TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
58.9K photos
1.5K videos
211 files
4.07K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#Tigray

ከ ' ጠላት ተባብራችኃል' በሚል ግምገማና ክስ ከስራና ከሃላፊነት ውጭ ሆነው የቆዩት 19 የትግራይ ቴሌቪዥን ጋዜጠኞችና ድጋፍ ሰጪ ሰራተኞች ወደ መደበኛ ስራቸውና የሃላፊነት ቦታቸው እንዲመለሱ ፍርድ ቤት ወሰነ።

በፍርድ ቤት ውሳኔ ወደ ሰራቸው ከተመለሱት መካከል 10 ጋዜጠኞች ፣ 7 የቴክኒክ ባለሙያዎች ፣ 2 የፕሮሞሽን ክፍል ሰራተኞች ባጠቃላይ 19 እንደሆኑ ቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ አረጋግጧል።

የፍርድ ቤት ወሳኔ ተከትሎ ጥቅምት 29/2016 ዓ.ም በትግራይ ቴሌቪዥን ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ተሻለ በቀለ ተፅፎ ማህተም ያረፈበት ደብዳቤ ፦

" ለስቪል ስርቪስ ኮሚሽን ፍርድ ቤት ባቀረባችሁት አቤቱታ መሰረት በቀን 03/12/2015 ዓ.ም በደብዳቤ ይ/ፍ/መ ቁጥር 001650/2015 ዓ.ም በሰጠው ውሳኔ ወደ ስራ ምድባችሁ እንድትመለሱ ተወስኗል። " ይላል።

ጉዳዩ መቼና ? እንዴት እንደተጀመረ ?

የቀድሞው የትግራይ ቴሌቪዥን ዋና ስራ አስኪያጅ ጋዜጠኛ ካሕሳይ ብሩ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ አስተያየቱ አጋርተዋል።

ጥቅምት 24/2013 ዓ.ም የተቀሰቀሰውን ጦርነት ተከትሎ ህዳር 19/2013 ዓ.ም የፌደራል መንግስት መቐለን ሲቆጣጠር በክልሉ ከነበሩ ድምፂ ወያነ ትግራይና የትግራይ ቴሌቪዥን ጣብያዎች መሃል ድምፂ ወያነ ባጋጠመው ውድመት እስከ ሰኔ 2013 ዓ.ም ሰርጭት ሲያቆም ከ8 ወራት ጦርነት በኃላ ሰኔ 21 /2013  ዓ.ም የትግራይ ሃይሎች መቐለን መልሰው ሲቆጣጠሩ ስራ አስኪያጁ ጋዜጠኛ ካሕሳይ ብሩ ጨምሮ 46 ባለሙያዎችና ደጋፍ ሰጪ ሰራተኞች ' ከጠላት ተባብራቹሃል ' የሚል ግምገማና ክስ ቀርቦባቸው ታስረዋል፣ ከስራ ተባረዋል ፣ ትግራይ ለቀው የወጡም አሉ።

' ከጠላት ተባብራቹሃል ' የሚል ክስ ቀርቦባቸው ከታሰሩና ከስራ ከተባረሩት  መካከል 19 ጋዜጠኛችና ድጋፍ ሰጪ ሰራተኞች ለሁለት አመታት ሲከላከሉና ሲከራከሩ ቆይተው ፍርድ ቤት አዘግይቶም ቢሆን ወደ ስራ መደባቸው እንዲመለሱ መወሰኑ የቀድሞ ስራ አስኪያጅ ጋዜጠኛ ካሕሳይ ብሩ 'ሕጊ ስዒሩ ' 'ህግ አሸንፈዋል ' ሲል ገልፆታል። 

ቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ ፣ ከመቐለ ከሚገኙ ቤተሰቡ ተለያይቶ በአዲስ አበባ ለሚገኘው የቀድሞ ስራ አስኪያጅ ጋዜጠኛ ካሕሳይ ብሩ ፍርድ ቤት በሰጠው ትእዛዝ መሰረት ወደ ስራው ይመለስ እንደሆነ ላቀረብንለት ጥያቄ ' ከነበርኩበት የሃላፊነት እርከን ሁለት ደረጃ ወደ ታች ወርደህ ስራ በመባሌ እና አሁን በተቋሙ ካለው ማኔጅመንት ለመስራት ፍላጎት ስለሌለኝ አልመልስም ' ብሏል።

በፍርድ ቤት ትእዛዝ ወደ ስራ ምድባቸው እንዲመለሱ ከተወሰነላቸው 19 ጋዜጠኞችና ድጋፍ ሰጪ ሰራተኞች በተጨማሪ በ2013 ዓ.ም በቀጥታ  (በሃንቲንግ) የተቀጠሩ 8 ጋዜጠኞች ወደ ስራ መደባቸው እንዲመለሱ ወደ ክልሉ እንባ ጠባቂና ሰብአዊ መብት ኮሚሽን አመልክተው መልስ በመጠበቅ ላይ እንደሆኑ ቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ ለማወቅ ችሏል።    
                        
@tikvahethiopia
#እንድታውቁት

የተሽከርካሪ ቀረጥና ታክስ አወሳሰን !

