TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.2K photos
1.5K videos
211 files
4.1K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
አትሌት ለተሰንበት ግደይ አሸናፊ ሆነች። ኢትዮጵያዊቷ አትሌት ለተሰንበት ግደይ የዓለም አትሌቲክስ ኢንተርናሽናል ፌርፕሌይ (ስፖርታዊ ጨዋነት) ሽልማት አሸናፊ ሆናለች። አትሌቷ የሽልማቱ አሸናፊ የሆነችው በቡዳፔሽቱ የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ውድድር ላይ ከትውልደ ኢትዮጵያዊቷ አትሌት ሲፋን ሀሰን ጋር በነበራት ቅፅበት መሆኑ ተገልጿል። አትሌት ሲፋን በውድድሩ ላይ መውደቋን ተከትሎ አትሌት ለተሰንበት…
#TigistAssefa👏

ኢትዮጵያዊቷ አትሌት ትዕግስት አሰፋ ከስቴዲየም ውጭ ባሉ የጎዳና ላይ ውድድሮች ባሳየችው ድንቅ የሆነ ብቃት የዓመቱ ምርጥ አትሌት መባሏን የዓለም አትሌቲክስ ከደቂቃዎች በፊት ይፋ አድርጓል።

አትሌት ትዕግስት የሴቶች ማራቶንን ከሁለት ደቂቃ በላይ በማሻሻል (2:11:53 በመግባት) የዓለም ክብረወሰን ባለቤት እንደሆነች ይታወቃል።

ከቀናት በፊት ኢትዮጵያዊቷ አትሌት ለተሰንበት ግደይ ኢንተርናሽናል ፌርፕለይ (በስፖርታዊ ጨዋነት) ማሸነፏ የሚታወስ ነው።

More - @tikvahethsport

@tikvahethiopia
#አቢሲንያ_ባንክ

2ኛ ዙር የጥያቄና መልስ ውድድር ሐሙስ ታህሳስ 4 ከቀኑ 6:30 በቴሌግራም ቻናላችን ይደረጋል፡፡ ቀላል ጥያቄዎች በመመለስ ይሳተፉ፤ ይሸለሙ፡፡ በየሳምንቱ አምስት አምስት አሸናፊዎች ይሸለማሉ! ዛሬውኑ የቴሌግራም ቻናላችንን በመቀላቀል ይሸለሙ!

ሊንክ፡ https://t.iss.one/BoAEth

#telegram #giveaway #contest #Boa #bankinginethiopia #banksinethiopia #bankofabyssinia #Ethiopia #የሁሉም_ምርጫ
TIKVAH-ETHIOPIA
አቶ ታዬ ደንደአ በቁጥጥር ስር ዋሉ። የሰላም ሚኒስትር ዴኤታ የነበሩት አቶ  ታዬ ደንደአ በህግ ቁጥጥር ሥር መዋላቸውን የፀጥታ እና ደኀንነት የጋራ ግብረ ኃይል አሳውቋል። @tikvahethiopia
#Update

የአቶ ታዬ ደንአደን በቁጥጥር ስር መዋል በተመለከተ የፀጥታና ደህንነት የጋራ ግብረኃይል ምን አለ ?

ግብረ ኃይሉ አቶ ታዬ ደንደአ፥ ከለውጡ በፊት የኦነግ አባል የነበሩና በእስር ቤት የቆዩ መሆኑን ገልጿል።

የለውጡ መንግስት ባደረገላቸው ምህረት ከማረሚያ ቤት ተለቀው በተሰጣቸው እድል በተለያዩ የክልል እና የፌደራል መንግስት የኃላፊነት ቦታዎች ላይ ሲሰሩ ነበር ብሏል።

ይሁን እንጂ አቶ ታዬ ከህዝብና የመንግስት የተሰጣቸውን ኃላፊነት በተለይም ደግሞ የሰላም ሚንስትር ዴኤታ ሆነው ሰላምን ለማስፈን መሥራት ሲገባቸው በተቃራኒዉ ኢትዮጵያን ለማፍረስ ከሚንቀሳቀሱ ፀረሰላም ኃይሎች ጋር በመተሳሰር ለጥፋት ተልዕኮ በህቡዕ ሲሰሩ እንደተደረሰባቸው ገልጿል።

