TIKVAH-ETHIOPIA
#Update የሶማሊያ ካቢኔ በነገው ዕለት አስቸኳይ ስብሰባ እንደተጠራ ተሰምቷል። አስቸኳይ ስብሰባው ፤ ዛሬ በሶማሌላንድ (ሶማሊያ ሶማሌላንድን እንደ ሰሜናዊ ክልሏ ነው የምትቆጥራት) እና በኢትዮጵያ መካከል ተደርጓል ስለተባለው ስምምነት በተመለከተ ተወያይቶ ውሳኔ ለማሳለፍ ነው ተብሏል። ከዚሁ ከነገው አስቸኳይ የካቢኔ ስብሰባ ዝግጅት ጋር በተያያዘ #በአሁን_ሰዓት በሶማሊያ ጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት…
#Ethiopia 🤝 #Somaliland
" ታሪክ እየተሰራ ነው " - አሊ ሀሰን ሞሃመድ
ኢትዮጵያ እስካሁን በይፋ ከሶማሌላንድ ጋር በተፈረመው የትብብር ስምምነት የባህር በር ለመጠቀም እና የባህር ኃይል ቤዝ እንዲኖራት በምላሹ ደግሞ የ " ሶማሌላንድን " የነፃ ሀገርነት እውቅና እንደምትሰጥ አንዲትም ቃል #አልተናገረችም።
የሶማሌላንዱ ፕሬዜዳንት ግን ከስምምነቱ በኃላ ኢትዮጵያ ለሶማሌላንድ የነፃ ሀገርነት ውቅና እንደምትሰጥ በምላሹ የባህር በር እና የባህር ኃይል እንዲኖራት 20 ኪሎሜትር መሬት በሊዝ እንደምትሰጥ ገልጸዋል።
የራስ ገዟ ሶማሌላንድ ባለስልጣናትም ተመሳሳይ መረጃዎችን ሰጥተዋል።
ለአብነት አሊ ሀሰን ሞሃመድ የኢንፎርሜሽን ሚኒስትር ፤ " ታሪክ እየተሰራ ነው " ብለዋል።
ኢትዮጵያ በሊዝ የ20 ኪሎሜትር የባህር በር ተጠቃሚ እንድትሆን በምላሹ ደግሞ #እውቅና እና የኢኮኖሚ እድገት እንደምትሰጥ ገልጸዋል።
" ይህ ጨዋታ ቀያሪ፤ ትልቅ ትርጉም ያለው ስምምነት ነው " ያሉት ባለስልጣኑ " ትልቅና ደፍረትን የሚጠይቅ እርምጃ ነው ፤ ወደፊት ለሶማሌላንድ እና ኢትዮጵያ የብሩህ አድማስ በሮችን የሚከፍት ነው " ብለዋል።
ይህንኑ የአሊ ሀሰን ሞሀመድ ሃሳብን ሞባረክ ታኒ የተባሉት የፕሬዜዳንቱ ዋና ፀሐፊ ተጋርተውታል።
በሌላ በኩል ፤ ሶማሊያ እንደራሷ አንድ ግዛት የምታያት " ሶማሌላንድ " ከኢትዮጵያ ጋር ተፈራረመች ስለተባለው የመግባቢያ ስምምነት በተመለከተ ነገ ካቢኔዎቿ አስቸኳይ ስብሰባ ተቀምጠው ውሳኔ ያሳልፋሉ ተብሏል።
ለነገው አስቸኳይ ስብሰባ ዝግጅት ዛሬ ምሽት በጠቅላይ ሚኒስትሩ ቢሮ ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ ምክትላቸው እና ከፍተኛ የካቢኔ አባላት የተገኙበት ሰብሰባ ሲደረግ አምሽቷል።
የሶማሊያ ባለስልጣናትም የመግባቢያ ስምምነቱ ክፉኛ እንዳስቆጣቸው ተነግሯል።
የሶማሊያ የማዕድን እና ነዳጅ ሚኒስትሩ አብዲሪዛቅ ሞሀመድ ፤ " ሶማሊያ አትከፋፈልም ፤ በሉዓላዊነት እና የግዛት አንድነታችን አንደራደርም " ብለዋል።
ሚኒስትሩ ፤ " ኢትዮጵያ ከግዛት (ክልል) አስታዳዳሪ ጋር ወደብን ለመከራየት / ወታደራዊ ስምምነት (MOU) ማድረግ እንደማትችል በደንብ አድርጋ ታውቃለች ይህ ስልጣን ሙሉ በሙሉ የፌዴራላዊ ሶማሊያ መንግሥት ነው ፤ ኢትዮጵያ የግዛት አንድነታችንን የሚጥስ ተግባር መፈፀም አትችልም " ሲሉ ገልጸዋል።
የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ የዛሬውን " ታሪካዊ " የተባለ የትብብር ስምምነት መፈረሙን ተከትሎ " ኢትዮጵያ #ቀይ_ባህርን የመጠቀምና በዛውም የማልማት ፍላጎት ከሶማሌላንድ ጋር የመግባቢያ ስምምነት ሰነድ ተፈርሟል " ሲሉ አብስረዋል።
ዶክተር ዐቢይ፤ " እኛ ያሉንን ሃብቶች የመጋራት ፣ የመካፈልና በጋራ የመልማት ፍላጎት እንጂ ማንንም በኃይል የማስገደድ ፍላጎት የለንም ስንል የነበረው ሃሳብ በተግባር ታይቷል " ሲሉም ነው ያሳውቁት።
#ቲክቫህኢትዮጵያ
@tikvahethiopia
" ታሪክ እየተሰራ ነው " - አሊ ሀሰን ሞሃመድ
ኢትዮጵያ እስካሁን በይፋ ከሶማሌላንድ ጋር በተፈረመው የትብብር ስምምነት የባህር በር ለመጠቀም እና የባህር ኃይል ቤዝ እንዲኖራት በምላሹ ደግሞ የ " ሶማሌላንድን " የነፃ ሀገርነት እውቅና እንደምትሰጥ አንዲትም ቃል #አልተናገረችም።
የሶማሌላንዱ ፕሬዜዳንት ግን ከስምምነቱ በኃላ ኢትዮጵያ ለሶማሌላንድ የነፃ ሀገርነት ውቅና እንደምትሰጥ በምላሹ የባህር በር እና የባህር ኃይል እንዲኖራት 20 ኪሎሜትር መሬት በሊዝ እንደምትሰጥ ገልጸዋል።
የራስ ገዟ ሶማሌላንድ ባለስልጣናትም ተመሳሳይ መረጃዎችን ሰጥተዋል።
ለአብነት አሊ ሀሰን ሞሃመድ የኢንፎርሜሽን ሚኒስትር ፤ " ታሪክ እየተሰራ ነው " ብለዋል።
ኢትዮጵያ በሊዝ የ20 ኪሎሜትር የባህር በር ተጠቃሚ እንድትሆን በምላሹ ደግሞ #እውቅና እና የኢኮኖሚ እድገት እንደምትሰጥ ገልጸዋል።
" ይህ ጨዋታ ቀያሪ፤ ትልቅ ትርጉም ያለው ስምምነት ነው " ያሉት ባለስልጣኑ " ትልቅና ደፍረትን የሚጠይቅ እርምጃ ነው ፤ ወደፊት ለሶማሌላንድ እና ኢትዮጵያ የብሩህ አድማስ በሮችን የሚከፍት ነው " ብለዋል።
ይህንኑ የአሊ ሀሰን ሞሀመድ ሃሳብን ሞባረክ ታኒ የተባሉት የፕሬዜዳንቱ ዋና ፀሐፊ ተጋርተውታል።
