" በር አልሰበር ሲላቸው በፈንጂ ሰብረው በመግባት ከፍተኛ ጉዳት አድርሰዋል " - የምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት
በምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት ጥንታዊው የ " ሶደሬ ፈለገ ሰላም መድኃኔዓለም ገዳም " ለጊዜው ማንነታቸው ባልታወቀ በታጠቁ ኃይሎች ከፍተኛ ጉዳት እንደደረሰበት ተገለፀ።
ጥንታዊውና በ1963 ዓ.ም የተመሠረተው የሶደሬ ፈለገ ሰላም መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን ከአዳማ 25 ኪ/ሜ ርቀት ላይ ነው የሚገኘው።
ትናንት ከምሽቱ 4:00 ሰዓት ከ50 በላይ የሚሆኑ ለጊዜው ማንነታቸው ያልታወቀ የታጠቁ ኃይሎች የቤተክርስቲያኑን በር አልሰበር ሲላቸው በፈንጂ ሰብረው በመግባት ከፍተኛ ጉዳት እንዳደረሱ የ " ምስራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት " አሳውቋል።
የደረሰውን ጉዳት ለማጣራት የሀገረ ስብሰቱ ጽ/ቤት ልዑካንን የላከ ሲሆን ወደ ቦታው ያቀኑ ልዑካን የሀገረ ስብከቱ ም/ሥራ አስኪያጅ፣ የሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ልዩ ፀሐፊን ጨምሮ ሌሎች አባቶች እና ሓላፊዎች ናቸው።
ልዑኩ በደረሰው ጉዳት ከልብ ማዘኑን ያሳወቀ ሲሆን ካህናትና የአካባቢውን ምዕመናን እንዳፅናኑ ተመላክቷል።
በጥቃቱ ምን ጉዳት ደረሰ ?
የ " ምስራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት "ይፋ ባደረገው መረጃ በታጣቂዎቹ ጥቃት ፦
- በርካታ ነዋየ ቅድሳት ተቃጥለዋል፤
- የቤተክርቲያኑ ቅዱሳት ስዕላት በእሳት አረር ተለብለበዋል።
- የቤተክርስቲያኑን አስተዳዳሪ መኖሪያ ቤት በመጠየቅ ቤት ሰብሮ በመግባት በወቅቱ አስተዳዳሪው ባይኖሩም በቤት እቃዎች ላይ ጉዳት ደርሷል።
- የአንድ አገልጋይ ካህናት መኖሪያ ቤት ሙሉ ለሙሉ ተቃጥሏል።
- በቤተክርስቲያን ተጠግተው የሚገኙ ምዕመናን ከፍተኛ ማዋከብ ተፈጽሞባቸዋል።
ሀገረ ስብከቱ ይኸው የታጠቀ ኃይል የደብሩን ገንዘብ ያዥ የሆኑትን አቶ ተስፋ ደሳለኝን አስገድደው እንደወሰዷቸውና ልዑካኑ አስከተገኙበት ሰዓት እንዳልተለቀቁ ገልጿል።
ፎቶ / መረጃ፦ የ ምስራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት
@tikvahethiopia
በምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት ጥንታዊው የ " ሶደሬ ፈለገ ሰላም መድኃኔዓለም ገዳም " ለጊዜው ማንነታቸው ባልታወቀ በታጠቁ ኃይሎች ከፍተኛ ጉዳት እንደደረሰበት ተገለፀ።
ጥንታዊውና በ1963 ዓ.ም የተመሠረተው የሶደሬ ፈለገ ሰላም መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን ከአዳማ 25 ኪ/ሜ ርቀት ላይ ነው የሚገኘው።
ትናንት ከምሽቱ 4:00 ሰዓት ከ50 በላይ የሚሆኑ ለጊዜው ማንነታቸው ያልታወቀ የታጠቁ ኃይሎች የቤተክርስቲያኑን በር አልሰበር ሲላቸው በፈንጂ ሰብረው በመግባት ከፍተኛ ጉዳት እንዳደረሱ የ " ምስራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት " አሳውቋል።
የደረሰውን ጉዳት ለማጣራት የሀገረ ስብሰቱ ጽ/ቤት ልዑካንን የላከ ሲሆን ወደ ቦታው ያቀኑ ልዑካን የሀገረ ስብከቱ ም/ሥራ አስኪያጅ፣ የሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ልዩ ፀሐፊን ጨምሮ ሌሎች አባቶች እና ሓላፊዎች ናቸው።
ልዑኩ በደረሰው ጉዳት ከልብ ማዘኑን ያሳወቀ ሲሆን ካህናትና የአካባቢውን ምዕመናን እንዳፅናኑ ተመላክቷል።
በጥቃቱ ምን ጉዳት ደረሰ ?
