#ብርሃን_ባንክ
በሆቴሎች፤ በሱፐርማርኬቶች እና በቅርንጫፎቻችን በሚገኙት የፖስ ማሽኖቻችን የቪዛና ማስተር ካርድዎን ተጠቅመው ግብይትዎን ያቅልሉ፡፡
አዳዲስ እና ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት ከታች የሚገኙትን ሊንኮች በመጫን የማህበራዊ ድህረ-ገጾቻችንን ይቀላቀሉ !
Facebook: https://www.facebook.com/berhanbanksc
Telegram: https://t.iss.one/berhanbanksc
Instagram: https://www.instagram.com/berhanbanksc/
Twitter: https://twitter.com/berhanbanksc
LinkedIn: https://www.linkedin.com/company/76151001
YouTube: https://www.youtube.com/channel/UCvOxWe439dzMSvNnMrjcYVQ
እንደ ስማችን ብርሃን ነው ስራችን!
በሆቴሎች፤ በሱፐርማርኬቶች እና በቅርንጫፎቻችን በሚገኙት የፖስ ማሽኖቻችን የቪዛና ማስተር ካርድዎን ተጠቅመው ግብይትዎን ያቅልሉ፡፡
አዳዲስ እና ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት ከታች የሚገኙትን ሊንኮች በመጫን የማህበራዊ ድህረ-ገጾቻችንን ይቀላቀሉ !
Facebook: https://www.facebook.com/berhanbanksc
Telegram: https://t.iss.one/berhanbanksc
Instagram: https://www.instagram.com/berhanbanksc/
Twitter: https://twitter.com/berhanbanksc
LinkedIn: https://www.linkedin.com/company/76151001
YouTube: https://www.youtube.com/channel/UCvOxWe439dzMSvNnMrjcYVQ
እንደ ስማችን ብርሃን ነው ስራችን!
#Mekelle
የኢፌዴሪ የብሄራዊ ተሃድሶ ኮሚሽን የባለድርሻ እና አጋር አካላት የውይይት መድረክ #በመቐለ ለመጀመርያ ጊዜ ይካሄዳል።
ኮሚሽኑ ባወጣው መግለጫ የባለድርሻ እና አጋር አካላት መድረክ ለመጀመርያ ጊዜ የሚካሄድ ሲሆን በመቐለ እንዲደረግ የተወሰነበት ምክንያት ከሰላም ስምምነቱ ብኋላ ክልሉ ላይ አንፃራዊ መረጋጋት መፈጠሩ እና በሁለቱም ተስማሚ ወገኖች የመተማመን ጉዳዩ መጎልበቱን ማሰያ ነው ብሏል።
በመድረኩ ለመሳተፍ የተለያዮ ባለድርሻ እና አጋር አካላት ከፌዴራል መንግስት የተላከ የልኡኳን ቡድን በአምባሳደር ተሾመ ቶጋ መሪነት ዛሬ መቐለ ገብቷል።
የፌደራል መንግስቱ ልኡኳን ብድኑ ከጠቅላይ ሚኒስተር ፅህፈት ቤት፣ የሰላም ሚኒስቴር ፣ የመከላከያ ሰራዊት፣ የሰቪክ ማህበራት፣ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲሁም ከንግድ ሚኒስቴር እና የተለያዮ ክልሎች ተወካዮች ያካተተ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል።
#ድምፂወያነ
@tikvahethiopia
