TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.4K photos
1.51K videos
215 files
4.12K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update

የተቋረጠው #የባጃጅ_ትራንስፖርት አገልግሎትን አስመልከቶ ዛሬ መጋቢት 8/2015 ዓ.ም መግለጫ ይሰጣል ተብሏል።

የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ ዛሬ ከሰዓት 9 ሰዓት የካቲት 30 ቀን 2015 ዓ.ም የተቋረጠውን የባጃጅ ትራንስፖርት አገልግሎት አሰጣጥን በተመለከተ መግለጫ እንደሚሰጥ " አሻም ቴሌቪዥን " ዘግቧል።

የባጃጅ ትራንስፖርት አገልግሎት መቋረጡን ተከትሎ አሽከርካሪዎች የዕለቱ ጉርሳቸውን ማጣታቸውን፣ ተጠቃሚዎችም ለከፍተኛ እንግልት መዳረጋቸውን እየገለፁ እንደሚገኙ ይታወቃል።

የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን /ኢሰመኮ ትላንት ባወጣው መግለጫ የባጃጅ ትራንስፖርት እገዳው እንዲነሳ መጠየቁ ይታወሳል፡፡

Credit : #AshamTV

@tikvahethiopia
#አቢሲንያ_ባንክ

ውድ ደንበኞቻችን ፦

ባንካችን አቢሲንያ ለደንበኞቹ የአገልግሎት አሰጣጡን የበለጠ ለማሻሻል እንዲረዳው የፊታችን ቅዳሜና እሁድ ማለትም መጋቢት 9 እና 10 ቀን 2015 ዓ.ም ነባሩን ሲስተም የማሳደግ (System Upgrading) ያከናውናል፡፡

በመሆኑም በተጠቀሱት ቀናት መላው ቅርንጫፎቻችን፤የቨርቹዋል ባንኪንግ ማዕከሎቻችን፤ የኦንላይን ባንኪንግ ሲስተሞቻችንና ከባንክ ወደባንክ የማስተላለፍ አገልግሎት የማንሰጥ መሆኑን በታላቅ አክብሮት እናሳውቃለን፡፡

ይሁን እንጂ በተጠቀሱት ቀናት የኤቲኤም ማሽኖቻችን የተለመደውን አገልግሎት የሚሰጡ በመሆኑ ከ1275 በላይ በሆኑት የኤቲኤም ማሽኖቻችንን መጠቀም የምትችሉ መሆኑን በታላቅ አክብሮት እንገልፃለን፡፡    

አቢሲንያ የሁሉም ምርጫ!
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#ባጃጅ

• " ገደቡ ከነገ ጀምሮ ይነሳል "

• " በየትኛውም ርቀት ከ5 ብር በላይ ማስከፈል አይቻልም "


በአዲስ አበባ በባጃጅ አገልግሎት ላይ የተጣለው እግድ ከነገ ጀምሮ እንደሚነሳ የትራንስፖርት ቢሮ አስታውቋል።

ቢሮው ዛሬ በሰጠው መግለጫ የባጃጅ አገልግሎት ላይ የተጣለው እግድ ከነገ ቅዳሜ መጋቢት 8/2015 ጀምሮ እንደሚነሳ አስታውቋል።

የባጃጅ ተሽከርካሪዎች በየትኛውም ርቀት ከ5 ብር በላይ ማስከፈል እንደማይችሉ ቢሮው ገልጿል።

ቢሮው የባጃጅ ትራንስፖርት አገልግሎት የሚመራበት መመሪያ መዘጋጀቱን ይፋ ማድረጉን " ኢትዮጵያ ኢንሳይደር " ዘግቧል።

@tikvagethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ባጃጅ • " ገደቡ ከነገ ጀምሮ ይነሳል " • " በየትኛውም ርቀት ከ5 ብር በላይ ማስከፈል አይቻልም " በአዲስ አበባ በባጃጅ አገልግሎት ላይ የተጣለው እግድ ከነገ ጀምሮ እንደሚነሳ የትራንስፖርት ቢሮ አስታውቋል። ቢሮው ዛሬ በሰጠው መግለጫ የባጃጅ አገልግሎት ላይ የተጣለው እግድ ከነገ ቅዳሜ መጋቢት 8/2015 ጀምሮ እንደሚነሳ አስታውቋል። የባጃጅ ተሽከርካሪዎች በየትኛውም ርቀት ከ5 ብር በላይ…
#ተጨማሪ

