TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.3K photos
1.51K videos
212 files
4.11K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#GAT_Result

ብሔራዊ የድህረ ምረቃ የመግቢያ ፈተና (GAT) ውጤት ይፋ ሆኗል።

ፈተናውን የወሰዳችሁ አመልካቾች ተከታዩ ሊንክ ላይ በመግባትና የማመልከቻ ቁጥራችሁን በማስገባት ውጤታችሁን ማየት ትችላላችሁ።

ውጤት ለማየት፦

https://portal.aau.edu.et/Web/ApplyForAdmission/TestingStatus

የፈተናው የማለፊያ ነጥብ በቀጣይ ይፋ እንደሚደረግ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ አሳውቋል።

@tikvahuniversity
" የትምህርት ሚኒስቴር በዋናነት ለተገኘው ውጤት የኔ ውድቀት ነው ብሎ ኃላፊነቱን ሊወስድ ይገባል " - ዶ/ር ነገሪ ሌንጮ

የትምህርት ሚኒስቴር ለ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ዝቅተኛ ውጤት መመዝገብ ምክንያት የሆኑ ችግሮችን በጥናት ለይቶ እንዲያቀርብ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሰዉ ኃብት ልማት፣ ሥራ ሥምሪትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ጠየቀ።

በይህ የተጠየቀው በምክር ቤቱ የሰዉ ኃብት ልማት፣ ሥራ ሥምሪትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የትምህርት ሚኒስቴርን የ2016 እቅድና የመጀመሪያ ሩብ ዓመት የሥራ አፈፃፀም ዛሬ ሲገመግም ነው።

በዚሁ ጊዜ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ " ቀደም ሲል ሲሰጡ የነበሩ የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ውጤቶች የተማሪዎችን ትክክለኛ ችሎታ ያሳዩ አልነበሩም " ብለዋል።

የፈተና አሰጣጡን በመቀየር የተመዘገበው የተማሪዎች ውጤት በዘርፉ ከዚህ ቀደም የነበሩ ችግሮች ማሳያ መሆናቸውን ጠቁመው ለዚህም ከወላጆች ጀምሮ ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተጠያቂ መሆናቸውን ገልጸዋል።

የትምህርት ጥራት ችግሩን በዘላቂነት ለመፍታት የተለያዩ ጥረቶች እየተደረጉ መሆኑን ጠቅሰው እየተካሄዱ ያሉ የትምህርት ቤቶች ማሻሻያ መርኃ ግብሮችና የመምህራን አቅም ግንባታ ሥራዎችን ለአብነት አንስተዋል።

በምክር ቤቱ የሰዉ ኃብት ልማት፣ ሥራ ሥምሪትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ዶክተር ነገሪ ሌንጮ ፤ " ሚኒስቴሩ ለ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ዝቅተኛ ውጤት መምጣት ሁሉንም ተጠያቂ ማድረግ አይቻልም " ብለዋል።

በመሆኑም የትምህርት ሚኒስቴር የማስተማርና ፈተና የማስፈተን ተልዕኮ ተሰጥቶት እንደሚሰራ ተቋም በዋናነት ለተገኘው ውጤት ኃላፊነቱን ሊወስድ ይገባዋል ነው ያሉት።

ትምህርት ሚኒስቴርን ጨምሮ ተጠሪ ተቋማትና የትምህርቱ ዘርፍ ተዋንያን ለውጤቱ የነበራቸው ድርሻ ተለይቶ መቅረብ እንዳለበትም አሳስበዋል።

ለተማሪዎች ዝቅተኛ ውጤት ማጣት ምክንያት የሆኑ ሌሎች ችግሮችም በጥናት ተለይተው ሊቀርቡ እንደሚገባም ዶክተር ነገሪ ተናግረዋል። #ኢዜአ

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
አቶ ታምሩ ገምበታን ጨምሮ ለጊዜው ቁጥራቸው ያልታወቀ ሰዎች መታሰራቸው ተሰምቷል። የኢሚግሬሽንና ዜግነት ጉዳይ አገልግሎት ምክትል ዋና ዳይሬክተር የነበሩት አቶ ታምሩ ገምበታን ጨምሮ ቁጥራቸው ለጊዜው ያልታወቁ ሰዎች በሙስና ወንጀል ተጠርጥረው መታሰራቸውን ሪፖርተር ጋዜጣ ዘግቧል። ተጠርጣሪዎቹ በቁጥጥር ሥር የዋሉት ሰሞኑን መሆኑንና አቶ ታምሩ ገምበታ ግን ጥቅምት 5 ቀን 2016 ዓ.ም. መሆኑ ተገልጿል።…
#Update

42 የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት አመራሮች እና ሠራተኞች መታሰራቸው ተገለፀ።