አንድ ተሽከርካሪ ወደ ሀገር ሲገባ ቀረጥና ታክስ የሚታሰበው ፦

- በተሽከርካሪው ዓይነት (የቤት አውቶሞቢል፣ የህዝብ ማመላለሻ ወይም የዕቃ ማመላለሻ፣ ልዩ ልዩ)

- የተሸከርካሪዉን የመጫን አቅም (የሰው ብዛት፣ የጭነት ኪሎ መጠን)፣

- ጉልበት (ለቤት አውቶሞቢሎች) መሰረት በማድረግ እንዲሁም ClF (የተገዛበት ዋጋ + የትራንስፖርት ወጪ + የኢንሹራንስ ወጪ እና ሌሎች ወጪዎችን ጨምሮ) በሚገኘዉ ጠቅላላ ወጪ ነው፡፡

#ተገጣጥመው_ወደ_ሀገር_ውስጥ_የሚገቡ አዲስ የቤት አውቶሞቢል ተሽከርካሪዎች ጉልበታቸው እስከ 13ዐዐ ከሆነ 75.67% ሲሆን ጉልበታቸው ከ1301 እስከ 1800 ደግሞ 116.79% እንዲሁም ከ18ዐዐ በላይ ጉልበት ያላቸው ከሆኑ ደግሞ 231.9% አጠቃላይ የጉምሩክ ቀረጥና ታክስ ምጣኔ ተጥሎባቸዋል፡፡

ሹፌሩን ጨምሮ እስከ 16 የመቀመጫ አቅም ያላቸው የሰው ማጓጓዣዎች እና እስከ 1.5 ቶን እቃ የመጫን አቅም ያላቸው የእቃ ማጓጓዣዎች አጠቃላይ የቀረጥና ታክስ ምጣኔ 52.5% ሲሆን ከ16 ሰው በላይ የሚጭኑ የህዝብ ማመላለሻዎች እና ከ1.5 ቶን በላይ እቃ የሚጭኑ ተሸከራካሪዎች ደግሞ 29.5% አጠቃላይ የቀረጥና ታክስ ምጣኔ ተጥሎባቸዋል፡፡

በሌላ በኩል ሀገር ውስጥ ለመገጣጠም በአምራች ድርጅቶች ወደ ሀገር የሚገቡ ሙሉ ለሙሉ ወይም በከፊል የተበተኑ (CKD/SKD) የሆኑ ተሽከራካሪዎች በተመለከተ በአዲስ ይዞታ ተገጣጥመው ወደ ሀገር ከሚገቡ ተሸከራካሪዎች በተለየ በዝቅተኛ የቀረጥና ታክስ ምጣኔ የሚስተናገዱ ሲሆን በተቃራኒው #ያገለገሉ (USED) ተሽከራካሪዎች ደግሞ ከፍተኛ የሆነ የኤክሳይዝ ታክስ ስለተጣለባቸው በአዲስ ይዞታ ከሚገቡ ተሸከራካሪዎች በአንፃራዊነት በጣም ከፍተኛ አጠቃላይ የቀረጥና ታክስ ምጣኔ አላቸው፡፡

የተሽከርካሪው ቀረጥ ማስከፈያ ዋጋ (duty paying value) በተሽከርካሪው ጠቅላላ ቀረጥና ታክስ ማስከፈያ ምጣኔ ተባዝቶ የብዜቱ ውጤት ተከፋዩ ቀረጥና ታክስ ይሆናል፡፡

እንደ ተሽከርካሪው አይነት ወደ ሀገር ውስጥ የሚገቡ የተሸከርካሪዎች ላይ እስከ #አራት_ዓይነት የቀረጥና ታክስ ዓይነት የሚጣልባቸው ሲሆን ከአምራች ድርጅቶች ውጪ የሚገቡ ተሽከርካሪዎች ከሆኑ ደግሞ በተጨማሪነት #የዊዝሆልዲንግ_ታክስ ይሰበሰባል፡፡

የቀረጥ እና የታክስ ማስከፈያ መሠረት (Tax base) የሚሆነው የእቃው ዋጋ (CIF) እና በቅድም ተከተል የሚሰላው የቀረጥ ወይም ታክስ መጠን ፦
* የጉምሩክ ቀረጥ፣
* ኤክሳይዝ ታክስ፣
* የተጨማሪ ዕሴት ታክስ፣
* ሱር ታክስ ድምር ይሆናል፡፡

የቀረጥና ታክስ መጠኑን እንዴት ተደርጎ እንደሚታሰብ ለምሳሌ ሁሉም ዓይነት ታክስ በሚመለከተው በቤት አውቶሞቢል ተሽከርካሪ በምሳሌነት እንመልከት፡፡

የቀረጥ ማስከፈያ ዋጋው ብር 4ዐዐ,ዐዐዐ፣ የሲሊንደር አቅሙ 13ዐዐ የሆነ አዲስ አውቶሞቢል ወደ ሀገር ሲገባ ፦

🚘 በቅድሚያ የጉምሩክ ቀረጥ የሚሰላ ሲሆን ማስከፈያ ዋጋው በጉምሩክ ቀረጥ ምጣኔ በማባዛት የሚሰላ ነው፡፡ በዚህም መሰረት ተከፋዩ የጉምሩክ ቀረጥ 400,000 × 3ዐ%(ከፍተኛው መጣኔ) = 12ዐ,ዐዐዐ ይሆናል፡፡

🚘 ቀጥሎ ኤክሳይዝ ታክስ የሚሰላ ሲሆን ስሌቱ የአውቶሞቢሉ የቀረጥ ማስከፈያ ዋጋ እና ተከፋዩ የጉምሩክ ቀረጥ በመደመር በኤክሳይዝ ታክስ ምጣኔ ማባዛት ነው፡፡ በዚህ ስሌት መሰረት ተከፋዩ ኤክሳይስ ታክስ መጠን (400,000 + 120,000) 5%= 26,000 ብር ይሆናል፡፡

