TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.3K photos
1.51K videos
211 files
4.1K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
የትግራይ ተማሪዎች . . .

በትግራይ ጦርነት ምክንያት በክልሉ ያሉ ትምህርት ቤቶች ወድመዋል፣ ተዘርፈዋል፤ እንዳልነበሩ ሆነዋል።

ከምንም በላይ ደግሞ የትግራይ ልጆች ለከፍተኛ የስነ ልቦና እና የአካል ጉዳት ተዳርገዋል።

ከዓመታት በኃላ የመማር ማስተማር ሂደት በትግራይ ውስን አካባቢዎች ቢጀመርም የትግራይ ልጆች / ተማሪዎች የወደፊት ብሩህ ህልማቸው ለማሳካት ሲሉ በድንጋይ ላይ ፣ በዛፍ ግንድ ስር እና በወደሙ የመማሪያ ክፍሎች ውስጥ ቁጭ ብለው ለመማር እየታገሉ ይገኛሉ።

የትግራይ ልጆች / ተማሪዎች በድንጋይ ላይ ተቀምጠው የሚማሩበትን ጊዜ ለማሳጠር ብዙ ጥረት ይጠይቃል ተብሏል።

ይህን ችግር ለመፍታት ሁሉም ርብርብ እንዲያደርግ እየተጠየቀ ሲሆን ባለሃብቱ ዘርኡ ገብረሊባኖስ ፤ በሰለኽለኻ በድንጋይ ላይ ተቀምጠው ለሚማሩ ተማሪዎች ወንበር መግዣ ይሆን ዘንድ 1 ሚሊዮን ብር ማበርከታቸውን ከድምፂ ወያነ የተገኘው መረጃ ያሳያል።

በሌላ በኩል ፤ ባለሃብቱ ዘርኡ በሰሜናዊ ምዕራብ ትግራይ ፅምብላ ወረዳ ለሚያስገነበቱ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ዛሬ የመሰረት ድንጋይ የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት ተቀምጧል።

Photo Credit ፦ ድምፂ ወያነ / ፕሮፌሰር ክንደያ ገ/ህይወት

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Voice message
#Update

ፖሊስ ስለ #ወለንጪቲ ምን አለ ?

በኦሮሚያ ክልል፣ ምስራቅ ሸዋ ዞን የቦሰት ወረዳ ፖሊስ ፤ ትላንት ማክሰኞ ታጣቂዎች በወለንጪቲ ከተማ ላይ ጥቃት ከፍተው እንደነበር በማረጋገጥ የታጣቂዎቹ የጥቃት ዓላማ " እስረኞችን ለማስፈታት ነበር " ብሏል።

ፖሊስ ይህን ያለው ለቢቢሲ አማርኛው አገልግሎት በሰጠው ቃል ነው።

የቦሰት ወረዳ ፖሊስ አዛዥ ኮማንደር መሐመድ ሱፋ ምን አሉ ?

- በወለንጪቲ ከተማ የተፈጸመው ጥቃት በኦነግ ሸኔ / እራሱን የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት እያለ በሚጠራ ኃይል ነው ብለዋል።

- ትላንት አመሻሽ ወደ 11 ሰዓት አካባቢ ወደ ወለንጪቲ ከተማ ዘልቀው ለመግባት ባደረጉት ሙከራ ፤ በንጹሃን ሰዎች ላይ ሞትና ጉዳት አደርሰዋል ሲሉ ገልጸዋል። በዚህም ሁለት ንፁሃን መገደላቸውን ፣ ሁለት ንፁሃን መጎዳታቸውን አመልክተዋል።

- " በዚህ በእኛ ቦሰት ወረዳ ውስጥ ኦነግ ሸኔ የሚባለው ኃይል በሰፊው ይንቀሳቀሳል። በአብዛኛው ጊዜ መንግሥታዊ እና መንግሥታዊ ያልሆኑ ተቋማት ላይ ጉዳት ለማድረስ ይሞክራሉ። ከተማዋ ላይም ጥቃት ለማድረስ ሲጥሩ ነበር። " ብለዋል።

- ታጣቂ ቡድኑ ትላንት 11 ሰዓት አካባቢ በበርካታ ቁጥር ወደ ከተማዋ ለመግባት ሙከራ ያደረገ ሲሆን በአካበቢው የሚንቀሳቀሱ የመንግሥት የፀጥታ ኃይሎች በጥምረት ጥቃቱን ለመከላከል እንደቻሉ አመልክተዋል።

