TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.3K photos
1.51K videos
212 files
4.11K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
" ያፈራሀው ሃብት ውጤት የሚኖረው ህዝብ ተጠቃሚ ማድረግ በሚችል ቁምነገር ስታውለው ነው " - ባለሃብቱ ዘርኡ ገ/ሊባኖስ

ባለሃብቱ በሰባቱ የትግራይ ዞኖች ሰባት ትምህርት ቤቶች ለመገንባት የሚያስችል የሰምምነት ሰነድ ተፈራረሙ።

ትምህርት ቤቶቹ ከ350 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ የመነሻ ካፒታል ናቸው የሚገነቡት። 

ባለሃብቱ ኣቶ ዘርኡ ገ/ሊባኖስ ጥቅምት 11/2016 ዓ.ም በመቐለ በተከናወነው የመሰረት ድንጋይ ማስቀመጥና የስምምነት ፊርማ ስነ-ሰርአት እንዳሉት ፤ " ያፈራሀው ሃብት ውጤት የሚኖረው ህዝብ ተጠቃሚ ማድረግ በሚችል ቁምነገር ስታውለው ነው " ብለዋል። 

ትግራይ በደም አፋሳሹ ጦርነት ምክንያት ያጋጠማት ውድመት ከፍተኛ መሆኑ የጠቆሙት ባለሃብቱ ፤ ሁሉም በየአቅሙ በመልሶ ግንባታ በመሳተፍ ለትውልድ የሚተርፍ ቅዱስ ነገር መፈፀም እንዳለበት አሳስበዋል።  

በማብሰሪያ ስነ-ሰርዓቱ የተገኙት የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ፕረዚደንት ጌታቸው ረዳ በበኩላቸው ፤ " በጦርነት የወደመቸው ትግራይ መልሶ ለመገንባትና የተሰው ታጋዮች አደራ ለመፈፀም በሚደረገው ጥረት የሁሉም ትግራዋይ ተሳትፎ እጅግ ወሳኝ ነው " ብለዋል። 

በስነ-ሰርዓቱ ማብሰሪያ እንደተገለፀው የሚገነቡት ሰባት ትምህርት ቤቶች ለያንዳንዳቸው ብር 50 ሚሊዮን ፤ በአጠቃላይ 350 ሚሊዮን ብር መመደቡንና በጥራትና በጊዜ ሰሌዳ ለመፈፀም ይሰራል ተብሏል። 

ባለሃብቱ አቶ ዘርኡ ገ/ሊባኖስ የተቸገሩትን በመርዳት ባሳዩት መልካምነት ከናይጀሪያው ዎልደስ የኒቨርስቲ መስከረም 9/2016 ዓ.ም የክብር ዶክትሬት አግኝተዋል።

መረጃውን የመቐለ የቲክቫህ ቤተሰብ አባል ነው ያደረሰን።

@tikvahethiopia
" አኲርፈው የተለዩትን በጠባይ ወደ እኛ እናምጣቸው ፤ እኛም ኲርፊያን ከሚያስከትል ድርጊት እንራቅ " - ቅዱስነታቸው

የጥቅምት ወር 2016 ዓ/ም የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ በዛሬው ዕለት ተከፈተ።

ምልዓተ ጉባኤው የተከፈተው ፥ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት ባሰሙት የመክፈቻ ንግግር ነው።

ቅዱስነታቸው ምን አሉ ?

ቅዱስነታቸው ባሰሙት የመክፈቻ ንግግር ወቅት ፤ ቤተክርስቲያኗ አሁን ለጀመረችውና ለወደፊትም ለምትጀምራቸው የመልካም አስተዳደርና የልማት ስራዎች ዋስትና እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል።

" የስራዎቻችን ዋስትና በሀገርና በቤተክርስቲያን ፍጹም የሆነ ሰላምና አንድነት መኖር ነው " ብለዋል።

የጠማንን ሰላምና አንድነት መልሶ ለማምጣት የቤተክርስቲያን ኃይል የአንበሳውን ድርሻ እንደሚወስድ ገልጸዋል።

ሆኖም የቤተክርስቲያን የሰላም ጉዞ ከማንኛውም #ወገንተኝነት_በጸዳ፣ ማእከሉና ዓላማው የሀገርና የቤተክርስቲያንን አንድነት ብቻ መሠረት ያደረገ መሆን እንደሚገባው አስገንዝበዋል።