በሀገራችን በተለያዩ አካባቢዎች በንፁሃን ዜጎች ላይ ሲፈፀሙ በነበሩ የሽብር ተግባራት በተለይም ደግሞ #ከእገታ_ጋር በተያያዘ እጃቸው እንደአለበት ተደርሶበታል ብሏል።

አቶ ታዬ ደንደአ፤ በመንግስት ቁጥጥር ስር ሊውሉ እንደሚችሉ ሲገምቱ ታጋይ ለመምሰል በራሳቸውና በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ ትስስር ገጾች አፍራሽና ፀረ ሰላም ፅሁፎችን፣ ንግግሮችንና መግላጫዎችን በማን አለብኝነት ሲያስተላልፉና ሲሰጡ ቢቆዩም ከተጠያቂነት ማምለጥ ባለመቻላቸው በቁጥጥር ስር ውለዋል ብሏል።

ግብረኃይሉ አቶ ታዬ መንግስታዊ ኃላፊነታቸውን ተቀብለው እየሰሩ በነበረበት ወቅት መንግስታዊና የፓርቲ መዋቅሩን በሴራ ለመናድ በህቡእ እንቅስቃሴ ሲያደርጉ መቆየታቸውና ጥናትና ክትትል ሲደረግበት እንደነበር አመልክቷል።

በተደረገው ክትትልም አቶ ታዬ " ከኦነግ ሸኔ " አመራሮችና በሽብር ወንጀል ከተጠረጠሩ ጽንፈኛ ኃይሎች ጋር ትስስር በመፍጠር መንግስትን በአመጽ፣ በሽብርና፣ በትጥቅ ትግል ለመጣል ሲያሴሩ እንደ ተደረሰበት ገልጿል።

ተጠርጣሪ ታዬ በህግ ቁጥጥር ሥር ሲውሉ በመኖሪያ ቤታቸው ዉስጥ በተደረገ ፍተሻ ፦
* በህቡዕ ለሚያደርጓቸው ፀረ-ሰላም እንቅስቃሴ ሲገለገልባቸዉ የነበሩ የተለያዩ 9 ሞባይሎች፣
* 4 ላፕቶፖች፣ 3 አይፖዶች፣ በርካታ ፍላሾች፣
* 4 የተለያዩ ተሸከርካሪ ሰሌዳዎች
* ልዩ ልዩ የኤሌክትሮኒክስ መሳሪያዎች፣
* ክላሽንኮቭ ጠመንጃና ሽጉጦች ከመሰል ጥይቶች ጋር
* የኦነግ ሸኔ አርማዎችና በተለያዩ ግለሰቦች ስም የተዘጋጁ የኦነግ ሸኔ መታወቂያዎች፣ ሰነዶችና ማስታወሻዎች ተገኝተዋል ብሏል።

ከዚህም በተጨማሪ በብርበራ ወቅት በመኖሪያ ቤታቸው ውስጥ በ3 መታወቂያዎች የሚጠቀም አንድ " የኦነግ ሸኔ " አባል ተደብቆ መገኘቱንና በቁጥጥር ሥር መዋሉንም ገልጿል።

ግብረኃይሉ አቶ ታዬ ደንደአ በተመደቡባቸው ከፍተኛ የመንግስት ስልጣን ላይ ሆነው በተደጋጋሚ መንግስትን #ገዳይ እና #ጨፍጫፊ እያሉ ሲወቅሱ የሚደመጥ ቢሆንም፤ በተግባር ግን ከሽብርተኞች፣ ጽንፈኛችና ነፍሰ ገዳዮች ጋር የጥፋት ትስስር የነበራቸው ራሳቸው መሆኑ በተደረገ ክትትል ተረጋግጧል ብሏል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#TayeDendea

አቶ ታዬ ደንደአ ትላንት በይፋዊ ፌስቡክ ገፃቸው ከስልጣን መነሳታቸውን የሚገልፅ የስንብት ደብዳቤ አያይዘው ከለጠፉ እና ጠቅላይ ሚኒስትሩ ላይ ጠንካራ ቃላትን ተጠቅመው ትችት ከሰነዘሩ በኃላ #በሕግ_ሊያስጠይቃቸው የሚችል ጉዳይ ይኖር እንደሆነ ተጠይቀው ነበር።

