#ቮልስዋገን
" ህጋዊ ፈቃድ ያለው መሆኑ እስኪረጋገጥ ድረስ በጊዜያዊነት ወደ ሀገር እንዳይገባ ታግዷል " - የትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ ሚኒስቴር
ወደ ኢትዮጵያ ከሚገቡ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች መካከል በቻይና ሀገር ተገጣጥሞ ወደ ኢትዮጲያ እየገባ የሚገኘው " ቮልስ ዋገን " የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ ህጋዊ የሆነ ፍቃድ የሌለው መሆኑን የጀርመን ኩባንያ በኢንባሲው በኩል ለትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ ሚኒስቴር በጻፈው ደብዳቤ አሳውቋል።
ይህ ቻይና ሀገር የሚመረተው የ " ቮልስ ዋገን " የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ ከኩባንያው ህጋዊ ፈቃድ ያለው መሆኑ እስኪረጋገጥ ድረስ በጊዜያዊነት ወደ ሀገር ውስጥ እንዳይገባ መታገዱን ሚኒስቴሩ ዛሬ አሳውቋል።
ምንጭ፦ የትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ ሚኒስቴር
@tikvahethiopia
" ህጋዊ ፈቃድ ያለው መሆኑ እስኪረጋገጥ ድረስ በጊዜያዊነት ወደ ሀገር እንዳይገባ ታግዷል " - የትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ ሚኒስቴር
ወደ ኢትዮጵያ ከሚገቡ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች መካከል በቻይና ሀገር ተገጣጥሞ ወደ ኢትዮጲያ እየገባ የሚገኘው " ቮልስ ዋገን " የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ ህጋዊ የሆነ ፍቃድ የሌለው መሆኑን የጀርመን ኩባንያ በኢንባሲው በኩል ለትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ ሚኒስቴር በጻፈው ደብዳቤ አሳውቋል።
ይህ ቻይና ሀገር የሚመረተው የ " ቮልስ ዋገን " የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ ከኩባንያው ህጋዊ ፈቃድ ያለው መሆኑ እስኪረጋገጥ ድረስ በጊዜያዊነት ወደ ሀገር ውስጥ እንዳይገባ መታገዱን ሚኒስቴሩ ዛሬ አሳውቋል።
ምንጭ፦ የትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ ሚኒስቴር
@tikvahethiopia
#አቢሲንያ_ባንክ
የቪዛ ካርድዎን ከአቢሲኒያ ባንክ በ72 ሰዓታት ውስጥ ይረከቡ! ልክ እንደጊዜው አገልግሎታችንም ፍጥነትን ከጥራት ያሟላ ነው!
መተግበሪያውን ለማውረድ ሊንኩን ይጠቀሙ።
https://apollo.bankofabyssinia.com/download-apollo
#Apollodigitalproduct #AbyssiniaDigital #VISA #ATMcard #poweredbybankofabyssinia #የሁሉም_ምርጫ #The_Choice_For_all
የቪዛ ካርድዎን ከአቢሲኒያ ባንክ በ72 ሰዓታት ውስጥ ይረከቡ! ልክ እንደጊዜው አገልግሎታችንም ፍጥነትን ከጥራት ያሟላ ነው!
መተግበሪያውን ለማውረድ ሊንኩን ይጠቀሙ።
https://apollo.bankofabyssinia.com/download-apollo
#Apollodigitalproduct #AbyssiniaDigital #VISA #ATMcard #poweredbybankofabyssinia #የሁሉም_ምርጫ #The_Choice_For_all
TIKVAH-ETHIOPIA
የንብረት ግብር . . . " ግብር ከፋዮች የሚከፍሉት የንብረት ግብር ተከራይን የማይመለከትና ወደ ተከራይ መተላለፍ የሌለበት መሆኑን ማወቅ አለባቸው " - የአዲስ አበባ ፋይናንስ ቢሮ ነዋሪዎች ስለ ንብረት ግብር ምን አሉ ? " የኑሮ ውድነቱ ከብዶ ባለበት ሁኔታ ግብሩ መሻሻሉ የመጨረሻ ጫናው ተከራዮች ላይ እንዳያርፍ ያደርጋል። መንግሥት ገበያውን መቆጣጣር አለበት። ግብርን መክፈል የሥልጣኔ መገለጫ…
የቤት ግብር . . .
" የከፈልኩት ክፍያ አሰራሩን የጣሰ ነው "
የአዲስ አበባ ከተማ ቦሌ ክ/ከተማ ነዋሪ የሆኑት አቶ አስቻለው ጣሰው (በብሔራዊ ቴሌቪዥን ላይ ቀርበው የተናገሩት) ፦
" የምኖረው ቦሌ ክፍለ ከተማ ነው።
በወረዳ 14 የታዘብኩትን መናገር እፈልጋለሁ።
እኔ የሚጠበቅብኝን የ ' Property Tax ' ከፍያለሁ ነገር ግን የከፈልኩት ክፍያ አሰራሩን የጣሰ ነው።
ታክስ የመክፈል የዜግነት ግዴታዬ ነው ፤ መጀመሪያ መመሪያውን አይቼ ነው ልከፍል የሄድኩት።
መመሪያው ሰርኩላር የተደረገው ሚያዚያ 7 /2015 ነው። እዚህ መመሪያ ላይ ሂሳቡ የሚሰራበት ቀመር አለ እሱን እስልቼ ነበር የሄድኩት ነገር ግን እዛ ወረዳ ላይ ያየሁት ነገር ከ1000 እስከ 1500 በላይ ምኑንም ያላመላከተ፣ ከመመሪያውም ጋር ያልተናበበ ክፍያ ሰዎች እንዲከፍሉ ይደረጋል።
ይሄ ከተመን በፊት ያለ ነው።
ለምሳሌ ፦ እኔ ካርታዬን ' ዲጅታል ' አስደርጊያለሁ ፣ ዲጂታል ሳስደርግ የመሃንዲስ 1500 ብር ከፍያለሁ ነገር ግን በዚህ ወቅት እንድከፍል የተደረገው መሃንዲስ ስሙ ተጠርቶ ብቻ 500 ብር የመሃንዲስ፣ ፋይሌ ወጥቶ ክፍያ ለምፈፅምበት 500 ፣ እንደገና ቅጣት ተብሎ 500 ፤ ቅጣት የአፈር እና የጣራ ግብር የሚባለው ከሆነ ኮንዶሚኒየሞች በዚህ ሲስተም ሲስተናገዱ አልነበረምና ኮንዶሚኒየሞች በምን ታይቶ ነው ከየካቲት አንድ ጀምሮ ሲስተሙ ቅጣት 5 % እየሰራ የሚሄደው ?
ከዚህ በፊት ተግባራዊ ያልተደረገባቸው የጋራ መኖሪያ ቤቶች / ኮንዶሚኒየም ላይ እንዴት በመኖሪያ ቤቶች አሰራር እዛ ላይ ተግባራዊ ተደረገ ? ይሄ ቅጣት ሚያዚያ ላይ በወጣ ሰርኩላር እንዴት ከየካቲት ጀምሮ ሰው ይቀጣል ?