እንዚህ ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ሊውሉ የቻሉት ፦
- ከብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት፣
- ከኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ
- ከኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት የተውጣጣ ግብረ-ኃይል ከሙስናና ሕገወጥ ተግባር ጋር በተያያዘ ክትትልና ምርመራ ሲያደርግ ከቆየ በኃላ ነው ተብሏል።

ተጠርጣሪዎቹ ፤ ተገልጋዮች በመደበኛ የመንግሥት ስርዓት የሚፈልጉትን የፓስፖርትና መሰል አገልግሎቶችን በአፋጣኝና በአነስተኛ ዋጋ ማግኘት ሲችሉ የፈጠሯቸው የተንዛዙና እና የተወሳሰቡ አሠራሮች ዜጎችን ለከፋ እንግልት ዳርገዋል ተብሏል። በተጨማሪ ላልተገባ ወጪ እንደዳረጉ ተመላክቷል።

ከፍተኛ ገንዘብ በመጠየቅ በሙስና ተግባር ተሰማርተው የግል ጥቅማቸውን ሲያሳድዱ ነበር ተብሏል።

የተሰጣቸውን ስልጣንና ኃላፊነት በመተው  ለግል ጥቅማቸው ሲሉ ፦

- በዜግነት ኢትዮጵያዊ ላልሆኑ የውጭ ሀገራት ዜጎች፣

- በወንጀል ተከሰው የጉዞ ሰነዳቸው ለታገደባቸውና ሐሰተኛ የማንነት መገለጫ ላላቸው ሕገወጦች ጭምር የፓስፖርት፣ ሊሴፓሴና ቪዛ አየር በአየር በመሸጥና በማስተላለፍ መንገደኞች በሌሉበት ጉዞ እንዳላቸው በማስመሰል እንዲሁም የጉዞ ሰነድ በማዘጋጀት ወደ ተለያዩ ሀገራት እንደተዘዋወሩ የሚገለፅ ማሕተም በማዘጋጀት ተግባር ተሰማርተው መገኘታቸው ተገልጿል።

በተጨማሪም ከሠራተኛና ማኅበራዊ ጉዳይ ተመልምለው ያለፉ እንደሆኑ በማስመሰል ግለሰቦች ባልተገባ መንገድ ለሥራ ወደ ተለያዩ የዓረብ ሀገራት እንዲወጡ በማድረግ እንዲሁም የሕጋዊ ግለሰብን ፓስፖርት ፎቶግራፍ በመቀየር ከፍተኛ የማጭበርበር ወንጀል ሲፈጽሙ ተደርሶባቸዋል ተብሏል።

እነዚህ ተጠርጣሪዎች ከአዲስ አበባ እስከ ክልሎች የጥቅም ትስስር  በመዘርጋት ሙስና  ሲፈጽሙ እንደቆዩ ተገልጿል።

ሐሰተኛ የማንነት መታወቂያዎችን በማዘጋጀትም ተግባር ላይ ተሰማርተው ከነበሩ የውጭ ሀገር ዜጎች ጋርም ግንኙነት በመፍጠር የወንጀል ተግባር ሲፈፅሙ ቆይተዋል ተብሏል።

ይህን ተከትሎም በተደረገ ክትትል ከ200 በላይ የሚሆኑ በሕገወጥ መንገድ የተዘጋጁ #ፓስፖርቶች እንዲመክኑ መደረጉና የወንጀል ድርጊቱም መንግሥትን በሚሊየን የሚቆጠር የውጭ ምንዛሪ እንዳሳጣው ተገልጿል።

በዚህም ፦
- በአዲስ አበባ ከተማ፣
- ኦሮሚያ፣
- አማራ፣
- ሲዳማ፣
- ሶማሌ፣
- ጋምቤላ እና ቤንሻንጉል ጉምዝ ክልሎች በወንጀሉ የተሳተፉ  በኢሚግሬሽንና ዜግነት  አገልግሎት ሲያገለግሉ የነበሩ ከከፍተኛ አመራርነት እስከ ባለሙያ ያሉ 42 ተጠርጣሪዎች በሕግ ቁጥጥር ስር መዋላቸው ተገልጿል።

በወንጀል ድርጊቱ ተሰማርተው ከተገኙና በሕግ ቁጥጥር ስር ከዋሉ ተጠርጣሪዎች መካከል ፦

- የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ምክትል ዋና ዳይሬክተር የነበሩት ታምሩ ግንበቶ አዋልሶ
- ዘመድኩን ጌታቸው፣
- ከድር ሰዒድ ስሩር፣
- አስቻለው እዘዘው፣
- አብዱላሂ አሊ መሀመድ (አብዱላሂ ጃርሶ)፣
- ቴዎድሮስ ቦጋለ፣
- ጌትነት አየለ፣
-  ጀማል ገዳ፣
- ሙላት ደስታ፣
- ጅላሎ በድሩ፣
- ገነት ኃ/ማርያም፣
- ደገፋ ቤኩማ ፣
- ወንድይፍራው ሽመልስ ገ/ሰንበት እና ሌሎችም ይገኙበታል።

