TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.3K photos
1.51K videos
212 files
4.11K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#ሶማሊያ #ኢትዮጵያ #ኤርትራ

የሶማሊያው ፕሬዝደንት ሐሰን ሼይክ መሐሙድ " የሶማልያ እና የኢትዮጵያን የሁለትዮሽ ግንኙነት እና ስልታዊ አጋርነት ለማጠናከር ቁርጠኛ ነኝ " ሲሉ አሳውቀዋል።

ፕሬዝደንቱ ይህን የገለጹት ዛሬ በሶማሊያ የኢትዮጵያ አምባሳደር ሙክታር ሞሐመድ ዋሬ የሹመት ደብዳቤ በተቀበሉበት ወቅት እንደሆነ የሶማሊያ ብሔራዊ ቴሌቪዥን ጣቢያ ዘግቧል።

ፕሬዝደንት ሐሰን ሼይክ መሐሙድ ዛሬ የአምባሳደሩን የሹመት ደብዳቤ የተቀበሉት ለሥራ ጉብኝት ከተጓዙበት አስመራ ወደ ሞቃዲሾ ከተመለሱ በኃላ ነው።

ፕሬዝደንቱ በአስመራ ከኤርትራው አቻቸው ፕሬዜዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ተገናኝተው መወያየታቸው ታውቋል።

ውይይቱ " የጋራ ጠቀሜታ ባላቸው የቀጠናዊ ጉዳዮች " ላይ እንደነበረ የኤርትራ ማስታወቂያ ሚኒስትር የማነ ገብረመስቀል መናገራቸውን ዶቼ ቨለ ዘግቧል።

የሶማሊያው ፕሬዜዳንት ወደ ስልጣን ከመጡ በኃላ ለስራ ጉብኝት ወደ ኤርትራ በተደጋጋሚ ጊዜ መጓዛቸው ይታወቃል።

@tikvahethiopia
ብሊንከን ወደ #ኢትዮጵያ እየመጡ ነው።

የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን ወደ ኢትዮጵያ እየመጡ ይገኛሉ።

ሚኒስትሩ ነገ በአዲስ አበባ ጉብኝት የሚያደርጉ ሲሆን በዚህ ጉብኝታቸው ወቅት ከኢትዮጵያ ባለሥልጣናት ጋር የሰሜን ኢትዮጵያ ግጭትን ለማስቆም የተደረሰው ስምምነት አተገባበር እና የሽግግር ፍትሕ ጉዳይ ላይ ውይይት ያደርጋሉ ተብሏል።

ባለፈው ሳምንት መጨረሻ ላይ የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት የአፍሪካ ጉዳዮች ረዳት ኃላፊ ሞሊ ፊ ብሊንከን አዲስ አበባ ላይ የትግራይ ክልል ባለሥልጣናትን አግኝተው እንደሚነጋገሩ ተናግረዋል።

ብሊንከን የኢትዮጵያ ጉብኝታቸውን እንደጨረሱ ወደ ኒጀር ያቀናሉ።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ህዝቡ የመረጠውን ህጋዊ መንግስት በመጣል ስልጣንን በኃይል ለመቆጣጠር የማለም ተግዳሮቶች ገጥመዋል " - ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ህዝቡ የመረጠውን ህጋዊ መንግስት በመጣል ስልጣንን በኃይል ለመቆጣጠር በማለም ፤ ከተማዋንም ወደ አለመረጋጋት የማስገባት ተግዳሮቶች ገጥመዋል ሲሉ ገለፁ። ከንቲባዋ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ ይህንን…
#Update

ዛሬ የአዲስ አበባ ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ ያቀረቡትን የ6 ወራት የስራ አፈጻጸም ሪፖርት ተከትሎ፤ ከም/ቤት አባላት ጥያቄዎች ቀርበው ነበር።

የም/ቤት አባል ዶ/ር ሲሳይ መንግስቴ " ከአንዳንድ ክልሎች በከፍተኛ መጠን ወደ ከተማዋ ይገባሉ " የተባሉ " ፍልሰተኞችን " በተመለከተ "ከአንዳንድ ክልሎች " የሚለው አገላለጽ ምን ማለት ነው? ክልሎቹ ቢገለጹ " ሲሉ ጠይቀዋል።