በሌላ በኩል ፤ ሶማሊያ እንደራሷ አንድ ግዛት የምታያት " ሶማሌላንድ " ከኢትዮጵያ ጋር ተፈራረመች ስለተባለው የመግባቢያ ስምምነት በተመለከተ ነገ ካቢኔዎቿ አስቸኳይ ስብሰባ ተቀምጠው ውሳኔ ያሳልፋሉ ተብሏል።
ለነገው አስቸኳይ ስብሰባ ዝግጅት ዛሬ ምሽት በጠቅላይ ሚኒስትሩ ቢሮ ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ ምክትላቸው እና ከፍተኛ የካቢኔ አባላት የተገኙበት ሰብሰባ ሲደረግ አምሽቷል።
የሶማሊያ ባለስልጣናትም የመግባቢያ ስምምነቱ ክፉኛ እንዳስቆጣቸው ተነግሯል።
የሶማሊያ የማዕድን እና ነዳጅ ሚኒስትሩ አብዲሪዛቅ ሞሀመድ ፤ " ሶማሊያ አትከፋፈልም ፤ በሉዓላዊነት እና የግዛት አንድነታችን አንደራደርም " ብለዋል።
ሚኒስትሩ ፤ " ኢትዮጵያ ከግዛት (ክልል) አስታዳዳሪ ጋር ወደብን ለመከራየት / ወታደራዊ ስምምነት (MOU) ማድረግ እንደማትችል በደንብ አድርጋ ታውቃለች ይህ ስልጣን ሙሉ በሙሉ የፌዴራላዊ ሶማሊያ መንግሥት ነው ፤ ኢትዮጵያ የግዛት አንድነታችንን የሚጥስ ተግባር መፈፀም አትችልም " ሲሉ ገልጸዋል።
የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ የዛሬውን " ታሪካዊ " የተባለ የትብብር ስምምነት መፈረሙን ተከትሎ " ኢትዮጵያ #ቀይ_ባህርን የመጠቀምና በዛውም የማልማት ፍላጎት ከሶማሌላንድ ጋር የመግባቢያ ስምምነት ሰነድ ተፈርሟል " ሲሉ አብስረዋል።
ዶክተር ዐቢይ፤ " እኛ ያሉንን ሃብቶች የመጋራት ፣ የመካፈልና በጋራ የመልማት ፍላጎት እንጂ ማንንም በኃይል የማስገደድ ፍላጎት የለንም ስንል የነበረው ሃሳብ በተግባር ታይቷል " ሲሉም ነው ያሳውቁት።
#ቲክቫህኢትዮጵያ
@tikvahethiopia
#አቢሲንያ_ባንክ
የገና ስጦታ!
ለጥያቄና መልስ ውድድራችን ዝግጁ ነዎት?
5ኛ ዙር የጥያቄና መልስ ውድድር ሐሙስ ታህሳስ 25 ከቀኑ 6:30 በቴሌግራም ቻናላችን ይደረጋል፡፡ ቀላል ጥያቄዎችን በመመለስ ይሳተፉ፤ ይሸለሙ፡፡ የገናን በዓል ምክንያት በማድረግ ከ4ኛ ዙር ጀምሮ ባሉት ውድድሮች አስር አስር አሸናፊዎች በየሳምንቱ ይሸለማሉ! ዛሬውኑ የቴሌግራም ቻናላችንን በመቀላቀል ይሸለሙ!
የቴሌግራም ሊንክ፡ https://t.iss.one/BoAEth
#telegram #giveaway #contest #Boa #bankinginethiopia #banksinethiopia #bankofabyssinia #Ethiopia #የሁሉም_ምርጫ
የገና ስጦታ!
ለጥያቄና መልስ ውድድራችን ዝግጁ ነዎት?
5ኛ ዙር የጥያቄና መልስ ውድድር ሐሙስ ታህሳስ 25 ከቀኑ 6:30 በቴሌግራም ቻናላችን ይደረጋል፡፡ ቀላል ጥያቄዎችን በመመለስ ይሳተፉ፤ ይሸለሙ፡፡ የገናን በዓል ምክንያት በማድረግ ከ4ኛ ዙር ጀምሮ ባሉት ውድድሮች አስር አስር አሸናፊዎች በየሳምንቱ ይሸለማሉ! ዛሬውኑ የቴሌግራም ቻናላችንን በመቀላቀል ይሸለሙ!
የቴሌግራም ሊንክ፡ https://t.iss.one/BoAEth
#telegram #giveaway #contest #Boa #bankinginethiopia #banksinethiopia #bankofabyssinia #Ethiopia #የሁሉም_ምርጫ
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
የሶማሊላንዱ ፕሬዝዳንት ሙሴ ቢሂ አብዲ ምን አሉ ?
የሶማሊላንዱ ፕሬዝደንት በይፋዊ የማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ላይ ከኢትዮጵያ ጋር የመግባቢያ ስምምነት ሰነድ መፈረሙን ገልጸዋል።
በዚህም ስምምነት መሰረት ኢትዮጵያ ለሶማሊላንድ ሪፐብሊክ እውቅና እንደምትሰጥ ፤ ሶማሊላንድ በበኩሏ ኢትዮጵያ የባህር ኃይል እና የንግድ ባህር በር መዳረሻ እንዲኖራት ለ50 ዓመታት #በሊዝ እንደምትሰጥ ገልጸዋል።
ፕሬዝዳንቱ ይህንን ጉዳይ በትላንትናው መግለጫ ወቅትም የተናገሩት ሲሆን አሁንም በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው አረጋግጠዋል።
ከኢትዮጵያ ባለስልጣናት በኩል እስካሁን በስምምነቱ መሰረት ለሶማሊላንድ የነፃ ሀገርነት እውቅና እንሰጣለን የሚል ቃል አልወጣም።
በሌላ በኩል ስምምነቱ ያስቆጣቸው የሶማሊያ መንግሥት የካቢኔ አባላት ዛሬ ተሰብሰበው ውሳኔ ያሳልፋሉ ተብሏል።
ሶማሊያ ፤ ራዝ ገዟን ሶማሊላንድ እንደ አንድ ሉኣላዊ ግዛቷ ነው የምትቆጥራት።
ለሶማሊያ ጠቅላይ ሚኒስትር ፅ/ቤት ቅርብ የሆኑ ምንጮች ፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ በይፋ ይቅርታ ካልጠየቁ እና ለሶማሊያ ልዓላዊነት ክብር ካልሰጡ ሶማሊያ ከኢትዮጵያ ጋር የዲፕሎማሲያዊ ግንኙነቷን እንደምታቋርጥ ገልጸዋል።
ከዚህ በተጨማሪ ሶማሊያ ፤ በኢትዮጵያ እና በሶማሌላንድ መካከል የተደረሰውን ስምምነት በመቃወም እርምጃ ልትወስድ እንደምትችል እኚሁ ለፅ/ቤቱ ቅርብ የሆኑት ምንጮች አመልክተዋል።
ተጨማሪ . . .
