TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.3K photos
1.51K videos
212 files
4.11K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#ነእፓ

ነፃነት እና እኩልነት ፓርቲ (ነእፓ) ለኢፌዴሪ ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ደብዳቤ ፃፈ።

ፓርቲው በዚህ ደብዳቤው ፤ " የፓርቲ አባል ያልሆኑ የመንግሥት ሰራተኞች በብልፅግና ፓርቲ ስልጠና እንዲሳተፉ የሚደረግበት አሰራር እንዲቆም " ሲል ጠይቋል።

ነእፓ ፤ #የመንግስት እና #የፓርቲ መደበላለቅ በለውጡ ማግስት መጠነኛ መሻሻል አሳይቶ እንደነበር አስታውሷል።

ነገር ግን በተለይ ከ6ኛው ጠቅላላ ምርጫ ማግስት ጀምሮ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተባባሰ መጥቷል ብሏል።

ከቅርብ ወራት ጀምሮ ገዢው ፓርቲ እያካሄደ ባለው የአባላት ስልጠና፣ የፓርቲው አባል ያልሆኑ የፌዴራል እና የክልል የመንግስት ሰራተኞች (Public servants) የገዢውን ፓርቲ ድርጅታዊ ስልጠና እንዲወስዱ እየተደረገ መሆኑ ለዚህ አንድ ማሳያ ነው ሲል አስረድቷል።

ፓርቲው አለኝ ባለው መረጃ የገዢው ፓርቲ አባላት ያልሆኑ የመንግስት ሰራተኞች ስልጠናውን እንዲወስዱ በተለያየ መንገድ ጫና እየተደረገባቸው መሆኑን ገልጿል።

ይባስ ብሎ በየአካባቢው እየተካሄዱ ያሉ ስልጠናዎች ፦
- አበል፣
- ትራንስፖርት፣
- ሆቴል እና ሌሎች የስልጠና ወጪዎች የሚሸፈኑት #በመንግስት_በጀት መሆኑ ችግሩን ይበልጥ አሳሳቢ አድርጎታል ብሏል።

በመሆኑም የፓርቲ አባል ያልሆኑ የፌዴራል እና የክልል የመንግስት ሰራተኞች የገዢውን ፓርቲ ስልጠና እንዲወስዱ ማድረግ ህገ መንግስቱን እና የኢትዮጵያ የምርጫ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ስነ ስርአት አዋጃ ቁጥር 1162/2011 የሚቃረን በመሆኑ የሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ድርጊቱ ይቆም ዘንድ የሚጠበቅበትን እንዲያደርግ ፓርቲው ጥሪ አቅርቧል።

በቀጣይ ተመሳሳይ የህግ ጥሰቶች እንዳይፈጠሩ አስፈላጊውን እርምጃ እንዲወሰድም አሳስቧል።

ከዚሁ ጋር በተያያዘ ጉዳዩ በቀጥታ የሚመለከታቸው አካላት፤ ገዢው ፓርቲ የስልጠናና ሌሎች ድርጅታዊ እንቅስቃሴውን በመንግስት ሀብት የሚሸፍንበት አሰራር ህግ እና ስርአትን ያልተከተለ ከመሆኑም ባሻገር የፖለቲካ ሜዳውን የሚያዛንፍ በመሆኑ፣ ድርጊቱ ይታረም ዘንድ ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ ጠይቋል።

በተለይም ፦
- የምርጫ ቦርድ፣
- የገንዘብ ሚንስቴር
- የክልል የገንዘብ እና ኢኮኖሚ ቢሮዎች፣
- በየደረጃው ያሉ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምከር ቤቶች አዋጁን በማስከበር ገዢው ፓርቲ ድርጅታዊ መዋቅሩን ከመንግስት መዋቅር ለይቶ እንዲሰራ ኋላፈነታቸውን እንዲወጡ ጥሪ አቅርቧል።

(ፓርቲው የላከው መግለጫ ከላይ ተያይዟል)

@tikvahethiopia
#አቢሲንያ_ባንክ

ወደ አፖሎ አካውንት አንድ ሰው ባስመዘገቡ ቁጥር የ50 ብር ጉርሻ!