የ " ምስራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት "ይፋ ባደረገው መረጃ በታጣቂዎቹ ጥቃት ፦
- በርካታ ነዋየ ቅድሳት ተቃጥለዋል፤
- የቤተክርቲያኑ ቅዱሳት ስዕላት በእሳት አረር ተለብለበዋል።
- የቤተክርስቲያኑን አስተዳዳሪ መኖሪያ ቤት በመጠየቅ ቤት ሰብሮ በመግባት በወቅቱ አስተዳዳሪው ባይኖሩም በቤት እቃዎች ላይ ጉዳት ደርሷል።
- የአንድ አገልጋይ ካህናት መኖሪያ ቤት ሙሉ ለሙሉ ተቃጥሏል።
- በቤተክርስቲያን ተጠግተው የሚገኙ ምዕመናን ከፍተኛ ማዋከብ ተፈጽሞባቸዋል።
ሀገረ ስብከቱ ይኸው የታጠቀ ኃይል የደብሩን ገንዘብ ያዥ የሆኑትን አቶ ተስፋ ደሳለኝን አስገድደው እንደወሰዷቸውና ልዑካኑ አስከተገኙበት ሰዓት እንዳልተለቀቁ ገልጿል።
ፎቶ / መረጃ፦ የ ምስራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#እንድታውቁት ከሚያዚያ 16 ጀምሮ በመላው አዲስ አበባ የነዳጅ ግብይት በአስገዳጅነት በ " ቴሌብር " ብቻ ተግባራዊ ይደረጋል ሲል የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ አሳውቋል። በ " ቴሌብር " ነዳጅ ስለ መቅዳት አሸከርካሪዎች ሊያውቋቸው የሚገቡ ነጥቦች ምንድናቸው ? ☞ በቅድሚያ የ " ቴሌብር "ተጠቃሚ መሆን፤ ☞ በቂ ክፍያ የቴሌብር አካውንት ውስጥ መኖሩን ማረጋገጥ፤ ☞ የ " ቴሌብር " የሚስጥር…
#ነዳጅ #አዲስአበባ
ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት በዲጂታል አማራጭ ተግባራዊ መደረጉን ተከትሎ ተጠቃሚዎች ከቴሌ ብር በተጨማሪ ሌሎችም የክፍያ ሥርዓቶችን መጠቀም እንደሚችሉ ተገልጿል።
ይህን ተከትሎ የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ክፍያ በ " ቴሌ ብር " ብቻ እንደሚፈፀም እያሳወቀ ይገኛል።
ባለፉት ተከታታይ ቀናትም ቢሮው የመኪና ባለቤቶች በቀሩት ጥቂት ቀናት የነዳጅ ክፍያ በ" ቴሌ ብር ብቻ " እንደሚከፈል በመገንዘብ ከእንግልት ለመዳን አስፈላጊውን ሁሉ ዝግጅት እንዲያደርጉ በተደጋጋሚ እያሳወቀ ነው።
ቢሮው መሰል መልዕክቶችን በተረጋገጠ የማህበራዊ መገናኛ ዘዴዎቹ ነው ለህዝብ እያሰራጨ የሚገኘው።
ለመሆኑን የነዳጅ ክፍያ ከ " ቴሌ ብር " ውጭ መፈፀም አይቻልም ?