እንደገና ለመክፈል የሄደ ሰው ፋይሉን ከፋይል አውጥቶ፣ አምጥቶ ክፍል ላለው ሰው እንዴት ፋይል ለወጣበት አገልግሎት ተብሎ 500 ብር ለምንድነው ?
ቀመር የተሰራበትን ተቀበለ አብዛኛው በዝቶብናል አስተያየት ይደረግልን ቢልም ግን አብዛኛውን ህዝብ የማተራመስ በፕሮግራም ያለመጥራት ነገር አለ።
ለምሳሌ ወደ ገርጂ ብዙ የኮንዶሚኒየም ሳይቶች አሉ ፤ እንደውም ሰው ሃሳብ ሲሰጣቸው ምናለ ሳይቶቹን በፕሮግራም አድርጋቹ ብትጠሩን ለአሰራር ለናተም ያመቻል ህዝቡም እንዳለ ከሰኞ እስከ አርብ ሲተራመስ አይውልም ምናለ ፕሮግራም አውጥታችሁ ብታስተናግዱን ? እያለ ይጠይዋል ህዝቡ።
የኔን ያለአገባብ ክፍያ ያየ ጓደኛዬ ክፍለ ከተማ ሄዶ 500 ብር ብቻ ከፈለ። ተመልከቱ ክ/ከተማውን እና ወረዳዎች በምን ደረጃ ነው የሚናበቡት ? ቦሌ እና ለሚ ኩራ የሚያስከፍሉት ይለያያል 100 ብር ከፍለን ያሉ አሉ። እዛው ወረዳ 14 እና 13 እራሱ ወረዳ 13 100 ብር ሲያስከፍል ወረዳ 14 1000 ብር ያስከፍላል ይህ አገልግሎት ለሚባለው ነው ቅጣቱን ተውትና።
ሁሉም ቦታ የአገልግሎት እያሉ ይቀበላሉ፤ ግን ወጥ አይደለም ። ለምን ጉራማይሌ ሆነ ? አንዱ ጋር መቶ ሌላው ጋር ሌላ በተለይ የመሃንዲሱ ብቻ 500 ፣ የአገልግሎት 500 እኔ ደረሰኝ ይዤ ነው ይሄንን የምናገረው።
አፈፃፀሙ ላይ ሰዎች ቅር እያላቸው ባላመኑበት ሁኔታ ላይ ተገደው የመክፈል ሁኔታ አለ። ከምንገላታ በሚልም ... አንድ ሰው በጣም ፈጠነ ከተባለ 3 ቀን ነው የሚፈጅበት እኔ 3 ቀን ከመ/ቤት አስፈቅጃለሁ ይሄንን ጉዳይ ለመፈፀም።
ልገብር ብሎ የሚሄድ ሰው ሶስት ቀን ከስራው ቀርቶ አስቡት።
እናስተካክላለን ይላሉ ፤ እሺ የከፈሉ ሰዎች ጉዳይ ምን ይደረጋል ? ሌላው የባንክ እዳ ያለባቸውና ካርታው ባንክ የሆናባቸው አሉ አሁን እነዚህ ሰዎች ሙሉ ባለቤት ነን አይሉም የባንክ እዳ እየከፈሉ ነው ይሄስ እንዴት ነው የሚታየው ?
ኮንዶሚኒየም እና የማህበር ቤቶች በጣም ልዩነት አለው ፤ የማህበር ቤቶች ሲሰሩበት ኖረዋል የአፈር እና የጣራ ግብር እየተባለ አሁን የዛ Update የሆነ ነው እየተባለ ነው ፤ እንዲህ በሆነበት ሁኔታ የኮንዶሚኒየም በዛ ህግ መገዛት አለበት ወይ ? እሺ በህጉ ይገዛ ከዚህ በፊት ባልከፈለበት ሁኔታ ቅጣት የሚባለው ለምን ጨመረ ?
ህዝቡ በአሰራሩና በፕሮግራም አልባነቱ እያመረረ እየተንገላታ ነው። ለመክፈልም ሄዶ መንገላታት በጣም አለ።
ወጥ የሆነው አሰራር ከክፍለ ከተማ እስከ ወረዳ የለም ፤ በራሳቸው በክ/ከተሞች መካከል ተመሳሳይ አከፋፈል የለም ፤ ከአንድ ቢሮ የሚወጣ ከሆነ አሰራሩ ወጥ ሊሆን ይገባል። "
በአዲስ አበባ አስተዳደር የመሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮ አማካሪ ዶ/ር ፈቀደ ተረፈ ፦
" አንዳንድ ቦታዎች ላይ የአገልግሎት ክፍያ ተብሎ የተነሳውና መሃንዲስ እንዲሁም የፋይል ተብሎ የተቀመጠው በአሰራር ውስጥ የለም። ይሄ መከፈል የለበትም ይሄ በአሰራር ውስጥ ስለሌለ መከፈል የለበትም።
ከህብረተሰቡ የሚነሱትን ቅሬታዎች እያስተካከልን እንሄዳለን። "
@tikvahethiopia @tikvah_eth_BOT
" የከፈልኩት ክፍያ አሰራሩን የጣሰ ነው "
የአዲስ አበባ ከተማ ቦሌ ክ/ከተማ ነዋሪ የሆኑት አቶ አስቻለው ጣሰው (በብሔራዊ ቴሌቪዥን ላይ ቀርበው የተናገሩት) ፦
" የምኖረው ቦሌ ክፍለ ከተማ ነው።
በወረዳ 14 የታዘብኩትን መናገር እፈልጋለሁ።
እኔ የሚጠበቅብኝን የ ' Property Tax ' ከፍያለሁ ነገር ግን የከፈልኩት ክፍያ አሰራሩን የጣሰ ነው።
ታክስ የመክፈል የዜግነት ግዴታዬ ነው ፤ መጀመሪያ መመሪያውን አይቼ ነው ልከፍል የሄድኩት።
መመሪያው ሰርኩላር የተደረገው ሚያዚያ 7 /2015 ነው። እዚህ መመሪያ ላይ ሂሳቡ የሚሰራበት ቀመር አለ እሱን እስልቼ ነበር የሄድኩት ነገር ግን እዛ ወረዳ ላይ ያየሁት ነገር ከ1000 እስከ 1500 በላይ ምኑንም ያላመላከተ፣ ከመመሪያውም ጋር ያልተናበበ ክፍያ ሰዎች እንዲከፍሉ ይደረጋል።
ይሄ ከተመን በፊት ያለ ነው።
ለምሳሌ ፦ እኔ ካርታዬን ' ዲጅታል ' አስደርጊያለሁ ፣ ዲጂታል ሳስደርግ የመሃንዲስ 1500 ብር ከፍያለሁ ነገር ግን በዚህ ወቅት እንድከፍል የተደረገው መሃንዲስ ስሙ ተጠርቶ ብቻ 500 ብር የመሃንዲስ፣ ፋይሌ ወጥቶ ክፍያ ለምፈፅምበት 500 ፣ እንደገና ቅጣት ተብሎ 500 ፤ ቅጣት የአፈር እና የጣራ ግብር የሚባለው ከሆነ ኮንዶሚኒየሞች በዚህ ሲስተም ሲስተናገዱ አልነበረምና ኮንዶሚኒየሞች በምን ታይቶ ነው ከየካቲት አንድ ጀምሮ ሲስተሙ ቅጣት 5 % እየሰራ የሚሄደው ?
