TIKVAH-ETHIOPIA
#Update በብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ የሚመራ የልዑካን ቡድን ሐምሌ 3 ቀን 2015 ዓ.ም ወደ ትግራይ ርዕሰ ከተማ መቐለ ይጓዛል። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ ባስተላለፈው ውሳኔ መሰረት በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት የሚመራ 13 አባላት ያሉት የልዑካን ቡድን ሐምሌ…
#Update
ቅዱስ ሲኖዶስ የትግራይ ህዝብን ይቅርታ ጠየቀ።
በክልል ትግራይ በተካሄደው ጦርነት ወቅት ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ሐዋርያዊትና ታሪካዊት ቤተ ክርስቲያን እንደመሆኗ መጠን ፦
- ጦርነቱ እንዲቆም በወቅቱ መግለጫ ባለመስጠቷ፣
- በጦርነቱ መካከል ወደ ትግራይ ክልል መግባትና መውጣት በሚቻልበት ወቅትም በክልሉ የሚገኙ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳትን፣ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያንንና መላው #ሕዝበ_ትግራይን በአካል በቦታው ተገኝታ ባለመጠየቋና ባለማጽናናቷ፣
- ጦርነቱ ቁሞ በአገር አቀፍ ደረጃ እርቀ ሰላም ከወረደበት ጊዜ ጀምሮ ለደረሰው ጉዳት በቅዱስ ሲኖዶስ የተወሰነውን ሰብአዊ ድጋፍ በውሳኔው መሠረት በወቅቱ ማድረስ ባለመቻሏ፣ በዚሁም የተነሣ በቤተ ክርስቲያኗና በመላው ሕዝበ ትግራይ መካከል ለተፈጠረው ቅሬታና አለመግባባት ቅዱስ ሲኖዶስ በይፋ ይቅርታ ጠይቋል።
@tikvahethiopia
ቅዱስ ሲኖዶስ የትግራይ ህዝብን ይቅርታ ጠየቀ።
በክልል ትግራይ በተካሄደው ጦርነት ወቅት ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ሐዋርያዊትና ታሪካዊት ቤተ ክርስቲያን እንደመሆኗ መጠን ፦
- ጦርነቱ እንዲቆም በወቅቱ መግለጫ ባለመስጠቷ፣
- በጦርነቱ መካከል ወደ ትግራይ ክልል መግባትና መውጣት በሚቻልበት ወቅትም በክልሉ የሚገኙ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳትን፣ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያንንና መላው #ሕዝበ_ትግራይን በአካል በቦታው ተገኝታ ባለመጠየቋና ባለማጽናናቷ፣
- ጦርነቱ ቁሞ በአገር አቀፍ ደረጃ እርቀ ሰላም ከወረደበት ጊዜ ጀምሮ ለደረሰው ጉዳት በቅዱስ ሲኖዶስ የተወሰነውን ሰብአዊ ድጋፍ በውሳኔው መሠረት በወቅቱ ማድረስ ባለመቻሏ፣ በዚሁም የተነሣ በቤተ ክርስቲያኗና በመላው ሕዝበ ትግራይ መካከል ለተፈጠረው ቅሬታና አለመግባባት ቅዱስ ሲኖዶስ በይፋ ይቅርታ ጠይቋል።
@tikvahethiopia
#Update
የኢትዮጵያ የፌዴራል መንግሥት የ2016 ዓ/ም በጀት 801 ቢልዮን ብር ሆኖ ፀደቀ።
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው 28ኛ መደበኛ ስብሰባው የ2016 በጀት ዓመት የፌደራል መንግስት በጀትን 801 ነጥብ 6 ቢልዮን ብር አድርጎ በአንድ ድምፀ-ተአቅቦ በአብላጫ ድምፅ አጽድቋል።
Via HoPR
@tikvahethiopia
የኢትዮጵያ የፌዴራል መንግሥት የ2016 ዓ/ም በጀት 801 ቢልዮን ብር ሆኖ ፀደቀ።
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው 28ኛ መደበኛ ስብሰባው የ2016 በጀት ዓመት የፌደራል መንግስት በጀትን 801 ነጥብ 6 ቢልዮን ብር አድርጎ በአንድ ድምፀ-ተአቅቦ በአብላጫ ድምፅ አጽድቋል።
Via HoPR
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ዶ/ር ደሳለኝ ጫኔ ምን አሉ ? የተ/ም/ቤት አባል ዶ/ር ደሳለኝ ጫኔ ፦ " ጠ/ሚ ዐቢይ ወደ መንበረ ስልጣን ከወጡበት ከመጋቢት 2010 ዓ/ም ጀምሮ እየተወሳሰቡ የሄዱት የሀገራችን ፖለቲካዊ ፣ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ችግሮች አሁን ላይ ወደ ሁለንተናዊ ቀውስ መሸጋገራቸውን ማሸፋፈን ወደማይቻልበት ደረጃ ደርሰዋል። ብልፅግና መራሹ መንግስትዎ ፦ - የኢትዮጵያ ህዝብ በሰላም ወጥቶ የሚገባበት ፣ - ነጋዴው…
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለዶ/ር ደሳለኝ ምን ምላሽ ሰጡ ?
