#ብሔራዊ_ፈተና
ባለፉት ሁለት የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተናዎች በሚሊዮን የሚቆጠሩ ተማሪዎች ተፈትነው ያለፉት ግን እጅግ በጣም ጥቂት ናቸው።
ምን የተቀረ ነገር ኖሮ ነው ? የትምህርት ሚኒስትሩ ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ ከሰሞኑን በብሄራዊ ቴሌቪዥን ጣቢያ ቀርበው ማብራሪያ ሰጥታዋል።
ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ ፦
" የፈተናው ክብደ እና ቅለት ከሆነ ምንም የተቀየረ ነገር የለም።
የፈተና አሰጣጥ እና ዝግጅት ሂደት አለ፤ እራሱን የቻለ ሳይንስ አለው በጣም እንዳይከብድም በጣም እንዳይቀልም።
እስከ ዛሬ ሲሰራ ከነበረው ምንም የተለየ ነገር የለም። የተለየው ፈተና አሰጣጡ ነው።
ፈተና አሰጣጡ ያመጣው ለውጥ ምንድነው ከተባለ ፤ ከዚህ በፊት ፈተናዎች በየትምህርት ቤት ነው የሚሰጡት ፈተና መታተም ከጀመረ ጊዜ ጀምሮ ፣ ከወጣ ጊዜ ጀምሮ ፈተናዎቹ ይሰረቃሉ።
ፈተና ሲሰረቅ የነበረው በተደራጀ መልክ ነው በክልሎች ፈታኞች በየክልሉ ሲሄዱ ትልቅ ግብዣ ተደርጎ ጉቦ ተሰጥቷቸው ተማሪዎቹ እንዲኮራረጁ ይደረጋል። ውጤቱ ትርጉም ያለው አልነበረም።
እኔ ትምህርት ሚኒስቴር የመጣሁ ጊዜ በሁለተኛው ሳምንት ፈተና ሰጥተን ነበር በድሮው አሰጣት ፎርማት ያኔ ነው የማለፊያ ውጤት 50 በመቶ ነው ብለን ፖሊሲ ያደረግነው ፣በወቅቱ ፈተና አሰጣጡን አልቀየርንም ነበር ያኔ ያለፈው 48% ነው። አንዳንድ ክልሎች 70-80 በመቶ አሳልፈዋል።
በምንም አይነት የተማሪዎቹ ችሎታና ብቃት አይደለም። ... መሰረቅ መኮረጁን ለማወቅ ዳታውን ከተታትሎ ማግኘት ይቻላል፤ ግልፅ ነው።
ፈተናው እራሱ የተማሪዎች ችሎታና ብቃት መለኪያ አልነበረም። ያንን ነው የቀየርነው። ከምንም በፊት የሰራነው በተማሪዎች ጭንቅላት ውስጥ በስርቆት፣ በማጭበርበር ፣ ሌላ ሰው በማስፈተን ፣ በመኮረጅ የሚገኝ ትምህርት የለም የሚል ነው። ይሄን አውቀው እንደ ችሎታቸው እንዲያጠኑ ነው ያደረግነው።
የዛ ውጤት፣ እንደ ሀገር ያለንበትን ልክ ነው ያሳወቀን። በዚህም ይሄ ነው የትምህርት ስርዓቱ ካልን በኃላ ሪፎርሞችን በተግባር አውለን አንድ ትውልድ ቢበላሽብን ቀጣዩን እንዴት እናድናለን ብለን ነው እየሰራን ያለነው። "
እንደ ትምህርት ሚኒስቴር መረጃ ፤ በ2014 እና በ2015 በድምሩ 1,741,619 ተማሪዎች የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና ውስደዋል። ከነዚህ ውስጥ ያለፉት በድምሩ 57,301 ተፈታኞች ናቸው።
በዚህ ልክ ተፈታኝ ተማሪዎች መውደቃቸው ዜጎችን ያስደነገጠ ቢሆንም ከነዚህ ተማሪዎች በፊትም ፈተናው አሰጣጡ በዚህ መንገድ ቢሆን ውጤቱ ከዚህ እንደማይለይና የትምህርት ስርዓቱ ውድቀት ከታች ጀምሮ የመጣ እንደሆነ የሚገልጹ በርካቶች ናቸው።
ለዚህ ውድቀት ደግሞ ሁሉም ባለድርሻ ኃላፊነት እንዳለበትና ተማሪዎቹን ከሚያስተምሯቸው መምህራን ብቃት አንስቶ ፣ የትምህርት ቤቶች የጥራት ጉዳይ፣ የግብዓት አቅርቦት ሁሉ ሊፈተሽ የሚገባው እንደሆነ የሚያመላክት መሆኑ ይነሳል።
@tikvahethiopia
ባለፉት ሁለት የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተናዎች በሚሊዮን የሚቆጠሩ ተማሪዎች ተፈትነው ያለፉት ግን እጅግ በጣም ጥቂት ናቸው።
ምን የተቀረ ነገር ኖሮ ነው ? የትምህርት ሚኒስትሩ ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ ከሰሞኑን በብሄራዊ ቴሌቪዥን ጣቢያ ቀርበው ማብራሪያ ሰጥታዋል።
ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ ፦
" የፈተናው ክብደ እና ቅለት ከሆነ ምንም የተቀየረ ነገር የለም።
የፈተና አሰጣጥ እና ዝግጅት ሂደት አለ፤ እራሱን የቻለ ሳይንስ አለው በጣም እንዳይከብድም በጣም እንዳይቀልም።
እስከ ዛሬ ሲሰራ ከነበረው ምንም የተለየ ነገር የለም። የተለየው ፈተና አሰጣጡ ነው።