ከዚህ በፊት ተግባራዊ ያልተደረገባቸው የጋራ መኖሪያ ቤቶች / ኮንዶሚኒየም ላይ እንዴት በመኖሪያ ቤቶች አሰራር እዛ ላይ ተግባራዊ ተደረገ ? ይሄ ቅጣት ሚያዚያ ላይ በወጣ ሰርኩላር እንዴት ከየካቲት ጀምሮ ሰው ይቀጣል ?
እንደገና ለመክፈል የሄደ ሰው ፋይሉን ከፋይል አውጥቶ፣ አምጥቶ ክፍል ላለው ሰው እንዴት ፋይል ለወጣበት አገልግሎት ተብሎ 500 ብር ለምንድነው ?
ቀመር የተሰራበትን ተቀበለ አብዛኛው በዝቶብናል አስተያየት ይደረግልን ቢልም ግን አብዛኛውን ህዝብ የማተራመስ በፕሮግራም ያለመጥራት ነገር አለ።
ለምሳሌ ወደ ገርጂ ብዙ የኮንዶሚኒየም ሳይቶች አሉ ፤ እንደውም ሰው ሃሳብ ሲሰጣቸው ምናለ ሳይቶቹን በፕሮግራም አድርጋቹ ብትጠሩን ለአሰራር ለናተም ያመቻል ህዝቡም እንዳለ ከሰኞ እስከ አርብ ሲተራመስ አይውልም ምናለ ፕሮግራም አውጥታችሁ ብታስተናግዱን ? እያለ ይጠይዋል ህዝቡ።
የኔን ያለአገባብ ክፍያ ያየ ጓደኛዬ ክፍለ ከተማ ሄዶ 500 ብር ብቻ ከፈለ። ተመልከቱ ክ/ከተማውን እና ወረዳዎች በምን ደረጃ ነው የሚናበቡት ? ቦሌ እና ለሚ ኩራ የሚያስከፍሉት ይለያያል 100 ብር ከፍለን ያሉ አሉ። እዛው ወረዳ 14 እና 13 እራሱ ወረዳ 13 100 ብር ሲያስከፍል ወረዳ 14 1000 ብር ያስከፍላል ይህ አገልግሎት ለሚባለው ነው ቅጣቱን ተውትና።
ሁሉም ቦታ የአገልግሎት እያሉ ይቀበላሉ፤ ግን ወጥ አይደለም ። ለምን ጉራማይሌ ሆነ ? አንዱ ጋር መቶ ሌላው ጋር ሌላ በተለይ የመሃንዲሱ ብቻ 500 ፣ የአገልግሎት 500 እኔ ደረሰኝ ይዤ ነው ይሄንን የምናገረው።
አፈፃፀሙ ላይ ሰዎች ቅር እያላቸው ባላመኑበት ሁኔታ ላይ ተገደው የመክፈል ሁኔታ አለ። ከምንገላታ በሚልም ... አንድ ሰው በጣም ፈጠነ ከተባለ 3 ቀን ነው የሚፈጅበት እኔ 3 ቀን ከመ/ቤት አስፈቅጃለሁ ይሄንን ጉዳይ ለመፈፀም።
ልገብር ብሎ የሚሄድ ሰው ሶስት ቀን ከስራው ቀርቶ አስቡት።
እናስተካክላለን ይላሉ ፤ እሺ የከፈሉ ሰዎች ጉዳይ ምን ይደረጋል ? ሌላው የባንክ እዳ ያለባቸውና ካርታው ባንክ የሆናባቸው አሉ አሁን እነዚህ ሰዎች ሙሉ ባለቤት ነን አይሉም የባንክ እዳ እየከፈሉ ነው ይሄስ እንዴት ነው የሚታየው ?
ኮንዶሚኒየም እና የማህበር ቤቶች በጣም ልዩነት አለው ፤ የማህበር ቤቶች ሲሰሩበት ኖረዋል የአፈር እና የጣራ ግብር እየተባለ አሁን የዛ Update የሆነ ነው እየተባለ ነው ፤ እንዲህ በሆነበት ሁኔታ የኮንዶሚኒየም በዛ ህግ መገዛት አለበት ወይ ? እሺ በህጉ ይገዛ ከዚህ በፊት ባልከፈለበት ሁኔታ ቅጣት የሚባለው ለምን ጨመረ ?
ህዝቡ በአሰራሩና በፕሮግራም አልባነቱ እያመረረ እየተንገላታ ነው። ለመክፈልም ሄዶ መንገላታት በጣም አለ።
ወጥ የሆነው አሰራር ከክፍለ ከተማ እስከ ወረዳ የለም ፤ በራሳቸው በክ/ከተሞች መካከል ተመሳሳይ አከፋፈል የለም ፤ ከአንድ ቢሮ የሚወጣ ከሆነ አሰራሩ ወጥ ሊሆን ይገባል። "
በአዲስ አበባ አስተዳደር የመሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮ አማካሪ ዶ/ር ፈቀደ ተረፈ ፦
" አንዳንድ ቦታዎች ላይ የአገልግሎት ክፍያ ተብሎ የተነሳውና መሃንዲስ እንዲሁም የፋይል ተብሎ የተቀመጠው በአሰራር ውስጥ የለም። ይሄ መከፈል የለበትም ይሄ በአሰራር ውስጥ ስለሌለ መከፈል የለበትም።
ከህብረተሰቡ የሚነሱትን ቅሬታዎች እያስተካከልን እንሄዳለን። "
@tikvahethiopia @tikvah_eth_BOT
የጣሪያና ግድግዳ ግብር . . .