የኢፌዴሪ የብሄራዊ ተሃድሶ ኮሚሽን የባለድርሻ እና አጋር አካላት የውይይት መድረክ #በመቐለ ለመጀመርያ ጊዜ ይካሄዳል።
ኮሚሽኑ ባወጣው መግለጫ የባለድርሻ እና አጋር አካላት መድረክ ለመጀመርያ ጊዜ የሚካሄድ ሲሆን በመቐለ እንዲደረግ የተወሰነበት ምክንያት ከሰላም ስምምነቱ ብኋላ ክልሉ ላይ አንፃራዊ መረጋጋት መፈጠሩ እና በሁለቱም ተስማሚ ወገኖች የመተማመን ጉዳዩ መጎልበቱን ማሰያ ነው ብሏል።
በመድረኩ ለመሳተፍ የተለያዮ ባለድርሻ እና አጋር አካላት ከፌዴራል መንግስት የተላከ የልኡኳን ቡድን በአምባሳደር ተሾመ ቶጋ መሪነት ዛሬ መቐለ ገብቷል።
የፌደራል መንግስቱ ልኡኳን ብድኑ ከጠቅላይ ሚኒስተር ፅህፈት ቤት፣ የሰላም ሚኒስቴር ፣ የመከላከያ ሰራዊት፣ የሰቪክ ማህበራት፣ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲሁም ከንግድ ሚኒስቴር እና የተለያዮ ክልሎች ተወካዮች ያካተተ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል።
#ድምፂወያነ
@tikvahethiopia
#EOTC
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ፤ የ " ቤተክርስቲያን ችግሮች እና ዘለቄታዊ መፍትሔ ጥናትና ትግበራ ኮሚቴ " በሚል ስያሜ እንደተቋቋመ የገለፀችውና ከሁሉም የሞያ ዘርፎች የተውጣጡ የቤተክርስቲያኗን ልጆች ያቀፈው ቡድን ወደ ትግበራ ሊገባ መሆኑን አስታወቀች።
ኮሚቴው የጥናታዊ ጽሑፍ በማቅረብ አላማውን እና የአሰራር ሂደቱን ያብራራ ሲሆን ሰፊ ውይይት አካሂዷል ተባቧል።
በቅድስት ቤተክርስቲያኗ መዋቅር ውስጥ #ከዶግማ_በስተቀር ከላይ ጀምሮ እስከ ታች ድረስ ያሉ ችግሮችን ለማስተካከል እንደሠራም ተገልጿል።
ውጤቱን በተመለከተ ቤተክርስቲያን የራሷ #መንፈሳዊ_ፍርድ_ቤት እንዲኖራት ማድረግን ጨምሮ 25 ዝርዝር ነጥቦች ላይ ማተኮሩ ተመላክቷል።
#ከ90_በላይ አባላትን በጥናት ያሳተፈው ኮሚቴ በ14 ቡድኖች ተዋቅሮ ስራውን #በቅርቡ እንደሚጀምር ቤተክርስቲያኗ አሳውቃለች።
#EOTC_TV
@tikvahethiopia
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ፤ የ " ቤተክርስቲያን ችግሮች እና ዘለቄታዊ መፍትሔ ጥናትና ትግበራ ኮሚቴ " በሚል ስያሜ እንደተቋቋመ የገለፀችውና ከሁሉም የሞያ ዘርፎች የተውጣጡ የቤተክርስቲያኗን ልጆች ያቀፈው ቡድን ወደ ትግበራ ሊገባ መሆኑን አስታወቀች።
ኮሚቴው የጥናታዊ ጽሑፍ በማቅረብ አላማውን እና የአሰራር ሂደቱን ያብራራ ሲሆን ሰፊ ውይይት አካሂዷል ተባቧል።
በቅድስት ቤተክርስቲያኗ መዋቅር ውስጥ #ከዶግማ_በስተቀር ከላይ ጀምሮ እስከ ታች ድረስ ያሉ ችግሮችን ለማስተካከል እንደሠራም ተገልጿል።
ውጤቱን በተመለከተ ቤተክርስቲያን የራሷ #መንፈሳዊ_ፍርድ_ቤት እንዲኖራት ማድረግን ጨምሮ 25 ዝርዝር ነጥቦች ላይ ማተኮሩ ተመላክቷል።
#ከ90_በላይ አባላትን በጥናት ያሳተፈው ኮሚቴ በ14 ቡድኖች ተዋቅሮ ስራውን #በቅርቡ እንደሚጀምር ቤተክርስቲያኗ አሳውቃለች።
