TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.3K photos
1.5K videos
211 files
4.1K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update የብፁዕ አቡነ አረጋዊ (ዶ/ር) እና የብፁዕ አቡነ ባስልዮስ ሥርዓተ ቀብር እሑድ መጋቢት 17 ቀን 2015 ዓ.ም በመንበረ ጸባኦት ቅደስት ሥላሴ ካተድራል እንደሚፈጸም የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ (ዶ/ር) መግለፃቸውን የኢኦተቤ ቴሌቪዥን ዘግቧል። ብፁዕ አቡነ አረጋዊ (ዶ/ር) ለረጅም ጊዜ በሀገር ውስጥ እና በውጭ በህክምና ሲረዱ ቆይተው ሊሻላቸው ሳይችል ቀርቶ ትላንት…
ፎቶ፦ ዛሬ የብፁዕ አቡነ ባስልዮስ እና የብፁዕ ዶ/ር አቡነ አረጋዊ ሥርዓተ ቀብር ተፈፅሟል።

ስርዓተ ቀብራቸው የተፈፀመው ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት በሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን የሃይማኖት ተቋማት አባቶች፤ የመንግስት ኃላፊዎች፤ ከኖርዌይና ከተለያየ አካባቢ የመጡ የውጪ ሀገር ወዳጆቻቸው እና በበርካታ ምዕመናን በተገኙበት ነው።

Photo Credit : EOTC TV

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ፤ ሊቀ ጉባኤ አባ ተክለሃይማኖት ወልዱ በትላንትናው ዕለት የተደረገውን ጥሪ በመቀበል የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ በተገኙበት የተደረሰውን ስምምነት ሙሉ በሙሉ በመቀበል በዛሬው ዕለት ወደ እናት ቤተክርስቲያን መመለሳቸውን የሚገልዕ ደብዳቤ ለመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት በማቅረብ በይፋ መመለሳቸውን አሳወቀች።

ቤተክርስቲያኗ በተደረሰው ስምምነት መሰረት ፦

- ወደ ሥራ እንደምትመልሳቸው
- ደመወዛቸውን እንደምትከፍል
-  የታሸገውን ቤታቸውን በመክፈት እንደምታስረክባቸው ገልጻለች።

@tikvahethiopia
#ጫሞ

በደቡብ ክልል ጫሞ ሐይቅ ላይ በጀልባ ሲጓዙ የነበሩ 8 ሰዎች፤ ባጋጠማቸው የማዕበል አደጋ ምክንያት ሰጥመው ህይወታቸው አለፈ።

" ኢትዮጵያ ኢንሳይደር " የአማሮ ልዩ ወረዳ ኮሚዩኒኬሽን ዋቢ አድርጎ እንደዘገበው አደጋው የደረሰው ትላንት ቅዳሜ ከሰዓት ለኃላ ነው።

ባለሞተር ጀልባው የአማሮ ልዩ ወረዳ አልፋጮ ቀበሌ ነዋሪዎችን አሳፍሮ ወደ አርባ ምንጭ በመጓዝ ላይ ሳለ ነው በጫሞ ሐይቅ ላይ በነበረው ማዕበል የመስጠም አደጋው ያጋጠመው።

በአደጋው የጀልባውን ሹፌር ጨምሮ ስምንት ሰዎች ህይወታቸው አልፏል።

አደጋው መከሰቱ እንደታወቀ የተጎጂዎችን ህይወት ለማትረፍ ጥረት ቢደረግም በጫሞ ሐይቅ ላይ በነበረው ከፍተኛ ማዕበል ምክንያት አልተሳካም።

ከአደጋው መድረስ በኋላ ከአርባ ምንጭ ከተማ በመጡ ዋናተኞች ጭምር ሕይወት ለማዳን ቢሞከርም በሰዓቱ የነበረው ማዕበል አላስቻለም ተብሏል።

በጫሞ ሐይቅ ላይ የነበረው ማዕበል ዛሬ ጠዋት ጋብ ማለቱን ተከትሎም ፤ የሟቾችን አስክሬን ለማግኘት ፍለጋው መቀጠሉን የወረዳው ኮሚኒኬሽን አሳውቋል።

(እስካሁን የተገኘ አስክሬን የለም)

Credit : Ethiopia Insider

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ጫሞ በደቡብ ክልል ጫሞ ሐይቅ ላይ በጀልባ ሲጓዙ የነበሩ 8 ሰዎች፤ ባጋጠማቸው የማዕበል አደጋ ምክንያት ሰጥመው ህይወታቸው አለፈ። " ኢትዮጵያ ኢንሳይደር " የአማሮ ልዩ ወረዳ ኮሚዩኒኬሽን ዋቢ አድርጎ እንደዘገበው አደጋው የደረሰው ትላንት ቅዳሜ ከሰዓት ለኃላ ነው። ባለሞተር ጀልባው የአማሮ ልዩ ወረዳ አልፋጮ ቀበሌ ነዋሪዎችን አሳፍሮ ወደ አርባ ምንጭ በመጓዝ ላይ ሳለ ነው በጫሞ ሐይቅ ላይ በነበረው…
" ተሳፋሪዎችን ከዚህ በኋላ በሕይወት የማግኘት ተስፋው ተሟጧል " - የአማሮ ልዩ ወረዳ ሰላም እና ጸጥታ ቢሮ