በኢትዮጵያ እና ሶማሊላንድ መካከል ከተፈረመው ስምምነት ጋር በተያያዘ ዛሬ ማክሰኞ ሁለቱ የፌደራል ፓርላማ ምክር ቤቶች አስቸኳይ የጋራ ስብሰባ እንደሚያደርጉና የሶማሊያው ፕሬዝዳንትም ሀሰን ሼክ ሞሀሙድ ንግግር እንደሚያደርጉ ተነግሯል።
@tikvahethiopia
የሶማሊላንዱ ፕሬዝደንት በይፋዊ የማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ላይ ከኢትዮጵያ ጋር የመግባቢያ ስምምነት ሰነድ መፈረሙን ገልጸዋል።
በዚህም ስምምነት መሰረት ኢትዮጵያ ለሶማሊላንድ ሪፐብሊክ እውቅና እንደምትሰጥ ፤ ሶማሊላንድ በበኩሏ ኢትዮጵያ የባህር ኃይል እና የንግድ ባህር በር መዳረሻ እንዲኖራት ለ50 ዓመታት #በሊዝ እንደምትሰጥ ገልጸዋል።
ፕሬዝዳንቱ ይህንን ጉዳይ በትላንትናው መግለጫ ወቅትም የተናገሩት ሲሆን አሁንም በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው አረጋግጠዋል።
ከኢትዮጵያ ባለስልጣናት በኩል እስካሁን በስምምነቱ መሰረት ለሶማሊላንድ የነፃ ሀገርነት እውቅና እንሰጣለን የሚል ቃል አልወጣም።
በሌላ በኩል ስምምነቱ ያስቆጣቸው የሶማሊያ መንግሥት የካቢኔ አባላት ዛሬ ተሰብሰበው ውሳኔ ያሳልፋሉ ተብሏል።
ሶማሊያ ፤ ራዝ ገዟን ሶማሊላንድ እንደ አንድ ሉኣላዊ ግዛቷ ነው የምትቆጥራት።
ለሶማሊያ ጠቅላይ ሚኒስትር ፅ/ቤት ቅርብ የሆኑ ምንጮች ፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ በይፋ ይቅርታ ካልጠየቁ እና ለሶማሊያ ልዓላዊነት ክብር ካልሰጡ ሶማሊያ ከኢትዮጵያ ጋር የዲፕሎማሲያዊ ግንኙነቷን እንደምታቋርጥ ገልጸዋል።
ከዚህ በተጨማሪ ሶማሊያ ፤ በኢትዮጵያ እና በሶማሌላንድ መካከል የተደረሰውን ስምምነት በመቃወም እርምጃ ልትወስድ እንደምትችል እኚሁ ለፅ/ቤቱ ቅርብ የሆኑት ምንጮች አመልክተዋል።
ተጨማሪ . . .
በኢትዮጵያ እና ሶማሊላንድ መካከል ከተፈረመው ስምምነት ጋር በተያያዘ ዛሬ ማክሰኞ ሁለቱ የፌደራል ፓርላማ ምክር ቤቶች አስቸኳይ የጋራ ስብሰባ እንደሚያደርጉና የሶማሊያው ፕሬዝዳንትም ሀሰን ሼክ ሞሀሙድ ንግግር እንደሚያደርጉ ተነግሯል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
የሶማሊላንዱ ፕሬዝዳንት ሙሴ ቢሂ አብዲ ምን አሉ ? የሶማሊላንዱ ፕሬዝደንት በይፋዊ የማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ላይ ከኢትዮጵያ ጋር የመግባቢያ ስምምነት ሰነድ መፈረሙን ገልጸዋል። በዚህም ስምምነት መሰረት ኢትዮጵያ ለሶማሊላንድ ሪፐብሊክ እውቅና እንደምትሰጥ ፤ ሶማሊላንድ በበኩሏ ኢትዮጵያ የባህር ኃይል እና የንግድ ባህር በር መዳረሻ እንዲኖራት ለ50 ዓመታት #በሊዝ እንደምትሰጥ ገልጸዋል። ፕሬዝዳንቱ…
ዛሬ በራዝ ገዟ ሶማሊላንድ ይፋዊ መግለጫ ወጥቷል።
በዚህም መግለጫ ስምምነቱ ታሪካዊ ነው ተብሏል።
ይህ ታሪካዊ ስምምነት ኢትዮጵያ ለሶማሌላንድ ሪፐብሊክ እውቅና በመስጠት በሊዝ የባህር በር / ለባህርኃይሎቿ የባህር መዳረሻ እንደምታገኝ መግለጫው ይገልጻል።
" ስምምነቱ የጋራ ተጠቃሚነትን መሰረት ያደረገ ነው " ያለው መግለጫው ለኢትዮጵያ የባህር ኃይል ተጠቃሚነት 20 ኪሎሜትር የባህር በር እንደሚሰጥ ይህም በሊዝ ለ50 ዓመት እንደሚቆይ ተመላክቷል።
@tikvahethiopia
በዚህም መግለጫ ስምምነቱ ታሪካዊ ነው ተብሏል።
ይህ ታሪካዊ ስምምነት ኢትዮጵያ ለሶማሌላንድ ሪፐብሊክ እውቅና በመስጠት በሊዝ የባህር በር / ለባህርኃይሎቿ የባህር መዳረሻ እንደምታገኝ መግለጫው ይገልጻል።
" ስምምነቱ የጋራ ተጠቃሚነትን መሰረት ያደረገ ነው " ያለው መግለጫው ለኢትዮጵያ የባህር ኃይል ተጠቃሚነት 20 ኪሎሜትር የባህር በር እንደሚሰጥ ይህም በሊዝ ለ50 ዓመት እንደሚቆይ ተመላክቷል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ዛሬ በራዝ ገዟ ሶማሊላንድ ይፋዊ መግለጫ ወጥቷል። በዚህም መግለጫ ስምምነቱ ታሪካዊ ነው ተብሏል። ይህ ታሪካዊ ስምምነት ኢትዮጵያ ለሶማሌላንድ ሪፐብሊክ እውቅና በመስጠት በሊዝ የባህር በር / ለባህርኃይሎቿ የባህር መዳረሻ እንደምታገኝ መግለጫው ይገልጻል። " ስምምነቱ የጋራ ተጠቃሚነትን መሰረት ያደረገ ነው " ያለው መግለጫው ለኢትዮጵያ የባህር ኃይል ተጠቃሚነት 20 ኪሎሜትር የባህር በር እንደሚሰጥ…
#Ethiopia #Seaport
የጠቅላይ ሚኒስትሩ የብሄራዊ ደህንነት አማካሪ አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን ከሶማሊለንድ ጋር ስለተፈረመው ስምምነት ምን አሉ ?
