#AdigratUniversity
የዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ በዛሬው ዕለት በላከልን መልዕክት ፦
1. የዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ መደበኛ ተማሪዎች ሆናችሁ ላላፉት ሁለት ዓመታት በሌሎች ዩኒቨርሲቲዎች ተመድባችሁ የመማር እድል ያላጋጠማችሁ፤
2. በዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ የተከታታይ መርሃ ግብር ተማሪዎች፤
3. በሌሎች ዩኒቨርሲቲዎች በመደበኛነት ስትማሩ ቆይታችሁ፣ ላለፉት ሁለት አመታት አቛርጣችሁ አሁን ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ ለመመዝገብ የምትፈልጉ ተማሪዎች፤
በዚህ ማስፈንጠሪያ https://197.156.104.178/ በኦንላይን የቅድመ ምዝገባ ቅፅ ከግንቦት 03 አስከ 15/2015 እንድትሞሉ ጥሪ አቅርቦላችኃል።
ዩኒቨርሲቲው ትምህርት የሚጀመርበት ቀን በቅርቡ እንደሚያሳውቅ ገልጿል።
@tikvahethiopia
የዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ በዛሬው ዕለት በላከልን መልዕክት ፦
1. የዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ መደበኛ ተማሪዎች ሆናችሁ ላላፉት ሁለት ዓመታት በሌሎች ዩኒቨርሲቲዎች ተመድባችሁ የመማር እድል ያላጋጠማችሁ፤
2. በዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ የተከታታይ መርሃ ግብር ተማሪዎች፤
3. በሌሎች ዩኒቨርሲቲዎች በመደበኛነት ስትማሩ ቆይታችሁ፣ ላለፉት ሁለት አመታት አቛርጣችሁ አሁን ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ ለመመዝገብ የምትፈልጉ ተማሪዎች፤
በዚህ ማስፈንጠሪያ https://197.156.104.178/ በኦንላይን የቅድመ ምዝገባ ቅፅ ከግንቦት 03 አስከ 15/2015 እንድትሞሉ ጥሪ አቅርቦላችኃል።
ዩኒቨርሲቲው ትምህርት የሚጀመርበት ቀን በቅርቡ እንደሚያሳውቅ ገልጿል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#AddisAbaba የአዲስ አበባ ከተማ ትምህርት ቢሮ የ6ኛ እና 8 ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተና የሚሰጥባቸውን ቀናት ይፋ አደርጓል። የ8ኛ ክፍል ፈተና ሰኔ 19 እና 20 እንዲሁም የ6ኛ ክፍል ፈተና ሰኔ 26 እና 27 እንደሚሰጥ ተገልጿል። ቢሮው ከተማ አቀፍ ፈተናዎቹን ውጤታማ በሆነ መልኩ ለመስጠት ከፍተኛ ዝግጅት ሲያደርግ መቆየቱን የገለፀ ዲሆን ትምህርት ቤቶች ተማሪዎቹን የበለጠ ማዘጋጀት እንዲችሉ…
" ፈተናው የሚሰጥበት ቀን ይስተካከል " - የአዲስ አበባ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ም/ቤት
የአዲስ አበባ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ም/ቤት ፤ ከተማ አቀፉ የ8ኛ ክፍል ፈተና መስጫ ቀን እንዲስተካከል ለከተማው ትምህርት ቢሮ በፃፈው ደብዳቤ አሳስቧል።
የከተማው ትምህርት ቢሮ የ2015 ትምህርት ዘመን የ8ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተና ሰኔ 19-20/2015 ለመስጠት መታቀዱን ማሳወቁ ይታወሳል።