ፈተና አሰጣጡ ያመጣው ለውጥ ምንድነው ከተባለ ፤ ከዚህ በፊት ፈተናዎች በየትምህርት ቤት ነው የሚሰጡት ፈተና መታተም ከጀመረ ጊዜ ጀምሮ ፣ ከወጣ ጊዜ ጀምሮ ፈተናዎቹ ይሰረቃሉ።
ፈተና ሲሰረቅ የነበረው በተደራጀ መልክ ነው በክልሎች ፈታኞች በየክልሉ ሲሄዱ ትልቅ ግብዣ ተደርጎ ጉቦ ተሰጥቷቸው ተማሪዎቹ እንዲኮራረጁ ይደረጋል። ውጤቱ ትርጉም ያለው አልነበረም።
እኔ ትምህርት ሚኒስቴር የመጣሁ ጊዜ በሁለተኛው ሳምንት ፈተና ሰጥተን ነበር በድሮው አሰጣት ፎርማት ያኔ ነው የማለፊያ ውጤት 50 በመቶ ነው ብለን ፖሊሲ ያደረግነው ፣በወቅቱ ፈተና አሰጣጡን አልቀየርንም ነበር ያኔ ያለፈው 48% ነው። አንዳንድ ክልሎች 70-80 በመቶ አሳልፈዋል።
በምንም አይነት የተማሪዎቹ ችሎታና ብቃት አይደለም። ... መሰረቅ መኮረጁን ለማወቅ ዳታውን ከተታትሎ ማግኘት ይቻላል፤ ግልፅ ነው።
ፈተናው እራሱ የተማሪዎች ችሎታና ብቃት መለኪያ አልነበረም። ያንን ነው የቀየርነው። ከምንም በፊት የሰራነው በተማሪዎች ጭንቅላት ውስጥ በስርቆት፣ በማጭበርበር ፣ ሌላ ሰው በማስፈተን ፣ በመኮረጅ የሚገኝ ትምህርት የለም የሚል ነው። ይሄን አውቀው እንደ ችሎታቸው እንዲያጠኑ ነው ያደረግነው።
የዛ ውጤት፣ እንደ ሀገር ያለንበትን ልክ ነው ያሳወቀን። በዚህም ይሄ ነው የትምህርት ስርዓቱ ካልን በኃላ ሪፎርሞችን በተግባር አውለን አንድ ትውልድ ቢበላሽብን ቀጣዩን እንዴት እናድናለን ብለን ነው እየሰራን ያለነው። "
እንደ ትምህርት ሚኒስቴር መረጃ ፤ በ2014 እና በ2015 በድምሩ 1,741,619 ተማሪዎች የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና ውስደዋል። ከነዚህ ውስጥ ያለፉት በድምሩ 57,301 ተፈታኞች ናቸው።
በዚህ ልክ ተፈታኝ ተማሪዎች መውደቃቸው ዜጎችን ያስደነገጠ ቢሆንም ከነዚህ ተማሪዎች በፊትም ፈተናው አሰጣጡ በዚህ መንገድ ቢሆን ውጤቱ ከዚህ እንደማይለይና የትምህርት ስርዓቱ ውድቀት ከታች ጀምሮ የመጣ እንደሆነ የሚገልጹ በርካቶች ናቸው።
ለዚህ ውድቀት ደግሞ ሁሉም ባለድርሻ ኃላፊነት እንዳለበትና ተማሪዎቹን ከሚያስተምሯቸው መምህራን ብቃት አንስቶ ፣ የትምህርት ቤቶች የጥራት ጉዳይ፣ የግብዓት አቅርቦት ሁሉ ሊፈተሽ የሚገባው እንደሆነ የሚያመላክት መሆኑ ይነሳል።
@tikvahethiopia
#SafaricomEthiopia
በሁለት አማራጮች የቀረቡልንን የYoutube ጥቅሎች በመግዛት ማርሻችንን ወደ ላቀ መዝናናት እንቀይር ፤ ፈታ ዘና እያለን እንዋል!
#SafaricomEthiopia
#FurtherAheadTogether
በሁለት አማራጮች የቀረቡልንን የYoutube ጥቅሎች በመግዛት ማርሻችንን ወደ ላቀ መዝናናት እንቀይር ፤ ፈታ ዘና እያለን እንዋል!
#SafaricomEthiopia
#FurtherAheadTogether
#ኤክሶደስ_የፊዝዮቴራፒ_ልዩ_ክሊኒክ
በውቢቷ ባህርዳር አዲስ ቅርንጫፍ ከፍተናል ፤ የምንሰጣቸው የህክምና አገልግሎቶች፦
- ለአንገት፣ ለትክሻ፣ለወገብ ህመም
- ከዲስክ መንሸራተት ጋር በተያያዘ ለሚመጣ ችግር
- ለማዞር ወይንም ሚዛን የመጠበቅ ችግር
- ለፊት መጣመም
- ከስትሮክ በኋላ ለሚመጣ ግማሽ የሰውነት ክፍል መዛል
- ለስፖርታዊ ጉዳቶች
- በአጠቃላይ ከነርቭ፣ ከጡንቻ፣ ከመገጣጠሚያ ጋር በተገናኘ ለሚከሰቱ ችግሮች
አድራሻችን፦ ቁጥር 1_ አዲስ አበባ 22 ከመክሊት ህንፃ ፊት ለፊት ባሮ ህንፃ ላይ እንገኛለን ፤ ቁጥር 2_ ባህርዳር ቀበሌ 14 አልዋቅ ሆቴል አጠገብ ስልክ ቁጥር 0979099909 / 0911039377
በቴሌግራም ቻናላችን ጠቃሚ መረጃ ያግኙ
https://t.iss.one/ExodPhysioClinic
በውቢቷ ባህርዳር አዲስ ቅርንጫፍ ከፍተናል ፤ የምንሰጣቸው የህክምና አገልግሎቶች፦
- ለአንገት፣ ለትክሻ፣ለወገብ ህመም
- ከዲስክ መንሸራተት ጋር በተያያዘ ለሚመጣ ችግር
- ለማዞር ወይንም ሚዛን የመጠበቅ ችግር
- ለፊት መጣመም
- ከስትሮክ በኋላ ለሚመጣ ግማሽ የሰውነት ክፍል መዛል
- ለስፖርታዊ ጉዳቶች
- በአጠቃላይ ከነርቭ፣ ከጡንቻ፣ ከመገጣጠሚያ ጋር በተገናኘ ለሚከሰቱ ችግሮች