ከዚህ አንጻርም በሀገራችን ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን በቤተክርስቲያንም እንከን የለሽ አንድነት እንዲረጋገጥ በብርቱ መስራት ይኖርብናል ብለዋል።

" አኲርፈው የተለዩትን በጠባይ ወደ እኛ እናምጣቸው " ያሉት ቅዱስነታቸው " እኛም ኲርፊያን ከሚያስከትል ድርጊት እንራቅ። በአንድነት፣ በእኩልነትና በጋራ ሆነን ታላቋን ቤተክርስቲያን እንሰብስብ፣ እናገልግል፣ እንምራ፣ እንጠብቅ፡፡ ለዚህም ሙሉ ዝግጅት እናድርግ። " ብለዋል።

ቅዱስነታቸው ፤ " የዕለት ተዕለት ስራችን የቤተክርስቲያንን ጭንቀት የሚያቃልል ይሁን "  ያሉ ሲሆን " ይህ ከሆነ ቤተክርስቲያንን ያለ ምንም ጥርጥር በዕድገት ጐዳና ወደ ፊት እናሻግራለን " ሲሉ ገልጸዋል።

የታላቋን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን መንፈሳዊ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮችን መርምሮ ገምግሞና አጥንቶ ችግር ፈቺ ውሳኔን የመስጠት ኃላፊነት ያለው የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ በዛሬው ዕለት የተከፈተ መሆኑንም ቅዱስነታቸው በቤተክርቲያን ስም አብስረዋል።

(የቅዱስነታቸው ሙሉ ንግግር ከላይ ተያይዟል)

@tikvahethiopia
የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ምክር ቤት ፦

" ... በአስቸካይ ጊዜ አዋጅ ውስጥም ቢሆን በጋዜጠኞችና በመገናኛ ብዙሃን ተቀማት ላይ የሚኖር ተጠያቂነት በህጉ አግባብ ብቻ መከናወን ይኖርበታል። ይህ አለመሆኑ ግን ሀገሪቱ በአለም አቀፍ ደረጃ ያላት ገፅታ ላይ ጥላ የሚያጠላ ሆኗል፡፡

ላለፉት አምስት ዓመታት የፍትህ አካሉ የተለያዩ ማሻሻያዎች እየተደረጉበት ያለ ቢሆንም ጋዜጠኞችንና ተቋማቱን በተመለከተ በሕጉ አግባብ ተደጋጋሚ የመብት ጥሰቶችን ለማስቀረት ያለመቻሉ ምክር ቤታችንን በእጅጉ ያሳስበዋል፡፡

ችግሩ እንዲፈታም በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ለአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መርማሪ ቦርድ ጉዳዩን በማሳወቅ ክትትል እያደረገ ነው፡፡ "

(ሙሉ መግለጫው ከላይ ተያይዟል)

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#GAT_Result ብሔራዊ የድህረ ምረቃ የመግቢያ ፈተና (GAT) ውጤት ይፋ ሆኗል። ፈተናውን የወሰዳችሁ አመልካቾች ተከታዩ ሊንክ ላይ በመግባትና የማመልከቻ ቁጥራችሁን በማስገባት ውጤታችሁን ማየት ትችላላችሁ። ውጤት ለማየት፦ https://portal.aau.edu.et/Web/ApplyForAdmission/TestingStatus የፈተናው የማለፊያ ነጥብ በቀጣይ ይፋ እንደሚደረግ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ…
#GAT የመቁረጫ ነጥብ ይፋ ሆነ።

" 62 (50%) እና በላይ ጥያቄዎችን የመለሱ / 80 ፐርሰንታይል ያገኙ በሚፈልጉበት ተቋም ገብተው መማር ይችላሉ "

የትምህርት ሚኒስቴር ለሁሉም የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች እና ለሁሉም የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በፃፈው ደብዳቤ የአገራዊ የድህረ ምረቃ ፕሮግራም የመግቢያ ፈተና (National GAT) የመቁረጫ ነጥብ አሳውቋል።