- ኢትዮጵያ የባህር በር ተጠቃሚ እንድትሆን በምክክር፣ በሰላማዊ መንገድ ብቻ በሰጥቶ መቀበል መርህ የተለያዩ የዲፕሎማሲ ስራዎች ሲሰሩ ቆይተዋል።
- ከሌሎች ጎረቤት ሀገራት ጋር ብዙ ሞክረን ያልተሳካው ከሶማሊላንድ ጋር በተመሳሳይ መንገድ ጥረት ሲደረግ ቆይቷል።
- መንግሥት አቋሙን ይፋ ካደረገ በኃላ ያሉ ሃብቶችን ከመጋራት አንፃር የነበረው ጉዳይ ጥርቶ ከወጣ በኃላ ዝርዝር ውይይት ሲካሄድ ነው የቆየው።
- ጉዳዩ መልክ እስኪይዝ በተወሰነ በጠባብ ቡድን፣ በመሪዎች ደረጃ እና በተወሰኑ አካላት ደረጃ እንዲያዝ እየበሰለ ሲሄድ ደግሞ ሁለቱም አካላት የየራሳቸውን አመራር እያሳተፉ የሚሄዱበት ሁኔታ እንዲፈጠር ተደርጓል።
- የወደብ ስምምነት ተጠቃሚነት በሊዝ አማካኝነት የሚፈፀም ነው።
- ይህ የስምምነት ማዕቀፍ ሶማሌለንድ እና ኢትዮጵያ አንዳቸው ጋር ያለውን ሃብት ለመጋራት በጋራ ጥቅም ላይ የተመሰረተ እድል የሚያሰፋበት፣ በመከላከያና ደህንነት ዘርፍ ኢትዮጵያ ያላትን አቅምና ልምድ ለሶማሊላንድ የምታጋራበት ፤ የጋራ ጥቅማቸውን ማስጠበቅ የሚችሉበት አቅም ይገነባል።
- የስምምነቱ ማዕቀፍ ኢትዮጵያ ሶማሌላንድ ውስጥ Military base እና Commercial maritime ሰፈር እንዲኖራት ይፈቅዳል። ይህ #በሊዝ የሚታሰብ ይሆናል። ለ50 ዓመት እና ከዛ በላይ #በማራዘም የሚካሄድ እንዲሆን ያደርጋል።
- ኢትዮጵያ አማራጭ ወደብን እድል ለማግኘት በርበራ ኮሊደርን የምታሰፋበት ፣ የመከላከያ አቅሟን አዲስ በምትከራየው ቦታ የምታጠናክርበት እድል ይሰጣል።
- ኢትዮጵያ ለሊዝ ተጠቃሚነቷ ቴሌኮም ይሁን፣ አየር መንገድ ይሁን ጥቅም በሚያስገኙ መሰረተ ልማቶች ላይ ድርሻ ትሰጣለች። ምን ያህል ነው ? የሚለው የሚከፈለው ሊዝም ምን ያህል ይሆናል ? የሚለው በዝርዝር ውይይቶች ይወሠናል።
- በጤና፣ በትምህርት ፣ በመከላከያ የሚሰሩት ዝርዝር ስምምነቶች በተናጠል ውይይት ይካሄድባቸዋል። ወደ ፓርላማ ሄደው የሚፀድቁ በርካታ ስምምነቶች ከዚህ ይፈልቃሉ።
- የጋራ የመግባቢያ ስምምነት ሰነዱ አጠቃላይ ማዕቀፍ ሁለቱ አካላት በጋራ ተባብረው የሚያድጉበትን ማዕቀፍ ነው የሚያስቀምጠው። ዋና ዋና አንጓዎች ተቀምጠዋል። የኢትዮጵያ የባህር በር የምታገኝበትን ዕድል በተጨባጭ ወደመሬት ለማውረድ እድል ይሰጣል።
- ስምምነቱ በ1 ወር ጊዜ ውስጥ ሂደቱ ያልቃል / ወደ ተግባር / ስራ ይገባል።
- ከሌሎች ሀገራት ጋር የጀመርናቸው አሉ #ከኤርትራ ጋር በዝርዝር ውይይት ተጀምሮ የሆነ ቦታ ላይ ነው የቆመው።
- ኢትዮጵያ አንድ ወደብ ፣ ሁለት ወደብ ፣ ሶስት ወደብ ሳይሆን ፤ ኢትዮጵያ አሁን ባለው ሁኔታ እያደገች ከሄደች ሁሉም ቀጠናዎች የሁሉም ጫፎች የኢትዮጵያን ምርቶች የሚያስገቡበት በር ያስፈልጋል።
አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን በማብራሪያቸው በስምምነቱ ሶማሊያ ልዓላዊ ግዛቴ ናት ለምትለው ራስ ገዟ #ሶማሌላንድ በይፋ የነፃ ሀገርነት እውቅናን ትስጠ እንደሆነ የተናግሩት አንዳች ነገር የለም።
@tikvahethiopia
የጠቅላይ ሚኒስትሩ የብሄራዊ ደህንነት አማካሪ አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን ከሶማሊለንድ ጋር ስለተፈረመው ስምምነት ምን አሉ ?
- ኢትዮጵያ የባህር በር ተጠቃሚ እንድትሆን በምክክር፣ በሰላማዊ መንገድ ብቻ በሰጥቶ መቀበል መርህ የተለያዩ የዲፕሎማሲ ስራዎች ሲሰሩ ቆይተዋል።
- ከሌሎች ጎረቤት ሀገራት ጋር ብዙ ሞክረን ያልተሳካው ከሶማሊላንድ ጋር በተመሳሳይ መንገድ ጥረት ሲደረግ ቆይቷል።
- መንግሥት አቋሙን ይፋ ካደረገ በኃላ ያሉ ሃብቶችን ከመጋራት አንፃር የነበረው ጉዳይ ጥርቶ ከወጣ በኃላ ዝርዝር ውይይት ሲካሄድ ነው የቆየው።
- ጉዳዩ መልክ እስኪይዝ በተወሰነ በጠባብ ቡድን፣ በመሪዎች ደረጃ እና በተወሰኑ አካላት ደረጃ እንዲያዝ እየበሰለ ሲሄድ ደግሞ ሁለቱም አካላት የየራሳቸውን አመራር እያሳተፉ የሚሄዱበት ሁኔታ እንዲፈጠር ተደርጓል።
- የወደብ ስምምነት ተጠቃሚነት በሊዝ አማካኝነት የሚፈፀም ነው።
- ይህ የስምምነት ማዕቀፍ ሶማሌለንድ እና ኢትዮጵያ አንዳቸው ጋር ያለውን ሃብት ለመጋራት በጋራ ጥቅም ላይ የተመሰረተ እድል የሚያሰፋበት፣ በመከላከያና ደህንነት ዘርፍ ኢትዮጵያ ያላትን አቅምና ልምድ ለሶማሊላንድ የምታጋራበት ፤ የጋራ ጥቅማቸውን ማስጠበቅ የሚችሉበት አቅም ይገነባል።
- የስምምነቱ ማዕቀፍ ኢትዮጵያ ሶማሌላንድ ውስጥ Military base እና Commercial maritime ሰፈር እንዲኖራት ይፈቅዳል። ይህ #በሊዝ የሚታሰብ ይሆናል። ለ50 ዓመት እና ከዛ በላይ #በማራዘም የሚካሄድ እንዲሆን ያደርጋል።
- ኢትዮጵያ አማራጭ ወደብን እድል ለማግኘት በርበራ ኮሊደርን የምታሰፋበት ፣ የመከላከያ አቅሟን አዲስ በምትከራየው ቦታ የምታጠናክርበት እድል ይሰጣል።
- ኢትዮጵያ ለሊዝ ተጠቃሚነቷ ቴሌኮም ይሁን፣ አየር መንገድ ይሁን ጥቅም በሚያስገኙ መሰረተ ልማቶች ላይ ድርሻ ትሰጣለች። ምን ያህል ነው ? የሚለው የሚከፈለው ሊዝም ምን ያህል ይሆናል ? የሚለው በዝርዝር ውይይቶች ይወሠናል።
