TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.5K photos
1.51K videos
215 files
4.12K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
" ኢትዮጵያ የአረብ ሊግ መግለጫን አጥብቃ ትቃወማለች " - አምባሳደር ምስጋኑ አረጋ የኢፌዴሪ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ምስጋኑ አርጋ ፤ ኢትዮጵያ የአረብ ሊግ መግለጫን አጥብቃ ትቃወማለች ብለዋል። የአረብ ሊግ መግለጫ በኢትዮጵያ የውስጥ ጉዳይ እና ሉዓላዊነት ላይ ጣልቃ የመግባት ሙከራ ነው ብለዋል። " ኢትዮጵያ ከብዙ የአረብ ሀገራት ጋር ጥሩ የሁለትዮሽ ግንኙነት አላት። " ያሉት ሚኒስትር…
" ግብፅ እና አረብ ሊግ የአንድ ሳንቲም ሁለት ገፅታ ናቸው "

የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር መለስ አለም ስለ ግብፅ እና አረብ ሊግ ምን አሉ ?

" ከአረብ ሊግ የተሰጠው መግለጫ ተቀባይነት የለውም።

ይህ ድርጅት በማን እንደሚዘወር ይታወቃል። የወጣው መግለጫ ተቋሙንም አባል ሀገራቱንም የሚመጥን አይደለም። የማን ድርጅት እንደሆነም ይታወቃል።

ከምንም በላይ ለአፍሪካውያን ንቀት ነው። አፍሪካውያን የራሳቸውን ችግር የመፍታት ብቃቱ አላቸው፤ በተግባርም አሳይተዋል።

ለአፍሪካዊ ችግር አፍሪካዊ መፍትሄ የሚለውን እሳቤ የሚያጣጥል ነው ተቀባይነት የለውም።

... በግብፅ እና አረብ ሊግ መካከል ያለው ግንኙነት የአንድ ሳንቲም ሁለት ገፅታ ተደርጎ ነው መወሰድ ያለበት፤ ምንም ልዩነት የለውም በግልፅ መናገር ያስፈልጋል ይሄ ወጣቱ ትውልድም እንዲያውቀው መደረግ አለበት።

የግብፅ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የሰጡት መግለጫ ጠቃሚ አይደለም። ሁለቱ ሀገሮች ካላቸው ግንኙነት አንፃር የሚመጥን አይደለም። ግብፅ እና ኢትዮጵያ የአባይ ልጆች ናቸው፤ ከአንድ ውሃ ነው የሚጠጡት ከአንድ ውሃ ነው የሚጠቀሙት።

በኢትዮጵያ በኩል ነገሮችን ማጋጋም ፣ ከልካቸው በላይ መስቀል ፣ማጋነን ጠቃሚ ነው ብላ አታምንም። ከምንም በላይ የአፍሪካ ህብረት እንደገለፀው የውጭ ጣልቃ ገብነት የሚደገፍ አይደለም።

ይህ የመጀመሪያ ጊዜ አይደለም። ከህዳሴ ግድብ ጋር በተያያዘ በርካታ መግለጫዎች ሰጥተዋል። በእኛ በኩል ድርድሩም የሁለትዮሽ ውይይቱንም በሚዲያ ማድረግ አንፈልግም።

የአረብ ሊግ ከህዳሴ ግድብ ጋር በተያያዘ ስንት መግለጫው አውጥቷል ? የኢትዮጵያ ጥያቄ ውሃ የማግኘት ሳይሆን ብርሃን የማግኘት ጉዳይ ነው። ተማሪዎች ብርሃን ያስፋጋቸዋል፤ እህቶቻችን በወሊድ መሞት የለባቸውም ሀኪም ቤት መሄድ አለባቸው ሀኪም ቤቶች ብርሃን ያስፈልጋቸዋል።

ስለዚህ ' ምንም በማያቁበት ሀገር ሄዶ ቁርበት አንጥፉልኝ ይላል ' ኢትዮጵያ ያለመረጋጋት ሳይሆን የመረጋጋት መንስኤ ናት ለዚህ አካባቢ ፤ ኢትዮጵያን በአለመረጋጋት መንስኤነት መክሰስ በአንድ ቃል ለመግለፅ #ቧልት ነው፤ የዘመኑ ቀልድ ተብሎ ሊቀመጥ ይችላል። "

