#ኢዜማ
ጉምቱው ፖለቲከኛ ከፓርቲያቸው ለቀቁ።
የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ ፓርቲ (ኢዜማ) መስራቾች አንዱ የሆኑት ጉምቱው ፖለቲከኛ አቶ አንዱዓለም አራጌ ከፓርቲው መልቀቃቸውን አስታውቀዋል።
የመልቀቂያ ደብዳቤው በትላንትናው እለት ለሚመለከተው አካል ገቢ ማድረጋቸውንም ገልጸዋል።
አቶ አንዱዓለም አራጌ ፓርቲውን ለምን ለቀቁ ? የመልቀቂያ ደብዳቤያቸው ላይ በዝርዝር አስረድተዋል ፤ ከላይ ተያይዟል ያንብቡት !
ምንጭ፦ የተረጋገጠው የማህበራዊ ትስድር ገፃቸው
@tikvahethiopia
ጉምቱው ፖለቲከኛ ከፓርቲያቸው ለቀቁ።
የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ ፓርቲ (ኢዜማ) መስራቾች አንዱ የሆኑት ጉምቱው ፖለቲከኛ አቶ አንዱዓለም አራጌ ከፓርቲው መልቀቃቸውን አስታውቀዋል።
የመልቀቂያ ደብዳቤው በትላንትናው እለት ለሚመለከተው አካል ገቢ ማድረጋቸውንም ገልጸዋል።
አቶ አንዱዓለም አራጌ ፓርቲውን ለምን ለቀቁ ? የመልቀቂያ ደብዳቤያቸው ላይ በዝርዝር አስረድተዋል ፤ ከላይ ተያይዟል ያንብቡት !
ምንጭ፦ የተረጋገጠው የማህበራዊ ትስድር ገፃቸው
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update በሱዳን እየተካሄደ ባለው ውጊያ ኢትዮጵያውያንን ጨምሮ በርካታ ሰላማዊ ሰዎች እየተገደሉ ናቸው። በሱዳን የኢትዮጵያ ኤምባሲ ፤ በሱዳን እየተካሄደ ባለው ውጊያ በርካታ ሲቪሎች ለጉዳት መዳረጋቸውና ህይወትም እየተቀጠፈ መሆኑን ገልጿል። ከእነዚህ መካከል #ኢትዮጵያውያን እንደሚገኙበት መረጃዎች እንደደረሱት አመልክቷል። ኤምባሲው ምን ያህል ኢትዮጵያውያን እንደሞቱ እና እንደተጎዱ በዝርዝር አልገለፀም።…
#Update
በሱዳን እየተካሄደ ያለው ውጊያ ዛሬ 5ኛ ቀኑን ይዟል።
ምን አዳዲስ ጉዳዮች አሉ ?
- ትላንት የሱዳን ጦርና RSF ለ24 ሰዓታት የሚዘልቅ ለሰብዓዊነት ተኩስ የማቆም ስምምነት ላይ ደርሰናል ቢሉም ምንም አልተከበረም። እንደውም ከዛ በኃላ 36 ሰዎች መገደላቸው ተሰምቷል።
- የሱዳን ጦር ለተኩስ ማቆም ስምምነቱ መጣስ RSFን ተጠያቂ አድርጓል።
- 5ኛው ቀን ውጊያ በቀጠለበት በዚህ ሰዓት የሱዳን ጎረቤት የሆኑ የሦስት አገራት መሪዎች (ሳልቫ ኪር፣ ኢስማኤል ኦማር ጌሌ እና ዊሊያም ሩቶ) ሁለቱን የጦር ጀነራሎች ለማደራደር ካርቱም ይገባሉ መባሉን ቢቢሲ ዘግቧል።
- ዛሬ በማዕከላዊ ካርቱም በጦሩ ዋና መስሪያ ቤት፣ በፕሬዜዳንቱ ቤተመንግስት፣ እና ካርቱም ኤርፖርት አቅራቢያ ውጊያ እየተደረገ ነው።
- የሱዳን ጤና ጥበቃ ሚኒስቴር 16 ሆስፒታሎች ከአገልግሎት ውጪ መሆናቸውን በመግለፅ በጤና ስርዓቱ ላይ ጠቅላላ ውድቀት እየመጣ መሆኑን አስጠንቅቋል።
- ጃፓን ዜጎቿን በጦርነት ከምትታመሰው ሱዳን ለማስወጣት በዝግጅት ላይ መሆኗን የሀገሪቱ መንግሥት ገልጿል። ጃፓን ዜጎቿን ከሱዳን የምታስወጣበት መንገድ ከተሳካ ዜጎቿን ከሱዳን ያስወጣች የመጀመሪያዋ የውጭ ሀገር ትሆናለች።
- ካርቱም ውስጥ ነዋሪዎች ያለ ውሃ እና ኤሌክትሪክ አገልግሎት ቤት ውስጥ ይገኛሉ፤ ነዋሪዎች ከቤት መውጣት ያልቻሉ ሲሆን በርካቶችም የሚበሉት ማጣታቸውን ቢቢሲ ዘግቧል።
@tikvahethiopia
በሱዳን እየተካሄደ ያለው ውጊያ ዛሬ 5ኛ ቀኑን ይዟል።
ምን አዳዲስ ጉዳዮች አሉ ?
