This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
የአንድ ሰው ግድያ ፈረንሳይን በተቃውሞ እየናጣት ነው።
በፈረንሳይ ሀገር ፓሪስ አቅራቢያ ባለፈው ማክሰኞ ዕለት አንድ የ17 ዓመት ታዳጊ በፈረንሳይ ፖሊስ መገደሉን ከተትሎ ፈረንሳያውያን ከፍተኛ ተቃውሞ እያሰሙ ይገኛሉ።
ናሄል ኤም የተሰኘው ታዳጊ በቅርብ ርቀት በፖሊስ ተተኩሶበት የተገደለ ሲሆን ግድያው " የትራፊክ መብራት ጥሷል " በሚል የተፈፀመ መሆኑ ተነግሯል።
ግድያውን የፈፀመው የፖሊስ አባል ፤ ሽጉጡን የመዘዘው ሕይወቱ አደጋ ላይ እንዳለ ስለተሰማው እንደሆነ ተናግሯል።
የታዳጊውን ግድያ ተከትሎ የተቀሰቀሰው ተቃውሞ ግን ሀገሪቱን እየናጣት ነው።
የታዳጊ መኖሪያ በሆነችው የፓሪስ አካባቢ የሚገኙ ባለሥልጣናት ሥፍራውን ለቀው ከወጡ ቀናት አልፈዋል።
በርካቶች ወደ አደባባይ ወጥተው ተቃውሞ እያሰሙ ሲሆን በዚህ መሃል ዝርፊያን ጨምሮ የአመፅ ተግባራት መፈፀማቸው ተመላክቷል።
ምንም እንኳን ታዳጊውን የገደለው የፖሊስ መኮንን ክስ ቢመሰረትም አመጹ በመላው አገሪቱ ተጠናክሮ መቀጠሉ ተገልጿል።
- በሊል እና ማርሴ ከተሞች በርካታ ሰልፍ የወጡ ሰዎች ለእሥር በቅተዋል።
- ናንቴር በተሰኘችው ታዳጊው በሚኖርባት ከተማ አንድ ባንክ ያለበት ሕንፃ በእሳት ተቃጥሏል።
- በማህበራዊ ሚዲያ በርካታ ሥፍራዎች በእሣት እየጋዩ ታይተዋል።
- በፓሪስና በሌሎች ከተማዎች የአውቶቡስና ባቡር ትራንስፖርት በሃገሪቱ ሰዓት አቆጣጠር ከምሽት 3 ሰዓት ጀምሮ ተቋርጧል።
- አንዳንድ ከተሞች ሰዎች ምሽት እንዳንይንቀሳቀሱ የሰዓት እላፊ ገደብ ጥለዋል።
- የፈረንሳይ መንግሥት አመፁን ለመግታት 40 ሺህ የፖሊስ ሠራዊት በሃገሪቱ አሰማርቷል።
- ማክሰኞ እና ረቡዕ ምሽት በነበሩ ተቃውሞዎች በርካታ ተሽከርካሪዎችና ሕንፃዎች በእሳት ጋይተዋል።
- የሟች እናት ሐሙስ ዕለት የጠሩት ሰልፍ በርካታ ግጭቶችን አስከትሏል።
ማን ምን አለ ?
የፈረንሳይ የሃገር ውስጥ ሚኒስትሩ ዤራልድ ዳርማኒን ፥ " ረቡዕ ማታ 170 የፖሊስ መኮንኖች ጉዳት እንደደረሰባቸውና 180 ሰዎች በቁጥጥር ውለዋል። " ብለዋል።
የፈረንሳይ ጠ/ሚ ኤሊሳቤት ቦርን ፤ " በ17 ዓመቱ ታዳጊ ሞት የተነሳ የተፈጠረውን ስሜታዊነት እንረዳለን። " ያሉ ሲሆን " ግን ምንም ነገር ለአመፅ ምክንያት ሊሆን አይችልም። " ሲሉ ተናግረዋል።
የታጊው ናሄል ጠበቃ ያሲን ቦዝሩ በበኩላቸው ፤ " ሃገራችን የምትከተለው ሕግ የፖሊስ መኮንኖች የሚጠብቅ ነው። ይህ ደግሞ ያለመከሰስ ባሕልን ያዳብራል። " ሲሉ ተችተዋል።
ታዳጊውን የገደለው ፖሊስ ሽጉጡን የመዘዘው ሕይወቱ አደጋ ላይ እንዳለ ስለተሰማው እንደሆነ የተናገረ ሲሆን ጠበቃዎቹ ደንበኛቸው ድርጊቱን የፈፀመው " ሕጉን በተከተለ መንገድ ነው " ብለዋል።