በዚህም መሠረት ፤ አጠቃላይ ከተፈተኑት ጥያቄዎች ውስጥ 62 (50%) እና በላይ ጥያቄዎችን የመለሱ ወይም 80 ፐርሰንታይል (80 Percentile) ያገኙ ተፈታኞች #ብቻ ለመማር በሚፈልጉበት ተቋም አመልክተው መማር የሚችሉ እንደሆነ ተገልጿል።

የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት አመልካቾች ለማመልከት ሲመጡ ውጤታቸውን እንዲያቀርቡ በማድረግ እንዲሁም በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ https://portal.aau.edu.et/Web/ApplyForAdmission/TestingStatus በመግባት እና የተማሪውን የመግቢያ ስም (Username) እና የይለፍ ቃል (Password) በመጠቀም ማረጋገጥ ይቻላሉ ተብሏል።

በአዲሱ የትምህርት ፖሊሲ መሰረት ፤ በሁሉም የድህረ ምረቃ ፕሮግራሞች በመንግስትና በግል የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ገብተው ለመማር የሚፈልጉ አመልካቾች በሙሉ በአገር አቀፍ ደረጃ የሚሰጠውን የድህረ ምረቃ የመግቢያ ፈተና (National Graduate Admission Test-NGAT) ተፈትነው ያለፉ ብቻ መሆን እንዳለባቸው አቅጣጫ መቀመጡ ይታወሳል።

(ዛሬ ጥቅምት 12 ቀን 2016 ዓ/ም በትምህርት ሚኒስትሩ ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ ተፈርሞ የተላከው ደብዳቤ ከላይ ተያይዟል)

* ቲክቫህ ኢትዮጵያ የደብዳቤውን ትክክለኝነት ከትምህርት ሚኒስቴር አመራር ማረጋገጡን በዚሁ አጋጣሚ ያሳውቃል።

@tikvahethiopia
የሳፋሪኮምን የፌስቡክ ጥቅል በተመጣጣኝ ዋጋ በመግዛት ፤ ከምንወዳቸው ጋር እንገናኝ።

ፌስቡክ፦ https://www.facebook.com/SafaricomET
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/safaricomet/
ትዊተር- https://twitter.com/SafaricomET
ሊንክዲን- https://www.linkedin.com/company/safaricom-ethiopia/
ቴሌግራም- https://t.iss.one/Safaricom_Ethiopia_PLC

#SafaricomEthiopia #FurtherAheadTogether
TIKVAH-ETHIOPIA
#ሾኔ ከ500 በላይ የሾኔ መጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ሠራተኞች የሥራ ማቆም አድማ ላይ እንደሚገኙ ተሰማ። በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ፤ ሐዲያ ዞን ሾኔ ከተማ ፣ ላለፉት 3 ወራት የተቋረጠባቸው ደመወዝ እንዲከፈላቸው ያቀረቡት ተደጋጋሚ ጥያቄ ምላሽ አለማግኘቱን የገለጹ የሾኔ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ሠራተኞች በሥራ ማቆም አድማ ላይ እንደሚገኙ ቪኦኤ አማርኛ ዘግቧል። በጊዜያዊ ውል የተቀጠሩትን ጨምሮ…
#Update

🔹 " የፌዴራሉ መንግሥት ያለንበትን ሁኔታ አይቶ መፍትሄ እንዲሰጠን እንፈልጋለን፤ ... ጥያቄያችንን በወከልናቸው ሰዎች ለማቅረብም ወደ አዲስ አበባ ለመሄድ ዝግጅት እያደረግን ነው " - ነዋሪዎች

🔹" ሳንበላ ማከም አንችልም " - የጤና ባለሞያዎች

▪️ ባለስልጣናት ስለጉዳዩ አስተያየት እንዲሰጡ ሲደወልላቸው ስልክ አያነሱም አንዳንዶቹ ስልካቸው ዝግ ነው።

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል፣ ሃዲያ ዞን ፣ የምስረቅ ባድዋቾ ወረዳ ነዋሪዎች የህክምና እና የትምህርት አገልግሎት በመቋረጡ መቸገራቸውን እየገለፁ ይገኛሉ።