- ትላንት የሱዳን ጦርና RSF ለ24 ሰዓታት የሚዘልቅ ለሰብዓዊነት ተኩስ የማቆም ስምምነት ላይ ደርሰናል ቢሉም ምንም አልተከበረም። እንደውም ከዛ በኃላ 36 ሰዎች መገደላቸው ተሰምቷል።
- የሱዳን ጦር ለተኩስ ማቆም ስምምነቱ መጣስ RSFን ተጠያቂ አድርጓል።
- 5ኛው ቀን ውጊያ በቀጠለበት በዚህ ሰዓት የሱዳን ጎረቤት የሆኑ የሦስት አገራት መሪዎች (ሳልቫ ኪር፣ ኢስማኤል ኦማር ጌሌ እና ዊሊያም ሩቶ) ሁለቱን የጦር ጀነራሎች ለማደራደር ካርቱም ይገባሉ መባሉን ቢቢሲ ዘግቧል።
- ዛሬ በማዕከላዊ ካርቱም በጦሩ ዋና መስሪያ ቤት፣ በፕሬዜዳንቱ ቤተመንግስት፣ እና ካርቱም ኤርፖርት አቅራቢያ ውጊያ እየተደረገ ነው።
- የሱዳን ጤና ጥበቃ ሚኒስቴር 16 ሆስፒታሎች ከአገልግሎት ውጪ መሆናቸውን በመግለፅ በጤና ስርዓቱ ላይ ጠቅላላ ውድቀት እየመጣ መሆኑን አስጠንቅቋል።
- ጃፓን ዜጎቿን በጦርነት ከምትታመሰው ሱዳን ለማስወጣት በዝግጅት ላይ መሆኗን የሀገሪቱ መንግሥት ገልጿል። ጃፓን ዜጎቿን ከሱዳን የምታስወጣበት መንገድ ከተሳካ ዜጎቿን ከሱዳን ያስወጣች የመጀመሪያዋ የውጭ ሀገር ትሆናለች።
- ካርቱም ውስጥ ነዋሪዎች ያለ ውሃ እና ኤሌክትሪክ አገልግሎት ቤት ውስጥ ይገኛሉ፤ ነዋሪዎች ከቤት መውጣት ያልቻሉ ሲሆን በርካቶችም የሚበሉት ማጣታቸውን ቢቢሲ ዘግቧል።
@tikvahethiopia
" በር አልሰበር ሲላቸው በፈንጂ ሰብረው በመግባት ከፍተኛ ጉዳት አድርሰዋል " - የምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት
በምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት ጥንታዊው የ " ሶደሬ ፈለገ ሰላም መድኃኔዓለም ገዳም " ለጊዜው ማንነታቸው ባልታወቀ በታጠቁ ኃይሎች ከፍተኛ ጉዳት እንደደረሰበት ተገለፀ።
ጥንታዊውና በ1963 ዓ.ም የተመሠረተው የሶደሬ ፈለገ ሰላም መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን ከአዳማ 25 ኪ/ሜ ርቀት ላይ ነው የሚገኘው።
ትናንት ከምሽቱ 4:00 ሰዓት ከ50 በላይ የሚሆኑ ለጊዜው ማንነታቸው ያልታወቀ የታጠቁ ኃይሎች የቤተክርስቲያኑን በር አልሰበር ሲላቸው በፈንጂ ሰብረው በመግባት ከፍተኛ ጉዳት እንዳደረሱ የ " ምስራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት " አሳውቋል።
የደረሰውን ጉዳት ለማጣራት የሀገረ ስብሰቱ ጽ/ቤት ልዑካንን የላከ ሲሆን ወደ ቦታው ያቀኑ ልዑካን የሀገረ ስብከቱ ም/ሥራ አስኪያጅ፣ የሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ልዩ ፀሐፊን ጨምሮ ሌሎች አባቶች እና ሓላፊዎች ናቸው።
ልዑኩ በደረሰው ጉዳት ከልብ ማዘኑን ያሳወቀ ሲሆን ካህናትና የአካባቢውን ምዕመናን እንዳፅናኑ ተመላክቷል።
በጥቃቱ ምን ጉዳት ደረሰ ?