#Video ከላይ የተያያዙት ቪድዮዎች የታዳጊውን ግድያ እሱን ተከትሎ በፈረንሳይ የተቀጣጠለውን ተቃውሞና አመፅ የሚያሳዩ ናቸው። (ከተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያዎች የተገኙ)
Credit : BBC
@tikvahethiopia
በፈረንሳይ ሀገር ፓሪስ አቅራቢያ ባለፈው ማክሰኞ ዕለት አንድ የ17 ዓመት ታዳጊ በፈረንሳይ ፖሊስ መገደሉን ከተትሎ ፈረንሳያውያን ከፍተኛ ተቃውሞ እያሰሙ ይገኛሉ።
ናሄል ኤም የተሰኘው ታዳጊ በቅርብ ርቀት በፖሊስ ተተኩሶበት የተገደለ ሲሆን ግድያው " የትራፊክ መብራት ጥሷል " በሚል የተፈፀመ መሆኑ ተነግሯል።
ግድያውን የፈፀመው የፖሊስ አባል ፤ ሽጉጡን የመዘዘው ሕይወቱ አደጋ ላይ እንዳለ ስለተሰማው እንደሆነ ተናግሯል።
የታዳጊውን ግድያ ተከትሎ የተቀሰቀሰው ተቃውሞ ግን ሀገሪቱን እየናጣት ነው።
የታዳጊ መኖሪያ በሆነችው የፓሪስ አካባቢ የሚገኙ ባለሥልጣናት ሥፍራውን ለቀው ከወጡ ቀናት አልፈዋል።
በርካቶች ወደ አደባባይ ወጥተው ተቃውሞ እያሰሙ ሲሆን በዚህ መሃል ዝርፊያን ጨምሮ የአመፅ ተግባራት መፈፀማቸው ተመላክቷል።
ምንም እንኳን ታዳጊውን የገደለው የፖሊስ መኮንን ክስ ቢመሰረትም አመጹ በመላው አገሪቱ ተጠናክሮ መቀጠሉ ተገልጿል።
- በሊል እና ማርሴ ከተሞች በርካታ ሰልፍ የወጡ ሰዎች ለእሥር በቅተዋል።
- ናንቴር በተሰኘችው ታዳጊው በሚኖርባት ከተማ አንድ ባንክ ያለበት ሕንፃ በእሳት ተቃጥሏል።
- በማህበራዊ ሚዲያ በርካታ ሥፍራዎች በእሣት እየጋዩ ታይተዋል።
- በፓሪስና በሌሎች ከተማዎች የአውቶቡስና ባቡር ትራንስፖርት በሃገሪቱ ሰዓት አቆጣጠር ከምሽት 3 ሰዓት ጀምሮ ተቋርጧል።
- አንዳንድ ከተሞች ሰዎች ምሽት እንዳንይንቀሳቀሱ የሰዓት እላፊ ገደብ ጥለዋል።
- የፈረንሳይ መንግሥት አመፁን ለመግታት 40 ሺህ የፖሊስ ሠራዊት በሃገሪቱ አሰማርቷል።
- ማክሰኞ እና ረቡዕ ምሽት በነበሩ ተቃውሞዎች በርካታ ተሽከርካሪዎችና ሕንፃዎች በእሳት ጋይተዋል።
- የሟች እናት ሐሙስ ዕለት የጠሩት ሰልፍ በርካታ ግጭቶችን አስከትሏል።
ማን ምን አለ ?
የፈረንሳይ የሃገር ውስጥ ሚኒስትሩ ዤራልድ ዳርማኒን ፥ " ረቡዕ ማታ 170 የፖሊስ መኮንኖች ጉዳት እንደደረሰባቸውና 180 ሰዎች በቁጥጥር ውለዋል። " ብለዋል።
የፈረንሳይ ጠ/ሚ ኤሊሳቤት ቦርን ፤ " በ17 ዓመቱ ታዳጊ ሞት የተነሳ የተፈጠረውን ስሜታዊነት እንረዳለን። " ያሉ ሲሆን " ግን ምንም ነገር ለአመፅ ምክንያት ሊሆን አይችልም። " ሲሉ ተናግረዋል።
የታጊው ናሄል ጠበቃ ያሲን ቦዝሩ በበኩላቸው ፤ " ሃገራችን የምትከተለው ሕግ የፖሊስ መኮንኖች የሚጠብቅ ነው። ይህ ደግሞ ያለመከሰስ ባሕልን ያዳብራል። " ሲሉ ተችተዋል።
ታዳጊውን የገደለው ፖሊስ ሽጉጡን የመዘዘው ሕይወቱ አደጋ ላይ እንዳለ ስለተሰማው እንደሆነ የተናገረ ሲሆን ጠበቃዎቹ ደንበኛቸው ድርጊቱን የፈፀመው " ሕጉን በተከተለ መንገድ ነው " ብለዋል።