በተያዙት ተጠርጣሪዎች ዙሪያ ምርመራ ይቀጥላል የተባለ ሲሆን  በግለሰቦቹ ዙሪያ ተጨማሪ  መረጃ ያላቸው ዜጎች ለፌዴራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ቢሮ #ጥቆማ_መስጠት ይችላሉ ተብሏል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" የትምህርት ሚኒስቴር በዋናነት ለተገኘው ውጤት የኔ ውድቀት ነው ብሎ ኃላፊነቱን ሊወስድ ይገባል " - ዶ/ር ነገሪ ሌንጮ የትምህርት ሚኒስቴር ለ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ዝቅተኛ ውጤት መመዝገብ ምክንያት የሆኑ ችግሮችን በጥናት ለይቶ እንዲያቀርብ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሰዉ ኃብት ልማት፣ ሥራ ሥምሪትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ጠየቀ። በይህ የተጠየቀው በምክር ቤቱ የሰዉ ኃብት ልማት፣ ሥራ…
ለተማሪዎች መውደቅ ማነው ተጠያቂው ?

በህ/ተ/ም/ ቤት የሰዉ ኃብት ልማት ፣ ሥራ ሥምሪትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ዶ/ር ነገሪ ሌንጮ ፦

" ... ትምህርት ሚኒስቴር ኃላፊነቱን ወደራሱ መውሰድ አለበት በምንልበት ጊዜ ፤ ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር በቅንጅት የሚሰሩ የክልል ትምህርት ቢሮዎችን የሚመሩና እስከ ወረዳ እስከታች ድረስ እንዲሁም የትምህርት አመራሩ በትምህርት ቤት ደረጃ ምን ያህል Shock ሆነዋል ?

ተማሪው እና ወላጁ ብቻ ነው እንጂ ይሄንን እዳ የተሸከመው ሁሉም ባለበት እየሄደ ነው ማንም ኃላፊነት እየወሰደ አይደለም።

ምንድነው እየተወሰደ ያለው እርምጃ ? የትምህርት ቢሮ ኃላፊዎች፣ ከዛም እስከ ታች ያሉ ዳይሬክተሮች ሁሉም በነበረበት ቀጥሏል። በቃ ተማሪ አለፈ አላለፈ ጉዳያቸው አይደለም፤ ምንም አይቀነስባቸውም ምንም ማስጠንቀቂያ የለም ተማሪ አላሳለፈ አሳለፈ ጉዳዩ አይደለም።

እንዲህ አይነት ሁኔታ ውስጥ መቀጠል አለብን ወይ ? አይደለም ይሄንን ቢያንስ ተጠያቂነት መኖር አለበት ብሎ የሆነ ነገር ማድረግ ያለበት ትምህርት ሚኒስቴር እና ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር የሚሰሩ የክልል እና ከተማ አስተዳደሮች የቢሮ ኃላፊዎች ናቸው። "

ዶ/ር ነገሪ ሌንጮ ተጨማሪ ምን አሉ?

- በ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከ96 በመቶ በላይ የሚሆኑት ተማሪዎች 50 በመቶ እና በላይ ይማምጣት አለማቻላቸው እንዲሁ እንደኖርማል የሚወሰድ አይደለም።

- ይሄን ያህል ተማሪ አለማለፉ እንድምታው ቀላል አይደለም።

- በዚህ ነገር ተጠያቂ የሚሆነው " ሁሉም ነው " የሚለው ነገር አይቸጋሪ ነው። ተጠያቂው everybody ነው ከተባለ nobody ነው ማለት ነው።

- " ሁሉም ተጠያቂ ነው " ማለት እነማናቸው ሁሉም ? ሁሉም የሚለው መፍትሄ አያመጣም። ወላጅ የራሱ ፣ መምህራን፣ ተማሪዎች፣ ትምህርት ቢሮ በየደረጃ ከሆነ ያግባባናል።

- በሀገር ደረጃ አስፈፃሚዎች (እንደ ገንዘብ፣ ጤና...ሚኒስቴሮች) የተደራጁት በራሳቸው ተልዕኮ አኳያ በመሆኑ ትምህርት ሚኒስቴር በተሰጠው ተልዕኮ ይሄ የኔ ውድቀት ነው ብሎ መውሰድ አለበት።

- ትምህርት ሚኒስቴር ውድቀቱ የኔነው ብሎ ሲወስድ በስሩ ያሉ የክልልና የሁለቱ ከተማ አስተዳደር ቢሮዎችን ጨምሮ ነው።

- እነዚህ ተማሪዎች ከታች ጀምሮ 50 በመቶና በላይ እያመጡ ነው እዚህ የደረሱት ይህ የሚያሳየው ከታች ጀምሮ የምዘና ስርዓቱ ችግር እንዳለበት ነው። የትምህርት አሰጣጡም ችግር አለበት። አንዳንዶቹ እራሳቸው የማያውቁት እንዲያስተምሩ ይደረጋል፤ አንዳንዶች ደግሞ ኮሌጅ ሳይገቡ፣ ዲፕሎማ ዲግሪ ሳይኖራቸው የሀሰት ማስረጃ አሰርተው ዓመታት ሲያስተምሩ የቆዩ መኖራቸንም በሚዲያ ሰምተናል። ስለዚህ አጠቃላይ ስርዓቱ መፈተሽ አለበት።

- ከታች ጀምሮ ብቁዎች ብቻ ለ12ኛ ክፍል እንዲቀመጡ እያደረግን ነው ?

