#WSU
➡ “ አንድ ዓመት መዘግየት በጣም ከባድ ነው። ግዴታ መማር እንዳለብን አስጠንቅቀውናል ” - የወላይታ ሶዶ ዩኒበርሲቲ ተማሪዎች
➡ “ የተማሩበት ታይም ምን ያህል ነው? ተብሎ መወሰን አለበት” - የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ህብረት
የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ የ4ኛ ዓመት ተማሪዎች በዚህ ዓመት መመረቅ ሲገባቸው “ አላወቅነውም ” ባሉት ምክንያት ለምረቃ አንድ ‘ዓመት ትጨምራላችሁ’ ተብለው እየተገደዱ መሆኑን አማረው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ቅሬታቸውን አሰምተዋል።
ለምን የእናንተ ብቻ ዘገዬ ወይም አንድ ዓመት ጭማሪ ተደረገ ? ሲል ቲክቫህ ኢትዮጵያ ጥያቄ አቅርቧል።
* ስኬጁሉ ላይ ነው ችግራቸው። በኮሮና ምክንያት 2013 ዓ/ም ሁሉም ግቢዎች ተማሪዎቻቸውን የጠሩት ሰኔ ወር ላይ ነበር። እኛም ከሁሉም ግቢ እኩል ነበር የገባነው (ሰኔ 26)። ወዲያውኑ (45 ቀናት አቆይቶ) አስወጣን (ከግቢ) ምንም ባላወቅንበት መንገድ። አንድ ሲሚስተር ጨርሰን መወሰጣት ሲገባን ሚድን ፈትኖ አስወጣን።
* በቀጣዩ ዓመት ደግሞ ሚዲ የወሰድነውን ሁለት ሲሚስተር አድርጎ በአጠቃላይ አስተማረ። ሙሉ 3 ሲሚስተር ነበር ማስተማር የነበረበት ግን አንዱን ዓመት በሁለት ሲሚስተር ብቻ አደረገ። ስህተቱን የሰሩት እዚሁ ላይ ነው።
* ሬጅስተራር ላይ የሰፈረው “4ኛ ዓመት ናችሁ” ነው የሚለው። እኛ የምንማረው ግን ገና ሦስተኛ ዓመት ሁለተኛ ሲሚስተርን እየጀመርን ነው። ሌሎች ግቢዎች ግን አሁን 4ኛ ዓመት ሁለተኛ ሲሚስተርን እያስተማሩ ነው። የእኛ ሙሉ 3 ሲሚስተሮች ወደ ኋላ ቀርቷል ማለት ነው።
* ‘ወደ ኋላ ቀረን’ ብለን ስናመለክት ‘#አስተካክላለሁ’ ብሎ ‘3 ሲሚስተር አስተምራለሁ’ ካለ በኋላ ሁለት ሲሚስተር አስተማረና ካፌ ዘጋ። እንደዛ እየተደረገ አንድ ዓመት ባከነ። የእኛን የአንድ ዓመት በጀት ለምን እንደፈለጉት አናውቅም። ከሌሎች ግቢዎች በሚለይ ሁኔታ በሚያስጠላ ሁኔታ ላይ ነው ያለነው።
የሚል ማብራሪያ በአንድ ተወካያቸው በኩል ሰጥተዋል።
“ ሌሎች ግቢዎች የእኛን ባቾች በዚህ ዓመት ያስመርቃሉ። የእኛ ግን በዚህ ዓመት አይደለም” ያሉት ተማሪዎቹ፣ “ በዚህ ሳምንት ክላስ አልገባንም። ነገር ግን ግዴታ በቀጣይ ሰኞ መግባት እንዳለብን ተነግሮናል። ግዴታ መማር እንዳለብን አስጠንቅቀውናል። ” ሲሉ አስረድተዋል።
አክለውም፣ “ አንድ ዓመት መዘግየት በጣም ከባድ ነው። ሙሉ 3 ሲሚስተር አስተምሮ ሰኔ ላይ ይፈትነን (እንመረቅ) አንልም። ቢያንስ ስለ Exit exam የሚሆኑ ኮርሶችን ወደዚህ አሸጋሽገውልን Exist ተፈትነን ቀጣዩን አንድ ሲሚስተር እንድንወስድ ያድርጉን። አንድ ዓመት ከመዘግየት ግማሽ ዓመት መዘግየት ይሻላል ብለዋል ” ሲሉ አሳስበዋል።
ቅሬታውን በተመለከተ ምን ምላሽ እንዳለው ለመጠየቅ ወደ ዩኒቨርስቲው ከፍተኛ አመራሮሽ የተደረገው ሙከራ ባይሳካም፣ የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲው የተማሪዎች ኀብረት ፕሬዝዳንት ተማሪ ፍሬው ተክሌ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል፣ “ ስኬጁል ላይ የተቀየረ ነገር የለም። ያልተጣራ መረጃ እንጂ በእኛ ፔጅ ላይ የተለጠፈ አይደለም ” ሲሉ አስተባብለዋል።
ተማሪ ፍሬው፣ “ የሚመረቁት መቼ ነው? ለሚለው የተማሩበት ታይም ምን ያህል ነው? የሚለው መወሰን አለበት” ያሉ ሲሆን፣ የዘንድሮ ተማሪዎቹ በቀጣይ ዓመት ነው የምትመረቁት ተብለዋል ወይስ አልተባሉም? ተብሎ ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ለቀረበላቸው ጥያቄም ቀጥኛ መልስ በመስጠት ፋንታ፤ “በእስኬጁል መሠረት ነው እኮ ይሄ ውሳኔ” ብለዋል።
መረጃውን አዘጋጅቶ የላከው የአ/አ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ነው።
@tikvahethiopia
➡ “ አንድ ዓመት መዘግየት በጣም ከባድ ነው። ግዴታ መማር እንዳለብን አስጠንቅቀውናል ” - የወላይታ ሶዶ ዩኒበርሲቲ ተማሪዎች
➡ “ የተማሩበት ታይም ምን ያህል ነው? ተብሎ መወሰን አለበት” - የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ህብረት
የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ የ4ኛ ዓመት ተማሪዎች በዚህ ዓመት መመረቅ ሲገባቸው “ አላወቅነውም ” ባሉት ምክንያት ለምረቃ አንድ ‘ዓመት ትጨምራላችሁ’ ተብለው እየተገደዱ መሆኑን አማረው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ቅሬታቸውን አሰምተዋል።
ለምን የእናንተ ብቻ ዘገዬ ወይም አንድ ዓመት ጭማሪ ተደረገ ? ሲል ቲክቫህ ኢትዮጵያ ጥያቄ አቅርቧል።
