TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.3K photos
1.51K videos
212 files
4.11K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
#ማስታወሻ ብሔራዊ የድህረ ምረቃ የመግቢያ ፈተና / Graduate Admission Test ከመስከረም 28 እስከ 30/2016 ዓ.ም በበይነ-መረብ ይሰጣል። ትምህርት ሚኒስቴር ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የትምህርት ምርምር ኢንስቲትዩት- የፈተና ማዕከል ጋር በመተባበር የሚሰጠው ፈተና በተጠቀሱት ቀናት በተለያዩ የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች ይከናወናል። ለፈተናው የተመረጡ ተፈታኞች ከመስከረም 21 እስከ 25/2016…
#MoE

ትምህርት ሚኒስቴር ከነገ መስከረም 23 ጀምሮ የብሔራዊ የድህረ ምረቃ ትምህርት መግቢያ የልምምድ ፈተና (Mock Exam) መሰጠት እንደሚጀመር አሳውቋል።

በሀገር አቀፍ ደረጃ ለመጀመሪያ ጊዜ የሚሠጠው ብሔራዊ የድህረ-ምረቃ ትምህርት መግቢያ ፈተና ከመስከረም 28 እስከ 30 ቀን 2016 ዓ.ም በመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ ይሰጣል።

ሚኒስቴሩ ፤ በሁሉም የመንግስትና የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ውስጥ የሚሰጡ የድህረ ምረቃ ትምህርት ፕሮግራሞችን ለመማር የብሄራዊ ድህረ ምረቃ ትምህርት መግቢያ ፈተና መውሠድ ቅድመ ሁኔታ መሆኑን ዛሬ በሰጠው መግለጫ አስገንዝቧል።

በሁሉም የሀገሪቱ ክፍሎች ለሚሠጠው ብሔራዊ የድህረ ምረቃ ትምህርት መግቢያ ፈተና ከመስከረም 21 ጀምሮ እስከ 25 ቀን 2016 ዓ.ም የሚቆይ ምዝገባ እየተካሄደ ነው ያለው ትምህርት ሚኒስቴር ፤ ከነገ መስከረም 23 እስከ 25 ቀን 2016 ዓ.ም የልምምድ ፈተና ይሰጣል ብሏል።

ተፈታኞች በተመዘገቡበት ዩኒቨርሲቲ በመገኘት User name እና Password በመጠቀም የልምምድ ፈተና መውሰድ ይችላሉ ሲል ገልጿል።

(የፈተና አሰጣጡን ዝርዝር መረጃ ከላይ ተያይዟል)

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#DigitalLottery አድማስ ዲጂታል ሎተሪ ዛሬ ወጥቷል። 4 ሚሊዮን ብር ባለዕድለኛ የሚያደርገው የዕጣ ቁጥር 0140621904 ሆኖ ወጥቷል። 👉 4 ,000,000 ብር - 0140621904 👉 2,000,000 ብር - 0140163695 👉 1,000,000 ብር - 0140946766 👉 700,000 ብር - 0141151136 👉 350,000 ብር - 0140607557 👉 250,000 ብር - 0140928442…
#DigitalLottery

አድማስ ዲጂታል ሎተሪ ዛሬ ወጥቷል።

4 ሚሊዮን ብር ባለዕድለኛ የሚያደርገው የዕጣ ቁጥር 0150143960 ሆኖ ወጥቷል።

👉 4 ,000,000 ብር - 0150143960
👉 2,000,000 ብር - 0151052252
👉 1,000,000 ብር - 0150894268
👉 700,000 ብር - 0150596781
👉 350,000 ብር - 0150608082
👉 250,000 ብር - 0150715350
👉 175,000 ብር - 0150997042
👉 100,000 ብር - 0150896057

(ተጨማሪ የዕጣ ቁጥሮች ከላይ ተያይዘዋል)

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#MoE ትምህርት ሚኒስቴር ከነገ መስከረም 23 ጀምሮ የብሔራዊ የድህረ ምረቃ ትምህርት መግቢያ የልምምድ ፈተና (Mock Exam) መሰጠት እንደሚጀመር አሳውቋል። በሀገር አቀፍ ደረጃ ለመጀመሪያ ጊዜ የሚሠጠው ብሔራዊ የድህረ-ምረቃ ትምህርት መግቢያ ፈተና ከመስከረም 28 እስከ 30 ቀን 2016 ዓ.ም በመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ ይሰጣል። ሚኒስቴሩ ፤ በሁሉም የመንግስትና የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት…
" ፈተናው የምርጫ ጥያቄዎችን የያዘ ነው " - ትምህርት ሚኒስቴር

