TIKVAH-ETHIOPIA
1.52M subscribers
59.7K photos
1.52K videos
215 files
4.14K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
" ተፈታኞች በአካልም ይሁን በስነልቦና እራሳችሁን ዝግጁ አድርጉ " - የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት የ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና መርሃ ግብርን ይፋ አድርጓል። በዚህም ፥ የማህበራዊ ሳይንስ ተፈታኞች ሐምሌ 16 እና 17/2015 ዓ.ም ወደተመደቡበት ተቋም ይገባሉ። ሐምሌ 18/2015 ዓ.ም ገልጻ ይሰጣቸዋል። ከሐምሌ 19 እስከ 21/2015…
ተፈታኞች ከነገ ጀምሮ ይገባሉ።

የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ተፈታኝ የሆኑ የማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች ከነገ ሐምሌ 16 ጀምሮ ወደ ተመደቡባቸው ዩኒቨርሲቲዎች ይገባሉ።

ተፈታኝ ተማሪዎች ከሚማሩባቸው ትምህርት ቤቶች ወደ ተመደቡባቸው ዩኒቨርሲቲዎች የሚጓዙት በተዘጋጅላቸው ተሽከርካሪዎች ነው።

ተፈታኞች ዩኒፎርማቸውን መልበስ ፤ ብርድልብስና አንሶላ ይዘው መገኝት ይጠበቅባቸዋል። 

ወደ መፈተኛ ተቋማት ቆሎ፣ ጭኮ፣ በሶ የመሳሰሉ ደረቅ ምግቦችን ይዞ መግባት የሚፈቀድ ሲሆን የቴክኖሎጂ ውጤቶች፣ ሞባይል፣ አይፓድ፣ ላፕቶፕ የመሳሰሉ እንዲሁም ማንኛውም ጌጣጌጥ ይዞ መግባት ፈፅሞ የተከለከለ ነው።

ተማሪዎቹ ከቤታቸው ሲወጡ፦
- መታወቂያ ፣
- አድሚሽን ካርድ
- የት/ቤት ዩኒፎርም መያዛቸውን እንዳይረሱ ፤ ወላጆችም ይህንን እንዲያስታውሷቸው ጥሪ ቀርቧል።

ዘንድሮ የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በከፍተኛ የመንግሥት የትምህርት ተቋማት ውስጥ ለሁለተኛ ጊዜ ይሰጣል።

ፎቶ ፦ ፋይል

@tikvahethiopia
#CBE

ግብርዎን በሲቢኢ ብር እንዴት ይከፍላሉ?
================================
ለአዲስ አበባ፣ ድሬዳዋ እና ሶማሌ ክልል ግብር ከፋዮች

ከግብር ሰብሳቢው ተቋም
• የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር፣
• የገንዘብ መጠን እና
• የክፍያ ማዘዣ ቁጥር የያዘ መልእክት ሲደርስዎት

ወደ *847# በመደወል ቅደም ተከተሉን ጠብቀው ግብርዎን በቀላሉ ይክፈሉ፡፡
#MyWish

አስተማማኝ የሆነውንና ቱርክ ሰራሹን ኢሳን ሲልድ ባትሪን በተለያዩ አማራጮች ማለትም በ12V35AH፣ በ12V45AH፣ በ12V55AH፣ በ12V60AH፣ በ12V70AH፣ በ12V90AH፣ በ12V100AH፣በ12V120AH እና በ12V150AH በጅምላና በችርቻሮ በተመጣጣኝ ዋጋ ይዘንላችሁ ቀርበናል፡፡
0910041280  0911135133  0921612272  0911159234   0984733988  0941473413
ዋና መስሪያ ቤት፡ ሀይሌ ጋርመንት ወደለቡ መብራት በሚወስደው መንገድ ቅርንጫፍ፡ ወሎ ሰፈር ጎርጎሪዮስ አደባባይ አጠገብ
ማይ ዊሽ ኢንተርፕራይዝ ኃላ/የተ/የግ/ማ 
የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ: https://t.iss.one/MYWISHENT
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update

የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና የሚወስዱ የማህበራዊ ሳይንስ ተፈታኞች ወደየተመደቡበት ከፍተኛ ትምህርት ተቋም ዛሬ መግባት ጀምረዋል።

የማህበራዊ ሳይንስ ተፈታኞች እስከ ነገ ሐምሌ 17/2015 ዓ.ም ወደተመደቡበት ተቋም ተጠቃለው ይገባሉ።

የማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች ፈተና ከሐምሌ 19 እስከ 21/2015 ዓ.ም ይሰጣል፡፡

@tikvahuniversity
#Tigray

የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ ትግራይ አስመልክቶ በብድር ወለድ አከፋፈል  ያወጣው መመሪያ መልሶ እንዲያጤነው ተጠየቀ።

የመቐለና የዓዲግራት የንግድና የዘርፍ ማህበራት ምክር ቤቶች ለቲክቫህ የትግራይ ቅርንጫፍ ቤተሰብ በሰጡት ቃለመጠይቕ ብሄራዊ ባንክ የተለያዩ ባንኮች ከጦርነቱ በፊት  ለትግራይ የንግድ ማህበረሰብ የሰጡት በድርና አመላለሱ አስመልክቶ ሰኔ 9 ቀን 2015 ዓ.ም ያወጣው መምሪያ ዳግም ሊጤን ይገባዋል ብለዋል።

የመቐለ የንግድና የዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት ዋና ፀሃፊ አቶ በርሀ አርከበ በጦርነቱ ምክንያት በትግራይ የንግድ ማህበረሰብ የደረሰው ኢኮኖሚያ ፣ ሰብአዊና ማህበራዊ ኪሳራ እጅግ ግዙፍ ነው። ጉዳቱ እጅግ እጅግ ከባድ ነው፤ ኢኮኖሚያዊ ጉዳቱ ብቻ ለይተን ብናይ የንግድ ማህበረሰቡ አካላዊ ጥቃት ደርሶታል። ተዘርፈዋል ፤ ኪሳራ አጋጥሞታል ብለዋል።

የትግራይ የንግድ ማህበረሰብ ከሰላም ስምምነቱ በኋላ የኢትዮጵያ መንግስት ያጋጠመውን ኪሳራ የሚሽር አሰራር ያወጣል ብለን እንጠብቅ ነበር ያሉት ዋና ፀሃፊው ፤ ይሁን እንጂ ብሄራዊ ባንክ ከተለያዩ ባንኮች የተወሰደው በድር ከነወለዱ ይከፈል የሚል መመሪያ ማውጣቱ በንግድ ማህበረሰቡ ዘንድ ድንጋጤ እና መረበሽ ፈጥረዋል ብለዋል።

ብሄራዊ ባንክ ያወጣው እጅግ አስደንጋጭና ተስፋ አስቆራጭ መመሪያ በሰላም ስምምነቱ ምክንያት በንግድ ማህበረሰቡ የተፈጠረውን መነቃቃትና መነሳሳት ያደበዘዘ ነው ያሉት የዓዲግራት የንግድና የዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት ፕረዚደንት አቶ ዲበኩሉ አለም በርሃነ በበኩላቸው ፤ ብሄራዊ ባንክ ያወጣው መመሪያ እንዲሻር የንግድ ማህበረሰብ ተወካዮች ለክልሉ ግዚያዊ አስተዳደርና ለብሄራዊ ባንክና ለገንዘብ ሚኒስቴር ጥያቄ አቅርበናል ብለዋል።

በትግራይ የንግድ ማህበረሰብ የደረሰው ውድመትና ያጋጠመው ኪሳራ የክልሉና የፌደራል መንግስት ተወያዮቹ እንደ አንድ ኢኮኖሚያዊ የመወያያ አጀንዳ ማየት ይገባቸዋል ያሉት አቶ ዲበኩሉ ፤ ብሄራዊ ባንክ ያወጣው መምሪያ የሚያስትለው ኢኮኖሚያዊ ቅጣት የትግራይ የንግድ ማህበረሰብ የሚያቀጭጭ ፤ ከገበያ ውድድር የሚያስወጣ በውጤቱም ክልሉንና አገርን የሚገዳ በመሆኑ የፌደራል መንግስት ለችግሩ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ መፍታት አለበት ሲሉ አክለዋል።

