#ትግራይ
የመኪና አደጋ የአባትና ልጅ ህይወት ቀጠፈ።
ሦስት ተጓዦች ላይ ደግሞ ከባድ ጉዳት ደርሷል።
ዛሬ ጠዋት ጥር 25/2016 ዓ.ም ከዓድዋ ወደ መቐለ 5 ሰዎች ጭኖ ሲጓዝ የነበረ ባለቤትነቱ የመሰቦ ስሚንቶ ፋብሪካ የሆነ ትዮታ ዳብል ጋቢና መኪና ተምቤን ልዩ ቦታ " መነወ " በደረሰበት የመገልበጥ አደጋ በውስጡ የነበሩ ሁሉም ተጓዦች ላይ የሞትና የጉዳት አደጋ አድርሷል።
በመኪናው የነበሩ የመሰቦ ስሚንቶ ፋብሪካ ማርኬቲንግ መምሪያ ሃላፊ ከነልጃቸው ህይወታቸው ሲያልፍ ፤ ከፍተኛ ጉዳት የደረሰባቸው 3 ተጓዦች ደግም በመቐለ ዓይደር ሆስፒታል የህክምና እርዳታ እየተደረገላቸው እንደሚገኝ ለማወቅ ተችሏል።
የራስ አሉላ አባነጋ የትውልድ ቦታ የሆነው " መነወ " ጠመዝማዛ ቦታና ተደጋጋሚ የመኪና አደጋ የሚከሰትበት በመሆኑ መንገዱ ትኩረት እንደሚያሻው አደጋው አስመልክተው የሚሰጡ የህዝብ አስተያየቶች ያመለክታሉ።
የመኪና አደጋው መንስኤ ምን እንደሆነ በመጣራት ላይ እንደሚገኝ ፓሊስ ትራፊክ ገልጿል።
መረጃውን የመቐለ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ነው የላከው።
@tikvahethiopia
የመኪና አደጋ የአባትና ልጅ ህይወት ቀጠፈ።
ሦስት ተጓዦች ላይ ደግሞ ከባድ ጉዳት ደርሷል።
ዛሬ ጠዋት ጥር 25/2016 ዓ.ም ከዓድዋ ወደ መቐለ 5 ሰዎች ጭኖ ሲጓዝ የነበረ ባለቤትነቱ የመሰቦ ስሚንቶ ፋብሪካ የሆነ ትዮታ ዳብል ጋቢና መኪና ተምቤን ልዩ ቦታ " መነወ " በደረሰበት የመገልበጥ አደጋ በውስጡ የነበሩ ሁሉም ተጓዦች ላይ የሞትና የጉዳት አደጋ አድርሷል።
በመኪናው የነበሩ የመሰቦ ስሚንቶ ፋብሪካ ማርኬቲንግ መምሪያ ሃላፊ ከነልጃቸው ህይወታቸው ሲያልፍ ፤ ከፍተኛ ጉዳት የደረሰባቸው 3 ተጓዦች ደግም በመቐለ ዓይደር ሆስፒታል የህክምና እርዳታ እየተደረገላቸው እንደሚገኝ ለማወቅ ተችሏል።
የራስ አሉላ አባነጋ የትውልድ ቦታ የሆነው " መነወ " ጠመዝማዛ ቦታና ተደጋጋሚ የመኪና አደጋ የሚከሰትበት በመሆኑ መንገዱ ትኩረት እንደሚያሻው አደጋው አስመልክተው የሚሰጡ የህዝብ አስተያየቶች ያመለክታሉ።
የመኪና አደጋው መንስኤ ምን እንደሆነ በመጣራት ላይ እንደሚገኝ ፓሊስ ትራፊክ ገልጿል።
መረጃውን የመቐለ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ነው የላከው።
@tikvahethiopia
M-PESA
ሁለተኛና ሦስተኛ ዙር ‘ተረክ በ M-PESA’ መርሀ ግብር አሸናፊዎች መሸለማቸውን ድርጅቱ አስታወቀ።
በሁለተኛውና ሦስተኛው ዙር የ’ተርክ በ M-PESA’ ሽልማት መርሀ ግብር ከመኪናው በተጨማሪ እድለኛ ደንበኞች አራት ባጃጆች፣ 360 ስልኮችና በሺህዎች የሚቆጠሩ የአየር ሰዓት (በእያንዳንዱ ሁለቱም ዙሮች) ተሸልመዋል ተብሏል።
ሦስት መኪናዎች፣ 12 ባጃጆች፣ 1,080 ስልኮች እና በሺህዎች የሚቆጠሩ ሽልማቶች ለእድለኞች በቀጣይ (እስከ መጋቢት 2 ቀን 2016 ዓ.ም) እንደሚሰጡ ድርጅቱ ተመላክቷል።
ደንበኞች በአንድ ቀን የሚደርሳቸው ከፍተኛ የእጣ ብዛት 10 ሲሆን፣ "ይህም በየእለቱ፣ በሁለት ሳምንት አንዴ እና በወር አንዴ የሚወጡ ሽልማቶችን በሚያስገኘው እጣ አወጣጥ ውስጥ ተሳታፊ እንዲሆኑ ያስችላችዋል" ብሏል ድርጅቱ።
ደንበኞች፣ ወኪሎች እና ነጋዴዎች በM-PESA ለሚያደርጉት ለእያንዳንዱ የ20 ብር ግብይት አንድ እጣ በአጭር የስልክ መልእክት እንደሚላክላቸው፣ M-PESAን መጠቀም በመጀመራቸው አምስት እጣ እንደሚያገኙ ተነግራል።
M-PESA ሳፋሪኮም አሸናፊዎችን በ+251-700 700 700 ብቻ በመደወል እንዴት ሽልማታቸውን መውሰድ እንደሚችሉ ድርጅቱ አብስሯል።
እንደ ገለጻው ከሆነ፣ ደንበኞች የአየር ሰዓት ሽልማት ሲደርሳቸው ደግሞ ከተረክ በM-PESA አጭር የጽሁፍ መልእክት ይደርሳቸውና ወዲያው የአየር ሰዓታቸው የሚሞላ ይሆናል።
@tikvahethiopia
ሁለተኛና ሦስተኛ ዙር ‘ተረክ በ M-PESA’ መርሀ ግብር አሸናፊዎች መሸለማቸውን ድርጅቱ አስታወቀ።
በሁለተኛውና ሦስተኛው ዙር የ’ተርክ በ M-PESA’ ሽልማት መርሀ ግብር ከመኪናው በተጨማሪ እድለኛ ደንበኞች አራት ባጃጆች፣ 360 ስልኮችና በሺህዎች የሚቆጠሩ የአየር ሰዓት (በእያንዳንዱ ሁለቱም ዙሮች) ተሸልመዋል ተብሏል።
ሦስት መኪናዎች፣ 12 ባጃጆች፣ 1,080 ስልኮች እና በሺህዎች የሚቆጠሩ ሽልማቶች ለእድለኞች በቀጣይ (እስከ መጋቢት 2 ቀን 2016 ዓ.ም) እንደሚሰጡ ድርጅቱ ተመላክቷል።
ደንበኞች በአንድ ቀን የሚደርሳቸው ከፍተኛ የእጣ ብዛት 10 ሲሆን፣ "ይህም በየእለቱ፣ በሁለት ሳምንት አንዴ እና በወር አንዴ የሚወጡ ሽልማቶችን በሚያስገኘው እጣ አወጣጥ ውስጥ ተሳታፊ እንዲሆኑ ያስችላችዋል" ብሏል ድርጅቱ።
ደንበኞች፣ ወኪሎች እና ነጋዴዎች በM-PESA ለሚያደርጉት ለእያንዳንዱ የ20 ብር ግብይት አንድ እጣ በአጭር የስልክ መልእክት እንደሚላክላቸው፣ M-PESAን መጠቀም በመጀመራቸው አምስት እጣ እንደሚያገኙ ተነግራል።