አድራሻችን፦ ቁጥር 1_ አዲስ አበባ 22 ከመክሊት ህንፃ ፊት ለፊት ባሮ ህንፃ ላይ እንገኛለን ፤ ቁጥር 2_ ባህርዳር ቀበሌ 14 አልዋቅ ሆቴል አጠገብ ስልክ ቁጥር 0979099909 / 0911039377
በቴሌግራም ቻናላችን ጠቃሚ መረጃ ያግኙ
https://t.iss.one/ExodPhysioClinic
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update
- በእስራኤል - ሃማስ ጦርነት ጋዛ ውስጥ የሞቱ ፍልስጤማውያን ቁጥር 2,670 የደረሰ ሲሆን የቆሰሉ 9,600 ደርሰዋል። እስራኤል ውስጥ የሞቱ ደግሞ 1,400 እንደሆኑና የቆሰሉ 3,418 መሆናቸው ተነግሯል።
- የአሜሪካ ፕሬዜዳንት ጆ ባይደን ሃማስ እስራኤል ላይ የፈፀመውን ጥቃት ለማውገዝ ከፍልስጤሙ ፕሬዜዳንት ሞሃሙድ አባስ ጋር በስልክ መነጋገራቸውን ገልፀዋል። ባይደን ፤ ሃማስ ለፍልስጤም ህዝብ ክብር እና የራስን እድል በራስ የመወሰን መብት ከቆመ እንዳልሆነ በድጋሚ እንደገለፁላቸው አመልክተዋል። ባይደን " በጋዛ ላሉ ሲቪሎች የሰብአዊ አቅርቦቶች እንዲደርሱ እና ግጭቱ እንዳይስፋፋ ለማድረግ በቀጠናው ካሉ አጋሮች ጋር እየሰራን መሆኑን አረጋግጫለሁ " ብለዋል።
- የፍልስጤም ፕሬዝዳንት ማህሙድ አባስ " የሃማስ ተግባራትና እርምጃዎች እንዲሁም ፖሊሲዎች የፍልስጤምን ህዝብ አይወክሉም " ሲሉ ተናግረዋል። አባስ ከቬንዙዌላው ፕሬዝዳንት ኒኮላስ ማዱሮ ጋር ባደረጉት የስልክ ውይይት " የፍልስጤም ነፃ አውጪ ድርጅት ፤ የፍልስጤም ብቸኛ ህጋዊ ተወካይ " ነው ብለዋል።
- የማሌዢያ ጠ/ሚ አንዋር ኢብራሂም የፍልስጤም ታጣቂ ቡድን ሃማስን ለማውገዝ በምዕራባውያን የሚደረገውን ግፊት እንደማይስማሙበት ተናግረዋል። አንዋር ማሌዢያ እንደ ፖሊሲ ከሃማስ ጋር ግንኙነት እንዳላት እና ይህም እንደሚቀጥል ገልጸዋል።
- እስራኤል ወደ ጋዛ እርዳታ እንዲገባ ፈቅዳለች ተብሏል። ከአሜሪካ እና ከግብፅ ጋር የተደረገ ውይይትን ተከትሎ እስራኤል በመጨረሻ የሰብአዊ እርዳታ ውሃ፣ ምግብ፣ መድሃኒት ወደ ጋዛ እንዲገባ ፈቅዳለች ተብሏል። የውጭ ዜጎችም በግብፅ በኩል እንዲወጡ መንገድ ተመቻችቷል። በጋዛ እና በግብፅ መካከል ያለው የራፋህ ድንበር አቋራጭ ዛሬ እንደሚከፈት ተገልጿል። የተወሰነ ሰዓት የሚቆይ ተኩስ አቁም እንደሚኖር ተመላክቷል። ሃማስ ግን ስለ ሁኔታው የሚያውቀው እንደሌለው ገልጿል።
- ኢራን ፤ እስራኤል ጥቅሟንና ዜጎቿን ለማጥቃት እስካልደፈረች ድረስ ሃይሏ ከእስራኤል ጋር ወደ ጦርነት እንደማይገባ በተመድ ልዑኳ በኩል ገልጻለች። ይህ ከማለቷ ሰዓታት በፊት በውጭ ጉዳይ በኩል በሰጠችው ቃል እስራኤል ጥቃቷን ካላቆመች ሁኔታው እንደሚባባስና ሌሎች ወገኖች እርምጃ ለመውሰድ ዝግጁ መሆናቸውን አሳውቃለች።
- የተባበሩት መንግስታት ድርጅት (UN) ዋና ጸሃፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ " ሃማስ " ሁሉንም አግቶ የወሰዳቸውን ሰዎች በአስቸኳይ እንዲፈታ እና እስራኤልም ወደ ጋዛ ሰብአዊ ርዳታ እንዲገባ እንድታደርግ ጠይቀዋል።
- እስራኤል ትላንት ለሊቱን የጋዛ ሰርጥን በቦንብ ስትደበደብ ማደሯ ተነግሯል። ቃላቸውን ለዓለም አቀፍ ሚዲያዎች የሰጡ የጋዛ ነዋሪዎች እስራኤል ሚሊሻና ተዋጊ በሌለባቸው መንደሮች ንፁሃንን ያለየ ጭካኔ የተሞላበት ጥፋት እያደረሰች ነው ሲሉ ከሰዋል። በእስራኤል በኩል ባለፉት ሰዓታት የሮኬት ጥቃት ከሃማስ በኩል ሲሰነዘርባት የነበረ ሲሆን ግጭቱ ከተጀመረ አንስቶ 6000 ሮኬት ተወርውሮባታል።
- የሃማስ ባለስልጣናት እስራኤል " የጦር ወንጀል እየፈፀመች ነው " ሲሉ ከሰዋል። ንፁሃን፣ ህፃናት፣ ሴቶች በምትፈፅመው ጥቃት ሳይለዩ ተገድለዋል ብለዋል።
Via @BirlikEthiopia
የውጭ ጉዳዮችን፦ https://t.iss.one/+LM-bJ8NzZMcxMjA8
- በእስራኤል - ሃማስ ጦርነት ጋዛ ውስጥ የሞቱ ፍልስጤማውያን ቁጥር 2,670 የደረሰ ሲሆን የቆሰሉ 9,600 ደርሰዋል። እስራኤል ውስጥ የሞቱ ደግሞ 1,400 እንደሆኑና የቆሰሉ 3,418 መሆናቸው ተነግሯል።