'አገራዊ ፋይዳ ያላቸው እቃዎች እና ምርቶች ከውጭ ለሚያስገቡ ተጨማሪ ብድርና የውጭ ምንዛሬ ቅድሚያ እንዲያገኙ የሚል ብሄራዊ ባንክ ባወጣው መመሪያ የተካተተው ለንግድ ማህበረሰቡና ለአገር ጠቃሚ እንደሆነ የተናገሩት የመቐለ የንግድና የዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት ዋና ፀሃፊ አቶ በርሀ አርከበ ፤ ከጦርነት በፊት በክልሉ ለተወሰደው የብድር ወለድ አንዲነሳ አለማድረግ ነጋዴው ተጨማሪ ብድር  እንዳይወስድ ስለሚከለክል እጅግ ጎጂ ነው ብለዋል።

ከተለያዩ ባንኮች የተወሰደው የብድር ወለድ ይነሳ ሲባል ባንኮች ለኪሳራ እንደሚዳረጉ እንገነዘባለን ያሉት አመራሮቹ ፤ ለኪሳራ ማካካሻ የሚሆን መፍትሄ ከፌደራል መንግስት፣ ከጠቅላይ ሚኒስቴር ቢሮ ፣ ከብሄራዊ ባንክን ከገንዘብ ሚኒስቴር ይጠበቃል ብለዋል።

በትግራይ ክልል ከጦርነቱ በፊት 4.3 ሚሊዮን ቆጣቢዎች 70 ቢሊዮን ብር ቆጠብው ፣ ከጦርነቱ በኋላ ወለድ ጨምሮ 90 ቢሊዮን መድረሱ ፣ በብድር የተወሰደው 35 ሚሊዮን ብር ከጦርነቱ በኋላ ወለድ ጨምሮ 50 ቢሊዮን ብር መድረሱ የክልሉ የፋይንናስ የኢኮኖሚ ባለሙያዎች ያካሄዱት ጥናት ያመለክታል።

ያንብቡ ፦ https://telegra.ph/Tikvah-Ethiopia-07-23-2

@tikvahethiopia
#Update

የመውለጃ ቀናቸው የደረሰ ነፍሰ ጡር እና ጡት የሚያጠቡ ሴት የ12ኛ ክፍል ተፈታኞች በሚቀጥለው ዓመት እንደ መደበኛ ተፈታኝ መፈተን እንደሚችሉ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቋል።

" መውለጃ ወራቸው የደረሰ ነፍሰ ጡር እና ጡት የሚያጠቡ ሴት ተፈታኞች በሚቀጥለው ዓመት ተዘጋጅተው እንደ መደበኛ ተፈታኝ እንዲፈተኑ እንመክራለን " ብሏል አገልግሎቱ።

" ሆኖም ለመፈተን የወሰኑ ጡት የሚያጠቡ ተፈታኞች አንድ ሴት ሞግዚት ይዘው በመግባት እንዲፈተኑ ተገቢው ድጋፍ የሚደረግላቸው መሆኑን " አገልግሎቱ ገልጿል።