M-PESA ሳፋሪኮም አሸናፊዎችን በ+251-700 700 700 ብቻ በመደወል እንዴት ሽልማታቸውን መውሰድ እንደሚችሉ ድርጅቱ አብስሯል።
እንደ ገለጻው ከሆነ፣ ደንበኞች የአየር ሰዓት ሽልማት ሲደርሳቸው ደግሞ ከተረክ በM-PESA አጭር የጽሁፍ መልእክት ይደርሳቸውና ወዲያው የአየር ሰዓታቸው የሚሞላ ይሆናል።
@tikvahethiopia
#Amhara #Merawi
በአማራ ክልል ፤ በየጊዜው በተለያዩ አካባቢዎች ላይ በመንግሥት የፀጥታ ኃይል መከላከያ እና በ " ፋኖ " ታጣቂ ኃይሎች መካከል ግጭቶች ይደረጋሉ።
በእነዚህ ግጭቶችም በሁለቱም በኩል ከሚሞተው የግጭቱ ተካፋይ ባለፈ ንፁሃን ሰዎች ሰለባ እየሆኑ እንዳለ በተደጋጋሚ ተገልጿል።
ምንም እንኳን #መንግሥት ፤ " ከእውነታው ያፈነገጠ እና ሚዛናዊነት የጎደለው " ብሎ ቢያጣጥለውም የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮኒሽን (#ኢሰመኮ) ይፋ አድርጎት በነበረው ሪፖርት በክልሉ ፦
- የአንድ ዓመት ከሰባት ወር #ሕፃንን ጨምሮ በርካታ ሲቪል ሰዎች በድሮን መገደላቸው / የአካል ጉዳት እንደደረሰባቸው።
- በከባድ መሣሪያ ድብደባ ምክንያት #ሲቪል_ሰዎች ላይ የሞትና የአካል ጉዳት መድረሱ።
- በመንግሥት የጸጥታ ኃይል አባላት #ከሕግ_ውጪ የሆኑ ግድያዎች እንደሚፈፀሙ።
- ከዚህ ቀደም ግጭቶች በተካሄደባቸው አካባቢዎች የመንግሥት የጸጥታ አካላት በመንገድ ላይ ወይም ቤት ለቤት ፍተሻ በማድረግ ከያዟቸው በርካታ ሲቪል ሰዎች ውስጥ ፦
➡" ፋኖን ትደግፋላችሁ "
➡" ለፋኖ መረጃ ትሰጣላችሁ "
➡" መሣሪያ አምጡ "
➡ " የተኩስ ድምጽ ስለተሰማበት አቅጣጫ መረጃ ስጡ " በሚልና ይህንን በመሰሉ ምክንያቶች ከሕግ ውጭ የሆኑ በርካታ #ግድያዎች መፈጸማቸውን በይፋ ማሳወቁ አይዘነጋም።
ከሰሞኑን ዳግሞ በሰሜን ጎጃም ዞን መርዓዊ ከተማ በመከላከያ ሠራዊት እና በፋኖ ታጣቂዎች መካከል፣ ሰኞ ጥር 20/2016 ዓ/ም የነበረውን ውጊያ ተከትሎ በርካታ ሰዎች መገደላቸው ተሰምቷል።
አንድ የአካባቢው ነዋሪ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ገለጻ ፤ በሰሞኑ ተኩስ እሳቸው የሚያውቋቸው ብቻ 15 ወጣቶች መገደላቸውን ተናግረዋል።
ከዚህም ባለፈ ግን ፤ " የሟቾቹን ቁጥር በዚህ ወቅት ለመግለጽ መሞከር የጥቃቱን አድማስ ያሳንዋል እንጂ አይገለጸውም" ብለዋል።
እኚሁ ነዋሪ በግፍ የተገደሉ ንጹሐን ሰዎችን ቁጥር በሂደት እንጂ አሁን ሁሉንም ማወቅ እንደማይቻል ገልጸው ፤ " የዚህ ህዝብ ጭፋጨፋ ግን መቼ ነው የሚያበቃው? " ሲሉ ጠይቀዋል።
በሌላ በኩል ለቢቢሲ አማርኛው አገልግሎት ቃላቸውን የሰጡ ነዋሪዎች፣ የሆስፒታል ሰዎችና የአይን እማኞች በከተማው ከ50 በላይ ሰዎች መገደላቸውን ተናግረዋል።
አብዛኞቹ ነዋሪዎች ግድያው የተፈጸመው በቤታቸው እና በመንገድ ላይ በተገኙ ሰላማዊ ሰዎች ላይ መሆኑን ተናግረዋል።
አንድ የህክምና ባለሙያ 13ት ሰዎች ከአስፓልት ዳር መገደላቸውን እንደሚያውቁ ተናግረው በአጠቃላይ በከተማዋ በዚያ ዕለት 85 ሰዎች መገደላቸውን አመልክተዋል።
አንድ የአይን እማኝ በርካታ ቀብሮች ላይ መገኘታቸውን ጠቅሰው የሟቾችን ቁጥር " ከ100 በላይ ነው " ብለዋል። ጥቃቱ በተፈጸመ ማግስት ጠዋት ላይ 48 አስከሬን መቆጠራቸውን ተናግረው ፤ " ከማርዘነብ ሆቴል እስከ በረድ ወንዝ ድረስ ግራ እና ቀኝ አስከሬን ብቻ ነበር " ብለዋል።
የሟቾችን ቁጥር 115 ገደማ የሚያደርሱ አንድ የዐይን እማኝ ደግሞ መከላከያ ከተማዋን ከተቆጣጠረ በኋላ ስታዲየም እና ጤና ጣቢያ በተባሉ ሰፈሮች " ከ6 ዓመት ህጻን እስከ 75 ዓመት አዛውንት " ድረስ ግድያ ተፈጽሟል ብለዋል።
የሆስፒታል ሠራተኛ የሆኑት የዐይን እማኝ በከተማዋ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል የ6 ወር ነፍሰ ጡርን ጨምሮ 25 ሰዎች ቆስለው መጥተው " የተረፈ የለም " ሲሉ ገልጸዋል።
" 24ቱ ሆስፒታል የመጡት ሞተው ነው። አንዲት የ6 ወር ነፍሰ ጡር ሴት ከነ ነፍሷ መጥታ ሆስፒታል እንደደረሰች አርፋለች። አጠቃላይ 25 ነበር የመጡት " ብለዋል።
ቃላቸውን የሰጡ ነዋሪዎች ፤ #በመርዓዊ_አስተዳደር ህንጻ ውስጥ በነበሩት የመከላከያ ሰራዊት አባላት ላይ የፋኖ ታጣቂዎች ሰኞ ጠዋት ድንገተኛ ጥቃት ፈፀመው እንደነበርና ለዚህ ምላሽ " የበቀል እርምጃ " በመወሰዱ ነው ለበርካታ ሰዎች ግድያ ምክንያት የሆነው ብለዋል።
ስለ ግድያው ምን ምላሽ እንዳለቸው ቲክቫህ ኢትዮጵያ ጥያቄ ያቀረበላቸው የአማራ ክልል ኮሚዩኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ መንገሻ ፈንታው (ዶ/ር)፣ " ስብሰባ ላይ ነኝ መልሸ ልደውል " ብለዋል።
መንገሻ (ዶ/ር) ይህን ያሉት እንዲያብራሩ የተፈለገውን ጥያቄ በዝርዝር ከሰሙ በኋላ ሲሆን፣ በድጋሚም ስልክ ሲደወል ስልክ ለማንሳት ፈቃደኛ አልሆኑም።