* ስኬጁሉ ላይ ነው ችግራቸው። በኮሮና ምክንያት 2013 ዓ/ም ሁሉም ግቢዎች ተማሪዎቻቸውን የጠሩት ሰኔ ወር ላይ ነበር። እኛም ከሁሉም ግቢ እኩል ነበር የገባነው (ሰኔ 26)። ወዲያውኑ (45 ቀናት አቆይቶ) አስወጣን (ከግቢ) ምንም ባላወቅንበት መንገድ። አንድ ሲሚስተር ጨርሰን መወሰጣት ሲገባን ሚድን ፈትኖ አስወጣን።
* በቀጣዩ ዓመት ደግሞ ሚዲ የወሰድነውን ሁለት ሲሚስተር አድርጎ በአጠቃላይ አስተማረ። ሙሉ 3 ሲሚስተር ነበር ማስተማር የነበረበት ግን አንዱን ዓመት በሁለት ሲሚስተር ብቻ አደረገ። ስህተቱን የሰሩት እዚሁ ላይ ነው።
* ሬጅስተራር ላይ የሰፈረው “4ኛ ዓመት ናችሁ” ነው የሚለው። እኛ የምንማረው ግን ገና ሦስተኛ ዓመት ሁለተኛ ሲሚስተርን እየጀመርን ነው። ሌሎች ግቢዎች ግን አሁን 4ኛ ዓመት ሁለተኛ ሲሚስተርን እያስተማሩ ነው። የእኛ ሙሉ 3 ሲሚስተሮች ወደ ኋላ ቀርቷል ማለት ነው።
* ‘ወደ ኋላ ቀረን’ ብለን ስናመለክት ‘#አስተካክላለሁ’ ብሎ ‘3 ሲሚስተር አስተምራለሁ’ ካለ በኋላ ሁለት ሲሚስተር አስተማረና ካፌ ዘጋ። እንደዛ እየተደረገ አንድ ዓመት ባከነ። የእኛን የአንድ ዓመት በጀት ለምን እንደፈለጉት አናውቅም። ከሌሎች ግቢዎች በሚለይ ሁኔታ በሚያስጠላ ሁኔታ ላይ ነው ያለነው።
የሚል ማብራሪያ በአንድ ተወካያቸው በኩል ሰጥተዋል።
“ ሌሎች ግቢዎች የእኛን ባቾች በዚህ ዓመት ያስመርቃሉ። የእኛ ግን በዚህ ዓመት አይደለም” ያሉት ተማሪዎቹ፣ “ በዚህ ሳምንት ክላስ አልገባንም። ነገር ግን ግዴታ በቀጣይ ሰኞ መግባት እንዳለብን ተነግሮናል። ግዴታ መማር እንዳለብን አስጠንቅቀውናል። ” ሲሉ አስረድተዋል።
አክለውም፣ “ አንድ ዓመት መዘግየት በጣም ከባድ ነው። ሙሉ 3 ሲሚስተር አስተምሮ ሰኔ ላይ ይፈትነን (እንመረቅ) አንልም። ቢያንስ ስለ Exit exam የሚሆኑ ኮርሶችን ወደዚህ አሸጋሽገውልን Exist ተፈትነን ቀጣዩን አንድ ሲሚስተር እንድንወስድ ያድርጉን። አንድ ዓመት ከመዘግየት ግማሽ ዓመት መዘግየት ይሻላል ብለዋል ” ሲሉ አሳስበዋል።
ቅሬታውን በተመለከተ ምን ምላሽ እንዳለው ለመጠየቅ ወደ ዩኒቨርስቲው ከፍተኛ አመራሮሽ የተደረገው ሙከራ ባይሳካም፣ የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲው የተማሪዎች ኀብረት ፕሬዝዳንት ተማሪ ፍሬው ተክሌ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል፣ “ ስኬጁል ላይ የተቀየረ ነገር የለም። ያልተጣራ መረጃ እንጂ በእኛ ፔጅ ላይ የተለጠፈ አይደለም ” ሲሉ አስተባብለዋል።
ተማሪ ፍሬው፣ “ የሚመረቁት መቼ ነው? ለሚለው የተማሩበት ታይም ምን ያህል ነው? የሚለው መወሰን አለበት” ያሉ ሲሆን፣ የዘንድሮ ተማሪዎቹ በቀጣይ ዓመት ነው የምትመረቁት ተብለዋል ወይስ አልተባሉም? ተብሎ ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ለቀረበላቸው ጥያቄም ቀጥኛ መልስ በመስጠት ፋንታ፤ “በእስኬጁል መሠረት ነው እኮ ይሄ ውሳኔ” ብለዋል።
መረጃውን አዘጋጅቶ የላከው የአ/አ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ነው።
@tikvahethiopia
Unleash your entrepreneurial spirit with the Jasiri Talent Investor Programme! We're seeking visionary entrepreneurs ready to create high-impact businesses that will shape the future. Our fully-funded 13-month program is uniquely designed to support your growth journey, providing the resources to foster Market-Creating Innovation and find the perfect product-market fit. With a focus on competency and a comprehensive support system, we're here to help you overcome any barriers to success. Apply for Cohort 6 now at jasiri.org/application and start building your venture with us. #JasiriTalentInvestor #Entrepreneurship #Innovation #BusinessGrowth #ApplyToday
የሁለተኛ እና የሶስተኛ ዙር ተረክ በM-PESA የባጃጅ አሸናፊዎቻችን ሽልማታቸውን ተረክበዋል!
አዲስ አበባ፣ አምቦ፣ ጅማ፣ ሰንዳፋ እና አዳማ እንኳን ደስ አላችሁ!
ቀጣይ በM-PESA የተዘጋጀው ምርጥ ሽልማት ማን የሚውስደው ይመስላቹዋል?
M-PESA ላይ እንመዝገብ፣ በM-PESA እንገበያይ፣ ቀጣይ እድለኛ አሸናፊዎች እንሁን።
🔗 የM-PESA ሳፋሪኮምን መተግበሪያ በዚህ ሊንክ ያውርዱ: https://bit.ly/M-PESA_SafaricomEthiopia
#MPESASafaricom #TerekBeMPESA
#FurtherAheadTogether
አዲስ አበባ፣ አምቦ፣ ጅማ፣ ሰንዳፋ እና አዳማ እንኳን ደስ አላችሁ!