የ " ምስራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት "ይፋ ባደረገው መረጃ በታጣቂዎቹ ጥቃት ፦
- በርካታ ነዋየ ቅድሳት ተቃጥለዋል፤
- የቤተክርቲያኑ ቅዱሳት ስዕላት በእሳት አረር ተለብለበዋል።
- የቤተክርስቲያኑን አስተዳዳሪ መኖሪያ ቤት በመጠየቅ ቤት ሰብሮ በመግባት በወቅቱ አስተዳዳሪው ባይኖሩም በቤት እቃዎች ላይ ጉዳት ደርሷል።
- የአንድ አገልጋይ ካህናት መኖሪያ ቤት ሙሉ ለሙሉ ተቃጥሏል።
- በቤተክርስቲያን ተጠግተው የሚገኙ ምዕመናን ከፍተኛ ማዋከብ ተፈጽሞባቸዋል።
ሀገረ ስብከቱ ይኸው የታጠቀ ኃይል የደብሩን ገንዘብ ያዥ የሆኑትን አቶ ተስፋ ደሳለኝን አስገድደው እንደወሰዷቸውና ልዑካኑ አስከተገኙበት ሰዓት እንዳልተለቀቁ ገልጿል።
ፎቶ / መረጃ፦ የ ምስራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት
@tikvahethiopia
በምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት ጥንታዊው የ " ሶደሬ ፈለገ ሰላም መድኃኔዓለም ገዳም " ለጊዜው ማንነታቸው ባልታወቀ በታጠቁ ኃይሎች ከፍተኛ ጉዳት እንደደረሰበት ተገለፀ።
ጥንታዊውና በ1963 ዓ.ም የተመሠረተው የሶደሬ ፈለገ ሰላም መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን ከአዳማ 25 ኪ/ሜ ርቀት ላይ ነው የሚገኘው።
ትናንት ከምሽቱ 4:00 ሰዓት ከ50 በላይ የሚሆኑ ለጊዜው ማንነታቸው ያልታወቀ የታጠቁ ኃይሎች የቤተክርስቲያኑን በር አልሰበር ሲላቸው በፈንጂ ሰብረው በመግባት ከፍተኛ ጉዳት እንዳደረሱ የ " ምስራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት " አሳውቋል።
የደረሰውን ጉዳት ለማጣራት የሀገረ ስብሰቱ ጽ/ቤት ልዑካንን የላከ ሲሆን ወደ ቦታው ያቀኑ ልዑካን የሀገረ ስብከቱ ም/ሥራ አስኪያጅ፣ የሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ልዩ ፀሐፊን ጨምሮ ሌሎች አባቶች እና ሓላፊዎች ናቸው።
ልዑኩ በደረሰው ጉዳት ከልብ ማዘኑን ያሳወቀ ሲሆን ካህናትና የአካባቢውን ምዕመናን እንዳፅናኑ ተመላክቷል።
በጥቃቱ ምን ጉዳት ደረሰ ?