እንዲሁም፣ " እባክዎ ስልክዎን ያንሱና በኮሚዩኒኬሽን በኩል ያለውን የመርዓዊ ጉዳይ ማብራሪያ በመስጠት ኃላፊነትዎን ይወጡ " የሚል የፅሑፍ መልዕክት (SMS) ቢላክላቸውም ምላሽ ሳይሰጡ ቀርተዋል።
በተጨማሪ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ፦
* የክልሉ የኮሚዩኒኬሽን ምክትል፣
* የክልሉና የሰሜን ጎጃም ዞን ኮማንድ ፖስት፣
* የክልሉ ሰላምና ጸጥታ ቢሮ ስለጉዳዩ ምን ምላሽ እንዳለቸው ለማወቅ እና ሃሳባቸውን ለማካተት ስልክ ቢደውልም ለማንሳት ፈቃደኛ ባለመሆናቸው ሀሳባቸውን ማካተት አልተቻለም።
የኢትዮጵያ ሰብዓዊ ኮሚሽን ( #ኢሰመኮ ) ምክትል ኮሚሽነር ራኬብ መሰለ ፤ " መረጃው ደርሶናል (የመርዓዊ ጉዳይ) ። እያረጋገጥን ነው " ብለዋል።
አክለው ፣ "የጸጥታ ጉዳይ ስለሆነ ትንሽ መንቀሳቀስና መረጃ መሰብሰብ አስቸጋሪ ሊሆን ስለሚችል ሊዘገይ ይችላል። ግን እያጣራን ነው" ሲሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አረጋግጠዋል።
@tikvahethiopia
በአማራ ክልል ፤ በየጊዜው በተለያዩ አካባቢዎች ላይ በመንግሥት የፀጥታ ኃይል መከላከያ እና በ " ፋኖ " ታጣቂ ኃይሎች መካከል ግጭቶች ይደረጋሉ።
በእነዚህ ግጭቶችም በሁለቱም በኩል ከሚሞተው የግጭቱ ተካፋይ ባለፈ ንፁሃን ሰዎች ሰለባ እየሆኑ እንዳለ በተደጋጋሚ ተገልጿል።
ምንም እንኳን #መንግሥት ፤ " ከእውነታው ያፈነገጠ እና ሚዛናዊነት የጎደለው " ብሎ ቢያጣጥለውም የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮኒሽን (#ኢሰመኮ) ይፋ አድርጎት በነበረው ሪፖርት በክልሉ ፦
- የአንድ ዓመት ከሰባት ወር #ሕፃንን ጨምሮ በርካታ ሲቪል ሰዎች በድሮን መገደላቸው / የአካል ጉዳት እንደደረሰባቸው።
- በከባድ መሣሪያ ድብደባ ምክንያት #ሲቪል_ሰዎች ላይ የሞትና የአካል ጉዳት መድረሱ።
- በመንግሥት የጸጥታ ኃይል አባላት #ከሕግ_ውጪ የሆኑ ግድያዎች እንደሚፈፀሙ።
- ከዚህ ቀደም ግጭቶች በተካሄደባቸው አካባቢዎች የመንግሥት የጸጥታ አካላት በመንገድ ላይ ወይም ቤት ለቤት ፍተሻ በማድረግ ከያዟቸው በርካታ ሲቪል ሰዎች ውስጥ ፦
➡" ፋኖን ትደግፋላችሁ "
➡" ለፋኖ መረጃ ትሰጣላችሁ "
➡" መሣሪያ አምጡ "
➡ " የተኩስ ድምጽ ስለተሰማበት አቅጣጫ መረጃ ስጡ " በሚልና ይህንን በመሰሉ ምክንያቶች ከሕግ ውጭ የሆኑ በርካታ #ግድያዎች መፈጸማቸውን በይፋ ማሳወቁ አይዘነጋም።
ከሰሞኑን ዳግሞ በሰሜን ጎጃም ዞን መርዓዊ ከተማ በመከላከያ ሠራዊት እና በፋኖ ታጣቂዎች መካከል፣ ሰኞ ጥር 20/2016 ዓ/ም የነበረውን ውጊያ ተከትሎ በርካታ ሰዎች መገደላቸው ተሰምቷል።
አንድ የአካባቢው ነዋሪ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ገለጻ ፤ በሰሞኑ ተኩስ እሳቸው የሚያውቋቸው ብቻ 15 ወጣቶች መገደላቸውን ተናግረዋል።
ከዚህም ባለፈ ግን ፤ " የሟቾቹን ቁጥር በዚህ ወቅት ለመግለጽ መሞከር የጥቃቱን አድማስ ያሳንዋል እንጂ አይገለጸውም" ብለዋል።
እኚሁ ነዋሪ በግፍ የተገደሉ ንጹሐን ሰዎችን ቁጥር በሂደት እንጂ አሁን ሁሉንም ማወቅ እንደማይቻል ገልጸው ፤ " የዚህ ህዝብ ጭፋጨፋ ግን መቼ ነው የሚያበቃው? " ሲሉ ጠይቀዋል።
በሌላ በኩል ለቢቢሲ አማርኛው አገልግሎት ቃላቸውን የሰጡ ነዋሪዎች፣ የሆስፒታል ሰዎችና የአይን እማኞች በከተማው ከ50 በላይ ሰዎች መገደላቸውን ተናግረዋል።
አብዛኞቹ ነዋሪዎች ግድያው የተፈጸመው በቤታቸው እና በመንገድ ላይ በተገኙ ሰላማዊ ሰዎች ላይ መሆኑን ተናግረዋል።
አንድ የህክምና ባለሙያ 13ት ሰዎች ከአስፓልት ዳር መገደላቸውን እንደሚያውቁ ተናግረው በአጠቃላይ በከተማዋ በዚያ ዕለት 85 ሰዎች መገደላቸውን አመልክተዋል።
አንድ የአይን እማኝ በርካታ ቀብሮች ላይ መገኘታቸውን ጠቅሰው የሟቾችን ቁጥር " ከ100 በላይ ነው " ብለዋል። ጥቃቱ በተፈጸመ ማግስት ጠዋት ላይ 48 አስከሬን መቆጠራቸውን ተናግረው ፤ " ከማርዘነብ ሆቴል እስከ በረድ ወንዝ ድረስ ግራ እና ቀኝ አስከሬን ብቻ ነበር " ብለዋል።
የሟቾችን ቁጥር 115 ገደማ የሚያደርሱ አንድ የዐይን እማኝ ደግሞ መከላከያ ከተማዋን ከተቆጣጠረ በኋላ ስታዲየም እና ጤና ጣቢያ በተባሉ ሰፈሮች " ከ6 ዓመት ህጻን እስከ 75 ዓመት አዛውንት " ድረስ ግድያ ተፈጽሟል ብለዋል።
የሆስፒታል ሠራተኛ የሆኑት የዐይን እማኝ በከተማዋ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል የ6 ወር ነፍሰ ጡርን ጨምሮ 25 ሰዎች ቆስለው መጥተው " የተረፈ የለም " ሲሉ ገልጸዋል።
" 24ቱ ሆስፒታል የመጡት ሞተው ነው። አንዲት የ6 ወር ነፍሰ ጡር ሴት ከነ ነፍሷ መጥታ ሆስፒታል እንደደረሰች አርፋለች። አጠቃላይ 25 ነበር የመጡት " ብለዋል።
ቃላቸውን የሰጡ ነዋሪዎች ፤ #በመርዓዊ_አስተዳደር ህንጻ ውስጥ በነበሩት የመከላከያ ሰራዊት አባላት ላይ የፋኖ ታጣቂዎች ሰኞ ጠዋት ድንገተኛ ጥቃት ፈፀመው እንደነበርና ለዚህ ምላሽ " የበቀል እርምጃ " በመወሰዱ ነው ለበርካታ ሰዎች ግድያ ምክንያት የሆነው ብለዋል።