#EOTC_TV
@tikvahethiopia
#AddisAbaba
" የቤት ኪራይ ዋጋ አከራዮች እስክ ሰኔ #እንዳይጨምሩ ተወስኗል "
የአዲስ አበባ አስተዳደር ካቢኔ 2ኛ አመት 11ኛ መደበኛ ስብሰባውን አካሂዶ የተለያዩ ውሳኔዎችን አሳልፏል።
ካቢኔው ያሳለፋቸው ውሳኔዎች ፦
1. የመኖሪያ ቤቶችን በመንግስትና የግል አጋርነት በ70/30 አሰራር መቶ ሺህ የሚደርሱ ቤቶችን ለመገንባት የተዘጋጀውን 35 ሄክታር መሬት ላይ ተወያይቶ ወስኗል።
2. ሃገራዊ ፋይዳ ያላቸው የተለያዩ ፕሮጀክቶች እና የስራ እድል የሚፈጥሩ የ373 ፕሮጀክቶች የመሬት ጥያቄ እነሱም ፦
2.1. ለኢንዱስትሪ ልማት
2.2 ሆቴሎችና ሞሎች ፣
2.3 የሀይማኖት ተቋማት ፣
2.4 ቀደም ሲል በካቢኔ ተወስነው የመሬት ለውጥ የቀረበባቸው ቦታዎች ፣ ለተለያዩ የግንባታ ግባዓት ማስቀመጫ የሚሆኑ ጊዜያዊ መጠቀሚያ ቦታዎች ናቸው።
3. ወቅታዊ የኑሮ ውድነትና የገበያ መረጋጋት የዋጋ መናር መነሻ በማድረግ በአስቸኳይ ምርት ወደ ከተማ እንዲገባና እንዲሰራጭ ግብረ ኃይል አቋቁሟል።
4. ለተማሪዎች ምገባ የሚያቀርቡ እናቶች በአሁኑ ዋጋ ማቅረብ መቸገራቸውን መነሻ በማድረግ ለተማሪዎች ምገባ በወር 54,000,000 ብር (ሀምሳ አራት ሚሊየን) በዓመት 540,000,000 ብር (አምስት መቶ አርባ ሚሊየን) ተጨማሪ በጀት አጽድቋል፤ ይህ ማለት ለአንድ ተማሪ በቀን ሃያ ብር የነበረው ወደ የሀያ ሶስት ብር ከፍ እንዲል ተደርጓል።
5. ከወቅቱ ዋጋ መናር እና የገበያ አለመረጋጋት ጋራ ተያይዞ የነበረው የቤት ኪራይ ዋጋ አከራዮች እስክ ሰኔ እንዳይጨምሩ ተውስኗል።
(የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር)
@tikvahwthiopia
" የቤት ኪራይ ዋጋ አከራዮች እስክ ሰኔ #እንዳይጨምሩ ተወስኗል "
የአዲስ አበባ አስተዳደር ካቢኔ 2ኛ አመት 11ኛ መደበኛ ስብሰባውን አካሂዶ የተለያዩ ውሳኔዎችን አሳልፏል።
ካቢኔው ያሳለፋቸው ውሳኔዎች ፦
1. የመኖሪያ ቤቶችን በመንግስትና የግል አጋርነት በ70/30 አሰራር መቶ ሺህ የሚደርሱ ቤቶችን ለመገንባት የተዘጋጀውን 35 ሄክታር መሬት ላይ ተወያይቶ ወስኗል።
2. ሃገራዊ ፋይዳ ያላቸው የተለያዩ ፕሮጀክቶች እና የስራ እድል የሚፈጥሩ የ373 ፕሮጀክቶች የመሬት ጥያቄ እነሱም ፦
2.1. ለኢንዱስትሪ ልማት
2.2 ሆቴሎችና ሞሎች ፣
2.3 የሀይማኖት ተቋማት ፣
2.4 ቀደም ሲል በካቢኔ ተወስነው የመሬት ለውጥ የቀረበባቸው ቦታዎች ፣ ለተለያዩ የግንባታ ግባዓት ማስቀመጫ የሚሆኑ ጊዜያዊ መጠቀሚያ ቦታዎች ናቸው።
3. ወቅታዊ የኑሮ ውድነትና የገበያ መረጋጋት የዋጋ መናር መነሻ በማድረግ በአስቸኳይ ምርት ወደ ከተማ እንዲገባና እንዲሰራጭ ግብረ ኃይል አቋቁሟል።
4. ለተማሪዎች ምገባ የሚያቀርቡ እናቶች በአሁኑ ዋጋ ማቅረብ መቸገራቸውን መነሻ በማድረግ ለተማሪዎች ምገባ በወር 54,000,000 ብር (ሀምሳ አራት ሚሊየን) በዓመት 540,000,000 ብር (አምስት መቶ አርባ ሚሊየን) ተጨማሪ በጀት አጽድቋል፤ ይህ ማለት ለአንድ ተማሪ በቀን ሃያ ብር የነበረው ወደ የሀያ ሶስት ብር ከፍ እንዲል ተደርጓል።