ምንም እንኳን የሰራተኞች የወራት ደመወዝ  ባለመከፈሉ የህክምና እና የትምህርት አገልግሎት ከተቋረጠ ቀናት ቢያልፉም እስከአሁን መፍትሄ እንዳልተገኘ ከነዋሪዎች ተሰምቷል።

የመንግሥት ሠራተኞች የጀመሩት የሥራ ማቆም አድማ ዛሬ ሰኞ ሁለተኛ ሳምንቱን ያስቆጠረ ሲሆን ሠራተኞቹ የሥራ ማቆም አድማውን ማካሄድ የጀመሩት  ካለፈው ሐምሌ ጀምሮ ያለው ደሞዛቸው እንዲከፈላቸው በመጠይቅ ነው።

ነዋሪዎቹ ምን አሉ ?

(በዶቼ ቨለ ሬድዮ)

- የወረዳው ሀኪሞችና መምህራን ደሞዝ አልተከፈለንም በሚል ሥራ ካቆሙ ሁለት ሳምንት አስቆጥረዋል። በዚህ ምክንያት ልጆቻችን ቤት ለመዋል ተገደዋል፤ የታመሙ ሰዎችም ህክምና ለማግኘት ተቸግረዋል።

- በሠራተኞቹ አድማ የተነሳ በወረዳው የሚገኙ መንግሥታዊ ተቋማት አሁን ድረስ አገልግሎታቸው እንደተስተጓጎለ ነው።

- የሾኔ ሆስፒታልን ጨምሮ የህክምና ተቋማትና ትምህርትት ቤቶች ሙሉ በሙሉ በመዘጋታቸው ለከፍተኛ ችግር ተደራገናል።

- በሠራተኞች ደሞዝ አለመከፍል ምክንያት የተቋረጡ የአገልግሎት መስጫ ተቋማትን ለማስቀጠል በአካባቢው ባለሥልጣናት በኩል የሚደረግ ጥረት የለም።

- ችግሩ ከወረዳ፣ ከዞኑና ከክልሉ አቅም በላይ የሆነ ይመስላል። የፌዴራሉ መንግሥት ያለንበትን ሁኔታ አይቶ መፍትሄ እንዲሰጠን እንፈልጋለን። ጥያቄያችንን ለማቅረብም በወከልናቸው ሰዎች አማካኝነት ወደ አዲስ አበባ ለመሄድ ዝግጅት እያደረግን ነው።

የመንግሥት ባለልስጣናት ምን ምላሽ ሰጡ ?

ሬድዮ ጣቢያው የምሥራቅ ባድዋቾ ወረዳ አስተዳደር፣ የሃድያ ዞን የሰው ሀብት ልማትና የመንግሥት አገልግሎት መምሪያ እና የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የፋይናንስ ቢሮ ሃላፊዎችን ለማነጋገር ጥረት ቢያሰርግም ባለሥልጣናቱ " ስብሰባ ላይ ስለሆንን ቆይታችሁ ደውሉ " የሚል ምላሽ ከሰጡ በኃላ በተባለው ሰዓት ሲደወልላቸው አንዳንዶች ጭራሽ ጥሪ አይመልሱም፤ የተቀሩት ደግሞ ሥልካቸው ተዘግቷል።

በሌላ በኩል ፤ የአካባቢው ባለሥልጣናት ትናንት እሑድ የሾኔ ሆስፒታል ሠራተኞችን ያነጋገሩ ቢሆንም ከስምምነት ሳይደርሱ መቅረታቸውን አንድ የሆስፒታሉ ሠራተኛ አሳውቀዋል።

ሠራተኛው ስብሰባውን ለጠሩት የወረዳው አመራሮች " ሳንበላ ማከም አንችልም " የሚል ምላሽ መሰጠቱን የጠቀሱት እኝሁ አስተያየት ሰጪ " መጀመሪያ ደሞዛችንን አስገቡልንና ወደ ሥራ እንመለሳለን የሚል ምላሽ ከሠራተኛው በኩል ተነስቷል ፤ መፍትሄው መክፈል ብቻ ነው ከዚህ ውጭ አማራጭ የለም በሚል ከአመራሮቹ ጋር ከስምምነት ሳንደርስ ቀርተናል " ብለዋል።