ስለ ግድያው ምን ምላሽ እንዳለቸው ቲክቫህ ኢትዮጵያ ጥያቄ ያቀረበላቸው የአማራ ክልል ኮሚዩኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ መንገሻ ፈንታው (ዶ/ር)፣ " ስብሰባ ላይ ነኝ መልሸ ልደውል " ብለዋል።
መንገሻ (ዶ/ር) ይህን ያሉት እንዲያብራሩ የተፈለገውን ጥያቄ በዝርዝር ከሰሙ በኋላ ሲሆን፣ በድጋሚም ስልክ ሲደወል ስልክ ለማንሳት ፈቃደኛ አልሆኑም።
እንዲሁም፣ " እባክዎ ስልክዎን ያንሱና በኮሚዩኒኬሽን በኩል ያለውን የመርዓዊ ጉዳይ ማብራሪያ በመስጠት ኃላፊነትዎን ይወጡ " የሚል የፅሑፍ መልዕክት (SMS) ቢላክላቸውም ምላሽ ሳይሰጡ ቀርተዋል።
በተጨማሪ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ፦
* የክልሉ የኮሚዩኒኬሽን ምክትል፣
* የክልሉና የሰሜን ጎጃም ዞን ኮማንድ ፖስት፣
* የክልሉ ሰላምና ጸጥታ ቢሮ ስለጉዳዩ ምን ምላሽ እንዳለቸው ለማወቅ እና ሃሳባቸውን ለማካተት ስልክ ቢደውልም ለማንሳት ፈቃደኛ ባለመሆናቸው ሀሳባቸውን ማካተት አልተቻለም።
የኢትዮጵያ ሰብዓዊ ኮሚሽን ( #ኢሰመኮ ) ምክትል ኮሚሽነር ራኬብ መሰለ ፤ " መረጃው ደርሶናል (የመርዓዊ ጉዳይ) ። እያረጋገጥን ነው " ብለዋል።
አክለው ፣ "የጸጥታ ጉዳይ ስለሆነ ትንሽ መንቀሳቀስና መረጃ መሰብሰብ አስቸጋሪ ሊሆን ስለሚችል ሊዘገይ ይችላል። ግን እያጣራን ነው" ሲሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አረጋግጠዋል።
@tikvahethiopia
ከ7.5 ሚሊዮን ብር በላይ ወጥቶበታል የተባለ ፊልም ሊመረቅ ነዉ።
የሲዳማን ህዝብ ባህላዊ የግጭት አፈታት እና የውይይት ባህልን በሰፊዉ ይዳስሳል የተባለው " አፊኒ " የተሰኘ ፊልም የካቲት 2 እና 3 በሀዋሳ ከተማ እንደሚመረቅ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ሰምቷል።
ፊልሙን በፋይናንስ የደገፈው የክልሉ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ መሆኑንም ለመረዳት ተችሏል።
የፊልሙ ደራሲና ተዋናይ የሆኑት አቶ እለፋቸዉ ብርሀኑ (ልኡል) ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ጋር በነበራቸዉ ቆይታ " ፊልሙ የሲዳማ ባህላዊ የግጭት አፈታትና የንግግር ባህል የሆነዉን አፊኒ በዓለም ላይ የማስተዋወቅ አቅም ያለዉ ነው " ብለዋል።
ለዚህም ሲባል የፊልሙን ደረጃ ዓለማቀፍ ለማድረግ ታስቦ መሰራቱን ገልጸዋል።
" ፊልሙ በፋይናንስ በሰዉ ኃይልና በቴክኒክ የተሟላ ሆኖ መሰራቱ አስደስቶኛል የሚሉት " አቶ እለፋቸው " ለዚህም ከ7.5 ሚሊየን ብር በላይ ወጥቶበታል " ብለዋል።
" ተዋናይ ግሩም ኤርሚያስ እና ተዋናይ አማኑኤል የመሳሰሉ አርቲስቶች የሲዳማን ውብና አስተማሪ የግጭት አፈታት ባህል የሚገልጽ የድርሰት ሀሳብ ውበትና ጉልበት ሰጥተውታል " ሲሉም አክለዋል።
በሌላ በኩል ፤ ቲክቫህ ኢትዮጵያ የምርቃቱን ጉዳይ እና በማህበራዊ ሚዲያ ተመድቧል እየተባለ ስለሚነገረው በሚሊዮኖች ገንዘብ መጠን ጠይቋል።
አቶ እለፋቸው ብርሃኑ ፤ " ከፊልሙ ተዋንያን ባለሙያዎችና ፊልሙን በፋይናንስ ከደገፈዉ የክልሉ ባህል እና ቱሪዝም ቢሮ የተወጣጡ የምረቃ ኮሜቲ አባላት በቅርቡ ተቋማዊ ገለጻ ያደርጋሉ " ያሉ ሲሆን ለጊዜዉ ፊልሙ የካቲት 2 እና 3 ከመመረቁ ዉጭ ዝርዝር መረጃ ከመስጠት ተቆጥበዋል።
መረጃዉ የሀዋሳዉ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ነዉ።
@tikvahethiopia
የሲዳማን ህዝብ ባህላዊ የግጭት አፈታት እና የውይይት ባህልን በሰፊዉ ይዳስሳል የተባለው " አፊኒ " የተሰኘ ፊልም የካቲት 2 እና 3 በሀዋሳ ከተማ እንደሚመረቅ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ሰምቷል።
ፊልሙን በፋይናንስ የደገፈው የክልሉ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ መሆኑንም ለመረዳት ተችሏል።
የፊልሙ ደራሲና ተዋናይ የሆኑት አቶ እለፋቸዉ ብርሀኑ (ልኡል) ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ጋር በነበራቸዉ ቆይታ " ፊልሙ የሲዳማ ባህላዊ የግጭት አፈታትና የንግግር ባህል የሆነዉን አፊኒ በዓለም ላይ የማስተዋወቅ አቅም ያለዉ ነው " ብለዋል።
ለዚህም ሲባል የፊልሙን ደረጃ ዓለማቀፍ ለማድረግ ታስቦ መሰራቱን ገልጸዋል።
" ፊልሙ በፋይናንስ በሰዉ ኃይልና በቴክኒክ የተሟላ ሆኖ መሰራቱ አስደስቶኛል የሚሉት " አቶ እለፋቸው " ለዚህም ከ7.5 ሚሊየን ብር በላይ ወጥቶበታል " ብለዋል።
" ተዋናይ ግሩም ኤርሚያስ እና ተዋናይ አማኑኤል የመሳሰሉ አርቲስቶች የሲዳማን ውብና አስተማሪ የግጭት አፈታት ባህል የሚገልጽ የድርሰት ሀሳብ ውበትና ጉልበት ሰጥተውታል " ሲሉም አክለዋል።