" ከአንዳንድ ክልሎች የሚመጡ ሰዎች እንደዚሁ ሁከት እና ብጥብጥ ለመፍጠር አስበው ወይም ህጋዊውን መንግስት ለመገልበጥ አሲረው " በሚል የተቀመጠው ሃሳብ ያልተብራራ መሆኑንም አንስተዋል። 

• የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ጌቱ አርጋው ተከያዮቹን ነጥቦች አንስተዋል ፦

- የአደባባይ በዓላትን እንደ መልካም አጋጣሚ በመጠቀም ረብሻ እና ሁከት ለመፍጠር የሚንቀሳቀሱ ኃይሎች አሉ።

- በአደባባይ በዓላት ላይ ለመፍጠር የሚፈለገው ችግር በተቀናጀ መንገድ የሚመራ ነው፤ ለዚሁ ሲባል ከክልሎች ወደ አዲስ አበባ የሚገቡ ኃይሎች አሉ።

- ፍልሰቱ የተለመደ ነው ከሁሉም አካባቢ ሰው ይመጣል። ነገር ግን  በዓላት ሲቃረቡ የተለያየ ተልዕኮም ተሰጥቷቸው የሚመጡ አሉ። ባሳለፍነው 2 እና 3 ዓመታት የምናውቃቸው ተጨባጭ የሆኑ መረጃዎች አሉ፤ ይህ ጉዳይ በዚህ ዓመት ብቻ የታየ አይደለም።

- ሰዎች በብዛት ወደ አዲስ አበባ የሚገቡት 64 ፐርሰንት የሚሆኑ ከአማራ ክልል አካባቢ ነው፤ 21 ፐርሰንት የሚሆኑት ከደቡብ አካባቢ ነው። 14 ፐርሰንት ከኦሮሚያ ነው።

• የአዲስ አበባ ከተማ ሰላም እና ጸጥታ አስተዳደር ቢሮ ኃላፊ ሊዲያ ግርማ ተከታዮቹ ነጥቦች አንስተዋል ፦

- በርከት ያሉ ኃይሎች ሰላም እና ጸጥታ ለማደፍረስ ወደ ከተማ ይገባሉ የመጀመሪያውን ስፍራውን የሚይዙት ከአማራ ክልል የሚገቡ ኃይሎች ናቸው፤ ከደቡብ እና ከኦሮሚያ አጎራባች ክልሎች አካባቢ ወደ ከተማዋ የሚገቡ ሰዎች በተከታታይ ደረጃ ይቀመጣሉ።

- ችግሩን በተደራጀ መልኩ ይዞ መጥቶ፤ ከተማዋን ለመበጥበጥ የሚፈልግ ኃይል አለ።

- አዲስ አበባ ውስጥ ሃይማኖት፣ ብሔር፣ ፖለቲካ እና መደበኛ ወንጀል መከላከልን ማዕከል ያደረጉ ፤ የጸጥታ መደፍረሶች አሉ። ከእነዚህ የፀጥታ ችግር መነሻዎች ውስጥ ከተማዋን በተደጋጋሚ እየፈተናት ያለው በዓላትን መነሻ ባደረጉ እና የፖለቲካ ፍላጎት ባላቸው ኃይሎች የሚፈጸመው ነው።

• ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ ከሰጡት የማጠቃለያ ሀሳብ ፦

- በዓላትን ተከትሎ ወደ አዲስ አበባ ከተማ የሚደረገውን ፍልሰት በተመለከተ ዳታው ቅድም የተገለፀው (በፖሊስ ኮሚሽን) ነው።

- ወደ ከተማዋ የሚፈልሱት ሰዎች የሚመጡባቸውን አካባቢዎች ላይ በጣም ከፍተኛ፣ አንጻራዊ ያልሆነ መበላለጥ አለ።

- በከተማዋ ውስጥ የሚፈጠሩ ችግሮች በሙሉ ከከተማዋ ውጪ በሚመጡ ሰዎች የተፈጸሙ አይደሉም። ከተማው ውስጥ ባለው ኔትወርክ ነው። የተለያየ ጥቅም እና የፖለቲካ ትርፍን ማግኘት የሚፈልጉ ሰዎች ለዚሁ ቅስቀሳ አድርገዋል።