- በጤና፣ በትምህርት ፣ በመከላከያ የሚሰሩት ዝርዝር ስምምነቶች በተናጠል ውይይት ይካሄድባቸዋል። ወደ ፓርላማ ሄደው የሚፀድቁ በርካታ ስምምነቶች ከዚህ ይፈልቃሉ።
- የጋራ የመግባቢያ ስምምነት ሰነዱ አጠቃላይ ማዕቀፍ ሁለቱ አካላት በጋራ ተባብረው የሚያድጉበትን ማዕቀፍ ነው የሚያስቀምጠው። ዋና ዋና አንጓዎች ተቀምጠዋል። የኢትዮጵያ የባህር በር የምታገኝበትን ዕድል በተጨባጭ ወደመሬት ለማውረድ እድል ይሰጣል።
- ስምምነቱ በ1 ወር ጊዜ ውስጥ ሂደቱ ያልቃል / ወደ ተግባር / ስራ ይገባል።
- ከሌሎች ሀገራት ጋር የጀመርናቸው አሉ #ከኤርትራ ጋር በዝርዝር ውይይት ተጀምሮ የሆነ ቦታ ላይ ነው የቆመው።
- ኢትዮጵያ አንድ ወደብ ፣ ሁለት ወደብ ፣ ሶስት ወደብ ሳይሆን ፤ ኢትዮጵያ አሁን ባለው ሁኔታ እያደገች ከሄደች ሁሉም ቀጠናዎች የሁሉም ጫፎች የኢትዮጵያን ምርቶች የሚያስገቡበት በር ያስፈልጋል።
አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን በማብራሪያቸው በስምምነቱ ሶማሊያ ልዓላዊ ግዛቴ ናት ለምትለው ራስ ገዟ #ሶማሌላንድ በይፋ የነፃ ሀገርነት እውቅናን ትስጠ እንደሆነ የተናግሩት አንዳች ነገር የለም።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update የሶማሊያ ካቢኔ በነገው ዕለት አስቸኳይ ስብሰባ እንደተጠራ ተሰምቷል። አስቸኳይ ስብሰባው ፤ ዛሬ በሶማሌላንድ (ሶማሊያ ሶማሌላንድን እንደ ሰሜናዊ ክልሏ ነው የምትቆጥራት) እና በኢትዮጵያ መካከል ተደርጓል ስለተባለው ስምምነት በተመለከተ ተወያይቶ ውሳኔ ለማሳለፍ ነው ተብሏል። ከዚሁ ከነገው አስቸኳይ የካቢኔ ስብሰባ ዝግጅት ጋር በተያያዘ #በአሁን_ሰዓት በሶማሊያ ጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት…
#Update #Seaport
ሶማሊያ በኢትዮጵያ ያሉትን አምባሳደሯን ጠራች።
ሶማሊያ እንደ ራሷ ግዛት በምታያት ሱማሊላንድ እና ኢትዮጵያ መካከል ትላንት በተፈረመው የመግባቢያ ስምምነት ሰነድ እንዳስቆጣት መነገሩ ይታወሳል።
ይህን ተከትሎ ከኢትዮጵያ አምባሳደሯን ለምክክር በሚል ጠርታለች።
የሀገሪቱ ካቢኔ ዛሬ ማክሰኞ ባካሄደው አስቸኳይ ስብሰባ ፦
- የተመድ ፀጥታው ምክር ቤት)
- አፍሪካ ህብረት
- ኦአይሲ
- ኢጋድ
- አረብ ሊግ ጣልቃ እንዲገቡ ጥሪ አቅርቧል።
በተጨማሪ የሶማሊያ ካቢኔ በሶማሌላንድ እና በኢትዮጵያ መካከል ለወደብ አጠቃቀም የተፈረመው ስምምነት " ዋጋ ቢስ እና ህጋዊ መሰረት የሌለው " ነው ማለቱ ተነግሯል።
ካቢኔው የኢትዮጵያ እርምጃ የቀጠናውን መረጋጋት እና ሰላም አደጋ ላይ የሚጥል ነው ማለቱም ተዘግቧል።
የካቢኔውን ስብሰባ የመሩት ጠ/ሚ ሃምዛ አብዲ ባሬ " ሉዓላዊነታችንን ለመጠበቅ ቁርጠኛ ነን " ብለው " ማንም የሶማሊያን የመሬት፣ የባህር እና የአየር ክፍል ሊጥስ አይችልም " ሲሉ ተደምጠዋል።
ራስ ገዟ ሶማሌላንድ ለሶስት አስርት ዓመታት ዓለም አቀፍ እውቅናን ማግኘት ያልቻለች ሲሆን ከኢትዮጵያ ጋር ባደረገችው ስምምነት ኢትዮጵያ በሊዝ የባህር ኃይል እና የንግድ የባህር በር እንዲኖራት አድርጋ በምላሹ እውቅናን ትጠብቃለች። ከዚህ ባለፈ በኢትዮጵያ አየር መንገድ ድርሻ ይኖራታል።
ለሶማሊያ ጠቅላይ ሚኒስትር ፅ/ቤት ቅርብ የሆኑ ምንጮች ፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ በይፋ ይቅርታ ካልጠየቁ እና ለሶማሊያ ልዓላዊነት ክብር ካልሰጡ ሶማሊያ ከኢትዮጵያ ጋር የዲፕሎማሲያዊ ግንኙነቷን #እንደምታቋርጥ እየገለፁ ናቸው።
@tikvahethiopia
ሶማሊያ በኢትዮጵያ ያሉትን አምባሳደሯን ጠራች።
ሶማሊያ እንደ ራሷ ግዛት በምታያት ሱማሊላንድ እና ኢትዮጵያ መካከል ትላንት በተፈረመው የመግባቢያ ስምምነት ሰነድ እንዳስቆጣት መነገሩ ይታወሳል።
ይህን ተከትሎ ከኢትዮጵያ አምባሳደሯን ለምክክር በሚል ጠርታለች።
የሀገሪቱ ካቢኔ ዛሬ ማክሰኞ ባካሄደው አስቸኳይ ስብሰባ ፦
- የተመድ ፀጥታው ምክር ቤት)
- አፍሪካ ህብረት
- ኦአይሲ
- ኢጋድ
- አረብ ሊግ ጣልቃ እንዲገቡ ጥሪ አቅርቧል።
በተጨማሪ የሶማሊያ ካቢኔ በሶማሌላንድ እና በኢትዮጵያ መካከል ለወደብ አጠቃቀም የተፈረመው ስምምነት " ዋጋ ቢስ እና ህጋዊ መሰረት የሌለው " ነው ማለቱ ተነግሯል።
ካቢኔው የኢትዮጵያ እርምጃ የቀጠናውን መረጋጋት እና ሰላም አደጋ ላይ የሚጥል ነው ማለቱም ተዘግቧል።
የካቢኔውን ስብሰባ የመሩት ጠ/ሚ ሃምዛ አብዲ ባሬ " ሉዓላዊነታችንን ለመጠበቅ ቁርጠኛ ነን " ብለው " ማንም የሶማሊያን የመሬት፣ የባህር እና የአየር ክፍል ሊጥስ አይችልም " ሲሉ ተደምጠዋል።
ራስ ገዟ ሶማሌላንድ ለሶስት አስርት ዓመታት ዓለም አቀፍ እውቅናን ማግኘት ያልቻለች ሲሆን ከኢትዮጵያ ጋር ባደረገችው ስምምነት ኢትዮጵያ በሊዝ የባህር ኃይል እና የንግድ የባህር በር እንዲኖራት አድርጋ በምላሹ እውቅናን ትጠብቃለች። ከዚህ ባለፈ በኢትዮጵያ አየር መንገድ ድርሻ ይኖራታል።