በሌላ በኩል ፤ ቲክቫህ ኢትዮጵያ የምርቃቱን ጉዳይ እና በማህበራዊ ሚዲያ ተመድቧል እየተባለ ስለሚነገረው በሚሊዮኖች ገንዘብ መጠን ጠይቋል።
አቶ እለፋቸው ብርሃኑ ፤ " ከፊልሙ ተዋንያን ባለሙያዎችና ፊልሙን በፋይናንስ ከደገፈዉ የክልሉ ባህል እና ቱሪዝም ቢሮ የተወጣጡ የምረቃ ኮሜቲ አባላት በቅርቡ ተቋማዊ ገለጻ ያደርጋሉ " ያሉ ሲሆን ለጊዜዉ ፊልሙ የካቲት 2 እና 3 ከመመረቁ ዉጭ ዝርዝር መረጃ ከመስጠት ተቆጥበዋል።
መረጃዉ የሀዋሳዉ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ነዉ።
@tikvahethiopia
#ጥቆማ
የአዲስ አበባ ቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን ፤ የመኖሪያ እና የንግድ ቤቶችን በጨረታ ለሽያጭ አቅርቧል።
ኮርፖሬሽኑ ፤ " ያለብኝን የፋይናንስ እጥረት በመፍታት ተጨማሪ ወጪ ቆጣቢ ቤቶችን ገንብቼ ዜጎችን ተጠቃሚ ለማድረግ እንድችል ከዲዛይን ግንባታ ቢሮ ጋር በመሆን በመንግስት በተመደበ ካፒታል በጀት በተለያዩ ክፍለ ከተሞች ተገንብተው #የተጠናቀቁ ፦
➡️ 3,146 የመኖሪያ ቤቶችን
➡️ 306 የንግድ ቤቶችን በድምሩ 3,452 ቤቶችን ባሉበት ሁኔታ በጨረታ አወዳድሬ በሽያጭ ማስተላለፍ እፈልጋለሁ " ሲል አሳውቋል።
ማንኛውም ለጨረታ የቀረቡ የመኖሪያ እና የንግድ ቤቶችን ለመግዛት የሚፈልግ ሁሉ ማንነቱን የሚገልጽ መታወቂያ በመያዝ የጨረታ ሰነድ ከ27/05/2016 ዓ.ም ጀምሮ እስከ 20/06/2016 ዓ.ም ድረስ ቅዳሜን እስከ 11፡00 ሰአት እና እሁድ ግማሽ ቀን ጨምሮ ዘወትር በስራ ቀናት ከጠዋቱ 1፡30 እስከ ማታ 1፡30 ድረስ በመቅረብ የማይመለስ ብር 1000.00 (አንድ ሺህ) በመክፈል የጨረታ ሰነዱ መግዛት ይችላል ተብሏል።
የሰነድ መሸጫ ቦታ ከላይ ባለው ሰንጠረዥ ተመላክቷል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ይህ መረጃ ከአዲስ አበባ ቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን ማግኘቱን ያሳውቃል።
@tikvahethiopia
የአዲስ አበባ ቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን ፤ የመኖሪያ እና የንግድ ቤቶችን በጨረታ ለሽያጭ አቅርቧል።
ኮርፖሬሽኑ ፤ " ያለብኝን የፋይናንስ እጥረት በመፍታት ተጨማሪ ወጪ ቆጣቢ ቤቶችን ገንብቼ ዜጎችን ተጠቃሚ ለማድረግ እንድችል ከዲዛይን ግንባታ ቢሮ ጋር በመሆን በመንግስት በተመደበ ካፒታል በጀት በተለያዩ ክፍለ ከተሞች ተገንብተው #የተጠናቀቁ ፦
➡️ 3,146 የመኖሪያ ቤቶችን
➡️ 306 የንግድ ቤቶችን በድምሩ 3,452 ቤቶችን ባሉበት ሁኔታ በጨረታ አወዳድሬ በሽያጭ ማስተላለፍ እፈልጋለሁ " ሲል አሳውቋል።
ማንኛውም ለጨረታ የቀረቡ የመኖሪያ እና የንግድ ቤቶችን ለመግዛት የሚፈልግ ሁሉ ማንነቱን የሚገልጽ መታወቂያ በመያዝ የጨረታ ሰነድ ከ27/05/2016 ዓ.ም ጀምሮ እስከ 20/06/2016 ዓ.ም ድረስ ቅዳሜን እስከ 11፡00 ሰአት እና እሁድ ግማሽ ቀን ጨምሮ ዘወትር በስራ ቀናት ከጠዋቱ 1፡30 እስከ ማታ 1፡30 ድረስ በመቅረብ የማይመለስ ብር 1000.00 (አንድ ሺህ) በመክፈል የጨረታ ሰነዱ መግዛት ይችላል ተብሏል።
የሰነድ መሸጫ ቦታ ከላይ ባለው ሰንጠረዥ ተመላክቷል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ይህ መረጃ ከአዲስ አበባ ቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን ማግኘቱን ያሳውቃል።
@tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
📣 ሰምተዋል?
በማንኪያ ሲሉ በጭልፋ ፤ በጭልፋ ሲሉ በአካፋ!
👉 ከጥር 6 እስከ መጋቢት 22 ድረስ ከሚጠቀሙት ፓኬጅ ከፍ ካሉ በእኛ ወጪ ወደ ቀጣዩ ትልቅ ፓኬጅ ለአንድ ወር ከፍ ይላሉ!
⏰ ይህ አገልግሎት ክፍያ ከፈፀሙ ከ48 ሰዓት በኋላ ተግባራዊ ይሆናል።
*ደንብና ሁኔታዎች ተፈፃሚነት አላቸው።
የዲኤስቲቪ አገልግሎቶችን ለማግኘት ከታች ያለውን
የMyDStv Telegram ሊንክ ይጫኑ!
👇👇👇
https://bit.ly/2WDuBLk
#ሁሉምያለውእኛጋርነው #DStvEthiopia #StepUp
በማንኪያ ሲሉ በጭልፋ ፤ በጭልፋ ሲሉ በአካፋ!
👉 ከጥር 6 እስከ መጋቢት 22 ድረስ ከሚጠቀሙት ፓኬጅ ከፍ ካሉ በእኛ ወጪ ወደ ቀጣዩ ትልቅ ፓኬጅ ለአንድ ወር ከፍ ይላሉ!
⏰ ይህ አገልግሎት ክፍያ ከፈፀሙ ከ48 ሰዓት በኋላ ተግባራዊ ይሆናል።
*ደንብና ሁኔታዎች ተፈፃሚነት አላቸው።
የዲኤስቲቪ አገልግሎቶችን ለማግኘት ከታች ያለውን
የMyDStv Telegram ሊንክ ይጫኑ!
👇👇👇
https://bit.ly/2WDuBLk
#ሁሉምያለውእኛጋርነው #DStvEthiopia #StepUp
#CBE
በአዲስ መልክ!
****
የነበሩትን አሻሽሎ፣
በርካታ አዳዲስ ነገሮችን አካቶ፣
ለአጠቃቀም ቀሎ፣
ፍጥነት እና ምቾት ጨምሮ፣
በአዲስ መልክ በቀረበው የሲቢኢ ብር መተግበሪያ ይጠቀሙ!