ቀጣይ በM-PESA የተዘጋጀው ምርጥ ሽልማት ማን የሚውስደው ይመስላቹዋል?
M-PESA ላይ እንመዝገብ፣ በM-PESA እንገበያይ፣ ቀጣይ እድለኛ አሸናፊዎች እንሁን።
🔗 የM-PESA ሳፋሪኮምን መተግበሪያ በዚህ ሊንክ ያውርዱ: https://bit.ly/M-PESA_SafaricomEthiopia
#MPESASafaricom #TerekBeMPESA
#FurtherAheadTogether
TIKVAH-ETHIOPIA
#FederalGovernment የፌዴራል መንግሥት ፤ " የፕሪቶርያው ስምምነት ከምንም በላይ ተግባራዊ ምላሽ እንደሚፈልግ " በገለፀበት የዛሬ መግለጫው ፤ በትግራይ ክልል ተፈናቃዮችን ወደ መደበኛ መኖሪያቸው ለመመለስ እንዲቻል የሚመለከታቸውን አካላት አቀናጅቶ ሥራ መጀመሩን አመልክቷል። በአንዳንድ አካባቢዎች ትክክለኛ ተፈናቃዮችን ወደ መኖሪያቸው እንዲመለሱ መደረጉንም ገልጿል። የአከራካሪ ቦታዎችን ሁኔታ…
#Update
የትግራይ ክልል ጊዚያዊ አስተዳደር የፌዴራል መንግስት ኮሙዩኒኬሽን አገልግሎት ጥር 23 /2016 ዓ.ም የሰጠውን መግለጫ አስመልክቶ ዛሬ መግለጫ አውጥቷል።
በዚህ መግለጫው ፤ ከፕሪቶርያ ስምምነት አፈፃፅም ጋር በተያያዙ በኮሚኒኬሽን አገልግሎት መግለጫ ላይ የተጠቀሰውና ከትግራይ ሉአላዊ ግዛት መረጋገጥ ጋር በተያያዘ " ጉዳዩን በሪፈረንደም ለመፍታት መረዳዳት ተደርሶ ነበር " በሚል የቀረበው መግለጫ ፍፁም የተሳሳተ ነው ብሏል።
" ጊዚያዊ አሰተዳደሩም ሆነ ፌደራል መንግስቱ በፕሪቶሪያ ስምምነት መሰረት ሕገ መንግስቱን መሰረት በማድረግ ጉዳዩን ለመፍታት ከደረሱበት ስምምነትም ሆነ ካላቸው ስልጣን ውጪ የሆነ ተግባር መሆኑን በተደጋጋሚ ያነሳነው ስለሆነ ተቀባይነት የሌለዉ መሆኑን መግለፅ እንወዳለን። " ሲል አክሏል።
ሌላው ፤ ከተፈናቃዮች መመለስ ጋር ተያይዞ " ትክክለኛ ተፈናቃዮች ተመልሰዋል " በሚል የቀረበው የመግለጫው ክፍል እጅግ አደገኛና በጉልበት የሃገሪቱ ካርታ ለመቀየር የፌዴራል መከላከያ ሆነ የጎረቤት ሃገራትን አቅም ተጠቅሞ የተደረገን አውዳሚ እንቅስቃሴ ሕጋዊ ሽፋን ለመስጠት የሚያግዝ ነው ብሏል።
ከምንም ነገር በላይ ግን " ትክክለኛ ተፈናቃይ " ፤ " ትክክለኛ ያልሆነ ተፈናቃይ " በሚል መፈታት የነበረበትን ችግር የበለጠ የሚያባብስ አደገኛ ትንታኔ ስለሆነ አንቀበለዉም ሲል አሳውቋል።
ጊዜያዊ አስተዳደሩ በመግለጫው ፤ " አሁንም ከሚልዮን በላይ ቁጥር ያላቸው ተፈናቃዮች በአስከፊ ሁኔታ የሚኖሩበት፤ ያፈናቀላቸዉ ፀረ ህዝብ እና ሕገ ወጥ አስተዳደሪዎች ፌደራል መንግስቱ ከመንበራቸው ሊያስወግዳቸው ሲገባ አሁንም ሕግ አስከባሪዎች ነን ብለው በሚመፃደቁበት ሁኔታ ውስጥ ሆነው እንደዚህ ዓይነት መግለጫ መውጣቱ የፌደራል መንግስቱ የመፍትሄው አካል መሆን ሲገባው የችግሩ አካል ለመሆን የወሰነ የሚያስመሰለው ስለሆነ በፍፁም ተቀባይነት የለውም " ብሏል።
" የፌደራል መንግስቱ ከፕሪቶርያ ስምምነት ወዲህ የወሰናቸው በተለይም ከበጀትና መሰል ጉዳዮች ጋር የተያያዙ አበረታችም ሆኑ መታረም ያለባቸው ጉዳዮች በሚመለከት ለክቡር ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሪፓርት የሚቀርብ በመሆኑ በዚህ ጉዳይ ላይ የምንለው ነገር አይኖርም " ሲል አሳውቋል።
የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ባወጣው መግለጫ ፤ ሰላም በሁሉም የትግራይ እና የኢትዮጵያ አከባቢዎች በተሟላ መልኩ የሚረጋገጥበት ሁኔታ እስኪፈጠር ድረስ ከፌደራል መንግስት በመቀራረብ እንደሚሰራ ቁርጠኛ መሆኑን ገልጿል።
(ሙሉ መግለጫው ከላይ ተያይዟል)
@tikvahethiopia
የትግራይ ክልል ጊዚያዊ አስተዳደር የፌዴራል መንግስት ኮሙዩኒኬሽን አገልግሎት ጥር 23 /2016 ዓ.ም የሰጠውን መግለጫ አስመልክቶ ዛሬ መግለጫ አውጥቷል።
በዚህ መግለጫው ፤ ከፕሪቶርያ ስምምነት አፈፃፅም ጋር በተያያዙ በኮሚኒኬሽን አገልግሎት መግለጫ ላይ የተጠቀሰውና ከትግራይ ሉአላዊ ግዛት መረጋገጥ ጋር በተያያዘ " ጉዳዩን በሪፈረንደም ለመፍታት መረዳዳት ተደርሶ ነበር " በሚል የቀረበው መግለጫ ፍፁም የተሳሳተ ነው ብሏል።
" ጊዚያዊ አሰተዳደሩም ሆነ ፌደራል መንግስቱ በፕሪቶሪያ ስምምነት መሰረት ሕገ መንግስቱን መሰረት በማድረግ ጉዳዩን ለመፍታት ከደረሱበት ስምምነትም ሆነ ካላቸው ስልጣን ውጪ የሆነ ተግባር መሆኑን በተደጋጋሚ ያነሳነው ስለሆነ ተቀባይነት የሌለዉ መሆኑን መግለፅ እንወዳለን። " ሲል አክሏል።