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የኮሚኒኬሽን ቢሮ ፤ የጣሪያና ግድግዳ ግብርን በተመለከተ ዛሬ ለግንዛቤ በሚል አንድ መረጃ አሰራጭቷል።
በዚሁ መረጀው ፤ " መንግስት በሚያለማው መሰረተ ልማት እና የህግ ማሻሻያ ምክንያት በመሬት እና መሬት ነክ ንብረቶች እሴታቸው (Value) ይጨምራል " ያለ ሲሆን " መሬትና መሬት ነክ ንብረቶች እሴታቸው በመጨመሩ ምክኒያት የአከባቢ መንግስታት የሚሰበስቡት ገቢ የቤት ግብር ወይንም የጣራና ግድግዳ ግብር በመባል ይታወቃል " ሲል አስረድቷል።
የጣሪያና ግድግዳ ግብር የሚሰበሰበው ፦
- ከጣሪያና ግድግዳ ግብር የሚሰበሰበው ገቢ መሰረቱ የተረጋጋና አስተማማኝ የገቢ ምንጭ በመሆኑ፣
- የማይለዋወጥና የማይሰወር የግብር አይነት በመሆኑ፣
- ለቁጥጥር አመቺና ከታክስ ለመሸሽ የማይመች የግብር መሰረት በመሆኑ፣
- ለከተሞች የመሰረተ ልማት እድገት የጀርባ አጥንት እንዲሁም ለከተሞች መሰረታዊ የመሰረተ ልማት ችግሮችን ፍላጎት የሚያሟላ በመሆኑ
- ከፋዮች በከፈሉት ልክ የመሰረተ ልማት ተጠቃሚ እንዲሆኑ የሚያደርግ በመሆኑ ነው ብሏል።
ቢሮው ፤ የጣራና ግድግዳ ግብር በአገራችን በህግ በተደገፈ በዘመናዊ መልኩ መተግበር የጀመረው በ1937 ዓ.ም ነው ብሏል።
በመጀመሪያው በከተማ ውስጥ የንብረት ግብር ይጣል የነበረው በማናቸውም የማይንቀሳቀስ ንብረት በመሬትና በህንፃዎች ላይ ነበር ሲል አስታውሷል።
ሁለተኛው በከተማ መሬት ኪራይና በከተማ ቤት ግብር አዋጅ ቁጥር 80/1968 መሆኑን ገልጾ በአዋጁ አንቀጽ 6 መሰረት የጣሪያ ግድግዳ ግብር ዓመታዊ የቤት ኪራይ ግምት መሰረት በማድረግ እንደሚሰበሰብ አመልክቷል።
ሶስተኛው " የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ህገመንግስት አንቀጽ 49 መሰረት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የስልጣን ይዘት እና ወሰን ለመደንገግ በወጣው የፌደራል ቻርተር አዋጅ 361/1995 መሰረት በከተማው ውስጥ የከተማ ቦታ ኪራይ እና የቤት ግብር ይወስናል ይሰበስባል ይላል " ሲል አስረድቷል።
እንደ ኮሚኒኬሽን ቢሮው መረጃ በከተማ አስተዳደሩ ውስጥ ይኖራሉ ተብሎ የሚገመተው 1,020,528 መኖሪያ ቤቶች ሲሆኑ ከዚህ ውስጥ የግል ቤቶች 891,628 ቤቶች እንደሆኑ ይገመታል። ከነዚህ መካከል ግብር እየከፈሉ ያሉት 182,842 ባለይዞታዎች እንደሆኑ የተገለፀ ሲሆን የከፋዮች ቁጥር ማነስ ብቻ ሳይሆን የሚሰበሰበውም ገቢ በጣም አነስተኛ ነው ተብሏል።
" የክፍያ ጫናውን ለማቅለል ሲባል የዚህ ዓመት ክፍያ ያልከፈሉ የቤት ግብር ከፋዮች በጥናት በተለየው የአንድ ሜትር ካሬ የቤት ስፋት ወርሀዊ ኪራይ ግምት ወይም ዓመታዊ የኪራይ ግምት መጠንን ለመኖሪያ ቤት በ50% እና ለመሥሪያ ቤት ደግሞ በ75% ላይ ብቻ ግብሩን በማስላት እንዲከፍሉ ይደረጋል " ሲል የከተማው ኮሚኒኬሽን አስረድቷል።
@tikvahethiopia
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የኮሚኒኬሽን ቢሮ ፤ የጣሪያና ግድግዳ ግብርን በተመለከተ ዛሬ ለግንዛቤ በሚል አንድ መረጃ አሰራጭቷል።
በዚሁ መረጀው ፤ " መንግስት በሚያለማው መሰረተ ልማት እና የህግ ማሻሻያ ምክንያት በመሬት እና መሬት ነክ ንብረቶች እሴታቸው (Value) ይጨምራል " ያለ ሲሆን " መሬትና መሬት ነክ ንብረቶች እሴታቸው በመጨመሩ ምክኒያት የአከባቢ መንግስታት የሚሰበስቡት ገቢ የቤት ግብር ወይንም የጣራና ግድግዳ ግብር በመባል ይታወቃል " ሲል አስረድቷል።
የጣሪያና ግድግዳ ግብር የሚሰበሰበው ፦
- ከጣሪያና ግድግዳ ግብር የሚሰበሰበው ገቢ መሰረቱ የተረጋጋና አስተማማኝ የገቢ ምንጭ በመሆኑ፣
- የማይለዋወጥና የማይሰወር የግብር አይነት በመሆኑ፣
- ለቁጥጥር አመቺና ከታክስ ለመሸሽ የማይመች የግብር መሰረት በመሆኑ፣
- ለከተሞች የመሰረተ ልማት እድገት የጀርባ አጥንት እንዲሁም ለከተሞች መሰረታዊ የመሰረተ ልማት ችግሮችን ፍላጎት የሚያሟላ በመሆኑ
- ከፋዮች በከፈሉት ልክ የመሰረተ ልማት ተጠቃሚ እንዲሆኑ የሚያደርግ በመሆኑ ነው ብሏል።
ቢሮው ፤ የጣራና ግድግዳ ግብር በአገራችን በህግ በተደገፈ በዘመናዊ መልኩ መተግበር የጀመረው በ1937 ዓ.ም ነው ብሏል።
በመጀመሪያው በከተማ ውስጥ የንብረት ግብር ይጣል የነበረው በማናቸውም የማይንቀሳቀስ ንብረት በመሬትና በህንፃዎች ላይ ነበር ሲል አስታውሷል።
ሁለተኛው በከተማ መሬት ኪራይና በከተማ ቤት ግብር አዋጅ ቁጥር 80/1968 መሆኑን ገልጾ በአዋጁ አንቀጽ 6 መሰረት የጣሪያ ግድግዳ ግብር ዓመታዊ የቤት ኪራይ ግምት መሰረት በማድረግ እንደሚሰበሰብ አመልክቷል።
ሶስተኛው " የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ህገመንግስት አንቀጽ 49 መሰረት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የስልጣን ይዘት እና ወሰን ለመደንገግ በወጣው የፌደራል ቻርተር አዋጅ 361/1995 መሰረት በከተማው ውስጥ የከተማ ቦታ ኪራይ እና የቤት ግብር ይወስናል ይሰበስባል ይላል " ሲል አስረድቷል።
እንደ ኮሚኒኬሽን ቢሮው መረጃ በከተማ አስተዳደሩ ውስጥ ይኖራሉ ተብሎ የሚገመተው 1,020,528 መኖሪያ ቤቶች ሲሆኑ ከዚህ ውስጥ የግል ቤቶች 891,628 ቤቶች እንደሆኑ ይገመታል። ከነዚህ መካከል ግብር እየከፈሉ ያሉት 182,842 ባለይዞታዎች እንደሆኑ የተገለፀ ሲሆን የከፋዮች ቁጥር ማነስ ብቻ ሳይሆን የሚሰበሰበውም ገቢ በጣም አነስተኛ ነው ተብሏል።
" የክፍያ ጫናውን ለማቅለል ሲባል የዚህ ዓመት ክፍያ ያልከፈሉ የቤት ግብር ከፋዮች በጥናት በተለየው የአንድ ሜትር ካሬ የቤት ስፋት ወርሀዊ ኪራይ ግምት ወይም ዓመታዊ የኪራይ ግምት መጠንን ለመኖሪያ ቤት በ50% እና ለመሥሪያ ቤት ደግሞ በ75% ላይ ብቻ ግብሩን በማስላት እንዲከፍሉ ይደረጋል " ሲል የከተማው ኮሚኒኬሽን አስረድቷል።
@tikvahethiopia
(ኢትዮ ቴሌኮም)
ቢዝነስዎን ከጊዜው ጋር ለማራመድ ኢንተርኔት፤ ስራዎን ለማሳለጥ ፈጣን ግንኙነት የግድ ሆኗል!