ትምህርት ሚኒስቴር ከመስከረም 28 እስከ 30 /2016 ዓ/ም በሀገር ደረጃ የሚሰጠው የድህረ ምረቃ ትምህርት የመግቢያ ፈተና ወጥ በሆነ መንገድ በአንድ የፈተና መተግበሪያ የሚከወን መሆኑን ገልጿል።

ፈተናው #ምርጫ_ጥያቄዎችን የያዘ ነው ብሏል።

ለፈተናው 53 የፈተና ማእከላት እና 84 የፈተና ጣቢዎች የተዘጋጁ ሲሆን በግማሽ ቀን ውስጥ የሚጠናቀቅ ይሆናል ተብሎ ታቅዷል።

አይነስውራን ተፈታኞች የቃል እና ምክንያታዊ አስተሣሠብ ክህሎቶቻቸው ላይ ያተኮሩ ፈተናዎችን ይወስዳሉ ያለው ሚኒስቴሩ በወሠዱትም ፈተና ከ100% ይመዘናሉ ብሏል።

ብሄራዊ የድህረ ምረቃ ትምህርት መግቢያ ፈተና ጥያቄዎች አመልካቾች መርጠው በሚያመለክቱበት የትምህርት መስክ ላይ ትኩረት ያደረገ እንዳልሆነ ትምህርት ሚኒስቴትር ገልጿል።

ትምህርት ሚኒስቴር የድህረ ምረቃ ትምህርት መግቢያ ፈተና ዓላማ ፦

- በግል እና በመንግስት የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ገብተው የድህረ ምረቃ ትምህርት በ2ኛ እና 3ኛ ዲግሪ የትምህርት ፕሮግራሞች ገብቶ ትምህርት ለመከታተል ፍላጎት ያላቸውን አመልካቾች ብቃት ለመመዘን፤

- ድህረ ምረቃ ትምህርት ፕሮግራሞች የሚገቡ ተማሪዎች ሂሣባዊ ትንተና (Quantitative reasoning) ፣ ምክናያታዊ አስተሳሠብ (Analytical reasoning) ፣ የቃልና የጹህፍ ከህሎት ለመመዘን ነው ሲል አስታውሷል።

@tikvahethiopia
በአዲስ ዓመት አዲስ ገፅታ!!

በአዲስ ዓመት አዲስ አስተሳሰብ ፤ አዲስ ስያሜና የንግድ ምልክት!!
ግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ !!

በከፍተኛ የዕድገትና የለውጥ ጉዞ  ላይ ከሚገኘው ባንካችን ጋር አብረው በመስራት ማሳካት ወደሚፈልጉት ራዕይ ይድረሱ ፡፡

ባንካችን የሚሰጣቸውን ዘርፈ ብዙ የባንክ አገልግሎቶች ፤ የተለያዩ ጨረታዎችና የስራ ማስታወቂያዎች  እንዲሁም ፈጣንና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኘት የባንካችንን የቴሌግራምና የፌስቡክ ቻናሎቻችን አሁኑኑ ይቀላቀሉ ፡፡

https://t.iss.one/Globalbankethiopia123  

ግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ
ለጋራ ስኬታችን!!
#ኦሮሚያ

" በቤጊ ሁለት ቀበሌዎች ረሃብ ተከስቷል "

በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ወለጋ ዞን ቤጊ ወረዳ በሁለት ቀበሌዎች ረሃብ መከሰቱ ተነገረ።

በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በሽብርተኝነት የተፈረጀውና ራሱን " የኦሮሞ ሕዝብ ነጻ አውጪ " ብሎ የሚጠራው ታጣቂ ቡድን ከ2011 ዓ.ም ጀምሮ ሲንቀሳቀስባቸው ከነበሩ አካባቢዎች መካከል በቤጊ ወረዳ በሁለት ቀበሌዎች ረሃብ መከሰቱን የምዕራብ ወለጋ ዞን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገለጸ።