ሌላው ፤ ከተፈናቃዮች መመለስ ጋር ተያይዞ " ትክክለኛ ተፈናቃዮች ተመልሰዋል " በሚል የቀረበው የመግለጫው ክፍል እጅግ አደገኛና በጉልበት የሃገሪቱ ካርታ ለመቀየር የፌዴራል መከላከያ ሆነ የጎረቤት ሃገራትን አቅም ተጠቅሞ የተደረገን አውዳሚ እንቅስቃሴ ሕጋዊ ሽፋን ለመስጠት የሚያግዝ ነው ብሏል።
ከምንም ነገር በላይ ግን " ትክክለኛ ተፈናቃይ " ፤ " ትክክለኛ ያልሆነ ተፈናቃይ " በሚል መፈታት የነበረበትን ችግር የበለጠ የሚያባብስ አደገኛ ትንታኔ ስለሆነ አንቀበለዉም ሲል አሳውቋል።
ጊዜያዊ አስተዳደሩ በመግለጫው ፤ " አሁንም ከሚልዮን በላይ ቁጥር ያላቸው ተፈናቃዮች በአስከፊ ሁኔታ የሚኖሩበት፤ ያፈናቀላቸዉ ፀረ ህዝብ እና ሕገ ወጥ አስተዳደሪዎች ፌደራል መንግስቱ ከመንበራቸው ሊያስወግዳቸው ሲገባ አሁንም ሕግ አስከባሪዎች ነን ብለው በሚመፃደቁበት ሁኔታ ውስጥ ሆነው እንደዚህ ዓይነት መግለጫ መውጣቱ የፌደራል መንግስቱ የመፍትሄው አካል መሆን ሲገባው የችግሩ አካል ለመሆን የወሰነ የሚያስመሰለው ስለሆነ በፍፁም ተቀባይነት የለውም " ብሏል።
" የፌደራል መንግስቱ ከፕሪቶርያ ስምምነት ወዲህ የወሰናቸው በተለይም ከበጀትና መሰል ጉዳዮች ጋር የተያያዙ አበረታችም ሆኑ መታረም ያለባቸው ጉዳዮች በሚመለከት ለክቡር ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሪፓርት የሚቀርብ በመሆኑ በዚህ ጉዳይ ላይ የምንለው ነገር አይኖርም " ሲል አሳውቋል።
የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ባወጣው መግለጫ ፤ ሰላም በሁሉም የትግራይ እና የኢትዮጵያ አከባቢዎች በተሟላ መልኩ የሚረጋገጥበት ሁኔታ እስኪፈጠር ድረስ ከፌደራል መንግስት በመቀራረብ እንደሚሰራ ቁርጠኛ መሆኑን ገልጿል።
(ሙሉ መግለጫው ከላይ ተያይዟል)
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#እንድታውቁት የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በነበረበት ይቀጥላል። ሁሉም የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በታህሳስ ወር ሲሸጥ በነበረበት ዋጋ የሚቀጥል መሆኑን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር አስታውቋል። የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ስንት ነው ? - ቤንዚን በሊትር 77 ብር ከ65 ሳንቲም - ነጭ ናፍጣ በሊትር 79 ብር ከ75 ሳንቲም - ኬሮሲን በሊትር 79 ብር ከ75 ሳንቲም…
#እንድታውቁት
የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በነበረበት ይቀጥላል።
ሁሉም የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በጥር ወር ሲሸጥ በነበረበት ዋጋ የሚቀጥል መሆኑን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር አስታውቋል።
የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ስንት ነው ?
- ቤንዚን በሊትር 77 ብር ከ65 ሳንቲም
- ነጭ ናፍጣ በሊትር 79 ብር ከ75 ሳንቲም
- ኬሮሲን በሊትር 79 ብር ከ75 ሳንቲም
- ቀላል ጥቁር ናፍጣ በሊትር 62 ብር ከ36 ሳንቲም
- ከባድ ጥቁር ናፍጣ በሊትር 61 ብር ከ16 ሳንቲም ነው።
@tikvahethiopia
የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በነበረበት ይቀጥላል።
ሁሉም የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በጥር ወር ሲሸጥ በነበረበት ዋጋ የሚቀጥል መሆኑን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር አስታውቋል።
የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ስንት ነው ?
- ቤንዚን በሊትር 77 ብር ከ65 ሳንቲም
- ነጭ ናፍጣ በሊትር 79 ብር ከ75 ሳንቲም
- ኬሮሲን በሊትር 79 ብር ከ75 ሳንቲም
- ቀላል ጥቁር ናፍጣ በሊትር 62 ብር ከ36 ሳንቲም
- ከባድ ጥቁር ናፍጣ በሊትር 61 ብር ከ16 ሳንቲም ነው።
@tikvahethiopia
የአፍሪካ ሕብረት ጉባኤ መቼ ነው ?