የ " ምስራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት "ይፋ ባደረገው መረጃ በታጣቂዎቹ ጥቃት ፦
- በርካታ ነዋየ ቅድሳት ተቃጥለዋል፤
- የቤተክርቲያኑ ቅዱሳት ስዕላት በእሳት አረር ተለብለበዋል።
- የቤተክርስቲያኑን አስተዳዳሪ መኖሪያ ቤት በመጠየቅ ቤት ሰብሮ በመግባት በወቅቱ አስተዳዳሪው ባይኖሩም በቤት እቃዎች ላይ ጉዳት ደርሷል።
- የአንድ አገልጋይ ካህናት መኖሪያ ቤት ሙሉ ለሙሉ ተቃጥሏል።
- በቤተክርስቲያን ተጠግተው የሚገኙ ምዕመናን ከፍተኛ ማዋከብ ተፈጽሞባቸዋል።
ሀገረ ስብከቱ ይኸው የታጠቀ ኃይል የደብሩን ገንዘብ ያዥ የሆኑትን አቶ ተስፋ ደሳለኝን አስገድደው እንደወሰዷቸውና ልዑካኑ አስከተገኙበት ሰዓት እንዳልተለቀቁ ገልጿል።
ፎቶ / መረጃ፦ የ ምስራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#እንድታውቁት ከሚያዚያ 16 ጀምሮ በመላው አዲስ አበባ የነዳጅ ግብይት በአስገዳጅነት በ " ቴሌብር " ብቻ ተግባራዊ ይደረጋል ሲል የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ አሳውቋል። በ " ቴሌብር " ነዳጅ ስለ መቅዳት አሸከርካሪዎች ሊያውቋቸው የሚገቡ ነጥቦች ምንድናቸው ? ☞ በቅድሚያ የ " ቴሌብር "ተጠቃሚ መሆን፤ ☞ በቂ ክፍያ የቴሌብር አካውንት ውስጥ መኖሩን ማረጋገጥ፤ ☞ የ " ቴሌብር " የሚስጥር…
#ነዳጅ #አዲስአበባ
ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት በዲጂታል አማራጭ ተግባራዊ መደረጉን ተከትሎ ተጠቃሚዎች ከቴሌ ብር በተጨማሪ ሌሎችም የክፍያ ሥርዓቶችን መጠቀም እንደሚችሉ ተገልጿል።
ይህን ተከትሎ የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ክፍያ በ " ቴሌ ብር " ብቻ እንደሚፈፀም እያሳወቀ ይገኛል።
ባለፉት ተከታታይ ቀናትም ቢሮው የመኪና ባለቤቶች በቀሩት ጥቂት ቀናት የነዳጅ ክፍያ በ" ቴሌ ብር ብቻ " እንደሚከፈል በመገንዘብ ከእንግልት ለመዳን አስፈላጊውን ሁሉ ዝግጅት እንዲያደርጉ በተደጋጋሚ እያሳወቀ ነው።
ቢሮው መሰል መልዕክቶችን በተረጋገጠ የማህበራዊ መገናኛ ዘዴዎቹ ነው ለህዝብ እያሰራጨ የሚገኘው።
ለመሆኑን የነዳጅ ክፍያ ከ " ቴሌ ብር " ውጭ መፈፀም አይቻልም ?
ኤግል ላየን ሲስተም ቴክኖሎጂ ኃ/የተ/የግል ማኅበር ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጋር በመተባበር ለዚሁ አገልግሎት የሚውል " #ነዳጅ " የተባለ የሞባይል መተግበሪያ ማቅረባቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።
መተግበሪያው ተገልጋዮች የነዳጅ ክፍያቸውን ከንግድ ባንክ አካውንታቸው የተርጋ ቁጥራቸውን ብቻ በመጠቀም መክፈል ያስችላል ያለ ሲሆን የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ የነዳጅ ክፍያው " በቴሌ ብር ብቻ " ነው የሚፈፀመው እያለ ለህዝብ እያሰራጨ ያለው መልዕክት ትክክል እንዳልሆነ አስረድቷል።
" ነዳጅ " የተሰኘው የሞባይል መተግበሪያ ከክፍያ አማራጭነት በተጨማሪ አሽከርካሪዎች አቅራቢያቸው የሚገኙትን ማደያዎች ከአቅርቦታቸው ጋር ማግኘት የሚችሉበት አማራጭም እንዳለው ድርጅቱ ገልጾልናል።
የክፍያ አማራጩ በሀገሪቱ ከሚገኙ ማደያዎች 60 በመቶ ማዳረስ መቻሉንም ጠቁሟል።
መተግበሪያው የት ይገኛል ? https://play.google.com/store/apps/details?id=com.eaglelionsystems.nedaj