የምዕራብ ወለጋ ዞን አስተዳዳሪ አቶ ሰለሞን ታምሩ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል፣ " ሸኔ የያዛቸውና ለጥቂት ጊዜያት ያስተዳደራቸው ወረዳዎች ነበሩ።  እነዛ ወረዳዎች ብዙ ችግሮች ገጥሟዋቸዋል " ብለዋል።

ለአብነት ታጣቂ ቡድኑ ሲንቀሳቀስባቸው በነበሩ አንዳንድ አካባቢዎች #ረሃብ መከሰቱን ገልጸዋል።

አቶ ሰለሞን ፣ " እስፔሻሊ ጠረፍ ላይ የሚገኙ ቀበሌዎች ተጎድተዋል። በምዕራብ ወለጋ ዞን ቤጊ ወረዳ ተጋባና ሻንታ ቀበሌዎች ረሃብ አለባቸው " ብለዋል።

ረሃብ ተከሰተበት የተባለውን የቤጊ ወረዳ ሁኔታን ሲያስረዱም አቶ ሰለሞን ፣ " መሰረተ ልማት፣ ቀበሌዎች፣ የአስተዳደር ጽሕፈት ቤቶች ጤና ኬላዎች፣ ጤና ጣቢያዎች ከ2011 ዓ.ም ጀምሮ በጣም ጉዳት የደረሰበት ወረዳ ነው " ብለዋል።

" ከጤና ጋር በተያያዘ ቢያንስ 45 የሚሆን ጤና ኬላ ወድሟል ወደ አምስት ጤና ጣቢያዎች ተቃጥለዋል " ሲሉ አስታውሰው፣ ወረዳውን ታጣቂ ቡድኑ ሲቆጣጠረው አርሶ አደሩ እንዳያርስ በማዳበሪያ እንዳይጠቀም፣ ማኅበረሰቡ የሕክምና አገልግሎት እንዳያገኝ ማድረጉን አስረድተዋል።

" ሸኔ አገሪቱን ወደ ድህነት የሚመራ እንጂ ምንም አላማ የሌለው ነው " ያሉት የዞኑ አስተዳዳሪ ታጣቂ ቡድኑ " በቄለም ወለጋና  በቤጊ፣ በቆንዳላ በተለይ ገጠሩን አካባቢ ተቆጣጥሮ ጉዳት አድርሷል። ሰው ገድሏል። ብዙ ንብረቶች በዚህ ታጣቂ ቡድን ወድመዋል " በማለት ተናግረዋል።

ረሃብ የተጋረጠባቸው የሰሊጥ አምራቾች ናቸው ያሉት የዞኑ አስተዳዳሪ፣ " ሸኔ አርሶ አደሩ ማዳበሪያ በሚወስድበት ጊዜ ቀቅሎ እንዲበላ ሲያደርግ ነበር። መብላት ማለት እንደ ምግብ እንዲበላ በማድረግ እንዳያርስበት፣ እንዳይጠቀምበት ማድረግ ነው " ብለዋል።

ነዋሪዎች በበኩላቸው በተከሰተው ረሃብ የሰዎች ሕይወት ማለፉን ገልጸው፣ መንግሥት የምግብ ድጋፍ እንዲያደርግ ጠይቀዋል።

አክለውም፣ በወባ ወረርሽኝም የሰው ሕይወት እያለፈ መሆኑን አስረድተዋል።

በረሃብ የሞተ ሰው እንዳለና እንዴሌለ ማብራሪያ እንዲሰጡ ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ለቀረበላቸው ጥያቄ በሰጡት ምላሽ አቶ ሰለሞን ፣ " ከረሃብ የተነሳ የሞተ ሰው ሪፓርት አልደረሰኝም። ከምግብ ጋር በተያያዘ ግን የኦሮሚያ ቡሳ ጎኖፋ ሰሞኑን 400 ኩንታል ዱቄት አድርሷል። እርዳታ ግን አሁንም ያስፈልጋል " ብለዋል።

ከረሃብ ባሻገርም በዞኑ በሚጉኙ ወረዳዎች የወባ ወረርሽኝ እንደተከሰተ፣ #የሞቱ ሰዎችም እንዳሉ ገልጽው፣ መንግሥትና መንግስታዊ ያልሆኑ የተራድኦ ድርጅቶች እርብርብ እንዲያደርጉ ጠይቀዋል።