የተፈታኞች መብትና ግዴታ እንዲሁም የተከለከሉ ነገሮች በተፈታኟና በሞግዚቷ ላይ ተግባራዊ እንደሚሆን አገልግሎቱ ጠቁሟል።

Via @tikvahuniversity
አዋሽ ኢ-ስኩል ሲስተም
=========
 ፋይል ጠፋ አልጠፋ ብለው ከመጨነቅ ይገላግልዎታል፣
 አንድ ቦታ ሆነው ሁሉ ቦታ ያደርስዎታል፣
 የመምህራንና የወላጆች መረጃ፣ እጅግ ዘመናዊ የክፍያ አሰባሰብና የቅጣት መቆጣጠሪያ ሥርዓት እንዲሁም ሌሎችም ጥቅም የሚያገኙበት
 በአዋሽ ኢ-ስኩል ቤተ መጽሀፍት የተለያዩ ለትምህርት አጋዥ የሆኑ መጽሀፍትን የሚያገኙበት
 ያሉበት ቦታ ሆነው የገፅ ለገፅ ትምህርት አገልግሎት እንዲያገኙ ያስችልዎታል፡፡
አዋሽ ኢ-ስኩል ሲስተም የግዜው ውድ ስጦታ!
አዋሽ ባንክ!
https://eschool.awashbank.com/

Telegram: https://t.iss.one/awash_bank_official
#Hawassa

በሀዋሳ ከተማ የሚሰተዋለዉ የሞተር ስርቆት ትኩረት ያሻዋል ሲሉ  ነዋሪዎች ገለጹ።

ፖሊስ በበኩሉ  በተዘረጉ ጠንካራ የጸጥታ ሰንሰለቶችና በከተማዉ ዋና ዋና መንገዶች በተተከሉ ካሜራዎች በመታገዝ ችግሩን ለመቅረፍ ጥረት ላይ መሆኑን አስታዉቋል።

ቅሬታቸዉን ካጋሩን የከተማዉ ነዋሪዎች  መካከል  መምህር  ወንድሙ በየነ ከወራት በፊት መንገድ ዳር ያቆሙት ሞተር ጠፍቶባቸዉ ለፖሊስ ቢያመለክቱም መፍትሄ እንዳልተሰጣቸዉና ሞተራቸዉ ጠፍቶ መቅረቱን ይገልጻሉ።

በሌላ በኩል ደግሞ ግቢያቸዉ ዉስጥ ያቆሙት ሞተር የተሰረቀባቸዉ አሰተያየት ሰጭም በተመሳሳይ ሞተራቸዉ ጠፍቶ መቅረቱን ያወሳሉ ።

በዚህ ጉዳይ ምን እየተሰራ ነዉ ስንል ላነሳነዉ ጥያቄ ምላሽ የሰጡን የሀዋሳ ከተማ ፖሊስ አዛዥ ኢንስፔክተር  መልካሙ አየለ ችግሩ በሚነገርለት ደረጃ አለመሆኑን  ገልጸዉ ፖሊስ ችግሩን ለመፍታት ባደረገዉ የተቀናጀ ጥረት ጥሩ ዉጤት መመዝገቡን ያነሳሉ።

ኢንስፔክተሩ አክለዉም በቅርቡ በከተማዉ ዋና ዋና መንገዶች  የተተከሉ  ካሜራዎች ከፍተኛ እገዛ እያደረጉ መሆኑንና በዚህ አመት ብቻ 41 የተሰረቁ  ሞተሮችን  ለባለቤቱ በመመለስ ወንጀለኞችን ለፍርድ ማቅረባቸዉን ያነሳሉ።

በመሆኑም አሁን ላይ ኢትዮጵያ ዉስጥ ካሉ ሰላማዊ ከተሞች አንዷ ሀዋሳ መሆኗን በማንሳት  ከተማዉን ከዚህ በተሻለ ሰላማዊ ለማድረግ ግን የሁሉም ነዋሪ ትብብር አስፈላጊ መሆኑን ገልጸዋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
' ሕዝበ ውሳኔ ' የአማራ ክልል መንግሥት የማንነት እና የወሰን ጥያቄ በሕዝበ ውሳኔ እንዲፈታ ስራዎች እየተሰሩ ነው ሲል አሳወቀ። የክልሉ መንግሥት ይህን ያሳወቀው ዛሬ በኮሚኒኬሽን ቢሮው በኩል በሰጠው መግለጫ ነው። የክልሉ የኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ኃላፊ አቶ ግዛቸው ሙሉነህ ለመገናኛ ብዙሃን በሰጡት መግለጫቸው ፤ የአማራ እና የትግራይ ክልሎች ጥያቄ የሚያነሱባቸውን የማንነት እና የወሰን ጉዳዮችን…
" እኛ የፌዴሬሽን ምክር ቤት የሚሰጠውን ውሳኔ እየጠበቅን ነው " - ኮሎኔል ደመቀ ዘውዱ