ኢትዮጵያ ቀውስ ውስጥ መሆኗና ለዚህም ተጠያቂው ገዢው ብልፅግና ፓርቲና የጠቅላይ ሚኒስትሩ የወደቀ አመራር በመሆኑ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከስልጣናቸውን #እንዲለቁና ስልጣናቸውን ለሚቋቋም ጊዜያዊ ሲቪል አስተዳደር እንዲያስረክቡ ፤ ፓርላማውም ተበትኖ ለምርጫ መንገድ እንዲጠርግ በሚል በዶ/ር ደሳለኝ ጫኔ ለተጠየቀው ጥያቄ ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ምላሽ ሰጥተዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በፓርቲያቸውና መንግሥታቸው ላይ ከታቃዋሚ ፓርቲ በኩል የቀረበውን ክስ በተመለከተ " እንዲህ ያለው ንግግር ለዛሬ #ፌስቡክ፣ ለዛሬ #ዩትዩብ ጥሩ ነው ፤ አቶ እንትና እንትና እንዲህ አደረጉ ለሚለው ለፌስቡክ ፍጆታ ጥሩ ነው ለትውልድ እና ሀገር ግን አይጠቅምም " ብለዋል።
" ቆም ብለን እኛ ማናየውን በማሳየት ለኢትዮጵያ ህዝብ የሚጠቅመውን ሃሳብ ብናቀርብ ጠቃሚ ነው " ሲሉ ተደምጠዋል።
" በኢኮኖሚ፣ በሰላም እና በአንዳንድ ጉዳዮች የቀረቡትን የምንወስዳቸውና የምንሰራባቸው እንደሆነ ምንም ጥያቄ የለውም " ያሉት ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ " በጥቅሉ ኢትዮጵያ ጨለማ ውስጥ ናት ከተባለ ግን ከሰሀራ በታች ካሉ ሀገራት በኢኮኖሚ 3ኛ ናት፣ ከምስራቅ አፍሪካ አንደኛ ናት ፣ ትላልቅ ተቋማትን እየገነባች ያለች ሀገርናት የሚል መልስ ሆኖ ያልቃል " ሲሉ ተናግረዋል።
ምርጫን በተመለከተ ፤ " ምርጫ ይካሄድ የሚለውን ሃሳብ በጣም አደንቃለሁ ፤ ብዙ ጊዜ የተቃዋሚዎች ችግር ምርጫ አይፈልጉም ዝም ብላችሁ ልቀቁና እኛ እንያዝ ነው የሚሉት ፤ አሁን ምርጫ ይደረግ የሚለው በጣም ጠቃሚ ነው ግን ሶስት ዓመት #መታገስ አለብን " ብለዋል።
" በየሳምንቱ ምርጫ ስለማይደረግ ፤ ሶስት አመት ታግሰን ያለንን ሃሳብ ይዘን ቀርበን እኛም ይዘን ቀርበን የኢትዮጵያ ህዝብ የሚፈርደውን ፍርድ በፀጋ መቀበል ነው ፤ የዛሬ ሁለት ዓመት የፈረደውን ፍርድ አልተቀበልኩምና አሁን ፓርላማው ፈርሶ ምርጫ ካልተካሄደ አሁንም ፈርሶ ቢካሄድና ቢመረጥ ካልተመረጥን ይቀጥላል ጉዳዩ በየሁለት አመቱ ምርጫ ለማካሄድ አቅም ስለሚያንሰን በተቀመጠው መንገድ በ5 ዓመት እናደርጋለን " ብለዋል።
" ምርጫ ሲደረግ ያሉ ሀሳቦች ለህዝብ ቀርበው እኛ ህዝቡ በሚፈልገው ልክ ካላገለገልንና ካልጠቀምን ህዝቡ በምርጫው ሲቀጣን እጅ ስመን፣ ባንስምም እጅ ነስተን እናስረክባለን ፤ እስከዛ መታገስ ጥሩ ነው ፤ ፍርዱን ለህዝብ እንተወው " ሲሉ መልሰዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሀገሪቱ ከገባችበት ቀውስ ጋር በተያያዘ ስልጣናቸውን እንዲለቁ በአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) ህዝብ በመረጣቸው የምክር ቤት አባላት ሲጠየቁ የዛሬው ሁለተኛ ነው።
የምክር ቤት አባሉ አቶ ክርስቲያን ታደለ ከወራት በፊት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ስልጣን በመልቀቅ " ላለው ችግር የመፍትሄው አካል ለመሆን አላሰቡም ወይ ? በሰብዓዊነት ላይ በተፈፀሙ እንዲሁም በማንነት ተኮር የዘር ማጥፋት ፣ የዘር ማፅዳት እና የማንነት ማሳሳት ወንጀሎች ተጠያቂ ለመሆን ምን ያህል ዝግጁ ኖት ? " የሚል ጥያቄ አቅርበው የነበረ።
በወቅቱ ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ፤ ኃላፊነት መውሰድ ካለብን በጋራ ቢሆን መልካም ስለሆነ " ስልጣን ብንለቅ " ነው የሚባለው ምክንያቱም መንግስት ማለት አስፈፃሚ ብቻ አይደለም የሚል ምላሽ ሰጥተዋቸው ነበር።
የዶ/ር ደሳለኝ ጫኔ ንግግር : https://t.iss.one/tikvahethiopia/79527
#TikvahEthiopia
@tikvahethiopia
ኢትዮጵያ ቀውስ ውስጥ መሆኗና ለዚህም ተጠያቂው ገዢው ብልፅግና ፓርቲና የጠቅላይ ሚኒስትሩ የወደቀ አመራር በመሆኑ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከስልጣናቸውን #እንዲለቁና ስልጣናቸውን ለሚቋቋም ጊዜያዊ ሲቪል አስተዳደር እንዲያስረክቡ ፤ ፓርላማውም ተበትኖ ለምርጫ መንገድ እንዲጠርግ በሚል በዶ/ር ደሳለኝ ጫኔ ለተጠየቀው ጥያቄ ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ምላሽ ሰጥተዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በፓርቲያቸውና መንግሥታቸው ላይ ከታቃዋሚ ፓርቲ በኩል የቀረበውን ክስ በተመለከተ " እንዲህ ያለው ንግግር ለዛሬ #ፌስቡክ፣ ለዛሬ #ዩትዩብ ጥሩ ነው ፤ አቶ እንትና እንትና እንዲህ አደረጉ ለሚለው ለፌስቡክ ፍጆታ ጥሩ ነው ለትውልድ እና ሀገር ግን አይጠቅምም " ብለዋል።