ኤግል ላየን ሲስተም ቴክኖሎጂ ኃ/የተ/የግል ማኅበር ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጋር በመተባበር ለዚሁ አገልግሎት የሚውል " #ነዳጅ " የተባለ የሞባይል መተግበሪያ ማቅረባቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።
መተግበሪያው ተገልጋዮች የነዳጅ ክፍያቸውን ከንግድ ባንክ አካውንታቸው የተርጋ ቁጥራቸውን ብቻ በመጠቀም መክፈል ያስችላል ያለ ሲሆን የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ የነዳጅ ክፍያው " በቴሌ ብር ብቻ " ነው የሚፈፀመው እያለ ለህዝብ እያሰራጨ ያለው መልዕክት ትክክል እንዳልሆነ አስረድቷል።
" ነዳጅ " የተሰኘው የሞባይል መተግበሪያ ከክፍያ አማራጭነት በተጨማሪ አሽከርካሪዎች አቅራቢያቸው የሚገኙትን ማደያዎች ከአቅርቦታቸው ጋር ማግኘት የሚችሉበት አማራጭም እንዳለው ድርጅቱ ገልጾልናል።
የክፍያ አማራጩ በሀገሪቱ ከሚገኙ ማደያዎች 60 በመቶ ማዳረስ መቻሉንም ጠቁሟል።
መተግበሪያው የት ይገኛል ? https://play.google.com/store/apps/details?id=com.eaglelionsystems.nedaj
በተጨማሪም የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በሲቢኢ ብር መተግበሪያ አማካኝነት ነዳጅ ለመቅዳት የሚያስችል አዲስ የዲጅታል አሠራር መዘርጋቱን ገልጿል።
ክፍያውም በማንኛውም ስልክ በሲቢኢ ብር አጭር ቁጥር ወይም በሞባይል መተግበሪያው መፈጸም ይቻላል ተብሏል። አሰራሩ በሀገሪቱ በሚገኙ ሁሉም ማደያዎች ተግባራዊ እንደሚደረግ ነው የተጠቆመው።
@tikvahethiopia
ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት በዲጂታል አማራጭ ተግባራዊ መደረጉን ተከትሎ ተጠቃሚዎች ከቴሌ ብር በተጨማሪ ሌሎችም የክፍያ ሥርዓቶችን መጠቀም እንደሚችሉ ተገልጿል።
ይህን ተከትሎ የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ክፍያ በ " ቴሌ ብር " ብቻ እንደሚፈፀም እያሳወቀ ይገኛል።
ባለፉት ተከታታይ ቀናትም ቢሮው የመኪና ባለቤቶች በቀሩት ጥቂት ቀናት የነዳጅ ክፍያ በ" ቴሌ ብር ብቻ " እንደሚከፈል በመገንዘብ ከእንግልት ለመዳን አስፈላጊውን ሁሉ ዝግጅት እንዲያደርጉ በተደጋጋሚ እያሳወቀ ነው።
ቢሮው መሰል መልዕክቶችን በተረጋገጠ የማህበራዊ መገናኛ ዘዴዎቹ ነው ለህዝብ እያሰራጨ የሚገኘው።
ለመሆኑን የነዳጅ ክፍያ ከ " ቴሌ ብር " ውጭ መፈፀም አይቻልም ?
ኤግል ላየን ሲስተም ቴክኖሎጂ ኃ/የተ/የግል ማኅበር ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጋር በመተባበር ለዚሁ አገልግሎት የሚውል " #ነዳጅ " የተባለ የሞባይል መተግበሪያ ማቅረባቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።
መተግበሪያው ተገልጋዮች የነዳጅ ክፍያቸውን ከንግድ ባንክ አካውንታቸው የተርጋ ቁጥራቸውን ብቻ በመጠቀም መክፈል ያስችላል ያለ ሲሆን የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ የነዳጅ ክፍያው " በቴሌ ብር ብቻ " ነው የሚፈፀመው እያለ ለህዝብ እያሰራጨ ያለው መልዕክት ትክክል እንዳልሆነ አስረድቷል።
" ነዳጅ " የተሰኘው የሞባይል መተግበሪያ ከክፍያ አማራጭነት በተጨማሪ አሽከርካሪዎች አቅራቢያቸው የሚገኙትን ማደያዎች ከአቅርቦታቸው ጋር ማግኘት የሚችሉበት አማራጭም እንዳለው ድርጅቱ ገልጾልናል።
የክፍያ አማራጩ በሀገሪቱ ከሚገኙ ማደያዎች 60 በመቶ ማዳረስ መቻሉንም ጠቁሟል።
መተግበሪያው የት ይገኛል ? https://play.google.com/store/apps/details?id=com.eaglelionsystems.nedaj
በተጨማሪም የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በሲቢኢ ብር መተግበሪያ አማካኝነት ነዳጅ ለመቅዳት የሚያስችል አዲስ የዲጅታል አሠራር መዘርጋቱን ገልጿል።
ክፍያውም በማንኛውም ስልክ በሲቢኢ ብር አጭር ቁጥር ወይም በሞባይል መተግበሪያው መፈጸም ይቻላል ተብሏል። አሰራሩ በሀገሪቱ በሚገኙ ሁሉም ማደያዎች ተግባራዊ እንደሚደረግ ነው የተጠቆመው።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Tigray
በፕሪቶሪያው ስምምነት መሰረት ከዚህ ቀደም ህወሓት የከባድ መሳሪያ ትጥቅ እንደፈታና ለሀገር መከላከያ እንዳስረከበ መነገሩ ይታወሳል።
ትላንት ደግሞ መካከለኛ እና ቀላል የቡድን መሳሪያዎችን በመፍታት ለሀገር መከላከያ ሰራዊት እንዳስረከበ ተነግሯል።
ከሀገር መከላከያ ሰራዊት ተወካይ ኮሎኔል ጉደታ ኦፍካ ምን አሉ ?