🚘 በሶስተኛ ደረጃ ላይ የሚሰላው ተከፋይ የተጨማሪ ዕሴት ታክስ ሲሆን በዚህ ስሌት የአውቶሞቢሉን የቀረጥ ማስከፈያ ዋጋ ፣ ተከፋይ የጉምሩክ ቀረጥ እና ኤክሳይዝ ታክስን በመደመር በተጨማሪ ዕሴት ታክስ መጣኔ ይባዛል፡፡ በዚህ መሰረት የሚከፈለው ተጨማሪ ዕሴት thn (400,000 + 120,000 + 26,000) 15% = 81,9ዐዐ ብር ይሆናል፡፡

🚘 በአራተኛ ደረጃ የሚሰላው ሱር ታክስ ሲሆን ስሌቱ የአውቶሞቢሉን የቀረጥ ማስከፈያ ዋጋ፣ ተከፋይ የጉምሩክ ቀረጥ፣ ኤክሳይዝ ታክስ እና ተጨማሪ እሴት ታክስ በመደመር በሱር ታክስ መጣኔ በማባዛት ነው፡፡ በዚህ መሰረት የሚከፈለው ሱር ታክስ (400,000 + 120,000 + 26,000 +81,900) 10% = 86,190 ብር ይሆናል፡፡

🚘 ተሽከርካሪው በመደበኛ አስመጪ (ከአምራች ድርጅት ውጪ...) የሚመጣ ከሆነ በአምስተኛ ደረጃ ተከፋዩን ዊዝሆልዲንግ ታክስ ነው፡፡ ይህ ታክስ የሚሰላው የቀረጥ ማስከፈያ ዋጋን በዊዝሆልዲንግ ታክስ መጣኔ በማባዛት ነው፡፡ በዚህ መሰረት ተከፋዩ የዊዝሆልዲንግ ታክስ 4ዐዐ, 000 × 3%= 12,ዐዐዐ ብር ይሆናል፡፡

በመጨረሻም የስሌት ደረጃ ሁሉም ተከፋይ ቀረጥና ታክስ የሚደመሩ ሲሆን በዚህ መሰረት መንግስት ከዚህ አውቶሞቢል የሚሰበስበው ቀረጥና ታክስ ስሌት 120,000 + 26,000 + 81,900 + 86,190 + 12, 000= 326,090 ብር ይሆናል፡፡

#ማሳስቢያ ፦ ያገለገሉ ተሸከርካሪዎች የአገልግሎት ጊዜያቸው መሠረት በማድረግ የተለያየ ኤክሳይዝ ታክስ ይጣልባቸዋል።

ይህ መረጃ የገቢዎች ሚኒስቴር ነው።

@tikvahethiopia
"ብልሆች ወደ ህልማቸው ለመድረስ ይቆጥባሉ!" ከባንካችን ጋር አብረው ሲሰሩ ለስኬትዎ ብርቱ አጋር በመሆን የድርሻችንን እንወጣለን ፡፡

የግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ የቴሌግራም ቻናል
https://t.iss.one/Globalbankethiopia123    

ግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ !!
ለጋራ ስኬታችን !!

#globalbankethiopia #GBE #banksinethiopia #fintech #bank #finance #ethiopia #ethiopian #digitalbanking #Globaldigital
#SafaricomEthiopia

500 MB ዳታ በነጻ! 
የM-PESA ሳፋሪኮም የሞባይል አፕን በማውረድ እና ወደ አካውንቶ በመግባት ብቻ ነጻ የ500 MB ዳታ  ያግኙ!

ፕለይ ስቶር/ አፕ ስቶር https://bit.ly/M-PESA_SafaricomEthiopia  

#MPESASafaricom  
#FurtherAheadTogether
#ትግራይ

መሰቦ ስሚንቶ ፋብሪካ አዲስ የመሸጫ ዋጋ ይፋ አደረገ። 

ፋብሪካው በቴሌግራም ገፁ ይፋ ያደረገው መረጃ እንደሚያመላክተው ፤ በ PPC አይነት ስሚንቶ አዲስ የመሸጫ ዋጋ ተመን ይፋ አድርገዋል።

በዚሁ መሰረት በአዲሱ የመሸጫ አሰራር ከፋብሪካ ሰሚንቶ ለመግዛት ፣ ለማከፋፈልና ለመቸርቸር ፍቃድ ተሰጥቶዋቸው ውል ያሰሩ አካላት ፣ በችርቻሮ የሚሸጡበት ዋጋ አውጥቷል።

ፋብሪካው ጨምሮ እንደገለፀው በትግራይ ንግድና ኤክስፓርት ኤጀንሲ የስሚንቶ ምርት ተደራሽነቱ ለማስተዳርና ለመቆጣጠር በወጣውና በፀደቀው አዲስ መመሪያ ቁጥር 02/2015 መሰረት ከፋብሪካው ገዝተው በመላ ትግራይ በችርቻሮ የሚሸጡበት  የዋጋ ተመን አውጥቷል።

አዲስ የመሸጫ ዋጋው PPC አይነት ስሚንቶ የሚመለከት ሆኖ የትራንስፓርት : የመጋዘንና አስተዳደራዊ ወጪዎች ግምት ያስገባ የችርቻሮ ዋጋ እንደተቀመጠለት የፋብሪካው የቴሌግራም ገፅ  ጠቅሶ የቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ ዘግቧል።

(የሲሚንቶ መሸጫ ዋጋ ዝርዝር ከላይ ተያይዟል)