" ቆም ብለን እኛ ማናየውን በማሳየት ለኢትዮጵያ ህዝብ የሚጠቅመውን ሃሳብ ብናቀርብ ጠቃሚ ነው " ሲሉ ተደምጠዋል።
" በኢኮኖሚ፣ በሰላም እና በአንዳንድ ጉዳዮች የቀረቡትን የምንወስዳቸውና የምንሰራባቸው እንደሆነ ምንም ጥያቄ የለውም " ያሉት ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ " በጥቅሉ ኢትዮጵያ ጨለማ ውስጥ ናት ከተባለ ግን ከሰሀራ በታች ካሉ ሀገራት በኢኮኖሚ 3ኛ ናት፣ ከምስራቅ አፍሪካ አንደኛ ናት ፣ ትላልቅ ተቋማትን እየገነባች ያለች ሀገርናት የሚል መልስ ሆኖ ያልቃል " ሲሉ ተናግረዋል።
ምርጫን በተመለከተ ፤ " ምርጫ ይካሄድ የሚለውን ሃሳብ በጣም አደንቃለሁ ፤ ብዙ ጊዜ የተቃዋሚዎች ችግር ምርጫ አይፈልጉም ዝም ብላችሁ ልቀቁና እኛ እንያዝ ነው የሚሉት ፤ አሁን ምርጫ ይደረግ የሚለው በጣም ጠቃሚ ነው ግን ሶስት ዓመት #መታገስ አለብን " ብለዋል።
" በየሳምንቱ ምርጫ ስለማይደረግ ፤ ሶስት አመት ታግሰን ያለንን ሃሳብ ይዘን ቀርበን እኛም ይዘን ቀርበን የኢትዮጵያ ህዝብ የሚፈርደውን ፍርድ በፀጋ መቀበል ነው ፤ የዛሬ ሁለት ዓመት የፈረደውን ፍርድ አልተቀበልኩምና አሁን ፓርላማው ፈርሶ ምርጫ ካልተካሄደ አሁንም ፈርሶ ቢካሄድና ቢመረጥ ካልተመረጥን ይቀጥላል ጉዳዩ በየሁለት አመቱ ምርጫ ለማካሄድ አቅም ስለሚያንሰን በተቀመጠው መንገድ በ5 ዓመት እናደርጋለን " ብለዋል።
" ምርጫ ሲደረግ ያሉ ሀሳቦች ለህዝብ ቀርበው እኛ ህዝቡ በሚፈልገው ልክ ካላገለገልንና ካልጠቀምን ህዝቡ በምርጫው ሲቀጣን እጅ ስመን፣ ባንስምም እጅ ነስተን እናስረክባለን ፤ እስከዛ መታገስ ጥሩ ነው ፤ ፍርዱን ለህዝብ እንተወው " ሲሉ መልሰዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሀገሪቱ ከገባችበት ቀውስ ጋር በተያያዘ ስልጣናቸውን እንዲለቁ በአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) ህዝብ በመረጣቸው የምክር ቤት አባላት ሲጠየቁ የዛሬው ሁለተኛ ነው።
የምክር ቤት አባሉ አቶ ክርስቲያን ታደለ ከወራት በፊት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ስልጣን በመልቀቅ " ላለው ችግር የመፍትሄው አካል ለመሆን አላሰቡም ወይ ? በሰብዓዊነት ላይ በተፈፀሙ እንዲሁም በማንነት ተኮር የዘር ማጥፋት ፣ የዘር ማፅዳት እና የማንነት ማሳሳት ወንጀሎች ተጠያቂ ለመሆን ምን ያህል ዝግጁ ኖት ? " የሚል ጥያቄ አቅርበው የነበረ።
በወቅቱ ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ፤ ኃላፊነት መውሰድ ካለብን በጋራ ቢሆን መልካም ስለሆነ " ስልጣን ብንለቅ " ነው የሚባለው ምክንያቱም መንግስት ማለት አስፈፃሚ ብቻ አይደለም የሚል ምላሽ ሰጥተዋቸው ነበር።
የዶ/ር ደሳለኝ ጫኔ ንግግር : https://t.iss.one/tikvahethiopia/79527
#TikvahEthiopia
@tikvahethiopia
የኤሌክትሪክ ፍጆታ ክፍያዎን በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሞባይል ባንኪንግ አገልግሎት እና በሲቢኢ ብር ባሉበት፣ በየትኛውም ሰዓት፣ በማንኛውም የስልክ አይነት መቾትዎ እንደተጠበቀ
በቀላሉ ይክፈሉ!
አሊያም በአቅራቢያዎ ወደሚገኝ የሲቢኢ ብር ወኪል ዘንድ በመሄድ መክፈል ይችላሉ፡፡
******
የሞባይል ባንኪንግ አገልግሎት ተጠቃሚ ካልሆኑ አቅራቢያዎ ወደሚገኝ የባንኩ ቅርንጫፍ በመቅረብ የአገልግሎቱ ተጠቃሚ መሆን የሚችሉ ሲሆን፣ የሲቢኢ ብር አገልግሎት መጠቀም ካልጀመሩ ደግሞ
• ወደ *847# በመደወል፣ ወይም
• የሲቢኢ ብር መተግበሪያን ከ Play Store ወይም App Store በማውረድ ተመዝግበው የአገልግሎቱ ተጠቃሚ መሆን ይችላሉ፡፡
ለበለጠ መረጃ ወደ 951 ነጻ የጥሪ ማዕከል ይደውሉ።
የሲቢኢ ብር መተግበሪን ለማውረድ የሚከተሉትን ማስፈንጠሪያዎች ይጠቀሙ፡
• ለአንድሮይድ ስልኮች፡
https://play.google.com/store/apps/details?id=prod.cbe.birr
• ለአፕል ስልኮች፡
https://apps.apple.com/us/app/cbebirr/id1600841787
በቀላሉ ይክፈሉ!