" የስራ ሰዓት ከጠዋቱ 12 ሰአት እስከ ምሽቱ 3 ሰዓት ብቻ ነው " - የአዲስ አበባ ከተማ ትራንስፖርት ቢሮ

ተቋርጦ የነበረው የባጃጅ ትራንስፖርት አገልግሎት ከነገ ጀምሮ ባጃጆቹ በተመደቡላቸው መስመሮች ብቻ አገልግሎት መስጠት እንደሚጀምሩ የአዲስ አበባ ከተማ ትራንስፖርት ቢሮ ዛሬ በሰጠው መግለጫ አሳውቋል።

በመግለጫው ምን ተባለ ?

- ከአገልግሎቱ ጋር በተያያዘ ለተፈጠሩ ችግሮች መንስኤ ናቸው የተባሉት ፦
• ህግን አክብሮ አገልግሎት አለመስጠት፣
• በአብዛኛው አሽከርካሪ ዘንድ ደረጃውን የሚመጥን መንጃ ፍቃድ አለመያዝ
• የታሪፍ ስርዓት አለመኖር ዋንኞቹ ናቸው።

- አሁን በተዘጋጀ መመሪያ መሰረት ቢሮው በለያቸው የስምሪት መስመሮች አገልግሎት እንደሚሰጥ ተገልጿል።

- 138 ጊዜአዊ ታፔላዎችን ከዋናው መስመር ውጪ ተዘጋጅተዋል።

- የትራፊክ ምልክቶች ተከላ ማከናወን እና ማህበራትን ማደራጀት ዋንኛ ስራ ነበር። በ8 ክ/ከተሞች 123 ማህበራትን የማደራጀት ስራ የተሰራ ሲሆን አገልግሎቱም በኮድ 1 ታርጋ ብቻ ይሰጣል።

- የተሳፋሪ መጠን አሽከርካሪውን ጨምሮ 4 ሰው ብቻ ሴሆን የስራ ሰዓት ከጠዋቱ 12 ሰአት እስከ ምሽቱ 3 ሰዓት ብቻ ነው። ህጉን ተላልፈው የተገኙ አሽከርካሪዎች በየደረጃው ቅጣት ይጣልባቸዋል።

- በከተማው መደበኛ ትራንስፖርት በማይገኝበት ከ0 ነጥብ 9 እስከ 2 ነጥብ 45 ኪሎ ሜትር ርቀት ብቻ በ5 ብር ታሪፍ አገልግሎት እንዲሰጡ ተወስኗል።

- የባጃጅ ተሽከርካሪዎች በየትኛውም ርቀት ከ5 ብር በላይ ማስከፈል አይችሉም።

Credit : ADDIS MEDIA NETWORK / FBC

@tikvahethiopia
የጀግና እናቶች ቀን . . .

የኢንፊኒቲ በጎ አድራጎት ድርጅት "የጀግና እናቶች ቀን በሚል" የተለያዩ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጫናዎችን ተቋቁመው የሚኖሩ እናቶችን ጀግንነት ለመመስከር ያለመ ዝግጅት ነገ ቅዳሜ በግዮን ሆቴል አዘጋጅቷል።

ዝግጅቱ በተለይ በአእምሮ ልምሻ/ Cerbral Palsy የተጠቁ ልጆችን የሚያሳድጉ እናቶች ጥንካሬያቸውንና ተሞክሯቸውን የሚያካፍሉበት በመሆኑ ይህንን ቀን አብረናቸው እንድናሳልፍ ነው ጥሪ ያቀረቡት።