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" የቢሮዉ ቁልፍ በመቀየሩና አካባቢዉ አስጊ በመሆኑ ስራ መስራት አልቻልንም " - የሲዳማ ፌዴራሊስት ፓርቲ " በተቀነባበረ ድራማ ቢሯችን ከነዶክመንቱ ተቀምተናል " ሲል የሲዳማ ፌደራሊስት ፖርቲ የክልሉን መንግስት ከሰሰ። የፓርቲው ዋና ጽህፈት ቤት ሀላፊ የሆኑት አት ገነነ ሀሳና ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ባሰሙት ቅሬታ እንደገለጹት ከሆነ ፤ ከወራት በፊት በዲስፕሊን ግድፈት ከፓርቲዉ የታገዱት አቶ ጴጥሮስ…
" በእኛ ክልል ደረጃ በፖለቲካ አስተሳሰባቸው የሚታሰሩ ሰዎች የሉም " - አቶ ወንሰንየለህ ስምዖን (የሲዳማ ክልል ኮሚኒኬሽን ኃላፊ)

የሲዳማ ክልል መንግሥት በሲዳማ ፌዴራሊስት ፓርቲ (ሲፌፓ) ለሚቀርበው ክስ ምላሽ ሰጠ።

ክልሉ ምላሽ የሰጠው በኮሚኒኬሽን ቢሮው አማካኝነት ነው።

የሲዳማ ፌዴራሊስት ፓርቲ ምንድነው ያለው ?

(አቶ ገነነ ሀሰና - የፓርቲው የፅ/ቤት ኃላፊ / ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ሀዋሳ ቤተሰብ እና ለቪኦኤ ሬድዮ ከሰጡት ቃል)

- ጥቅምት 27 /2016 በክልሉ መንግሥት የፀጥታ አስከባሪዎች ተወሮ ተሰብሯል። ይህ ድርጊት ተፎካካሪ ፓርቲን ሆን ብሎ ለማዳከም ነው።

- ከወራት በፊት በዲስፕሊን ግድፈት ከፓርቲዉ የታገዱት አቶ ጴጥሮስ ዱቢሶ በክልሉ ፖሊስ ድጋፍ ወደቢሮዉ በመግባት የቢሮዉን ቁልፍ ቀይረውና ፋይሎቹን ይዘው ወጥተዋል።

- በወቅቱ ቢሮ ዉስጥ የነበረዉና ድርጊቱን ለመከላከል የሞከረው የፓርቲዉ አባል አቶ ሳሙኤል ላንቃሞ ተደብድበው ለእስር ተዳርገዋል።

- በአሁን ሰዓት እኔን ጨምሮ ሌሎችም ስራ አስፈፃሚ አካላት ወደ ቢሮ መግባት አልቻልንም።

- በአሁን ሰዓት ቢሮው ተወሮ ያለው በመንግሥት አካላት ነው። ሰነድ እንደፈለጉ እየበረበሩ ነው።

- ከዚህ በፊት ሲፌፓን ትደግፋላችሁ ተብለው 22 የሚደርሱ ሰዎች ታስረው ይገኛሉ። እያጣራን ነው እያሉ 2 ወር ሙሉ እስር ቤት አስቀምጠዋቸዋል። መጀመሪያ ሲያስሯቸው " ክልሉን ለማፍረስ ተንቀሳቅሰዋል " በሚል ነው። ልጆቹ ላይ ምንም መረጃ አላገኙም ዝም ብለው እያንገላቷቸው ነው።

- 48 ሌሎች ይፈለጋሉ በሚል እየተሳደዱ ነው። የኛ አባላት ተሰደው ነው ያሉት። አብዛኛው የማዕከላዊ አባላት ስደት ላይ ናቸው።

የሲዳማ ክልላዊ መንግስት ምላሽ ምንድነው ?

የሲዳማ ክልል መንግሥት ኮሚኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ አቶ ወሰንየለህ ስምዖን ለቪኦኤ ሬድዮ በሰጡት ቃል በፓርቲው አመራሮች መካከል ባለ የእርስ በእርስ ሽኩቻ እንጂ በክልሉ መንግስት ላይ የሚቀርበው ክስ እና ወቀሳ መሰረተቢስ ውንጀላ ነው ብለዋል።

ከዚህ በተጨማሪ በወንጀል የተጠረጠሩ ግለሰቦች ታስረዋል ሲሉ ተናግረዋል።

አቶ ወሰንየለህ ስምዖን (ለቪኦኤ ሬድዮ የተናገሩት) ፦

" መንግሥት አንዱ ግዴታው ህግ የማስከበር እና የህግ የበላይነትን ማረጋገጥ ነው።

በክልላችን ውስጥ በተለያየ መልኩ በአመራርነት ላይ ያላቸውን ኃላፊነት በአግባቡ ባለመጠቀም እንዲሁም ከሚዲያ አጠቃቀም ጋር ተያይዞ በሀገር ደረጃ ባሉ ህጎች መሰረት አድርጎ ጥፋተኞች ተጠርጥረው የተያዙ ሰዎች አሉ። ጉዳያቸው በህግ እየታየ ነው ሂደቱም ያለ ነው።

አያያዛቸውም ማንኛውም ዜጋ ክብሩ ተጠብቆ ተጠርጣሪ እንደሚደረገው ተደርገው ተይዘው ነው ያሉት። በህግ ስለሚታይ እሱ በሂደት ላይ ነው ያለው ሲያልቅ ለሚዲያ እናሳውቃለን።

በኛ ክልል ደረጃ በፖለቲካ አስተሳሰባቸው የሚታሰር ሰው የለም። ስለዚህ ነገሮች መደባለቅ የለባቸውም። ሴኩላር መንግስት ነው ያለን ማንም ሰው ኢትዮጵያ ውስጥ በሚታወቀው መልኩ የተለያየ ህጋዊ ፓርቲ አቋቁሞ የሚሰራበት ሀገር ነው ማንም በክልላችን በፖለቲካ አስተሳሰቡ ሊጠየቅ አይችልም። እንደ ሀገር እየተዳደርን ያለነው እየተመራም ያለው የፖለቲካ ስርዓት ስለማይፈቅድ በዚህ ደረጃ የሚመጣ ውንጀላ ትክክል አይደለም ብለን ነው የምናስበው። "