እኛም ለመፍትሄው ከጎንዎ ሁሌም አለን በገመድ አልባ ኢንተርኔት አገልግሎት ላይ እስከ 53% ቅናሽ አድርገን በተለያዩ አማራጮች ማቅረባችንን ስንገልጽ በልዩ ደስታ ነው!
አገልግሎቱን ለማግኘት በአቅራቢያዎ በሚገኝ የቢዝነስ አገልግሎት ማዕከላችን ጎራ ይበሉ!
ቢዝነስዎን ከጊዜው ጋር ለማራመድ ኢንተርኔት፤ ስራዎን ለማሳለጥ ፈጣን ግንኙነት የግድ ሆኗል!
እኛም ለመፍትሄው ከጎንዎ ሁሌም አለን በገመድ አልባ ኢንተርኔት አገልግሎት ላይ እስከ 53% ቅናሽ አድርገን በተለያዩ አማራጮች ማቅረባችንን ስንገልጽ በልዩ ደስታ ነው!
አገልግሎቱን ለማግኘት በአቅራቢያዎ በሚገኝ የቢዝነስ አገልግሎት ማዕከላችን ጎራ ይበሉ!
#ትግራይ
" እስካሁን ወደ ህግ የቀረቡት 7 ብቻ ናቸው " - ግብረ ኃይሉ
የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር የተሰረቀ የሰብዓዊ እርዳትን ለማጣራት ያቋቋመው ግብረ ኃይል እስካሁን ሲሰራቸው የቆዩትን ስራዎች በተመለከተ ለክልሉ ቴሌቪዥን ማብራሪያ ሰጥቶ ነበር።
በዚህም ወቅት በክልሉ የሰብዓዊ እርዳታ በኤርትራ ኃይሎች፣ በፌዴራል እና በትግራይ ክልል መንግስታት መዋቅር ዝርፊያ መፈፀሙን ለማወቅ ችሏል።
በተጨማሪም በግብረሰናይ ድርጅቶች ፣ የተፈናቃይ ወገኖች አስተባባሪዎች ለሰብዓዊ እርዳታ የመጣ ድጋፍን መዝረፋቸውን የሚያመላክት ማስረጃ ተገኝቷል።
የተዘረፈው ዘይት፣ ስንዴ፣ ክክ እና ሌሎች ድጋፎች ናቸው።
እስካሁን በተሰራው የማጣራት ስራ የኤርትራ ሰራዊት በሽራሮ 28,880 ኩንታል ስንዴ መዝረፉ፣ 43,200 ሊትር ዘይት፣ አተር ክክ 1440 ኩንታል መዝረፉን ግብረኃይሉ አሳውቋል። ይህ ኃይል የዘረፈውን ዘርፎ የተቀረውን እንዲባክን አድርጓል።
የፌዴራል መንግስት " አስተዳደር ብሎ ያስቀመጣቸው አመራሮች " 43,196 ኩንታል ስንዴ፣ 129,585 ሊትር ዘይት ፣ 4,184 ኩንታል የአተር ክክ እንደወሰዱ በጥናት ተረጋግጧል።
በትግራይ መዋቅር 14, 317 ኩንታል ስንዴ፣ 42,759 ሊትር ዘይት፣ 1,424 ኩንታል የአተር ክክ መዘረፉን ለማረጋገጥ ተችሏል።
እንደ ግብረ ኃይሉ መረጃ እስካሁን በክልልና በዞን ለማጣራት እንደተቻለው ከፌዴራል መንግሥት መዋቅር፣ ከትግራይ ክልል መንግሥት መዋቅር፣ ከግብረ ሰናይ ድርጅቶች እንዲሁም ከተፈናቃይ ወገኖች አስተባባሪዎች እስካሁን 186 ተጠርጣሪዎች ሰብዓዊ እርዳታ በማጥፋት ተሳታፊ ሆነው መገኘታቸውን ለመወቅ እንደተቻለና 7 ሰዎች ወደ ህግ እንዲቀርቡ መደረጉን አሳውቋል።
የተጀመረው የማጣራት ስራ ገና የሚቀጥል ሲሆን በየጊዜውም መረጃውን ለህዝብ እንደሚያሳውቅ ገልጿል።
@tikvahethiopia
" እስካሁን ወደ ህግ የቀረቡት 7 ብቻ ናቸው " - ግብረ ኃይሉ
የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር የተሰረቀ የሰብዓዊ እርዳትን ለማጣራት ያቋቋመው ግብረ ኃይል እስካሁን ሲሰራቸው የቆዩትን ስራዎች በተመለከተ ለክልሉ ቴሌቪዥን ማብራሪያ ሰጥቶ ነበር።
በዚህም ወቅት በክልሉ የሰብዓዊ እርዳታ በኤርትራ ኃይሎች፣ በፌዴራል እና በትግራይ ክልል መንግስታት መዋቅር ዝርፊያ መፈፀሙን ለማወቅ ችሏል።
በተጨማሪም በግብረሰናይ ድርጅቶች ፣ የተፈናቃይ ወገኖች አስተባባሪዎች ለሰብዓዊ እርዳታ የመጣ ድጋፍን መዝረፋቸውን የሚያመላክት ማስረጃ ተገኝቷል።
የተዘረፈው ዘይት፣ ስንዴ፣ ክክ እና ሌሎች ድጋፎች ናቸው።
እስካሁን በተሰራው የማጣራት ስራ የኤርትራ ሰራዊት በሽራሮ 28,880 ኩንታል ስንዴ መዝረፉ፣ 43,200 ሊትር ዘይት፣ አተር ክክ 1440 ኩንታል መዝረፉን ግብረኃይሉ አሳውቋል። ይህ ኃይል የዘረፈውን ዘርፎ የተቀረውን እንዲባክን አድርጓል።
የፌዴራል መንግስት " አስተዳደር ብሎ ያስቀመጣቸው አመራሮች " 43,196 ኩንታል ስንዴ፣ 129,585 ሊትር ዘይት ፣ 4,184 ኩንታል የአተር ክክ እንደወሰዱ በጥናት ተረጋግጧል።
በትግራይ መዋቅር 14, 317 ኩንታል ስንዴ፣ 42,759 ሊትር ዘይት፣ 1,424 ኩንታል የአተር ክክ መዘረፉን ለማረጋገጥ ተችሏል።
እንደ ግብረ ኃይሉ መረጃ እስካሁን በክልልና በዞን ለማጣራት እንደተቻለው ከፌዴራል መንግሥት መዋቅር፣ ከትግራይ ክልል መንግሥት መዋቅር፣ ከግብረ ሰናይ ድርጅቶች እንዲሁም ከተፈናቃይ ወገኖች አስተባባሪዎች እስካሁን 186 ተጠርጣሪዎች ሰብዓዊ እርዳታ በማጥፋት ተሳታፊ ሆነው መገኘታቸውን ለመወቅ እንደተቻለና 7 ሰዎች ወደ ህግ እንዲቀርቡ መደረጉን አሳውቋል።
የተጀመረው የማጣራት ስራ ገና የሚቀጥል ሲሆን በየጊዜውም መረጃውን ለህዝብ እንደሚያሳውቅ ገልጿል።
@tikvahethiopia
#AAU
አንጋፋው የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፤ በትግራይ ክልል ለሚገኙ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት መልሶ ማቋቋሚያ ከ12 ሚሊዮን ብር በላይ ድጋፍ ማድረጉን አሳውቋል።
ይኸው ድጋፍ ዛሬ ወደ ክልሉ መላኩን ተቋሙ ገልጿል።
ድጋፉ 11 ሚሊዮን ብር በጥሬ ገንዘብ ሲሆን ቀሪው አንድ ሚሊዮን ብር የሚያወጡ ኮምፒዩተሮችና የህክምና መሳሪያ ቁሳቁሶች መሆናቸው ተገልጿል።
ዩኒቨርሲቲው መሰል ድጋፎችን በቀጣይነት ለማድረግ ቁርጠኛ መሆኑን አሳውቆ በምርምርና ቴክኖሎጂዎች ረገድም በመልሶ ማቋቋሚያ ስራዎች ላይ የራሱን እገዛ እንደሚያደርግም ገልጿል።
#ኢዜአ
@tikvahethiopia @tikvahuniversity
አንጋፋው የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፤ በትግራይ ክልል ለሚገኙ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት መልሶ ማቋቋሚያ ከ12 ሚሊዮን ብር በላይ ድጋፍ ማድረጉን አሳውቋል።