አሊያም በአቅራቢያዎ ወደሚገኝ የሲቢኢ ብር ወኪል ዘንድ በመሄድ መክፈል ይችላሉ፡፡
******
የሞባይል ባንኪንግ አገልግሎት ተጠቃሚ ካልሆኑ አቅራቢያዎ ወደሚገኝ የባንኩ ቅርንጫፍ በመቅረብ የአገልግሎቱ ተጠቃሚ መሆን የሚችሉ ሲሆን፣ የሲቢኢ ብር አገልግሎት መጠቀም ካልጀመሩ ደግሞ
• ወደ *847# በመደወል፣ ወይም
• የሲቢኢ ብር መተግበሪያን ከ Play Store ወይም App Store በማውረድ ተመዝግበው የአገልግሎቱ ተጠቃሚ መሆን ይችላሉ፡፡
ለበለጠ መረጃ ወደ 951 ነጻ የጥሪ ማዕከል ይደውሉ።
የሲቢኢ ብር መተግበሪን ለማውረድ የሚከተሉትን ማስፈንጠሪያዎች ይጠቀሙ፡
• ለአንድሮይድ ስልኮች፡
https://play.google.com/store/apps/details?id=prod.cbe.birr
• ለአፕል ስልኮች፡
https://apps.apple.com/us/app/cbebirr/id1600841787
#PropertyTax
ኢትዮጵያ ውስጥ " ፕሮፐርቲ ታክስ " እስካሁን እንዳልተጀመረ ነገር ግን ተግባራዊ እንደሚደረግ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ዛሬ ይፋ አደረጉ።
ዶ/ር ዐቢይ ፤ ፕሮፐርቲ ታክስ መላው ኢትዮጵያ ውስጥ በአዲስ አበባ ጨምሮ እንዳልተጀመረ ገልጸው በአ/አ እየተከናወነ ያለው ከዚህ ቀደም የነበረውን የጣሪያ እና ግርግዳ ግብር ህግ በማሻሻል እየተሰበሰበ ያለ ግብር ነው ሲሉ ጠቁመዋል።
" ይህ የተሻሻለው የጣሪያ እና የግድግዳ ግብር ማለት ፕሮፐርቲ ታክስ ማለት አይደለም " ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ " ወደፊት የፕሮፐርቲ ታክስ አዋጅ በዝርዝር የሚታይ ጉዳይ ነው ብለዋል።
" ፕሮፐርቲ ታክስ " ካቢኔው አፅድቆ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ቀርቦ አዋጁ ፀድቆ ተግባራዊ እንደሚደረግም ጠቁመዋል።
ከጣሪያና ግድግዳ ግብር ጋር በተያያዘ ያለው የታክስ ምንጭ በአዲስ አበባ ነዋሪዎች ላይ ጉዳት አምጥቶ ያልተገባ ሀብት ወስዶ ከሆነ ቅሬታ የሚሰማበት ስርአት ስላለ በዚያው ስርአት ቅሬታ ቀርቦ ሊታይ እንደሚችልም አስገንዝበዋል።
በአዲስ አበባ እየተሰበሰበ ያለው የጣራ እና የግድግዳ ግብር መሆኑንና ይህም ከ1937ዓ.ም ጀምሮ የመጣ እና ማሻሻያ የተደረገበት ነው ብለዋል፡፡
#ኤፍቢሲ
@tikvahethiopia
ኢትዮጵያ ውስጥ " ፕሮፐርቲ ታክስ " እስካሁን እንዳልተጀመረ ነገር ግን ተግባራዊ እንደሚደረግ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ዛሬ ይፋ አደረጉ።
ዶ/ር ዐቢይ ፤ ፕሮፐርቲ ታክስ መላው ኢትዮጵያ ውስጥ በአዲስ አበባ ጨምሮ እንዳልተጀመረ ገልጸው በአ/አ እየተከናወነ ያለው ከዚህ ቀደም የነበረውን የጣሪያ እና ግርግዳ ግብር ህግ በማሻሻል እየተሰበሰበ ያለ ግብር ነው ሲሉ ጠቁመዋል።
" ይህ የተሻሻለው የጣሪያ እና የግድግዳ ግብር ማለት ፕሮፐርቲ ታክስ ማለት አይደለም " ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ " ወደፊት የፕሮፐርቲ ታክስ አዋጅ በዝርዝር የሚታይ ጉዳይ ነው ብለዋል።
" ፕሮፐርቲ ታክስ " ካቢኔው አፅድቆ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ቀርቦ አዋጁ ፀድቆ ተግባራዊ እንደሚደረግም ጠቁመዋል።
ከጣሪያና ግድግዳ ግብር ጋር በተያያዘ ያለው የታክስ ምንጭ በአዲስ አበባ ነዋሪዎች ላይ ጉዳት አምጥቶ ያልተገባ ሀብት ወስዶ ከሆነ ቅሬታ የሚሰማበት ስርአት ስላለ በዚያው ስርአት ቅሬታ ቀርቦ ሊታይ እንደሚችልም አስገንዝበዋል።
በአዲስ አበባ እየተሰበሰበ ያለው የጣራ እና የግድግዳ ግብር መሆኑንና ይህም ከ1937ዓ.ም ጀምሮ የመጣ እና ማሻሻያ የተደረገበት ነው ብለዋል፡፡
#ኤፍቢሲ
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
" ቅዱስ ፓትርያርኩ የተመረጡትን አባቶችን አልሾምም አላሉም ፤ ወደ ትግራይም በተያዘው መርሀግብር ይጓዛሉ " - ቤተክርስቲያኗ
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ፤ በአንዳንድ ማኅበራዊ ሚዲያዎች ላይ " ቅዱስ ፓትርያርኩ በቅዱስ ሲኖዶስ የተመረጡትን መነኮሳት አልሾምም ፤ ወደ ትግራይም አልሔድም " ብለዋል ተብሎ እየተሰራጨ ያለው ዜና ፍጹም ሐሰት ነው አለች።
ቤተክርስቲያኗ ቅዱስ ፓትርያርኩ " የተመረጡትን አባቶችንም አልሾምም አላሉም። በተያዘው መርሐ ግብር መሠረትም ወደ ትግራይ ይጓዛሉ " ስትል አሳውቃላች።
ቤተክርስቲያንኗ " እንዲህ ዓይነቱ ሆን ተብሎ የሚሰራጭ የሐሰት ዘገባ ፤ #የእርቅ ሂደቱን የማደናቀፍ እና የቅዱስ ፓትርያርኩንስም በሐስት የማጠልሽት የተለመደና ቀጣይ የሐሰተኞችና ስም አጥፊዎች ዘመቻ አካል ነው " ያለች ሲሆን " ይህን አይነቱን የሐሰትና የፈጠራ ወሬ በቅድስት እርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተክርስቲያናችን ላይ የሚነዙ አካላትም ከዚህ ደርጊታቸው እንዲታቀቡ በጥብቅ እናሳስባለን " ብላለች።