- የመንግስት ስልጣንን በህጋዊ መንገድ ያላገኙ አካላት፤ በተለያየ መንገድ እነኚህን በተለየ ሁኔታ በመቀስቀስ እና ተልዕኮ በመስጠት ወጣቶችን ወደ ጥፋት በመማገድ ላይ ተሰማርተው ታይተዋል።

- ችግሮች በሚፈጠሩበት ጊዜ የም/ቤት አባላት በምታስተላልፏቸው መልዕክቶች ላይ ጥንቃቄ ልታደርጉ ይገባል። ችግሮች በሚፈጸሙበት ሰዓት በተለያዩ ሶሻል ሚዲያዎች በመጻፍ፣ አነቃቂ ንግግር በሚመስል፣ በተለያየ መንገድ፤ እኛ ልንሞገስበት ህዝቡ ግን ዋጋ ሊከፍልበት የሚደረገው ድርጊት መታረም ያለበት። የምታደርጉት የምትናገሩትና የምትፈፅሙት ነገሮች የህዝብን ሰላምና ደህንነትን ያገናዘበ መሆን አለበት።

#EthiopianInsider

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update ዛሬ የአዲስ አበባ ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ ያቀረቡትን የ6 ወራት የስራ አፈጻጸም ሪፖርት ተከትሎ፤ ከም/ቤት አባላት ጥያቄዎች ቀርበው ነበር። የም/ቤት አባል ዶ/ር ሲሳይ መንግስቴ " ከአንዳንድ ክልሎች በከፍተኛ መጠን ወደ ከተማዋ ይገባሉ " የተባሉ " ፍልሰተኞችን " በተመለከተ "ከአንዳንድ ክልሎች " የሚለው አገላለጽ ምን ማለት ነው? ክልሎቹ ቢገለጹ " ሲሉ ጠይቀዋል። " ከአንዳንድ…
#አብን

አብን የፌዴራል መንግስቱ/ገዢው ብልፅግና ፓርቲ የአዲስ አበባ ከንቲባን ከስልጣን እንዲያስነሳ እና ለፍርድ እንዲያቀርብ ጠየቀ።

የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ ፓርቲ ( #አብን ) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ዛሬ ለምክር ቤት ያቀረቡትን ሪፖርት አጥብቆ አውግዟል።

ፓርቲው ከንቲባ አዳነች አበቤ ዛሬ ለአዲስ አበባ ከተማ ም/ ቤት ባቀረቡት ሪፖርት " ከአንዳንድ ክልሎች የሚደረገው ከፍተኛ ፍልሰት መንግስትን በመጣል በኃይል ስልጣን ለመቆጣጠር ያለመ ነው " ሲሉ ሪፖርት ማቅረባቸውን ከተለያዩ ሚዲያ ዘገባዎች እና ከውስጥ ምንጮቻችን አረጋግጠናል ብሏል።

ከንቲባዋ በሪፖርታቸው ይህን ማለታቸው አደገኛ ከፋፋይ እና የዘር ማጥፋት ወንጀል ቅስቀሳ ነው ያለ ሲሆን ይህም አገረ መንግስቱን አደጋ ላይ የሚጥል እና በማናቸውም መመዘኛ ተቀባይነት የሌለው የዓለም አቀፍ ወንጀል ጥሪ ነው ሲል ገልጾታል።

አብን ፤ ዜጎች በነፃነት ተዘዋውረው የመስራት እና የመኖር ሰብዓዊ መብት ያላቸው መሆኑ ኢትዮጵያ በፈረመቻቸው ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት ሥምምነቶች ድንጋጌዎች እና በሥራ ላይ ባለው ሕገ-መንግስት ጭምር የተረጋገጡ ተፈጥሯዊ መብቶች ናቸው ብሏል።