ቁጥራቸው ከሁለት ሺህ በላይ የሚሆኑት በሃድያ ዞን የምሥራቅ ባድዋቾ ወረዳ መንግሥት ሠራተኞች " የሠራንበት የሦስት ወር ደሞዝ ይከፈልን " በሚል ከሁለት ሳምንት በፊት ጀምሮ በሥራ ማቆም አድማ ላይ ናቸው።

ለሠራተኞቹ ደሞዝ መክፈል ያልተቻለው የቀድሞው የደቡብ ክልል ለወሰደው የአፈር ማዳበሪያ ብድር የወረዳውን ባጀት በዋስትና በማስያዙ እንደሆነ ከዚህ በፊት የወረዳው ባለሥልጣናት መግለፃቸውን ዶቼ ቨለ ሬድዮ በዘገባው አስታውሷል።

Credit - #DeutscheWelleRadio

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" ትምህርት ሚኒስቴር ስላለንበት ሁኔታ ከወዲሁ ያስብበት " - በአማራ ክልል ነዋሪ የሆኑ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች ሰላም በራቃቸው የአማራ ክልል ቀጠናዎች  ነዋሪ የሆኑ በተለያዩ የመንግሥት ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የሚማሩ ተማሪዎች ወቅቱ ዩኒቨርሲቲዎች የመግቢያ ቀን እያሳወቁ የሚገኙበት ቢሆንም አሁን ላይ ያለው ሁኔታ በተባለው ቀን እንዲገኙ ላያደርጋቸው እንደሚችል ስጋታቸውን ገልጸው ትምህርት…
" እባክችሁ መፍትሄ ስጡን ፤ ጊዜው ያለ ትምህርት እየሄደብን ነው " - ተማሪዎች

በአማራ ክልል ባሉ ዩኒቨርሲቲዎች ተመድበው የሚማሩ ተማሪዎች እስካሁን ወደ ትምህርት እንዳልተመለሱ በመግለፅ ትምህርት ሚኒስቴር መፍትሄ እንዲፈልግላቸው ጥሪ አቀረቡ።

መልዕክታቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የላኩ ተማሪዎች እስካሁን የሚማሩባቸው ግቢዎች እንዳልጠሯቸው በማመልከት ያለ ትምህርት መቀመጣቸውን ገልጸዋል።

በእነሱ እድሜና ተመሳሳይ የትምህርት ደረጃ የሚገኙ በሌሎች ክልሎች በሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች የሚማሩ ጓደኞቻቸው ትምህርታቸውን ለመጀመር ወደ ሚማሩበት ተቋም ከበርካታ ቀናት በፊት መግባታቸውን እነሱ ግን እስካሁን መቼ እንኳን እንደሚጠሩ እንደማያውቁ በመግለፅ ትምህርት ሚኒስቴር በጉዳዩ ላይ መፍትሄ ቢሰጥ ብለዋል።

ተማሪዎቹ ከእኩዮቻቸው ወደ ኃላ እየቀሩ መሆኑን አመልክተው ይህም የሚያሳድረው ጫና ከፍተኛ መሆኑን ገልጸዋል። በተለይም የመጀመሪያ ዓመት ተማሪዎች የፊልድ ምርጫ ካደረጉ በኃላ ወደቤት ተመልሰው ከወራት በላይ ያለትምህርት መቀመጣቸውን አመልክተዋል።

" ትምህርት ሚኒስቴር ስለኛ ጉዳይ ችላ ማለት የለበትም " ሲሉ ያሳስቡት ተማሪዎቹ የትግራይ ተማሪዎች አይነት ዕጣ ፋንታ እንዳይደርሰን ከወዲሁ አፋጣኝ መፍትሄ ይፈለግልን ሲሉ ጥሪያቸውን አቅርበዋል።

በሌላ በኩል ፤ በአማራ ክልል ባለው ተለዋዋጭ የሆነ የፀጥታ ሁኔታ ከአማራ ክልል ወደ ተለያዩ ክልሎች ወደሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች ሄደው መማር ያልቻሉ ተማሪዎች ስለመኖራቸው ለማወቅ ተችሏል።