የሲዳማ ፌዴራሊስት ፓርቲ ምንም እንኳን በህጋዊ መንገድ ተቋቁሞ ወደ ስራ ቢገባም በክልሉ ውስጥ በነፃነት እንዳይቀሳቀስ በርካታ ጫናዎች እየደረሱበት ፣ አባላቱም ለእስር እና ለስደት እየተዳረጉ እንደሆነ ከዚህ ቀደም በተደጋጋሚ ማሳወቁ አይዘነጋም።

@tikvahethiopia
" የእኛን ምሩቃን ለመቅጠር ስትፈልጉ የትምህርት ማስረጃቸውን #ለማረጋገጥ ጠይቁን ፤ ትክክለኛውን ማስረጃ በአንድ ቀን ውስጥ እንሰጣችኃለን " - ዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ

ዋቻሞ ዩኒቨርሲቲ ፤ በተለያዩ ጊዜያት በተደረገው የትምህርት ማስረጃ ማጣራት በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ስም የተሠሩ #የሀሰት የትምህርት ማስረጃዎች መገኘታቸውን አሳወቀ።

ተቋሙ ፤ ህገወጥ የሀሰት የትምህርት ማስረጃ ለማጣራት በተሰራው ስራ የቀድሞ የዩኒቨርሲቲ ምሩቃን ትክክለኛ ያልሆነውን ውጤት በራሳቸው ጊዜ የራሳቸው አድርገው ውጤት ማሻሸል እንደቻሉ ተደርሶባቸዋል ብሏል።

" ይህ አሳፋሪ ወንጀል ነው " ያለው ዩኒቨርሲቲው ግለሰቦቹ ይህን በመፈፀም በአቋራጭ መንገድ ስራ የመቀጠር እና የሌሎች ሰዎች የስራ እድል ጭምር በማጥፋት ድርጊት መሰማራታቸውን አመልክቷል።

በተጨማሪም የዩኒቨርሲቲውን ስም ለመጥፋት እንደሞከሩ ገልጿል።

በእንደዚህ ዓይነት የሀሰት የትምህርት ማስረጃ ላይ መሳተፍ ከዜጎች የማይጠበቅ ተግባር ነው ያለው ዩኒቨርሲቲው በሀሰት የትምህርት ማስረጃ ማጣራት የተደረሰባቸው የቀድሞ የዩኒቨርሲቲውን ተማሪዎች ዝርዝር ይፋ አድርጓል።

ከዚህ ባለፈ ማንኛውም መንግስታዊ እና መንግስታዊ ያልሆኑ እንዲሁም የግል ተቋማትና ድርጅቶች ከዛሬ ህዳር 01/2016 ዓ.ም ጀምሮ ከዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ በሁሉም የትምህርት ፕሮግራሞች የተመረቁ ምሩቃንን ለመቅጠር ሲፈልጉ የተቀጣሪዎችን መረጃ በፖስታ ቁጥር P.O.Box 667 እንዲሁም በዩኒቨርሲቲው ኢሜይል email address: [email protected] በመላክ ማረጋገጥ እንደሚችሉ ገልጿል።

ዩኒቨርሲቲው የምሩቃንን ትክክለኛውን የትምህርት ማስረጃ በአንድ ቀን ውስጥ ሰጣለሁኝ ብሏል።

* ከላይ የዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ በሀሰት የትምህርት ማስረጃ ማጣራት የተደረሰባቸው የቀድሞ የዩኒቨርሲቲው ተማሪዎች ስም የተያያዘ ሲሆን አብዛኞቹ በተለያዩ የሀገሪቱ #ባንኮች ውስጥ እንዲሁም በመንግሥት መ/ቤት ውስጥ ተቀጥረው ሲሰሩ የተገኙ ናቸው።

@tikvahethiopia
እርሶ ፈገግ ይበሉ ሌላውን ለፋንተም ቪ ፍሊፕ ይተዉት!

አዲሱ የቴክኖ ሞባይል ምርት የሆነው ፋንተም ቪ ፍሊፕ በ(ultra clear freecam system) በመታገዝ በእጅዎ ሳይነኩ በ 64ሜጋ ፒክስል የጀርባ እና 32ሜጋ ፒክስል የፊት ካሜራ ጥርት ባለ መልኩ የፈለጉትን ያንሱ። ከፍተኛ የባትሪ አቅም እና 45ዋት ፍስት ቻርጂንግ ቴክኖሎጂ የተገጠመለት በመሆኑ በ45 ደቂቃ 100% ቻርጅ የማድረግ አቅም የያዘ አዲስ ሞዴል ያደርገዋል። እራሶን በነፃነት ለመግለፅ ቦታ እና ጊዜ ሳይገድቦ ፍላጎቶን ያጋሩ።

ቴክኖ ሞባይል ኢትዮጵያ
#PhantomVFlip#TecnoMobile #TecnoEthiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
የዳሬሰላሙ ድርድር ምን ይዞ ይመጣል ?