5. ከወቅቱ ዋጋ መናር እና የገበያ አለመረጋጋት ጋራ ተያይዞ የነበረው የቤት ኪራይ ዋጋ አከራዮች እስክ ሰኔ እንዳይጨምሩ ተውስኗል።
(የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር)
@tikvahwthiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#አስተያየቶች
ከትላንት በስቲያ የሦስት እግር ተሽከርካሪ (ባጃጅ) በአዲስ አበባ ከተማ መከልከሉን ተከትሎ የተለየዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ሀሳባቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አጋርተዋል። የቀረቡ ሀሳቦችን አንደሚከተለው አቅርበናል።
🧑💻 የባጃጅ ትራንስፖርት በመታገዱ ስለደረሱ መጉላላቶች የተሰጡ አስተያየቶች፦
- " ከለቡ ጀሞ በጣም ተቸግረናል አካባቢያችን በብዛት የነበረው ትራንስፓርት ባጃጅ ነበር ለተማሪ ሰርቪስ ብዙዎቹ ይሰሩ ነበር፤ ልጆቻችንን ት/ት ቤት የሚያደርስልን አጥተናል፣ ዕቃ ገዝተን ኮንትራት የምንይዘው(ከአትክልት ተራም ይሁን ሌላ) በባጃጅ ነበር እና አሁን ሚኒ ባስ ኮንትራት ልንይዝ ነው ? "
😓 ውሳኔው የባጃጅ አሽከርካሪዎችን ሰርቶ የመኖር መብት ስለመጋፉቱ የተሰጡ አስተያየቶች፦
" በባጃጅ ሥራ የሚተዳደር ስንት ሰው አለ! ቢያንስ እንኳ ማስጠንቀቂያ መሰጠት ነበረበት በጣም ነው የሚያሳፍረው እንደዚህ አይደረግም። "
" ብዙ ሰው በዚህ ሥራ ቤተሰብ እንደሚያስተዳድርና ኑሮውን እንደሚገፋ መንግስት ጠፍቶት ነው?! ሥራቸውንስ እየሰሩ ህግ ማስተካከል አይቻልም ነበር? ምን አይነት አሰራር ነው? "
👨💻 የውሳኔ አሰጣጡ ላይ የተሰጡ አስተያየቶች፦
" ችግር ካለ ሳያግዱ ችግሩን መቅረፍ ይቻላል። ማገዱ ከባጃጅ ባለንብረቶች እና አሽከርካሪዎች በተጨማሪ ተጠቃሚውንም ለእንግልት ይዳርጋል። በዚህ ላይ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ሀገራችን ላይ ታግደው የተረሱ ብዙ ነገሮች አሉ ! "
- " የጅምላ ውሳኔ ይቁም። የመንግስት ኀላፊዎች እና የህግ አስከባሪዎች ደሞዝ የሚከፈላቹ ከሕብረተሰቡ በሚሰበሰብ ግብር መሆኑን አትርሱ ስራችሁን ስሩ ያጠፋውን ለዩ የሚቀጣዉንም ቅጡ። ትራንስፖርት ዘርፍ ላይ የሚሰሩ ማኅበራት እና አሽከርካሪዎችን በተመደበላቸዉ ቦታ ላይ እና ታሪፍ ብቻ እንዲሰሩ የሚያደርግ አስገዳጅ እና ጠንካራ ህግ አውጡ እንጂ ስራችሁን መስራት ሲያቅታቹ የፈሪ፣ የትዕቢት እና የማንአለብኝነት የጅምላ ውሳኔ አትወስኑ። "
👨💻 ውሳኔውን ተከትሎ ከዚህ ቀደም በአገልግሎቱ ላይ ስለነበሩ ክፍተቶች የተሰጡ አስተያየቶች፦
- " ቤተል-ዓለም ባንክ 0.6Km ለማትሆን መንገድ 10 ብር ያስከፍላሉ ሲመሽ ደግሞ እጥፍ ያደርጉታል፡፡ ግን ደግሞ ባጃጅ ሲታገድ ቦታውን ታክሲዎች ተረክበው በባጃጆች ዋጋ ነው እሚሰሩት፡፡ "