- የአሜሪካ ፕሬዜዳንት ጆ ባይደን ሃማስ እስራኤል ላይ የፈፀመውን ጥቃት ለማውገዝ ከፍልስጤሙ ፕሬዜዳንት ሞሃሙድ አባስ ጋር በስልክ መነጋገራቸውን ገልፀዋል። ባይደን ፤ ሃማስ ለፍልስጤም ህዝብ ክብር እና የራስን እድል በራስ የመወሰን መብት ከቆመ እንዳልሆነ በድጋሚ እንደገለፁላቸው አመልክተዋል። ባይደን " በጋዛ ላሉ ሲቪሎች የሰብአዊ አቅርቦቶች እንዲደርሱ እና ግጭቱ እንዳይስፋፋ ለማድረግ በቀጠናው ካሉ አጋሮች ጋር እየሰራን መሆኑን አረጋግጫለሁ " ብለዋል።
- የፍልስጤም ፕሬዝዳንት ማህሙድ አባስ " የሃማስ ተግባራትና እርምጃዎች እንዲሁም ፖሊሲዎች የፍልስጤምን ህዝብ አይወክሉም " ሲሉ ተናግረዋል። አባስ ከቬንዙዌላው ፕሬዝዳንት ኒኮላስ ማዱሮ ጋር ባደረጉት የስልክ ውይይት " የፍልስጤም ነፃ አውጪ ድርጅት ፤ የፍልስጤም ብቸኛ ህጋዊ ተወካይ " ነው ብለዋል።
- የማሌዢያ ጠ/ሚ አንዋር ኢብራሂም የፍልስጤም ታጣቂ ቡድን ሃማስን ለማውገዝ በምዕራባውያን የሚደረገውን ግፊት እንደማይስማሙበት ተናግረዋል። አንዋር ማሌዢያ እንደ ፖሊሲ ከሃማስ ጋር ግንኙነት እንዳላት እና ይህም እንደሚቀጥል ገልጸዋል።
- እስራኤል ወደ ጋዛ እርዳታ እንዲገባ ፈቅዳለች ተብሏል። ከአሜሪካ እና ከግብፅ ጋር የተደረገ ውይይትን ተከትሎ እስራኤል በመጨረሻ የሰብአዊ እርዳታ ውሃ፣ ምግብ፣ መድሃኒት ወደ ጋዛ እንዲገባ ፈቅዳለች ተብሏል። የውጭ ዜጎችም በግብፅ በኩል እንዲወጡ መንገድ ተመቻችቷል። በጋዛ እና በግብፅ መካከል ያለው የራፋህ ድንበር አቋራጭ ዛሬ እንደሚከፈት ተገልጿል። የተወሰነ ሰዓት የሚቆይ ተኩስ አቁም እንደሚኖር ተመላክቷል። ሃማስ ግን ስለ ሁኔታው የሚያውቀው እንደሌለው ገልጿል።
- ኢራን ፤ እስራኤል ጥቅሟንና ዜጎቿን ለማጥቃት እስካልደፈረች ድረስ ሃይሏ ከእስራኤል ጋር ወደ ጦርነት እንደማይገባ በተመድ ልዑኳ በኩል ገልጻለች። ይህ ከማለቷ ሰዓታት በፊት በውጭ ጉዳይ በኩል በሰጠችው ቃል እስራኤል ጥቃቷን ካላቆመች ሁኔታው እንደሚባባስና ሌሎች ወገኖች እርምጃ ለመውሰድ ዝግጁ መሆናቸውን አሳውቃለች።
- የተባበሩት መንግስታት ድርጅት (UN) ዋና ጸሃፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ " ሃማስ " ሁሉንም አግቶ የወሰዳቸውን ሰዎች በአስቸኳይ እንዲፈታ እና እስራኤልም ወደ ጋዛ ሰብአዊ ርዳታ እንዲገባ እንድታደርግ ጠይቀዋል።
- እስራኤል ትላንት ለሊቱን የጋዛ ሰርጥን በቦንብ ስትደበደብ ማደሯ ተነግሯል። ቃላቸውን ለዓለም አቀፍ ሚዲያዎች የሰጡ የጋዛ ነዋሪዎች እስራኤል ሚሊሻና ተዋጊ በሌለባቸው መንደሮች ንፁሃንን ያለየ ጭካኔ የተሞላበት ጥፋት እያደረሰች ነው ሲሉ ከሰዋል። በእስራኤል በኩል ባለፉት ሰዓታት የሮኬት ጥቃት ከሃማስ በኩል ሲሰነዘርባት የነበረ ሲሆን ግጭቱ ከተጀመረ አንስቶ 6000 ሮኬት ተወርውሮባታል።
- የሃማስ ባለስልጣናት እስራኤል " የጦር ወንጀል እየፈፀመች ነው " ሲሉ ከሰዋል። ንፁሃን፣ ህፃናት፣ ሴቶች በምትፈፅመው ጥቃት ሳይለዩ ተገድለዋል ብለዋል።
Via @BirlikEthiopia
የውጭ ጉዳዮችን፦ https://t.iss.one/+LM-bJ8NzZMcxMjA8
TIKVAH-ETHIOPIA
#ወልቂጤ - " በሰዎች ላይ ቀላልና ከባድ የአካል ጉዳት ደርሷል። ቤቶች ተቃጥለዋል " - የወልቂጤ ከተማ አስተዳደር - " በቦታው አድማ የመበተን ሥራ እየተሰራ ነው " - የጉራጌ ዞን ፓሊስ ኮሚሽን - " ግጭቱ እንዲባባስ በሚፈልጉ አካላት ንብረት ወድሟል፣ በሰዎች ላይ ቀላልና ከባድ ጉዳት ደርሶባቸዋል " - የጉራጌ ዞን ኮማንድ ፓስት አዲስ በተዋቀረው በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ወልቂጤ ከተማና ቀቤና…
#Update
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ወልቂጤ ከተማና በቀቤና ልዩ ወረዳ በተቀሰቀሰው ግጭት ንጹሐን መገደላቸውንና ነዋሪዎችና ባለስልጣናት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አረጋግጠዋል።
ሥሜ ባይጠቀስ ያሉ አንድ የቀቤና ልዩ ወረዳ ነዋሪ " ሰሞኑን ሁለት የቀቤና ወጣቶች ተገድለዋል " ብለዋል።