" በሶስተኛ ዙር የመሳሪያ ርክክብ ሞርታር ዲሽቃ መሰል በርካታ የቡድን መሳሪያዎችን ተረክበናል።
ከፍተኛ ስራ እየተሰራ ነው የሚገኘው ፤ በኢትዮጵያ መንግሥት እና በትግራይ ክልል ባለው መንግሥት ከፍተኛ የትብብር መንፈስ ነው ያለው። ጥሩ ሂደት ነው ያለው ማለት ይቻላል። "
የትግራይ ኃይሎች ተወካይ ኮሎኔል ሙልጌታ ገብረክርስቶስ ምን አሉ ?
" በተደረገው የሰላም ስምምነት መሰረት ትጥቅ የማውረድ ስራ እየተሰራ ነው።
ባለፈው ከባድ መሳሪያዎችን አስረክበናል። አሁን ደግሞ መካከለኛ እና ቀላል የቡድን መሳሪያዎችን የማስረከብ ስራ ጀምረናል።
ስራው ጥሩ ነው፤ በተፋጠነ መልኩ እየሄደ ነው። በሁለቱም ኃይላት በኩል ተግባብቶ የመስራት ሂዘት ጥሩ እየሄደ ነው። "
በፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነትን ተከትሎ የትጥቅ መፍታት ሂደትን የአፍሪካ ህብረት የክትትል እና ቁጥጥር ኮሚሽን በማቋቋም እየተከታተለው ይገኛል።
ከላይ የተገለፁት ሁለቱ ተወካዮችም የዚሁ ኮሚሽን አካል ናቸው።
ፎቶ፦ ENA
@tikvahethiopia
በፕሪቶሪያው ስምምነት መሰረት ከዚህ ቀደም ህወሓት የከባድ መሳሪያ ትጥቅ እንደፈታና ለሀገር መከላከያ እንዳስረከበ መነገሩ ይታወሳል።
ትላንት ደግሞ መካከለኛ እና ቀላል የቡድን መሳሪያዎችን በመፍታት ለሀገር መከላከያ ሰራዊት እንዳስረከበ ተነግሯል።
ከሀገር መከላከያ ሰራዊት ተወካይ ኮሎኔል ጉደታ ኦፍካ ምን አሉ ?
" በሶስተኛ ዙር የመሳሪያ ርክክብ ሞርታር ዲሽቃ መሰል በርካታ የቡድን መሳሪያዎችን ተረክበናል።
ከፍተኛ ስራ እየተሰራ ነው የሚገኘው ፤ በኢትዮጵያ መንግሥት እና በትግራይ ክልል ባለው መንግሥት ከፍተኛ የትብብር መንፈስ ነው ያለው። ጥሩ ሂደት ነው ያለው ማለት ይቻላል። "
የትግራይ ኃይሎች ተወካይ ኮሎኔል ሙልጌታ ገብረክርስቶስ ምን አሉ ?