- ኩረጃ ስላስቀረን ነው ተማሪው የወደቀው የሚለው ሁሉንም ላያስምን ይችላል። በተወሰነ ደረጃ እውነት ነው።

- ተማሪዎች ለምን እንደወደቁ ይጠና። #ገለልተኛ ምሁራን የተካተቱበት ጥናት ይደረግና በዋናነት ተማሪዎች ለምን እንደወደቁ ይታወቅ፤ ሌሎችም ምክንያቶች ካሉ ይጠና።  እንዴት ይሄን ማስተካከል እንደሚቻል መፍትሄ ይመላከት። ያለዛ መፍትሄ አይገኝም።

ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ ስለ ገለልተኛ ጥናት ምን አሉ ?

" ገለልተኛ ጥናት ቢደረግ ለተባለው፤ ይሄ ተቋም (ፓርላማው) ገለልተኛ ስለሆነ ከተቻለ ነፃ የምሁራን ኮሚቴ አቋቁሞ ጥናቱን ለምን አያደርግም ? "

ዶ/ር ነገሪ ፤ ፓርላማው በጥናቱ ሰው ማሳተፍ እንደሚቻል ነገር ግን በባላይነት ኮሚቴ አቋቁሞ ለመስራት ከአሰራር አኳያ ተገቢ እንዳልሆነ ገልጸዋል። ጥናቱ ለሚኒስቴሩም ግብዓት ይሆናል ብለዋል።

@tikvahethiopia
#CBE

እጥፍ ወለድ ያግኙ! 
የውጭ ሐዋላ የቁጠባ ሂሳብ 
================= 

ደንበኞች ከውጭ ሀገራት የተላከላቸውን ገንዘብ ወይም በባንኩ የሚመነዝሩትን የውጭ ሀገር ገንዘብ የሚያስቀምጡበት የቁጠባ ሂሳብ ነው፡፡  

የቁጠባ ሂሳቡ በርካታ ጥቅሞች አሉት፡፡ 

• ከመደበኛው የቁጠባ ሂሳብ እጥፍ ወለድ ያስገኛል፤  
• ደንበኞች ገንዘብ ከውጭ ሀገራት ሲላክላቸው ወይም በባንኩ ሲመነዝሩ የአየር ሰዓት ስጦታ ያገኛሉ፤ 
• የሂሳቡ ባለቤቶች ለውጭ ሀገር ጉዞ የውጭ ምንዛሪ ፍላጎታቸው ቅድሚያ ይሰጣቸዋል፤ 
• ደንበኞች ከባንኩ ጋር ከሚሠሩ ድርጅቶች ለሚያገኙት አገልግሎት ወይም ለሚገዙት እቃ በፖስ ሲከፍሉ ቅናሽ ያገኛሉ፤ 
• ሌሎችንም በርካታ ጥቅሞች ያገኛሉ፡፡ 

ሂሳቡን በአቅራቢያዎ በሚገኝ ቅርንጫፍ ይክፈቱ፤ ለበለጠ መረጃ ወደ 951 ይደውሉ! 
  
ይቆጥቡ፤ የበለጠ ያግኙ!

ትክክለኛ የቴሌግራም ገፃችን https://t.iss.one/combankethofficial
TIKVAH-ETHIOPIA
የሩስያ ፕሬዜዳንት ፑቲን ቻይና ገብተዋል። ፕሬዜዳንት ቭላድሚር ፑቲን በቻይና የስራ ጉብኝት ለማድረግ እንዲሁም " የቤልት ኤንድ ሮድ " ዓለም አቀፍ ትብብር መድረክ ላይ ለመሳተፍ ቻይና ገብተዋል። በሁለት ቀን የቻይና ቆይታቸው ወቅት ከሀገሪቱ ፕሬዜዳንት እና ከሌሎች ሀገራት መሪዎች ጋር ይመክራሉ ተብሏል። ፑቲን በተለይ ሀገራቸው ከ #ዩክሬን ጋር ወደ ጦርነት ከገባች በኃላ እምብዛም ከሀገር ሲወጡ እንዳልነበር…
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ቪድዮ ፦ ፑቲን እና #የኒውክሌር_ማዘዣ ብሪፍኬዝ / ባርሳቸው ወይም “ ቼጌት ” በካሜራ እይታ ውስጥ መግባቱ የዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃንን ትኩረት ስቦ እየተቀባበሉት ነው።