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
እንኳን ለጥምቀት ከተራ በዓል አደረሳችሁ ! መልካም በዓል ! @tikvahethiopia
ፎቶ ፦በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ሥርዓት እና ትውፊት መሰረት የከተራ በዓል በመላው ሀገሪቱ እየተከበረ ይገኛል።

ታቦታት ከየአብያተክርስቲያናቱ ወጥተው ወደ የማደሪያቸው ባህረ-ጥምቀት በማምራት ላይ ይገኛሉ።

በተለያዩ የባህል አልባሳት ያሸበረቁ ምዕመናን፣ ካህናት፣ ዲያቆናትና መዘምራን ታቦታቱን አጅበው ወደየማደሪያቸው በመሸኘት ላይ ይገኛሉ።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ፎቶዎቹን ከኢፕድ እና ከተለያየ የማህበራዊ መገናኛዎች የወሰዳቸው ናቸው።

መልካም በዓል !

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#AfricanDevelopmentBank የአፍሪካ ልማት ባንክ ዓለም አቀፍ ሰራተኞቹን በአስቸኳይ #ከኢትዮጵያ ሊያስወጣ ነው። ባንኩ እዚህ ውሳኔ ላይ የደረሰው ከአንድ ወር በፊት ዋና የኢትዮጵያ ተወካዩ እና ሌላ የባንኩ ሰራተኛ ላይ በፀጥታ አካላት ድብደባ መፈፀሙን ተከትሎ ነው። በወቅቱ ባንኩ ቅሬታውን ለመንግስት አቅርቦ የነበረ ሲሆን መንግስትም አስቸኳይ ማጣራት አድርጎ ውጤቱን ይፋ እንደሚያደርግ ገልፆ…
#Update

የአፍሪካ ልማት ባንክ ዓለም አቀፍ ሰራተኞች ወደ ኢትዮጵያ ሊመለሱ ነው።

የአፍሪቃ ልማት ባንክ በመንግሥት የጸጥታ ኃይሎች በሠራተኞቹ ላይ የደረሰውን ጥቃት ተከትሎ ዓለም አቀፍ ሠራተኞቹን ካስወጣ ከ1 ወር በኋላ ሠራተኞቹ በሙሉ ወደ #ኢትዮጵያ እንደሚመለሱ ዛሬ አስታውቋል።

ባለፈው ወር የልማት ባንኩ ፕሬዝደንት አኪንዋሚ አዴሲና ከጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ጋር ከተነጋገሩ በኋላ ዶ/ር ዐቢይ ለአፍሪቃ ልማት ባንክ ይቅርታ በመጠየቅና ለሠራተኞቹም ደህነትና የጸጥታ ዋስትና መስጠታቸውን ሮይተርስ ዘግቧል።

ባንኩ ዛሬ ባወጣው መግለጫም የተለመደው ሥራውን ለመጀመር ባለሥልጣናት የደህንነት ዋስትና እንደሰጡት ገልጿል።

የአፍሪቃ ልማት ባንክ በዚሁ መግለጫው፤ ዶ/ር ዐቢይ እና አዴሲና ያካሄዱትን ውጤታማ ስብሰባ ተከትሎ፤ መንግሥት ይፋዊ ይቅርታ በመጠየቁና ከክስተቱ ጋር የተገናኙ ጉዳዮችን በተመለከተ መፍትሄ ለመፈለግ ጠንካራ ቁርጠኝነት መኖሩን በመግለጹ ባንኩ ሥራውን ኢትዮጵያ ውስጥ ይጀምራል ብሏል።

በሌላ በኩል ፤ በዑጋንዳ ካምፓላ የገለልተኛ ሀገራት ንቅናቄ ርዕሳነ ብሔር እና ርዕሳነ መንግሥታት 19ኛው ጉባኤ ዛሬ የተካሄደ ሲሆን ከጉባኤው ጎን ለጎን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ከአፍሪካ ልማት ባንክ ፕሬዚዳንት አኪንውሚ አዴሲና ጋር ተወያይተዋል።

ዶ/ር ዐቢይ ውይይቱን ተከትሎ ፤ " ከአፍሪካ ልማት ባንክ ጋር ያለንን ግንኙነታችንን በይበልጥ ለማጠናከር በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ መክረናል " ብለዋል፡፡