#Video ከላይ የተያያዙት ቪድዮዎች የታዳጊውን ግድያ እሱን ተከትሎ በፈረንሳይ የተቀጣጠለውን ተቃውሞና አመፅ የሚያሳዩ ናቸው። (ከተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያዎች የተገኙ)
Credit : BBC
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
የአንድ ሰው ግድያ ፈረንሳይን በተቃውሞ እየናጣት ነው። በፈረንሳይ ሀገር ፓሪስ አቅራቢያ ባለፈው ማክሰኞ ዕለት አንድ የ17 ዓመት ታዳጊ በፈረንሳይ ፖሊስ መገደሉን ከተትሎ ፈረንሳያውያን ከፍተኛ ተቃውሞ እያሰሙ ይገኛሉ። ናሄል ኤም የተሰኘው ታዳጊ በቅርብ ርቀት በፖሊስ ተተኩሶበት የተገደለ ሲሆን ግድያው " የትራፊክ መብራት ጥሷል " በሚል የተፈፀመ መሆኑ ተነግሯል። ግድያውን የፈፀመው የፖሊስ አባል ፤…
#France
በአንድ የፖሊስ አባል በተገደለ አንድ የ17 ዓመት ታዳጊ ሀገራቸው በከፍተኛ ተቃውሞና አመፅ ውስጥ የምትገኘው የፈረሳይ ፕሬዝደንት ኢማኑኤል ማክሮን የውጭ ሀገር ስብሰባቸውን አቋርጠው ወደ ሀገራቸው ተመልሰዋል።
ፕሬዜዳንቱ በብራስልስ የአውሮፓ ህብረት ጉባኤ እየታደሙ የነበረ ሲሆን በታዳጊው ግድያ ሀገሪቱ በተቃውሞ መናጧን ተከትሎ ስብሰባቸውን ጥለው ወደ ሀገራቸው ተመልሰዋል።
ወደ ሀገራቸው ከተመለሱ በኃላ ከባለሥልጣኖቻቸው ጋር አስቸኳይ ስብሰባ ተቀምጠው የተለያዩ ውሳኔዎችን አሳልፈዋል።
ካሳለፏቸው ውሳኔዎች መካከልም ፤ አንዳንድ የሚከናወኑ ዝግጅቶች እንዲሰረዙ፣ በማህበራዊ ሚዲያ ለዘረፋ የሚጠሩ ጥሪዎች ላይ ክትትል እንዲደርግ የሚሉት ይገኙበታል።
በተጨማሪ ፕሬዝዳንቱ ተቃውሞውን ለመቆጣጠር አሁን ከተሰማሩት 40 ሺህ የፀጥታ አካላት ተጨማሪ እንደሚሰማሩ አሳውቀዋል። ወላጆች ልጆቸውን ከጎዳና ላይ አመፅ እንዲጠብቁ አሳስበዋል።
ፕሬዜዳንት ማክሮን ፤ " በአንዳንድ ሰፈሮች የአንድ ጎረምሳ ሞት ተቀባይነት በሌለው መልኩ ለሌላ ነገር ውሏል " ሲሉ መናገራቸውን ኤኤፍፒ ዘግቧል።
በፈረንሳይ የአንድ የ17 ዓመት ታዳጊ በፖሊስ አባል መገደሉን ተከትሎ ለተከታታይ ቀናት በሀገሪቱ ብርቱ ተቃድሞ እና አመፅ እየተካሄደ ይገኛል። በተከሰተው አመፅ በተለያዩ ከተሞች በርካታ ተሽከርካሪዎች ጋይተዋል፣ ህንፃዎች ተቃጥለዋል፣ በፖሊስ እና በተቃውሞ አራማጆች ማካከል ግጭት ተፈጥሮ ሰዎች ተጎድተዋል፤ በርካቶችም ታስረዋል።
@tikvahethiopia
በአንድ የፖሊስ አባል በተገደለ አንድ የ17 ዓመት ታዳጊ ሀገራቸው በከፍተኛ ተቃውሞና አመፅ ውስጥ የምትገኘው የፈረሳይ ፕሬዝደንት ኢማኑኤል ማክሮን የውጭ ሀገር ስብሰባቸውን አቋርጠው ወደ ሀገራቸው ተመልሰዋል።
ፕሬዜዳንቱ በብራስልስ የአውሮፓ ህብረት ጉባኤ እየታደሙ የነበረ ሲሆን በታዳጊው ግድያ ሀገሪቱ በተቃውሞ መናጧን ተከትሎ ስብሰባቸውን ጥለው ወደ ሀገራቸው ተመልሰዋል።