መንግሥት " ኦነግ ሸኔ " እያለ የሚጠራውና እራሱን የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት የሚለው ታጣቂ ቡድን ከላይ በምዕራብ ወለጋ ዞን በቀረበበት ክስ ዙሪያ ይፋዊ ምላሽ የሚሰጥ ከሆነ ተከታትለን እናሳውቃለን።

@tikvahethiopia
#ነዳጅ📈

የነዳጅ ዋጋ እያሻቀበ ለረጅም ጊዜ ሊቆይ ይችላል ሲሉ የነዳጅ ላኪዎች ህብረት መሪ አስጠነቀቁ።

የ23 ነዳጅ ላኪ ሀገራት ህብረት የሆነው ኦፔክ+ ዋና ፀሀፊ ሄይታም አል ጋይስ ፤ ለሃይል አቅርቦት ያለው ፍላጎት በመጨመሩ የነደጅ ዋጋ እንዳሻቀበ ይቀጥላል ሲሉ ተናግረዋል።

ዋና ጸሃፊው " በቀን የነዳጅ ፍላጎት ወደ 2.4 ሚሊዮን በርሜል ሲያድግ እየተመለከትን ነው " ብለዋል።

ሁለቱ ዋነኛ የነዳጅ አምራችና ' ኦፔክ+ ' አባል የሆኑት ሳዑዲና ሩሲያ የወሰኑት ውሳኔ በዚህ ዓመት መጨረሻ ከፍተኛ የአቅርቦት እጥረት ያስከትላል ሲል ዓለም አቀፉ የኢነርጂ ኤጀንሲ አስታውቋል።

" ይህ ሁለት ሉአላዊ ሀገራት ሳዑዲ አረቢያ እና ሩስያ በፍቃደኝነት የወሰኑት ነው። ይህ ውሳኔ እርግጠኛ ልንሆንበት በማንችልበት ሁኔታ ምክንያት የተደረገ ጥንቃቄ ወይም ቅድመ ዝግጅት ብለን ልንገልጸው እንችላል " ሲሉ የኦፔክ+ ዋና ጸሃፊ ተናግረዋል።

ሰሞኑን በምርት እጥረት ምክንያት የአንድ በርሜል ድፍድፍ ነዳጅ ዋጋ 95 ዶላርን አልፎ የነበረ ሲሆን ዋጋው 100 ዶላርን ሊያልፍ ይችላል የሚል ስጋትን ፈጥሯል።

ይህ የዋጋ ለውጥ በሚቀጥሉት 10 ወራት ውስጥ የነዳጅ ዋጋ ሊያሻቅብ እንደሚችልና በወሳኝ የኢኮኖሚ መስኮች ያለው የዋጋ ግሽበት ለረዥም ጊዜ እንዲቀጥል ምክንያት ይሆናል የሚል ስጋትን ማጫሩን #ቢቢሲ ዘግቧል።

@tikvahethiopia
" እስካሁን ውጤት አልተገለፀም " - የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት

የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት የ2015 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ውጤት እስካሁን #አልተገለፀም ሲል አሳውቋል።

ተፈታኞችና መላው የትምህርት ማህበረሰብ #በትዕግስት እንዲጠባበቁ ጠይቋል።

ከሁለት ሳምንት በፊት በፀጥታና ሌሎች ምክንያቶች ፈተና ሳይወስዱ የቆዩ ተማሪዎች ፈተናቸውን መውሰዳቸው ይታወቃል።

የነዚህ ተማሪዎችን ፈተና ውጤት በሐምሌ 2015 ዓ.ም ከተፈተኑ ተማሪዎች ጋር አብሮ ይፋ ለማድረግ እየተሰራ እንደሚገኝ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።

ከዚህ ቀደም " እስከ መስከረም መጨረሻ ድረስ ውጤቱ ይፋ ሊደረግ እንደሚችል " የአገልግሎቱ ከፍተኛ ኃላፊ መግለጻቸው ይታወሳል፡፡

@tikvahethiopia
" በኢሬቻ በዓል ላይ ግጭት ቀስቃሽ የሆኑ  ፁህፎችና መልዕክቶችን ይዞ መገኘት ፈፅሞ የተከለከለ ነው " - ግብረ ኃይሉ