37ኛው የአፍሪካ ሕብረት የመሪዎች ጉባዔ የካቲት 9 እና 10 ቀን 2016 ዓ.ም በአዲስ አበባ ይካሄዳል።
44ኛው የአባል ሀገራቱ የሥራ አስፈጻሚዎች ምክር ቤት ስብሰባ ከመሪዎች ጉባዔ ቀደም ብሎ የካቲት 6 እና 7 ቀን 2016 ዓ.ም ይካሄዳል ተብሎ ይጠበቃል።
የአፍሪካ ሕብረት የ2024 መሪ ቃል " ለ21ኛው ክፍለ ዘመን የሚመጥን አፍሪካዊ ማስተማር፤ የማይበገሩ የትምህርት ስርዓቶች በመገንባት በአፍሪካ ሁሉን አቀፍ፣ የሕይወት ዘመን፣ ጥራትና አግባብነት ያለው የትምህርት ተደራሽነትን ማስፋት " የሚል ነው።
የአፍሪካ ሕብረት መቀመጫ የሆነችው ኢትዮጵያ (አዲስ አባባ) እንግዶቿን ለመቀበል ዝግጁ መሆኗን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መግለፁን ኢዜአ ዘግቧል።
@tikvahethiopia
37ኛው የአፍሪካ ሕብረት የመሪዎች ጉባዔ የካቲት 9 እና 10 ቀን 2016 ዓ.ም በአዲስ አበባ ይካሄዳል።
44ኛው የአባል ሀገራቱ የሥራ አስፈጻሚዎች ምክር ቤት ስብሰባ ከመሪዎች ጉባዔ ቀደም ብሎ የካቲት 6 እና 7 ቀን 2016 ዓ.ም ይካሄዳል ተብሎ ይጠበቃል።
የአፍሪካ ሕብረት የ2024 መሪ ቃል " ለ21ኛው ክፍለ ዘመን የሚመጥን አፍሪካዊ ማስተማር፤ የማይበገሩ የትምህርት ስርዓቶች በመገንባት በአፍሪካ ሁሉን አቀፍ፣ የሕይወት ዘመን፣ ጥራትና አግባብነት ያለው የትምህርት ተደራሽነትን ማስፋት " የሚል ነው።
የአፍሪካ ሕብረት መቀመጫ የሆነችው ኢትዮጵያ (አዲስ አባባ) እንግዶቿን ለመቀበል ዝግጁ መሆኗን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መግለፁን ኢዜአ ዘግቧል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#ExitExam2016
ከጥቂት ቀናት በኃላ የሚሰጠውን ሀገር አቀፉን የመውጫ ፈተና " ካለንበት ዩኒቨርሲቲ / ተቋም በርካታ ኪሎ ሜትሮችን ርቀን ተጉዘን እንድንፈተን #መመደባችን ተነግሮናል " ያሉ ተመራቂ ተማሪዎች ቅሬታቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አቀረቡ።
ቅሬታቸውን ካሰሙት መካከል የተወሰኑት የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፣ ጥቁር አንበሳ ' ስኩን ኦፍ ሜዲስን ' ተመራቂ ተማሪዎች ናቸው።
ተማሪዎቹ የካቲት 6 /2016 ዓ/ም መሰጠት የሚጀምረውን ፈተና ለመፈተን ከአዲስ አበባ ከ400 ኪሎ ሜትር በላይ ወደ ሚርቀው ወሎ ዩኒቨርሲቲ እንደተመደቡ እንደተነገራቸውና ጉዳዩ ፍፁም ያልጠበቁት ዱብእዳ እንደሆነ አስረድተዋል።
" የምርቃት ቀናችን 10 ቀናት እየቀሩት የመውጫ ፈተና ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ከ420 ኪ/ሜ ርቀን በወሎ ዩኒቨርስቲ እንደምንፈተን ተነግሮናል፤ ይህ ፍፁም ያጠበቅነውና ያልተለመደ ነው " ብለዋል።
ከተቋማችን እጅግ ርቀን ፈተናውን እንድንወስድ ተመድበናል ያሉት ተማሪዎች ፤ " ላለፉት 8 ዓመታት እዚህ ቀን ላይ ለመድረስ ከነቤተሰቦችን ከፍተኛ መስእዋትነት ከፍለናል፤ ብዙ ውጣ ውረድ አሳልፈናል " ያሉ ሲሆን ቤተሰቦችም የልጆቸውን ድካም ፍሬ ለማየት እየተጠባበቁ እንደሆነ ጠቁመዋል።
ተመራቂዎቹ ፦
- አሁን ባለው ሁኔታ ረጅም ጉዞ ማድረግ ደህንነቱ የተጠበቀ እንዳልሆነ እየታወቀ፤
- ለምርቃት የቀረው አጭር ቀን ሆኖ ሳለና በርካታ ካምፓሶች በአዲስ አበባ እያሉ፤
- የብሄራዊ የመውጫ ፈተናው በኦንላይ እንደሚሰጥ እየታወቀ፤
- የደህንነታችን እና በዚህ የምርቃት ወቅት የቤተሰብ ኢኮኖሚ ጉዳይ ፍፁም ታሳቢ ሳይደረግ ለምን እንደዚህ ያለው ውሳኔ እንደተላለፈ በፍፁም ሊገባን አልቻለም፤ ማብራሪያም ሊሰጠን የወደደ አካል የለም ሲሉ ተናግረዋል።
በመሆኑም " ይህ ወደ ሌላ ቦታ ሄዳችሁ በኦንላይ የሚሰጠውን ፈተና ትወስዳላችሁ " የሚለው ነገር ተገቢ ባለመሆኑ እርምት እንዲደረግ ጠይቀዋል።
ከ ' ስኩል ኦፍ ሜዲስን ' ተመራቂዎች በተጨማሪ የተወሰኑ የምህንድስና ተማሪዎችም ተመሳሳይ ቅሬታቸውን አድርሰዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ የተመራቂ ተማሪችዎች ጋር በውስጥ የደረሰ የመፈተኛ username ፣ password እንዲሁም የመፈተኛ ጣቢያ (ዩኒቨርሲቲ) የያዘ ፋይል ደርሶት ተመልክቷል።
ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በተጨማሪ ከሌሎች ተቋማት ተመራቂዎች መሰል ቅሬታዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ደርሰዋል።
አንዳንድ ተመራቂዎች አሁን ካሉበት ዩኒቨርሲቲ ርቀው እንደሚፈተኑ በተወካዮቻቸው በኩል እንደተነገራቸው ገልጸዋል።
በተመሳሳይ እነዚህ ተመራቂዎች ፤ በዚህ ወቅት ወደሌላ ቦታ እንዲጓዙ ተደርገው የኦንላይን ፈተና የሚወስዱበት ምክንያት ምንም ግልፅ እንዳልሆነላቸውና ይህ ነገር ተግባራዊ ከመደረጉ በፊት ማሰብና ማስተካከል እንደሚገባ አስገንዘበዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ጉዳዩን በተመለከተ ዝርዝር መረጃ ለማግኘት የትምህርት ሚኒስቴር አመራሮችን ለማነጋገርና መረጃ ለመስጠት ጥረት ያደርጋል።
በአመቱ አጋማሽ ላይ የሚሰጠው የሀገር አቀፍ የመውጫ ፈተና ተራዝሞ ከየካቲት 06 እስከ 09/2016 ዓ.ም እንደሚሰጥ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከትምህርት ሚኒስቴር ያገኘውን መረጃ ዋቢ በማድረግ መዘገቡ ይታወሳል።