ወደ ሀገራቸው ከተመለሱ በኃላ ከባለሥልጣኖቻቸው ጋር አስቸኳይ ስብሰባ ተቀምጠው የተለያዩ ውሳኔዎችን አሳልፈዋል።
ካሳለፏቸው ውሳኔዎች መካከልም ፤ አንዳንድ የሚከናወኑ ዝግጅቶች እንዲሰረዙ፣ በማህበራዊ ሚዲያ ለዘረፋ የሚጠሩ ጥሪዎች ላይ ክትትል እንዲደርግ የሚሉት ይገኙበታል።
በተጨማሪ ፕሬዝዳንቱ ተቃውሞውን ለመቆጣጠር አሁን ከተሰማሩት 40 ሺህ የፀጥታ አካላት ተጨማሪ እንደሚሰማሩ አሳውቀዋል። ወላጆች ልጆቸውን ከጎዳና ላይ አመፅ እንዲጠብቁ አሳስበዋል።
ፕሬዜዳንት ማክሮን ፤ " በአንዳንድ ሰፈሮች የአንድ ጎረምሳ ሞት ተቀባይነት በሌለው መልኩ ለሌላ ነገር ውሏል " ሲሉ መናገራቸውን ኤኤፍፒ ዘግቧል።
በፈረንሳይ የአንድ የ17 ዓመት ታዳጊ በፖሊስ አባል መገደሉን ተከትሎ ለተከታታይ ቀናት በሀገሪቱ ብርቱ ተቃድሞ እና አመፅ እየተካሄደ ይገኛል። በተከሰተው አመፅ በተለያዩ ከተሞች በርካታ ተሽከርካሪዎች ጋይተዋል፣ ህንፃዎች ተቃጥለዋል፣ በፖሊስ እና በተቃውሞ አራማጆች ማካከል ግጭት ተፈጥሮ ሰዎች ተጎድተዋል፤ በርካቶችም ታስረዋል።
@tikvahethiopia
#ተጠንቀቁ
UNICEF 2,800 ሰራተኞችን ለመቅጠር የቅጥር ማስታወቂያ አውጥቷል ?
UNICEF ማህበራዊ ሚዲያ ላይ የሚዘዋወረውን አይነት ምንም የቅጥር ማስታወቂያ #አላወጣም።
በማህበራዊ ሚዲያ ላይ የምትመለከቱት አይነት ሀሰተኛ የቅጥር ማስታወቂያ በስፋት እየተዘዋወረ ነው።
ማስታቂያው UNICEF በትግራይ፣ ሶማሌ፣ አፋር፣ ኦሮሚያ ፣ ቤኒሻንጉል ጉምዝ ክልል ለሚገኙ ዜጎች በ3 የስራ መደቦች የተመዘገቡ ሰራተኞችን አሰልጥኖ ለመቅጠር ይፈልጋል የሚል ነው።
በዚሁ ሀሰተኛ የቅጥር ጥሪ ፤ በባችለር ዲግሪ ፣ በማንኛውም ትምህርት መስክ ፣ በ0 ዓመት ፣ በ24,700 ብር ደመወዝ 2,800 ሰራተኞች እንደሚፈለጉ ይገልጻል።
በጣም የሚያስገርመው የስራው አመልካቾች የሚያመለክቱበት ሀሰተኛ አድራሻ የተቀመጠ ሲሆን በዚሁ አድራሻ ተመዝጋቢዎች የማመልከቻ ፎርም ሲሞሉ 1,000 ብር በCBE Birr ወይም በTelebirr ቀድመው እንዲከፍሉ ይጠይቃል።
ውድ ቤተሰቦቻችን ይህ ፍፁም ሀሰተኛ እንዲሁም በርካታ ወጣቶችን ለማጭበርበር እየተደረገ ያለ እንቅስቃሴ በመሆኑ ከፍተኛ ጥንቃቄ አድርጉ።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከUNICEF ተጨማሪ መረጃ ያገኘ ሲሆን በኦንላይን እየተሰራጨ ያለው ሀሰተኛ የቅጥር ማስታወቂያ መሆኑን ገልጿል።
UNICEF የስራ ዕድል የሚያስተዋውቀው በይፋዊ ድረገፁ unicef.org/careers/ ላይ ብቻ መሆኑን አስገንዝቧል። ከዚህም ባለፈ በየትኛውም የቅጥር ሂደት ገንዘብ እንደማያስከፍል እንዲሁም የባንክ መረጃን እንደማይጠይቅ አሳውቋል።
@tikvahethiopia
UNICEF 2,800 ሰራተኞችን ለመቅጠር የቅጥር ማስታወቂያ አውጥቷል ?