ይኸው ድጋፍ ዛሬ ወደ ክልሉ መላኩን ተቋሙ ገልጿል።
ድጋፉ 11 ሚሊዮን ብር በጥሬ ገንዘብ ሲሆን ቀሪው አንድ ሚሊዮን ብር የሚያወጡ ኮምፒዩተሮችና የህክምና መሳሪያ ቁሳቁሶች መሆናቸው ተገልጿል።
ዩኒቨርሲቲው መሰል ድጋፎችን በቀጣይነት ለማድረግ ቁርጠኛ መሆኑን አሳውቆ በምርምርና ቴክኖሎጂዎች ረገድም በመልሶ ማቋቋሚያ ስራዎች ላይ የራሱን እገዛ እንደሚያደርግም ገልጿል።
#ኢዜአ
@tikvahethiopia @tikvahuniversity
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
My Wish Enterprise
DEVELON (ዲቬሎን) የሚለው አዲሱ የዱሳን ስያሜ የ Develop (“ማደግ”) እና Onward (“ወደፊት”) ቃላቶች ውህድ ሲሆን፤ በኮንስትራክሽን ማሽነሪ ዘርፍ ያሳረፍነዉን ትልቅ አሻራ በማጎልበት በጎ ነገሮችን ይዘን “ወደፊት ለማደግ” ያለንን ምኞት ያንፀባርቃል።
• ከአዲሱ የብራንድ ስያሜ ለዉጥ ውጭ ምንም አይነት ውጫዊ ገፅታም ሆነ ውስጣዊ የማሽኑ አካላት ላይ ለውጥ አልተደረገም።
• ኦርጅናል መለዋወጫ፣ አስተማማኝ፣ ቀልጣፋና እና ተደራሽነት ያለው የጥገና አገልግሎት መለያችን ናቸው።
ማይ ዊሽ ኢንተርፕራይዝ ኃላ/የተ/የግ/ማ ቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ፡ https://t.iss.one/MYWISHENT
+251-913-356384 +251-912-710661 +251-910-626917 +251-928-414395
+251-911-606068 +251-922-475851 +251-935-409319 +251-911-602664
DEVELON (ዲቬሎን) የሚለው አዲሱ የዱሳን ስያሜ የ Develop (“ማደግ”) እና Onward (“ወደፊት”) ቃላቶች ውህድ ሲሆን፤ በኮንስትራክሽን ማሽነሪ ዘርፍ ያሳረፍነዉን ትልቅ አሻራ በማጎልበት በጎ ነገሮችን ይዘን “ወደፊት ለማደግ” ያለንን ምኞት ያንፀባርቃል።
• ከአዲሱ የብራንድ ስያሜ ለዉጥ ውጭ ምንም አይነት ውጫዊ ገፅታም ሆነ ውስጣዊ የማሽኑ አካላት ላይ ለውጥ አልተደረገም።
• ኦርጅናል መለዋወጫ፣ አስተማማኝ፣ ቀልጣፋና እና ተደራሽነት ያለው የጥገና አገልግሎት መለያችን ናቸው።
ማይ ዊሽ ኢንተርፕራይዝ ኃላ/የተ/የግ/ማ ቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ፡ https://t.iss.one/MYWISHENT
+251-913-356384 +251-912-710661 +251-910-626917 +251-928-414395
+251-911-606068 +251-922-475851 +251-935-409319 +251-911-602664
#ምርጥ_ዕቃ
እነዚህ ዕቃዎች በአስገራሚ ዋጋ እየተሸጡ ነው። ለበለጠ መረጃ፦ t.iss.one/MerttEka
☎️ 0944-22-23-24
☎️ 0904-94-48-48
🎯መገናኛ ዘፍመሽ ግራንድ ሞል 3ተኛ ፎቅ ከሊፍት ሲወርዱ ወደ ቀኝ 376
እነዚህ ዕቃዎች በአስገራሚ ዋጋ እየተሸጡ ነው። ለበለጠ መረጃ፦ t.iss.one/MerttEka
☎️ 0944-22-23-24
☎️ 0904-94-48-48
🎯መገናኛ ዘፍመሽ ግራንድ ሞል 3ተኛ ፎቅ ከሊፍት ሲወርዱ ወደ ቀኝ 376
" የመሬት ደላሎችንና ህገወጥ አሰራራቸውን መታገል ራሱን የቻለ ጦርነት እንደ መምራት ነው " - የወልዲያ ከተማ ተቀዳሚ ከንቲባ ዱባለ አብራሬ
የወልድያ ከተማ በሰሜኑ የሀገራችን ክፍሎች በጉልህ ስማቸው ከሚጠቀሱ ከተሞች አንዷ ብትሆንም እስካሁን ከተማዋ ያላትን ስም የሚመጥን ልማት አለ ብሎ ለመናገር አያስደፍርም። ይበልጡኑ በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል የነበረው ጦርነት የነበረውን ጭላንጭልም ያደበዘዘ ነበር።
ከተማዋ በጦርነቱ ከደረሰባት ኪሳራ ተነቃቅታ የመሰረተ ልማት ግንባታዎች እንዲፋጠኑ እንዲሁም የኢንቨስትመንት አማራጮች እንዲፈጠሩ የከተማ አስተዳደሩ በቁርጠኝነት እየሰራ እንደሚገኝ የከተማው ተቀዳሚ ከንቲባ ዱባለ አብራሬ ተናግረዋል።
ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ጋር ቆይታ ያደረጉት ከንቲባው የእሳቸው አስተዳደር ወደ ስልጣን ከመጣ ጀምሮ ሁኔታዎችን ሲያጠና መቆየቱን ገልጸው በተለይ ከመሬት ጋር ተያይዞ የነበሩ ከፍተኛ ምዝበራዎችን አጥንቶ እርምጃ መውሰድ መጀመሩን ገልጸዋል።
"የመሬት ደላሎች" ለከተማዋ እድገት እንቅፋቶች ሆነው ቆይተዋል የሚሉት ከንቲባው ይህንን ተታግሎ ማለፍ ወይም ስልጣን መልቀቅ የሚል አማራጭ ይዘን ተነስተን ህገወጦችን በመታገል ወልዲያን ለማልማት ወስነን እየተንቀሳቀስን ነው ሲሉ ተናግረዋል።
በከተማዋ " ሀሰተኛ ሳይት ፕላኖች ይሰራሉ፤ በአንድ ቦታ ሁለት አይነት ሳይት ፕላን ይወጣል፤ የከተማ ከንቲባ ውሳኔ ይሸጣል ይለወጣል፤ ምትክ ቦታ እየተባለ በባዶይሰጥ ነበር " የሚሉት ከንቲባው ይህንን ህገወጥ ተግባር የሚፈጽሙ በቁጥር 41 የሚሆኑ ሰዎች የተለዩ መሆናቸውንና በህግ ተጠያቂ የማድረግ ሥራ እየተሰራ መሆኑን አንስተዋል።
"የአርሶአደር መሬት አርሶአደሩ ማግኘት የሚገባውን ጥቅም እንዲያገኝ ከተደረገ በኋላ ለኢንቨስትመንት እስከተመረጠ ድረስ ኢንቨስት ማድረግ አለበት" የሚሉት ከንቲባው "እነሱ [የመሬት ደላሎች] ግን አርሶአደሩን ከመንግስት የምታገኘው ጥቅም ትንሽ ነው እያሉ መሬት እየሸነሸኑ እየሸጡ ነው" ብለዋል።
ከተማዋን ያነቃቃል ተብሎ ተስፋ የተጣለበት የመንገድ ፕሮጀከት ምን ላይ ይገኛል ?