በዚህ ሳምንት የሞዴል ፈተና ይሰጣል።
@tikvahethiopia
ከጥቂት ቀናት በኃላ የሚሰጠውን ሀገር አቀፉን የመውጫ ፈተና " ካለንበት ዩኒቨርሲቲ / ተቋም በርካታ ኪሎ ሜትሮችን ርቀን ተጉዘን እንድንፈተን #መመደባችን ተነግሮናል " ያሉ ተመራቂ ተማሪዎች ቅሬታቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አቀረቡ።
ቅሬታቸውን ካሰሙት መካከል የተወሰኑት የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፣ ጥቁር አንበሳ ' ስኩን ኦፍ ሜዲስን ' ተመራቂ ተማሪዎች ናቸው።
ተማሪዎቹ የካቲት 6 /2016 ዓ/ም መሰጠት የሚጀምረውን ፈተና ለመፈተን ከአዲስ አበባ ከ400 ኪሎ ሜትር በላይ ወደ ሚርቀው ወሎ ዩኒቨርሲቲ እንደተመደቡ እንደተነገራቸውና ጉዳዩ ፍፁም ያልጠበቁት ዱብእዳ እንደሆነ አስረድተዋል።
" የምርቃት ቀናችን 10 ቀናት እየቀሩት የመውጫ ፈተና ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ከ420 ኪ/ሜ ርቀን በወሎ ዩኒቨርስቲ እንደምንፈተን ተነግሮናል፤ ይህ ፍፁም ያጠበቅነውና ያልተለመደ ነው " ብለዋል።
ከተቋማችን እጅግ ርቀን ፈተናውን እንድንወስድ ተመድበናል ያሉት ተማሪዎች ፤ " ላለፉት 8 ዓመታት እዚህ ቀን ላይ ለመድረስ ከነቤተሰቦችን ከፍተኛ መስእዋትነት ከፍለናል፤ ብዙ ውጣ ውረድ አሳልፈናል " ያሉ ሲሆን ቤተሰቦችም የልጆቸውን ድካም ፍሬ ለማየት እየተጠባበቁ እንደሆነ ጠቁመዋል።
ተመራቂዎቹ ፦
- አሁን ባለው ሁኔታ ረጅም ጉዞ ማድረግ ደህንነቱ የተጠበቀ እንዳልሆነ እየታወቀ፤
- ለምርቃት የቀረው አጭር ቀን ሆኖ ሳለና በርካታ ካምፓሶች በአዲስ አበባ እያሉ፤
- የብሄራዊ የመውጫ ፈተናው በኦንላይ እንደሚሰጥ እየታወቀ፤
- የደህንነታችን እና በዚህ የምርቃት ወቅት የቤተሰብ ኢኮኖሚ ጉዳይ ፍፁም ታሳቢ ሳይደረግ ለምን እንደዚህ ያለው ውሳኔ እንደተላለፈ በፍፁም ሊገባን አልቻለም፤ ማብራሪያም ሊሰጠን የወደደ አካል የለም ሲሉ ተናግረዋል።
በመሆኑም " ይህ ወደ ሌላ ቦታ ሄዳችሁ በኦንላይ የሚሰጠውን ፈተና ትወስዳላችሁ " የሚለው ነገር ተገቢ ባለመሆኑ እርምት እንዲደረግ ጠይቀዋል።
ከ ' ስኩል ኦፍ ሜዲስን ' ተመራቂዎች በተጨማሪ የተወሰኑ የምህንድስና ተማሪዎችም ተመሳሳይ ቅሬታቸውን አድርሰዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ የተመራቂ ተማሪችዎች ጋር በውስጥ የደረሰ የመፈተኛ username ፣ password እንዲሁም የመፈተኛ ጣቢያ (ዩኒቨርሲቲ) የያዘ ፋይል ደርሶት ተመልክቷል።
ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በተጨማሪ ከሌሎች ተቋማት ተመራቂዎች መሰል ቅሬታዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ደርሰዋል።
አንዳንድ ተመራቂዎች አሁን ካሉበት ዩኒቨርሲቲ ርቀው እንደሚፈተኑ በተወካዮቻቸው በኩል እንደተነገራቸው ገልጸዋል።
በተመሳሳይ እነዚህ ተመራቂዎች ፤ በዚህ ወቅት ወደሌላ ቦታ እንዲጓዙ ተደርገው የኦንላይን ፈተና የሚወስዱበት ምክንያት ምንም ግልፅ እንዳልሆነላቸውና ይህ ነገር ተግባራዊ ከመደረጉ በፊት ማሰብና ማስተካከል እንደሚገባ አስገንዘበዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ጉዳዩን በተመለከተ ዝርዝር መረጃ ለማግኘት የትምህርት ሚኒስቴር አመራሮችን ለማነጋገርና መረጃ ለመስጠት ጥረት ያደርጋል።
በአመቱ አጋማሽ ላይ የሚሰጠው የሀገር አቀፍ የመውጫ ፈተና ተራዝሞ ከየካቲት 06 እስከ 09/2016 ዓ.ም እንደሚሰጥ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከትምህርት ሚኒስቴር ያገኘውን መረጃ ዋቢ በማድረግ መዘገቡ ይታወሳል።
በዚህ ሳምንት የሞዴል ፈተና ይሰጣል።
@tikvahethiopia
“ ወደ 10 የሚደርሱ ደጋፊዎችና አባላቶች ታስረዋል” - አቶ ጀሚል ሳኒ
የጎጎት ፓርቲ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ጀሚል ሳኒ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል፣ “በአመራር ደረጃ ሦስት ከፍተኛ አመራሮች እስር ላይ ናቸው። ደጋፊዎች የተለያየ ቦታ ይታሰራሉ። ቁጥራቸው አንዱ ሲታሰር ሌላው የመፈታት ሁኔታዎች አሉ” ብለዋል።
“ወደ 10 የሚደርሱ ደጋፊዎችና አባላቶች ታስረዋል” ያሉት ኃላፊው፣ “ኪዚያ በተጨማሪም አካባቢው ላይ የፓርቲያችን አባላቶች ባይሆኑም ወጣቶችን የማሳደድ፣ የማሰር (በተለይ የክልል ጥያቄ ጋር አክቲቭ ሆነው ሲሳተፉ የነበሩትንም የአካባቢው ወጣቶች አሳሳዶ የመያዝ) ሂደቶች አሉ” ሲሉ ተናግረዋል።
የታሰሩ ሰዎችን ለማስፈታት ፓርቲው ምን ያህል ጥረት አድርጓል ተብሎ ለቀረበላቸው ጥያቄም አቶ ጀሚል፣ “አብዛኛው እስሩ ፖለቲካል የሆነ እስር ነው ብለን ነው የምናስበው። ብዙ ጊዜ የፖለቲካ እስር ባለቤት አይኖረውም” ብለዋል።
አቶ ጀሚል አክለውም፣ “አሁንም አቃቢ ህጎች ‘ክስ እጃችን ላይ ምንም የለም’ ሲሉ ሁለት የጊዜ ቀጠሮ ተጠይቆባቸው ‘ይሄ ነው’ ነው ብለው በጥፋትም መልክ ወይም በክስም ቢሆን ያቀረቡት ነገር የለም” ሲሉ አስረድተዋል።
አቶ ጀሚል ሳኒ ስለ ጉዳዩ በዝርዝር ምን አሉ ?