@tikvahethiopia
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ፤ በአንዳንድ ማኅበራዊ ሚዲያዎች ላይ " ቅዱስ ፓትርያርኩ በቅዱስ ሲኖዶስ የተመረጡትን መነኮሳት አልሾምም ፤ ወደ ትግራይም አልሔድም " ብለዋል ተብሎ እየተሰራጨ ያለው ዜና ፍጹም ሐሰት ነው አለች።
ቤተክርስቲያኗ ቅዱስ ፓትርያርኩ " የተመረጡትን አባቶችንም አልሾምም አላሉም። በተያዘው መርሐ ግብር መሠረትም ወደ ትግራይ ይጓዛሉ " ስትል አሳውቃላች።
ቤተክርስቲያንኗ " እንዲህ ዓይነቱ ሆን ተብሎ የሚሰራጭ የሐሰት ዘገባ ፤ #የእርቅ ሂደቱን የማደናቀፍ እና የቅዱስ ፓትርያርኩንስም በሐስት የማጠልሽት የተለመደና ቀጣይ የሐሰተኞችና ስም አጥፊዎች ዘመቻ አካል ነው " ያለች ሲሆን " ይህን አይነቱን የሐሰትና የፈጠራ ወሬ በቅድስት እርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተክርስቲያናችን ላይ የሚነዙ አካላትም ከዚህ ደርጊታቸው እንዲታቀቡ በጥብቅ እናሳስባለን " ብላለች።
@tikvahethiopia
" የትኛው ፖሊስ ጋር ነው ያመለከቱት ? ፌክ ኒውስ በጣም በብዛት እያሰራጩ ነው " - የፌዴራል ፖሊስ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ጄይላን አብዲ
በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች በታጣቂዎች እገታዎች ተፈፅመው በሚሊዮን የሚቆጠር ገንዘብ እንደሚጠየቅ በተደጋጋሚ መገለፁ ይታወቃል።
በቅርቡ አንድ ሰዓሊ ከጓደኛው ጋር ሶደሬ አካባቢ ከታገተ በኃላ ቤተሰቦቹ ጋር ተደውሎ ገንዘብ ከተጠየቁ በኃላ ለመነጋገር ድጋሚ ሲደውሉ " በእሱ ጉዳይ አትደውሉልን አፈር አልብሰነዋል " የሚል መርዶ ተነግሯቸው ሀዘን ላይ እንደነበሩ ፤ ጓደኛው ግን 500 ሺህ ብር ከፍሎ ከእገታ መውጣቱን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ማሳወቁ ይታወሳል።
ከዚህ ክስተት በፊትም የሰዴን ሶዶ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ በቀለ ቃቻ ፤ ከመኖሪያ ቤታቸው በታጣቂዎች ታፍነው ከተወሰዱ ከሁለት ቀን በኃላ ተገድለው መገኘታቸውን መግለፃችን ይታወሳል።
እኚህን ባለስልጣን ያገቷቸው ታጣቂዎች 10 ሚሊዮን ብር መጠየቃቸው መነገሩም አይዘነጋም።
ወደ ጎጃም መስመር " ዓሊዶሮ " ላይም 30 ሹፌሮች እና ረዳቶች በታጣቂዎች መታገታቸውን ቤተሰቦቻቸው መግለፃቸው ፤ ከታገቱት ውስጥም 500 ሺህ እና 1 ሚሊዮን ብር ቤተሰቦቻቸው ከፍለው የተለቀቁ ስለመኖራቸው መግለፃችን የቅርብ ጊዜ ትውስታ ነው።
እንደውም ከቀናት በፊት ልጃቸውን ከእገታ ለማስለቀቅ 1 ሚሊዮን ብር የከፈሉ አሳዛኝ መምህር ታሪክ መሰራጨቱ ይታወሳል።
ወራትን ወደኃላ ብንጓዝ በርካቶች እየታገቱ ገንዘብ ተጠይቆባቸው ለአጋቾች ተከፍሎ ተለቀዋል ፤ በርካታ ሚዲያ ላይ ያልቀረቡ መሰል ክስተቶች አሉ።
ከታጋች ቤተሰቦች እንደሚሰማው ጉዳዩን ወደ ፖሊስ ቢወስዱት አጋቾች የያዙትን ሰው ህይወት ያጠፋሉ የሚል ስጋት አለ ፤ ከዛ ውጭ ግን ጉዳዩን ሀገር ያወቀው ፀሀይ የሞቀው ጉዳይ ነው።
ዛሬ በነበረው የፓርላማ ውሎም የምክር ቤት አባላት የእገታ ጉዳይን አንስተው አሳሳቢነቱን ገልጸዋል። ለጠ/ሚኒስትሩም ጥያቄ አቅርበዋል።
ይህንን የእገታ ጉዳይ በተመለከተ ዶቼ ቨለ ሬድዮ አንድ አጭር ዘገባ አሰራጭቶ የተመለከትን ሲሆን በዚሁ ዘገባ ላይ የነዋሪዎች / አሽከርካሪዎች እና የፌዴራል ፖሊስ ቃል ይገኝበታል።
አንድ ቃላቸውን የሰጡ አሽከርካሪ ፤ ጅቡቲ ኮሪደር ላይ እስካሁን ከነበረው አሁን ላይ መሻሻል እንዳለ፤ መንግሥት ከፍተኛ ሰራዊት መድቦ ከወለንጪቲ እስከ መተሃራ በፌዴራል እና መከላከያ የሚጠበቅ ቀጠና መሆኑን ገልጸዋል። አሁን ትልቁ ችግር ያለው ከፍቼ - ጎሃ ፂዮን ያለው ቀጠና ነው ብለዋል።
አንድ የአ/አ ነዋሪ ደግሞ ከእገታ ጋር በተያያዘ 3 ዓይነት ሰዎች አሉ ፤ እራሳቸው ሳይታገቱ " ታግተናል " በሚል ለፖለቲካም ሆነ ለሌላ አላማ የሚጠቀሙ ፣ የገንዘብ ፍላጎት ኖሯቸው የሚንቀሳቀሱ አሉ እነዚህ ገንዘብ ያላቸውን ፣ ቢዝነስ ውስጥ ያሉ ሰዎችን አጥንተው የሚንቀሳቀሱ ናቸው ፤ በረሃ ላይ አሸከርካሪዎችን የሚያግቱም አሉ እነዚህም ገንዘብ ይጠይቃሉ ሲሉ አስረድተዋል።
ልጅም " ታገትኩ " ብሎ አባቱን ገንዘብ የሚያስጠይቅም አለ እውነቱን ለማወቅ አቸጋሪ ጊዜ ነው ነገሩ ሁሉ ውስብስብ ነው ሲሉ አክለዋል።
የፌዴራል ፖሊስ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ጄይላን አብዲ ግን የሚሰራጨው #ሀሰተኛ_መረጃ መሆኑን ገልጸው አሽከርካሪዎችም ሆኑ ሌሎች ከታገቱ የት ፖሊስ ጣቢያ ሄደው እንዳመለከቱ መረጃ ሊጣራ ይገባል ብለዋል።