"እኚህ ጠንካራ እናቶች ያልተሰበረ ጽናት፤ ያልተበገረ ማንነት ያላቸው በመሆናቸው ከምንረዳቸው በላይ የምንማርባቸው ናቸው" በማለት ዝግጅቱን ማሰናዳቱንና ማንኛው ሰው አንዲገኝ ጥሪ መደረጉን ድርጅቱ በላከልን መልዕክት ገልጿል።

ዝግጅቱ ነገ ቅዳሜ መጋቢት 09 በጊዮን ሆቴል ከቀኑ 7:00 ጀምሮ የሚደረግ ሲሆን ማንኛውም ሰው በነጻ መሳተፍ ይችላል ተብሏል።

@tikvahethmagazine
#መተሐራ

በትላንትናው ዕለት በ #መተሐራ_ከተማ በደረሰ ጥቃት 6 የጎዳና ተዳዳሪዎችን ጨምሮ 8 ሰዎች ተገደሉ።

በመተሐራ እና አካባቢው ያሉ የቲክቫህ ቤተሰብ አባላት አሁንም በታጣቂዎች እየደረሰ ያለው ጥቃት መቀጠሉን ገልጸዋል።

በትላንትናው ዕለትም ታጣቂዎች ባደረሱት ጥቃት 6 የጎዳና ተዳዳሪዎችን ጨምሮ በአጠቃላይ 8 ሰዎች መገደላቸውን ጠቅሰዋል።

ጥቃቱ ትላንት ሐሙስ መጋቢት 07 ቀን 2015 ምሽት 3:00 አካባቢ መፈጸሙ የተገለጸ ሲሆን ህይወታቸው ካለፉ ሰዎች በተጨማሪ በ4 ሰዎች ላይ ጉዳት መድረሱን ነው የገለጹልን።

ጉዳት ከደረሰባቸው ሰዎች መካከልም ወደ አዳማ ሪፈር የተጻፈላቸው መኖራቸውንም ነው የጠቆሙት።

አንድ የቤተሰባችን አባል ፦ " ሌሊት ላይ መጥተው ሰው ገድለው ነው የሚሄዱት፤ ከ6 ወር በፊት 15 ሰዎች ገድለዋል፤ ከአንድ ወር በፊት ደግሞ እንዲሁ 4 ሰዎች ተገድለው ነበር። ትላንትና ደግሞ የጎዳና ልጆችን ጨምሮ 8 ሰዎችን ገድለዋል ፤ ማን እንደገደላቸው አይታወቅም፤ ያው ሁል ጊዜ ሸኔ ነው የሚባለው እንደዛ እየተባለ ነው እስካሁን መለየት አልቻልንም። ...መከላከያ በተደጋሚ ይመጣል፤ እነርሱ ሲመጡ እነዚ ይሸሻሉ ከዚያ ደግሞ ትንሽ መከላከያ ራቅ ሲልላቸው መጥተው ሰዎች ይገላሉ። " ሲሉ የነበረውን ሁኔታ ገልጸዋል።

አክለውም ፤  " በከተማችን ጥቃቱ በተደጋጋሚ የሚፈጸም ሲሆን የዚህኛው ዙር ጥቃት እጅግ ሰብዓዊነት በጎደለው መልኩ በጎዳና ላይ የነበሩ ልጆች ላይ የተፈጸመ በመሆኑ በጣም አሳዛኝ ነው። ይህ ምንም ዓላማ የሌለውና ህብረተሰቡን ለማሸበር የተደረገ ነው " ሲሉ ገልፀዋል።

ጥቃቱ ከመድረሱ በፊት መብራት እንዲሁም ኔትዎርክ ጠፍቶ እንደነበር የገለጹልን የመተሀራ ቤተሰቦች "ጥቃቱ ከተፈጸመ በኋላ ፊሽካ ነፍተው ከከተማው ሸሹ፤ ይህ ከዚህ በፊት በነበሩት ጥቃቶችም በተደጋጋሚ የተደረገ ነው። " ሲሉ መረጃቸውን አድርሰዋል።