እጅግ ከፍተኛ የህዝብ ቁጥር የሚገኝባቸው የኢሬቻ ሆራ ፊንፊኔ እና የሆራ አርሰዲ በዓላት በሰላም እንዲከበሩ የፀጥታ ኃይሎች ዝግጅታቸውን አጠናቀው ወደ ስራ መግባታቸው ተገለጸ።

ይህን የገለፀው የፀጥታና ደህንነት የጋራ ግብረ ኃይል ነው።

በአዲስ አበባ እና በቢሾፍቱ ከተሞች የሚከበረው የኢሬቻ በዓል በሰላም እንዲከበር የፀጥታ ስራው በዘመናዊ ቴክኖሎጂ ተደግፎ ይከናወናል ብሏል።

በአዲስ አበባ ለሚከበረው በዓል ለወንጀል መከላከል ተግባር ልዩ ትኩረት መሰጠቱ የተገለፀ ሲሆን አብዛኛውን የሰው ኃይል  በወንጀል መከላከል ስራ ላይ እንዲሰማራ መደረጉ ተነግሯል።

በኢሬቻ በዓል ላይ ምን ተከልክሏል ?

- ከባህላዊ አከባበሩ ተቃራኒ የሆኑ ተግባራት መፈፀም አይቻልም።

- ግጭት ቀስቃሽ የሆኑ  ፁህፎችና መልዕክቶችን ይዞ መገኘት ፈፅሞ የተከለከለ ነው።

- ባህላዊ ሥርዓቱን ሊያውክ የሚችል ማኛውም ተግባር ማከናወን ፍፁም የተከለከለ ነው።

ግብረ ኃይሉ በዓሉ ወደ ሚከበርበት ስፍራ የሚመጡ ታዳሚዎች #ፍተሻ መኖሩን ተገንዘበው አስፈላጊውን ትብብር እንዲያደርጉ መልዕክት አስተላልፏል።

ህብረተሰቡ ማንኛውም አጠራጣሪ ነገሮች ሲያጋጥሙት በ011-1-26-43-59 ፣ 011-5-52-63-02/03፣ 011-5-52-40-77፣ 011-5-54-36-78 እና 011-5-54-36-81 እንዲሁም በ987፣ 991 እና 816 ነፃ የስልክ መስመሮች ጥቆማ መስጠት ይቻላል ተብሏል።

@tikvahethiopia
#Amhara

#እቅድ፦ 6.2 ሚሊዮን ተማሪዎችን ለመመዝገብ

#እስካሁን_የተመዘገቡት ፦ 2,937,556 ተማሪዎች

በአማራ ክልል ለዘንድሮ ዓመት ትምህርት ይመዘገባሉ ተብለው ከታሰቡት 6.2 ሚሊዮን ተማሪዎች መመዝገብ የተቻለው 2,937,556 ተማሪዎችን እንደሆነ የክልሉ ትምህርት ቢሮ አሳውቋል።

ይህ ከቅድመ መደበኛ እስከ 2ኛ ደረጃ ሲሆን ካለፉት ዓመታት ሲነፃፀር እቅዱ አጥጋቢ እንዳልሆነ አመልክቷል።

የሚጠበቀውን ያህል ተማሪዎች እንዳይመዘገቡ ከሆነበት ምክንያቶች አንዱ በክልሉ ውስጥ በልዩ ልዩ ቦታዎች ያለው የትጥቅ ግጭት መሆኑ ተነግሯል።

አንዳንድ ዞኖች እስካሁን ጭራሽ ምዝገባም ያልጀመሩ ሲሆን እነዚህም የምዕራብ አማራ አካባቢዎች ፣ ምስራቅ ጎጃም ፣ ምዕራብ ጎጃም ደብረማርቆስ ፣ ሰሜን ጎጃም እንደሆኑ የክልሉ ትምህርት ቢሮ ገልጿል።

በክልሉ ያለው የፀጥታ ሁኔታ ተፅእኖ አሳድሮብናል ያለው ትምህርት ቢሮ አንፃራዊ ሰላም ባለባቸው አካባቢዎች ላይ የተማሪ ምዝገባ መከናወኑን አመልክቷል። አንዳንድ ዞኖችም የተሻለ አፈፃፀም አስመዝግበዋል ሲል አክሏል።