ሌላኛው የወልቂጤ ከተማ ነዋሪ ደግሞ " አንድ የወልቂጤ ሰው በወጣቶች ተገድሏል " ሲሉ ገልጸዋል።
ስማቸው እንዲጠቀስ ያልፈቀዱ የቀቤና ልዩ ወረዳ ባለስልጣን በሰጡት አጭር ቃል፣ " ሰዎች እየተገደሉ ነው። መንግሥት አስቸኳይ መፍትሄ ይስጥ " ብለዋል።
አንድ ስማቸው እንዲጠቀስ ያልፈለጉ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የወልቂጤ ከተማ አስተዳደር ባለሥልጣን በግጭቱ የንጹሐን ሕይወት ማለፉን አረጋግጠዋል።
ባለሥልጣኑ በሰጡት ቃል፣ " ሁለት ወጣቶች ከጸጥታ ኃይል በተተኮሰ ጥይት ሞተዋል። አንድ ሰው በወጣቶች ተገድሏል " ነው ያሉት።
አክለውም፣ " ቅዳሜ ጥቅምት 3 ቀን 2016 ዓ.ም ሁለት የቀቤና ወጣቶች ከጸጥታ ኃይል በተተኮሰ ጥይት ሞተዋል። እሁድ ጥቅምት 4 ቀን 2016 ዓ.ም በአመጹ ከጉራጌ አንድ ሰው በወጣቶች ተግድሏል። ዘረፋ ቤት ማፍረስ ቤት ቃጠሎ በከፍተኛ ደረጃ ቀጥሏል " ብለዋል።
በቁጥር ባይታወቅም የቆሰሉ ሰዎች እንዳሉ፣ የትራንስፖርት አገልግሎት እንደተቋረጠ፣ የጸጥታ ኃይሉ ግን ከፍተኛ ርብርብ እያደረገ እንደሚገኝ አስረድተዋል።
ሌሎች የመረጃ ምንጮች ነዋሪዎች በበኩላቸው፣ " ከቀቤና ልዩ ወረዳ መጥተው ቤት አቃጥለዋል፣ ንብረት ዘርፈዋል፣ ፌደራል ፓሊስ በመሳሪያ መትተው ገድለዋል። ከተማውና የዞኑ ፓሊስ አቅሙን እንዳይጠቀም ተደርጓል። ልዩ ኃይል እረብሻ ያለበትን ሥፍራ ትቶ መሀል ከተማ ላይ አስለቃሽ ጭስ ማኅበረሰስቡ ላይ ወርውሯል። በተጨማሪም የዞኑን ፓሊስ ኮማንደር ጠጄን አግተውታል፣ ብዙ ወጣቶች ተደብድበዋል" ብለዋል።
የወልቂጤ ከተማ አስተዳደር ባለስልጣን የኮማንደር ጠጄን እገታ በተመለከተ በሰጡት ምላሽ ፣ " ጉዳት ደርሶበታል መሬት ለመሬት ተጎትቶ በወጣቶቹ ሲደበደብ ነበር። እገታው የሚለው መረጃ እኔ ባለኝ መረጃ ልክ አይደለም " ነው ያሉት።
ለሰው ሕልፈተ ሕይወት ምክንያት የሆነው ግጭት ከምን ጥያቄ የተነሳ እንደሆነ ማብራሪያ እንዲሰጡ ሲጠየቁም፣ የሚከተሉትን ሦስት ጭብጦቹ ዘርዝረዋል።
- የቀቤና ልዩ ወረዳ ውስጥ በ24 ቀበሌ የሚኖሩ ብሄራቸው ጉራጌ የሆኑ የሕዝብ ክፍሎች በዚህ አንካለልም ማለታቸው ተከትሎ አለመግባባት አለ።
- የቀቤና ልዩ ወረዳ መቀመጫ ወልቂጤ መሆን የለበትም የሚሉ የጉራጌ ተወላጆች ወልቂጤ ከተማ መስተዳድር በጉራጌ የሚተዳደር አንድ መዋቅር የዞኑ መቀመጫ ጭምር ነው በማለት ያነሳሉ።
- ቀቤና ልዩ ወረዳ ደሞ የወልቂጤ ከተማ መስተዳድር በዙሪያው ባለው ቀበሌ ላይ የተሠመሰረተ በመሆኑ ከዚህ የትም ወጥቼ የልዩ ወረዳ መቀመጫ አልመሰርትም ብሎ ያምናል።
ከእነዚህ መሠረታዊ ኮዝ በመነሳት በወጣቶች መካከል ግጭት ተነስቶ ነው ለአጠቃላይ ሞት፣መንገድ መዘጋት፣ ንብረት መውደም ዘረፋ እንዲፈፀም ምክንያት የሆነው " ብለዋል።
የጉራጌ ዞን ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ የተፈጠረውን አለመግባባት ለመፍታት የሚመለከታቸው አካላት ሁሉ አደረጉት በተባለ ውይይት፣ አራቱ መዋቅሮች የአካባቢያቸውን ሰላምና የሕዝቦችን ደኅንነት ተቀናጅተው በጋራ ማስጠበቅ ሲገባቸው ወደ ሁከትና ብጥብጥ በመግባታቸው ከተጠያቂነት የማያድን በመሆኑ ከድርጊቱ ወጥትው በአስቸኳይ ማስቆም እንዳለባቸው ማስጠንቀቂያ መሰጠቱን ጥቅምት 4 ቀን 2016 ዓ.ም በማኅበራዊ ትስስር ገጹ አስፍሯል።
https://telegra.ph/Tikvah-10-16
መረጃው በአ/አ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ ተዘጋጅቶ የቀረበ ነው።
@tikvahethiopia
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ወልቂጤ ከተማና በቀቤና ልዩ ወረዳ በተቀሰቀሰው ግጭት ንጹሐን መገደላቸውንና ነዋሪዎችና ባለስልጣናት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አረጋግጠዋል።
ሥሜ ባይጠቀስ ያሉ አንድ የቀቤና ልዩ ወረዳ ነዋሪ " ሰሞኑን ሁለት የቀቤና ወጣቶች ተገድለዋል " ብለዋል።
ሌላኛው የወልቂጤ ከተማ ነዋሪ ደግሞ " አንድ የወልቂጤ ሰው በወጣቶች ተገድሏል " ሲሉ ገልጸዋል።