ስለደረሰው ጥቃት እንዲሁም ጥቃቱን ተከትሎ የመንግስት የጸጥታ አካላት ስለወሰዱት እርምጃ ከከተማው ከአስተዳደር አካላት መረጃ ለማግኘት ያደረግነው ጥረት ለጊዜው አልተሳካም።

@tikvahethiopia
" ምንም ትርጉም የሌለው ትዕዛዝ ነው " - ሩስያ

የዓለም አቀፉ የወንጀል ፍ/ቤት (ICC) በሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ላይ የእስር ትዕዛዝ ማውጣቱ ተሰምቷል።

ፕሬዝዳንቱ ህጻናትን በሕገወጥ መንገድ ከዩክሬን ወደ ሩሲያ ማፈናቀልን ጨምሮ በጦር ወንጀሎች ተጠያቂ ናቸው ሲል ነው የእስር ትዕዛዙን ያወጣባቸው።

እነዚህ ወንጀሎች የተፈጸሙት ካለፈው ዓመት የካቲት አጋማሽ ጀምሮ መሆኑኑ ተመላክቷል።

ዓለም አቀፉ የወንጀል ፍርድ ቤት " ፕሬዝዳንት ፑቲን ህጻናትን በማፈናቀል እጃቸው አለበት " በሚል ክስ የመሰረተው በድርጊቱ በቀጥታ በመሳተፍ እንዲሁም ከሌሎች ጋር እንደፈጸሙት የሚያሳምን በቂ ምክንያት እንዳለው በማመልከት ነው።

በተጨማሪ የሩሲያው መሪ ህጻናቱን ከዩክሬን የሚያባርሩ ሌሎች አካላትን ለማስቆም ያላቸውን ሥልጣናቸውን ሳይጠቀሙ እንደቀሩ ነው ፍርድ ቤቱ ያሳወቀው።

ከፕሬዝዳንት ፑቲን በተጨማሪ የሩሲያ የህጻናት መብት ኮሚሽነር ማሪያ ሎቮቫ-ቤሎቫም በዓለም አቀፉ የወንጀል ፍርድ ቤት ተፈላጊ ሰው ሆነዋል።

በፕሬዝዳንቱም ሆነ በኮሚሽነሯ ላይ የፍርድ ቤቱ የእስር ትዕዛዝ ቢወጣም ፍ/ቤቱ ተጠርጣሪዎችን የመያዝ ሥልጣን ግን የለውም።

ይህ ዓለም አቀፍ የወንጀል ፍርድ ቤት የሚያወጣው ትዕዛዝ ተፈጻሚ የመሆን መብት ያለው ባቋቋሙት እና ስምምነት በፈረሙ አገራት ውስጥ ብቻ ነው።

ሩሲያ የዚህ ስምምነት #ፈራሚ_ባለመሆኗ የፕሬዝዳንት ፑቲን ለፍርድ ቤቱ ተላልፎ የመሰጠት ጉዳይ የመነመነ ነው።

ሩሲያ የዓለም አቀፉ ፍርድ ቤት የእስር ትዕዛዝ " ምንም ትርጉም የለውም " ብላለች።

ሩሲያ ከዩክሬን ጦርነት ጋር በተያያዘ በተደጋጋሚ የሚቀርቡባትን መጠነ ሰፊ ጥሰቶች ክስ በተደጋጋሚ ውድቅ ስታደርግ መቆየቷ ይታወቃል።