- በከተማዋ ላይ ጥቃት ለመፈጸም ተሰማርተው ከነበሩት ታጣቂዎች ወገን 6 መሞታቸውን እና 4 ደግሞ በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የፖሊስ አዛዡ ተናግረዋል።

- በታጣቂዎች የተፈጸመው ጥቃት እና የተካሄደው የተኩስ ልውውጥ ከ30 ደቂቃ በላይ አልቆየም ፤ የታጣቂዎቹ የጥቃት ዓላማ " እስረኞችን ለማስፈታት ነበር " ብለዋል።

- " በፖሊስ ጽህፈት ቤት ውስጥ ልዩ ልዩ እስረኞች አሉ። ከእነርሱም ወገን ተይዘው የታሰሩ አሉ። " ያሉት አዛዡ " እነዚህን ለማስፈታት ነበር ወደ ፖሊስ ጣቢያው የመጡት " ብለዋል። ነገር ግን ታጣቂዎቹ ወደ ፖሊስ ጣቢያው መግባት እንዳልቻሉ እና በአቅራቢያው ያለው የአገር መከላከያ ሠራዊት ደርሶ እርምጃ በመውሰዱ " የተወሰኑት ሲገደሉ እና ሲቆስሉ የቀሩት ደግሞ የያዙትን በመጣል ወደ ጫካ ሸሽተዋል " ሲሉ ተናግረዋል።

- የወለንጪቱ ከተማ ዛሬ ረቡዕ በተረጋጋ ሁኔታ ውስጥ መሆኗን ተናግረው፤ ወደ ምሥራቁ የአገሪቱ ክፍል የሚያቋርጠው ዋና መንገድ መደበኛ የትራንስፖርት አግልግሎት እየሰጠ መሆኑን አሳውቀዋል።

NB. የፖሊስ አዛዡ ቃላቸውን የሰጡት ለቢቢሲ አማርኛው አገልግሎት ነው።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ በትላንትናው ዕለት በወለንጪቲ ስለነበረው ሁኔታ ትላንት ከተቀበላቸው በተጨማሪ ከሌሎች ቤተሰቦቹ መልዕክቶችን ሲቀበል ነበር።

ቤተሰቦቻችን በከተማው ንፁሃን በተባራሪ ጥይት መገደላቸውን ፤ የቆሰሉም ሰዎች መኖራቸውን አሳውቀዋል።

አንድ የቤተሰባችን አባል ፤ ሁኔታው እጅግ በጣም አስከፊ እንደነበር በመግለፅ እራስሩ እራሱ በቅርብ የማያውቃቸው ሰዎች መገደላቸውን ጠቁሟል።

" የተገደሉት ምንም የማያወቁ ፤ እየተፈጠረ ስለነበረው ነገር መረጃ እንኳን የሌላቸው ንፁህ ሲቪል ሰዎች ናቸው " ብሏል።

በዚህ ቀጠና ያለው ነገር እጅግ በጣም አሳሳቢ ነው ያለው ይኸው የቤተሰባችን አባል ፤ ከዚህ በፊትም ተኩስ መስማት የተለመደ ነው ነገር ግን የትላንቱ እጅግ የከፋ ነበር ብሏል።

በዚህ የወለንጪቲ መስመር ላይ የታጣቂዎች እንቅስቃሴ መኖሩ ፣ ግድያን ጨምሮ ዝርፊያ እገታ እንደሚፈፀም በተደጋጋሚ መጠቆሙ ይታወቃል።

ፎቶ ፦ ፋይል

@tikvahethiopia @tikvah_eth_BOT
#CBEBirr

በሲቢኢ ብር መተግበሪያ ነዳጅ መቅዳት ይበልጥ ቀላል ነው!
***
ወደ ሲቢኢ ብር መተግበሪያ ‘Quick Pay’ በመግባት ‘Fuel Payment’ የሚለውን የአገልግሎት አማራጭ መርጠው
• የነዳጅ ቀጂውን የተመዘገበ ስልክ ቁጥር፣
• የሚገዙትን የነዳጅ ክፍያ መጠን፣
• የነዳጅ አይነት፣
• የሰሌዳ ቁጥርዎን፣ እና
• የሚስጥር ቁጥርዎን አስገብተው ክፍያውን በማከናወን ነዳጅ መቅዳት ይችላሉ፡፡

ስለሲቢኢ ብር አገልግሎት በቂ መረጃ ለማግኘት ወደ 951 ነፃ የጥሪ ማዕከል ይደውሉ!
*****
የሲቢኢ ብር መተግበሪያን ለመጫን ወይም ለማዘመን፡

• ለአንድሮይድ ስልኮች፡
https://play.google.com/store/apps/details?id=prod.cbe.birr

• ለአፕል ስልኮች፡
https://apps.apple.com/us/app/cbebirr/id1600841787
#MoE

ትምህርት ሚኒስቴር  ሀገር አቀፍ ፈተናዎችን መቼ ለመስጠት እቅድ ይዟል ?