UNICEF ማህበራዊ ሚዲያ ላይ የሚዘዋወረውን አይነት ምንም የቅጥር ማስታወቂያ #አላወጣም።
በማህበራዊ ሚዲያ ላይ የምትመለከቱት አይነት ሀሰተኛ የቅጥር ማስታወቂያ በስፋት እየተዘዋወረ ነው።
ማስታቂያው UNICEF በትግራይ፣ ሶማሌ፣ አፋር፣ ኦሮሚያ ፣ ቤኒሻንጉል ጉምዝ ክልል ለሚገኙ ዜጎች በ3 የስራ መደቦች የተመዘገቡ ሰራተኞችን አሰልጥኖ ለመቅጠር ይፈልጋል የሚል ነው።
በዚሁ ሀሰተኛ የቅጥር ጥሪ ፤ በባችለር ዲግሪ ፣ በማንኛውም ትምህርት መስክ ፣ በ0 ዓመት ፣ በ24,700 ብር ደመወዝ 2,800 ሰራተኞች እንደሚፈለጉ ይገልጻል።
በጣም የሚያስገርመው የስራው አመልካቾች የሚያመለክቱበት ሀሰተኛ አድራሻ የተቀመጠ ሲሆን በዚሁ አድራሻ ተመዝጋቢዎች የማመልከቻ ፎርም ሲሞሉ 1,000 ብር በCBE Birr ወይም በTelebirr ቀድመው እንዲከፍሉ ይጠይቃል።
ውድ ቤተሰቦቻችን ይህ ፍፁም ሀሰተኛ እንዲሁም በርካታ ወጣቶችን ለማጭበርበር እየተደረገ ያለ እንቅስቃሴ በመሆኑ ከፍተኛ ጥንቃቄ አድርጉ።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከUNICEF ተጨማሪ መረጃ ያገኘ ሲሆን በኦንላይን እየተሰራጨ ያለው ሀሰተኛ የቅጥር ማስታወቂያ መሆኑን ገልጿል።
UNICEF የስራ ዕድል የሚያስተዋውቀው በይፋዊ ድረገፁ unicef.org/careers/ ላይ ብቻ መሆኑን አስገንዝቧል። ከዚህም ባለፈ በየትኛውም የቅጥር ሂደት ገንዘብ እንደማያስከፍል እንዲሁም የባንክ መረጃን እንደማይጠይቅ አሳውቋል።
@tikvahethiopia
#BirhanBank
ለማንኛውም አስተያየት፤ ጥያቄ ወይም ጥቆማ በባንካችን የደንበኞች አገልግሎት መስመር #8292 ላይ ይደውሉ!
አዳዲስ እና ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት ከታች የሚገኙትን ሊንኮች በመጫን የማህበራዊ ድህረ-ገጾቻችንን ይቀላቀሉ !
Facebook: https://www.facebook.com/berhanbanksc
Telegram: https://t.iss.one/berhanbanksc
Instagram: https://www.instagram.com/berhanbanksc/
Twitter: https://twitter.com/berhanbanksc
እንደ ስማችን ብርሃን ነው ስራችን!
ለማንኛውም አስተያየት፤ ጥያቄ ወይም ጥቆማ በባንካችን የደንበኞች አገልግሎት መስመር #8292 ላይ ይደውሉ!
አዳዲስ እና ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት ከታች የሚገኙትን ሊንኮች በመጫን የማህበራዊ ድህረ-ገጾቻችንን ይቀላቀሉ !
Facebook: https://www.facebook.com/berhanbanksc
Telegram: https://t.iss.one/berhanbanksc
Instagram: https://www.instagram.com/berhanbanksc/
Twitter: https://twitter.com/berhanbanksc
እንደ ስማችን ብርሃን ነው ስራችን!
#MoE
ሀገር አቀፉ የ " ጤና ኢግዚቢሽን " በአዲስ አበባ ፤ በብሔራዊ ሳይንስ ሙዚየም እየተካሄደ ይገኛል።
የጤና ሚኒስቴር ባዘጋጀው በዚህ ኤግዚቢሽን ላይ በጤናው ዘርፍ በሚኒስቴሩ እየተሰሩ የሚገኙ ሥራዎች በሚኒስቴሩ በኩል የቀረቡ ሲሆን ሌሎች የግል እንዲሁም የመንግስት ተቋማትም በኤግዚቢሽኑ ተገኝተዋል።