በኦሮሚያ ክልል በተለያዩ ጊዜያት በተፈጠሩ ግጭቶች ተፈናቅለው በየመጠለያ ጣቢያ እና በተለያዩ አከባቢ ያሉ ተፈናቃዮች የኢትዮጵያ መንግስት እና የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት በተለምዶ (ኦነግ ሸኔ) በታንዛንያ ዳሬሰላም እያካሄዱ ያሉት ድርድር ተስፋ ሰጪ ነው ብለዋል።

በሰላም እጦቱ ብዙ ነገር ካፈራንበት ቀዬ ተፈናቅለናል የሚሉት አስተያየት ሰጪዎቹ ዘላቂ ሰላም የሚሰፍን ከሆነ ወደ ነባሩ ቀዬያቸው ተመልሰው የተረጋጋ ህይወት የመምራት ተስፋቸውንም አጋርተዋል።

ከኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ወለጋ ከተለያዩ  ወረዳዎች ተፈናቅለው በዚያው አከባቢ እንዲሁም በሰሜን ወሎ ጃራ የተፈናቃዮች ካምፕ እንዲሁም ደቡብ ወሎ ቃሉ የተፈናቃዮች ካምፕ የተጠለሉት ተፈናቃዮቹ በድርድሩ ሰላም የሚሰፍን ከሆነ ወደ ተረጋጋ ህይወት በመመለስ ኑሮያቸውን ለመምራት መደላድል እንደሚፈጥር ገልጸዋል።

ተፈናቃዮቹ በሁለቱ ተፋላሚ ኃይሎች መካከል የሚደረገው ድርድር ግን ለአጠቃላላው ህብረተሰብ የውይይት መድረኮች አዘጋጅቶ ዘላቂ ሰላም ማስፈን የሚችልና ለዚያም መደላድል የሚፈጥር መሆን ይገባል ብለዋል።

ተፈናቃዮች በዚሁ አስተያየታቸው ከታች የመንግስት መዋቅር ጀምሮ በመፈተሽ ለሰላሙ መደፈርስ መጠየቅ ያለብት አካል እንዲጠየቅ ተፈናቃዮቹ ጥሪ አቅርበዋል።

በክልሉ ያሉ ችግሮች በሰላም መፍታት ተፈናቃዮቹን ወደ መደበኛ ህይወታቸው እንደሚመልስም ተስፋው ሰፊ ነው ሲል ዶቼ ቨለ ሬድዮ ዘግቧል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
የዳሬሰላሙ ድርድር ምን ይዞ ይመጣል ? በኦሮሚያ ክልል በተለያዩ ጊዜያት በተፈጠሩ ግጭቶች ተፈናቅለው በየመጠለያ ጣቢያ እና በተለያዩ አከባቢ ያሉ ተፈናቃዮች የኢትዮጵያ መንግስት እና የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት በተለምዶ (ኦነግ ሸኔ) በታንዛንያ ዳሬሰላም እያካሄዱ ያሉት ድርድር ተስፋ ሰጪ ነው ብለዋል። በሰላም እጦቱ ብዙ ነገር ካፈራንበት ቀዬ ተፈናቅለናል የሚሉት አስተያየት ሰጪዎቹ ዘላቂ ሰላም የሚሰፍን…
ተፈናቃዮች ስለ ዳሬሰላሙ ድርድር ምን አሉ ?

#1 አስተያየት ሰጪ

" ይኸኛው ድርድር ህዝቡ በሰላም ወጥቶ እንዲገባ ያስችለዋል።

ለምሳሌ ካለንበት ቡሬ መድረስ አንችልም አይደለም ቡሬ ጊዳ እንኳን ወጥቶ መመመለስ አንችልም። ከዚህ ጉተን ደርሶ መመለስ አይቻልም ከዚህ 12 እና 13 ኪ/ሜ ርቀት ላይ እንኳን ወጥቶ መግባት አይቻልም።

ወደ እርቅ ከተገባ እና ድርድሩ ከተሰራበት ይሄ ህዝብ ከአዲስ አበባ የሚፈልገውን ገዝቶ ፣ የታመመውም ታክሞ ትምህርት የሚማረውም ትምህርቱን እንዲማር ጥሩ እንቅስቃሴ ይኖረዋል።

በተለይ ወላዶች እየሞቱ ነው። እኛ አካባቢ ሰሞኑን ብቻ 4 ወላዶች ሞተዋል በወሊድ ምክንያት ፤ እናቶች እያየናቸው እየሞቱ ነው። ወስደን የምናሳክምበት የለም። የሚያዋልድ የለም። ሆስፒታል ነቀምት፣ ጊዳ ነው ያለው መሃል ላይ ሸኔ ስላለ በየት በኩል አድርገን እንወስዳለን ? እስከዚህ ድረስ የከፋ ስቃይ አለ።

እነሱ ከታረቁ እንዲህ ያለው ነገር ይቀንሳል። "

#2 አስተያየት ሰጪ

" የኦሮሞ ነፃ አውጭ ድርጅት / ኦነግ ሸኔ እና የኢትዮጵያ መንግሥት እያደረጉ ያሉት ድርድር ማኛውም ኢትዮጵያዊ ደስ ብሎታል።

ይሄ ድርድር ዘላቂነት እንዲኖረውና ስር ሰደድ እንዲሆን ምኞታችን ነው። እንዲሁም የአማራ ህዝባዊ ፋኖ እና የኢትዮጵያ መንግሥት ለህዝባዊ ፋኖ ጥሪ ቀርቦ እንዲሁ ድርድር ቢደረግ ሰላሙ ለወደፊት የተጣራና ጥሩ እንዲሆን ያደርገዋል።

ከዚህ በኃላ እነሱ ተደራድረው ሲመለሱ ተፈናቃዩም ተሳታፊ ቢሆንና አብሮ ቢሳተፍና ቢነጋገር በጣም ደስ ይለናል። ምክንያቱም ይሄ ተፈናቃይ ነው ገፈጣ ቀማሹ ፣ ኃላም ሄዶ አደጋ ላይ የሚወድቀው፣ በፊትም የወደቀው ይኸው ተፈናቃይ ነው ስለዚህ ሰላሙ ዘላቂ እንዲሆን ተፈናቃዩ በተግባር በውይይት ላይ ተሳታፊ ቢሆን መልካም ነው። "