ቲክቫህ ኢትዮጵያ የደረሰውና በትምህርት ሚኒስትር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ተፈርሞ ለሁሉም የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች ፣ ለሁሉም የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ፣ ለሁሉም የክልል ትምህርት ቢሮዎች የተሰራጨ አንድ ደብዳቤ የዚህ ዓመት የሀገር አቀፍ ፈተናዎች ሊሰጡ #የታቀደበትን ጊዜ ያመለክታል።

የደብዳቤውን ትክክለኝነት ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከሚመለከታቸው የትምህርት ሚኒስቴር አካላት #ማረጋገጥ ችሏል።

በዚህ መሰረት ፦

1ኛ. በ2014 የ12ኛ ክፍል አጠናቀው ፈተና በመውሰድ በልዩ ሁኔታ የሬሜዲያል ኘሮግራም ተጠቃሚ ለሆኑ ተማሪዎች ለአንድ ሴሚስተር የተሰጠው ትምህርት #በማዕከል የጋራ ፈተና ተዘጋጅቶ ለተቋማት እንዲላክ፤ ተቋማት ፊተናውን የማስተዳደር ውጤት የመግለፅና በ2016 ፍሬሽማን ኘሮግራም ለመከታተል ብቁ ሆነው የተገኙት (ማለትም በተቋማት የውስጥ ፈተና 50 ከመቶ፣ በማዕከል የተዘጋጀውን ፈተና 50 ከመቶ) ተደምሮ በድምሩ 50 ከመቶና ከዚያ በላይ ያስመዘገቡቱን እንዲያሳወቁ፣ ይህ አጠቃላይ ሂደትም እስከ ሰኔ 30 ቀን ድረስ እንዲጠናቀቅ የትምህርት ሚኒስቴር አቅጣጫ አስመቅጧል።

2ኛ. በ2015 ዓ.ም የመውጫ ፈተና ለመውሰድ የተመዘገቡ በግልና በመንግስት ተቋማት የሚገኙ እጩ ምሩቃንና ባለፉት ዓመታት የህግ መውጫ ፈተና ወስደው የማለፊያ ውጤት ያላስመዘገቡት ተማሪዎች የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች የመፈተኛ ማእከላት ውስጥ ፈተናው ከሐምሌ 3 /2015 እስከ ሐምሌ 13 /2015 ባሉት ቀናት ተሰጥቶ እንዲጠናቀቅ አቅጣጫ ተቀምጧል።

3ኛ. የ2015 የ12ኛ ከፍል ማጠቃለያ ፈተና ከሐምሌ 19 እስከ 30 የሚሰጥ ሆኖ የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች ከሐምሌ 15 ቀን ጀምሮ ለዚሁ ሥራ ብቻ ዝግጁ እንዲሆኑ የትምህርት ሚኒስቴር አቅጣጫ አስቀምጧል።

በተጨማሪም እንደ አገር ዓመታዊ የትምህርት ካላንደር ከ2016 ጀምሮ ለማስተካከል ሁሉም ተቋማት ፕሮግራሞቻቸውን በዚሁ ማዕቀፍ አንዲያስተካክሉ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ አሳስበዋል።

ከሀገር አቀፍ ፈተናዎች ጋር በተያያዘ የቲክቫህ ቤተሰብ አባላት የሆኑ ተማሪዎች በማህበራዊ ሚዲያዎች የሚሰራጩ የተለያዩ #ያልተረጋገጡ መረጃዎችን እየሰሙ አለመረጋጋት ውስጥ መግባታቸውን ሲገልፁልን ነበር ፤ በቀጣይም ትምህርት ሚኒስቴር / የሀገር አቀፍ ትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት የሚሰጡትን ትክክለኛ መረጃ #ብቻ እንድትከታተሉ ፤ በቀረው አጭር ጊዜም ዝግጅታችሁን ታጠናክሩ ዘንድ መልዕክት እናስተላልፋለን።