****
አሁኑኑ ወደ Google Play ወይም App Store በመግባት የሲቢኢ ብር መተግበሪያዎን ያዘምኑ/ ይጫኑ!
• ለአንድሮይድ ስልኮች፡
https://play.google.com/store/apps/details?id=prod.cbe.birr
• ለአፕል ስልኮች፡
https://apps.apple.com/us/app/cbebirr/id1600841787
***
የፌስቡክ እና የቴሌግራም ገፆቻችንን ይቀላቀሉ!
• Facebook፡- https://www.facebook.com/combanketh
• Telegram፡- https://t.iss.one/combankethofficial
በአዲስ መልክ!
****
የነበሩትን አሻሽሎ፣
በርካታ አዳዲስ ነገሮችን አካቶ፣
ለአጠቃቀም ቀሎ፣
ፍጥነት እና ምቾት ጨምሮ፣
በአዲስ መልክ በቀረበው የሲቢኢ ብር መተግበሪያ ይጠቀሙ!
****
አሁኑኑ ወደ Google Play ወይም App Store በመግባት የሲቢኢ ብር መተግበሪያዎን ያዘምኑ/ ይጫኑ!
• ለአንድሮይድ ስልኮች፡
https://play.google.com/store/apps/details?id=prod.cbe.birr
• ለአፕል ስልኮች፡
https://apps.apple.com/us/app/cbebirr/id1600841787
***
የፌስቡክ እና የቴሌግራም ገፆቻችንን ይቀላቀሉ!
• Facebook፡- https://www.facebook.com/combanketh
• Telegram፡- https://t.iss.one/combankethofficial
#Amhara
ዛሬ በአማራ ክልል በተለያዩ ከተሞች የውይይት መድረኮች ሲካሄዱ መዋላቸውን ከመንግሥታዊ የዜና አውታሮች የተገኙ መረጃዎች ያሳያሉ።
ውይይቶቹ የተመሩት ከፌዴራል እና ከሌሎች የሀገሪቱ ክልል በመጡ ከፍተኛ ባለስልጣናት ነበር።
በዋነኝነት ትኩረት ያደረገው በክልሉ ያለውን ችግር ለማዳመጥና የመፍትሄ ሃሳቡን ከህዝቡ ለመረዳት ነው ተብሏል።
ባለስልጣናት በነዚህ መድረኮች ላይ ክልሉ በሰላም እጦት በሰብዓዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ እየከፈለ ስላለው ዋጋና እየደረሰ ስላለው ጫና ሲናገሩ ተደምጠዋል።
መንግሥት ለዘላቂ ሰላም ጥረት እያደረገ መሆኑንና ይህንንም ህዝቡ ሊደግፍ እንደሚገባም ተናግረዋል።
ጥያቄዎችን በሃይል አማራጭ ለመፍታት መሞከር ውጤት እንደሌለውና ክልሉን ወደ ባሰ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ቀውስ እንደሚከት ጠቁመው ፤ ሰላማዊ መንገድ መከተል ዓይነተኛ መፍትሄ መሆኑን አስገንዝበዋል።
ለጥያቄዎች ከትጥቅ ትግል ይልቅ በውይይት እንዲፈቱ ጥሪ አቅርበዋብ።
በተለይ በባህር ዳር ነበረ የውይይት መድረክ የክልሉ ህዝብ በተደጋጋሚ የሚያነሳቸው ፦
➡ የወሰንና የማንነት፣
➡ የፍትሃዊ ተጠቃሚነት
➡ ከክልሉ ውጭ የሚኖሩ የአማራ ተወላጆች በሰላም የመኖር መብት ሌሎች ጥያቄዎች ታውቀው ያደሩ መሆናቸውና በቀጣይ ዘላቂ መፍትሄ እንዲያገኙ መንግስት እየሰራ ነው ብለዋል።
ዛሬ ውይይት እንደተደረገባቸው ከተሰሙት አንዷ በሆነችው ደሴ የተገኙ ተሳታፊዎች ፤ የእርስ በእርስ ግጭቱ እያደረሰ ካለው ጉዳት በተጨማሪ፦
☑ የኑሮ ውድነት
☑ የሥራ አጥነት
☑ የመልካም አስተዳደር ችግሮች እና ሌሎችም ተዳምረው ህብረተሰቡን ለከፍተኛ እንግልት መዳረጉ ተነስቷል።
የአማራ ህዝብ #አንኳር ጥያቄዎች በተገቢው ጊዜ እና ፍጥነት መመለስ ባለመቻሉ ዛሬ ለተደረሰው የሰላም እጦት ምክንያት መሆናቸውን ተሳታፊዎች አንስተዋል።
በመንግሥትና በታጣቂ ኃይሎች መካከል ሀቅ ላይ የተመሰረተ በእውነትም ሀገርን ከትርምስ ሊያወጣ የሚችል ውይይት ማድረግ እና ክልሉም አሁን ካለበት አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ማውጣት እንደሚገባ ተነስቷል።
ዛሬ በተመሳሳይ ጊዜ ውይይት ተደርጎባቸዋል ከተባሉ ከተሞች መካከል ባህር ዳር፣ ደሴ፣ ወልድያ፣ ደባርቅ፣ ደብረ ታቦር፣ እንጅባራ፣ ሰቆጣ ከተሞች ይጠቀሳሉ።
በአማራ ክልል ከተሞች በነበሩት መድረኮች ላይ ፦ የሶማሌ ፣ የኦሮሚያ ፣ የሲዳማ ፣ የሐረሪ፣ የቤኒሽንጉል ጉሙዝ ክልሎች ፕሬዜዳንቶች እንዲሁም የአዲስ አበባ ከንቲባ ተገኝተው ነበር።
የሀገር መከላከያ ፣ የገንዝብ ፣ የሥራ እና ክህሎት ፣ የትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ሚኒስትሮችን ጨምሮ ሌሎች የፌዴራል አመራሮችም ተገኝተው እንደነበር ለማወቅ ተችሏል።
ከዚህ ቀደም በክልሉ ከተሞች መሰል የውይይት መድረኮች ሲዘጋጁ የነበረ ቢሆንም በአንድ ጊዜ በዚህ ልክ ከፍተኛ እና የክልል አመራሮች ወደ ክልሉ ከተሞች ውይይት ሲቀመጡ ይህ የመጀመሪያ ነው።
የአማራ ክልል በተለያዩ ጊዜያት በተለያዩ ቦታዎች በመንግሥት የፀጥታ ኃይል እና በፋኖ ታጣቂዎች መካከል የሚካሄዱ ግጭቶች ከግጭቱ ተሳታፊዎች ባለፈ ንፁሃን ሰለባ እያደረጉ፣ ወጥቶ ለመግባት ፣ ለንግድ ፣ ለቱሪዝምም ትልቅ እንቅፋት እየሆኑ እንዳለ በተደጋጋሚ ተነግሯል።
@tikvahethiopia
ዛሬ በአማራ ክልል በተለያዩ ከተሞች የውይይት መድረኮች ሲካሄዱ መዋላቸውን ከመንግሥታዊ የዜና አውታሮች የተገኙ መረጃዎች ያሳያሉ።
ውይይቶቹ የተመሩት ከፌዴራል እና ከሌሎች የሀገሪቱ ክልል በመጡ ከፍተኛ ባለስልጣናት ነበር።