ስማቸው እንዲጠቀስ ያልፈቀዱ የቀቤና ልዩ ወረዳ ባለስልጣን በሰጡት አጭር ቃል፣ " ሰዎች እየተገደሉ ነው። መንግሥት አስቸኳይ መፍትሄ ይስጥ " ብለዋል።
አንድ ስማቸው እንዲጠቀስ ያልፈለጉ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የወልቂጤ ከተማ አስተዳደር ባለሥልጣን በግጭቱ የንጹሐን ሕይወት ማለፉን አረጋግጠዋል።
ባለሥልጣኑ በሰጡት ቃል፣ " ሁለት ወጣቶች ከጸጥታ ኃይል በተተኮሰ ጥይት ሞተዋል። አንድ ሰው በወጣቶች ተገድሏል " ነው ያሉት።
አክለውም፣ " ቅዳሜ ጥቅምት 3 ቀን 2016 ዓ.ም ሁለት የቀቤና ወጣቶች ከጸጥታ ኃይል በተተኮሰ ጥይት ሞተዋል። እሁድ ጥቅምት 4 ቀን 2016 ዓ.ም በአመጹ ከጉራጌ አንድ ሰው በወጣቶች ተግድሏል። ዘረፋ ቤት ማፍረስ ቤት ቃጠሎ በከፍተኛ ደረጃ ቀጥሏል " ብለዋል።
በቁጥር ባይታወቅም የቆሰሉ ሰዎች እንዳሉ፣ የትራንስፖርት አገልግሎት እንደተቋረጠ፣ የጸጥታ ኃይሉ ግን ከፍተኛ ርብርብ እያደረገ እንደሚገኝ አስረድተዋል።
ሌሎች የመረጃ ምንጮች ነዋሪዎች በበኩላቸው፣ " ከቀቤና ልዩ ወረዳ መጥተው ቤት አቃጥለዋል፣ ንብረት ዘርፈዋል፣ ፌደራል ፓሊስ በመሳሪያ መትተው ገድለዋል። ከተማውና የዞኑ ፓሊስ አቅሙን እንዳይጠቀም ተደርጓል። ልዩ ኃይል እረብሻ ያለበትን ሥፍራ ትቶ መሀል ከተማ ላይ አስለቃሽ ጭስ ማኅበረሰስቡ ላይ ወርውሯል። በተጨማሪም የዞኑን ፓሊስ ኮማንደር ጠጄን አግተውታል፣ ብዙ ወጣቶች ተደብድበዋል" ብለዋል።
የወልቂጤ ከተማ አስተዳደር ባለስልጣን የኮማንደር ጠጄን እገታ በተመለከተ በሰጡት ምላሽ ፣ " ጉዳት ደርሶበታል መሬት ለመሬት ተጎትቶ በወጣቶቹ ሲደበደብ ነበር። እገታው የሚለው መረጃ እኔ ባለኝ መረጃ ልክ አይደለም " ነው ያሉት።
ለሰው ሕልፈተ ሕይወት ምክንያት የሆነው ግጭት ከምን ጥያቄ የተነሳ እንደሆነ ማብራሪያ እንዲሰጡ ሲጠየቁም፣ የሚከተሉትን ሦስት ጭብጦቹ ዘርዝረዋል።
- የቀቤና ልዩ ወረዳ ውስጥ በ24 ቀበሌ የሚኖሩ ብሄራቸው ጉራጌ የሆኑ የሕዝብ ክፍሎች በዚህ አንካለልም ማለታቸው ተከትሎ አለመግባባት አለ።
- የቀቤና ልዩ ወረዳ መቀመጫ ወልቂጤ መሆን የለበትም የሚሉ የጉራጌ ተወላጆች ወልቂጤ ከተማ መስተዳድር በጉራጌ የሚተዳደር አንድ መዋቅር የዞኑ መቀመጫ ጭምር ነው በማለት ያነሳሉ።
- ቀቤና ልዩ ወረዳ ደሞ የወልቂጤ ከተማ መስተዳድር በዙሪያው ባለው ቀበሌ ላይ የተሠመሰረተ በመሆኑ ከዚህ የትም ወጥቼ የልዩ ወረዳ መቀመጫ አልመሰርትም ብሎ ያምናል።
ከእነዚህ መሠረታዊ ኮዝ በመነሳት በወጣቶች መካከል ግጭት ተነስቶ ነው ለአጠቃላይ ሞት፣መንገድ መዘጋት፣ ንብረት መውደም ዘረፋ እንዲፈፀም ምክንያት የሆነው " ብለዋል።
የጉራጌ ዞን ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ የተፈጠረውን አለመግባባት ለመፍታት የሚመለከታቸው አካላት ሁሉ አደረጉት በተባለ ውይይት፣ አራቱ መዋቅሮች የአካባቢያቸውን ሰላምና የሕዝቦችን ደኅንነት ተቀናጅተው በጋራ ማስጠበቅ ሲገባቸው ወደ ሁከትና ብጥብጥ በመግባታቸው ከተጠያቂነት የማያድን በመሆኑ ከድርጊቱ ወጥትው በአስቸኳይ ማስቆም እንዳለባቸው ማስጠንቀቂያ መሰጠቱን ጥቅምት 4 ቀን 2016 ዓ.ም በማኅበራዊ ትስስር ገጹ አስፍሯል።
https://telegra.ph/Tikvah-10-16
መረጃው በአ/አ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ ተዘጋጅቶ የቀረበ ነው።
@tikvahethiopia
#ኢትዮጵያ #ቻይና
የኢትዮጵያ ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ወደ ቻይና አቅንተው በቻይና ይፋዊ ጉብኝት እያደረጉ ናቸው።
ከጠ/ሚ ፅ/ቤት በወጣ መረጃ የቻይናው ጠ/ሚኒስትር ሊ ኪያንግ ለዶ/ር ዐቢይ አሕመድ ይፋዊ አቀባበል አድርገውላቸዋል።
በኃላም የሁለትዮሽ ውይይት አካሂደዋል። በዚህም በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን የምጣኔ ኃብት ትብብር ግንኙነት ማጠናከሪያ መንገዶች ላይ መክረዋል ተብሏል።