መረጃው ከቢቢሲ የተገኘ ነው።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ትግራይ በሰላም ስምምነቱ መሰረት የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ማቋቋሚያ ኮንፈረንስ በዚህ ሳምንት ለሁለት ቀናት ተካሂዷል። በኮንፈረንሱ የተለያዩ ውሳኔዎች መተላለፋቸው ተገልጿል። የኮንፈረንሱ ውክልና አስተዳደር፣ የሚቋቋመው ጊዜያዊ አስተዳደር ተልዕኮ፣ የአስተዳደሩ አደረጃጀትና የስልጣን ክፍፍል ላይ ውይይት እንደተደረገበት እና ስምምነት ላይ እንደተደረሰባቸው ተገልጿል። ወደ ጦርነት ያስገቡ የትግራይ…
#Tigray

አቶ ጌታቸው ረዳ የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት እንዲሆኑ በህወሓት ማዕከላይ ኮሚቴ አብላጫ ድምፅ ማግኘታቸው ተነገረ።

የህወሓት ማዕከላዊ ኮሚቴ ስብሰባ አድርጎ ነበር።

በዚህም #አቶ_ጌታቸው_ረዳን በትግራይ ክልል ለሚቋቋመው ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንታዊ እጩ አድርጎ አብላጫ ድምጽ መስጠቱን ቅርበት ያላቸው የፓርቲው ምንጮች እንደገለፁለት የአሜሪካ ድምፅ ሬድዮ ጣቢያ (ቪኦኤ) የትግርኛው አገልግሎት ክፍል ዘግቧል።

የአቶ ጌታቸው ረዳና ሌሎች የጊዜያዊ አስተዳደሩ ካቢኔ ኣባላት ሹመት፣ የክልሉ አመራሮች ከፌደራሉ መንግሥት ጋር በጊዜያዊ አስተዳደሩ አወቃቀር ጉዳይ ተወያይተው #ካፀደቁት በኋላ ጊዜያዊ አስተዳደሩ ሥራ እንደሚጀምር ነው ' ቪኦኤ ትግርኛ ' ምንጮቹን ዋቢ አድርጎ በዘገባው ያመለከተው።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ተጨማሪ " የስራ ሰዓት ከጠዋቱ 12 ሰአት እስከ ምሽቱ 3 ሰዓት ብቻ ነው " - የአዲስ አበባ ከተማ ትራንስፖርት ቢሮ ተቋርጦ የነበረው የባጃጅ ትራንስፖርት አገልግሎት ከነገ ጀምሮ ባጃጆቹ በተመደቡላቸው መስመሮች ብቻ አገልግሎት መስጠት እንደሚጀምሩ የአዲስ አበባ ከተማ ትራንስፖርት ቢሮ ዛሬ በሰጠው መግለጫ አሳውቋል። በመግለጫው ምን ተባለ ? - ከአገልግሎቱ ጋር በተያያዘ ለተፈጠሩ ችግሮች መንስኤ…
#AddisAbaba

ዛሬ የባለ ሶስት እግር ተሽከርካሪዎች በትራንስፖርት ቢሮ የተዘጋጁት መመሪያዎች መሰረት ወደ ስራ መመለሳቸው በከተማው የተለያዩ አካባቢዎች ተዘዋውረን ተመልክተናል።

ባጀጆች ዳግም ወደ አገልግሎት ተመልሰው እየሰሩባቸው ያሉት መመሪያዎች ምንድናቸው ?

1. የዘርፉ የስምሪት መስመሮች በከተማዋ ዳርቻዎችና አዋሳኝ አካባቢዎች፣ በሰፋፊ የጋራ መኖሪያ ቤቶች ሳይቶች እና በተለዩ አንዳንድ የከተማው የውስጥ ለውስጥ አጫጭር መንገዶች ላይ የተወሰነ ነው።

2. በዚህ ስምሪት ስርዓት ውስጥ መሳተፍ የሚችሉት ኮድ 1 ሰሌዳ ያላቸው ባለሦስት እና ባለአራት እግር በተለምዶ ባጃጅ ተብለው የሚጠሩ ተሸከርካሪዎች ብቻ ናቸው።