ነገር ግን ይህ ቀን በካላንደር ዝግ የሆኑ የህዝብ በዓላትን ባገናዘበ መልኩ የወጣ እቅድ እንዳልሆነ የአዲስ አበባ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ም/ቤት አስገንዝቧል።
ምክር ቤቱ ፤ " በካላንደር ዝግ የሆኑ የህዝብ በዓላትን ባገናዘበ መልኩ እቅድ ማዘጋጀት የቢሮው ሃላፊነት ቢሆንም ሰኔ 21 እና 22/2015 የአረፋና የዒድ አልአድሀ በዓል ቀን እና ዋዜማ ፈተና ለመስጠት ማቀድ አግባብነት የለውም " ብሏል።
እቅዱ ተማሪዎች ተረጋግተው ፈተና ላይ እንዳይቀመጡ የሚያደርግ ተግባር ነው ሲልም ኮንኖታል።
የፈተናው ቀን ከዒድ አልአድሐ በዓል ከ3 ቀናት በፊት ወይም ከ3 ቀናት በኃላ እንዲሆን ይህም በአንድ ሳምንት ጊዜ ውስጥ ለህዝብ ይፋ እንዲደረግ አሳስቧል።
@tikvahethiopia
የአዲስ አበባ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ም/ቤት ፤ ከተማ አቀፉ የ8ኛ ክፍል ፈተና መስጫ ቀን እንዲስተካከል ለከተማው ትምህርት ቢሮ በፃፈው ደብዳቤ አሳስቧል።
የከተማው ትምህርት ቢሮ የ2015 ትምህርት ዘመን የ8ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተና ሰኔ 19-20/2015 ለመስጠት መታቀዱን ማሳወቁ ይታወሳል።
ነገር ግን ይህ ቀን በካላንደር ዝግ የሆኑ የህዝብ በዓላትን ባገናዘበ መልኩ የወጣ እቅድ እንዳልሆነ የአዲስ አበባ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ም/ቤት አስገንዝቧል።
ምክር ቤቱ ፤ " በካላንደር ዝግ የሆኑ የህዝብ በዓላትን ባገናዘበ መልኩ እቅድ ማዘጋጀት የቢሮው ሃላፊነት ቢሆንም ሰኔ 21 እና 22/2015 የአረፋና የዒድ አልአድሀ በዓል ቀን እና ዋዜማ ፈተና ለመስጠት ማቀድ አግባብነት የለውም " ብሏል።
እቅዱ ተማሪዎች ተረጋግተው ፈተና ላይ እንዳይቀመጡ የሚያደርግ ተግባር ነው ሲልም ኮንኖታል።
የፈተናው ቀን ከዒድ አልአድሐ በዓል ከ3 ቀናት በፊት ወይም ከ3 ቀናት በኃላ እንዲሆን ይህም በአንድ ሳምንት ጊዜ ውስጥ ለህዝብ ይፋ እንዲደረግ አሳስቧል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update የግንቦት 2015 ዓ.ም ርክበ ካህናት የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ ዛሬ ተከፍቷል። ይህን በተመለከተ ቅዱስ ፓትርያርኩ የመክፈቻ ንግግር አቅርበዋል። ምን አሉ ? ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ባቀረቡት ንግግር ፥ በአሁኑ ጊዜ ቤተክርስቲያኗ እንደ ቤተክርስቲያን፣ ሕዝቡም እንደ ሕዝብ በፈተና…
" የተከፋፈለ ሲኖዶስ የለም "
የ2015 ዓ.ም የቅዱስ ሲኖዶስ ርክበ ካህናት የሁለተኛው ቀን ጉባኤ ዛሬ ሲካሄድ ውሏል።
ይህ አስመልክቶ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ (ዶ/ር) የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ እና የኒውዮርክና አካባባቢዋ አኅጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ማብራሪያ ሰጥተዋል።
ብፁዕነታቸው በሁለተኛው ቀን በነበረው የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ሁለት ርዕሰ ጉዳዮች መወያያየቱን ገልጸዋል።