ተማሪዎቹ በፀጥታ ሁኔታ ምክንያት ለመሄድ መንገዶች ፈታኝ እንደሆነባቸው አመልክተዋል።

አቅም ያላቸው በአየር ትራንስፖርት ፤ አንፃራዊ ሰላም ያለባቸው ቦታዎች የሚኖሩ በብዙ ብር በየብስ ትራንስፖርት ወደ ሚማሩበት ተቋም መግባታቸውን ነገር ግን የፀጥታና ደህንነት ሁኔታው ባልተሟላባቸው በተለይ ጎጃም አካባቢዎች ያሉ ተማሪዎች ወደ ትምህርት መመለስ እንዳልቻሉ የደረሱን መልዕክቶች ያስረዳሉ።

ያለው የትራንስፖርት ዋጋም ውድ በመሆኑና መንገዶችም ስለሚያሰጉ እንደ " ቀይ መስቀል " አይነት ተቋማት እስካሁን ወደ ተቋማቸው ያልገቡ ተማሪዎችን ወደ ትምህርት ተቋማቸው የሚወስዱበት መፍትሄ እንዲፈለግ ጠይቀዋል።

የትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ተወካይ ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ሰለሞን አብርሃ ከዚህ ጉዳይ ጋር በተያያዘ ከሰሞኑን ለቪኦኤ ሬድዮ ቃላቸውን ሰጥተው ነበር።

ዶ/ር ሰለሞን ፤ የደህንነት ችግር ካለባቸው አካባቢዎች የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችን ወደ ተቋማቸው የመመለሱ ስራ የሚሰራው ከወታደራዊ ኮማንድ ፖስት ጋር በመተባበር ነው ብለዋል።

" አሁን ባለው ሁኔታና ካለው የፀጥታ ሁኔታ ጋር በተያያዘ ዩኒቨርሲቲዎች በሴኔት ተማሪዎችን የሚቀበሉበትን ቀን እየወሰኑ ተማሪዎችን እየጠሩ ያለበት ሁኔታ ነው ያለው። ይሄ ደግሞ እየተሰራ ያለው በዋናነት የፀጥታ ችግር ባለባቸው አካባቢዎች በአካባቢው ከሚገኙ የኮማንድ ፖስት አካላት ጋር በቅርብ እየተወያዩ ለተማሪዎች ካለው Safety እና Security አኳያ እየተገመገመ እየተሰራ እንደሆነ እናውቃለን " ብለዋል።

" እንደ ትምህርት ሚኒስቴርም ያለው concern ትክክለኛ ስለሆነ በቅርብ እየተከታተልን ነው። የሚፈለገው የድጋፍ እና ክትትል ስራ እየሰራን ነው። እስካሁን የጎላ ችግር አልቀረበም በኛ በኩል ቀጣይ የሚነሱ ችግሮች ካሉ በዛው ካለው የፀጥታ አካላት ጋር በጋራ ሆነን እንሰራለን " ሲሉ ተናግረዋል።

#TikvahEthiopiaUniversity

@tikvahethiopia
#እንድታውቁት

ወባ (Malaria)

" በኢትዮጵያ ተከታታይ በሆኑ ጦርነቶች፣ መፈናቀሎች እንዲሁም ሌሎች ወረርሽኞች ሳቢያ በባለፉት 2 ዓመታት ላይ ተመስርቶ  በወጣ ሪፖርት የወባ በሽታ ቁጥር ከ150%-120% ጭማሪ አሳይቷል " - #WHO Ethiopia

ወባ ተላላፊ በሽታዎች ከሚባሉት መካከል አንዱ ሲሆን የሚተላለፈውም  Plasmodium በሚባል የፕሮተዞአ ዓይነት በሴቷ አኖፊለስ የወባ ትንኝ አማካኝነት ነው።

- የወባ ትንኝ ዉኃ የቋጠረ ረግረጋማ ቦታ ላይ በብዛት ትራባለች።

- የወባ በሽታ አምጪ ተህዋሲያን ብዙ በመሆናቸው የሚያስከትሉት ችግር አንዱ ከአንዱ ይለያያል። ለሞት የሚዳርጉ አሉ፤ቀለል ያለ ህመም የሚያስከትሉም አሉ። በኛ ሀገር ሁለቱም ይገኛሉ። በዋናነት የከፋ ችግር የሚያስከትሉት P.falciparum እና p.vaivax ተብለው የሚጠሩት ናቸው።