በዋነኝነት ትኩረት ያደረገው በክልሉ ያለውን ችግር ለማዳመጥና የመፍትሄ ሃሳቡን ከህዝቡ ለመረዳት ነው ተብሏል።
ባለስልጣናት በነዚህ መድረኮች ላይ ክልሉ በሰላም እጦት በሰብዓዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ እየከፈለ ስላለው ዋጋና እየደረሰ ስላለው ጫና ሲናገሩ ተደምጠዋል።
መንግሥት ለዘላቂ ሰላም ጥረት እያደረገ መሆኑንና ይህንንም ህዝቡ ሊደግፍ እንደሚገባም ተናግረዋል።
ጥያቄዎችን በሃይል አማራጭ ለመፍታት መሞከር ውጤት እንደሌለውና ክልሉን ወደ ባሰ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ቀውስ እንደሚከት ጠቁመው ፤ ሰላማዊ መንገድ መከተል ዓይነተኛ መፍትሄ መሆኑን አስገንዝበዋል።
ለጥያቄዎች ከትጥቅ ትግል ይልቅ በውይይት እንዲፈቱ ጥሪ አቅርበዋብ።
በተለይ በባህር ዳር ነበረ የውይይት መድረክ የክልሉ ህዝብ በተደጋጋሚ የሚያነሳቸው ፦
➡ የወሰንና የማንነት፣
➡ የፍትሃዊ ተጠቃሚነት
➡ ከክልሉ ውጭ የሚኖሩ የአማራ ተወላጆች በሰላም የመኖር መብት ሌሎች ጥያቄዎች ታውቀው ያደሩ መሆናቸውና በቀጣይ ዘላቂ መፍትሄ እንዲያገኙ መንግስት እየሰራ ነው ብለዋል።
ዛሬ ውይይት እንደተደረገባቸው ከተሰሙት አንዷ በሆነችው ደሴ የተገኙ ተሳታፊዎች ፤ የእርስ በእርስ ግጭቱ እያደረሰ ካለው ጉዳት በተጨማሪ፦
☑ የኑሮ ውድነት
☑ የሥራ አጥነት
☑ የመልካም አስተዳደር ችግሮች እና ሌሎችም ተዳምረው ህብረተሰቡን ለከፍተኛ እንግልት መዳረጉ ተነስቷል።
የአማራ ህዝብ #አንኳር ጥያቄዎች በተገቢው ጊዜ እና ፍጥነት መመለስ ባለመቻሉ ዛሬ ለተደረሰው የሰላም እጦት ምክንያት መሆናቸውን ተሳታፊዎች አንስተዋል።
በመንግሥትና በታጣቂ ኃይሎች መካከል ሀቅ ላይ የተመሰረተ በእውነትም ሀገርን ከትርምስ ሊያወጣ የሚችል ውይይት ማድረግ እና ክልሉም አሁን ካለበት አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ማውጣት እንደሚገባ ተነስቷል።
ዛሬ በተመሳሳይ ጊዜ ውይይት ተደርጎባቸዋል ከተባሉ ከተሞች መካከል ባህር ዳር፣ ደሴ፣ ወልድያ፣ ደባርቅ፣ ደብረ ታቦር፣ እንጅባራ፣ ሰቆጣ ከተሞች ይጠቀሳሉ።
በአማራ ክልል ከተሞች በነበሩት መድረኮች ላይ ፦ የሶማሌ ፣ የኦሮሚያ ፣ የሲዳማ ፣ የሐረሪ፣ የቤኒሽንጉል ጉሙዝ ክልሎች ፕሬዜዳንቶች እንዲሁም የአዲስ አበባ ከንቲባ ተገኝተው ነበር።
የሀገር መከላከያ ፣ የገንዝብ ፣ የሥራ እና ክህሎት ፣ የትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ሚኒስትሮችን ጨምሮ ሌሎች የፌዴራል አመራሮችም ተገኝተው እንደነበር ለማወቅ ተችሏል።
ከዚህ ቀደም በክልሉ ከተሞች መሰል የውይይት መድረኮች ሲዘጋጁ የነበረ ቢሆንም በአንድ ጊዜ በዚህ ልክ ከፍተኛ እና የክልል አመራሮች ወደ ክልሉ ከተሞች ውይይት ሲቀመጡ ይህ የመጀመሪያ ነው።
የአማራ ክልል በተለያዩ ጊዜያት በተለያዩ ቦታዎች በመንግሥት የፀጥታ ኃይል እና በፋኖ ታጣቂዎች መካከል የሚካሄዱ ግጭቶች ከግጭቱ ተሳታፊዎች ባለፈ ንፁሃን ሰለባ እያደረጉ፣ ወጥቶ ለመግባት ፣ ለንግድ ፣ ለቱሪዝምም ትልቅ እንቅፋት እየሆኑ እንዳለ በተደጋጋሚ ተነግሯል።
@tikvahethiopia
#Hawassa
" ተማሪው ላይ ጾታዊ ትንኮሳ ፈጽሟል " በሚል #የተጠረጠረው ርእሰ መምህር በቁጥጥር ስር እንዳሚገኝ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ሰምቷል።
በሀዋሳ ከተማ ታቦር አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ወስጥ አንዲት ተማሪ ርእሰ መምህሯን " ጾታዊ ትንኮሳ ፈጽሞብኛል " በሚል ክስ መመስረቷን ተከትሎ ፖሊስ ተጠርጣሪዉን ግለሰብ ከስራ ገበታዉ ድረስ በመሄድ በቀን 20/05/2016 ዓ/ም በቁጥጥር ስር ማዋሉን ለማወቅ ተችሏል።
የሀዋሳ ከተማ ሴቶችና ህጻናት ቢሮ ሀላፊዋ ወይዘሮ ፍሬህይወት ወልደጻዲቅ ጉዳዩን በተመለከተ ከቲክቫህ ኢትዮጽያ የሀዋሳው አባል ጋር በነበራቸዉ ቆይታ ፤ " የተጠቂዋ ቤተሰቦች ጉዳዩን ይዘዉ ቅድሚያ ለማመልከት የመጡት ወደእኛ ቢሮ ነበር " ያሉ ሲሆን ጉዳዩን ወደ ህግ እንዲወስዱት በማድረግ ማንኛዉንም የህግ ከለላና አስፈላጊ ድጋፎችን ሊሰጡ እንደሚችሉ ቃል ገብተው አንዳበረታቷቸው ገልጸዋል።
ከዚህ በኋላ ክሱ ተመስርቶ ተጠርጣሪዉ በህግ ጥላ እንደዋለና ምርመራ እየተደረገ መሆኑን የገለፁት ኃላፊዋ " አሁን ላይ የሀዋሳ ከተማ ትምህርት መምሪያ መረጃዎችን አጠናክሮ የክስ ሂደቱን ከኛ ጋር ለመደገፍ እንቅስቃሴ ላይ ነው " ሲሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አስረድተዋል።
ከጉዳዩ ጋር በተያያዘ ተጠርጣሪዉ በትምህርት ቤት ውስጥ ሲያዝ የነበረዉን ሁኔታ እና ድርጊቱን በተመለከተ የትምህርት ቤቱ አስተዳደር የሚያውቀዉ ነገር እንዳለ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ጥያቄ ያቀረበላቸው የትምህርት ቤቱ ምክትል ርእሰ መምህር አቶ ሀንዳሞ ፈይሳ ፤ በወቅቱ ተጠርጣሪው ለጥያቄ ትፈለጋለህ ተብለዉ መሄዳቸውን ፤ አሁን ላይ በህግ ቁጥጥር ስር ከዋሉ ሳምንት እንዳለፋቸው ገልጸዋል።