ቅዱስ ሲኖዶስ በቀዳሚነት በሀገር ሰላም ዙሪያ በተነሳው ርዕሰ ጉዳይ ጉባኤው ብዙ ሲወያይ ከቆየ በኋላ በመጨረሻም " ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ሁሉን ማድረግ ትችላለች ፤ ምእመናንም የቅድስት ቤተ ክርስቲያንን ድምጽ ይሰማሉ " የሚለው ሐሳብ አሸንፎ በዚህ ጉዳይ ላይ ቅዱስ ሲኖዶስን ወክለው የሚሰሩ ሦስት ብፁዓን አባቶች ተመርጠው የሀገር ሰላምን በተመለከተ ረዥም ርቀት በመሔድና ከሚመለከተው አካል ጋር ሁሉ በመነጋገር በሀገር ሰላም ዙሪያ ከፍተኛ እንቅስቃሴ እንዲያደርጉና አሁን ካለንበት መከራ የምንወጣበትን መፍትሔ እንዲያመጡ ተመርጠዋል።
በቀጣይነት በወቅታዊ የቅድስት ቤተ ክርስቲን ችግር አስመልክቶ በትግራይ እና በኦሮሚያ አህጉረ ስብከት የነበሩትን ችግሮች መነሻ በማድረግ ፦
ሀ/ በክልል ትግራይ የተፈጠረውን ችግር ለመፍታት የትግራይ አባቶችና አባላቱን በአካል ለማነጋገር በቋሚ ሲኖዶስ የተመረጠውን ኮሚቴ ምልዓተ ጉባኤው ተቀብሎ የጀመረውን ሥራ እንዲቀጥል ወስኗል።
በተጨማሪም ፦
👉 ተቋርጦ የነበረው በጀት እንዲለቀቅ፤
👉 የማጽናኛ መርሐ ግብር እንዲካሄድና በተቻለ መጠን አስቸኳይ እርዳታ እንዲደረግ በጉባኤው ተወስኗል።
ለ/ በጥር 14 ቀን 2015 ዓ.ም የተከሰተውን የቤተ ክርስቲያን ፈተና በተመለከተ ሰፊ ውይይት ከተደረገ እና ወደ መግባቢያ ሐሳቦች መደረሱ ተገልጿል።
በስድስት አኅጉረ ስብከቶች ምንም ዓይነት የቤተ ክርስቲያን አገልግሎት እየተሰጠ አለመሆኑን ቅዱስ ሲኖዶስ የደረሰውን መረጃ መነሻ በማድረግ
የማያዳግም የመፍትሔ ለመስጠት ጉዳዩ በቀጥታ ከሚመለከታቸው ከሦስቱ ብፁዓን አባቶች ጋር አራት ብፁዓን አባቶችን ተጨማሪ በማድረግ
በቀጥታ የነበረው ችግር ሙሉ በሙሉ መቀረፉንና ከአንድ ሲኖዶስ ውጪ ሌላ አለመኖሩን ለመንግሥት አካላት በጋራ ሔደው የተደረሰበትን ስምምነት ተገቢውን መረጃ እንዲሰጡ ፦
- ብፁዕ አቡነ ኤርሚያስን
- ብፁዕ አቡነ ሩፋኤልን
- ብፁዕ አቡነ ናትናኤልን
- ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስን
- ብፁፅ አቡነ ሳዊሮስን
- ብፁዕ አቡነ ዜና ማርቆስን እና ብፁዕ አቡነ ኤውስጣቴዎስን
በመመደብ እነዚህ ሰባት ብፁዓን አባቶች በአንድ ላይ ከመንግሥት ጋር በመነጋገር ፍጹም በሆነ የመግባባት ስምምነት መፈጠሩን ገልጸው ከእንግዲህ በኋላ የተከፋፈለ ሲኖዶስ እንደሌለ እና ከዚህ ሐሳብ ውጪ የሆነ አካል ከቅድስት ቤተ ክርስቲያን ሕግና ሥርዓት ውጪ የሆነ መሆኑን በአንድነት ለመንግሥት እንዲያሳውቁ መወከላቸው ተገልጿል።
ብፁዕነታቸው " በቀጣይ ያሉንን የመወያያ ርዕሰ ጉዳዮች በዚህ መልኩ በመግባባትና በመተማመን በመፍታት በሀገርና በቅድስት ቤተ ክርስቲያንን ሰላምና አንድነትን በማያዳግም ሁኔታ የሚያውጅ ቆይታ ይሆን ዘንድ መላው ሕዝበ ክርስቲያን በጸሎት አስቡን " ሲሉ አባታዊ መልእክታቸውንና ቡራኬአቸውን ሰጥተዋል።
ምንጭ፦ EOTC TV
@tikvahethiopia
የ2015 ዓ.ም የቅዱስ ሲኖዶስ ርክበ ካህናት የሁለተኛው ቀን ጉባኤ ዛሬ ሲካሄድ ውሏል።
ይህ አስመልክቶ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ (ዶ/ር) የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ እና የኒውዮርክና አካባባቢዋ አኅጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ማብራሪያ ሰጥተዋል።
ብፁዕነታቸው በሁለተኛው ቀን በነበረው የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ሁለት ርዕሰ ጉዳዮች መወያያየቱን ገልጸዋል።