በተጨማሪም የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በሲቢኢ ብር መተግበሪያ አማካኝነት ነዳጅ ለመቅዳት የሚያስችል አዲስ የዲጅታል አሠራር መዘርጋቱን ገልጿል።
ክፍያውም በማንኛውም ስልክ በሲቢኢ ብር አጭር ቁጥር ወይም በሞባይል መተግበሪያው መፈጸም ይቻላል ተብሏል። አሰራሩ በሀገሪቱ በሚገኙ ሁሉም ማደያዎች ተግባራዊ እንደሚደረግ ነው የተጠቆመው።
@tikvahethiopia
ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ግብይት በዲጂታል አማራጭ ተግባራዊ መደረጉን ተከትሎ ተጠቃሚዎች ከቴሌ ብር በተጨማሪ ሌሎችም የክፍያ ሥርዓቶችን መጠቀም እንደሚችሉ ተገልጿል።
ይህን ተከትሎ የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ ከሚያዚያ 16 ጀምሮ የነዳጅ ክፍያ በ " ቴሌ ብር " ብቻ እንደሚፈፀም እያሳወቀ ይገኛል።
ባለፉት ተከታታይ ቀናትም ቢሮው የመኪና ባለቤቶች በቀሩት ጥቂት ቀናት የነዳጅ ክፍያ በ" ቴሌ ብር ብቻ " እንደሚከፈል በመገንዘብ ከእንግልት ለመዳን አስፈላጊውን ሁሉ ዝግጅት እንዲያደርጉ በተደጋጋሚ እያሳወቀ ነው።
ቢሮው መሰል መልዕክቶችን በተረጋገጠ የማህበራዊ መገናኛ ዘዴዎቹ ነው ለህዝብ እያሰራጨ የሚገኘው።
ለመሆኑን የነዳጅ ክፍያ ከ " ቴሌ ብር " ውጭ መፈፀም አይቻልም ?
ኤግል ላየን ሲስተም ቴክኖሎጂ ኃ/የተ/የግል ማኅበር ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጋር በመተባበር ለዚሁ አገልግሎት የሚውል " #ነዳጅ " የተባለ የሞባይል መተግበሪያ ማቅረባቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።
መተግበሪያው ተገልጋዮች የነዳጅ ክፍያቸውን ከንግድ ባንክ አካውንታቸው የተርጋ ቁጥራቸውን ብቻ በመጠቀም መክፈል ያስችላል ያለ ሲሆን የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ የነዳጅ ክፍያው " በቴሌ ብር ብቻ " ነው የሚፈፀመው እያለ ለህዝብ እያሰራጨ ያለው መልዕክት ትክክል እንዳልሆነ አስረድቷል።
" ነዳጅ " የተሰኘው የሞባይል መተግበሪያ ከክፍያ አማራጭነት በተጨማሪ አሽከርካሪዎች አቅራቢያቸው የሚገኙትን ማደያዎች ከአቅርቦታቸው ጋር ማግኘት የሚችሉበት አማራጭም እንዳለው ድርጅቱ ገልጾልናል።
የክፍያ አማራጩ በሀገሪቱ ከሚገኙ ማደያዎች 60 በመቶ ማዳረስ መቻሉንም ጠቁሟል።
መተግበሪያው የት ይገኛል ? https://play.google.com/store/apps/details?id=com.eaglelionsystems.nedaj
በተጨማሪም የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በሲቢኢ ብር መተግበሪያ አማካኝነት ነዳጅ ለመቅዳት የሚያስችል አዲስ የዲጅታል አሠራር መዘርጋቱን ገልጿል።
ክፍያውም በማንኛውም ስልክ በሲቢኢ ብር አጭር ቁጥር ወይም በሞባይል መተግበሪያው መፈጸም ይቻላል ተብሏል። አሰራሩ በሀገሪቱ በሚገኙ ሁሉም ማደያዎች ተግባራዊ እንደሚደረግ ነው የተጠቆመው።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Tigray
በፕሪቶሪያው ስምምነት መሰረት ከዚህ ቀደም ህወሓት የከባድ መሳሪያ ትጥቅ እንደፈታና ለሀገር መከላከያ እንዳስረከበ መነገሩ ይታወሳል።
ትላንት ደግሞ መካከለኛ እና ቀላል የቡድን መሳሪያዎችን በመፍታት ለሀገር መከላከያ ሰራዊት እንዳስረከበ ተነግሯል።
ከሀገር መከላከያ ሰራዊት ተወካይ ኮሎኔል ጉደታ ኦፍካ ምን አሉ ?