አቶ ታዬ ፤ " በሕግ መጠየቅ ምን ችግር አለው ፣ ነገር ግን ሕግ የታለና በሕግ ይጠይቁኛል። ከጠየቁኝ ደግሞ ዝግጁ ነኝ " የሚል ምላሽ ነው የሰጡት።

በሕግ ሊጠየቁ የሚችልበት እድልም እንደሌለ ተናግረው ነበር።

ዛሬ የፀጥታ እና የደህንነት የጋራ ግብረኃይል አቶ ታዬን ደንደአን በሕግ ቁጥጥር ስር ያዋላቸው ሲሆን መኖሪያ ቤታቸው ላይም ብርበራ አድርጓል።

ግብረ ኃይሉ አቶ ታዬ ደንደአን ፦

- በሀገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች በንፁሃን ዜጎች ላይ ሲፈፀሙ በነበሩ የሽብር ተግባራት በተለይም ደግሞ #ከእገታ ጋር በተያያዘ እጃቸው እንዳለበት አሳውቋል።

(አቶ ታዬ ደንደአ በ #ሰላም_ሚኒስቴር ውስጥ ሆነው በተለያዩ ጊዜ በሚፈፀሙ የእግታ ጉዳዮች እጃቸው እንዳለበት የታወቀው መቼ ነው ? ከዚህ ቀደም ታውቆ ከሆነ ለምን እስከዛሬ ዝም ተባሉ ለሚለው ጉዳይ የተብራራ ነገር የለም)

- የሰላም ሚኒስትር ዴኤታ ሆነው ሰላምን ለማስፈን ከመስራት ይልቅ ከፀረሠላም ኃይሎች ጋር ተሳስረው ለጥፋት ተልዕኮ በህቡዕ ሲሰሩ ነበር ብሏቸዋል።

- መንግስት እና የፓርቲ መዋቅሩን በሴራ ለመናድ በህቡዕ ሲንቀሳቀሱ ነበር ብሏቸዋል።

- መንግሥት በሽብርተኝነት ከፈረጀው ከኦነግ ሸኔ አመራሮች እና በሽብር ወንጀል ከሚጠረጠሩ ፅንፈኛ ኃይሎች ጋር ትስስር ፈጥረው መንግስትን በአመፅ፣ በሽብርና በትጥቅ ለመጣል ሲያሴሩ ተደርሶባቸዋል ብሏል።

አቶ ታዬ ደንደአ ከሰሞኑን ለመገናኛ ብዙሃን እና በራሳቸው የማህበራዊ ትስስር ገፃቸው የተለያዩ አስተያየቶችን ሲሰጡ የነበረ ሲሆን ትላንት ታሕሳስ 1 በኢፌዴሪ ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ በተፃፈ ደብዳቤ ከስልጣን እንዲነሱ ተደርገዋል።

አቶ ታዬ ከስልጣን ለመነሳታቸው ምክንያቱ ጦርነት ተቃውመው ስለእርቅ ስለተናገሩ እንጂ ሌላ ምክንያት እንደሌለ ተናግረዋል። " በጦርነቱ ጊዜ ጦርነቱን ስደግፍ ሲያበረታቱኝ ነበር ሕዝቡ ይታረቅ ስንል ነው ያመማቸው " ያሉት አቶ ታዬ ሰላምን በመደገፌ ነው ከስልጣን የተነሳሁት ብለዋል።

ግብረ ኃይሉ ግን አቶ ታዬ ስልጣን ላይ ቁጭ ብለው እራሳቸው ያሉበትን #መንግስት እና #ፓርቲ ለመናድ መንግስትንም በሽብር ትጥቅ ለመጣል ከፀረሠላም ኃይሎች ጋር ሲሰሩ እንደደረሰባቸው አመልክቷል።

ልክ በቁጥጥር ስር እንደሚውሉ ሲያውቁ ደግሞ #ታጋይ ለመምሰል በየማህበራዊ ትስስር ገፆች ፀረ-ሰላም ፅሁፎችን እና ንግግሮችን ሲያስተላልፉ ነበር ብሏል።