ሰኔ 14 በተከፈተውና እስከ ሐምሌ 13 በሚቆየው በዚህ ኤግዚቢሽን ለህጻናትና ለተማሪዎች የሚሆኑ ዴስኮች፤ የኢትዮጵያ ባህላዊ ህክምናን የሚያስረዱ በተለያዩ እጸዋት ላይ የተደረጉ ምርምሮች ማሳያ፤ ስለ አጠቃላይ የሆስፒታል አገልግሎት እንዲሁም የዲጂታል የጤና ሥርዓቶች ላይ ማብራሪያ እንዲሁም ጉብኝት ማድረግ ይቻላል።
በተለይ በጤናው ዘርፍ ለተሰማሩ ፤ ወደፊት በጤና ትምህርት ውስጥ ማለፍ ለሚፈልጉና በትምህርት ላይ ለሚገኙ #ተማሪዎች እንዲሁም በሚኒስቴሩ ያሉ እንቅስቃሴዎችን መረዳት ለሚፈልጉ ጎብኚዎች በኤግዚቢሽኑ ቢሳተፉ እንደሚያተርፉ የጤና ሚኒስቴር ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።
@tikvahethiopia
ሀገር አቀፉ የ " ጤና ኢግዚቢሽን " በአዲስ አበባ ፤ በብሔራዊ ሳይንስ ሙዚየም እየተካሄደ ይገኛል።
የጤና ሚኒስቴር ባዘጋጀው በዚህ ኤግዚቢሽን ላይ በጤናው ዘርፍ በሚኒስቴሩ እየተሰሩ የሚገኙ ሥራዎች በሚኒስቴሩ በኩል የቀረቡ ሲሆን ሌሎች የግል እንዲሁም የመንግስት ተቋማትም በኤግዚቢሽኑ ተገኝተዋል።
ሰኔ 14 በተከፈተውና እስከ ሐምሌ 13 በሚቆየው በዚህ ኤግዚቢሽን ለህጻናትና ለተማሪዎች የሚሆኑ ዴስኮች፤ የኢትዮጵያ ባህላዊ ህክምናን የሚያስረዱ በተለያዩ እጸዋት ላይ የተደረጉ ምርምሮች ማሳያ፤ ስለ አጠቃላይ የሆስፒታል አገልግሎት እንዲሁም የዲጂታል የጤና ሥርዓቶች ላይ ማብራሪያ እንዲሁም ጉብኝት ማድረግ ይቻላል።
በተለይ በጤናው ዘርፍ ለተሰማሩ ፤ ወደፊት በጤና ትምህርት ውስጥ ማለፍ ለሚፈልጉና በትምህርት ላይ ለሚገኙ #ተማሪዎች እንዲሁም በሚኒስቴሩ ያሉ እንቅስቃሴዎችን መረዳት ለሚፈልጉ ጎብኚዎች በኤግዚቢሽኑ ቢሳተፉ እንደሚያተርፉ የጤና ሚኒስቴር ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።
@tikvahethiopia
" ሞሳድ " ኢራን ውስጥ ገብቶ አንድን ግለሰብ ጠልፎ መወሰዱ ተሰማ።
ለመገናኛ ብዙሃን እምብዛም መረጃ የማይሰጠው የእስራኤሉ የስለላ ድርጅት "ሞሳድ" ቆጵሮስ ውስጥ እስራኤላውያንን ለመግደል አቅዷል የተባለ ቡድን መሪ ነው ተብሎ የተጠረጠረን ግለሰብ ኢራን ውስጥ ዘልቆ በመግባት ለመያዝ መቻሉን አስታውቋል።
"ሞሳድ" በእስራኤላውያን ዜጎች ላይ ቆጵሮስ ውስጥ ግድያን ሊፈጽም ስለነበረው ገዳይ ቡድን ለቆጵሮስ ባለሥልጣናት መረጃ መስጠቱን እና ጥቃት ፈጻሚ ህዋሱም እንዲበተን መደረጉን አመልክቷል።
"ሞሳድ" ባወጣው መግለጫ ላይ ተካሄደ ያለውን ተልዕኮ "በኢራን ግዛት ውስጥ የተፈጸመ ልዩ ድፍረት የተሞላበት" በማለት ገልጾታል።
አንድ ከፍተኛ የሞሳድ ከፍተኛ ባለሥልጣን፤ "በየትኛውም የዓለም ክፍል ውስጥ በሚገኙ አይሁዳውያን እና እስራኤላውያን ላይ የሽብር ጥቃትን የሚያስፈጽሙ ባለሥልጣናትን የኢራን ግዛትን ጨምሮ ባሉበት ቦታ ሁሉ እናገኛቸዋለን" ስለማለታቸው ተነግሯል።
ይህ የሞሳድ ኦፕሬሽን ለረጅም ዘመናት በጠላትነት ሲፈላለጉ በነበሩት እስራኤል እና ኢራን መካከል ያለው ተዘዋዋሪ ፍልሚያ መቀጠሉን ያመለክታል ተብሏል።
እስራኤል ቆጵሮስ ውስጥ ዜጎቿን ለመግደል በኢራን አማካይነት ተቀነባብሮ ነበር ያለችውን ሴራ ከገለልተኛ ወገን #ማረጋገጥ ያልተቻለ ሲሆን ከኢራንም ሆነ ከቆጵሮስ በኩል እስካሁን የተሰጠ ምላሽ የለም።
በ "ሞሳድ" የተያዘው ግለሰብ ምን አለ ?