" በሶስተኛ ዙር የመሳሪያ ርክክብ ሞርታር ዲሽቃ መሰል በርካታ የቡድን መሳሪያዎችን ተረክበናል።
ከፍተኛ ስራ እየተሰራ ነው የሚገኘው ፤ በኢትዮጵያ መንግሥት እና በትግራይ ክልል ባለው መንግሥት ከፍተኛ የትብብር መንፈስ ነው ያለው። ጥሩ ሂደት ነው ያለው ማለት ይቻላል። "
የትግራይ ኃይሎች ተወካይ ኮሎኔል ሙልጌታ ገብረክርስቶስ ምን አሉ ?
" በተደረገው የሰላም ስምምነት መሰረት ትጥቅ የማውረድ ስራ እየተሰራ ነው።
ባለፈው ከባድ መሳሪያዎችን አስረክበናል። አሁን ደግሞ መካከለኛ እና ቀላል የቡድን መሳሪያዎችን የማስረከብ ስራ ጀምረናል።
ስራው ጥሩ ነው፤ በተፋጠነ መልኩ እየሄደ ነው። በሁለቱም ኃይላት በኩል ተግባብቶ የመስራት ሂዘት ጥሩ እየሄደ ነው። "
በፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነትን ተከትሎ የትጥቅ መፍታት ሂደትን የአፍሪካ ህብረት የክትትል እና ቁጥጥር ኮሚሽን በማቋቋም እየተከታተለው ይገኛል።
ከላይ የተገለፁት ሁለቱ ተወካዮችም የዚሁ ኮሚሽን አካል ናቸው።
ፎቶ፦ ENA
@tikvahethiopia
በፕሪቶሪያው ስምምነት መሰረት ከዚህ ቀደም ህወሓት የከባድ መሳሪያ ትጥቅ እንደፈታና ለሀገር መከላከያ እንዳስረከበ መነገሩ ይታወሳል።
ትላንት ደግሞ መካከለኛ እና ቀላል የቡድን መሳሪያዎችን በመፍታት ለሀገር መከላከያ ሰራዊት እንዳስረከበ ተነግሯል።
ከሀገር መከላከያ ሰራዊት ተወካይ ኮሎኔል ጉደታ ኦፍካ ምን አሉ ?
" በሶስተኛ ዙር የመሳሪያ ርክክብ ሞርታር ዲሽቃ መሰል በርካታ የቡድን መሳሪያዎችን ተረክበናል።
ከፍተኛ ስራ እየተሰራ ነው የሚገኘው ፤ በኢትዮጵያ መንግሥት እና በትግራይ ክልል ባለው መንግሥት ከፍተኛ የትብብር መንፈስ ነው ያለው። ጥሩ ሂደት ነው ያለው ማለት ይቻላል። "
የትግራይ ኃይሎች ተወካይ ኮሎኔል ሙልጌታ ገብረክርስቶስ ምን አሉ ?
" በተደረገው የሰላም ስምምነት መሰረት ትጥቅ የማውረድ ስራ እየተሰራ ነው።
ባለፈው ከባድ መሳሪያዎችን አስረክበናል። አሁን ደግሞ መካከለኛ እና ቀላል የቡድን መሳሪያዎችን የማስረከብ ስራ ጀምረናል።
ስራው ጥሩ ነው፤ በተፋጠነ መልኩ እየሄደ ነው። በሁለቱም ኃይላት በኩል ተግባብቶ የመስራት ሂዘት ጥሩ እየሄደ ነው። "
በፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነትን ተከትሎ የትጥቅ መፍታት ሂደትን የአፍሪካ ህብረት የክትትል እና ቁጥጥር ኮሚሽን በማቋቋም እየተከታተለው ይገኛል።
ከላይ የተገለፁት ሁለቱ ተወካዮችም የዚሁ ኮሚሽን አካል ናቸው።
ፎቶ፦ ENA
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
ፎቶ፦ ዛሬ የሲዳማ ብሔር የዘመን መለወጫ " ፊቼ ጫምበላላ " በዓል በሀዋሳ ጉዱማሌ በመከበር ላይ ይገኛል።
Photo Credit : EBC
@tikvahethiopia
Photo Credit : EBC
@tikvahethiopia