@tikvahethiopia
#እንድታውቁት

የክፍያ መንገዶች ላይ የታሪፍ ጭማሪ ተደረገ።

የኢትዮጵያ የክፍያ መንገዶች ኢንተርፕራይዝ በሚያስተዳድራቸውን የአዲስ አበባ - አዳማ፣ የድሬዳዋ - ዳዋሌ እና የሞጆ - ባቱ የክፍያ መንገድ ከታህሳስ 3 ቀን 2016 ዓ.ም የታሪፍ ጭማሪ አድርጓል፡፡

ኢንተርፕራይዙ ባለፉት 9 ዓመታት ለ2 ጊዜ ያህል ብቻ ነው የታሪፍ ጭማሪ / ማሻሻያ የተገበረው።

የመጀመሪያው በመጋቢት 2011 ዓ.ም በአዲስ-አዳማ የክፍያ መንገድ ላይ የተተገበረ ነው።

በኮቪድ ወረርሽኝ እና ሃገራዊ የጸጥታ ችግሮች ምክንያት ለ4 አመታት የአገልግሎት ክፍያ ታሪፍ ጭማሪ ሳይደረግ ቆይቶ በህዳር 2015 ዓ.ም. የአገልግሎት ክፍያ ታሪፍ ጭማሪ መተግበሩን አመልክቷል።

የአሁኑ የታሪፍ ጭማሪ ለምን ተደረገ ?

1ኛ. የስራ ማስኬጃና መደበኛ ጥገና ወጪዎች የዋጋ ግሽበትን በመቋቋም ተቋማዊ የፋይናንስ አቅምን ለማሳደግ፤

2ኛ. ለወቅታዊ ጥገና (Periodic Maintenance) መጠባበቂያ ፈንድ ዓመታዊ ተቀማጭን በማረጋገጥ የክፍያ መንገዶችን የአገልግሎት ደረጃ ለማስጠበቅ፤

3ኛ. ምክንያታዊ ትርፍ በማስመዝገብ የመንግስት የትርፍ ድርሻ አስተዋጽዖን ለመወጣት የሚያበቃ የፋይናንስ አቋምን ለማረጋገጥ ዓመታዊ የክፍያ መንገዶች የአገልግሎት ክፍያ ታሪፍ ተመን መወሰን አስፈላጊ በመሆኑ ነው ብሏል።

የአዲስ-አዳማ እና የሞጆ-ባቱ የፍጥነት መንገዶች የአገልግሎት ደረጃቸው በፍጥነት መንገድ ደረጃ ያሉ እና ተመጋጋቢ የክፍያ መንገዶች በመሆናቸው በአንድ ዓይነት የታሪፍ ተመን የሚተዳደሩ ሲሆን በዚህም ለአዲስ-አዳማ እና የሞጆ-ባቱ የፍጥነት መንገዶች በተመሳሳይ 31% የታሪፍ ዕድገት እንዲኖረው ተደርጓል።

ለድሬደዋ - ዳዋሌ የክፍያ መንገድ ደግሞ 42% የታሪፍ ዕድገት እንዲኖረው ተደርጓል፡፡

በድሬዳዋ - ደዋሌ የክፍያ መንገድ " ባለሶስት እግር " ተሸከርካሪ ይከፍሉ የነበረው ታሪፍ ብር 10 ተቋማዊ ማህበራዊ ሃላፊነትን ከመወጣት አንጻር ታይቶ ማህበረሰቡ ለተጋነነ ትራንስፖርት ወጪ ጫና እንዳይዳረግ በሚል የአገልግሎት ክፍያ ታሪፉ በልዩ ሁኔታ ባለበት ይቀጥላል ተብሏል።

(የተደረገው የታሪፍ ጭማሪ ከላይ ተያይዟል)

@tikvahethiopia
በዘመናችን እንቅስቃሴዎች ሁሉ በጎግል መተግበሪያዎች ተደግፈው ድካም እና ወጪ ተቆጥቧል !