3. በቢሮው በተለዩ የስምሪት መስመሮች ብቻ ነው አገልግሎት እየተሰጠ የሚገኘው።

4. የመጫን አቅም 3 ሰው ብቻ ነው።

5. ለየትኛውም ርቀት ታሪፍ 5 ብር ነው።

6. መደበኛ የትራንስፖርት አገልግሎት መስጫ ሰዓት ከጠዋቱ 12፡00 ጀምሮ እስከ ምሽቱ 03፡00 ሰዓት ድረስ ብቻ ነው።

7. በዋና መንገድና አደባባይ ላይ የስምሪት መነሻና አገልግሎት አሰጣጥ አይፈቀድም፣ የነዳጅ ድጎማ አይደረገም።

@tikvahethiopia
" ትምህርት ቤቶቹን በመጪው ሚያዝያ ወር እንደገና ለመክፈት ዕቅድ ተይዟል " - UNICEF

በትግራይ በጦርነቱ ምክንያት ከሁለት ዓመታት በላይ ተዘግተው የነበሩ ትምህርት ቤቶችን እንደገና ለመክፈት ዕቅድ መውጣቱ ተገልጿል።

በትግራይ ተማሪዎች ከትምህርት ገበታቸው ከመራቃቸው ባለፈ መምህራንም ለሁለት ዓመታት ደመወዝ አልተከፈላቸውም።

ትምህርት ቤቶቹን በመጪው #ሚያዝያ_ወር እንደገና ለመክፈት ዕቅድ እንደተያዘም የዩኒሴፍ (UNICEF) የትምህርት ኃላፊ ቻንስ ብሪግስ ተናግረዋል።

ይህን ያሉት ለBBC Focus on Africa ሬዲዮ ነው።

" በትግራይ ሙሉ በሙሉ የትምህርት ሥርዓቱ ፈርሷል። " ያሉት ቻንስ ብሪግስ " ካለፈው ዓመት ሐምሌ ወር ጀምሮ 2.3 ሚሊዮን ህጻናት ከትምህርት ገበታ ውጪ መሆናቸው የሚያሳይ መረጃ አለን "  ብለዋል።

በመቐለ ከባለቤታቸው እና ከአራት ልጆቻቸው ጋር ነዋሪ የሆኑት አቶ መንግሥት ገብረመድኅን የእርስ በርስ ጦርነቱ በተቀሰቀሰበት ወቅት ሁለቱ ልጆቻቸው የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርታቸውን ይከታተሉ ነበር።

ትምህርት ከተቋረጠም በኋላ " እነሱን ለማስተማር ሞከርኩ፣ ነገር ግን መረጋጋት እና ትኩረታቸውን መሰብሰብ አልቻሉም " ብለዋል።

" የአየር ጥቃቶች እና የድሮን ጥቃቶች ድምጽ ይሰማሉ። ህጻናቱን ጠመንጃ ይዘው የሚሄዱ ወታደሮችንም ያያሉ። እነሱንም ለማስመሰል ይሞክራሉ። " ሲሉ የነበረውን ሁኔታ ገልጸዋል።

በመቐለ ዩንቨርስቲ ረዳት ፕሮፌሰር የሆኑት አቶ መንግሥት ለወራት ደመወዝ ሳይከፈላቸው መቆየቱን ተናግረዋል።

" ደመወዛችን አየተሰጠን ስላልነበር ልጆቻችን ምን እንደምንመግባቸው ያስጨንቀን ነበር። ስለዚህ እነሱን በማስተማር ላይ ማተኮር ፈታኝ ነበር። ነገር ግን ትናንትና ደመወዜን ተቀበልኩ፣ አሁን ለልጆቼም ልብስ እና ምግብ መግዛት እችላለሁ " ብለዋል።

በትግራይ በነበረው ጦርነት ከዛም በፊት በነበረው የኮቪድ-19 ወረርሽኝ ሚሊዮኖች ተማሪዎች  ከትምህርት ገበታቸው ርቀዋል ፤ መምህራን ደግሞ በጦርነት ምክንያት ደሞዝ ሳይከፈላቸው ቆይቷል።