#3 አስተያየት ሰጪ

" ድርድር መስማታችን በጣም ጥሩ ነው።

ያ ውይይት ሀገርም ያረጋጋል። እኛ ሰላም በማጣታችን ነው እዛ ካፈራነው ንብረት የወለድናቸውን ልጆችና የተለያየ ነገር አጥተን ዛሬ ቀን በፀሀይ ማታ ለብርድ ሸራ ውስጥ ያለነው።

ሰላሙ በጣም ትልቅ ነገር ነው ግን ይሄ ነገር ሲታሰብ መንግሥት እና ኦነግ ሸኔ መግባባትና ድርድር ብቻ ሳይሆን ኦሮሚያ ክልል ላይ ብሄር ብሄረሰቦች ይኖራሉ በተለይ 4ቱ ወለጋ ላይ ይታወቃል እሱን ታሳቢ ያደረገና ከግምት ያስገባ ድርስር መሆን አለበት።

ሰው እንዴት እንደሚኖር ፣ ተፋቅሮ፣ አንድ ላይ መብቱ ተከብሮ ፣ የሚፈልገውን አግኝቶ ወጥቶ ገብቶ ሰርቶ እንዲኖር ነው ሰላም የሚያስፈልገው። መቼም አንደኛው ገፍቶ አንደኛው ተገፍቶ እንደማይኖር ይታወቃል ስለዚህ ይህን ከግምት ያስገባ ውይይት እና ድርድር ተደርጎ ኦሮሚያን ሰላም ለማድረግ ከሆነ በጣም ጥሩ ነው። ተስፋ ሰጪ ነው።

ሰላም ከራሳቸው ክልል ነው የሚጀምረው ፣ ከኦነግ ሸኔ ጋር ታርቆ የሚፈልጉትን መፍታት ከቻሉ ያለው ነገር ሊፈታ ይችላል። 

እዛ ኪረሙ አካባቢ ያሉ የሁሉም ወገን ነው የተፈናቀለው ይሄንን እውነት በጥልቀት የሚሰራበት ከሆነ መጀመሪያ ህዝብን መመለስ ሳይሆን አካባቢው በአግባቡ ካረጋጋና ሰላሙ ከተጠበቀለት በኃላ የተፈናቀለና የተጎዳ ህዝብ እንዴት መመለስ እንዳለበት ማቀድና ካስገባም በኃላ ምን ይደርስበታል ? ምን ያስፈልገዋል ? የሚለውን ማሰብ ያስፈልጋል። ድርግም ያለ ሀሳብ መሆን የለበትም። "

#4

" ሰላም በውይይት እንጂ በአፈሙዝ እንደማይመጣ እንረዳለን። እኛ ነገ ከነገ በስቲያ ወደ ኦሮሚያ ክልል ሄዶ የመኖር ነገር ያሰጋናል። ለምን ? ቢባል ከዚህ ቀደም በየቦታው ተሰጋስገን ያለነው። አንድነት የለንም ስለዛ ገፈጣ ቀማሽ ሆነናል። አሁን ደግሞ በየቦታው ሄደን መውደቃችን ያሳስበናል፤ ከመጠን በላይ ። ያው በጠረጴዛ ዙሪያ ተወያይቶ ሰላም እንዲመጣ ሙሉ ተስፋ አለን። "

#5 አስተያየት ሰጪ

" ይሄ ተፈናቃይ ከዚህ የሄደው በእኛ ምክንያት ነው ይሄ ሰላም የሆነው በእኛ ምክንያት ነው ተብሎ ልክ ኦነግ ሸኔና የብልፅግናው ኦሮሚያ ላይ ብቻቸው የሚደራደሩት ብቻ ሳይሆን ይሄ ማህበረሰብ ይሄ ብሄር ብሄረሰብ የተፈናቀለውን ከግምት አስገብቶ ለነሱም ሰላም ያመጣል እነሱም እንደዚህ ሆነው መኖር ይችላሉ ተብሎ ያን ሰላም ለመምጣት የመነጨ ከሆነ ለእኛም ለተፈናቃዮቹ እዛም ለሚኖረው ማህበረሰብ ተስፋ አለው ጥሩ ነገር ያመጣል።

ግን የኦነግ ሰራዊት እና የመከላከያ ሰራዊት  ብቻ በመታረቅ ምንም የሚመጣ ፋይዳ አለ ብዬ አላስብም። ሲቪልም ያማከለ ከሆነ ውስጥ ላይ ወርዶ የሚከታተሉ ከሆነ እዚህ ላይ ትልቁን ሚና ይጫወቱታል ብዬ አስባለሁ። "

#ዶቼቨለ

@tikvahethiopia
እያንዳንዱ ምርጫ እርሶን ይገልጾታል!

በተለየ መልክ ዘመኑ የደረሰበት የተራቀቀ ቴክኖሎጂ ከአስገራሚ ውበት ጋር ያካተተ፣ ታጣፊ በመሆኑ በቦርሳ በኪስ ቢይዙት ልክክ የሚል በዘመኑ የመጨረሻ የቴክኖሎጂ እና የፈጠራ ዉጤት አካቶ ወደ ላቀ ደረጃ በመድረስ ፋንተም ቪ ፍሊፕ 5ጂ ለተጠቃሚዎች ቀርቧል። እራሶን በልዩነት ለመግልጽ ታስቦ እና ከፍ ያለውን ህልሞን በሚመጥን ደረጃ ተመርቶ  በአስደማሚ ውበት እና ምቾት  ፋንተም ቪ ፍሊፕ 5ጂ ቀርቦሎታል ። የመጪውን ዘመን ፋሽን በአዲሱ ፋንተም ቪ ፍሊፕ ይቀላቀሉ!