ይህ መሰሉ ቪድዮ ሲሰራጭ ብዙም ያልተለመደ ነው።

የሩስያው ፕሬዜዳንት ቭላድሚር ፑቲን ከቀናት በፊት ወደ ቻይና ማቅናታቸው ይታወሳል።

ትላንት ረቡዕ ፑቲን #ቤጂንግ ውስጥ በደህንነቶች ተከበው ወደ ስብሰባ ሲያመሩ በካሜራ እይታ ውስጥ የገቡ ሲሆን አብረዋቸው (ከኃላ) እያንዳንዳቸው ብሪፍኬዝ / ቦርሳ የያዙ ሁለት የሩሲያ የባህር ሃይል መኮንኖች ዩኒፎርም የለበሱ ሰዎች ታይተዋል።

እነዚህ መኮንኖች የያዙት የኒውክሌር ጥቃትን ለማዘዝ የሚያገለግለውን የኒውክሌር ብሪፍኬዝ/ቦርሳ ወይም ቼጌት የሚባለውን ነው ተብሏል። ይህ በአስፈላጊ ሰዓት የኒውክሌር ጥቃት የሚታዘዝበት ቦርሳ አስፈላጊውን ኮዶች የያዘ ነው።

ከላይ በተያያዘው ቪድዮ ካሜራው አንደኛውን ቦርሳ አቅርቦ ሲያሳይ ተስተውሏል።

የሩስያን የኒውክሌር ብሪፍኬዝ በተለምዶ የሚያዘው በባህር ኃይል መኮንን ነው። 

ይህ ብሪፍኬዝ / ቦርሳ በማንኛውም ጊዜ ከፕሬዚዳንቱ አጠገብ የማይለይ ቢሆንም ብዙም በካሜራ እይታ ውስጥ አይገባም / አይቀረጽም።

አንዳንዶች ይህ የማዘዣ ብሪፍኬዝ #በቪድዮ_ተቀርፆ እንዲሰራጭ የተደረገው ሆን ተብሎ ለባላንጣዎቻቸው መልዕክት ለማስተላለፍ ነው ብለውታል።

ከፑቲን በተጨማሪ ፤ የሩሲያ የመከላከያ ሚኒስትርም በተመሳሳይ የኒውክሌር ብሪፍኬዝ / ቦርሳ አላቸው።

ሌሎች " ኒውክሌር " የታጠቁ ሀገራት በተመሳሳይ የማዘዣ ቦርሳ ከመሪዎቹ አጠገብ ባይጠፋም በቪድዮ እይታው ውስጥ እንዲገባ አይደረግም።

ለአብነት የአሜሪካው ፕሬዜዳንት " ኒውክሌር ፉትቦል " የሚባል ተንቀሳቃሽ የኒውክሌር ማዘዣ ያላቸው ሲሆን ፕሬዜዳንቱ ዋይትሀውስ በማኖርቡበት ጊዜ አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ ጥቃት እንዲፈፀም የሚያዙበት ነው።

Video Credit - Reuters

Via @BirlikEthiopia

@tikvahethiopia
#ሾኔ

ከ500 በላይ የሾኔ መጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ሠራተኞች የሥራ ማቆም አድማ ላይ እንደሚገኙ ተሰማ።

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ፤ ሐዲያ ዞን ሾኔ ከተማ ፣ ላለፉት 3 ወራት የተቋረጠባቸው ደመወዝ እንዲከፈላቸው ያቀረቡት ተደጋጋሚ ጥያቄ ምላሽ አለማግኘቱን የገለጹ የሾኔ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ሠራተኞች በሥራ ማቆም አድማ ላይ እንደሚገኙ ቪኦኤ አማርኛ ዘግቧል።

በጊዜያዊ ውል የተቀጠሩትን ጨምሮ ከ500 በላይ የሆስፒታሉ ጠቅላላ ሠራተኞች እንደተስማሙበት በጠቀሱት በዚሁ የሥራ ማቆም አድማ ምክንያት ከ600 ሺህ በላይ ለሚሆን ሕዝብ አገልግሎት ይሰጣል የተባለው የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታሉ ሥራ ከአቆመ 7 ቀን እንዳለፈው ሠራተኞቹ ተናግረዋል፡፡

አንድ ስማቸውን ለደህንነታቸው ሲባል እንዲገለፅ ያልፈለጉ የሆስፒታሉ ሰራተኛ ፤ " የባጀት እጥረት እየተባለ፣ ከባጀቱም ከፍቶ አሁን ደግሞ የነሃሴ ፣ መስከረም ሙሉ ወር ደመወዝ አልተከፈለም። አምናም ደሞዝ ሳይከፈል ቀርቶ ብዙ ባለሞያዎች ስራ ለቀው ሲሄዱ ነበር። እኛ ያለነውም ደመወዝ ሳይከፈለን ስራ መስራት አንችልም ብለን ነው ለቀን የወጣነው " ሲሉ ተናግረዋል።