የአማራ እና የትግራይ ክልሎች የሚዋሰኑባቸውን የወልቃይት፣ የጠለምትና የራያ አካባቢዎችን " ይገባኛል " ጥያቄን በተመለከተ የፌዴሬሽን ምክር ቤት የሚሰጠውን ውሳኔ እየተጠበቁ መሆናቸውን ኮሎኔል ደመቀ ዘውዱ ለሪፖርተር ጋዜጣ በሰጡት ቃል አሳውቀዋል።

ኮሎኔል ደመቀ ዘውዱ በአሁን ሰዓት የወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ  ምክትል አስተዳዳሪ እና የሰላምና የፀጥታ መምርያ ኃላፊ በመሆን እያገለገሉ ሲሆን በቅርቡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ በፓርላማ በቀረቡበት ወቅት " ሁለቱ ክልሎች የሚዋሰኑባቸውን አካባቢዎች በሕዝብ ውሳኔና በሕጋዊ መንገድ መፍታት አለባቸው " በሚል ስለሰጡት አስተያየት ተጠይቀው መልሰዋል።

ኮሎኔል ደመቀ ዘውዱ ምን አሉ ?

" በወልቃይት ጉዳይ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ውሳኔ እናደርጋለን ሲሉ በግልጽ አልሰማንም፡፡

ነገር ግን በሕጋዊ መንገድ ቢፈታ ይሻላል የሚለውን ምክር አዘል ነገር ለፓርላማው ሲናገሩ ሰምተናል፡፡

ግን በዚህኛው ቀጣና በዚህኛው ዞን ብለው ሲያነሱ እኔም በግል አልሰማሁም፣ እኛም የምናውቀው ነገርም የለም። ነገር ግን የወልቃይት ጉዳይ በየትኛው መንገድ ነው ሊፈታ የሚገባው የሚለውን ቀደም ሲል በተደጋጋሚ ተናግረናል፡፡

ሊፈታ በሚገባው መንገድ እንዲፈታ ለመንግሥት አመልክተናል።

ራያም፣ ጠለምትም፣ ወልቃይትም ስላሉ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ስለየትኛው እንደተናገሩ ግልጽ አልሆነልኝም። በግምት መልስ ለመስጠት ያስቸግራል።

ብዙ ሰው መላምት ሊኖረው ይችላል፡፡ ነገር ግን የወልቃይት ጉዳይ ሊፈታ የሚገባበትን መንገድ ጠቅሰን ለፌዴሬሽን ምክር ቤት ስላቀረብን ውሳኔውን እየጠበቅን ነው።

በሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት ወቅትም ሆነ አሁን ከማኅበረሰቡ ጋር ነኝ ፤ የአገር መከላከያ ሠራዊት የወልቃይት አካባቢን እየተከላከለና እየጠበቀ እንዳለ ነው የምናውቀው።

በአካባቢው ከመከላከያ ጋር ምንም ዓይነት ጦርነት የለም፣ ተባብረን ነው እየሠራን ያለነው፡፡ አካባቢው ሰላማዊ በመሆኑ ፋኖ በሚል ምክንያት ምንም ዓይነት ግጭትም ሆነ ጦርነት የለም። "

የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳዳር በበኩሉ የክልሉ አስተዳደራዊ ወሰን ከጦርነቱ በፊት ወደ ነበረበት እንዲመለስ፣ በጦርነቱ ምክንያት ከምዕራብ ትግራይና ከሌሎች የአማራ ክልል አዋሳኝ አካባቢዎች የተፈናቀሉ የክልሉ ነዋሪዎቸ በአፋጣኝ ወደ ቀዬአቸው እንዲመለሱ በተደጋጋሚ ጥያቄ እያቀረበ ነው፡፡

#ሪፖርተር

@tikvahethiopia