ቅዱስ ሲኖዶስ በቀዳሚነት በሀገር ሰላም ዙሪያ በተነሳው ርዕሰ ጉዳይ ጉባኤው ብዙ ሲወያይ ከቆየ በኋላ በመጨረሻም " ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ሁሉን ማድረግ ትችላለች ፤ ምእመናንም የቅድስት ቤተ ክርስቲያንን ድምጽ ይሰማሉ " የሚለው ሐሳብ አሸንፎ በዚህ ጉዳይ ላይ ቅዱስ ሲኖዶስን ወክለው የሚሰሩ ሦስት ብፁዓን አባቶች ተመርጠው የሀገር ሰላምን በተመለከተ ረዥም ርቀት በመሔድና ከሚመለከተው አካል ጋር ሁሉ በመነጋገር በሀገር ሰላም ዙሪያ ከፍተኛ እንቅስቃሴ እንዲያደርጉና አሁን ካለንበት መከራ የምንወጣበትን መፍትሔ እንዲያመጡ ተመርጠዋል።
በቀጣይነት በወቅታዊ የቅድስት ቤተ ክርስቲን ችግር አስመልክቶ በትግራይ እና በኦሮሚያ አህጉረ ስብከት የነበሩትን ችግሮች መነሻ በማድረግ ፦
ሀ/ በክልል ትግራይ የተፈጠረውን ችግር ለመፍታት የትግራይ አባቶችና አባላቱን በአካል ለማነጋገር በቋሚ ሲኖዶስ የተመረጠውን ኮሚቴ ምልዓተ ጉባኤው ተቀብሎ የጀመረውን ሥራ እንዲቀጥል ወስኗል።
በተጨማሪም ፦
👉 ተቋርጦ የነበረው በጀት እንዲለቀቅ፤
👉 የማጽናኛ መርሐ ግብር እንዲካሄድና በተቻለ መጠን አስቸኳይ እርዳታ እንዲደረግ በጉባኤው ተወስኗል።
ለ/ በጥር 14 ቀን 2015 ዓ.ም የተከሰተውን የቤተ ክርስቲያን ፈተና በተመለከተ ሰፊ ውይይት ከተደረገ እና ወደ መግባቢያ ሐሳቦች መደረሱ ተገልጿል።
በስድስት አኅጉረ ስብከቶች ምንም ዓይነት የቤተ ክርስቲያን አገልግሎት እየተሰጠ አለመሆኑን ቅዱስ ሲኖዶስ የደረሰውን መረጃ መነሻ በማድረግ
የማያዳግም የመፍትሔ ለመስጠት ጉዳዩ በቀጥታ ከሚመለከታቸው ከሦስቱ ብፁዓን አባቶች ጋር አራት ብፁዓን አባቶችን ተጨማሪ በማድረግ
በቀጥታ የነበረው ችግር ሙሉ በሙሉ መቀረፉንና ከአንድ ሲኖዶስ ውጪ ሌላ አለመኖሩን ለመንግሥት አካላት በጋራ ሔደው የተደረሰበትን ስምምነት ተገቢውን መረጃ እንዲሰጡ ፦
- ብፁዕ አቡነ ኤርሚያስን
- ብፁዕ አቡነ ሩፋኤልን
- ብፁዕ አቡነ ናትናኤልን
- ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስን
- ብፁፅ አቡነ ሳዊሮስን
- ብፁዕ አቡነ ዜና ማርቆስን እና ብፁዕ አቡነ ኤውስጣቴዎስን
በመመደብ እነዚህ ሰባት ብፁዓን አባቶች በአንድ ላይ ከመንግሥት ጋር በመነጋገር ፍጹም በሆነ የመግባባት ስምምነት መፈጠሩን ገልጸው ከእንግዲህ በኋላ የተከፋፈለ ሲኖዶስ እንደሌለ እና ከዚህ ሐሳብ ውጪ የሆነ አካል ከቅድስት ቤተ ክርስቲያን ሕግና ሥርዓት ውጪ የሆነ መሆኑን በአንድነት ለመንግሥት እንዲያሳውቁ መወከላቸው ተገልጿል።
ብፁዕነታቸው " በቀጣይ ያሉንን የመወያያ ርዕሰ ጉዳዮች በዚህ መልኩ በመግባባትና በመተማመን በመፍታት በሀገርና በቅድስት ቤተ ክርስቲያንን ሰላምና አንድነትን በማያዳግም ሁኔታ የሚያውጅ ቆይታ ይሆን ዘንድ መላው ሕዝበ ክርስቲያን በጸሎት አስቡን " ሲሉ አባታዊ መልእክታቸውንና ቡራኬአቸውን ሰጥተዋል።
ምንጭ፦ EOTC TV
@tikvahethiopia
#አቢሲንያ_ባንክ
ጊዜ ገና ብዙ ያሳየናል !
አፖሎን ይበልጥ ተመራጭ የሚያደርገው የጣት አሻራዎን በመጠቀም የባንክ ሒሳብዎን ደህንነት አስተማማኝ ማድረግ ማስቻሉ ነው።
መተግበሪያውን ለማውረድ ሊንኩን ይጠቀሙ።
https://apollo.bankofabyssinia.com/download-apollo
#Apollodigitalproduct #AbyssiniaDigital #Abyssiniabank #poweredbybankofabyssinia #BankofAbyssinia #የሁሉም_ምርጫ #The_Choice_For_all
ጊዜ ገና ብዙ ያሳየናል !