▫️P.falciparum የተባለው በአብዛኞቹ የአፍሪካ ሃገሮች ላይ በስፋትም በገዳይነትም ብዙውን ድርሻ ይወስዳል፡፡

-ለወባ በሽታ ማንኛውም ሊጋለጥ ይችላል::የወባ በሽታ ከተላላፊ በሽታዎች በገዳይነቱ ወደር የሌለው ነው።በተለይ በህፃናት፣ ነብሰ ጡር እናቶችና አረጋዊያን ላይ ሲከሰት የገዳይነት ጉልበት ያገኛል።

ምልክቶቹ ፦
▪️ከፍተኛ የሆነ ትኩሳት ፣ ማንቀጥቀጥ
▪️ከፍተኛ የሆነ የድካም ስሜት
▪️ሆድ ህመም፣ማስታወክ፣የምግብ ፍላጎት መቀነስ
▪️ራስ ምታት፣ሰውነትን ጥምቅ ሚያደርግ ላብ

- ወባ አብዛኛውን የሰውነት ክፍል ያጠቃል። የከፋ ከሚሆንባቸው አንዱ አንጎልን ሲያጠቃ ነው። በተለምዶ የጭንቅላት ወባ (Cerebral malaria) ተብሎ ይጠራል።

- ሌላው ወባ የኩላሊት መድከምን ሲያስከትል ነው። አንዳንዴ የኩላሊት እጥበት የሚያስፈልጋቸው ደረጃም ላይ ይደርሳል።

- የልብና የሳንብ ችግር በማስከተል ለሞት የመዳረግ አቅም አለው። በተጨማሪም የደም ማነስ ያስከትላል።

* መከላከያ መንገዶች

የወባ ትንኝ ንክሻን በመከላከል፤ የመራባት አቅሟን በማስቆም፣ ቅድመ መከላከል መድሐኒት በመውሰድ መከላከል ይቻላል።

- በወባ በሽታ በብዛት ተጠቂ በሆኑ ቦታዎች ላይ የቤት ውስጥ ፀረ-ወባ ትንኝ ኬሚካል ርጭት ማድረግ እንዱሁም ደግሞ በፀረ-ወባ ትንኝ ኬሚካል የተነከረ አጎበርን በአግባቡና በትክክል መጠቀም፤ዉኃ የቋጠረ ረግረጋማ ቦታን በማፋሰስ የወባ ትንኝ እንዳትራባ ማድረግ እና ወባ በብዛት ያለበት ቦታ ልንሄድ ከሆነ ሃኪም በማማከር ቀድመን ፀረ-ወባ መድሃኒት መውሰድ ናቸው፡፡

▪️ከላይ የተባሉትን ምልክቶች ብዙ ጊዜ በሽታውን በያዘችው ትንኝ ከተነከስን ከጥቂት ቀናት ወይም ሳምንታት በኋላ ልናይ እንችላለን፤አንዳንድ የወባ በሽታ አይነቶች ግን እስከ አመት ድረስ ምልክት ሳያሳዩ በሰዉነታችን ውስጥ ሊቆዩ ይችላሉ።