ፓርቲው በመግለጫው ፤ ከንቲባዋ " የኦሮሚያ ሚዲያ ኔትዎርክ " እየተባለ በሚጠራው ጽንፈኛ እና በአንድ ወቅት መንግስት ራሱ " የሽብርተኞች መጠቀሚያ ነው " ብሎ በፈረጀው ሚዲያ በተከታታይ የወጡ ቅስቀሳዎች ቅጥያ የሆነ አደገኛ የወንጀል ቅስቀሳ አድርገዋል ሲል ከሷል።

" ዓለም አቀፍ ከተማን በከንቲባነት እመራለሁ ከሚል የመንግስት ባለስልጣን እንዲህ ዓይነት አደገኛ ቅስቀሳ በሪፖርትነት መሰማቱ እስካሁን ሲፈፀሙ ለነበሩ በሰብዓዊነት ላይ የተፈፀሙ ወንጀሎች እና እየታወጀ ላለው የዘር ማጥፋት ወንጀል ከለላ የሚሆን አደገኛ የወንጀል ድርጊት ጥሪ ነው " ሲል ፓርቲው ገልጿል።

አብን በመግለጫው ፤ " ሁሉም አገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን እና የዓለም አቀፍ ማኅበረሰቡ ይኼንን አደገኛ የዘር ማጥፋት ወንጀል ቅስቀሳ ትኩረት በመስጠት አስቀድሞ ተገቢውን እርምጃ እንዲወስዱ ታሪካዊ ጥሪ እያደረግን፤ በተለይ የዓለም አቀፉ ማኅበረሰቡ ይኼንን ባያደርግ በሩዋንዳ የፈፀመውን ታሪካዊ ስህተት የሚደግመው መሆኑን ማስረገጥ እንሻለን " ብሏል።

በሌላ በኩል ፥ የፌደራል መንግስቱ ሆነ ገዥው የብልጽግና ፓርቲ ይኼንን አደገኛ የዘር ማጥፋት ወንጀል ቅስቀሳ ያደረጉትን ግለሰብ ከስልጣን እንዲያነሳና ለፍርድ እንዲያቀርብ ጥሪ እናቀርባለን ያለ ሲሆን " መሰል ድርጊት በድጋሚ እንዳይፈፀም መንግስታዊ ማረጋገጫ ጭምር እንዲሰጥ ጥሪ እናቀርባለን " ብሏል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ብሊንከን ወደ #ኢትዮጵያ እየመጡ ነው። የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን ወደ ኢትዮጵያ እየመጡ ይገኛሉ። ሚኒስትሩ ነገ በአዲስ አበባ ጉብኝት የሚያደርጉ ሲሆን በዚህ ጉብኝታቸው ወቅት ከኢትዮጵያ ባለሥልጣናት ጋር የሰሜን ኢትዮጵያ ግጭትን ለማስቆም የተደረሰው ስምምነት አተገባበር እና የሽግግር ፍትሕ ጉዳይ ላይ ውይይት ያደርጋሉ ተብሏል። ባለፈው ሳምንት መጨረሻ ላይ የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ መሥሪያ…
#Update

ብሊንከን አዲስ አበባ ደርሰዋል።

የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን ለይፋዊ የስራ ጉብኝት አዲስ አበባ ገብተዋል።

ብሊንከን ቦሌ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ምስጋኑ አርጋ አቀባበል አድርገውላቸዋል።

የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚንስትር በይፋዊ ጉብኝታቸው ከምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን ጋር ውይይት ያደርጋሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ዘግቧል።

@tikvahethiopia
#ኮሜርስፓል

ኮሜርስፓል አዲስና ዘመናዊ የግብይት መድረክ ሲሆን ተንቀሳቃሽ ስልኮን በመጠቀም ማንኛውንም እቃ መግዛትና መሸጥ ያስችላል።

አዲሱን የኮሜርስፓል መተግበርያ አሁኑኑ በማውረድ የሞባይል ካርድ ሸልመንዎ መገበያየት ይጀምሩ !
የሞባይል ካርድ ለማግኘት ይህን መመሪያ ይከተሉ፦
1:- ከፕለይ ስቶር ወይም አፕ ስቶር የኮሜርስፓል መተግበርያ ያውርዱ
2:- ሙሉ ስም፣ ስልክ ቁጥር እና የይለፍ ቃሉን (ፓስዎርድ) ይሙሉ
3:- የኮሜርስፓል መተግበርያ በመግባት User የሚለው ውስጥ Validate Your Number (Validate) በማድረግ የሞባይል ካርድ ስጦታ ይሸለሙ፡፡

ለበለጠ መረጃ 9491 ላይ ይደውሉልን !!