ያንብቡ ፦ https://telegra.ph/Tikvah-Ethiopia-02-06
@tikvahethiopia
የጎጎት ፓርቲ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ጀሚል ሳኒ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል፣ “በአመራር ደረጃ ሦስት ከፍተኛ አመራሮች እስር ላይ ናቸው። ደጋፊዎች የተለያየ ቦታ ይታሰራሉ። ቁጥራቸው አንዱ ሲታሰር ሌላው የመፈታት ሁኔታዎች አሉ” ብለዋል።
“ወደ 10 የሚደርሱ ደጋፊዎችና አባላቶች ታስረዋል” ያሉት ኃላፊው፣ “ኪዚያ በተጨማሪም አካባቢው ላይ የፓርቲያችን አባላቶች ባይሆኑም ወጣቶችን የማሳደድ፣ የማሰር (በተለይ የክልል ጥያቄ ጋር አክቲቭ ሆነው ሲሳተፉ የነበሩትንም የአካባቢው ወጣቶች አሳሳዶ የመያዝ) ሂደቶች አሉ” ሲሉ ተናግረዋል።
የታሰሩ ሰዎችን ለማስፈታት ፓርቲው ምን ያህል ጥረት አድርጓል ተብሎ ለቀረበላቸው ጥያቄም አቶ ጀሚል፣ “አብዛኛው እስሩ ፖለቲካል የሆነ እስር ነው ብለን ነው የምናስበው። ብዙ ጊዜ የፖለቲካ እስር ባለቤት አይኖረውም” ብለዋል።
አቶ ጀሚል አክለውም፣ “አሁንም አቃቢ ህጎች ‘ክስ እጃችን ላይ ምንም የለም’ ሲሉ ሁለት የጊዜ ቀጠሮ ተጠይቆባቸው ‘ይሄ ነው’ ነው ብለው በጥፋትም መልክ ወይም በክስም ቢሆን ያቀረቡት ነገር የለም” ሲሉ አስረድተዋል።
አቶ ጀሚል ሳኒ ስለ ጉዳዩ በዝርዝር ምን አሉ ?
ያንብቡ ፦ https://telegra.ph/Tikvah-Ethiopia-02-06
@tikvahethiopia
#አሁን
የኢፌዴሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 14ኛ መደበኛ ስብሰባውን እያካሄደ ይገኛል።
በስበስባው ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተገኙ ሲሆን በምክር ቤት አባላት ጥያቄዎች እየቀረበላቸው ይገኛሉ።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከምክር ቤት አባላት ለሚቀርብላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ይሰጣሉ።
@tikvahethiopia
የኢፌዴሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 14ኛ መደበኛ ስብሰባውን እያካሄደ ይገኛል።
በስበስባው ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተገኙ ሲሆን በምክር ቤት አባላት ጥያቄዎች እየቀረበላቸው ይገኛሉ።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከምክር ቤት አባላት ለሚቀርብላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ይሰጣሉ።
@tikvahethiopia
#BeledHawo
በደቡባዊ ሶማሊያ ፤ ጌዶ ክልል ፣ በሌደሀዎ በተባለ ወረዳ በታጣቂዎች በተፈጸመ ጥቃት ኢትዮጵያውያን እና አንድ ሶማሊያዊ መገደላቸውን ቢቢሲ ሶማልኛ ዘግቧል።
በዚህ ምክንያት በርካቶች ስጋት ውስጥ መሆናቸው ተነግሯል።
ታጣቂዎቹ ሌሊት ኢትዮጵያውያን ወደ ሚኖሩበት ቤት በመግባት በፈጸሙት ጥቃት 3 ሴቶች እና 3 ወንዶችን ሲገድሉ 1 ሶማሊያዊም መገደላቸው ተነግሯል።
ስማቸው እንዲገለፅ ያልፈለጉ በሶማሊያ የኢትዮጵያውያን ማኅበረሰብ ተወካይ በሰጡት ቃል ፤ ቅዳሜ ሌሊት 6 እሁድ 1 በተለያየ ስራ ላይ የተሰማሩ ኢትዮጵያውያን ተገድለዋል ብለዋል።
" ከተገደሉት መካከል ሁለቱ ሕጻናት ሲሆኑ ፣ እናት እና አባቷ ተገድለውባት ብቻዋን የቀረች ሕጻንም አለች " ሲሉ አክለዋል።
" የተገደሉት ሰዎች ወደ አገራቸው ተመልሰው በሥነ ሥርዓት ቀብራቸው እንዲፈጸም እንፈልጋለን። መንግሥት ይህን ማድረግ ይችላል። ለተገደሉትም ፍትሕ እንዲሰፍንም እንፈልጋለን " ሲሉ አክለዋል።
ጥቃቱ ተከትሎ ኢትዮጵያውያን ስጋት ላይ እንደሆኑና በርካቶች ወደ አገር ቤት መመለስ እንደሚፈልጉም ተናግረዋል።
የበለደሀዎ አስተዳዳሪ አብዲራሺድ አብዲ ፤ ግድያው ሌሊት 9 ሰዓት መፈጸሙን እንደታወቀ አመልክተዋል።
ግድያ መፈፀሙ የታወቀው የአካባቢው የፀጥታ ባልደረቦች የተኩስ ድምጽ ከሰሙ በኋላ ሲሆን 7 ሰዎች ተገድለው መገኘታቸውን አስረድተዋል።
" ማቾቹ በአጠቃላይ ለሥራ የመጡ ስደተኞች ናቸው " ሲሉ ገልጸዋል።
በአካባቢው ሆስፒታል የሚሠራ አንድ ዶክተር በሰጠው ቃል በጥቃቱ የተገደሉ የ6 ኢትዮጵያውያን አስከሬን ወደ ሆስፒታሉ መምጣቱን አረጋግጧል።
በተጨማሪ ጉዳት የደረሰባቸው ሌሎች 6 ሰዎች ሆስፒታል መግባታቸውንም ገልጿል።