የደቡብ ፖሊስ ትላንትና በ #ጫሞ_ሐይቅ ላይ ለሰመጠችው ጀልባ መንስኤው ከመጠን በላይ መጫን እና ባልተለመደ ሁኔታ የተከሰተ ማዕበል ነው ብሏል።

የዞን ፖሊስ በበኩሉ ጀልባዋ ከሥምንቱ ሰዎች በተጨማሪ #ሙዝ እና #ዕቃ መጫኗን አሳውቋል።

የሕይወት አድን ሥራ ተጠናክሮ ቀጥሏል ያለው ፖሊስ ለዚህም የተለያዩ ጀልባዎችና ዋናተኞች ፍለጋ ላይ መሆናቸውን ገልጿል።

በተከናወነው የፍለጋ ሥራ ከጫማዎች እና የተለያዩ አልባሳት ባለፈ የተገኘ ነገር እንደሌለ ተገልጿል።

የአማሮ ልዩ ወረዳ አስተዳደር ሰላምና ጸጥታ ቢሮ ለኤፍ ቢ ሲ በሰጠው ቃል እስካሁን ድረስ በሕይወት የተገኘ አለመኖሩን ጠቁመዋል።

ተሳፋሪዎችን ከዚህ በኋላ በሕይወት የማግኘት ተስፋው መሟጠጡንም ቢሮው ገልጿል።

(ኤፍቢሲ)

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ካህኑን ማን ገደላቸው ? " ኃይሌ ጋርመንት " የሁርሲሳ ደብረ ገነት ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን ቀዳሽ ካህን ቀሲስ ዐባይ መለስ " ማንነታቸው አልታወቀም " በተባሉ አካላት በተፈፀመባቸው ጥቃት ተገድለዋል። ካህኑን የሚያውቋቸው አገልጋዮች /ምዕመናን  ስለነበረው ሁኔታ / ስለጥቃቱ ምን አሉ ? (ለማህበረ ቅዱሳን ቴሌቪዥን ከተናገሩት የተወሰደ) ቃላቸውን የሰጡ ምዕመን አንድ ፦ " ትላንት/መጋቢት…
#መግለጫ

በኢትዮጵያ ኦርቶኮስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ፤ መንግስት የቄስ ዓባይ መለሰን ገዳዮች ተከታትሎ ለፍርድ ያቅርብ አለ።

ሀገረ ስብከቱ በሰጠው መግለጫ ፤ " መንግሥት የቤተ ክርስቲያን አገልጋይ በመሆናቸው ምክንያት በአሰቃቂ ሁኔታ በመንገድ ላይ ተደብድበው ሕይወታቸው እንዲያልፍ የተደረጉት የቄስ ዐባይ መለሰ ገዳዮችን ተከታትሎ ለፍርድ ያቅርብ " ብሏል።

አክሎም ፤ " ችግሩን ከሥር ከመሠረቱ በመፍታት የአገልጋዮችንና የምእመናን መብት እንዲያስከብር " ሲል ጠይቋል።

ከዚህ ባለፈ በሸገር ከተማ አስተዳደር አብያተ ክርስቲያናትን የማፍረስ ድርጊት እየተፈፀመ መሆኑን በመግለፅ ይህ ድርጊት በአስቸኴይ እንዲቆም እንዲደረግ ጥሪ አቅርቧል።

እስካሁን የፈረሱትን አብያተ ክርስቲያናት ቦታ ተመላሽ እንዲያደርግ እና የፈረሰውን ቤተ ክርስቲያንም በራሱ ወጪ እንዲያሠራ እንዲደረግ ሀገረ ስብከቱ ጠይቋል።

(ሙሉ መግለጫው ከላይ ተያይዟል)

@tikvahethiopia
ፎቶ / ቪድዮ ፦ የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ክለብ የሆነው ቼልሲ ትላንት እሁድ እለት በክለቡ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ ክፍት የሆነ የ " ኢፍጣር " ስነሥርዓት በስታምፎርድ ብሪጅ ስታዲየም አስተናግዷል።

በመቶዎች የሚቆጠሩ ምዕመናን በምዕራብ ለንደኑ ግፉዝ ስታዲየም  ተሰብስበው የኢፍጣር ስነስርዓቱን ያከናወኑ ሲሆን ስነስርዓቱ የተዘጋጀው በቼልሲ ፋውንዴሽን እና በ " ረመዷን ቴንት ፕሮጀክት " ነው።

Video Credit : Bein Sport

@tikvahethiopia