የከተማዋ ነዋሪ ማለቁን በጉጉት ከሚጠብቀው ፕሮጀክት አንዱ የሆነው በከተማዋ የሚሰራው የአስፓልት መንገድ ግንባታ ነው።
ከጎንደር በር ፒያሳ እየተገነባ የሚገኘው ይህ የመንገድ ግንባታ ከዚህ ቀደም ጥሩ ሂደት ላይ የነበረ ቢሆንም በጦርነቱ ምክንያት ከዚያም ጋር ተያይዞ ተቋራጩ በተፈጸመበት ዝርፊያ መቀጠል ተቋርጦ ቆይቷል።
አሁን ላይ የመንገዱን ግንባታ የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን ኮምቦልቻ ዲስትሪክት ተረክቦት በመሰራት ላይ እንደሚገኝ ከንቲባው ገልጸውልናል።
" የጎደሉ እቃዎችን እያሟላን፤ ከሌሎች ቦታዎች ጭምር ጥሬ እቃዎችን በማስመጣት በጥሩ ክትትል አብረን እየሰራን ነው። .... ከዝናብ ጋር ተያይዞ የመጣ መዘግየት እንጂ ዳግም ፕሮጀክቱ ከተጀመረ በኋላ በፍጥነት እየሄደ ይገኛል። " ብለዋል።
ከዚህም በተጨማሪም የ30 ሜትር ስፋት ያለውን የቀለበት መንገድ እንዲሁም ከስታዲየም አደባባይ የሚደርስ የአስፋልት ግንባታ በከተማዋ እየተከናወነ እኝደሚገኝ ከንቲባ ዱባለ አንስተዋል።
ወልድያ ከተማ ባለ አምስት በር እንዲሁም በተራራ የተከበበች እንደመሆኗ ለቱሪዝም እንዲሁም ለሥራ ፈጠራ እንዲውል እየተሰራ ይገኛል የሚሉት ከንቲባው ከዚህ ጋር ተያይዞም የሚያጠና ቡድን ተቋቁሞ 12 ተግባራት መለየታቸውንና ለዚህም 662 ሚሊዮን ብር እንደሚያስፈልግ መለየቱን ጠቁመው የገንዘብ ማሰባሰብ ሥራዎች በቴሌቶንና በሌሎች አማራጮች እየተሰራ ይገኛልም ብለዋል።
@tikvahethiopia
የወልድያ ከተማ በሰሜኑ የሀገራችን ክፍሎች በጉልህ ስማቸው ከሚጠቀሱ ከተሞች አንዷ ብትሆንም እስካሁን ከተማዋ ያላትን ስም የሚመጥን ልማት አለ ብሎ ለመናገር አያስደፍርም። ይበልጡኑ በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል የነበረው ጦርነት የነበረውን ጭላንጭልም ያደበዘዘ ነበር።
ከተማዋ በጦርነቱ ከደረሰባት ኪሳራ ተነቃቅታ የመሰረተ ልማት ግንባታዎች እንዲፋጠኑ እንዲሁም የኢንቨስትመንት አማራጮች እንዲፈጠሩ የከተማ አስተዳደሩ በቁርጠኝነት እየሰራ እንደሚገኝ የከተማው ተቀዳሚ ከንቲባ ዱባለ አብራሬ ተናግረዋል።
ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ጋር ቆይታ ያደረጉት ከንቲባው የእሳቸው አስተዳደር ወደ ስልጣን ከመጣ ጀምሮ ሁኔታዎችን ሲያጠና መቆየቱን ገልጸው በተለይ ከመሬት ጋር ተያይዞ የነበሩ ከፍተኛ ምዝበራዎችን አጥንቶ እርምጃ መውሰድ መጀመሩን ገልጸዋል።
"የመሬት ደላሎች" ለከተማዋ እድገት እንቅፋቶች ሆነው ቆይተዋል የሚሉት ከንቲባው ይህንን ተታግሎ ማለፍ ወይም ስልጣን መልቀቅ የሚል አማራጭ ይዘን ተነስተን ህገወጦችን በመታገል ወልዲያን ለማልማት ወስነን እየተንቀሳቀስን ነው ሲሉ ተናግረዋል።
በከተማዋ " ሀሰተኛ ሳይት ፕላኖች ይሰራሉ፤ በአንድ ቦታ ሁለት አይነት ሳይት ፕላን ይወጣል፤ የከተማ ከንቲባ ውሳኔ ይሸጣል ይለወጣል፤ ምትክ ቦታ እየተባለ በባዶይሰጥ ነበር " የሚሉት ከንቲባው ይህንን ህገወጥ ተግባር የሚፈጽሙ በቁጥር 41 የሚሆኑ ሰዎች የተለዩ መሆናቸውንና በህግ ተጠያቂ የማድረግ ሥራ እየተሰራ መሆኑን አንስተዋል።
"የአርሶአደር መሬት አርሶአደሩ ማግኘት የሚገባውን ጥቅም እንዲያገኝ ከተደረገ በኋላ ለኢንቨስትመንት እስከተመረጠ ድረስ ኢንቨስት ማድረግ አለበት" የሚሉት ከንቲባው "እነሱ [የመሬት ደላሎች] ግን አርሶአደሩን ከመንግስት የምታገኘው ጥቅም ትንሽ ነው እያሉ መሬት እየሸነሸኑ እየሸጡ ነው" ብለዋል።
ከተማዋን ያነቃቃል ተብሎ ተስፋ የተጣለበት የመንገድ ፕሮጀከት ምን ላይ ይገኛል ?