ባንካችን አቢሲንያ በተለያዩ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚገኙ ተማሪዎችን የአፖሎ የተማሪ አምባሳደር  በማድረግ፣ አፖሎን ለደንበኞች በማስተዋወቅ እና በምዝገባ ባሳኩት መጠን የኮሚሽን ክፍያ መክፈል ጀምሯል፡፡ ስለሆነም የአፖሎ አምባሳደር ለመሆን ፍላጎት ያላቸውን የከፍተኛ ትምህርት ተቌማት ተማሪዎች አወዳድሮ እየወሰደ ነው፡፡

የከፍተኛ ትምህርት ተቌማት ማለትም
1. ዩኒቨርሲቲ
2. ኮሌጅ
3. ቴክኒክ እና ሙያ ማሰልጠኛ ተቋማት ናቸው

የዚህ እድል ተሳታፊ ለመሆን በቀላሉ ከታች ያለውን መስፈንጠሪያ በመጠቀም ይመዝግቡ፡፡
https://apolsup.bankofabyssinia.com/studentAgent

የ50 ብር ኮሚሽን አግኙ!
ከአፖሎ ጋር ተፍ ተፍ በሉ፡፡
ከስራ በፊት ስራ ጀምሩ፡፡
በሃገር ልዩ ወግ እና ባህል ተውቦ፤
በደማቅ አብሮነት ታጅቦ፤
በደስታ የሚያከብሩት የልደት በዓል እንዲሆን ከልብ እንመኛለን!

እስከ 25% ቅናሽ የተደረገባቸውን ልዩ የገና በዓል የሞባይል ጥቅሎች በቴሌብር ሱፐርአፕ ከተጨማሪ 10% ስጦታ ጋር ወይም በማይ ኢትዮቴል፣ አርዲ ቻት ቦት እንዲሁም *999# ለራስዎ እየገዙ ለሚወዷቸውም በስጦታ እያበረከቱ የበዓል መልካም ምኞትዎን ያድርሱ!

መልካም የገና በዓል!

#Ethiotelecom #telebirr #HappyHolidays
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update ትምህርት ሚኒስቴር በአማራ ክልል የሚገኙ የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች ከጥር 1/2016 ዓ.ም ጀምሮ ባሉት 2 ሳምንታት ትምህርት ይጀምራሉ ማለቱ ይታወሳል። ይህ ተከትሎ አንዳንድ ተቋማት ለተማሪዎቻቸው ጥሪ አድርገዋል። ጥሪ ካደረጉት ውስጥ አንዱ የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ነው። ባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ለነባር እና አዲስ የቅድመ-ምረቃ ተማሪዎቹ ባደረገው ጥሪ ፤ የ1ኛ ዓመት 2ኛ ወሰነ ትምህርት…
#Update

በአማራ ክልል የሚገኙ ተጨማሪ ዩኒቨርሲቲዎች የተማሪዎች መግቢያ ቀንን ይፋ አድርገዋል።

ከቀናት በፊት ባህር ዳር ፣ ወልዲያ ፣ ደብረታቦር ዩኒቨርሲቲዎች የተማሪዎቻቸውን የመግቢያ ቀን ይፋ ማድረጋቸው ይታወቃል።

ማስታወሻ፦ https://t.iss.one/tikvahethiopia/84044

ከተጠቀሱት ዩኒቨርሲቲዎች በተጨማሪ፦
* እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ፣
* ደባርቅ ዩኒቨርሲቲ
* ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ
* ወሎ ጥሪ አድርገዋል።

እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ፤ የነባር መደበኛ ተማሪዎች የመግቢያ ጊዜ ጥር 25 እና 26 መሆኑን ገልጿል።

አዲስ ገቢ ተማሪዎች እና የሪሚዲያል ትምህርት ወስደው ያለፉ እንዲሁም በዚሁ ፕሮግራም ለመማር የተመደቡ ተማሪዎች መግቢያ የካቲት 7 እና 8/2016 ዓ.ም መሆኑን አሳውቋል።

ደባርቅ ዩኒቨርሲቲ የነባር መደበኛ ተማሪዎቹ ማለትም የ2ኛ፣ 3ኛ እና 5ኛ ዓመት ተማሪዎች የ2016 ዓ.ም ምዝገባ ጥር 15 እና 16/2016 ዓ.ም መሆኑን ይፋ አድርጓል።