App Store
: https://apps.apple.com/us/app/commercepal/id1669974212

Play Store: https://play.google.com/store/apps/details?id=com.commercepal

Visit our website: Commercepal.com
የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ //t.iss.one/CommercePal_et
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update

የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር እና ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን ከአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን ጋር መወያየታቸውን የኢ.ፌ.ዴ.ሪ. ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አሳውቋል።

ሚኒስቴሩ ይፋ ባደረገው መረጃ ውይይቱን በተመለከተ ዝርዝር ጉዳዮችን ባያብራራም አቶ ደመቀ እና የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ብሊንከን በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ምክክር መደረጉን አመልክቷል።

@tikvahethiopia
የተማሪ ሊዲያ አበራ ጉዳይ ...

በደቡብ ክልል ሀላባ ቁሊቶ ከተማ በሚገኘው የሀለባ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የ10ኛ ክፍል ተማሪዋ #ሊዲያ_አበራ የካቲት 22 ቀን 2015 ዓ/ም ከትምህርት ቤቷ ተወስዳ ከታሰረች በኋላ ጉዳዩ የማኅበራዊ ሚዲያ መነጋገሪያ ሆኗል።

ሊዲያ ከታሰራች በኋላ ለ5 ቀናት ፍርድ ቤት ሳትቀርብ መቆየቷን እና በእስር ቤት ውስጥ የሰብአዊ መብት ጥሰት እንደተፈጸመባት አባቷ አቶ አበራ ሻሞሮ እንዲሁም ጠበቃዋ አቶ አበባየሁ ጌታ እንዳገለፁለት ቢቢሲ አማርኛው አገልግሎት በድረገፁ አስነብቧል።

በኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን የሕግ እና ፖሊስ ሥራ ክፍል ዳይሬክተር ወ/ሮ ታሪኳ ጌታቸው የ14 ዓመቷ ተማሪን ጉዳይ ኮሚሽኑ እየተከታተለ መሆኑን ገልፀዋል።

የሊዲያ እስር ምክንያት ምንድን ነው ?

በሀላባ ቁሊቶ 30 ዓመታት የኖሩት አቶ አበራ ሻሞሮ፣ ሁለት ሴት ልጆች የሃላባ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት የ10ኛ እና 11ኛ ክፍል ተማሪዎች ናቸው።

ሊዲያ የካቲት 22/2015 ዓ.ም. በመደበኛ ትምህርቷ ላይ ተገኝታ ነበር።

በዚያን ዕለት ሊዲያ በምትማርበት ክፍል ውስጥ አንዲት ተማሪ መውደቋ የነገሮች ሁሉ መነሻ ነው።

👉 ጉዳዩን በተመለከት ሰሜ አይጠቀስ ያሉ የሀላባ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት መምህር የሰጡት ቃል ፦

" ተማሪዋ የወደቀችው ሊዲያ መተት አሰርታባት ነው በሚል በተፈጠረ ግርግር የትምህርት ቤቱ ሥራ በጊዜያዊነት ተስተጓግሎ ነበር።

ከጥቂት ጊዜ በኋላም ፖሊሶች ወደ ትምህርት ቤቱ መጡ።

ያለምንም መጥሪያ...ፖሊሶች መጥተው ከነዩኒፎርሟ፣ ከነደብተሯ እያለቀሰች” ከትምህርት ቤት ወሰዷል።

ይህ በጣም አሳሳቢ እና የሚያሳዝን ነው። "