አቶ ጄይላን ፤ " የትኛው ፖሊስ ጋር ነው ያመለከቱት ? ፌክ ኒውስ በጣም በብዛት እያሰራጩ ነው ፤ ፌዴራል ፖሊስ መንገድ ላይ እዛው አመልክተዋል ወይ ? ሆን ተብሎ ፌክኒውስ ሀገሪቱ ላይ ሰላም እንደሌለ ለማስመሰል ፤ፌክኒውስ እየተሰራጨ ነው ያለው ሰው ታግቷል ተብሎ " ሲሉ ተደምጠዋል።
@tikvahethiopia
በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች በታጣቂዎች እገታዎች ተፈፅመው በሚሊዮን የሚቆጠር ገንዘብ እንደሚጠየቅ በተደጋጋሚ መገለፁ ይታወቃል።
በቅርቡ አንድ ሰዓሊ ከጓደኛው ጋር ሶደሬ አካባቢ ከታገተ በኃላ ቤተሰቦቹ ጋር ተደውሎ ገንዘብ ከተጠየቁ በኃላ ለመነጋገር ድጋሚ ሲደውሉ " በእሱ ጉዳይ አትደውሉልን አፈር አልብሰነዋል " የሚል መርዶ ተነግሯቸው ሀዘን ላይ እንደነበሩ ፤ ጓደኛው ግን 500 ሺህ ብር ከፍሎ ከእገታ መውጣቱን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ማሳወቁ ይታወሳል።
ከዚህ ክስተት በፊትም የሰዴን ሶዶ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ በቀለ ቃቻ ፤ ከመኖሪያ ቤታቸው በታጣቂዎች ታፍነው ከተወሰዱ ከሁለት ቀን በኃላ ተገድለው መገኘታቸውን መግለፃችን ይታወሳል።
እኚህን ባለስልጣን ያገቷቸው ታጣቂዎች 10 ሚሊዮን ብር መጠየቃቸው መነገሩም አይዘነጋም።
ወደ ጎጃም መስመር " ዓሊዶሮ " ላይም 30 ሹፌሮች እና ረዳቶች በታጣቂዎች መታገታቸውን ቤተሰቦቻቸው መግለፃቸው ፤ ከታገቱት ውስጥም 500 ሺህ እና 1 ሚሊዮን ብር ቤተሰቦቻቸው ከፍለው የተለቀቁ ስለመኖራቸው መግለፃችን የቅርብ ጊዜ ትውስታ ነው።
እንደውም ከቀናት በፊት ልጃቸውን ከእገታ ለማስለቀቅ 1 ሚሊዮን ብር የከፈሉ አሳዛኝ መምህር ታሪክ መሰራጨቱ ይታወሳል።
ወራትን ወደኃላ ብንጓዝ በርካቶች እየታገቱ ገንዘብ ተጠይቆባቸው ለአጋቾች ተከፍሎ ተለቀዋል ፤ በርካታ ሚዲያ ላይ ያልቀረቡ መሰል ክስተቶች አሉ።
ከታጋች ቤተሰቦች እንደሚሰማው ጉዳዩን ወደ ፖሊስ ቢወስዱት አጋቾች የያዙትን ሰው ህይወት ያጠፋሉ የሚል ስጋት አለ ፤ ከዛ ውጭ ግን ጉዳዩን ሀገር ያወቀው ፀሀይ የሞቀው ጉዳይ ነው።
ዛሬ በነበረው የፓርላማ ውሎም የምክር ቤት አባላት የእገታ ጉዳይን አንስተው አሳሳቢነቱን ገልጸዋል። ለጠ/ሚኒስትሩም ጥያቄ አቅርበዋል።
ይህንን የእገታ ጉዳይ በተመለከተ ዶቼ ቨለ ሬድዮ አንድ አጭር ዘገባ አሰራጭቶ የተመለከትን ሲሆን በዚሁ ዘገባ ላይ የነዋሪዎች / አሽከርካሪዎች እና የፌዴራል ፖሊስ ቃል ይገኝበታል።
አንድ ቃላቸውን የሰጡ አሽከርካሪ ፤ ጅቡቲ ኮሪደር ላይ እስካሁን ከነበረው አሁን ላይ መሻሻል እንዳለ፤ መንግሥት ከፍተኛ ሰራዊት መድቦ ከወለንጪቲ እስከ መተሃራ በፌዴራል እና መከላከያ የሚጠበቅ ቀጠና መሆኑን ገልጸዋል። አሁን ትልቁ ችግር ያለው ከፍቼ - ጎሃ ፂዮን ያለው ቀጠና ነው ብለዋል።
አንድ የአ/አ ነዋሪ ደግሞ ከእገታ ጋር በተያያዘ 3 ዓይነት ሰዎች አሉ ፤ እራሳቸው ሳይታገቱ " ታግተናል " በሚል ለፖለቲካም ሆነ ለሌላ አላማ የሚጠቀሙ ፣ የገንዘብ ፍላጎት ኖሯቸው የሚንቀሳቀሱ አሉ እነዚህ ገንዘብ ያላቸውን ፣ ቢዝነስ ውስጥ ያሉ ሰዎችን አጥንተው የሚንቀሳቀሱ ናቸው ፤ በረሃ ላይ አሸከርካሪዎችን የሚያግቱም አሉ እነዚህም ገንዘብ ይጠይቃሉ ሲሉ አስረድተዋል።
ልጅም " ታገትኩ " ብሎ አባቱን ገንዘብ የሚያስጠይቅም አለ እውነቱን ለማወቅ አቸጋሪ ጊዜ ነው ነገሩ ሁሉ ውስብስብ ነው ሲሉ አክለዋል።
የፌዴራል ፖሊስ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ጄይላን አብዲ ግን የሚሰራጨው #ሀሰተኛ_መረጃ መሆኑን ገልጸው አሽከርካሪዎችም ሆኑ ሌሎች ከታገቱ የት ፖሊስ ጣቢያ ሄደው እንዳመለከቱ መረጃ ሊጣራ ይገባል ብለዋል።
አቶ ጄይላን ፤ " የትኛው ፖሊስ ጋር ነው ያመለከቱት ? ፌክ ኒውስ በጣም በብዛት እያሰራጩ ነው ፤ ፌዴራል ፖሊስ መንገድ ላይ እዛው አመልክተዋል ወይ ? ሆን ተብሎ ፌክኒውስ ሀገሪቱ ላይ ሰላም እንደሌለ ለማስመሰል ፤ፌክኒውስ እየተሰራጨ ነው ያለው ሰው ታግቷል ተብሎ " ሲሉ ተደምጠዋል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" አብዛኞቹ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ለመውጫ ፈተና በተዘጋጁ የመንግሥት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት አልተገኙም " - ባለስልጣን መ/ቤቱ የትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን ከመውጫ ፈተና ጋር በተያያዘ አስጠንቅቋል። የግል እና የመንግሥት ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ሞዴል የቅድመ ምረቃ መውጫ ፈተና ከዛሬ ሰኔ 26/2015 ዓ.ም እስከ ሰኔ 29/2015 ዓ.ም መሰጠት ተጀምሯል፡፡…