- " በባጃጅ ማኅበሮች ውስጥ አዲስ ባጃጅ መስመር ውስጥ ለመግባት የሚጠየቀው ገንዘብ እጅግ በጣም የተጋነነ ለዚያውም ግለሰቦች ኪስ የሚገባ ገንዘብ ነው "
- " አንዳንድ ባጃጆች ከሚሰጡት አገልግሎት ይልቅ ሌብነትና ዝርፊያ ላይ ተሰማርተዋል። በትንሽ ነዳጅ ብዙ ርቀት የሚሄዱ ሲሆን ለትንሽ ርቀት ከሚኒባስ በላይ ሁለትና ሶስት እጥፍ እያስከፈሉ ያሰቃዩናል። "
@tikvahethiopia
ከትላንት በስቲያ የሦስት እግር ተሽከርካሪ (ባጃጅ) በአዲስ አበባ ከተማ መከልከሉን ተከትሎ የተለየዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ሀሳባቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አጋርተዋል። የቀረቡ ሀሳቦችን አንደሚከተለው አቅርበናል።
- " ከለቡ ጀሞ በጣም ተቸግረናል አካባቢያችን በብዛት የነበረው ትራንስፓርት ባጃጅ ነበር ለተማሪ ሰርቪስ ብዙዎቹ ይሰሩ ነበር፤ ልጆቻችንን ት/ት ቤት የሚያደርስልን አጥተናል፣ ዕቃ ገዝተን ኮንትራት የምንይዘው(ከአትክልት ተራም ይሁን ሌላ) በባጃጅ ነበር እና አሁን ሚኒ ባስ ኮንትራት ልንይዝ ነው ? "
" በባጃጅ ሥራ የሚተዳደር ስንት ሰው አለ! ቢያንስ እንኳ ማስጠንቀቂያ መሰጠት ነበረበት በጣም ነው የሚያሳፍረው እንደዚህ አይደረግም። "
" ብዙ ሰው በዚህ ሥራ ቤተሰብ እንደሚያስተዳድርና ኑሮውን እንደሚገፋ መንግስት ጠፍቶት ነው?! ሥራቸውንስ እየሰሩ ህግ ማስተካከል አይቻልም ነበር? ምን አይነት አሰራር ነው? "
" ችግር ካለ ሳያግዱ ችግሩን መቅረፍ ይቻላል። ማገዱ ከባጃጅ ባለንብረቶች እና አሽከርካሪዎች በተጨማሪ ተጠቃሚውንም ለእንግልት ይዳርጋል። በዚህ ላይ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ሀገራችን ላይ ታግደው የተረሱ ብዙ ነገሮች አሉ ! "
- " የጅምላ ውሳኔ ይቁም። የመንግስት ኀላፊዎች እና የህግ አስከባሪዎች ደሞዝ የሚከፈላቹ ከሕብረተሰቡ በሚሰበሰብ ግብር መሆኑን አትርሱ ስራችሁን ስሩ ያጠፋውን ለዩ የሚቀጣዉንም ቅጡ። ትራንስፖርት ዘርፍ ላይ የሚሰሩ ማኅበራት እና አሽከርካሪዎችን በተመደበላቸዉ ቦታ ላይ እና ታሪፍ ብቻ እንዲሰሩ የሚያደርግ አስገዳጅ እና ጠንካራ ህግ አውጡ እንጂ ስራችሁን መስራት ሲያቅታቹ የፈሪ፣ የትዕቢት እና የማንአለብኝነት የጅምላ ውሳኔ አትወስኑ። "
- " ቤተል-ዓለም ባንክ 0.6Km ለማትሆን መንገድ 10 ብር ያስከፍላሉ ሲመሽ ደግሞ እጥፍ ያደርጉታል፡፡ ግን ደግሞ ባጃጅ ሲታገድ ቦታውን ታክሲዎች ተረክበው በባጃጆች ዋጋ ነው እሚሰሩት፡፡ "
- " በባጃጅ ማኅበሮች ውስጥ አዲስ ባጃጅ መስመር ውስጥ ለመግባት የሚጠየቀው ገንዘብ እጅግ በጣም የተጋነነ ለዚያውም ግለሰቦች ኪስ የሚገባ ገንዘብ ነው "
- " አንዳንድ ባጃጆች ከሚሰጡት አገልግሎት ይልቅ ሌብነትና ዝርፊያ ላይ ተሰማርተዋል። በትንሽ ነዳጅ ብዙ ርቀት የሚሄዱ ሲሆን ለትንሽ ርቀት ከሚኒባስ በላይ ሁለትና ሶስት እጥፍ እያስከፈሉ ያሰቃዩናል። "