" በተደረገው የሰላም ስምምነት መሰረት ትጥቅ የማውረድ ስራ እየተሰራ ነው።
ባለፈው ከባድ መሳሪያዎችን አስረክበናል። አሁን ደግሞ መካከለኛ እና ቀላል የቡድን መሳሪያዎችን የማስረከብ ስራ ጀምረናል።
ስራው ጥሩ ነው፤ በተፋጠነ መልኩ እየሄደ ነው። በሁለቱም ኃይላት በኩል ተግባብቶ የመስራት ሂዘት ጥሩ እየሄደ ነው። "
በፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነትን ተከትሎ የትጥቅ መፍታት ሂደትን የአፍሪካ ህብረት የክትትል እና ቁጥጥር ኮሚሽን በማቋቋም እየተከታተለው ይገኛል።
ከላይ የተገለፁት ሁለቱ ተወካዮችም የዚሁ ኮሚሽን አካል ናቸው።
ፎቶ፦ ENA
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
ፎቶ፦ ዛሬ የሲዳማ ብሔር የዘመን መለወጫ " ፊቼ ጫምበላላ " በዓል በሀዋሳ ጉዱማሌ በመከበር ላይ ይገኛል።
Photo Credit : EBC
@tikvahethiopia
Photo Credit : EBC
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update
ሱዳን ውስጥ የነበሩ የግብፅ ወታደሮች ወደ ሀገራቸው እንዲመለሱ ተደረገ።
የሱዳን ጦር 177 የግብፅ የአየር ኃይል ወታደሮች ወደ ግብፅ መወሰዳቸውን አስታውቋል።
የሱዳን ጦር ባወጣው መግለጫ የግብፅ ወታደሮቹ በአራት የግብፅ ወታደራዊ አውሮፕላኖች ከሰሜናዊቷ ዶንጎላ ከተማ ወደ ሀገራቸው እንዲመለሱ ተደርገዋል።
ጦሩ ፤ ግብፃውያኑ ሱዳን የነበሩት የጋራ የአየር ሃይል ልምምድ ለማድረግ እንደነበር አመልክቷል።
የግብፅ ጦር የሰራዊት አባላቱ ሱዳንን ለቀው ስለመውጣታቸውን እስካሁን በይፋ ባያሳውቅም ሱዳን ያሉ ወታደሮቹን ወደ ሀገራቸው እንዲመለሱ ለማድረግ ከሱዳን ባለስልጣናት ጋር በመስራት ላይ እንደሚገኝ ገልጾ ነበር።
የሱዳን ጦር አሁን መመለሳቸውን የገለፃቸው የግብፅ ወታደሮች ከቀናት በፊት በRSF የተያዙትን እንዳልሆነና በRSF ስር ያሉት 28 ወታደሮች መሆናቸውንና አሁንም በነሱ እጅ እንደሚገኙ ገልጿል።
ትላንት ምሽት ግን የሱዳን ጦር ወደ ግብፅ የተወሰዱት በRSF የተያዙት / የታሰሩ ወታደሮች መሆናቸውን ገልጾ መግለጫ አውጥቶ ነበር ፤ ይህንን መግለጫም ዋቢ በማድረግ ዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃን ዘገባዎችን ሰርተው ነበር።
ጦሩ ዛሬ ባወጣው መግለጫ የትላንቱ መግለጫው ትክክለኛ እንዳልሆነ አመልክታል። የተያዙት / የታሰሩት በሚል የገባው ቃል ሳይታወቅ በስህተት ነው ብሏል።
አሁን ወደ ግብፅ እንዲመለሱ የተደረጉት ወታደሮች ግጭቱ በተቀሰቀሰበት ወቅት ማራዊ ውስጥ የነበሩ ነገር ግን ከኤርፖርት ውጭ ስለነበሩ በRSF ያልተያዙ ናቸው ሲል አስረድቷል።
የሱዳን ውጊያ በተጀመረበት ወቅት በጄነራል መሐመድ ሃምዳን ደጋሎ (ሄሜቲ) የሚመራው የሱዳን ፈጥኖ ደራሻ (RSF) ሜሮዌ ላይ የግብፅ ወታደሮችን #መማረኩን ማሳወቁ ይታወሳል።
ከቀናት በፊት የግብፁ ፕሬዜዳንት አብድል ፈታህ አል ሲሲ ሱዳን ውስጥ የተያዙት የግብጽ ወታደሮች፣ በዚያ የተገኙት ከሱዳን አቻዎቻቸው ጋራ ወታደራዊ ልምምድ ለማድረግ እንጂ ፤ የትኛውንም ወገን ለመደገፍ አለመኾኑን ገልጸዋል።