#ቢቢሲ #BBCFocusonAfrica

@tikvahethiopia
#ብርሃን_ባንክ

በሆቴሎች፤ በሱፐርማርኬቶች እና በቅርንጫፎቻችን በሚገኙት የፖስ ማሽኖቻችን የቪዛና ማስተር ካርድዎን ተጠቅመው ግብይትዎን ያቅልሉ፡፡

አዳዲስ እና ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት ከታች የሚገኙትን ሊንኮች በመጫን የማህበራዊ ድህረ-ገጾቻችንን ይቀላቀሉ !

Facebook: https://www.facebook.com/berhanbanksc
Telegram: https://t.iss.one/berhanbanksc
Instagram: https://www.instagram.com/berhanbanksc/
Twitter: https://twitter.com/berhanbanksc
LinkedIn: https://www.linkedin.com/company/76151001
YouTube: https://www.youtube.com/channel/UCvOxWe439dzMSvNnMrjcYVQ

እንደ ስማችን ብርሃን ነው ስራችን!

@berhanbanksc
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#እጆች_ይናገራሉ_አይኖች_ያዳምጣሉ

የምልክት ቋንቋን የሥራ ቋንቋ ማድረግ ለሰብአዊ መብቶች መከበር ትልቅ አስተዋጽኦ ይኖረዋል።

በኢትዮጵያ ምን ያህል መስማት የተሳናቸው ሰዎች እንዳሉ ትክክለኛውን ቁጥር ለማወቅ አስቸጋሪ ቢሆንም፤ እስከ 1 ሚሊዮን የሚደርሱ ከመስማት ጋር የተገናኘ ጉዳት ያለባቸው ሰዎች እንደሚኖሩ ይገመታል።

የምልክት ቋንቋዎች የራሳቸው ሰዋሰው፣ መዝገበ ቃላት እና ዘዬ ያላቸው የተሟሉ፣ ቋንቋዎች ሲሆኑ፤ ከውልደት ጀምሮ መስማት ለተሳናቸው ሕጻናት ደግሞ ብቸኛ የመጀመሪያ ቋንቋቸው ነው፡፡

ከኢትዮጵያ የብሔር ብዝኃነት አንጻር ተጨማሪ ቋንቋዎችን በሥራ ቋንቋነት ለማካተት የሚያስችል የቋንቋ ፖሊሲ በቀረጻ ሂደት ላይ መሆኑ ቢታወቅም፤ መስማት ለተሳናቸው ሰዎች የግድ አስፈላጊ የሆነውን የምልክት ቋንቋን የሥራ ቋንቋ ለማድረግ በቂ ትኩረት አላገኘም።

ኢትዮጵያ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዓለም አቀፍ የአካል ጉዳተኞች መብቶች ስምምነትን በአዋጅ ቁጥር 676/2002 አጽድቃ ተቀብላለች። በዚህም የምልክት ቋንቋ ትምህርትን የማመቻቸትና የማበረታታት ግዴታ አለባት።

የምልክት ቋንቋን ይፋዊ የሥራ ቋንቋ ማድረግ መስማት የተሳናቸውን ሰዎች መረጃ የማግኘት መብት ለማረጋገጥ፣ በማኅበረሰብ ውስጥ በሁሉም ዘርፍ የሚኖራቸውን የተሳትፎ መጠንና የአገልግሎት ተደራሽነት ለማሳደግ ብሎም ሰብአዊ መብቶቻቸው ሙሉና ውጤታማ በሆነ ደረጃ እንዲረጋገጡ ለማስቻል አስፈላጊ ቅድመ ሁኔታ ነው፡፡

