውሃ - በብሔራዊ ቴአትር- ሜክሲኮ አደባባይ - አፍሪካ ህብረት አዳራሽ ዙሪያ

ከፓርላማ መብራት -ብሔራዊ ቤተ-መንግስት - ወዳጅነት ፓርክ - ንግድ ማተሚያ ቤት - ሞናርክ ሆቴል-ቴዎድሮስ አደባባይ-ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል- ኢትዮጵያ ቴሌቪዥን- ብሔራዊ ቴአትር - ሜክሲኮ አደባባይ - አፍሪካ ህብረት መንገዶቹ እንግዶች ሲያልፉ አሽከርካሪዎችም ሆኑ እግረኞች ለእንግዶቹ ቅድሚያ በመስጠት ተባባሪ እንዲሆኑና ሌሎች ተለዋጭ መንገዶችን እንዲጠቀሙ መልዕክት ተላልፏል።

ከዚህ ባለፈ ፦

ከፓርላማ መብራት-በሸራተን ሆቴል ቁልቁለቱን-ፍልውሃና አምባሳደር ቴአትር ዙሪያውን

ከንግድ ም/ቤት ጀምሮ በሱዳን ኤምባሲ-አፍሪካ ህብረት ዋናው በር-ሳርቤት ድረስ በሁለቱም አቅጣጫዎች ከነገ ሐሙስ የካቲት 7 ቀን / 2016 ዓ/ም ጀምሮ እንግዶች ተጠቃለው እስኪመለሱ ድረስ ግራና ቀኝ በሁለቱም አቅጣጫ ለአጭርም ሆነ ለረጅም ጊዜ ተሽከርካሪ አቁሞ መሄድ ፍፁም የተከለከለ ነው ተብሏል።

#AddisAbabaPolice

@tikvahethiopia
የውሃ ሽታ

እጁ ላይ ባለው የማስታወሻ ፅሁፍ ብቻ ፀሎትን በደንብ አወቃት። የበለጠ ሊያውቃትም ፈለገ ሊያገኛት ግን አይችልም። በህይወት ያለን ገዳይ ፍለጋ ውስጥ በህይወት ከሌለችው ፀሎት ጋር በፍቅር….
እንዴት? ለምን? የፀሎት የውሃ ሽታ መሆን ሮቤልን አወዛገበው።

ዛሬ ምሽት በ3:00 ሰዓት

እርስዎ ባልተጠበቀ መንገድ የሞተ ሰው ማስታወሻ ቢያገኙ ምን ያደርጋሉ?

በ አቦል ቲቪ 465

ፓኬጅ: ሜዳ

የዲኤስቲቪ ዲኮደር በ1,199 ብር ከ1 ወር ነፃ ሜዳ ፓኬጅ ጋር ያገኛሉ።

የዲኤስቲቪ የተለያዩ አገልግሎቶችን ለማግኘት ከታች  ያለውን የMyDStv Telegram ሊንክ ይጫኑ!
👇
https://bit.ly/2WDuBLk

#ሁሉምያለውእኛጋርነው #DStvEthiopia #YewehaSheta #የውሃሽታ
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update በአዱስ አበባ አጎና የተነሳው እሳት መጀመሪያ ላይ ከነበረበት የወደ መጥፋት ደረጃ ቢቀንስም እሳቱ ሙሉ በሙሉ አልጠፋም። በስፍራው የአዲስ አበባ እሳት አደጋ ተቆጣጣሪዎች እና ተሽከርካሪዎች የሚገኙ ሲሆን የፌዴራል ፖሊስም አጋዥ ተሽከርካሪዎችን ወደ ስፍራው በመላክ እሳቱን ሙሉ በሙሉ ለማጥፋት ርብርብ እየተደረገ ይገኛል። የእሳት አደጋ በተነሳበት ህንፃ ላይ የተለያዩ አገልግሎት ሰጪ ድርጅቶች…
" ቃጠሎ በደረሰበት ህንፃ ላይ ምንም አይነት የቤተክርስቲያን አገልግሎት አይሰጥም ፤ ይሄንን አረጋግጠናል ! " - አቶ ንጋቱ ማሞ