ለሶማሊያ ጠቅላይ ሚኒስትር ፅ/ቤት ቅርብ የሆኑ ምንጮች ፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ በይፋ ይቅርታ ካልጠየቁ እና ለሶማሊያ ልዓላዊነት ክብር ካልሰጡ ሶማሊያ ከኢትዮጵያ ጋር የዲፕሎማሲያዊ ግንኙነቷን #እንደምታቋርጥ እየገለፁ ናቸው።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Ethiopia 🤝 #Somaliland " ታሪክ እየተሰራ ነው " - አሊ ሀሰን ሞሃመድ ኢትዮጵያ እስካሁን በይፋ ከሶማሌላንድ ጋር በተፈረመው የትብብር ስምምነት የባህር በር ለመጠቀም እና የባህር ኃይል ቤዝ እንዲኖራት በምላሹ ደግሞ የ " ሶማሌላንድን " የነፃ ሀገርነት እውቅና እንደምትሰጥ አንዲትም ቃል #አልተናገረችም። የሶማሌላንዱ ፕሬዜዳንት ግን ከስምምነቱ በኃላ ኢትዮጵያ ለሶማሌላንድ የነፃ ሀገርነት…
" ስምምነቱ ሶማሊላንድ እና ኢትዮጵያን ለብዙ አስርት ዓመታት ይለውጣል " - ሞሀመድ አብዱላሂ ዱሌ
የራስ ገዟ ሶማሊላንድ ባለስልጣናት ከኢትዮጵያ ጋር የተፈረመው ስምምነትን እያደነቁ ይገኛሉ።
የአካባቢ እና የአየር ንብረት ለውጥ ሚኒስትሩ ሞሀመድ አብዱላሂ ዱሌ ፤
ስምምነቱን " ጨዋታ ቀያሪ ነው " ያሉ ሲሆን ሶማሊላንድ እና ኢትዮጵያን ለብዙ አስርት ዓመታት ይለውጣል ሲሉ ገልጸዋል።
@tikvahethiopia
የራስ ገዟ ሶማሊላንድ ባለስልጣናት ከኢትዮጵያ ጋር የተፈረመው ስምምነትን እያደነቁ ይገኛሉ።
የአካባቢ እና የአየር ንብረት ለውጥ ሚኒስትሩ ሞሀመድ አብዱላሂ ዱሌ ፤
ይህ
ፕሬዚዳንት ቢሂ እና ጠ/ሚ ዶ/ር አብይ የተፈራረሙት የመግባቢያ ሰነድ ታሪካዊ እና ትልቅ ስምምነት ነው ብለውታል።ስምምነቱን " ጨዋታ ቀያሪ ነው " ያሉ ሲሆን ሶማሊላንድ እና ኢትዮጵያን ለብዙ አስርት ዓመታት ይለውጣል ሲሉ ገልጸዋል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update #Seaport ሶማሊያ በኢትዮጵያ ያሉትን አምባሳደሯን ጠራች። ሶማሊያ እንደ ራሷ ግዛት በምታያት ሱማሊላንድ እና ኢትዮጵያ መካከል ትላንት በተፈረመው የመግባቢያ ስምምነት ሰነድ እንዳስቆጣት መነገሩ ይታወሳል። ይህን ተከትሎ ከኢትዮጵያ አምባሳደሯን ለምክክር በሚል ጠርታለች። የሀገሪቱ ካቢኔ ዛሬ ማክሰኞ ባካሄደው አስቸኳይ ስብሰባ ፦ - የተመድ ፀጥታው ምክር ቤት) - አፍሪካ ህብረት …
#Update
ሶማሊያ በኢትዮጵያ ያሉትን አምባሳደሯን መጥራቷን ተከትሎ አምባሳደር አብዱላሂ ዋርፋ ወደ #ሞቃዲሾ ማቅናታቸው ተሰምቷል።
በሌላ በኩል ደግሞ ፤ የሶማሊያ ሁለቱ የፌደራል ፓርላማ ምክር ቤቶች በአሁን ሰዓት አስቸኳይ የጋራ ስብሰባ የተቀመጡ ሲሆን በዚህ ስብሰባ ላይ የሀገሪቱ ፕሬዜዳንት ሀሰን ሼክ ሞሀሙድ ንግግር ያደርጋሉ ተብሏል።
ከ100 ሚሊዮን በላይ ህዝብ ያላት ኢትዮጵያ የወደብ እና የባህር በር ተጠቃሚ ለመሆን ከጎረቤት ሀገራት ጋር ሰላማዊ የሆነና በሰጥቶ መቀበል መርህ የተቃኘ ስምምነት ላይ ለመድረስ ሙከራ ስታደርግ ቆይታለች።
በዚህ ሙከራም ከሶማሊላንድ ጋር በሊዝ የባህር በር ለማግኘት መንገድ የሚጠርግ የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርማለች።
ስምምነቱ ግን በሶማሊያ መንግስት ዘንድ ተቀባይነት አላገኘም። ሶማሊያ ራስ ገዟን ሶማሊላንድ እንደ ራሷ አንድ ግዛት ነው የምታያት በመሆኑም መሰል የወደብም ሆነ ማንኛውም ስምምነት በክልል አስተዳደር በኩል ሊፈፀም አይችልም ፤ ይህ ልዓላዊነቴን የሚጥስ ነው እያለች ነው።
@tikvahethiopia
ሶማሊያ በኢትዮጵያ ያሉትን አምባሳደሯን መጥራቷን ተከትሎ አምባሳደር አብዱላሂ ዋርፋ ወደ #ሞቃዲሾ ማቅናታቸው ተሰምቷል።
በሌላ በኩል ደግሞ ፤ የሶማሊያ ሁለቱ የፌደራል ፓርላማ ምክር ቤቶች በአሁን ሰዓት አስቸኳይ የጋራ ስብሰባ የተቀመጡ ሲሆን በዚህ ስብሰባ ላይ የሀገሪቱ ፕሬዜዳንት ሀሰን ሼክ ሞሀሙድ ንግግር ያደርጋሉ ተብሏል።
ከ100 ሚሊዮን በላይ ህዝብ ያላት ኢትዮጵያ የወደብ እና የባህር በር ተጠቃሚ ለመሆን ከጎረቤት ሀገራት ጋር ሰላማዊ የሆነና በሰጥቶ መቀበል መርህ የተቃኘ ስምምነት ላይ ለመድረስ ሙከራ ስታደርግ ቆይታለች።
በዚህ ሙከራም ከሶማሊላንድ ጋር በሊዝ የባህር በር ለማግኘት መንገድ የሚጠርግ የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርማለች።
ስምምነቱ ግን በሶማሊያ መንግስት ዘንድ ተቀባይነት አላገኘም። ሶማሊያ ራስ ገዟን ሶማሊላንድ እንደ ራሷ አንድ ግዛት ነው የምታያት በመሆኑም መሰል የወደብም ሆነ ማንኛውም ስምምነት በክልል አስተዳደር በኩል ሊፈፀም አይችልም ፤ ይህ ልዓላዊነቴን የሚጥስ ነው እያለች ነው።
@tikvahethiopia
#Ethiopia 🤝 #Somaliland
የኢትዮጵያ ባህር ትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ (ኢባትሎ) ኢትዮጵያ በሱማሌላንድ በምትወስደው የወደብ ስፍራ ላይ ልማት ለማከናወን ሲዘጋጅ መቆየቱን አስታውቋል።
ትላንት የተፈረመው ስምምነት ለስራችን ትልቅ ዜና ነው ያሉት የኢባትሎ ዋና ስራ አስፈፃሚ በሪሶ አመሎ (ዶ/ር)፤ በድርጅቱ ስራ ላይ ትልቅ እመርታ የሚያመጣ ነው ብለውታል።