በ2015 ዓ.ም የሪሚዲያል ፕሮግራም ትምህርታቸውን ሲከታተሉ ቆይተው የማለፊያ ውጤት ያመጡ እንዲሁም በ2016 ዓ.ም የአንደኛ ዓመት እና በሪሚዲያል ፕሮግራም ደባርቅ ዩኒቨርሲቲ የተመደቡ ተማሪዎች በሌላ ማስታወቂያ በቅርቡ ጥሪ ይደረግላቸዋል ብሏል።

የደብረማርቆስ ዩኒቨርሲቲ በበኩሉ ፤  የ3ኛ ዓመት 2ኛ ወሰነ ትምህርትና ከዚያ በላይ ነባር መደበኛ የቅድመ-ምረቃ ተማሪዎች ምዘባ ከጥር 16-17/2016 ዓ/ም ይካሄዳል ብሏል።

የ2ኛ ዓመት 2ኛ ወሰነ ትምህርት ነባር መደበኛ የቅድመ-ምረቃ ተማሪዎች ምዘገባ ከጥር 23-24/2016 ዓ/ም ነው ብሏል።

የ1ኛ ዓመት 2ኛ ወሰነ ትምህርት ነባር መደበኛ የቅድመ-ምረቃ ተማሪዎች እና በ2015 ዓ.ም የሪሚዲያል ትምህርት ወስደው የማለፊያ ውጤት ያላቸው ነባር ተማሪዎች ምዝገባ ደግሞ ከየካቲት 7-8/2016 ዓ.ም መሆኑን ገልጿል።

በ2016 ዓ.ም የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ውጤት ያመጡ አዲስ ገቢ የ1ኛ ዓመት ተማሪዎችና በ2016 በሪሚዲያል ፕሮግራም የተመደቡ አዲስ ገቢ ተማሪዎች ምዝገባ ከየካቲት 7-8/2016 ዓ.ም መሆኑን ይፋ አድርጓል።

የሁሉም ነባር የተከታታይ ፕሮግራም የቅድመ-ምረቃ ተማሪዎች ምዝገባ ከጥር እንዲሁም የሁሉም የመደበኛ እና ተከታታይ ድህረ-ምረቃ ነባር ተማሪዎች ምዝገባ ከጥር 04-05/2016 ዓ.ም መሆኑን ገልጿል።

ወሎ ዩኒቨርሲቲ ደግሞ የነባር ተማሪዎች፣ በ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ወስደው የማለፊያ ውጤት ያመጡ አዲስ የተመደቡ የመጀመሪያ ዓመት ተማሪዎች እንዲሁም በ2015 ዓ.ም የሪሚዲያል ትምህርት ተከታትለው ያለፉ ተማሪዎች በሙሉ የመግቢያ ጊዜ ጥር 7 እና 8/2016 ዓ.ም መሆኑን አሳውቋል።

በሌላ በኩል፣ በ2016 ዓ.ም ለአቅም ማሻሻያ ትምህርት (Remedial Program) የተመደቡ ተማሪዎች የመግቢያ ጊዜ ጥር 16 እና 17/2016 ዓ.ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው ገልጿል፡፡

እስካሁን ለነባር መደበኛ ተውማሪዎች ጥሪ ያደረጉ በአማራ ክልል የሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች የትኞቹ ናቸው ?

ባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ
ደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ
ደባርቅ ዩኒቨርሲቲ
ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ
እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ
ወልድያ ዩኒቨርሲቲ
ወሎ ዩኒቨርስቲ

እስካሁን ይፋዊ ጥሪ ያላቀረቡ ጎንደር፣ ደብረብርሃን እና መቅደላአምባ ናቸው።

@tikvahethiopia @tikvahuniversity
#AddisAbaba

በአዲስ አበባ በቀላል ባቡር እና ቀለበት መንገዶች 30 የእግረኛ ማቋረጫ ተሻጋሪ ድልድዮችና መተላለፊያዎች ሊገነቡ መሆኑን የአዲስ አበባ መንገዶች ባለሥልጣን አስታውቋል።

በአዲስ አበባ ቀላል ባቡር በሚያልፍባቸውና ውስጠኛው ቀለበት መንገድ ተብለው በሚጠሩ ቦታዎች ላይ መሸጋገሪያ ድልድዮችና መተላለፊያዎች ባለመኖራቸው እግረኞች ለትራፊክ አደጋ እየተጋለጡና መንገድ ለማቋረጥ ረዥም ርቀት ለመጓዝ እንደሚገደዱ ባለስልጣን መ/ቤቱ ገልጿል።