አፖሎን ይበልጥ ተመራጭ የሚያደርገው የጣት አሻራዎን በመጠቀም የባንክ ሒሳብዎን ደህንነት አስተማማኝ ማድረግ ማስቻሉ ነው።
መተግበሪያውን ለማውረድ ሊንኩን ይጠቀሙ።
https://apollo.bankofabyssinia.com/download-apollo
#Apollodigitalproduct #AbyssiniaDigital #Abyssiniabank #poweredbybankofabyssinia #BankofAbyssinia #የሁሉም_ምርጫ #The_Choice_For_all
#ExodusPhysiotherapy
በኤክሶደስ የፊዚዮቴራፒ ስፔሻሊቲ ክሊኒክ የምንሰጣቸው የህክምና አገልግሎቶች ፦
- ለአንገት፣ለትክሻ፣ለወገብ ህመም;ከዲስክ መንሸራተት ጋር በተያያዘ ለሚመጣ ችግር፣ ለማዞር ወይንም ሚዛን የመጠበቅ ችግር፣ ለፊት መጣመም፣ ከስትሮክ በኋላ ለሚመጣ ግማሽ የሰውነት ክፍል መዛል፣ ለስፖርታዊ ጉዳቶች ፣ ከህፃናት የእድገት ውስንነት ጋር በተያያዘ ለሚከሰቱ የእንቅስቃሴ ችግሮች ፣ በአጠቃላይ ከነርቭ፣ ከጡንቻ፣ ከመገጣጠሚያ ጋር በተገናኘ ለሚከሰቱ ችግሮች መፍትሄ ያግኙ ይዳኑ !
የስራ ሰዓት ዘወትር ከሰኞ እስከ ቅዳሜ #ከጠዋቱ 2:30 እስከ #ምሽት 1:00 ሰዓት
አድራሻችን ፦ 22 ከመክሊት ህንፃ ፊት ለፊት ባሮ ህንፃ ላይ እንገኛለን።
ስልክ ፦ 0979099909/ 0911039377
በቴሌግራም ቻናላችን ጠቃሚ መረጃ ያግኙ
https://t.iss.one/ExodPhysioClinic
በኤክሶደስ የፊዚዮቴራፒ ስፔሻሊቲ ክሊኒክ የምንሰጣቸው የህክምና አገልግሎቶች ፦
- ለአንገት፣ለትክሻ፣ለወገብ ህመም;ከዲስክ መንሸራተት ጋር በተያያዘ ለሚመጣ ችግር፣ ለማዞር ወይንም ሚዛን የመጠበቅ ችግር፣ ለፊት መጣመም፣ ከስትሮክ በኋላ ለሚመጣ ግማሽ የሰውነት ክፍል መዛል፣ ለስፖርታዊ ጉዳቶች ፣ ከህፃናት የእድገት ውስንነት ጋር በተያያዘ ለሚከሰቱ የእንቅስቃሴ ችግሮች ፣ በአጠቃላይ ከነርቭ፣ ከጡንቻ፣ ከመገጣጠሚያ ጋር በተገናኘ ለሚከሰቱ ችግሮች መፍትሄ ያግኙ ይዳኑ !
የስራ ሰዓት ዘወትር ከሰኞ እስከ ቅዳሜ #ከጠዋቱ 2:30 እስከ #ምሽት 1:00 ሰዓት
አድራሻችን ፦ 22 ከመክሊት ህንፃ ፊት ለፊት ባሮ ህንፃ ላይ እንገኛለን።
ስልክ ፦ 0979099909/ 0911039377
በቴሌግራም ቻናላችን ጠቃሚ መረጃ ያግኙ
https://t.iss.one/ExodPhysioClinic
ዘማሪት ሂሩት በቀለ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየች።
ዘማሪት ሂሩት ዘማሪ ከመሆኗ በፊት በህዝብ ዘንድ ዛሬም ድረስ የሚደመጡና የሚወደዱ እጅግ በርካታ የዘፈን ስራዎች ነበሯት።
ከዘፈን ዓለም ወጥታ ወደ መንፈሳዊ ዓለም ከገባች በኃላ የተለያዩ የመዝሙር አልበሞችን ሰርታ ለአድማጭ አቅርባለች።
ዘማሪ ሂሩት ዛሬ በ80 ዓመቷ ከዚህ ዓለም በሞት የተለየች ሲሆን ፤ የ7 ልጆች እናት ፣ የ10 ልጆች አያት እና የ7 ልጆች ቅድመ አያት ነበረች።