በእስራኤል ባለሥልጣናት ይፋ በተደረገ ቪዲዮ ላይ ዋነኛ ተጠርጣሪ እንደሆነ የተገለጸው ዩሴፍ ሻሃባዚ የተባለ ግለሰብ ከኢራን ውጭ ለ " ሞሳድ " ወኪሎች በፋርስ ቋንቋ ሲናገር አሳይቷል።
በዚህ ቪድዮ፥ ግለሰቡ አንድ እስራኤላዊ ነጋዴን ለመግደል በቱርክ ቁጥጥር ሥር ወዳለው ሰሜን ቆጵሮስ በመግባት በሕገወጥ መንገድ ወደ ደቡቡ ክፍል መግባቱን ያስረዳል።
የግለሰቡን አድራሻና ፎቶግራፍ በኢራን አብዮታዊ ዘብ ውስጥ ያለ አዛዡ እንደላከለት ተናግሯል።
"ግለሰቡን እዚያ መኖሩን እና የት ሊሄድ እንደሆነ ካወቅኩ በኋላ ዕቅዴ እንቅስቃሴ የሌለበት እና ጸጥ ያለ ሁኔታ ሲፈጠር በጥይት መግደል ነበር" በማለት ሲናገር ይሰማል።
ግለሰቡ ኢላማው የሆነውን እስራኤላዊ ከለየ እና የመኖሪያ ቤቱን ፎቶ ካነሳ በኋላ፣ በፖሊስ እየተፈለገ መሆኑ ስለተነገረው ከቆጵሮስ በመውጣት ወደ ኢራን ተመልሷል ተብሏል።
በሞሳድ ከኢራን ተይዞ የወጣውና ግድያውን ሊፈጽም እንደነበር ሲያምን በቪዲዮ የተቀዳው ግለሰብ በአስገዳጅ ሁኔታ ውስጥ ሆኖ ቃሉን እየሰጠ ይሁን አይሁን ግልጽ አይደለም።
ግለሰቡ መቼ ተያዘ ?
"ሞሳድ" ግለሰቡን ከኢራን ግዛት ውስጥ መቼ እና ከየት ቦታ ይዞ እንዳወጣው እንዲሁም ቆጵሮስ ውስጥ ሊፈጸም የነበረው ጥቃት ለመቼ ታስቦ እንደነበር ዝርዝር መረጃ አልሰጠም።
የእስራኤል እና ኢራን ግንኙነት...
እስራኤል፤ ኢራንን ለረጅም አመታት እንደ ዋነኛ ጠላቷ አድርጋ ትቆጥራታለች።
የኢራን መንግሥት እስራኤልን ለማውደም የሚያደርገውን ተደጋጋሚ ዛቻና ጥቃት የሚፈጽሙባትን ታጣቂ ቡድኖችን ትደግፋለች በሚል ነው እንደጠላት የምታያት።
እስራኤል ኢራን የኑክሌር ጦር መሳሪያዎችን ለመገንባት እየጣረች መሆኗን ታምናለች።
በቅርብ ዓመታት እስራኤል በኢራን የኑክሌር ተቋማት ላይ ተከታታይ ጥቃቶችን የፈጸመች ሲሆን በርካታ የኢራን የኑክሌር ሳይንቲስቶችን በመግደል ትከሰሳለች።
ከ5 ዓመት በፊትም የሞሳድ ወኪሎች በኢራን ዋና ከተማ የሚገኝ የሰነዶች ማከማቻን ሰብረው በመግባት ከፍተኛ መጠን ያላቸውን የኑክሌር መረሃ ግብርን ሰነዶች መዝረፋቸውን እስራኤል አሳውቃ ነበር።
ኢራን ምን አለች ? 👉 telegra.ph/MOSAD-07-01
(BBC, NuR)
@tikvahethiopia
ለመገናኛ ብዙሃን እምብዛም መረጃ የማይሰጠው የእስራኤሉ የስለላ ድርጅት "ሞሳድ" ቆጵሮስ ውስጥ እስራኤላውያንን ለመግደል አቅዷል የተባለ ቡድን መሪ ነው ተብሎ የተጠረጠረን ግለሰብ ኢራን ውስጥ ዘልቆ በመግባት ለመያዝ መቻሉን አስታውቋል።
"ሞሳድ" በእስራኤላውያን ዜጎች ላይ ቆጵሮስ ውስጥ ግድያን ሊፈጽም ስለነበረው ገዳይ ቡድን ለቆጵሮስ ባለሥልጣናት መረጃ መስጠቱን እና ጥቃት ፈጻሚ ህዋሱም እንዲበተን መደረጉን አመልክቷል።
"ሞሳድ" ባወጣው መግለጫ ላይ ተካሄደ ያለውን ተልዕኮ "በኢራን ግዛት ውስጥ የተፈጸመ ልዩ ድፍረት የተሞላበት" በማለት ገልጾታል።
አንድ ከፍተኛ የሞሳድ ከፍተኛ ባለሥልጣን፤ "በየትኛውም የዓለም ክፍል ውስጥ በሚገኙ አይሁዳውያን እና እስራኤላውያን ላይ የሽብር ጥቃትን የሚያስፈጽሙ ባለሥልጣናትን የኢራን ግዛትን ጨምሮ ባሉበት ቦታ ሁሉ እናገኛቸዋለን" ስለማለታቸው ተነግሯል።
ይህ የሞሳድ ኦፕሬሽን ለረጅም ዘመናት በጠላትነት ሲፈላለጉ በነበሩት እስራኤል እና ኢራን መካከል ያለው ተዘዋዋሪ ፍልሚያ መቀጠሉን ያመለክታል ተብሏል።
እስራኤል ቆጵሮስ ውስጥ ዜጎቿን ለመግደል በኢራን አማካይነት ተቀነባብሮ ነበር ያለችውን ሴራ ከገለልተኛ ወገን #ማረጋገጥ ያልተቻለ ሲሆን ከኢራንም ሆነ ከቆጵሮስ በኩል እስካሁን የተሰጠ ምላሽ የለም።
በ "ሞሳድ" የተያዘው ግለሰብ ምን አለ ?