በመሆኑም ፤ 30 የእግረኛ ማቋረጫ ተሻጋሪ ድልድዮችና መተላለፊያዎች እንደሚገነቡ ይፋ አድርጓል።

ተሻጋሪ ድልድዮቹና መተላለፊያ መስመሮቹ ከመሬት በላይ እንዲሁም በመሬት ውስጥ እንደሚገነቡ ጠቁሟል።

የእግረኛ ተሻጋሪ ድልድዮቹ ፦
- ሐና ማርያም፣
- ኃይሌ ጋርመንት፣
- ሳሪስ ሐኪም ማሞ ሰፈር፣
- አደይ አበባ፣
- ጉርድ ሾላ፣
- አውቶቡስ ተራና አብነት አካባቢ እንዲሁም በሌሎችም አካባቢዎች ነው የሚገነቡት ብሏል። #ኢዜአ

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
የራስ ገዟ ሶማሌላንድ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው ስብሰባ ሶማሌላንድ ዓለም አቀፍ ስምምነቶችን የመፈፀም መብትን የሚደግፍ እና የሶማሊያን መንግሥት ጣልቃ ገብነትን ውድቅ የሚያደርግ ውሳኔ አሳልፏል። ሶማሌላንድን የራሴ አካል ናት የምትለውን ሶማሊያ እያቀረበች ያለውን የይገባኛል ጥያቄ #ውድቅ በማድረግም "የሶማሌላንድ ሪፐብሊክ ሉዓላዊነትና ነጻነቷ የተረጋገጠ ነው " ብሏል። የሶማሊያው…
#Update

ራስ ገዟ ሶማሌላንድ የሁለትዮሽ ስምምነት ለማድረግ " የሶማሊያ ፍቃድ "አያስፈልገኝም ፤ አልጠይቅምም " አለች።

ከሶማሊያ ተነጥላ ሶስት አስርት ዓመታት እንደሆናት የገለፀችው ሶማሌላንድ፤ ሶማሊያ የምታቀርበው " የኔ አካል ናት " የሚለው የባለቤትነት ጥያቄ ፍፁም ሀሰት ነው ስትል ገልጻለች።

የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክን በሶማሊላንድ የወደብ ተጠቃሚ ለማድረግ የተፈረመው የመግባቢያ ስምምነት አንድ ሀገር ከሌላ ሀገር ጋር ከሚደርገው #የሊዝ_ኮንትራቶች የተለየ አለመሆኑን አመልክታለች።

ራስ ገዟ ሶማሌላንድ ፤ ሶማሊያ የመግባቢያ ስምምነቱን በተመለከተ ያየዘችውን አቋም እና ያወጣቻቸውን መግለጫዎች ሁሉ #ውድቅ አድርጋለች።

ከዚህ ባለፈ ሶማሌላንድ የሁለትዮሽ ስምምነቶችን ለማድረግ የሶማሊያን ፈቃድ ትፈልጋለች የሚባል ማንኛውም ሀሳብ ፍፁም ውሸት ነው ስትል ገልጻለች።

ሶማሊላንድ ኢትዮጵያን ጨምሮ ከበርካታ ሀገራት ጋር የራሷን ነጻ የሆነ ግንኙነት ስታደርግ እንደነበርና አሁንም የምትቀጥል መሆኑን ገልጻ ከአሁኑ የመግባቢያ ስምምነት በፊት በርካታ ዓለም አቀፍ እና የሁለትዮሽ ስምምነቶችን በተሳካ ሁኔታ መፈፀሟን አስታውሳለች።

ከእነዚህ ከተፈፀሙ ዓለም አቀፍ እና የሁለትዮች ስምምነቶች መካከል አንዳቸውም ከሶማሊያ ፈቃድ አልተጠየቁም ወይም አልተቀበሉም ብላለች።