በተለይ ከዋጋ እና አላስፈላጊ ወጪ ጋር በተገናኘ እንደ አገር ትልቅ እፎይታ የሚያመጣ ነው ሲሉ ስምምነቱን አሞግሰዋል።
ድርጅታቸውም በተወሰደው ቦታ ላይ መሰረተልማት ለማከናወን ሲዘጋጅ እንዲሁም የሚያስተዳድራቸውን መርከቦች መጠን ለመጨመር ሲሰራ እንደቆየ ነው የገለፁት።
ትላንት ይፋ በተደረገው ስምምነት ኢትዮጵያ በሱማሌላንድ የበርበራ ከተማ በስተ ሰሜን አቅጣጫ በሚገኝ የባህር ዳርቻ የራሷን የጦር ሰፈር እና የንግድ ወደብ እንደምታለማ ተገልፀጿል።
Via CAPITAL
@tikvahethiopia
የኢትዮጵያ ባህር ትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ (ኢባትሎ) ኢትዮጵያ በሱማሌላንድ በምትወስደው የወደብ ስፍራ ላይ ልማት ለማከናወን ሲዘጋጅ መቆየቱን አስታውቋል።
ትላንት የተፈረመው ስምምነት ለስራችን ትልቅ ዜና ነው ያሉት የኢባትሎ ዋና ስራ አስፈፃሚ በሪሶ አመሎ (ዶ/ር)፤ በድርጅቱ ስራ ላይ ትልቅ እመርታ የሚያመጣ ነው ብለውታል።
በተለይ ከዋጋ እና አላስፈላጊ ወጪ ጋር በተገናኘ እንደ አገር ትልቅ እፎይታ የሚያመጣ ነው ሲሉ ስምምነቱን አሞግሰዋል።
ድርጅታቸውም በተወሰደው ቦታ ላይ መሰረተልማት ለማከናወን ሲዘጋጅ እንዲሁም የሚያስተዳድራቸውን መርከቦች መጠን ለመጨመር ሲሰራ እንደቆየ ነው የገለፁት።
ትላንት ይፋ በተደረገው ስምምነት ኢትዮጵያ በሱማሌላንድ የበርበራ ከተማ በስተ ሰሜን አቅጣጫ በሚገኝ የባህር ዳርቻ የራሷን የጦር ሰፈር እና የንግድ ወደብ እንደምታለማ ተገልፀጿል።
Via CAPITAL
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ዛሬ በራዝ ገዟ ሶማሊላንድ ይፋዊ መግለጫ ወጥቷል። በዚህም መግለጫ ስምምነቱ ታሪካዊ ነው ተብሏል። ይህ ታሪካዊ ስምምነት ኢትዮጵያ ለሶማሌላንድ ሪፐብሊክ እውቅና በመስጠት በሊዝ የባህር በር / ለባህርኃይሎቿ የባህር መዳረሻ እንደምታገኝ መግለጫው ይገልጻል። " ስምምነቱ የጋራ ተጠቃሚነትን መሰረት ያደረገ ነው " ያለው መግለጫው ለኢትዮጵያ የባህር ኃይል ተጠቃሚነት 20 ኪሎሜትር የባህር በር እንደሚሰጥ…
#Ethiopia #Somaliland
አምባሳደር ምስጋኑ አረጋ ምን አሉ ?
የኢፌዴሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ምስጋኑ አረጋ የኢትዮጵያ የባህር በር መዳረሻ መኖር ለቀጠናዊ ውህደት ቁልፍ መሆኑን ገልጸዋል።
ከሶማሊላንድ ጋር የተደረገው ስምምነት ቀጣናዊ ሰላምና መረጋጋትን ለማስፈን ትልቅ ሚና እንደሚጫወትም አሳውቀዋል።
ከዚህ በተጨማሪ በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ላይ " የሶማሌላንድ መንግስት ያወጣውን መግለጫ በደስታ እንቀበላለን። " ብለዋል።
የሶማሊላንድ መንግስት ዛሬ ጥዋት ባወጣው መግላጫ ኢትዮጵያ በሊዝ የባህር ወደብ እንድታገኝ በምላሹ ደግሞ ለሶማሊላንድ እውቅና እንድትሰጣት የመግባቢያ ስምምነት መፈረሙን አሳውቋል።
@tikvahethiopia
አምባሳደር ምስጋኑ አረጋ ምን አሉ ?
የኢፌዴሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ምስጋኑ አረጋ የኢትዮጵያ የባህር በር መዳረሻ መኖር ለቀጠናዊ ውህደት ቁልፍ መሆኑን ገልጸዋል።
ከሶማሊላንድ ጋር የተደረገው ስምምነት ቀጣናዊ ሰላምና መረጋጋትን ለማስፈን ትልቅ ሚና እንደሚጫወትም አሳውቀዋል።
ከዚህ በተጨማሪ በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ላይ " የሶማሌላንድ መንግስት ያወጣውን መግለጫ በደስታ እንቀበላለን። " ብለዋል።
የሶማሊላንድ መንግስት ዛሬ ጥዋት ባወጣው መግላጫ ኢትዮጵያ በሊዝ የባህር ወደብ እንድታገኝ በምላሹ ደግሞ ለሶማሊላንድ እውቅና እንድትሰጣት የመግባቢያ ስምምነት መፈረሙን አሳውቋል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update ሶማሊያ በኢትዮጵያ ያሉትን አምባሳደሯን መጥራቷን ተከትሎ አምባሳደር አብዱላሂ ዋርፋ ወደ #ሞቃዲሾ ማቅናታቸው ተሰምቷል። በሌላ በኩል ደግሞ ፤ የሶማሊያ ሁለቱ የፌደራል ፓርላማ ምክር ቤቶች በአሁን ሰዓት አስቸኳይ የጋራ ስብሰባ የተቀመጡ ሲሆን በዚህ ስብሰባ ላይ የሀገሪቱ ፕሬዜዳንት ሀሰን ሼክ ሞሀሙድ ንግግር ያደርጋሉ ተብሏል። ከ100 ሚሊዮን በላይ ህዝብ ያላት ኢትዮጵያ የወደብ እና…
#Somalia #Somaliland
" የሶማሊያ ደካማ መንግስት ይሄን ታሪካዊ ስምምነት ለማስቆም ምንም አይነት ሕጋዊነት የለውም " - አብዱላሂ አርሼ (የሶማሊላንድ ባለስልጣን)
የቀድሞ የሶማሊላንድ " የሀገር ውስጥ " ሚኒስትር አማካሪ እና በአሁን ሰዓት በሶማሌላንድ " የሀገር ውስጥ " ሚኒስቴር የሚዲያ እና የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር የሆኑት አብዱላሂ አርሼ የሶማሊያን መንግሥት " ደካማ መንግሥት " ሲሉ ጠርተው በኢትዮጵያ እና በሶማሊላንድ ሪፐብሊክ መካከል የተፈረመውን #ታሪካዊ_ስምምነት ለማስቆም ምንም አይነት ሕጋዊነት የለውም ብለዋል።