👉 የትምህርት ቤቱ ርዕሰ መምህር አቶ ወንድሙ መርጋም የሰጡት ቃል ፦

" በዚያን ዕለት ሌላም ተማሪ መውደቋ ለሊዲያ እስር ምክንያት ሆኗል። ሆኖም ታዳጊዋ ላይ ቀደም ብሎ ተማሪዎች እና ወላጆቻቸው አቤቱታ ያቀርቡባት ነበር።

ከእሷ ጋር አብረን ምግብ በልተናል የሚሉ 8 ተማሪዎች ወላጆች ቅሬታ አቅርበዋል፤ ትምህርት ቤቱ እርምጃ ይውሰድ የሚል ጫናም እየበረታ መጥቶ ነበር።

በዚህ ሳቢያ ትምህርት ቤቱ የቅሬታ አቅራቢ ተማሪዎች ወላጆች ጉዳዩን ወደ ፖሊስ ጣቢያ እንዲወስዱ አድርጓል።

በትምህርት ቤት ውስጥ ከእሷ [ሊዲያ] ጋራ ግንኙነት ነበረን፣ ምግብ በልተናል ያሉ 8 ተማሪዎች ወድቀዋል ፤ ይሄ ነገር ከእሷ ጋር ግንኙነት አለው? ወይስ የለውም ? የሚለውን ለማጣራት ነው ክስ ተመስርቶ በዚያው እየታየ ያለው።

በዕለቱ ተማሪዎች ስለተረበሹ እና እርምጃ መውሰድ ስላለብን...ለፖሊስ ልጅቷን በአፋጣኝ ይዛችሁ ብትሄዱ የተሻለ ይሆናል ያልነው። "

ሆኖም ይህ በሊዲያ ላይ የቀረበው ቅሬታ በእህቷ ላይ አልተሰማም ተብሏል።

👉 የሊዲያ ጠበቃ አቶ አበባየሁ ጌታ ፦

" ሊዲያ ወደ ፖሊስ ጣቢያ ከተወሰደች በኋላ ከሕግ ውጪ ለ5 ቀናት ፍርድ ቤት ሳትቀርብ ታስራ ቆይታለች።

ከአምስት (5) ቀናት በኋላ ሃላባ መጀመሪያ ፍርድ ቤት ካለ ጠበቃ ጋር ቀርባ የ14 ቀናት ቀጥሮ ለምርመራ ከተሰጠ በኋላ ወደ ሃላባ ቁሊቶ ማረሚያ ቤት ተወስዳለች።

ይህ ድርጊት ከሕግ ጋር የሚጻረር ነው። ለአካለ መጠን ያልደረሰ ሰው በወንጀል ሲጠረጠር ከቤተሰቦቹ ጋር ቆይቶ ለምርመራ ሲፈልግ እንደሚጠራ በሕግ ተደንግጓል።

በተጠረጠረችበት ወንጀል #ጥፋተኛ ሆና ብትገኝ እንኳን የማረሚያ ቤት እስር እንደማይፈረድባት የወንጀል ሕጉ ያስቀምጣል።

በተሰጠው የጊዜ ቀጠሮ ላይ ለሃላባ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ይግባኝ ተጠይቋል። ይግባኙም የታዳጊዋ አያያዝ እንዲሁም ለቀናት በእስር ላይ እንድትቆይ መደረጉ ተገቢ አይደለም የሚል ነው።

የሊዲያ ከሳሾች ጉዳት ደርሶብናል ያሉት ተማሪዎች ወላጆች ሲሆኑ ልጆቻችንን ላይ ባደረገችባቸው መተት/ድግምት አፍዝዛ ጉዳት አድርሳባቸዋለች የሚል ማመልከቻ አቅርበው ነው የተከሰሰችው።

ክሱ ተሰራ በተባለው መተት / ድግምት ተጎድተው ሕክምና ላይ የሚገኙ ተማሪዎች አሉ ይላል።

ሊዲያም ባለፈው አርብ አግኝተናት አናግረናት ነበር። በወቅቱም ንቅሳት ካለብሽ እናይሻለን በሚል እርቃኗን እንደፈተሿት ተናግራለች።