ከሁለትዮሽ ውይይቱ በመቀጠል ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ እና ጠ/ሚ ሊ ኪያንግ በተገኙበት በሁለቱ ሀገራት መካከል በተለያዩ መስኮች 12 ያህል የትብብር ስምምነቶች እና ሁለት የፍላጎት ሰነዶች ተፈርመዋል።
ዶ/ር ዐቢይ በቻይና ይፋዊ ጉብኝት ሲያደርጉ ይህ ከአራት ዓመት በኃላ ሲሆን በቀጣይ በሚካሄደው 3ኛው የቤልት ኤንድ ሮድ አለም አቀፍ ትብብር መድረክ ላይም ይሳተፋሉ ተብሎ ይጠበቃል።
ፎቶ፦ #PMOffice
@tikvahethiopia
የኢትዮጵያ ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ወደ ቻይና አቅንተው በቻይና ይፋዊ ጉብኝት እያደረጉ ናቸው።
ከጠ/ሚ ፅ/ቤት በወጣ መረጃ የቻይናው ጠ/ሚኒስትር ሊ ኪያንግ ለዶ/ር ዐቢይ አሕመድ ይፋዊ አቀባበል አድርገውላቸዋል።
በኃላም የሁለትዮሽ ውይይት አካሂደዋል። በዚህም በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን የምጣኔ ኃብት ትብብር ግንኙነት ማጠናከሪያ መንገዶች ላይ መክረዋል ተብሏል።
ከሁለትዮሽ ውይይቱ በመቀጠል ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ እና ጠ/ሚ ሊ ኪያንግ በተገኙበት በሁለቱ ሀገራት መካከል በተለያዩ መስኮች 12 ያህል የትብብር ስምምነቶች እና ሁለት የፍላጎት ሰነዶች ተፈርመዋል።
ዶ/ር ዐቢይ በቻይና ይፋዊ ጉብኝት ሲያደርጉ ይህ ከአራት ዓመት በኃላ ሲሆን በቀጣይ በሚካሄደው 3ኛው የቤልት ኤንድ ሮድ አለም አቀፍ ትብብር መድረክ ላይም ይሳተፋሉ ተብሎ ይጠበቃል።
ፎቶ፦ #PMOffice
@tikvahethiopia
የእህቱ ልጅ በሆነ የሰባት አመት ህፃን ላይ የግብረሰዶም ወንጀል የፈፀመ ተከሳሽ በፅኑ እስራት መቀጣቱ ተገለጸ።
ተከሳሹ የወንጀል ድርጊቱን የፈጸመው በሰኔ ወር 2014 ዓ/ም በጉለሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 4 በተለምዶ ማሪያም ወንዝ እየተባለ በሚጠራው አካባቢ በሚኖርበት ቤት ውስጥ ነው።
የ37 ዓመት ዕድሜ ያለው ተከሳሹ እና የተከሳሹ እህት በአንድ ቤት ውስጥ የሚኖሩ ሲሆን ተከሳሹ ሰው የሌለበትን አጋጣሚ ጠብቆ የሰባት ዓመት ዕድሜ ያለው የእህቱን ልጅ በስለት በማስፈራራት የግብረ ሰዶም ወንጀል ፈፅሞበታል።
ፖሊስ በቀረበለት ጥቆማ መነሻነት ተከሳሹን ተከታትሎ በቁጥጥር ስር ካዋለ በኋላ አስፈላጊ ማስረጃዎችን በማሰባሰብ በአቃቤ ህግ ክስ እንዲመሰረትበት አድርጓል፡፡
የተከሳሹን ጉዳይ ሲመለከት የቆየው የፌደራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ችሎት ጥፋተኝነቱን በማረጋገጥ ሰሞኑን በዋለው ችሎት በ13 ዓመት ጽኑ እስራት እንዲቀጣ ወስኖበታል።
ወላጆች ልጆቻቸው ለእንደዚህ አይነት ወንጀል ሰለባ እንዳይሆኑ ዕድሜያቸውን መሰረት በማድረግ አስቀድመው በግልፅ መወያየት እና ተገቢውን ክትትልና ጥበቃ ማድረግ እንደሚኖርባቸው የአዲስ አበባ ፖሊስ መልዕክቱን ያስተላልፏል።
#AddisAbabaPolice
@tikvahethiopia
ተከሳሹ የወንጀል ድርጊቱን የፈጸመው በሰኔ ወር 2014 ዓ/ም በጉለሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 4 በተለምዶ ማሪያም ወንዝ እየተባለ በሚጠራው አካባቢ በሚኖርበት ቤት ውስጥ ነው።
የ37 ዓመት ዕድሜ ያለው ተከሳሹ እና የተከሳሹ እህት በአንድ ቤት ውስጥ የሚኖሩ ሲሆን ተከሳሹ ሰው የሌለበትን አጋጣሚ ጠብቆ የሰባት ዓመት ዕድሜ ያለው የእህቱን ልጅ በስለት በማስፈራራት የግብረ ሰዶም ወንጀል ፈፅሞበታል።
ፖሊስ በቀረበለት ጥቆማ መነሻነት ተከሳሹን ተከታትሎ በቁጥጥር ስር ካዋለ በኋላ አስፈላጊ ማስረጃዎችን በማሰባሰብ በአቃቤ ህግ ክስ እንዲመሰረትበት አድርጓል፡፡
የተከሳሹን ጉዳይ ሲመለከት የቆየው የፌደራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ችሎት ጥፋተኝነቱን በማረጋገጥ ሰሞኑን በዋለው ችሎት በ13 ዓመት ጽኑ እስራት እንዲቀጣ ወስኖበታል።