#ETA
ለግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በድጋሚ ማሳሰቢያ ተሰጣቸው።
የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎቻቸውን የመውጫ ፈተና ወደሚያስፈትኑበት የመንግሥት ከፍተኛ ትምህርት ተቋም በመሔድ አስፈላጊውን ዝግጅት እንዲያጠናቅቁ የትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን በድጋሜ አሳስቧል።
የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማቱ የሚያስፈትኗቸውን ተማሪዎች ፦
- ፎቶ፣
- የይለፍ ቃል፣
- የተጠቃሚ ሥም እና የትምህርት ቤት ህጋዊ መታወቂያ በመያዝ ወደተመደቡበት ተቋም በመሔድ አስፈላጊውን ዝግጅት ማጠናቀቅ እንዳለባቸው ባለሥልጣኑ አስታውሷል።
ባለስሥልጣን መስሪያ ቤቱ ፤ በአሁኑ ወቅት ከመንግስት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ደረሶኛል ባለው መረጃ መሰረት ከላይ የተዘረዘሩ ጉዳዮችን በማሟላት ያቀረቡ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት አነስተኛ ናቸው።
የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማቱ አላስፈላጊ ቅድመ ሁኔታዎች ባለማሟላታቸው ምክንያት ተማሪዎች ለፈተና የማይቀመጡበት ሁኔታ ሊፈጠር እንደሚችል ባለሥልጣኑ ገልጿል።
በዚህም ለሚፈጠረው ማንኛውም ችግር የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ኃላፊነት የሚወስዱ መሆኑን ባለሥልጣኑ ጠቁሟል።
(ባለሥልጣኑ ዛሬ ያወጣው ደብዳቤ ከላይ ተያይዟል።)
Via @tikvahuniversity
@tikvahethiopia
ለግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በድጋሚ ማሳሰቢያ ተሰጣቸው።
የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎቻቸውን የመውጫ ፈተና ወደሚያስፈትኑበት የመንግሥት ከፍተኛ ትምህርት ተቋም በመሔድ አስፈላጊውን ዝግጅት እንዲያጠናቅቁ የትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን በድጋሜ አሳስቧል።
የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማቱ የሚያስፈትኗቸውን ተማሪዎች ፦
- ፎቶ፣
- የይለፍ ቃል፣
- የተጠቃሚ ሥም እና የትምህርት ቤት ህጋዊ መታወቂያ በመያዝ ወደተመደቡበት ተቋም በመሔድ አስፈላጊውን ዝግጅት ማጠናቀቅ እንዳለባቸው ባለሥልጣኑ አስታውሷል።
ባለስሥልጣን መስሪያ ቤቱ ፤ በአሁኑ ወቅት ከመንግስት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ደረሶኛል ባለው መረጃ መሰረት ከላይ የተዘረዘሩ ጉዳዮችን በማሟላት ያቀረቡ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት አነስተኛ ናቸው።
የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማቱ አላስፈላጊ ቅድመ ሁኔታዎች ባለማሟላታቸው ምክንያት ተማሪዎች ለፈተና የማይቀመጡበት ሁኔታ ሊፈጠር እንደሚችል ባለሥልጣኑ ገልጿል።
በዚህም ለሚፈጠረው ማንኛውም ችግር የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ኃላፊነት የሚወስዱ መሆኑን ባለሥልጣኑ ጠቁሟል።
(ባለሥልጣኑ ዛሬ ያወጣው ደብዳቤ ከላይ ተያይዟል።)
Via @tikvahuniversity
@tikvahethiopia
ሹፌሩን እና ረዳቱን #በመግደል 100 ኩንታል ሰሊጥ የጫነን " FSR መኪና " ይዘው ከተሰወሩ ተጠርጣሪ ወንጀለኞች አንዱ በቁጥጥር ስር መዋሉን ፖሊስ ገለፀ።
እንደ ደብረወርቅ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ መረጃ ፤ ድርጊቱ የተፈጸመው በምስራቅ ጎጃም ዞን ደብረወርቅ ከተማ አስተዳደር ፤ አባጀምበር ቀበሌ ፤ " የጨረቃን ጎጥ " ነው።
ከ " ገንዳ ውሃ " ከተማ ወደ " አዲስ አበባ " አንድ መቶ ኩንታል ሰሊጥ ጭነው ሲጓዙ የነበሩ ሾፌርና ረዳቱን ማንነታቸው ያልታወቁ ሰዎች ሰኔ 28/2015 ዓ/ም ሰዓቱ በትክክል ባልታወቀበት ሁኔታ ገድለው በመጣል መኪናውን ይዘው ይሰወራሉ፡፡
የደብረወርቅ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ከአካባቢው ነዋሪዎች የደረሰውን መረጃ መሰረት በማድረግ በሰራው ክትትል ተጠርጣሪ ወንጀለኛቹ መኪናውን ወደኋላ በመመለስ በእነብሴ ሳር ምድር ወረዳ ዲቦ ከተማ ማሳደራቸው መረጃ ይደርሰዋል፡፡