" ለረሃብ እና ለአደጋ ተጋልጠናል፤ ደመወዝ ሳይከፈል እንዴት እንሰራለን ? እኛ እየተራብን ምንድነው የምንሰራው መጀመሪያ እኛ እራሱ መታከም አለብን ፣ እኛ መዳን አለብን ብለን ነው ያቆምነው፤ ከሁለት ዓመት በፊትም ያልተከፈለ የትርፍ ሰዓት ክፍያ አለ የሁለት ወር ክፍያ የት እንደሄደም አይታወቅም። ማንም ባለሙያውን እንደ ባለሙያ እየቆጠረው አይደለም በሚል ነው በቁጣ ለቀን የወጣው " ሲሉ አክለዋል።

" በከተማው ሌላ ሆስፒታል የሌለ ሲሆን ያሉት የተወሰኑ ጤና ጣቢያዎች ነበሩ እነሱም ከተዘጉ ቆይተዋል። ለምን ተዘጋ ? የሚል አካልም የለም " ብለዋል።

የሆስፒታሉ የተኝቶ ታካሚዎች ክፍል አስተባባሪ ዶ/ር ፋብዩ አየለ ፤ " ከ7 ቀን በፊት የድንገተኛ ክፍል ብቻ የተወሰኑ ሰዎች ተመርጠው ይሰሩ ነበር ፤ ይከፈላችኃል ተባለ ዛሬ ነገ ሲባል 72 ሰዓት ሆነ የሚከፍል የለም ከዛ በኃላ ነው ሁሉንም ክፍሎች ለመዝጋት የወሰኑት። አብዛኛው ሰራተኛ ከሌላ ቦታ የመጣ አለ፤ የቤት ኪራይ፣ የሚበላ የሚጠጣ ያጣ አለ የሚከፍለውን ያጣው አብዛኛው ሰራተኛ ወደ ቤት ሄዷል ቤተሰቡ ጋር እዚህ ተወላጅ የሆነውም ቤት ኪራይ፣ መብላት መጠጣት አለ 3 ወር ሙሉ አልተከፈለንም። አሁንም እየጠየቅን ነው ልንከፍል አንችልም የተሰጠን ብር ጎሏል አይነት ነገር ነው የሚያወሩት " ብለዋል።

ዶ/ር ፋብዩ ፤ ከዚህ ቀደምም 2012 የሁለት ወር የትርፍ ሰዓት ክፍያ መበላቱን፣ በ2015 የጥቅምት ወር በተመሳሳይ እንዳልተከፈለ አስታውሰው አሁን በጣም ሲከፋ ሰራተኛው ስራ ማቆሙን ጠቁመዋል።

የሆስፒታሉ ሜዲካል ዳይሬክተር ዶ/ር ተድላ አካሉ፤ ሆስፒታሉ ሥራ ማቆሙን አረጋግጠዋል።

በተለይ የድንገተኛ ክፍልና ማዋለጃ ክፍል አገልግሎት ሲሰጡ የነበረ ሲሆን ከ3 ቀን በፊት አንስቶ እሱም እንደተቋረጠ ገልጸዋል።

የአካባቢው ነዋሪ ሆስፒታሉ አገልግሎት እየሰጠ ባለመሆኑ ወደሌሎች አካባቢዎች ለመሄድ መገደዱን ጠቁመዋል።

የሆስፒታሉ ሥራ አስኪያጅ አቶ መለሰ ተሰማ ሆስፒታሉ ሥራ ማቆሙን ባይክዱም መረጃ ከመስጠት ግን ተቆጥበዋል።

የሐዲያ ዞን ጤና መምሪያ ኃላፊ አቶ ታከለ ኦልባሞ ከሬድዮ ጣቢያው ስልክ ሲደወልላቸው #ስብሰባ ላይ እንደሆኑ ጠቅሰው " እዚያው ሆስፒታሉን ጠይቁ " የሚል አጭር ምላሽ ሰጥተዋል።

ይህ ከ600 ሺህ በላይ ህዝብ ተደራሽ ያደርጋል፣ በቀንም እስከ 200 ታካሚ ያስተናግዳል የተባለለት ሆስፒታል ስራ በመቆሙ ህዝቡ እንግልት እየደረሰበት ይገኛል።

መረጃው የቪኦኤ ሬድዮ (ዮናታን ዘብዲዮስ) ነው።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
" ዘንድሮ 164,242 ተማሪዎችን በሬሜዲያል እንቀበላለን " - ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ

የትምህርት ሚኒስትር ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ ለፓርላማ በሰጡት ማብራሪያ በዘንድሮው ዓመት 164,242 ተማሪዎች በአቅም ማሻሻያ (ሬሜዲያል) ፕሮግራም እንደሚታቀፉ አሳውቀዋል።

እንዚህ ተማሪዎች በግልና በመንግሥት ተቋማት የሬሜዲያል ትምህርት የሚከታተሉ መሆናቸውን ገልጸዋል።

ፕ/ር ፕርሃኑ ነጋ ምን አሉ ?