ትላንት ምሽት በአ/አ በቀድሞ አጎና ሲኒማ ህንፃ ላይ የተነሳው እሳት ለመቆጣጠር እጅግ ፈታኝ እንደነበር የአዲስ አበባ እሳትና ድንገተኛ አደጋ አሳውቋል።

እሳቱን መቆጣጠር ከባድ ያደረገው በፍጥነት በመስፋፋቱ ነው ተብሏል።

በእሳት አደጋው የህንፃው አንደኛ እና ሁለተኛ ወለሎች ከነሙሉ ንብረታቸው ወድመዋል።

ህንፃው ላይ የነበረው የውጭ የትርጉም ፊልም የሚያቀርበው " ያ " የተሰኘ የቴሌቪዥን ጣቢያ ሙሉ በሙሉ ንብረቱ የታቀጠለ ሲሆን ቤተክርስቲያን ላይ ጉዳት ደረሰ ተብሎ የተወራው ግን የተሳሳተ መረጃ ነው።

የእስት እና አደጋ ስጋት አመራር ኮሚሽን የሕዝብ ግንኙነት ባለሞያው አቶ ንጋቱ ማሞ ምን አሉ ?

- አደጋው በቀድሞ የአጎና ሲኒማ ህንፃ ላይ ነው የደረሰው።

- በአደጋው ምክንያት አንደኛ እና ሁለተኛ ፎቆ ላይ ያሉ ንብረቶችን ጨምሮ ከባድ ጉዳት ደርሷል።

- ከባድ ጉዳት ከገጠማቸው መካከል ያ የቴሌቪዥን ስቱዲዮ የፕሮዳክሽን ስራ የሚሰሩበት ተጠቃሽ ነው።

- እሳቱ እኛ ከመድረሳችን አስቀድሞ የተስፋፋ ስለነበር በቀላሉ ለመቆጣጠር ችግር ነበር።

- ለስቱዲዮ ሳውንድፕሩፍ ተብሎ አገልግሎት ላይ የዋለ ስፖንጅ እና የመሳሰለው ቁሳቁስ ለእሳቱ መስፋፋት አስተዋጽኦ አድርጓል። ለጊዜው ያላወቅነው በርካታ የፕላስቲክ ወንበሮች አንደኛ ፎቅ ላይ ነበሩ እነሱም ተደማምረው እሳቱ ሰፍቷል።

- በእኛ በኩል እሳቱ ተስፋፍቶ ሌሎች ቦታዎች ላይ ጉዳት እንዳያደርስ ማድረግ ተችሏል። ይህ ሂደት 5 ሰዓት ከ40 ደቂቃ ፈጅቷል።

- አደጋው ለመቆጣጠር ከተሰማሩት ሰራተኞች አንዱ መጠነኛ ጉዳት ደርሶበታል።

ከዚሁ ከእሳት አደጋ ጋር በተያያዘ ውድመት ከደረሰባቸው ውስጥ በአንደኛ ፎቅ ላይ የሚገኝ " ቤተክርስቲያን ይገኝበታል " በሚል የሚሰራጨውን መረጃ በተመለከተ ፤ " የተሳሳተ መረጃ ነው " ብለዋል።

" እስካሁን ማረጋገጥ የተቻለው ያ የቴሌቪዥን ስቱዲያውን ነው " ያሉት ባለሞያው " ሌሎች ህንፃው ላይ የነበሩ የንግድ እና አገልግሎት ሰጪዎችን እያጣራን ነው " ሲሉ ገልጸዋል።

አቶ ንጋቱ ፤ " ከቤተክርስቲያን ጋር ተያይዞ በዚህ ቃጠሎ በደረሰበት ህንፃ ላይ ምንም አይነት የቤተክርስቲያን አገልግሎት የሚሰጥበት አይደለም። ይሄን አረጋግጠናል። ከእምነት ተቋም ጋር ተያይዞ ምንም አይነት አደጋ አላጋጠመም ይሄን አረጋግጠናል። " ሲሉ አሳውቀዋል።

አጠቃላይ በአደጋው ስለደረሰው ጉዳት እና መንስኤ እስካሁን አልታወቀም።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ መረጃውን ከሸገር ኤፍ ኤም 102.1 ሬድዮ ጣቢያ ነው ያገኘው።

@tikvahethiopia