(ከላይ የተያያዘው ደብዳቤ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከሚመለከተው አካል #ትክክለኝነቱን ያረጋገጠው ነው።)

@tikvahethiopia @tikvah_eth_BOT
TIKVAH-ETHIOPIA
#MoE ትምህርት ሚኒስቴር  ሀገር አቀፍ ፈተናዎችን መቼ ለመስጠት እቅድ ይዟል ? ቲክቫህ ኢትዮጵያ የደረሰውና በትምህርት ሚኒስትር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ተፈርሞ ለሁሉም የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች ፣ ለሁሉም የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ፣ ለሁሉም የክልል ትምህርት ቢሮዎች የተሰራጨ አንድ ደብዳቤ የዚህ ዓመት የሀገር አቀፍ ፈተናዎች ሊሰጡ #የታቀደበትን ጊዜ ያመለክታል። የደብዳቤውን ትክክለኝነት ቲክቫህ…
#MoE #ይፋዊ

የትምህርት ሚኒስቴር የ2015 ዓ/ም የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቅያ ሀገር አቀፍ ፈተና የሚሰጥበትን ጊዜ #ይፋ አድርጓል።

ሚኒስቴሩ ፤ የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና ከሐምሌ 19 እስከ ሐምሌ 30/2015 ዓ.ም ድረስ #በመንግስት_ዩኒቨርሲቲዎች ይሰጣል ብሏል።

ዩኒቨርሲቲዎችም ያላቸውን ስራ በማጠናቀቅ ከሐምሌ15/2015 ዓ.ም ጀምሮ ለሚሰጠው የ12ኛ ክፍል ፈተና ራሳቸውን እንዲያዘጋጁ ሚኒስቴሩ አሳስቧል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#MoE #ይፋዊ የትምህርት ሚኒስቴር የ2015 ዓ/ም የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቅያ ሀገር አቀፍ ፈተና የሚሰጥበትን ጊዜ #ይፋ አድርጓል። ሚኒስቴሩ ፤ የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና ከሐምሌ 19 እስከ ሐምሌ 30/2015 ዓ.ም ድረስ #በመንግስት_ዩኒቨርሲቲዎች ይሰጣል ብሏል። ዩኒቨርሲቲዎችም ያላቸውን ስራ በማጠናቀቅ ከሐምሌ15/2015 ዓ.ም ጀምሮ ለሚሰጠው የ12ኛ ክፍል ፈተና ራሳቸውን እንዲያዘጋጁ ሚኒስቴሩ…
#MoE #ይፋዊ

ትምህርት ሚኒስቴር ፤ የዩኒቨርሲቲ እጩ ተመራቂ ተማሪዎች መውጫ ፈተና ከሐምሌ 03/2015 ዓ.ም ጀምሮ እንደሚሰጥ #በይፋ አሳውቋል።

ሚኒስቴሩ የዩኒቨርሲቲ ተመራቂ ተማሪዎች መውጫ ፈተና ከሐምሌ 3 እስከ ሐምሌ 13/2015 ዓ.ም በመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች የመፈተኛ ማዕከላት ይሰጣል ብሏል።

የ2015 ዓ.ም የመውጫ ፈተና ለመውሰድ የተመዘገቡ በግልና በመንግስት ተቋማት የሚገኙ እጩ ምሩቃን በመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች የመፈተኛ ማዕከላት ፈተናውን እንደሚወስዱም ገልጿል።

በ2014 ዓ.ም የህግ መውጫ ፈተና ተፈትነው ማለፊያ ነጥብ ያላስመዘገቡ ተማሪዎችም በዚሁ ጊዜ ፈተናውን የመንግስት ዩኒቨርሲቲ የመፈተኛ ማዕከላት ውስጥ መውሰድ ይችላሉ ሲል ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል።

ትምህርት ሚኒስቴር ፤ የዩኒቨርስቲ መውጫ ፈተናን ለመሥጠት የተለያዩ ዝግጅቶችን ሲያደርግ መቆየቱ አስታውሷል።

@tikvahethiopia
#big5construct

The doors to Big 5 Construct Ethiopia are OPEN NOW.

Come and experience the best and innovative solutions.