- በ2014 ዓ/ም ብሔራዊ ፈተና ተፈትነው ፦

• ወደ መንግሥት ተቋማት ተመድበው የሬሜዲያል ትምህርት ከተከታተሉት 105,00 ተማሪዎች 63,033 ተማሪዎች አልፈዋል።

• በግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ትምህርታቸውን ተከታትለው  ከተፈተኑት ውስጥ 44,500 ተማሪዎች 27,587 ተማሪዎች አልፈዋል።

በአጠቃላይ ወደ 145,000 ገደማ ተማሪዎች ሬሜዲያል ገብተው በዛው በተቋማቸው ከ30% እንዲሁም ከማዕከል 70% ተፈትነው ከ50% እና በላይ አምጥተው ያለፉት 90,620 ተማሪዎች ናቸው። እነዚህ ተማሪዎች ዘንድሮ የአንደኛ ዓመት ተማሪዎች ይሆናሉ።

- በ2015 ዓ/ም ብሔራዊ ፈተና ተፈትነው ያለፉት ተማሪዎች 3.2 በመቶ ብቻ ናቸው። እነዚህ ተማሪዎች 27,267 ገደማ ናቸው። በቀጥታ ፌሽማን / አንደኛ ዓመት ተማሪዎች ይሆናሉ።

- በአጠቃላይ በ2014 ዓ/ም ተፈትነው ሬሜዲያል ያለፉና በ2015 ዓ/ም 50 በመቶ አምትጥተው በቀጥታ ያለፉትን ጨምሮ 117,887 ተማሪዎች የአንደኛ ዓመት ተማሪዎች ይሆናሉ። (90,620 ከሬሜዲያል፤ 27,267 ከ2015 ዓ/ም አላፊዎች)

- ዘንድሮ በአጠቃላይ በዩኒቨርሲቲዎች የሚመደቡት 191, 509 ተማሪዎች ናቸው። ከነዚህ ውስጥ 164,242 የሬሜዲያል ተማሪዎች ናቸው፤ እነዚህ በግል እና በመንግሥት ተቋማት ገብተው እንዲማሩ ይደረጋል።

#MoE #TIKVAH_ETHIOPIA

@tikvahethiopia
#SUNChips

መምጣቱ ላይቀር የሚያስጠብቀን የእረፍት ቀን ደርሷል! ዘና ፈታ እንበል! #መክሰስTime ደርሷል- ከ #ሰንቺፕስ 😋 ጋር #ሰኒሞመንትስ ☀️
Looking forward to snacking on the weekend with SUNChips. #SUNChips 😋 #SunnyMoments. ☀️
Facebook: https://www.facebook.com/sunchipsethiopia
Instagram: https://instagram.com/sunchipsethiopia 
#ትኩረት

" #የጨረር_ሕክምና ባለመኖሩ ከ700 በላይ ሕሙማን አገልግሎት ማግኘት አልቻሉም " - ዓይደር ሆስፒታል

የዓይደር ሆስፒታል የካንሰር ሕክምና ማዕከል ኃላፊ ክብሮም ህሉፍ ( ዶ/ር ) ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በገለጹት መሠረት፣ የጨረር ሕክምና ባለመኖሩ ከ700 በላይ ሕሙማን አገልግሎት ማግኘት አልቻሉም።

" ባለፈው ሦስትና አራት ወራት ውስጥ ወደ 800 የሚሆኑ ሪፈር የተፃፈላቸው ፔሸንቶች አሉ " ያሉት ኃላፊው፣ " በመቐለ ዩኒቨርስቲ የተጀመረው የጨረር ሕክምና አግልግሎት መስጫ ህንፃ ግንባታ የፊኒሽንግ ሥራው ስላልተጠናቀቀ ታካሚዎቻችንን ወደ ጥቁር አንበሳ፣ ጅማና ሀረሚያ ሪፈር እያልናቸው ነው " ብለዋል።

አክለውም፣ " ከጦርነት ጋር ተያይዞ፣ የትራንስፖርት መወደድ፣ ከኑሮ ውድነቱ ጋር በተያያዘ ሪፈር ከተባሉት ታካሚዎች መካከል እዚያ የሚደርሱት 10 በመቶ ብቻ የሚሆኑት ብቻ ናቸው። 90 በመቶዎቹ ሕክምና እያስፈለጋቸው አይሄዱም። ምናልባት 80 ወይም 100 የሚሆኑ ታካሚዎች ናቸው የሚሄዱት፣ ቀሪዎቹ ወደ 700 ታካሚዎች ግን እየተጠባበቁ ያሉት ምናልባት እኛ ህንጻውን ከጨረስነው ነው፣ ካልሆነ ግን ሕመሙ ምን እንደሚያደርጋቸው እየጠበቁ ነው " ሲሉ አስረድተዋል።