@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
TIKVAH-ETHIOPIA
" ባጃጅ ታግዷል " በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከነገ የካቲት 30 ጀምሮ የባጃጅ ትራንስፖርት አገልግሎት ታገደ። ከነገ ጀምሮ በከተማዋ በየትኛውም አካባቢ ላልተወሰነ ጊዜ የባጃጅ አገልግሎት መታገዱን የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ አስታውቋል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትራንስፖርት ቢሮ " የባጃጅ ትራንስፖርት አገልግሎት አሰጣጥን በተሻለ መልክ ለመምራት እንዲያስችል አሰራር ማሻሻያ ስራዎችን…
#ባጃጅ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የባለ ሶስት እግር ተሽከርካሪዎች / ባጃጅ መታገዱን በተመለከተ ዛሬ ባወጣው መግለጫ አጭር ማብራሪያ ሰጥቷል።
በማብራሪያው ፤ " መንግስት የህዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት ሰጪዎችን #የነዳጅ_ድጎማ ተጠቃሚ እንዲሆን ማድረጉ እየታወቀ የባለሶስት ጎማ ወይም በተለምዶ አጠራራቸው የባጃጅ አሽከርካሪዎች ያልተገባ የዋጋ ጭማሪ በማድረግ እንዲሁም የተወሰኑት በወንጀል ድርጊቶች ላይ በመሰማራት የከተማችን ነዋሪ የቅሬታ ምንጭ ሆነዋል " ብሏል።
የከተማ አስተዳደሩ የባጃጅ አገልግሎትን ስርዓት ለማስያዝ የአሰራር ማስተካከያ እያደረገ መሆኑን ገልጾ ይህ ተግባራዊ እስከሚሆን ድረስ በከተማድ ሁሉም አካባቢዎች የባጃጅ ትራንስፖርት አገልግሎት #እንዲቆም መወሰኑን ገልጿል።
የተሸርካሪዎቹ ከስራ መውጣት በነዋሪው ላይ የትራንስፖርት ጫና እንዳያሳድር አስተዳደሩ ሌሎቹ የትራንስፖርት አገልግሎቶች በሙሉ አቅማቸውና በቅንጅት አገልግሎት የሚሰጡበትን ሁኔታ መመቻቸቱን አመላክቷል።
(የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሌሎች ጉዳዮችንም ያነሳበት የዛሬ መጋቢት 1 ቀን 2015 ዓ.ም መግለጫ ከላይ ተያይዟል)
@tikvahethiopia
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የባለ ሶስት እግር ተሽከርካሪዎች / ባጃጅ መታገዱን በተመለከተ ዛሬ ባወጣው መግለጫ አጭር ማብራሪያ ሰጥቷል።
በማብራሪያው ፤ " መንግስት የህዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት ሰጪዎችን #የነዳጅ_ድጎማ ተጠቃሚ እንዲሆን ማድረጉ እየታወቀ የባለሶስት ጎማ ወይም በተለምዶ አጠራራቸው የባጃጅ አሽከርካሪዎች ያልተገባ የዋጋ ጭማሪ በማድረግ እንዲሁም የተወሰኑት በወንጀል ድርጊቶች ላይ በመሰማራት የከተማችን ነዋሪ የቅሬታ ምንጭ ሆነዋል " ብሏል።
የከተማ አስተዳደሩ የባጃጅ አገልግሎትን ስርዓት ለማስያዝ የአሰራር ማስተካከያ እያደረገ መሆኑን ገልጾ ይህ ተግባራዊ እስከሚሆን ድረስ በከተማድ ሁሉም አካባቢዎች የባጃጅ ትራንስፖርት አገልግሎት #እንዲቆም መወሰኑን ገልጿል።