ጉዞዎን በጎግል ማፕ የሚደግፉ፣ በዩትዩብ ደስታን የሚፈጥሩ፣ የፍላጎትዎን የሚያገኙባቸው የጎግል መተግበሪያዎች የተጫነባቸውን ዘመናዊና ኦሪጂናል ስማርት ስልኮች በተመጣጣኝ ዋጋ በአገልግሎት መስጫ ማእከሎቻችን ሲገዙ ለ1 ዓመት በየወሩ የሚታደስ 2 ጊ.ባ ነጻ የዩትዩብ ጥቅል እንዲሁም እስከ 100 ጊ.ባ ዳታ እና 1000 ደቂቃ የድምጽ ወርሃዊ ጥቅሎች በስጦታ ያገኛሉ!

#Ethiotelecom #telebirr #RealizingDigitalEthiopia
ቀኑ እስከ ታኅሣሥ 21 ተራዝሟል                    

የመብቶች እና ዴሞክራሲ ዕድገት ማዕከል (ካርድ) ከሜታ ጋር በመተባበር ፈጠራ በተሞላበት መንገድ የሰላም መልዕክት አዘጋጅተው በማጋራት በርካታ ምላሽ ያገኙ የፌስቡክና ኢንስታግራም ተጠቃሚዎችን ለመሸለም ዝግጅቱን ማጠናቀቁ ይታወሳል።

ሆኖም ይህ ውድድር እስከ ታኅሣሥ 21 ድረስ ተራዝሟል። አሸናፊዎች ከ50 ሺሕ እስከ 100 ሺሕ ብር ድረስ ይሸለማሉ፡፡

በዚህ ውድድር ለመሳተፍ #Peace4Ethiopia #ሰላምለኢትዮጵያእና #CARDEthiopia ሃሽታጎችን ይጠቀሙ
TIKVAH-ETHIOPIA
#ETHIOPIA " ለመሆኑ ሰላም ሚኒስቴር ሰላም ነው ወይ ? " - አቶ ወንድሙ ኢብሳ " መከላከያ ወንድሞቹን መግደል የለበትም፤ ወንድሞቹም መከላከያን መግደል የለባቸውም " - አቶ ታዬ ደንደአ ሰላም ሚኒስቴር ረቡዕ ኅዳር 26 ቀን 2016 ዓ.ም አዳማ ከተማ አዘጋጅቶት በነበረው የውይይት መድረክ የተጋበዙት ጠበቃና የሕግ አማካሪ አቶ ወንድሙ ኢብሳ፣ ቲክቫህ ኢትዮጵያን ጨምሮ ከሌሎችም ጋዜጠኞች ፦ °…
" ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከስልጣን ለማባረር ዘግይተዋል " - ጠበቃና የህግ አማካሪ ወንድሙ ኢብሳ

ከቀናት በፊት አዳማ በነበረ መድረክ " ለመሆኑ ሰላም ሚኒስቴር እራሱ #ሰላም_ነው_ወይ ? ሰላም ሚኒስቴር ሰላም መስበክ ሲገባው በመ/ቤቱ ሆነው በስውር አማፂያንን የሚደግፉ ሰዎች አያለሁ " ሲሉ በወቅቱ የሚኒስትር ዴኤታ ለነበሩት አቶ ታዬ ደንደአ ጥያቄ ያቀረቡት ጠበቃና የሕግ አማካሪው አቶ ወንድሙ ኢብሳ የአቶ ታዬን ከስልጣን መነሳትና በፌስቡክ ላይ ጠቅላይ ሚኒስትሩን ተናግረው ስለፃፉት ፅሁፍ እንዲሁም አቶ በሕግ የሚያስጠይቃቸው ጉዳይ ይኖር እንደሆነ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።

ጠበቃና የሕግ አማካሪው አቶ ወንድሙ ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ጋር በነበራቸው ቆይታ ምን አሉ ?