@tikvahethiopia
ዘማሪት ሂሩት ዘማሪ ከመሆኗ በፊት በህዝብ ዘንድ ዛሬም ድረስ የሚደመጡና የሚወደዱ እጅግ በርካታ የዘፈን ስራዎች ነበሯት።
ከዘፈን ዓለም ወጥታ ወደ መንፈሳዊ ዓለም ከገባች በኃላ የተለያዩ የመዝሙር አልበሞችን ሰርታ ለአድማጭ አቅርባለች።
ዘማሪ ሂሩት ዛሬ በ80 ዓመቷ ከዚህ ዓለም በሞት የተለየች ሲሆን ፤ የ7 ልጆች እናት ፣ የ10 ልጆች አያት እና የ7 ልጆች ቅድመ አያት ነበረች።
@tikvahethiopia
#SUDAN
" ወደ ተኩስ አቁም ለማምራት መደላደል ነው " የተባለ ስምምነት በሱዳን ጦር እና ፈጥኖ ደራሽ ኃይል (RSF) መካከል ተፈረም።
በሱዳን ወጊያ ላይ የሚገኙት ሁለቱ ተፋላሚ ኃይሎች ሳዑዲ አረቢያ ፣ ጅዳ ሄደው ባካሄዱት ድርድር የመጀመሪያ ስምምነት ላይ መድረሳቸው ተነግሯል።
" የቅድሚያ ስምምነት መርሆች " መፈራረማቸውን የዘገበው አል አረቢያ ሁለቱም ወገኖች ለሱዳን ሉዓላዊነትና አንድነት ያላቸውን ቁርጠኝነት ገልጸዋል ብሏል።
ሁለቱ ኃይሎች የሱዳን ወዳጆች የሚያደርጉትን ጥረት በደስታ እንቀበላለን ማለታቸውንም ተነግሯል።
በመጀመሪያው ስምምነት መሰረት ፤ በሰላማዊ ሰዎች ላይ ጉዳት ከሚያደርሱ ጥቃቶች እንደሚታቀቡ ፤ በሱዳን ያሉ ሲቪሎች ያሉባቸውን አካባቢዎች ለቀው እንዲወጡ ያስገድዳል።
ተፋላሚ ኃይሎቹ በሱዳን የመንግስትና የግል ተቋማትን ለቆ ለመውጣት፣ የህክምና ባለሙያዎችን እና የህዝብ ተቋማትን መጠበቅ፣ የሰብዓዊ እርዳታ አቅርቦት መፍቀድ ያላቸውን ቁርጠኝነት ገልጸዋል።
የሳዑዲ አረቢያ የውጭ ጉዳይ ሚንስቴር ስምምነቱን በደስታ መቀበሉን ገልጾ፤ የጅዳ ድርድር በሁለቱ ወገኖች መካከል እስከ 10 ቀናት የሚቆይና የተኩስ አቁም ስምምነት ላይ ለመድረስ እንደሚያተኩር አስታውቋል።
" የደህንነት እርምጃዎቹ በአሜሪካ፣ በሳዑዲ አረቢያ እና በዓለም አቀፉ ማህበረሰብ የሚደገፍ የተኩስ አቁም ቁጥጥር ዘዴን ያካትታል " ብሏል።
የአሜሪካ መንግስት በሰጠው መግለጫ ስምምነቱ የተኩስ አቁም ስምምነት እንዳልሆነ ተናግሯል። የጂዳ ስምምነት ወደ ተኩስ አቁም ስምምነት እንዲያመራ መደላደል እንደሆነም ተነግሯል።
መረጃው የአል አረቢያ ቴሌቪዥን እና አል አይን ኒውስ ነው።
@tikvahethiopia
" ወደ ተኩስ አቁም ለማምራት መደላደል ነው " የተባለ ስምምነት በሱዳን ጦር እና ፈጥኖ ደራሽ ኃይል (RSF) መካከል ተፈረም።
በሱዳን ወጊያ ላይ የሚገኙት ሁለቱ ተፋላሚ ኃይሎች ሳዑዲ አረቢያ ፣ ጅዳ ሄደው ባካሄዱት ድርድር የመጀመሪያ ስምምነት ላይ መድረሳቸው ተነግሯል።
" የቅድሚያ ስምምነት መርሆች " መፈራረማቸውን የዘገበው አል አረቢያ ሁለቱም ወገኖች ለሱዳን ሉዓላዊነትና አንድነት ያላቸውን ቁርጠኝነት ገልጸዋል ብሏል።
ሁለቱ ኃይሎች የሱዳን ወዳጆች የሚያደርጉትን ጥረት በደስታ እንቀበላለን ማለታቸውንም ተነግሯል።