ክስ አቅራቢዋ ተማሪ ከትምህርት ገበታዋ ደጋግማ በመቅረቷ ምክንያት " ወላጅ አምጭ አታምጭ " በሚል ከሚመለከታቸዉ መምህራኖቿ እና ከተጠርጣሪው ርእሰ መምህር ጋር ስትጨቃጨቅ እንደነበር የሚያስታዉሱት አቶ ሀንዳሞ ፤ ይህ ጉዳይ ለእርሳቸውም ሆነ ለትምህርት ቤቱ ማህበረሰብ #አስደንጋጭ እና ግራ ያጋባ መሆኑን አስረድተዋል።
ፖሊስ አስፈላጊዉን ማጣራት አድርጎ እዉነቱ ላይ እስኪደርስ እየጠበቁ መሆኑንም ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።
መረጃውን አዘጋጅቶ የላከው የሐዋሳዉ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ነዉ።
@tikvahethiopia
" ተማሪው ላይ ጾታዊ ትንኮሳ ፈጽሟል " በሚል #የተጠረጠረው ርእሰ መምህር በቁጥጥር ስር እንዳሚገኝ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ሰምቷል።
በሀዋሳ ከተማ ታቦር አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ወስጥ አንዲት ተማሪ ርእሰ መምህሯን " ጾታዊ ትንኮሳ ፈጽሞብኛል " በሚል ክስ መመስረቷን ተከትሎ ፖሊስ ተጠርጣሪዉን ግለሰብ ከስራ ገበታዉ ድረስ በመሄድ በቀን 20/05/2016 ዓ/ም በቁጥጥር ስር ማዋሉን ለማወቅ ተችሏል።
የሀዋሳ ከተማ ሴቶችና ህጻናት ቢሮ ሀላፊዋ ወይዘሮ ፍሬህይወት ወልደጻዲቅ ጉዳዩን በተመለከተ ከቲክቫህ ኢትዮጽያ የሀዋሳው አባል ጋር በነበራቸዉ ቆይታ ፤ " የተጠቂዋ ቤተሰቦች ጉዳዩን ይዘዉ ቅድሚያ ለማመልከት የመጡት ወደእኛ ቢሮ ነበር " ያሉ ሲሆን ጉዳዩን ወደ ህግ እንዲወስዱት በማድረግ ማንኛዉንም የህግ ከለላና አስፈላጊ ድጋፎችን ሊሰጡ እንደሚችሉ ቃል ገብተው አንዳበረታቷቸው ገልጸዋል።
ከዚህ በኋላ ክሱ ተመስርቶ ተጠርጣሪዉ በህግ ጥላ እንደዋለና ምርመራ እየተደረገ መሆኑን የገለፁት ኃላፊዋ " አሁን ላይ የሀዋሳ ከተማ ትምህርት መምሪያ መረጃዎችን አጠናክሮ የክስ ሂደቱን ከኛ ጋር ለመደገፍ እንቅስቃሴ ላይ ነው " ሲሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አስረድተዋል።
ከጉዳዩ ጋር በተያያዘ ተጠርጣሪዉ በትምህርት ቤት ውስጥ ሲያዝ የነበረዉን ሁኔታ እና ድርጊቱን በተመለከተ የትምህርት ቤቱ አስተዳደር የሚያውቀዉ ነገር እንዳለ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ጥያቄ ያቀረበላቸው የትምህርት ቤቱ ምክትል ርእሰ መምህር አቶ ሀንዳሞ ፈይሳ ፤ በወቅቱ ተጠርጣሪው ለጥያቄ ትፈለጋለህ ተብለዉ መሄዳቸውን ፤ አሁን ላይ በህግ ቁጥጥር ስር ከዋሉ ሳምንት እንዳለፋቸው ገልጸዋል።
ክስ አቅራቢዋ ተማሪ ከትምህርት ገበታዋ ደጋግማ በመቅረቷ ምክንያት " ወላጅ አምጭ አታምጭ " በሚል ከሚመለከታቸዉ መምህራኖቿ እና ከተጠርጣሪው ርእሰ መምህር ጋር ስትጨቃጨቅ እንደነበር የሚያስታዉሱት አቶ ሀንዳሞ ፤ ይህ ጉዳይ ለእርሳቸውም ሆነ ለትምህርት ቤቱ ማህበረሰብ #አስደንጋጭ እና ግራ ያጋባ መሆኑን አስረድተዋል።
ፖሊስ አስፈላጊዉን ማጣራት አድርጎ እዉነቱ ላይ እስኪደርስ እየጠበቁ መሆኑንም ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።
መረጃውን አዘጋጅቶ የላከው የሐዋሳዉ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ነዉ።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#MoE ትምህርት ሚኒስቴር ረቂቅ መመሪያዎች ላይ አስተያየት መስጠት የሚፈልግ ማንኛውም ሰው አስተያየት እንዲሰጥ መድረክ መመቻቸቱን አሳውቋል። የትምህርት ሚኒስቴር : - 1ኛ. የአጠቃላይ ትምህርት የመምህራን የደረጃ እድገት የአፈጻጸም መመሪያ፣ 2ኛ. የር/መምህራን፣ የም/ር/መምህራንና ሱፐርቫይዘሮች የምልመላ መረጣና ምደባ የአፈጻጸም መመሪያ፣ 3ኛ. የቅድመ አንደኛና አንደኛ ደረጃ ትምህርት ዕጩ ምምህራን…
#Update
ትምህርት ሚኒስቴር በረቂቅ መመሪያዎች ላይ አስተያየት ለመስጠት ለሀሙስ የተጠራው ስብሰባ ወደ አርብ የካቲት 1/2016 ዓ.ም ጠዋት 3:30 ሰዓት መሸጋገሩን አሳውቋል።
ማንኛውም አስተያየት መስጠት ከሚፈልግ ሰው በሰዓቱ መገኘት ይችላል ተብሏል።
መመሪያዎቹ ፦
1ኛ. የአጠቃላይ ትምህርት የመምህራን የደረጃ እድገት የአፈጻጸም መመሪያ፣
2ኛ. የር/መምህራን፣ የም/ር/መምህራንና ሱፐርቫይዘሮች የምልመላ መረጣና ምደባ የአፈጻጸም መመሪያ፣
3ኛ. የቅድመ አንደኛና አንደኛ ደረጃ ትምህርት ዕጩ መምህራን ምልመላና መረጣ የአፈጻጸም መመሪያ፣ የሚሉ ናቸው።
@tikvahethiopia
ትምህርት ሚኒስቴር በረቂቅ መመሪያዎች ላይ አስተያየት ለመስጠት ለሀሙስ የተጠራው ስብሰባ ወደ አርብ የካቲት 1/2016 ዓ.ም ጠዋት 3:30 ሰዓት መሸጋገሩን አሳውቋል።
ማንኛውም አስተያየት መስጠት ከሚፈልግ ሰው በሰዓቱ መገኘት ይችላል ተብሏል።
መመሪያዎቹ ፦
1ኛ. የአጠቃላይ ትምህርት የመምህራን የደረጃ እድገት የአፈጻጸም መመሪያ፣
2ኛ. የር/መምህራን፣ የም/ር/መምህራንና ሱፐርቫይዘሮች የምልመላ መረጣና ምደባ የአፈጻጸም መመሪያ፣
3ኛ. የቅድመ አንደኛና አንደኛ ደረጃ ትምህርት ዕጩ መምህራን ምልመላና መረጣ የአፈጻጸም መመሪያ፣ የሚሉ ናቸው።
@tikvahethiopia