- ከዚህ በፊት አቶ ታዬ ደንደአ በሚዲያዎች ላይ የሚሰጡት አስተያየት ላይ ተቃውሞ ስላለኝ የዛሬ አመትም " አቶ ታዬ የሰላም ሚኒስቴር እራሱ ሰላም ነው ወይ ? " ብዬ ጠይቄያቸው ነበር። ባለፈውም እንዲሁ ጠይቄያቸዋለሁ።

- በሰላም ሚኒስቴር ውስጥ ሆነው ሰላምን ሲሰብኩ አልነበረም።

- ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከስልጣን ለማባረር ዘግይተዋል። (አንስተዋቸዋል ሳይሆን አባረዋቸዋል ነው የምለው)

- አቶ ታዬ ከስልጣን ከተባረሩ በኃላ ጠቅላይ ሚኒስትሩን እጅግ በጣም ወራዳ በሆነ ቃላት መናገራቸው ቦዶነታቸውን የሚያሳይ ነው።

- ምን ጊዜም ልዩነት ይፈጠራል ፤ በለማና በዐቢይ መሃከል ልዩነት ተፈጥሯል ተከባብረው ነው የተለያዩት አልተሰዳደቡም ፤ ጉዱም ከጠ/ሚኒስትሩ ጋር ወይም ከብልፅግና ጋር ልዩነት ፈጥሯል አልተሰዳደቡም ፤ ሌላው ቀርቶ የኦነጉ ዳውድ ኢብሳ ' ትጥቅ ፈቺ ትጥቅ አስፈቺ ማነው ? ' ከማለት ባለፈ ኢትዮጵያዊ ባህል ያልሆነ ስድብ አልተሳደቡም።

- አቶ ታዬ ባለፉት አምስት ዓመታት የብልፅግናን መዝሙር ሲዘምሩ ፣ ስለብፅግና ሲቀሰቅሱ ፣ ብልፅግና ትክክል እንደሆነ ሲሰብኩ ነበር ፤ ጠቅላይ ሚኒስትሩን ሲያወድሱ ቆይተዋል ይሄን አቋማቸውን እጥፍ አድርገው  " የሚፅፉትን የሚናገሩትን እውነት ነው ብዬ ተሸወድኩኝ " ማለታቸው አቋም የሌላቸው መሆኑን ነው ያሳየኝ።

- ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከስልጣን ሳያባርሯቸው በፊት አስቀድመው ስልጣን በገዛ ፍቃዳቸው ቢለቁ ኖሮ አንድ ነገር ነው። አቶ ለማ በጨዋ ደንብ  ' ከብልፅግና ጋር #አልስማማ አልሰራም ' ብለው እንደሄዱት አላደረጉም።

- የአቶ ታዬ ጉዳይ ሰሞኑን ይወራል በቃ ያልፋል።

- በሕግም ይጠየቃሉ፣ ከባድ ማኖ ነው የነኩት።

- እራሳቸው መንግሥት ውስጥ ሆነው " ይሄ መንግሥት ሰላም አይፈልግም ፀረሰላም ነው ፣ ድርድሩ እንዳይሳካ ያደረገው የኔ መንግሥት ነው " ማለታቸውም ያስጠይቃቸዋል።

- እስከ ትላንት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከስልጣን እስኪያባርሯቸው ድረስ ምንም ሳይሉ ነው የቆዩት። ልክ ከስልጣን ሲባረሩ ግን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ' ጨካኝ  ፣ በደም የሚነግድ ' ሆኑ፤ በዚህም ይጠየቃሉ።

- ወይ ለይቶላቸው እንደነ ክቡር ለማ፣ እንደነ ክቡር ገዱ ተቃውሟቸውን በጨዋ በሰለጠነ መንገድ ገልፀው አርፈው አልተቀመጡ። ከእሳቸው ይልቅ ጫካ ያሉት ሰዎች አቋም አላቸው ፤ ለይቶላቸው አቋማቸውን ገልጸው ግልፅ የሆነ ትግል እያደረጉ ናቸው።

- አቶ ታዬ ከብልፅግና " ስልጣን አልፈልግም " ብለው ስልጣን አለቀቁም። ከስልጣን እስኪባረሩ ድረስ ነው የቆየቱ። አቶ ለማ እኮ መከላከያ ሚኒስትርን ነው ለቀው የሄዱት።

- አቶ ታዬን መሳይ ሌሎችም ብልፅግና ውስጥ አሉ።

@tikvahethiopia