አሁንም የምዝገባ ቀኑ ያልተገደበ ሲሆን ዞኖች ጎን ለጎን የመማር ማስተማር ስራውን እና ምዝገባውን እንዲያከናውኑ እየተደረገ ነው ማለቱን ቪኦኤ ዘገቧል።

ፎቶ ፦ ፋይል

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Tigray #Update

ከጥቅምት 3 እስከ 5/2016 ዓ.ም ተፈፃሚ የሚሆነው የትግራይ የሃዘን ቀን ማሰፈፀምያ መመሪያ ይፋ ሆነ።

ከመስከረም 21/2016 ዓ/ም ጀምሮ ተፈፃሚ የሚሆንና የጊዚያዊ አስተዳደሩ ምክትል ፕረዚደንት ሌ/ጀነራል ታደሰ ወረደ ፊርማ ያረፈበት 18 አንቀፆችን የያዘ የትግራይ የሃዘንና መርዶ " መመሪያ ቁጥር 022016 " ምን ይላል ? 

የመርዶና የሃዘን ስነ-ሰርአቱ ጥቅምት 2 ታውጆ ከጥቅምት 3 እስከ 5 የሃዘን ቀናት ይሆናል። ጥቅምት 6 /2016 ዓ.ም የሃዘን ቀን ስነ-ሰርአቱ ያበቃል።

ከጥቅምት 3 እስከ 5 /2016 ዓ.ም በሚኖሩ የሃዘን ቀናት በመመሪያ የተከለከሉና በህግ የሚያስቀጡ ዝርዝር ተግባራት ተቀምጠዋል።

1ኛ. ስፓርታዊ ጨወታዎች ጨምሮ ድምፅ የሚፈጥር ንግዳዊና ንግዳዊ ያልሆነ ተግባር የተከለከለ ነው።  

2ኛ. ቀንና ማታ በሙዚቃ በመታጀብ የሚሰሩ መጠጥ ቤቶች ፣ የቡናና ተመሳሳይ የሽያጭ አገልግሎት የሚሰጡ ዝግ ይሆናሉ።

3ኛ. ሰርግ ፣ የህፃናት ክርስትና ፣ ልደትና የመሳሰሉ ድምፅ የሚፈጥሩ ተግባራት አይፈቀዱም። 

4ኛ. ጥይት መተኮስ የተከለከለ ነው። 

በትግራይ ደረጃ የሚከናወነው የሃዘን ቀን ስነ-ሰርአት ተጠናቆ ተለዋጭ መመሪያ እስከሚሰጥ ድረስ ፍፁም የተከለከሉና በህግ የሚያስቀጡ ተግባራት የሚከተሉት ናቸው። 

1ኛ. የተሰዋ ታጋይ አስከሬን ካረፈበት ቦታ ማንሳትና ማዘዋወር የተከለከለ ነው።

2ኛ. የተሰዋ ታጋይ ሃወልት መገንባት ወይ ደግሞ ያረፈበት መቃብር ማሻሻልና መለወጥ የተከለከለ ነው።

3ኛ. የተሰዋ ታጋይ አስከሬን ያረፈበት ቦታ መጠቆምና ከቦታው ለማንሳት ጥቅም መጠየቅና መቀበል የተከለከለ ነው።

4ኛ. የተሰዋ ቤተሰብ ክብርና መንፈስ የሚጎዳ ፣ የሚያደበዝዝ ተግባር መፈፀም የተከለከለ ነው።

5ኛ. አገልግሎት ሰጪ የግል ድርጅቶች ሳይጨምር መንግስታዊና መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማት #ዝግ ይሆናሉ።

በመመሪያ የተጠቀሱ ህጎች የማያከብሩና የሚጥሱ ግለሰቦችና ተቋማት ከ10 ሺህ እስከ 50 ሺህ ቅጣት የተቀመጠ ሲሆን ቅጣቱን ለማስፈፀም የፓሊስና የፍትህ አካላት ያካተተ 8 ኣባላት ያሉት ግብረ ሃይል በወረዳና ቀበሌ ደረጃ መቋቋሙ ቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ ዘግቧል።

#TikvahEthiopiaMekelle

@tikvahethiopia