ይህንን የገለፁት ከግብጽ ከፍተኛ ወታደራዊ ም/ቤት ጋር ስብሰባ በተቀመጡበት ወቅት ሲሆን የወታደሮቹን ደህንነት በተመለከተ ከRSF ጋር እየተነጋገሩ መሆኑን አስታውቀዋል።
@tikvahethiopia
ሱዳን ውስጥ የነበሩ የግብፅ ወታደሮች ወደ ሀገራቸው እንዲመለሱ ተደረገ።
የሱዳን ጦር 177 የግብፅ የአየር ኃይል ወታደሮች ወደ ግብፅ መወሰዳቸውን አስታውቋል።
የሱዳን ጦር ባወጣው መግለጫ የግብፅ ወታደሮቹ በአራት የግብፅ ወታደራዊ አውሮፕላኖች ከሰሜናዊቷ ዶንጎላ ከተማ ወደ ሀገራቸው እንዲመለሱ ተደርገዋል።
ጦሩ ፤ ግብፃውያኑ ሱዳን የነበሩት የጋራ የአየር ሃይል ልምምድ ለማድረግ እንደነበር አመልክቷል።
የግብፅ ጦር የሰራዊት አባላቱ ሱዳንን ለቀው ስለመውጣታቸውን እስካሁን በይፋ ባያሳውቅም ሱዳን ያሉ ወታደሮቹን ወደ ሀገራቸው እንዲመለሱ ለማድረግ ከሱዳን ባለስልጣናት ጋር በመስራት ላይ እንደሚገኝ ገልጾ ነበር።
የሱዳን ጦር አሁን መመለሳቸውን የገለፃቸው የግብፅ ወታደሮች ከቀናት በፊት በRSF የተያዙትን እንዳልሆነና በRSF ስር ያሉት 28 ወታደሮች መሆናቸውንና አሁንም በነሱ እጅ እንደሚገኙ ገልጿል።
ትላንት ምሽት ግን የሱዳን ጦር ወደ ግብፅ የተወሰዱት በRSF የተያዙት / የታሰሩ ወታደሮች መሆናቸውን ገልጾ መግለጫ አውጥቶ ነበር ፤ ይህንን መግለጫም ዋቢ በማድረግ ዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃን ዘገባዎችን ሰርተው ነበር።
ጦሩ ዛሬ ባወጣው መግለጫ የትላንቱ መግለጫው ትክክለኛ እንዳልሆነ አመልክታል። የተያዙት / የታሰሩት በሚል የገባው ቃል ሳይታወቅ በስህተት ነው ብሏል።
አሁን ወደ ግብፅ እንዲመለሱ የተደረጉት ወታደሮች ግጭቱ በተቀሰቀሰበት ወቅት ማራዊ ውስጥ የነበሩ ነገር ግን ከኤርፖርት ውጭ ስለነበሩ በRSF ያልተያዙ ናቸው ሲል አስረድቷል።
የሱዳን ውጊያ በተጀመረበት ወቅት በጄነራል መሐመድ ሃምዳን ደጋሎ (ሄሜቲ) የሚመራው የሱዳን ፈጥኖ ደራሻ (RSF) ሜሮዌ ላይ የግብፅ ወታደሮችን #መማረኩን ማሳወቁ ይታወሳል።
ከቀናት በፊት የግብፁ ፕሬዜዳንት አብድል ፈታህ አል ሲሲ ሱዳን ውስጥ የተያዙት የግብጽ ወታደሮች፣ በዚያ የተገኙት ከሱዳን አቻዎቻቸው ጋራ ወታደራዊ ልምምድ ለማድረግ እንጂ ፤ የትኛውንም ወገን ለመደገፍ አለመኾኑን ገልጸዋል።
ይህንን የገለፁት ከግብጽ ከፍተኛ ወታደራዊ ም/ቤት ጋር ስብሰባ በተቀመጡበት ወቅት ሲሆን የወታደሮቹን ደህንነት በተመለከተ ከRSF ጋር እየተነጋገሩ መሆኑን አስታውቀዋል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
የሱዳን ውጊያ 6ኛ ቀኑን ይዟል።
በተዋጊዎቹ ኃይሎች መካከል ለ2ኛ ጊዜ ትላንት የ24 ሰዓታት ለሰብዓዊት ተኩስ ለማቆም ሙከራ ተደርጎ የነበር ቢሆንም ሳይሳካ ቀርቶ ውጊያው ቀጥሎ እንደነበር ተሰምቷል።
የተኩስ አቁም እንዲደረግ የተሞከረው ዜጎቻቸውን ከሱዳን ለማስወጣት እየጣሩ ባሉ ሀገራት ግፊት መሆኑን አልጀዚራ ዘግቧል።