ሶማሌላንድ ባለፉት 33 ዓመታት የሶማሌላንድ እና የሶማሊያ #ተቃራኒ ሁኔታዎችን ብዙ ይናገራሉ ስትልም ገልጻለች።

ሶማሌላንድ ፤ በአፍሪካ ቀንድ የበለፀገ ዲሞክራሲ እና የመረጋጋት ምልክት ሆና የውስጥ ጉዳዮቿን፣ አስተዳደሯን እና ምርጫዋን ያለአለም አቀፍ ድጋፍ በብቃት በመምራት ላይ እንደሆነች አመልክታችለች።

" ሀገራችን እና የባህር ዳርቻዋ ያለማቋረጥ / በወጥነት ከዘረፋ፣ ከሽብርተኝነት እና ከሽፍታነት የፀዱ ናቸው። " ስትል አክላለች።

በአንፃሩ ሶማሊያ ላለፉት 33 ዓመታት ከውስጥ ሽኩቻ፣ ሙስና እና ሽብርተኝነት ጋር ስትታገል፣ በዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ዘንድ በተደጋጋሚ " የወደቀች / የከሸፈች ሀገር " ስትባል እንደነበር እና ለራሷ ጥበቃ የዓለም አቀፍ ሰላም አስከባሪ ሃይል ያስፈለጋት ሀገር መሆኗን ሶማሌላንድ ገልጻለች።

" ሶማሊያ ብዙ ጊዜ ' ብርቅዬ አፍሪካዊ ተአምር ' እየተባለች በሚነገርላት በሶማሌላንድ ላይ ያልተገባ አረዳድ እንዲኖር ከማድረግና መሠረተ ቢስ የባለቤትነት ጥያቄ ከማቅረብ ይልቅ፣ የራሷን ቤት ብታስተካክል ይመረጣል " ብላለች።

" እርግጥ ነው፣ ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ በሁለቱ አካላት መካከል ያለውን ከፍተኛ ልዩነት ይገነዘባል " ያለችው ሶማሌላንድ " እኛ ለአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ሰላምና መረጋጋት የምናደርገውን አስተዋጽኦ ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ የሚያደንቀው ነው " ስትል ገልጻለች።

ሶማሌላንድ እንደፈለገችው በነፃነት ዓለም አቀፍ ግንኙነት የመመሥረት ሉዓላዊ መብቷን ከማስጠበቅ ወደ ኋላ ባትልም፣ ከሶማሊያ ጋር እንደ #ጎረቤት ገንቢ ውይይት ለማድረግና ሰላማዊ በሆነ መንገድ አብሮ ለመኖር ቁርጠኛ ነኝ ብላለች።

ሶማሊያ ፤ እንደ አንድ የራሷ ግዛት በምትቆጥራት ሶማሌላንድ እና በኢትዮጵያ መካከል የተፈረመውን ስምምነት " ዋጋቢስ " በማለት ውድቅ ያደረገች ሲሆን የኢትዮጵያ ድርጊት ሉዓላዊነቴን ፣ ግዛታዊ አንድነቴ የሚዳፈር ነው ብላለች።

የሀገሪቱ ፕሬዜዳንት ሀሰን ሼክ ሞሀሙድም ስምምነቱን ተከትሎ ወደ ተለያዩ ሀገራት እና ተቋማት ጋር በመደወል ውይይት አድርገዋል።

በአሁን ሰዓት ደግሞ በኤርትራ ይፋዊ ጉብኝት እያደረጉ ሲሆን የግብፅ ፕሬዜዳንት አብዱል ፈታህ አልሲሲም ወደ ግብፅ መጥተው የስራ ጉብኝት እንዲያደርጉ ጥሪ ማቅረባቸው ተሰምቷል።

#ቲክቫህኢትዮጵያ

@tikvahethiopia
ሚና ፈርኒቸር .. ከዘመኑ ጋር 🤌

ሚና ፈርኒቸር መጪውን በዐል በማስመልከት
KSA4O የሚለውን code ይዞ ለመጣ ደንበኛ ከታህሳስ 20- ጥር 11 የሚቆይ ልዩ ቅናሽ ከነጻ ትራንስፖርት 🚚እና 4 አመት ዋስትና ጋር ልዪ ቅናሽ አዘጋጅተናል🎄