በእስራኤል ባለሥልጣናት ይፋ በተደረገ ቪዲዮ ላይ ዋነኛ ተጠርጣሪ እንደሆነ የተገለጸው ዩሴፍ ሻሃባዚ የተባለ ግለሰብ ከኢራን ውጭ ለ " ሞሳድ " ወኪሎች በፋርስ ቋንቋ ሲናገር አሳይቷል።
በዚህ ቪድዮ፥ ግለሰቡ አንድ እስራኤላዊ ነጋዴን ለመግደል በቱርክ ቁጥጥር ሥር ወዳለው ሰሜን ቆጵሮስ በመግባት በሕገወጥ መንገድ ወደ ደቡቡ ክፍል መግባቱን ያስረዳል።
የግለሰቡን አድራሻና ፎቶግራፍ በኢራን አብዮታዊ ዘብ ውስጥ ያለ አዛዡ እንደላከለት ተናግሯል።
"ግለሰቡን እዚያ መኖሩን እና የት ሊሄድ እንደሆነ ካወቅኩ በኋላ ዕቅዴ እንቅስቃሴ የሌለበት እና ጸጥ ያለ ሁኔታ ሲፈጠር በጥይት መግደል ነበር" በማለት ሲናገር ይሰማል።
ግለሰቡ ኢላማው የሆነውን እስራኤላዊ ከለየ እና የመኖሪያ ቤቱን ፎቶ ካነሳ በኋላ፣ በፖሊስ እየተፈለገ መሆኑ ስለተነገረው ከቆጵሮስ በመውጣት ወደ ኢራን ተመልሷል ተብሏል።
በሞሳድ ከኢራን ተይዞ የወጣውና ግድያውን ሊፈጽም እንደነበር ሲያምን በቪዲዮ የተቀዳው ግለሰብ በአስገዳጅ ሁኔታ ውስጥ ሆኖ ቃሉን እየሰጠ ይሁን አይሁን ግልጽ አይደለም።
ግለሰቡ መቼ ተያዘ ?
"ሞሳድ" ግለሰቡን ከኢራን ግዛት ውስጥ መቼ እና ከየት ቦታ ይዞ እንዳወጣው እንዲሁም ቆጵሮስ ውስጥ ሊፈጸም የነበረው ጥቃት ለመቼ ታስቦ እንደነበር ዝርዝር መረጃ አልሰጠም።
የእስራኤል እና ኢራን ግንኙነት...
እስራኤል፤ ኢራንን ለረጅም አመታት እንደ ዋነኛ ጠላቷ አድርጋ ትቆጥራታለች።
የኢራን መንግሥት እስራኤልን ለማውደም የሚያደርገውን ተደጋጋሚ ዛቻና ጥቃት የሚፈጽሙባትን ታጣቂ ቡድኖችን ትደግፋለች በሚል ነው እንደጠላት የምታያት።
እስራኤል ኢራን የኑክሌር ጦር መሳሪያዎችን ለመገንባት እየጣረች መሆኗን ታምናለች።
በቅርብ ዓመታት እስራኤል በኢራን የኑክሌር ተቋማት ላይ ተከታታይ ጥቃቶችን የፈጸመች ሲሆን በርካታ የኢራን የኑክሌር ሳይንቲስቶችን በመግደል ትከሰሳለች።
ከ5 ዓመት በፊትም የሞሳድ ወኪሎች በኢራን ዋና ከተማ የሚገኝ የሰነዶች ማከማቻን ሰብረው በመግባት ከፍተኛ መጠን ያላቸውን የኑክሌር መረሃ ግብርን ሰነዶች መዝረፋቸውን እስራኤል አሳውቃ ነበር።
ኢራን ምን አለች ? 👉 telegra.ph/MOSAD-07-01
(BBC, NuR)
@tikvahethiopia