ሙሉ ጹሑፉን ለማንበብ https://ehrc.org/expertview

#HandsSpeakEyesListen
#እጆች_ይናገራሉ_አይኖች_ያዳምጣሉ

@tikvahethiopia
#ደቡብ_አፍሪካ

• " የመንግሥት ለውጥ በምርጫ እንጂ በግርግር  አይመጣም " - ፕሬዜዳንት ሲሪል ራማፎሳ

• " መንግሥት እየተንቀጠቀጠ ነው ፤ ፈርቷል " - የራማፎሳ ተቃዋሚ ጁሊየስ ማሌማ (የኤኮኖሚ ነጻ አውጪዎች ፓርቲ)

• በተቃውሞው ሳቢያ የንግድ መደብሮች ገና ካሁኑ ሥጋት አድሮባቸዋል።

#በመጪው_ሳምንት በደቡብ አፍሪካ የተቃውሞ ሰልፍ ይካሄዳል ተብሎ ታቅዷል።

በዚህም ሳቢያ የአገሪቱ መንግሥት ቁልፍ የሚባሉ መሠረተ-ልማቶችን ለመጠበቅ እና የጸጥታ ጥበቃውን ለማጠናከር የሀገሪቱን ጦር (ወታደሮች) እንዳሰማራ ዶቼ ቨለ የፈረንሳይ ዜና አገልግሎትን ዋቢ በማድረግ ዘግቧል።

ጁሊየስ ማሌማ የሚመሩት ግራ ዘመም የኤኮኖሚ ነጻ አውጪዎች ፓርቲ በመጪው ሰኞ በመላ ደቡብ አፍሪካ የሥራ ማቆም አድማ መጥራቱ ተነግሯል።

ፓርቲው ፕሬዝደንት ሲሪል ራማፖሳ የደቡብ አፍሪቃን ኤኮኖሚ በመሩበት ስልት፣ በመብራት እጥረት እና እየበረታ በሚሔደው የሥራ አጥነት ሳቢያ ከሥልጣን መልቀቅ አለባቸው የሚል አቋም አለው።

የደ/አፍሪቃ ጦር ለአገሪቱ ፖሊስ እገዛ እንዲያደርግ መታዘዙን አስታውቋል።

ጦሩ በእጁ በሚገኙ የስለላ መረጃዎች መሠረት ሥጋት አለባቸው የተባሉ ቁልፍ ቦታዎችን ለመጠበቅ ከትላንት አርብ ጀምሮ ለአንድ ወር ወታደሮች አሰማርቷል።

ከዚህ በተጨማሪ ከጸጥታ አስከባሪ ተቋማት አቅም በላይ ለሚፈጠሩ ኩነቶች ወታደሮች ምላሽ ይሰጣሉ ተብሏል።

የደቡብ አፍሪቃ ፕሬዝደንታዊ ምርጫ አንድ ዓመት የቀረው ሲሆን ፕሬዜዳንት ራማፎሳ የታቀደው ሰልፍ " ፖለቲካዊ ሴራ ነው "  የሚል አቋም አላቸው።

ፕሬዜዳንቱ ባለፈው ሐሙስ " ሥርዓተ-አልበኝነት እና ግርግር እንደማይፈቀድ " ሲሉ አስጠንቅቀዋል።

ራማፎሳ የመንግሥት ለውጥ " በምርጫ እንጂ በግርግር " እንደማይመጣም ገልጸዋል።

የኤኮኖሚ ነጻ አውጪዎች ፓርቲ መሪ ጁሊየስ ማሌማ ትላንት በስዌቶ ለደጋፊዎቻቸው " ማንም አብዮትን ሊያስቆም አይችልም " ሲሉ ተናግረዋል።

" መንግሥት እየተንቀጠቀጠ ነው፤ ፈርቷል " ያሉት ማሌማ ራማፎሳ ከሥልጣን እንዲወርዱ ጠይቀዋል።

በተቃውሞው ሳቢያ የንግድ መደብሮች ገና ካሁኑ ሥጋት እንደገባቸው የፈረንሳይ ዜና አገልግሎትን ዋቢ በማድረግ ዶቼ ቨለ ዘግቧል።

ፎቶ ፦ ፋይል

@tikvahethiopia