ዛሬም በሱዳን የተለያዩ ከተሞች ውጊያ መኖሩ በተለይ በካርቱም የፕሬዜዳንቱ ቤተመንግስት እና የሱዳን ጦር ዋና መስሪያ ቤት አካባቢ ወታደራዊ ግጭት መኖሩ ተመላክቷል።
በርካቶች ያለምግብ፣ውሃ፣ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በቤታቸው ውስጥ ዘግተው እንደተቀመጡ ይገኛሉ።
በሺዎች የሚቆጠሩ ደግሞ ቤታቸውን ጥለው ከካርቱም እየሸሹ እንደሚገኙ ተነግሯል።
@tikvahethiopia
በተዋጊዎቹ ኃይሎች መካከል ለ2ኛ ጊዜ ትላንት የ24 ሰዓታት ለሰብዓዊት ተኩስ ለማቆም ሙከራ ተደርጎ የነበር ቢሆንም ሳይሳካ ቀርቶ ውጊያው ቀጥሎ እንደነበር ተሰምቷል።
የተኩስ አቁም እንዲደረግ የተሞከረው ዜጎቻቸውን ከሱዳን ለማስወጣት እየጣሩ ባሉ ሀገራት ግፊት መሆኑን አልጀዚራ ዘግቧል።
ዛሬም በሱዳን የተለያዩ ከተሞች ውጊያ መኖሩ በተለይ በካርቱም የፕሬዜዳንቱ ቤተመንግስት እና የሱዳን ጦር ዋና መስሪያ ቤት አካባቢ ወታደራዊ ግጭት መኖሩ ተመላክቷል።
በርካቶች ያለምግብ፣ውሃ፣ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በቤታቸው ውስጥ ዘግተው እንደተቀመጡ ይገኛሉ።
በሺዎች የሚቆጠሩ ደግሞ ቤታቸውን ጥለው ከካርቱም እየሸሹ እንደሚገኙ ተነግሯል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
የሱዳን ውጊያ 6ኛ ቀኑን ይዟል። በተዋጊዎቹ ኃይሎች መካከል ለ2ኛ ጊዜ ትላንት የ24 ሰዓታት ለሰብዓዊት ተኩስ ለማቆም ሙከራ ተደርጎ የነበር ቢሆንም ሳይሳካ ቀርቶ ውጊያው ቀጥሎ እንደነበር ተሰምቷል። የተኩስ አቁም እንዲደረግ የተሞከረው ዜጎቻቸውን ከሱዳን ለማስወጣት እየጣሩ ባሉ ሀገራት ግፊት መሆኑን አልጀዚራ ዘግቧል። ዛሬም በሱዳን የተለያዩ ከተሞች ውጊያ መኖሩ በተለይ በካርቱም የፕሬዜዳንቱ ቤተመንግስት…
#ሱዳን
" ቤተሰቦቻችን ስላሉበት ሁኔታ ለማወቅ አልቻልንም ፤ጭንቀት ላይ ነን "
በሱዳን እየተካሄደ ያለው ውጊያ ዛሬ 6ኛ ቀኑን መያዙ ይታወቃል።
በሱዳን ያሉ ቤተሰቦቻችን ያሉበትን ሁኔታ ለማወቅ ካርቱም ወዳለው የኢትዮጵያ ኤምባሲ ስልክ ብንደውልም ምላሽ አላገኘንም ሲሉ እዚህ ኢትዮጵያ የሚገኙ የቲክቫህ ቤተሰብ አባላት መልዕክት ልከዋል።
በሱዳን ያሉ ቤተሰቦቻቸውን ለማግኘት ባለመቻላቸው እንደተጨነቁ የገለፁት እንዚሁ አባላት ፤ ማንን መጠየቅ እንዳለብን ግራ ገብቶናል ይህ ጉዳይ የሚመለከተው አካል ምላሽ ሊሰጠን ይገባል ብለዋል።
ለበርካታ ኢትዮጵያውያን ሁለተኛ ቤት በሆነችው ሱዳን ውስጥ ኢትዮጵያውያን ለስራ እና በቋሚነት ለኑሮ እንደሚገኙ ይታወቃል።
የሰሞኑ የሱዳን ውጊያ ደግሞ እዛ ያሉትን ብቻ ሳይሆን እዚህ ያሉ ቤተሰቦችንም ጭምር ጭንቀት ውስጥ ጥሏል።
ከትላንት በስቲያ በሱዳን የኢትዮጵያ ኤምባሲ ፤ በሱዳን እየተካሄደ ባለው ውጊያ በርካታ ሲቪሎች ለጉዳት መዳረጋቸውና ህይወትም እየተቀጠፈ መሆኑን በመግለፅ ከእነዚህ መካከል #ኢትዮጵያውያን እንደሚገኙበት መረጃዎች እንደደረሱት አሳውቋል።
ኤምባሲው ምን ያህል ኢትዮጵያውያን እንደሞቱ እና እንደተጎዱ በዝርዝር ባይገልፅም ይህን አስቸጋሪ ጊዜ ለማለፍ ኢትዮጵያዊን የተቻላቸውን ሁሉ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ አሳስቧል።