የከተማዋ ነዋሪ ማለቁን በጉጉት ከሚጠብቀው ፕሮጀክት አንዱ የሆነው በከተማዋ የሚሰራው የአስፓልት መንገድ ግንባታ ነው።
ከጎንደር በር ፒያሳ እየተገነባ የሚገኘው ይህ የመንገድ ግንባታ ከዚህ ቀደም ጥሩ ሂደት ላይ የነበረ ቢሆንም በጦርነቱ ምክንያት ከዚያም ጋር ተያይዞ ተቋራጩ በተፈጸመበት ዝርፊያ መቀጠል ተቋርጦ ቆይቷል።
አሁን ላይ የመንገዱን ግንባታ የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን ኮምቦልቻ ዲስትሪክት ተረክቦት በመሰራት ላይ እንደሚገኝ ከንቲባው ገልጸውልናል።
" የጎደሉ እቃዎችን እያሟላን፤ ከሌሎች ቦታዎች ጭምር ጥሬ እቃዎችን በማስመጣት በጥሩ ክትትል አብረን እየሰራን ነው። .... ከዝናብ ጋር ተያይዞ የመጣ መዘግየት እንጂ ዳግም ፕሮጀክቱ ከተጀመረ በኋላ በፍጥነት እየሄደ ይገኛል። " ብለዋል።
ከዚህም በተጨማሪም የ30 ሜትር ስፋት ያለውን የቀለበት መንገድ እንዲሁም ከስታዲየም አደባባይ የሚደርስ የአስፋልት ግንባታ በከተማዋ እየተከናወነ እኝደሚገኝ ከንቲባ ዱባለ አንስተዋል።
ወልድያ ከተማ ባለ አምስት በር እንዲሁም በተራራ የተከበበች እንደመሆኗ ለቱሪዝም እንዲሁም ለሥራ ፈጠራ እንዲውል እየተሰራ ይገኛል የሚሉት ከንቲባው ከዚህ ጋር ተያይዞም የሚያጠና ቡድን ተቋቁሞ 12 ተግባራት መለየታቸውንና ለዚህም 662 ሚሊዮን ብር እንደሚያስፈልግ መለየቱን ጠቁመው የገንዘብ ማሰባሰብ ሥራዎች በቴሌቶንና በሌሎች አማራጮች እየተሰራ ይገኛልም ብለዋል።
@tikvahethiopia
የብድር ስርዓት . . . #ብሔራዊ_ባንክ
ባንኮች ብድር ለመስጠት መያዣ የሚጠይቁበት አሰራር እንዳለ ይታወቃል።
ከዚህ ቀደም ዜጎች ቋሚ የሆነ ማስያዣ ሳያቀርቡ ከባንክ እንዲበደሩ ለማስቻል ስራዎች ተጀምረው እንደነበር መነገሩ ይታወሳል።
አሁን ላይ ይህ ስራ ከምን ደረሰ ?
የብሔራዊ ባንክ ምክትል ገዥ ሰለሞን ደስታ #ለሸገር_ኤፍ_ኤም 102.1 ሬድዮ የሰጡት ቃል ፦
" ተንቀሳቃሽ ዋስትና ሲስተም ዘርግተናል።
ብዙ ነገሮች ከዚህ በፊት ተቀባይነት የሌላቸው ፦
- የቁም እንስሳት
- እህል
- በግምጃ ቤት ውስጥ እህል እናስቀምጥና ርሲት እንይዛለን
- የመሬት አጠቃቀም የምንለው አለ
- ሶፋ
- ፍሪጅ
- ቴሌቪዥን . . . ሌሎችም አሉ፤ አስይዘን የምንበደርበት ሁኔታ ተፈጥሯል።
ከዚህም ባለፈ IP (Intellectual Property) ጭምር ሃሳብ (Idea) ፋይናንስ የሚደረግበት ስርዓት ነው ይሄ፤ ስለዚህ ሃሳቡን Patent ወይም የሆነ certified ነገር ይዞ ከመጣ ያንን ያሳያል እንደ Collateral ከዚያ በኃላ ብድር ይሰጡታል (ባንኮች) ማለት ነው። ያን ሂደት አሁን ተጀምሮ ወደ 70 ሺህ በMovable Collateral Registry ላይ ተመዝግቧል። ተንቀሳቃሽ ዋስትና አስይዘው ወደ 70 ተበዳሪ ተበድሯል።
ከእውቀት ጋር ፣ ከConsumer protection ጋር ተያይዞ የሚሰራ ስራ አለ፣ ለግብርና ... ወዘተ ከ5 % ያላነሰ ብድር እንዲሰጥ መመሪያ አውጥተን እሱንም ተግባራዊ እያደረግን እንገኛለን። አሁን ባለን መረጃ ከ5 % በላይ ሄዷል። "
@tikvahethiopia
ባንኮች ብድር ለመስጠት መያዣ የሚጠይቁበት አሰራር እንዳለ ይታወቃል።
ከዚህ ቀደም ዜጎች ቋሚ የሆነ ማስያዣ ሳያቀርቡ ከባንክ እንዲበደሩ ለማስቻል ስራዎች ተጀምረው እንደነበር መነገሩ ይታወሳል።
አሁን ላይ ይህ ስራ ከምን ደረሰ ?
የብሔራዊ ባንክ ምክትል ገዥ ሰለሞን ደስታ #ለሸገር_ኤፍ_ኤም 102.1 ሬድዮ የሰጡት ቃል ፦
" ተንቀሳቃሽ ዋስትና ሲስተም ዘርግተናል።
ብዙ ነገሮች ከዚህ በፊት ተቀባይነት የሌላቸው ፦
- የቁም እንስሳት
- እህል
- በግምጃ ቤት ውስጥ እህል እናስቀምጥና ርሲት እንይዛለን
- የመሬት አጠቃቀም የምንለው አለ
- ሶፋ
- ፍሪጅ
- ቴሌቪዥን . . . ሌሎችም አሉ፤ አስይዘን የምንበደርበት ሁኔታ ተፈጥሯል።
ከዚህም ባለፈ IP (Intellectual Property) ጭምር ሃሳብ (Idea) ፋይናንስ የሚደረግበት ስርዓት ነው ይሄ፤ ስለዚህ ሃሳቡን Patent ወይም የሆነ certified ነገር ይዞ ከመጣ ያንን ያሳያል እንደ Collateral ከዚያ በኃላ ብድር ይሰጡታል (ባንኮች) ማለት ነው። ያን ሂደት አሁን ተጀምሮ ወደ 70 ሺህ በMovable Collateral Registry ላይ ተመዝግቧል። ተንቀሳቃሽ ዋስትና አስይዘው ወደ 70 ተበዳሪ ተበድሯል።
ከእውቀት ጋር ፣ ከConsumer protection ጋር ተያይዞ የሚሰራ ስራ አለ፣ ለግብርና ... ወዘተ ከ5 % ያላነሰ ብድር እንዲሰጥ መመሪያ አውጥተን እሱንም ተግባራዊ እያደረግን እንገኛለን። አሁን ባለን መረጃ ከ5 % በላይ ሄዷል። "
@tikvahethiopia