" ከባንኩ ጋር ያለን አጋርነት ለኢትዮጵያ የምግብ ሉዓላዊነት ጥረቶች ወሳኝ ነው " ሲሉ አክለዋል።

መረጃው ከአፍሪካ ልማት ባንክ ድረገፅ / ሮይተርስ እና ዶቼ ቨለ የተሰበሰበ ነው።

@tikvahethiopia
#አቢሲንያ_ባንክ

የአቢሲንያን የሞባይል ባንክ አገልግሎት ወደ *815# በመደወል ብቻ ያለ ኢንተርኔት ወይም በስማርት ፎን መገልገል ይቻላል።


#BoAmobile #mobilebanking #BoA #bankinginethiopia #banksinethiopia #bankofabyssinia #Ethiopia #የሁሉም_ምርጫ
#NAM

ትላንት በኢንቴቤ የምሥራቅ አፍሪካ የልማት በየነ መንግሥታት ድርጅት (ኢጋድ) አስቸኳይ የመሪዎች ስብሰባን ያስተናገደችው ኡጋንዳ ዛሬ የገለልተኛ ሀገራት ንቅናቄ (NAM) ርዕሳነ ብሔር እና ርዕሳነ መንግሥታት 19ኛው ጉባኤ አስተናግዳለች።

በትላንቱ የኢጋድ ስብሰባ ላይ ያልተገኘችው ኢትዮጵያ በዛሬው ጉባኤ ላይ ተገኝታ ነበር።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ዛሬ ወደ ካምፓላ አምርተው ጉባኤውን የተካፈሉ ሲሆን ንግግርም አድርገው ነበር።

በዚሁ ንግግራቸው ፤ " የባሕር በር የሌላቸው ሀገራት የሕዝብን የመልማት ጥያቄ ለመመለስ ፈተናዎችን እየተጋፈጡ ነው " ብለዋል።

የባሕር በር የሌላት ኢትዮጵያም ችግሩን ለመፍታት በሰላማዊና በጋራ ተጠቃሚነት መርኅ መሰረት ጥረት እያደረገች እንደምትገኝ አሳውቀዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከጉባዔው ጎን ለጎን ፦
- ከኬንያ ፕሬዚዳንት ዊሊያም ሩቶ፣
- ከሲሪላንካ ፕሬዚዳንት ራኒል ዊከርሜሲንጌ 
- ከአፍሪካ ልማት ባንክ ፕሬዚዳንት አኪንውሚ አዴሲና 
- ከኡጋንዳ ፕሬዜዳንት ዩዌሪ ሙሴቬኒ ጋር ውይይት አድርገዋል።

ውይይቶቹ  በሁለትዮሽ እና ቀጠናዊ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ ነበሩ።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ የካምፓላ ቆይታቸውን አጠናቀው ማምሻውን ወደ ሀገራቸው ተመልሰዋል።

የገለልተኛ ሀገራት ንቅናቄ (NAM) እኤአ በ1961 ላይ የተመሰረተ ሲሆን 120 ሀገራትን በአባልነት ይዟል።

ንቅናቄው ሲመሰረት በታዳጊ ሀገራት ላይ የሚደርሱ ጭቆናዎችን በጋራ መታገል፣ ጸረ ቅኝ ግዛት ትግሎችን መደገፍ ፣ ብሔራዊ ነፃነትን፣ ሉዓላዊነትንና የግዛት አንድነርን መደገፍ የሚሉ ዓላማዎችን ይዞ ነው።

ከተመድ በመቀጠል በርካታ ሀገራትን በአባልነት የያዘ ንቅናቄ ሲሆን ዋና መቀመጫውን ሰርቢያ፣ ቤልግሬድ ነው።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#ከተራ2016

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ምዕመናን በቤተክርስቲያኗ ሥርዓት እና ትውፊት መሰረት የ2016 ዓ/ም የጥምቀት ከተራ በዓልን በመላው ሀገሪቱ አክብረዋል።

በተለይ በአዲስ አበባ ከተራ ሃይማኖታዊ ስርዓቱን በጠበቀ መልኩ በድምቀት ተከብሯል።

ታቦታት ከየአብያተክርስቲያናቱ ወጥተው ወደ የማደሪያቸው ባህረ-ጥምቀት ገብተዋል።

በነገው ዕለት በመላው ሀገሪቱ የጥምቀት በዓል ይከበራል።

@tikvahethiopia