" የዓለም አቀፉ ማህበረሰብ እውቅና የሰጠው የሶማሊያ ስርዓት እንደ ወቀደ መንግስት ነው፣ ሞቃዲሾ ውስጥ የአስተዳደር ስርዓት የለም። " ሲሉ ጠንካራ ትችት ሰንዝረዋል።
ኢስማኤል ሺርዋክ የተባሉ የሶማሊላንድ ዲፕሎማት ደግሞ ፤ " ሀገራችን አንድ እርምጃ ወደፊት ስትሄድ ሶማሊያ በታሪክ ግልፅ የሆነ ጥላቻ አሳይታለች። " ያሉ ሲሆን " ሶማሌላንድ እና የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ (#UAE) ስምምነት ላይ ሲደርሱ ተመሳሳይ እርምጃ ወስደዋል፣ ነገር ግን ምንም አይነት ውጤት አላመጣም። " ብለዋል።
" እንደ አንድ ሉዓላዊ ሀገር የዜጎቻችንን ጥቅም መሰረት አድርገን የሚያስፈልገውን እንወስናል " ሲሉ ገልጸዋል።
በሌላ በኩል የሶማሊያ ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ ሞሀሙድ ዛሬ ለሁለቱ የፌዴራል ም/ቤት አባላት ንግግር ማድረጋቸው የተሰማ ሲሆን የሶማሊላንድ እና የኢትዮጵያን የትብብር ስምምነት ሰነድ ተቃውመዋል።
" አንድም ኢንች የሶማሊያ ግዛት በማንም ሊፈረም አይችልም ፤ሉዓላዊነታችንንና የግዛት አንድነታችንን እንጠብቃለን ፤ በዓለም አቀፍ ህጎች መሰረት እናስከብራለን፤ እያንዳንዱን ኢንች መሬት እንጠብቃለን፤ ሶማሊያ የሶማሊያውያን ነች ፤ ይሄ የመጨረሻው ነው " ሲሉ ተናግረዋል።
" አቶ መለስ ዜናዊ በሶማሊያ ውስጥ የገቡት ጣልቃ ገብነት የአልሸባብን መነሳት አስከትሏል " ሲሉ የተደመጡት ፕሬዜዳንቱ " የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ እርምጃም ያሸነፍነውን አልሸባብ ዳግም እንዲነሳሳ ሌላ ዕድል የሚሰጥ ነው " ብለዋል።
" የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ጥር 1 ከያዙት መንገድ እንዲመለሱ " ያሉት ፕሬዜዳንቱ " ሶማሊያ እና ኢትዮጵያ ያላቸው አማራጭ አንድ ብቻ ነው እሱም በሰላም መኖር ነው " ሲሉ ተደምጠዋል።
የሶማሊንላንድ ባለልስጣናት ስምምነቱን የደገፉ ሲሆን በሶማሊያ ባለስልጣናት ላይም ጠንክራ ትችት እየሰነዘሩ ይገኛሉ። ስምምነቱን የማስቆም ምንም አይነት አቅም የላቸውም ሲሉ እየተደመጡ ናቸው።
@tikvahethiopia
" የሶማሊያ ደካማ መንግስት ይሄን ታሪካዊ ስምምነት ለማስቆም ምንም አይነት ሕጋዊነት የለውም " - አብዱላሂ አርሼ (የሶማሊላንድ ባለስልጣን)
የቀድሞ የሶማሊላንድ " የሀገር ውስጥ " ሚኒስትር አማካሪ እና በአሁን ሰዓት በሶማሌላንድ " የሀገር ውስጥ " ሚኒስቴር የሚዲያ እና የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር የሆኑት አብዱላሂ አርሼ የሶማሊያን መንግሥት " ደካማ መንግሥት " ሲሉ ጠርተው በኢትዮጵያ እና በሶማሊላንድ ሪፐብሊክ መካከል የተፈረመውን #ታሪካዊ_ስምምነት ለማስቆም ምንም አይነት ሕጋዊነት የለውም ብለዋል።
" የዓለም አቀፉ ማህበረሰብ እውቅና የሰጠው የሶማሊያ ስርዓት እንደ ወቀደ መንግስት ነው፣ ሞቃዲሾ ውስጥ የአስተዳደር ስርዓት የለም። " ሲሉ ጠንካራ ትችት ሰንዝረዋል።
ኢስማኤል ሺርዋክ የተባሉ የሶማሊላንድ ዲፕሎማት ደግሞ ፤ " ሀገራችን አንድ እርምጃ ወደፊት ስትሄድ ሶማሊያ በታሪክ ግልፅ የሆነ ጥላቻ አሳይታለች። " ያሉ ሲሆን " ሶማሌላንድ እና የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ (#UAE) ስምምነት ላይ ሲደርሱ ተመሳሳይ እርምጃ ወስደዋል፣ ነገር ግን ምንም አይነት ውጤት አላመጣም። " ብለዋል።
" እንደ አንድ ሉዓላዊ ሀገር የዜጎቻችንን ጥቅም መሰረት አድርገን የሚያስፈልገውን እንወስናል " ሲሉ ገልጸዋል።
በሌላ በኩል የሶማሊያ ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ ሞሀሙድ ዛሬ ለሁለቱ የፌዴራል ም/ቤት አባላት ንግግር ማድረጋቸው የተሰማ ሲሆን የሶማሊላንድ እና የኢትዮጵያን የትብብር ስምምነት ሰነድ ተቃውመዋል።
" አንድም ኢንች የሶማሊያ ግዛት በማንም ሊፈረም አይችልም ፤ሉዓላዊነታችንንና የግዛት አንድነታችንን እንጠብቃለን ፤ በዓለም አቀፍ ህጎች መሰረት እናስከብራለን፤ እያንዳንዱን ኢንች መሬት እንጠብቃለን፤ ሶማሊያ የሶማሊያውያን ነች ፤ ይሄ የመጨረሻው ነው " ሲሉ ተናግረዋል።
" አቶ መለስ ዜናዊ በሶማሊያ ውስጥ የገቡት ጣልቃ ገብነት የአልሸባብን መነሳት አስከትሏል " ሲሉ የተደመጡት ፕሬዜዳንቱ " የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ እርምጃም ያሸነፍነውን አልሸባብ ዳግም እንዲነሳሳ ሌላ ዕድል የሚሰጥ ነው " ብለዋል።
" የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ጥር 1 ከያዙት መንገድ እንዲመለሱ " ያሉት ፕሬዜዳንቱ " ሶማሊያ እና ኢትዮጵያ ያላቸው አማራጭ አንድ ብቻ ነው እሱም በሰላም መኖር ነው " ሲሉ ተደምጠዋል።
የሶማሊንላንድ ባለልስጣናት ስምምነቱን የደገፉ ሲሆን በሶማሊያ ባለስልጣናት ላይም ጠንክራ ትችት እየሰነዘሩ ይገኛሉ። ስምምነቱን የማስቆም ምንም አይነት አቅም የላቸውም ሲሉ እየተደመጡ ናቸው።
@tikvahethiopia