ፖሊስ ተጠርጣሪ ወንጀለኞቹን ክትትል በማድረግ ላይ እያለ ሰኔ 29 ቀን 2015 ዓ/ም መኪናውን ይዘው ወደ ግንደወይን ከተማ በመመለስ ላይ ሳሉ ግንደወይን ከተማ አካባቢ ሲደርሱ በጎንቻ ሲሶ እነሴና በግንደወይን ከተማ አንዱ ተጠርጣሪ ወንጀለኛ #ከመኪናው ጋር በቁጥጥር ስር ሊውል ችሏል።
ሌሎች ተጠርጣሪ ወንጀለኞችን ለመያዝ ርብርብ እየተደረገ ነው ሲል የደብረወርቅ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ አስታወቋል።
የጎንቻ ሲሶ እነሴና ግንደወይን ከተማ ነዋሪዎች፣ የጸጥታ አካላት ላደረጉት ከፍተኛ ርብርብ ልዩ ምስጋና ቀርቦላቸዋል።
መረጃው የምስራቅ ጎጃም ፖሊስ ነው።
@tikvahethiopia
እንደ ደብረወርቅ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ መረጃ ፤ ድርጊቱ የተፈጸመው በምስራቅ ጎጃም ዞን ደብረወርቅ ከተማ አስተዳደር ፤ አባጀምበር ቀበሌ ፤ " የጨረቃን ጎጥ " ነው።
ከ " ገንዳ ውሃ " ከተማ ወደ " አዲስ አበባ " አንድ መቶ ኩንታል ሰሊጥ ጭነው ሲጓዙ የነበሩ ሾፌርና ረዳቱን ማንነታቸው ያልታወቁ ሰዎች ሰኔ 28/2015 ዓ/ም ሰዓቱ በትክክል ባልታወቀበት ሁኔታ ገድለው በመጣል መኪናውን ይዘው ይሰወራሉ፡፡
የደብረወርቅ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ከአካባቢው ነዋሪዎች የደረሰውን መረጃ መሰረት በማድረግ በሰራው ክትትል ተጠርጣሪ ወንጀለኛቹ መኪናውን ወደኋላ በመመለስ በእነብሴ ሳር ምድር ወረዳ ዲቦ ከተማ ማሳደራቸው መረጃ ይደርሰዋል፡፡
ፖሊስ ተጠርጣሪ ወንጀለኞቹን ክትትል በማድረግ ላይ እያለ ሰኔ 29 ቀን 2015 ዓ/ም መኪናውን ይዘው ወደ ግንደወይን ከተማ በመመለስ ላይ ሳሉ ግንደወይን ከተማ አካባቢ ሲደርሱ በጎንቻ ሲሶ እነሴና በግንደወይን ከተማ አንዱ ተጠርጣሪ ወንጀለኛ #ከመኪናው ጋር በቁጥጥር ስር ሊውል ችሏል።
ሌሎች ተጠርጣሪ ወንጀለኞችን ለመያዝ ርብርብ እየተደረገ ነው ሲል የደብረወርቅ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ አስታወቋል።
የጎንቻ ሲሶ እነሴና ግንደወይን ከተማ ነዋሪዎች፣ የጸጥታ አካላት ላደረጉት ከፍተኛ ርብርብ ልዩ ምስጋና ቀርቦላቸዋል።
መረጃው የምስራቅ ጎጃም ፖሊስ ነው።
@tikvahethiopia
#አቢሲንያ_ባንክ
በከተማችን አሉ በተባሉ ሬስቶራንቶች በልተው ጠጥተው እስከ 15% ድረስ ቅናሽ ያግኙ!
ለበለጠ መረጃ ድረ-ገፃችንን ይጎብኙ፡፡
https://apollo.bankofabyssinia.com/deals-discounts/
#Apollodigitalproduct #AbyssiniaDigital #Abyssiniabank #poweredbybankofabyssinia #BankofAbyssinia #የሁሉም_ምርጫ #The_Choice_For_all
በከተማችን አሉ በተባሉ ሬስቶራንቶች በልተው ጠጥተው እስከ 15% ድረስ ቅናሽ ያግኙ!
ለበለጠ መረጃ ድረ-ገፃችንን ይጎብኙ፡፡
https://apollo.bankofabyssinia.com/deals-discounts/
#Apollodigitalproduct #AbyssiniaDigital #Abyssiniabank #poweredbybankofabyssinia #BankofAbyssinia #የሁሉም_ምርጫ #The_Choice_For_all
የመውጫ ፈተና ተጀመረ።
የኢፌዴሪ ትምህርት ሚኒስቴር በሀገር አቀፍ ደረጃ ለመጀመሪያ ጊዜ ተግባራዊ ያደረገው የመጀመሪያ ዲግሪ ምሩቃን የመውጫ ፈተና በዛሬው ዕለት መሰጠት ተጀምሯል።
በመንግሥት ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ውስጥ የመንግሥት እንዲሁም የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች ፈተናቸውን በ " ኦንላይን " መውሰድ ጀምረዋል።
ዛሬ የመውጫ ፈተናቸውን መውሰድ የጀመሩት የጤና ተማሪዎች ናቸው።
በቀጣይ ሳምንት ሰኞ ደግሞ ከጤና ተማሪዎች ውጭ የሆኑ የዘንድሮ ተመራቂ ተማሪዎች የመውጫ ፈተናቸውን የሚወስዱ ይሆናል።
ፎቶ ፦ ከዩኒቨርሲቲዎች
@tikvahethiopia
የኢፌዴሪ ትምህርት ሚኒስቴር በሀገር አቀፍ ደረጃ ለመጀመሪያ ጊዜ ተግባራዊ ያደረገው የመጀመሪያ ዲግሪ ምሩቃን የመውጫ ፈተና በዛሬው ዕለት መሰጠት ተጀምሯል።
በመንግሥት ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ውስጥ የመንግሥት እንዲሁም የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች ፈተናቸውን በ " ኦንላይን " መውሰድ ጀምረዋል።
ዛሬ የመውጫ ፈተናቸውን መውሰድ የጀመሩት የጤና ተማሪዎች ናቸው።
በቀጣይ ሳምንት ሰኞ ደግሞ ከጤና ተማሪዎች ውጭ የሆኑ የዘንድሮ ተመራቂ ተማሪዎች የመውጫ ፈተናቸውን የሚወስዱ ይሆናል።
ፎቶ ፦ ከዩኒቨርሲቲዎች
@tikvahethiopia