Make sure you don’t miss out.
Beat the queue and pre-register online here: https://bit.ly/3oI8P6L
📍 Millennium Hall, Addis Ababa
📅 18 - 20 May 2023
#Tigray

የህፃናት አድን ድርጅት / Save the Children / በትግራይ ክልል ትምህርት ቤቶችን ከስጋት ነፃ ለማድረግ በተሰራ ስራ 1 ሺህ 231 ያልመከኑ ፈንጂዎች መገኘታቸው ገለፀ።

አሀዱ ሬድዮ ፤ የህጻናት አደን ድርጅት በኢትዮጵያ / Save the Children /  የትግራይ ክልል አስተተባባሪ የሆኑትን አቶ አታክልቲ ገብረ ዮሓንስን ዋቢ በማድረግ ባሰራጨው መረጃ ፤ ከሰላም ስምምነቱ በኃላ 1 ሺህ 218 ት/ ቤቶች የተከፈቱ ሲሆን  722ቱ የሚሆኑት በደረሰባቸው ከባድ ጉዳት አገልግሎት አልጀመሩም።

ተማሪዎች 3 ዓመት የትምህርት ገበታቸው ላይ አለመገኘታቸውን ያነሱት አስተባባሪው አሁን ላይ ለ39 ሺህ መምህራን የ3 ወር  ደሞዝ መከፈሉን አሳውቀዋል።

ት/ቤቶችን ከስጋት ነጻ ለማድረግና የተማሪዎቹ ደህንነት እንዲጠበቅ ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር የተለያዩ ስራዎች መሰራታቸውን እና ከክልሉ ትምህርት ቢሮ ጋር በተሰራው ስራ በ1 ሺ 544 ትምህርት ቤቶች ውስጥ 1 ሺህ 231  #ያልመከኑ ፈንጂዎች መገኘታቸውን  ጠቁመዋል።

ድርጅቱ የተሸከርካሪ እና ሌሎችም ድጋፎችን በማድረግ በጋራ በተሰራው ስራ ትምህርት ቤቶችን ከስጋት ነጻ ማድረግ እንደተቻለ ተናግረዋል፡፡

ለ40 ሺህ ተማሪዎች በ59 ትምህርት ቤቶች ላይ የህጻናት አደን ድርጅት በኢትዮጵያ የተለያዩ ድጋፎችን ማድረጉን አቶ አታክልቲ ገብረ ዮሓንስ ለአሐዱ ገልፀዋል።

#አሐዱ #SavetheChildren

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" በአስቸኳይ መስጂዶችን ማፍረስ አቁሙ ፤ የፈረሱትንም በፍጥነት መልሳችሁ አሰሩ ፤ ህዝበ ሙስሊሙንም በይፋ ይቅርታ ጠይቁ " - የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የኢትዮጵያ የእስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት በአዲሱ "በሸገር ከተማ " መስጂዶች እየፈረሱ መሆኑን በመግለፅ ይህ ድርጊት በአስቸኳይ እንዲቆም አሳሰበ። ምክር ቤቱ ለኦሮምያው ክልላዊ መንግስት ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሽመልስ…
ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ደብዳቤ ተፃፈ።

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፤ ለጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ደብዳቤ ፃፈ።

ጠቅላይ ምክር ቤቱ ፤ በደብዳቤው በሸገር ከተማ እያፈረሱ ስላሉ መስጂዶች አስቸኳይ መፍትሄ እንዲሰጥ ጠይቋል።

" በቅርቡ በአዲስ መልኩ ' ሸገር ከተማ ተብሎ ' በተመሠረተው ከተማ ህገወጥ በሚል በርካታ መስጂዶች በከተማ አስተዳደሩ አማካኝነት እየፈረሱብን ይገኛል " ያለው ምክር ቤቱ  " በመስጅዶች ፈረሳ ጉዳይ ላይ ከከተማ አስተዳደሩ ከንቲባ ጋር በስልክ በመነጋገር መፍትሄ ላይ እንደደረስን ብናምንም የከተማ አስተዳደሩ ግን በረመዳን ወር ለጊዜው የመስጂዶች ፈረሳውን እንዲቆም በማድረግ ከረመዳን በኋላ የመስጂዶች ፈረሳ በአዲስ መልክ በብዛት ቀጥሏል " ሲል ለጠ/ሚኒስትሩ በፃፈው ደብዳቤ አመልክቷል።