ሊዲያ እስሩ በተፈጸመባቸው የመጀመሪያዎቹ ቀናት ታለቅስ ነበር። አሁን መምህራን፣ የትምህርት ቤት ጓደኞቿ እና ሌሎች ሰዎች እየጠየቋት በመሆኑ በጥሩ ሞራል ላይ ትገኛለች።

በኢትዮጵያ ሕግ ድግምት ፣ ጥንቆላ፣ እኔ አውቅልሃለሁ ባይነት፣ መንፈስ መጥራት እና መሰል ወንጀሎች የሚዳኙበት ድንጋጌ አለ።

ሆኖም እነዚህ ወንጀሎች ጥቅምን ለማግኘት በማሰብ እና የሌላን ሰው ገንዘብ ለማግኘት የሚፈጸም እንጂ የግል ጥቅም ምን እንደሆነ በማታውቅ ታዳጊ ልጅ፣ ገንዘብ ያለበትን እጠቁማቸኋለሁ ባላለችበት ሁኔታ. . . [ሕጉ] ይህንን ሁኔታ ሊቀበለው አይችለም።

ሰዎችን ለማፍዘዝ የተለያዩ ዱቄት መሰል ምርቶችን ማምረት፣ መሸጥ እና ማሰተላለፍ ወንጀል ነው ሊዲያ ግን ይህንን ሁሉ አላደረገችም።

በማኅበራዊ ሚዲያዎች ለሕይወቷ የሚያሰጉ ዛቻዎች እና ማስፈራሪያዎች እየተዘዋወሩ ነው። በደረሰባት የሥነ ልቦና ጫና ምክንያት ከሥነ ልቦና ጫናው ተላቃ ትምህርቷን ትቀጥላለች ማለት ይከብዳል። "

👉 የሊዲያ አባት አቶ አበራ ሻሞሮ ፦

" ... የልጄ እስር የተወረወረ ዱብ ዕዳ ነው። ልጆቼ በትምህርታቸው ከአጠቃላይ ተማሪ ተሸላሚ ናቸው። እያጠኑ የሚያድሩ ናቸው።

የተቀረውን የትምህርት ጊዜ ሌላ አካባቢ እንዲጨርሱ እየሞከርኩ ነው።

ልጄም በማረሚያ ቤት ባነጋገርኩበት ወቅት መቼ ነው ከዚህ የምወጣው? ብላ ጠይዋኛለች። "

👉 ጉዳዩን በተመለከተ የሀላባ ዞን የቁሊቶ ከተማ አሰተዳደር ሰላም እና ፀጥታ ጽህፈት ቤት ከቀናት በፊት በፌስቡክ ገጹ ይህን ብሏል ፦

" ... በከተማችን በሙሰሊም ሴት ተማሪዎች ላይ ድግምት አሲራለች ተብላ በታሰረች ተማሪ ሊዲያ አበራ በተያያዥ ጉዳይ በአቶ ናስር በሀላባ በዚህም ጉዳይ መሰል ተያያዥነት ያላቸው ግለሰቦችም ጭምር ተይዘው በምርመራ ሂደት በማረሚያ መኖራቸው ይታወቃል።

በታሰሩበት ኬዝ እንዳንድ አክቲቪስቶች ጉዳዩን ወደ ሓይማኖታዊ ለማስመሰል በማጦዝ የሚሞክሩ እንዳላችሁ በማሕበራዊ ሚዲያ እየታየ ያለው ሁኔታ በፖሊስ እና በምርመራ ባለሙያዎች ሂደቱ እየተጣራና ማንም በተጠረጠረበት ወንጀል ታሰሮ አንደሚጣራ የሚታወቅ  ስለሆነ ሁሉም ማህበረሰብ በትዕግስት እንዲጠብቅ ስንል እናሳስባችኋለን።

#ይህንን_ተላልፎ የሚገኝ ማንኛውንም  አካል በህግ የምንጠይቅ መሆኑን እናውቃለን። "

የመረጃ ምንጭ ፦ ቢቢሲ የአማርኛው አገልግሎት / የሀላባ ዞን የቁሊቶ ከተማ አሰተዳደር ሰላም እና ፀጥታ ጽህፈት ቤት ናቸው።

@tikvahethiopia