☎️ 0924245151  /0932325151

Telegram👉 https://t.iss.one/minafurniture

Facebook👉 https://www.facebook.com/Minafurnitur?mibextid=LQQJ4d

TikTok👉 www.tiktok.com/@minafurniture

Instagram👉 https://www.instagram.com/mina.furniture1?igsh=OGQ5ZDc2ODk2ZA==
TIKVAH-ETHIOPIA
#ይፈለጋል #Wanted " ... ሟች ያሳድጉት የነበረው መሀመድ ሽኩር አበባው ፤ ሼህ አብዲ ያሲንን በመግደል ወንጀል ተጠርጥሮ ይፈለጋል " - ፖሊስ የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን፤ ሼህ አብዱ ያሲንን በመግደል የሚጠረጠረው መሀመድ ሽኩር አበባው የተባለ ግለሰብ መሆኑን ገልጿል። ግለሰቡ #እጁን_እንዲሰጥም ፖሊስ አሳስቧል። ፖሊስ ተጠርጣረው ያለበትን የሚያውቅ ጥቆማ በመስጠት እንዲተባበር ጥሪውን አስተላልፏል።…
#ይፈለጋል #Wanted

ሼህ አብዱ ያሲንን በመግደል የሚጠረጠረው መሀመድ ሽኩር አበባው በቁጥጥር ስር ለማዋል ፖሊስ ክትትሉን አጠናክሮ መቀጠሉን የአዲስ አበባ ፖሊስ ገልጿል።

አንዳንድ ማህበራዊ ሚዲያዎች ተጠርጠሪው እንደተያዘ በማስመሰል የሚያሰራጩት መረጃ #ሀሰተኛ መሆኑን አስታውቋል።

በማህበራዊ ሚዲያ ላይ ተጠርጣሪው ሳይያዝ እንደ ተያዘ አድርጎ መረጃ ማሰራጨት ተገቢ እንዳልሆነ የገለፀው የአዲስ አበባ ፖሊስ መሀመድ ሽኩር አበባው ያለበትን የሚያውቅም ሆነ ማነኛውም መረጃ ያለው በስልክ ቁጥር 011-1-11-01-11 ወይም በነፃ ስልክ ቁጥር 991 መረጃ በመስጠት እንዲተባበር ጥሪ ቀርቧል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" 15 ሺህ 592 ሰራተኞች ፈተና ወስደዋል " - የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፐብሊክ ሰርቪስ እና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ የመንግስት ሰራተኞች የብቃይ ምዘና ፈተና በዛሬው ዕለት ተሰጥቷል። ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፐብሊክ ሰርቪስ እና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ ባገኘነው መረጃ ፈተናውን 15 ሺህ 592 ሰራተኞች ፈተናቸውን ወስደዋል። ፈተናው በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ እና በኮተቤ የትምህርት…
#Update

የሰራተኞች ፈተና ውጤት ይፋ ሆነ።

ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሰራተኞች የተሰጠው ፈተና #ውጤት ይፋ ሆኗል።

በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ እና በኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ የተዘጋጀው እና ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሰራተኞች ሲሰጥ የነበረው ፈተናን በሚመለከት በዛሬው ዕለት መግለጫ ተሰጥቷል።

በዚህ መግለጫም ፤ የቴክኒክና ባህሪ ብቃት ፈተናው የወሰዱት የከተማ አስተዳደሩ አመራሮች፣ ባለሙያዎችና ሰራተኞች ቁጥር 15 ሺህ 151 መሆኑ ተገልጿል።

ከዚህ ውስጥ የአመራሩ ቁጥር 4 ሺህ 213 ሲሆን የፈተውን ማለፊያ ውጤት ያመጡት 1 ሺህ 422 ናቸው። ይህም 34 በመቶው አመራሮች አልፈዋል። አመራሩ ለማለፍ ከ60 በመቶ በላይ ማምጣት ይጠበቅባቸዋል።

ፈተናውን የወሰዱ የሠራተኞች ቁጥር 10 ሺህ 257 ሲሆኑ ያለፉት 5 ሺህ 95 ናቸው ተብሏል። ይህም 50 በመቶ ነው። ሰራተኞች ለማለፍ ከ50 በመቶ በላይ ማምጣት አለባቸው።