በመሆኑም የመስጂዶች ፈረሳ ጉዳይ በከተማ አስተዳደሩ " ህገ-ወጥ " ስለተባለ ብቻ በቀላሉ የሚታይ ሳይሆን የህዝበ ሙስሊሙ የኃይማኖት ዋነኛ ህልውና በመሆኑ በአስቸኳይ እንዲቆም ለኦሮሚያ ክልል ፕሬዝዳንት አቶ ሽመልስ አብዲሳ ደብዳቤ ብንፅፍም እስካሁን ምላሽ አላገኘም ብሏል።

" በስልክም በጉዳዩ ላይ ለመነጋጋር ያደረግነው ተደጋጋሚ ሙከራ አልተሳካም " ሲል አክሏል።

" ተጨማሪ መስጅዶች የማፍረስ ተግበሩ ለክልሉ ፕሬዜዳንት ደብዳቤ ከፃፍንና በጉዳዩ ላይ በአካል በመገናኘት ለመነጋገር ቀጠሮ እየጠየቅን ባለንበት ወቅት መስጅዶች እየፈረሱ መሆኑ የጠቅላይ ምክር ቤት አመራሮችን እንዲሁም ሕዝበ ሙስሊሙም በእጅጉ አሳዝኗል " ብሏል።

ጠቅላይ ምክር ቤቱ በደብዳቤው ፥ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ፤ እንደ ጠቅላይ ሚኒስተርና እንደ የብልጽግና ፓርቲ መሪ ለመስጂዶች ፈረሳ ጉዳይ አስቸኳይ መፍትሄ የመስጠት ሙሉ ስልጣኑ እንዳላቸው በማመን ለችግሩ የማያዳግም መፍትሄ እንዲሰጡ ጠይቋል።

@tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#አቢሲንያ_ባንክ

አፖሎን በመጠቀም የATM ካርድዎን አገልግሎት እንዴት ማቋረጥ (Block) ወይም አገልግሎቱን መልሶ ማግኘት (Unblock) ይቻላል?

ስለ አፖሎ የዲጅታል ባንክ መተግበሪያ አጠቃቀም እና የተለያዩ መረጃዎች ለማግኘት የአፖሎ የቴሌግራም ቻነልን ይቀላቀሉ።
https://t.iss.one/apollodigitalproduct

#Apollodigitalproduct #AbyssiniaDigital #Abyssiniabank #poweredbybankofabyssinia #BankofAbyssinia #የሁሉም_ምርጫ #The_Choice_For_all
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#ይፋዊ

የትምህርት ሚኒስቴር ፤ የሪሜዲያል ፕሮግራም ተማሪዎች ፈተና ማጠናቀቂያ ጊዜን በይፋ አሳውቋል።  

በ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና ወስደው በልዩ ሁኔታ በሪሜዲያል ፕሮግራም ተጠቃሚ የሆኑ  ተማሪዎች ፈተና ተዘጋጅቶ እንዲላክና አጠቃላይ ሂደቱ  እስከ ሰኔ 30/2015 ዓ.ም ድረስ እንዲጠናቀቅ በትምህርት ሚኒስቴር አቅጣጫ ተቀምጧል።

ፈተናውም በዩኒቨርሲቲ ቆይታቸው በተሰጠው ትምህርት መሠረት ከማዕከል በጋራ ተዘጋጅቶ ለተቋማት እንዲላክ  ተብሏል።

በዚህም መሰረት በሴሚስተሩ በተሰጠው ትምህርት የተቋማት የውስጥ ፈተና ውጤት 50 ከመቶ እንዲሁም በማዕከል የተዘጋጀው ፈተና ውጤት 50 ከመቶ  ይይዛል ተብሏል።

ተማሪዎችም በ2016 ዓ.ም ትምህርታቸውን ለመከታተል ብቁ ሆነው ለመገኘት የሁለቱ ድምር አማካይ 50 ከመቶና በላይ ውጤት ማስመዝገብ ይጠበቅባቸዋል።

ዩኒቨርሲቲዎችም ፈተናውን በማስተዳደርና ውጤት በመግለጽ በ2016 የፍሬሽማን ፕሮግራም ለመከታተል ብቁ የሆኑ ተማሪዎችን  ለይተው እስከ ሰኔ 30 ቀን 2015 ዓ/ም እንዲያጠናቅቁ ተገልጿል።

ዩኒቨርሲቲዎች ያላቸውን ስራ በማጠናቀቅ የ2016 የትምህርት ካሌንደር የተስተካከለ እንዲሆን ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ  ሚኒስቴሩ አሳስቧል።

#ትምህርት_ሚኒስቴር

@tikvahethiopia