▫️ምልክቶቹን ካየን ግን በአፋጣኝ ወደ ህክምና ተቋም መሄድ ይኖርብናል።

#WHO, #EthioDemographyAndHealth

@tikvahethiopia
#የውሃ_ዋጋ 📈

🔹" በዚህ ልክ የተጋነነ ጭማሪ አልተደረገበትም " - ውሃ አምራች ኩባንያዎች

🔹" ከአከፋፋዮች የሚሸጥልን ዋጋ የሶስት ብር ጭማሪ አሳይቷል " - ነጋዴዎች

🔹" የነዳጅ ወጪዎች በመኖራቸዉ እሱን ለማካካስ ለነጋዴዎች ሲቀርብ ጭማሪ ተደርጓል " - አከፋፋዮች

▪️ የታሸገ ውሃ አከፋፋዮች ምን ያህል ዋጋ ነው የጨመራሁት ? ተብለው ለተጠየቁት ጥያቄ ዋጋውን ከመናገር ተቆጥበዋል።

በታሸጉ የዉሃ ምርቶች ላይ ከሰሞኑ ከፍተኛ የዋጋ ጭማሪ መደረጉ ተነግሯል።

በታሸጉ የፕላስቲክ ጠርሙስ ዉሃ ምርቶች ላይ የተደረገዉ የዋጋ ጭማሪ ከጥሬ ዕቃ መወደድ ጋር የተያያዘ መሆኑ አምራቾች ሲገልፁ በአንድ በኩል ደግሞ ከአከፋፋዮች የምንረከበዉ ምርቶች ላይ ጭማሪ በመደረጉ ነዉ ሲሉ ነጋዴዎች ተናግረዋል።

በተለይ ከሶስት ሳምንታት ወዲህ በታሸጉ የዉሃ ምርቶች ላይ ጭማሪ የተደረገ ሲሆን ከዚህ ቀደም ሲሸጡ ከነበረበት ዋጋ ላይ በእያንዳንዱ ምርት የ5 ብር ጭማሪ ማሳየቱን ካፒታል ጋዜጣ አደረኩት ያለውን ቅኝት ዋቢ በማድረግ አስነብቧል።

የዋጋዉን ጭማሪ አስመልክቶ ማን ምን አለ ?

#አምራች_ኩባንያዎች ፦ ጭማሪው ከጥሬ እቃ መወደድ እና በቅንጦት እቃዎች ላይ በሚጣለዉ ኤክሳይስ ታክስ ሳቢያ መሆኑን አንስተዋል። ቢሆንም ግን በዚህ ልክ የተጋነነ ጭማሪ አልተደረገበትም ሲሉ አሳውቀዋል።

" በሁሉም ምርቶች ላይ ከአንድ ብር በላይ ጭማሪ አልተደረገበትም " የሚሉት የዉሃ አምራች ፋብሪካዎቹ ነገር ግን በገበያ ላይ የሚሸጥበት ዋጋዉ ከእነርሱ እዉቅና ዉጪ መሆኑን አስረድተዋል።

#ነጋዴዎች ፦ ከዚህ ቀደም ሲረከቡበት የነበረዉ የዋጋ ተመን ላይ ጭማሪ መደረጉን ገልፀዉ ከአከፋፋዮች የሚሸጥላቸዉ ዋጋ የሶስት ብር ጭማሪ አሳይቷል ብለዋል።

#አከፋፋዮች ፦ የዋጋዉ ጭማሪ ከፋብሪካዎቹ በተወሰነ ደረጃ ቢሆንም የነዳጅ ወጪዎች በመኖራቸዉ እሱን ለማካካስ ለነጋዴዎች ሲያቀርብ ጭማሪ ማድረጋቸዉን ተናግረዋል። ምን ያህል እንደሆነ ግን ከመግለፅ ተቆጥበዋል።

ጉዳዩን በተመለከተ የኢትዮጵያ የዉሃ አምራች ኢንዱስትሪዎች ማህበር ስራ አስኪያጅ አቶ አሸናፊ መርዕድ ፤ የዋጋዉ መጨመር መኖሩን አረጋግጠዋል።

ለዚህ በምክንያትነት ያነሱት " ፕላስቲክ ጠርሙሶቹ የሚሰሩት ከነዳጅ ተረፈ ምርት በመሆኑ የነዳጅ ምርቶች በጦርነቱ ሳቢያ ሊጨምር በመቻሉ ፣ ኤክሳይስ ታክስ ከፍተኛ መሆን ፣ ለአምራቾቹ ለስራ ማስኬጃ የብድር እጥረት መኖር ዋነኛዎቹ መሆናቸዉን ተናግረዋል።

በገበያ ላይ ያለዉ የዋጋ ጭማሪ የተጋነነ በመሆኑ ቁጥጥር እንዲደረግበት ለሚመለከታቸው አካላት ጥያቄ አቅርበዉ ምላሻቸዉን በመጠባበቅ ላይ እንደሚገኙ ተናግረዋል።

Credit - #CAPITAL #ካፒታል_ጋዜጣ

@tikvahethiopia