በመጀመሪያው ስምምነት መሰረት ፤ በሰላማዊ ሰዎች ላይ ጉዳት ከሚያደርሱ ጥቃቶች እንደሚታቀቡ ፤ በሱዳን ያሉ ሲቪሎች ያሉባቸውን አካባቢዎች ለቀው እንዲወጡ ያስገድዳል።
ተፋላሚ ኃይሎቹ በሱዳን የመንግስትና የግል ተቋማትን ለቆ ለመውጣት፣ የህክምና ባለሙያዎችን እና የህዝብ ተቋማትን መጠበቅ፣ የሰብዓዊ እርዳታ አቅርቦት መፍቀድ ያላቸውን ቁርጠኝነት ገልጸዋል።
የሳዑዲ አረቢያ የውጭ ጉዳይ ሚንስቴር ስምምነቱን በደስታ መቀበሉን ገልጾ፤ የጅዳ ድርድር በሁለቱ ወገኖች መካከል እስከ 10 ቀናት የሚቆይና የተኩስ አቁም ስምምነት ላይ ለመድረስ እንደሚያተኩር አስታውቋል።
" የደህንነት እርምጃዎቹ በአሜሪካ፣ በሳዑዲ አረቢያ እና በዓለም አቀፉ ማህበረሰብ የሚደገፍ የተኩስ አቁም ቁጥጥር ዘዴን ያካትታል " ብሏል።
የአሜሪካ መንግስት በሰጠው መግለጫ ስምምነቱ የተኩስ አቁም ስምምነት እንዳልሆነ ተናግሯል። የጂዳ ስምምነት ወደ ተኩስ አቁም ስምምነት እንዲያመራ መደላደል እንደሆነም ተነግሯል።
መረጃው የአል አረቢያ ቴሌቪዥን እና አል አይን ኒውስ ነው።
@tikvahethiopia
#እንድታውቁት
በአዲስ አበባ ከተማ 6ኛ ዙር የመሬት ይዞታ ማረጋገጥ ስራ ትላንት ተጀምሯል።
በ6ኛ ዙር በተመረጡ በሰባት ክፍለ ከተሞች ከግንቦት 03/09/2015 ዓ.ም ጀምሮ ባሉ ተከታታይ አምስት ወራት 50 ሺህ የመሬት ይዞታዎችን የማረጋገጥ ስራ ይካሄዳል ሲል የአዲስ አበባ ከተማ የመሬት ይዞታ ምዝገባና መረጃ ኤጀንሲ አስታውቋል።
ኤጀንሲው ምዝገባው ፦
👉 በኮልፌ ቀራኒዮ፣
👉 በቂርቆስ፣
👉 በንፋስ ስልክ ላፍቶ፣
👉 በቦሌ፣
👉 በአዲስ ከተማ፣
👉 በልደታና በአራዳ ክፍለ ከተሞች ባሉ 50 ቀጠናዎችና 211 ሰፈሮች እንደሚከናወን ገልጿል።
ይህ የይዞታ ማረጋገጥ እወጃ ከተላለፈ ከ15 ቀናት በኃላ የይዞታ ይረጋገጥልኝ ጥያቄዎች በክፍለ ከተማ ቅ/ጽ/ቤቶች ቀርበው ጥያቄዎቻቸውን ማቅረብ ይቻላል ተብሏል።
ለመሬት ይዞታ ማረጋገጥ በተመረጡ ቀጠናዎችና ሰፈሮች ስራው ተጀምሮ እስከሚጠናቀቅ ባለቱ አምስት ወራት ውስጥ የመረጃ ልዩነት እንዳይፈጠር ሲባል ምንም ዓይነት የስመ- ንብረት ዝውውር አገልግሎት እንደማይሰጥ ኤጀንሲው አሳውቋል።
የአዲስ አበባ ከተማ የመሬት ይዞታ ምዝገባና መረጃ ኤጀንሲ በአዋጅ ከተቋቋመ ጀምሮ እስካሁን ድረስ በ5 ዙር 147 ሺህ ይዞታዎችን በካዳስተር ሲስተም መመዝገቡ አስታውሷል።
መረጃው የአ/አ ከተማ ኮሚኒኬሽን ቢሮ ነው።
@tikvahethiopia
በአዲስ አበባ ከተማ 6ኛ ዙር የመሬት ይዞታ ማረጋገጥ ስራ ትላንት ተጀምሯል።
በ6ኛ ዙር በተመረጡ በሰባት ክፍለ ከተሞች ከግንቦት 03/09/2015 ዓ.ም ጀምሮ ባሉ ተከታታይ አምስት ወራት 50 ሺህ የመሬት ይዞታዎችን የማረጋገጥ ስራ ይካሄዳል ሲል የአዲስ አበባ ከተማ የመሬት ይዞታ ምዝገባና መረጃ ኤጀንሲ አስታውቋል።
ኤጀንሲው ምዝገባው ፦
👉 በኮልፌ ቀራኒዮ፣
👉 በቂርቆስ፣
👉 በንፋስ ስልክ ላፍቶ፣
👉 በቦሌ፣
👉 በአዲስ ከተማ፣