መረጃ ለመለዋወጥ እና ለምክክር የኤምባሲው ባልደረባ የሆኑትን አቶ ነጅብ አብደላ በስልክ ቁጥር +249911646547 ማነጋገር እንደሚቻልም ገልጿል።
@tikvahethiopia
" ቤተሰቦቻችን ስላሉበት ሁኔታ ለማወቅ አልቻልንም ፤ጭንቀት ላይ ነን "
በሱዳን እየተካሄደ ያለው ውጊያ ዛሬ 6ኛ ቀኑን መያዙ ይታወቃል።
በሱዳን ያሉ ቤተሰቦቻችን ያሉበትን ሁኔታ ለማወቅ ካርቱም ወዳለው የኢትዮጵያ ኤምባሲ ስልክ ብንደውልም ምላሽ አላገኘንም ሲሉ እዚህ ኢትዮጵያ የሚገኙ የቲክቫህ ቤተሰብ አባላት መልዕክት ልከዋል።
በሱዳን ያሉ ቤተሰቦቻቸውን ለማግኘት ባለመቻላቸው እንደተጨነቁ የገለፁት እንዚሁ አባላት ፤ ማንን መጠየቅ እንዳለብን ግራ ገብቶናል ይህ ጉዳይ የሚመለከተው አካል ምላሽ ሊሰጠን ይገባል ብለዋል።
ለበርካታ ኢትዮጵያውያን ሁለተኛ ቤት በሆነችው ሱዳን ውስጥ ኢትዮጵያውያን ለስራ እና በቋሚነት ለኑሮ እንደሚገኙ ይታወቃል።
የሰሞኑ የሱዳን ውጊያ ደግሞ እዛ ያሉትን ብቻ ሳይሆን እዚህ ያሉ ቤተሰቦችንም ጭምር ጭንቀት ውስጥ ጥሏል።
ከትላንት በስቲያ በሱዳን የኢትዮጵያ ኤምባሲ ፤ በሱዳን እየተካሄደ ባለው ውጊያ በርካታ ሲቪሎች ለጉዳት መዳረጋቸውና ህይወትም እየተቀጠፈ መሆኑን በመግለፅ ከእነዚህ መካከል #ኢትዮጵያውያን እንደሚገኙበት መረጃዎች እንደደረሱት አሳውቋል።
ኤምባሲው ምን ያህል ኢትዮጵያውያን እንደሞቱ እና እንደተጎዱ በዝርዝር ባይገልፅም ይህን አስቸጋሪ ጊዜ ለማለፍ ኢትዮጵያዊን የተቻላቸውን ሁሉ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ አሳስቧል።
መረጃ ለመለዋወጥ እና ለምክክር የኤምባሲው ባልደረባ የሆኑትን አቶ ነጅብ አብደላ በስልክ ቁጥር +249911646547 ማነጋገር እንደሚቻልም ገልጿል።
@tikvahethiopia
የዒድ አልፈጥር በዓል መቼ ነው ?
የፌዴራል ጠቅላይ ሼሪዓ ፍርድ ቤት ፥ የዒድ አልፈጥር በዓል ጨረቃ ዛሬ ሀሙስ ማታ ከታየች ነገ አርብ ፣ ካልታየች ደግሞ ቅዳሜ ይከበራል ሲል አሳውቋል።
ይህን ያሳወቀው ዛሬ በሰጠው መግለጫ ነው።
1 ሺህ 444ኛው የዒድ አልፈጥር በዓል ፤ ለኢትዮጵያና ለመላው ዓለም ህብረተሰብ የሰላም፣ የደስታና የፍቅር እንዲሆን መልካም ምኞቱን የገለፀው ሼሪዓ ፍርድ ቤቱ ሙስሊሙ ህብረተሰብ በዓሉን ሲያከብር ያጡና የተቸገሩ ወገኖችን በማሰብና በመርዳት እንዲሆን ጥሪ አቅርቧል።
#ኤፍቢሲ
@tikvahethiopia
የፌዴራል ጠቅላይ ሼሪዓ ፍርድ ቤት ፥ የዒድ አልፈጥር በዓል ጨረቃ ዛሬ ሀሙስ ማታ ከታየች ነገ አርብ ፣ ካልታየች ደግሞ ቅዳሜ ይከበራል ሲል አሳውቋል።
ይህን ያሳወቀው ዛሬ በሰጠው መግለጫ ነው።
1 ሺህ 444ኛው የዒድ አልፈጥር በዓል ፤ ለኢትዮጵያና ለመላው ዓለም ህብረተሰብ የሰላም፣ የደስታና የፍቅር እንዲሆን መልካም ምኞቱን የገለፀው ሼሪዓ ፍርድ ቤቱ ሙስሊሙ ህብረተሰብ በዓሉን ሲያከብር ያጡና የተቸገሩ ወገኖችን በማሰብና በመርዳት እንዲሆን ጥሪ አቅርቧል።
#ኤፍቢሲ
@tikvahethiopia