ክብሮም (ዶ/ር) ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ማብራሪያ ፣ " የጨረር ሕክምና ኢትዮጵያ ውስጥ ስድስት ነበር ለመትከል የታሰበው የዛሬ ስድስት፣ ሰባት ዓመታት። ጥቁር አንበሳ፣ ጅማና ሀረማያ ጀምረዋል። የሀዋሳው ተተክሎ አልቋል፣ የጎንደሩም እንደዚሁ ተቃርቧል" ሲሉ ተናግረው፣ " የእኛ የመቐሌው ግን በዚህ በነበረው ጦርነት ምክንያት፣ ከኮሮና ጋር ተያይዞ፣ መቐሌ ዩኒቨርሲቲ በገጠመው የበጀት እጥረት ሕንፃው ማለቅ አልቻለም " ብለዋል።

የጨረር ሕክምና አገልግሎት መስጫ ሕንፃ ግንባታውን ለማጠናቀቅ ምን ያህል ገንዘብ እንደሚያስፈልግ ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ለቀረበላቸው ጥያቄ በሰጡት ምላሽም፣ የሕንፃውን የፊንሺንግ ሥራዎች በማጠናቀቅ፣ ተገዝቶ የተቀመጠውን ማሽን በመገጣጠም አግልግሎቱን ለመጀመር ቢያንስ ከ60 እስከ 80 ሚሊዮን ብር ወጪ እንደሚጠይቅ ኮንትራክተሮች ተናግረዋል ብለዋል።

አክለውም፣ "በዶ/ር ሊያ የተመራ ልዑክ መቀሌ መጥቶ ነበር ከዚህ በፊት፣ በመጡበት ጊዜ ሕንፃውን ለመጨረስ ቃል ገብተው ነበር የሄዱት" ሲሉ አስታውሰው፣ " የፊኒሽንግ ሥራዎችን ለመጨረስ ብር ሊያግዙን ነበር አሁን ግን ሌሎች ቅድሚያ የሚያስፈልጋቸው የጤና ተቋማት አሉ በሚል እነርሱም እንደማይችሉ ነግረውናል። ትልቁ ችግራችን የጨረር ሕክምና ነው " ሲሉ ተናግረዋል።

በሌላ በኩል ከጦርነቱ ጋር በተያያዘ በመድኃኒት እጥረት ምክንያት ከ100 በላይ የካንሰር ሕሙማን መሞታቸውን ሆስፒታሉ ከአምስት ወራት በፊት ገልፆ ነበር። አሁን የመድኃኒት እጥረቱ እንደተቀረፈና እንዳልተቀረፈ እንዲያብራሩ ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ጥያቄ ቀርቦላቸው በሰጡት ምላሽ፣ "አሁን አዲስ አበባ ያሉት መድኃኒቶች እየመጡልን ነው። ሙሉ በሙሉ ባይሆንም በተወሰነ መልኩ ከእስከዛሬው አንፃር መሻሻሎች አሉ። ብለዋል።

"አሁንም የተወሰኑ የመድኃኒት እጥረቶች አሉ ያሉት ክብሮም (ዶ/ር) ፣ ምን ያህል ተመላላሽ የካንሰር ታካሚዎች እንዳሉ ሲያስረዱም፣ እስክ 1,500 ተመላላሽ የካንሰር ሕሙማን እንዳሉም ገልጸው፣ "አሁን ትልቁ ያለው ችግራችን የጨረር ሕክምና ነው" ሲሉ አስረድተዋል።

ያንብቡ ፦ https://telegra.ph/TikvahEthiopia-10-19

@tikvahethiopia
#MoE

ትምህርት ሚኒስቴር የ2015 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ አገር አቀፍ ፈተና ወስደው ለትምህርት ሚኒስቴር ተጠሪ በሆኑ የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች በወጪ መጋራት (ስኮላርሽፕ) ለመማር ያለፉ ተማሪዎች የዩኒቨርሲቲ እና የትምህርት መስክ ምርጫቸውን ማስተካከል ይችላሉ ብሏል።

ሚኒስቴሩ ፤ ያልፉ ተማሪዎች ምርጫቸውን ማስተካከል የሚችሉት በየትምህርት ቤታቸው በተወከሉ መምህራን በኩል እስከ ጥቅምት 14/2016 ዓ.ም ድረስ መሆኑን አስገንዝቧል።

በልዩ ሁኔታ በአዳማ እና በአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዪኒቨርሲቲዎች መማር የሚፈልጉ የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች የመግቢያ ፈተና የማይሰጥ መሆኑን አውቀው ምርጫቸው ውስጥ በማካተት መመደብ እንደሚችሉም የትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል። #MoE

@tikvahethiopia