👉 በልደታና በአራዳ ክፍለ ከተሞች ባሉ 50 ቀጠናዎችና 211 ሰፈሮች እንደሚከናወን ገልጿል።
ይህ የይዞታ ማረጋገጥ እወጃ ከተላለፈ ከ15 ቀናት በኃላ የይዞታ ይረጋገጥልኝ ጥያቄዎች በክፍለ ከተማ ቅ/ጽ/ቤቶች ቀርበው ጥያቄዎቻቸውን ማቅረብ ይቻላል ተብሏል።
ለመሬት ይዞታ ማረጋገጥ በተመረጡ ቀጠናዎችና ሰፈሮች ስራው ተጀምሮ እስከሚጠናቀቅ ባለቱ አምስት ወራት ውስጥ የመረጃ ልዩነት እንዳይፈጠር ሲባል ምንም ዓይነት የስመ- ንብረት ዝውውር አገልግሎት እንደማይሰጥ ኤጀንሲው አሳውቋል።
የአዲስ አበባ ከተማ የመሬት ይዞታ ምዝገባና መረጃ ኤጀንሲ በአዋጅ ከተቋቋመ ጀምሮ እስካሁን ድረስ በ5 ዙር 147 ሺህ ይዞታዎችን በካዳስተር ሲስተም መመዝገቡ አስታውሷል።
መረጃው የአ/አ ከተማ ኮሚኒኬሽን ቢሮ ነው።
@tikvahethiopia
የወረዳ አመራሩ ተገደሉ።
በአዲስ አበባ ከተማ የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ 08 ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ አለባቸው አሞኜ በዛሬው ዕለት በቢሮአቸው ውስጥ ተገደሉ።
የክፍለ ከተማው ኮሚኒኬሽን ባሰራጨው መረጃ ፤ " አቶ አለባቸው አሞኜ ቢሯቸው ውስጥ ቁጭ ብለው የህዝብ አገልግሎት በሚሰጡበት ወቅት ከአንድ #ተገልጋይ በደረሰባቸው #ጥቃት ህይወታቸው አልፏል " ብሏል።
ክ/ከተማው ምንም እንኳን ግድያውን በተመለከተ ዝርዝር መረጃ ይፋ ባያደርግም ጥቃት ያደረሰው ተጠርጣሪ በህግ ቁጥጥር ስር መዋሉን አመልክቷል።
ተገቢው የምርመራ ሂደት ተከትሎ ተጠያቂነት የማስፈን ስራ ይሰራልም ብላል።
" አቶ አለባቸው በስራ ቁርጠኝነት የሚታወቁ " ናቸው ያለው የቂርቆስ ክ/ከተማ " በበርካታ መንግስታዊና ህዝባዊ ተግባራት አርዓያነት ያለው ስራ የሰሩና ያስተባበሩ አመራራችን ነበሩ " ሲል ገልጿል።
@tikvahethiopia
በአዲስ አበባ ከተማ የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ 08 ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ አለባቸው አሞኜ በዛሬው ዕለት በቢሮአቸው ውስጥ ተገደሉ።
የክፍለ ከተማው ኮሚኒኬሽን ባሰራጨው መረጃ ፤ " አቶ አለባቸው አሞኜ ቢሯቸው ውስጥ ቁጭ ብለው የህዝብ አገልግሎት በሚሰጡበት ወቅት ከአንድ #ተገልጋይ በደረሰባቸው #ጥቃት ህይወታቸው አልፏል " ብሏል።
ክ/ከተማው ምንም እንኳን ግድያውን በተመለከተ ዝርዝር መረጃ ይፋ ባያደርግም ጥቃት ያደረሰው ተጠርጣሪ በህግ ቁጥጥር ስር መዋሉን አመልክቷል።
ተገቢው የምርመራ ሂደት ተከትሎ ተጠያቂነት የማስፈን ስራ ይሰራልም ብላል።
" አቶ አለባቸው በስራ ቁርጠኝነት የሚታወቁ " ናቸው ያለው የቂርቆስ ክ/ከተማ " በበርካታ መንግስታዊና ህዝባዊ ተግባራት አርዓያነት ያለው ስራ የሰሩና ያስተባበሩ አመራራችን ነበሩ " ሲል ገልጿል።
@tikvahethiopia