ምንም እንኳን እስካሁን ከግድያው ጀርባ ማን እንዳለ ያልታወቀና ኃላፊነት የወሰደም አካል የሌለ ቢሆንም የአካባቢው አስተዳዳሪ " ማስረጃዎች እንደሚጠቁሙት ገዳዮቹ #የአልሸባብ አሸባሪዎች ናቸው " ብለዋል።
" እስካሁን አልተያዙም። ለምን ስደተኞን ዒላማ አደረጉ ለሚለው ጥያቄ፣ ይህ ግድያ በመላው አገሪቱ ከሚፈጸመው ግድያ የሚለይ አይደለም " ሲሉ ተናግረዋል።
መረጃው የቢቢሲ ሶማልኛ አገልግሎት ነው።
@tikvahethiopia
በደቡባዊ ሶማሊያ ፤ ጌዶ ክልል ፣ በሌደሀዎ በተባለ ወረዳ በታጣቂዎች በተፈጸመ ጥቃት ኢትዮጵያውያን እና አንድ ሶማሊያዊ መገደላቸውን ቢቢሲ ሶማልኛ ዘግቧል።
በዚህ ምክንያት በርካቶች ስጋት ውስጥ መሆናቸው ተነግሯል።
ታጣቂዎቹ ሌሊት ኢትዮጵያውያን ወደ ሚኖሩበት ቤት በመግባት በፈጸሙት ጥቃት 3 ሴቶች እና 3 ወንዶችን ሲገድሉ 1 ሶማሊያዊም መገደላቸው ተነግሯል።
ስማቸው እንዲገለፅ ያልፈለጉ በሶማሊያ የኢትዮጵያውያን ማኅበረሰብ ተወካይ በሰጡት ቃል ፤ ቅዳሜ ሌሊት 6 እሁድ 1 በተለያየ ስራ ላይ የተሰማሩ ኢትዮጵያውያን ተገድለዋል ብለዋል።
" ከተገደሉት መካከል ሁለቱ ሕጻናት ሲሆኑ ፣ እናት እና አባቷ ተገድለውባት ብቻዋን የቀረች ሕጻንም አለች " ሲሉ አክለዋል።
" የተገደሉት ሰዎች ወደ አገራቸው ተመልሰው በሥነ ሥርዓት ቀብራቸው እንዲፈጸም እንፈልጋለን። መንግሥት ይህን ማድረግ ይችላል። ለተገደሉትም ፍትሕ እንዲሰፍንም እንፈልጋለን " ሲሉ አክለዋል።
ጥቃቱ ተከትሎ ኢትዮጵያውያን ስጋት ላይ እንደሆኑና በርካቶች ወደ አገር ቤት መመለስ እንደሚፈልጉም ተናግረዋል።
የበለደሀዎ አስተዳዳሪ አብዲራሺድ አብዲ ፤ ግድያው ሌሊት 9 ሰዓት መፈጸሙን እንደታወቀ አመልክተዋል።
ግድያ መፈፀሙ የታወቀው የአካባቢው የፀጥታ ባልደረቦች የተኩስ ድምጽ ከሰሙ በኋላ ሲሆን 7 ሰዎች ተገድለው መገኘታቸውን አስረድተዋል።
" ማቾቹ በአጠቃላይ ለሥራ የመጡ ስደተኞች ናቸው " ሲሉ ገልጸዋል።
በአካባቢው ሆስፒታል የሚሠራ አንድ ዶክተር በሰጠው ቃል በጥቃቱ የተገደሉ የ6 ኢትዮጵያውያን አስከሬን ወደ ሆስፒታሉ መምጣቱን አረጋግጧል።
በተጨማሪ ጉዳት የደረሰባቸው ሌሎች 6 ሰዎች ሆስፒታል መግባታቸውንም ገልጿል።
ምንም እንኳን እስካሁን ከግድያው ጀርባ ማን እንዳለ ያልታወቀና ኃላፊነት የወሰደም አካል የሌለ ቢሆንም የአካባቢው አስተዳዳሪ " ማስረጃዎች እንደሚጠቁሙት ገዳዮቹ #የአልሸባብ አሸባሪዎች ናቸው " ብለዋል።
" እስካሁን አልተያዙም። ለምን ስደተኞን ዒላማ አደረጉ ለሚለው ጥያቄ፣ ይህ ግድያ በመላው አገሪቱ ከሚፈጸመው ግድያ የሚለይ አይደለም " ሲሉ ተናግረዋል።
መረጃው የቢቢሲ ሶማልኛ አገልግሎት ነው።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#አሁን የኢፌዴሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 14ኛ መደበኛ ስብሰባውን እያካሄደ ይገኛል። በስበስባው ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተገኙ ሲሆን በምክር ቤት አባላት ጥያቄዎች እየቀረበላቸው ይገኛሉ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከምክር ቤት አባላት ለሚቀርብላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ይሰጣሉ። @tikvahethiopia
#Update
ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ከተናገሩት መካከል ፦
" ... ዋናው ኢትዮጵያ ውስጥ ያለው ችግር ሥራ አጥነት ነው።
አብዛኛው ሰው cause ኖሮት አይደለም። ሥራ ፍለጋ ይሄዳል ያግታል ብር ይጠይቃል።
ዓላማ መር ትግል ሳይሆን እገታ መር ትግል ነው ያለው።
ይሄን ደግሞ በርከት አድርጎ ሥራ በመፍጠር ወጣቱ ወደ ሥራ እንዲሄድ ማድረግ የመንግስት ዋነኛ ተግባሩ ነው ጥረት እየተደረገ ነው ማጠናከር ይኖርብናል። "
@tikvahethiopia
ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ከተናገሩት መካከል ፦
" ... ዋናው ኢትዮጵያ ውስጥ ያለው ችግር ሥራ አጥነት ነው።
አብዛኛው ሰው cause ኖሮት አይደለም። ሥራ ፍለጋ ይሄዳል ያግታል ብር ይጠይቃል።
ዓላማ መር ትግል ሳይሆን እገታ መር ትግል ነው ያለው።
ይሄን ደግሞ በርከት አድርጎ ሥራ በመፍጠር ወጣቱ ወደ ሥራ እንዲሄድ ማድረግ የመንግስት ዋነኛ ተግባሩ ነው ጥረት እየተደረገ ነው ማጠናከር ይኖርብናል። "
@tikvahethiopia