ወላጆች ልጆቻቸው ለእንደዚህ አይነት ወንጀል ሰለባ እንዳይሆኑ ዕድሜያቸውን መሰረት በማድረግ አስቀድመው በግልፅ መወያየት እና ተገቢውን ክትትልና ጥበቃ ማድረግ እንደሚኖርባቸው የአዲስ አበባ ፖሊስ መልዕክቱን ያስተላልፏል።
#AddisAbabaPolice
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
የትግራይ አካባቢዎች ከፍተኛ የሃዘን ድባብ ውስጥ ናቸው። ጥቅምት 2 በይፋ የታወጀው የትግራይ ሰማእታት የሃዘንና የክብር ቀን ስነ-ሰርአት ተከትሎ የክልሉ ከተሞችና ገጠሮች በከፍተኛ የሃዘን ድባብ ውስጥ ይገኛሉ። ቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ በትግራይ ያለው የሃዘንና የመርዶ ስነ-ሰርአትና ተዛማጅ ጉዳዮች አፈፃፀም በሚከተለው ሪፓርታዥ አጋርቶናል። ዓርብ ጥቅምት 2/2016 ዓ.ም ከሰዓት በኃላ በክልሉ…
#ትግራይ
የትግራይ ሰማእታት የሃዘንና የክብር ስነ-ሰርዓት ከታወጀ ዛሬ 3ኛ ቀኑ ሲሆን ፤ ሌላ ጊዜ በሳምንታዊ የሰኞ ገበያዋ ከመላ ክልሉ ፣ ከዓፋርና የአማራ ክልል አዋሳኝ አከባቢዎች በመጡ ገበያተኞች ትድምቅ የነበረች መቐለ የንግድ ተቋማትዋ ተዘግተው ፣ መኪኖች መንቀሳቀስ አቁመው ጭር ማለትዋ ቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ ዘግቧል።
በሌላ በኩል ፤ በውጭ አገራት የሚኖሩ የትግራይ ዳያስፓራ ማህበረሰብ የክልሉ የሰማእታት የሃዘንና የክብር ስነ-ሰርአት በማስመልከት ሃይማኖታዊ ፀሎትና ሌሎች ዝግጅቶች ማከናወናቸውን ያገኘናቸው መረጃዎች ያሳያሉ።
በውጭ የሚኖሩ የትግራይ ተወላጆች ፦
- በኬንያ ዋና ከተማ ናይሮቢ ፣
- በኔዘርላንድ ፣
- በጀርመን ሙኒክና ፍራንክፈርት ከተሞች ፣
- በእንግሊዝ ለንደን፣
- በስዊድን ስቶክሆልም ከተማ ፣
- በአሜሪካ ዋሽንግተን ደሲና አከባቢዋ ፣
- በአረብ አገራትና በሌሎች የሚኖሩ የትግራይ ዳያስፓራ አባላት ሰማእታት የሚዘክር የፀሎት ፣ የሻማ ማብራትና የተለያዩ ስነ-ሰርአቶች አከናውነዋል።
በተያያዘ ዓለም አቀፍ የትግራይ ማሕበረሰብ ሙሁራንና ባለሞያዎች ማህበር (GSTS) የሰማእታት የሃዝንና የክብር ቀን ስነ-ሰርዓት አስመልክቶ ባወጣው የፅሁፍ መግለጫ የተሰማው ጥልቅ ሃዘን በመገለፅ ሰማእታቱ የተሰውለት የትግራይ ድህንነትና ግዛታዊ አንድነት እንዲከበር ከመታገል ጎን ለጎን የሰማእታቱ ቤተሰቦች ለማቋቋምና ትግራይ መልሶ ለመገንባት በሚደረገው ጥረት የበኩሌ እወጣለሁኝ ብሏል።
@tikvahethiopia
የትግራይ ሰማእታት የሃዘንና የክብር ስነ-ሰርዓት ከታወጀ ዛሬ 3ኛ ቀኑ ሲሆን ፤ ሌላ ጊዜ በሳምንታዊ የሰኞ ገበያዋ ከመላ ክልሉ ፣ ከዓፋርና የአማራ ክልል አዋሳኝ አከባቢዎች በመጡ ገበያተኞች ትድምቅ የነበረች መቐለ የንግድ ተቋማትዋ ተዘግተው ፣ መኪኖች መንቀሳቀስ አቁመው ጭር ማለትዋ ቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ ዘግቧል።
በሌላ በኩል ፤ በውጭ አገራት የሚኖሩ የትግራይ ዳያስፓራ ማህበረሰብ የክልሉ የሰማእታት የሃዘንና የክብር ስነ-ሰርአት በማስመልከት ሃይማኖታዊ ፀሎትና ሌሎች ዝግጅቶች ማከናወናቸውን ያገኘናቸው መረጃዎች ያሳያሉ።
በውጭ የሚኖሩ የትግራይ ተወላጆች ፦
- በኬንያ ዋና ከተማ ናይሮቢ ፣
- በኔዘርላንድ ፣
- በጀርመን ሙኒክና ፍራንክፈርት ከተሞች ፣
- በእንግሊዝ ለንደን፣
- በስዊድን ስቶክሆልም ከተማ ፣
- በአሜሪካ ዋሽንግተን ደሲና አከባቢዋ ፣
- በአረብ አገራትና በሌሎች የሚኖሩ የትግራይ ዳያስፓራ አባላት ሰማእታት የሚዘክር የፀሎት ፣ የሻማ ማብራትና የተለያዩ ስነ-ሰርአቶች አከናውነዋል።
በተያያዘ ዓለም አቀፍ የትግራይ ማሕበረሰብ ሙሁራንና ባለሞያዎች ማህበር (GSTS) የሰማእታት የሃዝንና የክብር ቀን ስነ-ሰርዓት አስመልክቶ ባወጣው የፅሁፍ መግለጫ የተሰማው ጥልቅ ሃዘን በመገለፅ ሰማእታቱ የተሰውለት የትግራይ ድህንነትና ግዛታዊ አንድነት እንዲከበር ከመታገል ጎን ለጎን የሰማእታቱ ቤተሰቦች ለማቋቋምና ትግራይ መልሶ ለመገንባት በሚደረገው ጥረት የበኩሌ እወጣለሁኝ ብሏል።
@tikvahethiopia