ቴክኖ ሞባይል ኢትዮጵያ
#PhantomVFlip#TecnoMobile #TecnoEthiopia
@samcomptech

አዳዴስ  ላፕቶፕች ገብተዋል!!!!

ለተማሪዎች፣ ለቢሮ ሰራተኞች፣ ለጌመሮች, ለቪዴዮ ኢዲተሮች ፣ ለግራፌክስ ስራዎች ፣ ለዴዛይነሮች አዳዴስ  ላፕቶፕች እና ስልኮች  በቅናሽ እና ከአንድ አመት ዋስትና ጋር እናቀርባለን።
🔵 @samcomptech

በሚገርም ፍጥነት ፣ ቅለት እና ከ 10 ሰሀት በላይ የባትሪ ቆይታ ያላቸዉ  ዘመናዊ ላፕቶፖችም አሉን።

ቴሌግራም ላይ ሁሉም ዝርዝር አለ በመቀላቀል  የሜፈልጉትን ይምረጡ  ።
🔵https://t.iss.one/samcomptech 🔵 
🔼@sww2844

ስልክ፤ 0928442662 / 0940141114
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
#AddisAbaba

" በከተማችን በርካታ በሴተኛ አዳሪነት ሥራ የተሠማሩ ሴቶች አሉ " - ወ/ሮ ወይንሸት ዘሪሁን

በአዲስ አበባ ከተማ በወሲብ ንግድ የተሰማሩ በርካታ እንስቶች፣ አፈርማቲቭ አክሽን የሚያስፈልጋቸው አካል ጉዳተኞች እንዳሉ በተደጋጋሚ ይነገራል።

እነዚህን የማኅበረሰብ ክፍሎች ችግር የመቅረፍ ኃላፊነት እስካለበት ድረስ  ምን እየሰራ እንደሆነ ቲክቫህ ኢትዮጵያ የአዲስ አበባ ሴቶችና ህፃናት ቢሮን ጠይቋል።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሴቶች ሕፃናትና ማኅበራዊ ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ወይንሸት ዘሪሁን እንደገለጹት፣ " በከተማችን በርካታ በሴተኛ አዳሪነት ሥራ የተሠማሩ ሴቶች አሉ " ብለዋል።

ኃላፊዋ፣ " አሁን ካለሁበት ቢሮ አፃር በጣም በርካታ የማኅበራዊ ጉዳት የደረሰባቸው የኅብረተሰብ ክፍሎች አሉ። ወደዚህ ቢሮ ላይ እምናስተናግደው አካል ጉዳተኛ፣ ሴቶች፣ ህፃናት፣ አረጋውያን በጣም በርካታ የማኅበራዊ ጉዳይ ተጠቂ የሆኑ አካላት ቢሮየን አንኳኩተው ይገባሉ " ሲሉ ተናግረዋል።

በከተማዋ ምን ያህል በወሲብ ንግድ የተሰማሩ ሴቶች እንዳሉ ማብራሪያ እንዲሰጡ ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ለቀረበላቸው ጥያቄ በሰጡት ምላሽ ፣ " እውነቱን ለመናገር ለጊዜው ዳታው የለኝም። ጥናት ሊመልሰው ይገባል " ሲሉ አስረድተዋል።

ኃላፊዋ ይህን ይበሉ እንጂ የአዲስ አባባ ከተማ አስተዳደር ጤና ቢሮ በመዲናዋ በወሲብ ንግድ የተሰማሩ ከ25 ሺሕ በላይ ሴቶች አሉ ተብሎ እንደሚገመት፣ ቁጥራቸው ከዚህም ሊበልጥ እንደሚችል፣ ኤች.አይ.ቪ.ኤድስ የመጠቃት ዕድላቸውም ሚዛን የደፋ እንደሆነ በአንድ ወቅት አስታውቆ ነበር።

የፌደራል ኤች አይ ቪ ኤድስ መከላከያና መቆጣጠሪያ ጽሕፈት ቤት በበኩሉ የዓለም የኤድስ ቀን ኅዳር 22 ቀን 2014 ዓ.ም በተከበረበት ወቅት በወሲብ ንግድ የተሰማሩ ሴቶች 210 ሺሕ እንደሚልቅ ገልፆ ነበር።

በወሲብ ንግድ የተሰማሩ፣ እንደ ማንኛውም የሕብረተሰብ ክፍል በተለያዩ የሥራ ዘርፎች እንዳይሳተፉ እየተገደቡ ያሉ አልካ ጉዳተኞችን በተመለከተ ቢሮው ምን እየሰራ እንደሆነ ባደረጉት ገለፃ ወ/ሮ ወይንሸት፣ በዓመት ከ10 ሺሕ በላይ የሚሆኑ በወሲብ ንግድ የተሰማሩ ሴቶችን ካሉበት ሕይወት እንዲወጡ የሚያደርግ ፕሮጀክት " ከፍተኛ በጀት " በወጣበት እየተገነባ መሆኑን፣ የአካል ጉዳተኞችን በተመለከተም በርካታ ሥራዎች እየተሰሩ መሆኑን አስረድተዋል።

አክለውም፣ ፕሮጀክቱ ወደ 50 በመቶ ገደማ እንደደረሰ፣ ይህም በተያዘው በጀት ዓመት (2016 ዓ.ም) ወደ ሥራ ለመግባት የቅድመ ሁኔታ ሥራ እየተሰራ መሆኑን አስረድተዋል።

ዘገባው በአ/አ ቲክቫህ አትዮጵያ ቤተሰብ ተዘጋጅቶ የቀረበ ነው።

@tikvahethiopia