ለፈተና ከተቀመጡት አጠቃላይ ቁጥር 681 የሚሆኑት በተለያየ የስነ ምግባር ጥሰት ከፈተና ውጪ መሆናቸውን እና 441 የሚሆኑት ደግሞ በፈተና ስፍራ ያልተገኙ መሆናቸው ተገልጿል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ መረጃው ከኢፕድ እና ከአዲስ አበባ ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ልማት ቢሮ ነው ያገኘው።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
የራስ ገዟ ሶማሌላንድ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው ስብሰባ ሶማሌላንድ ዓለም አቀፍ ስምምነቶችን የመፈፀም መብትን የሚደግፍ እና የሶማሊያን መንግሥት ጣልቃ ገብነትን ውድቅ የሚያደርግ ውሳኔ አሳልፏል። ሶማሌላንድን የራሴ አካል ናት የምትለውን ሶማሊያ እያቀረበች ያለውን የይገባኛል ጥያቄ #ውድቅ በማድረግም "የሶማሌላንድ ሪፐብሊክ ሉዓላዊነትና ነጻነቷ የተረጋገጠ ነው " ብሏል። የሶማሊያው…
ሶማሊያ እና ኤርትራ ምን መከሩ ?

የሶማሊያው ፕሬዜዳንት ሀሰን ሼክ ሞሀሙድ ወደ ኤርትራ አቅንተው የሁለት ቀን የስራ ጉብኝት አድርገው ወደ ሞቃዲሾ ተመልሰዋል።

ፕሬዜዳንቱ ጉብኝታቸውን በተመለከተ ማብራሪያ ሰጥተው ነበር።

በማብራሪያቸውም ፤ " ኤርትራን በተደጋጋሚ ጎብኝቻለሁ። ኤርትራ ለኛ እንደ ቤታችን ናት " ብለዋል።

ወደ ኤርትራ የሄዱት ፦
- ኤርትራ ከፍተኛ ድጋፍ እያደረገች ባለችበት በሶማሊያ ሽብርተኝነትን መዋጋት ዙሪያ ለፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ገለጻ ለማድረግ፤
- ከሰሞኑ በቀጠናው እየተስተዋለ ስላለው ተለዋለዋጭ ሁኔታ ላይ ለፕሬዝዳንት ኢሳያስ ገለጻ ለማድረግ፤
- በአካባቢው ስለላለው ሁኔታ የሶማሊያን አቋም ለፕሬዜዳንት ኢሳያስ ለማስረዳት ነው ብለዋል።

ፕሬዜዳንቱ ፤ " ኤርትራ ሁልጊዜም ከሶማሊያ ጎን ናት፤ ለዚህም እናመሰግናለን " ሲሉ ተደምጠዋል።

" ኤርትራ የሶማሊያን አንድነት፣ ሉዓላዊነትና የግዛት አንድነት ለማስጠበቅ ስትደግፍ ቆይታለች ይህም የኤርትራ ዓለም አቀፍ አቋም ፤ አሁንም ይህንን አቋም ክቡር ፕሬዝዳንቱ ዛሬ ደግመውኛል፤ ለዚህም እናመሰግናለን " ሲሉ ተናግረዋል።

የኤርትራ መንግሥት ምን አለ?

የኤርትራ መንግሥት ፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ እና ፕሬዜዳንት ሀሰን ሼክ መሀሙድ ባለፉት ሁለት ቀናት በሁለትዮሽ፣ አህጉራዊ እና ዓለምአቀፋዊ ጉዳዮች ላይ ሰፊ እና ጥልቅ ውይይት አድርገዋል ብሏል።

ሁለቱ መሪዎች በሁለትዮሽ ጉዳዮች ዙሪያ በጋራ እንደሚሰሩ መስማማታቸውን እና በቅርቡ የሁለትዮሽ እና ቀጣናዊ ጉዳዮች ላይ ሰፊ መግለጫ እንደሚያወጣ አስታውቋል።

NB. የሶማሊያው ፕሬዜዳንት ሀሰን ሼክ ሞሀሙድ ኤርትራ በነበሩበት ወቅት የግብፁ መሪ አብዱል ፈታህ አል ሲሲ ግብፅን እንዲጎበኙ ግብዣ አድርገውላቸዋል። የኢትዮጵያ እና የራስ ገዟ ሶማሌላንድ የመግባቢያ ስምምነት ከተፈረመ በኃላ የሶማሊያው ፕሬዝዳንት በቅድሚያ ስልክ ደውለው የተነጋገሩ ከአል ሲሲ ጋር እንደነበር አይዘነጋም።

@tikvahethiopia