የተሸርካሪዎቹ ከስራ መውጣት በነዋሪው ላይ የትራንስፖርት ጫና እንዳያሳድር አስተዳደሩ ሌሎቹ የትራንስፖርት አገልግሎቶች በሙሉ አቅማቸውና በቅንጅት አገልግሎት የሚሰጡበትን ሁኔታ መመቻቸቱን አመላክቷል።
(የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሌሎች ጉዳዮችንም ያነሳበት የዛሬ መጋቢት 1 ቀን 2015 ዓ.ም መግለጫ ከላይ ተያይዟል)
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update #UAE በ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ 273 ተማሪዎች የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች መንግስት ሙሉ ስኮላርሺፕ መስጠቱን ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ መናገራቸውን ኤፍ ቢ ሲ ዘግቧል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህን የተናገሩት ዛሬ የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና ወስደው ከግማሽ በላይ ውጤት ካስመዘገቡ ተማሪዎች ውስጥ የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ 273 ተማሪዎች እውቅና በሰጡበት…
" ተማሪዎቹ ወደዉጪ እስኪሄዱ ድረስ የእንግሊዝኛ ቋንቋ ማሻሻያ ትምህርት በመማርና ሌሎች ለወደፊታቸዉ የሚያግዙ ቅድመ-ዝግጅቶችን እያደረጉ ይቆያሉ " - ትምህርት ሚኒስቴር
የካቲት 21 ቀን 2015 ዓ/ም ፤ በ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና የላቀ ውጤት ላመጡ 273 ተማሪዎች በሀገር አቀፍ ደረጃ የኢፌዲሪ ጠ/ሚ ዶ/ር ዐብይ አህመድ የእዉቅናና ሽልማት ማበርከታቸውና በዕለቱ ለተማሪዎቹ በተባበሩት አረብ ኤሜሬትስ የውጭ የትምህርት ዕድል መገኘቱን መግለፃቸው ይታወሳል።
ከዚህ የትምህርት እድል ጋር በተያያዘ ትምህርት ሚኒስቴር ዛሬ ማብራሪያ ሰጥቷል።
የትምህርት እድሉ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ባደረጉት ጥረት የተገኘ መሆኑን የገለፀው ሚኒስቴሩ ተማሪዎቹ ከመስከረም/2016 ዓ/ም ጀምሮ እንዲማሩ መመቻቸቱን ገልጿል።
ተማሪዎቹ ወደዉጪ እስኪሄዱ ድረስ ያሉትን ግዜያት #የእንግሊዝኛ_ቋንቋ ማሻሻያ ትምህርት በመማርና ሌሎች ለወደፊታቸዉ የሚያግዙ ቅድመ-ዝግጅቶችን እያደረጉ እንዲቆዩ የሚሰራ መሆኑን ገልጿል።
የተፈጠረዉ የትምህርት ዕድል ለተማሪዎቹም እንዲሁም እንደ አጠቃላይ ለሀገር በጣም ጥሩ እድል መሆኑን የገለፀው ሚኒስቴሩ ነገር ግን ዕድሉ ለተፈጠረላቸዉ ተማሪዎች #እንደግዴታ የሚወሰድ አይደለም ሲል አሳውቋል።
ተማሪዎቹ መማር የምፈልገዉ በሀገር ዉስጥ ባሉ ዩኒቨርስቲዎች ነዉ ብለዉ ካሰቡ የሚገደዱበት ሁኔታ እንደሌለ ሚኒስቴሩ ገልጿል።
በተባበሩት ኤሜሬትስ በየትኞቹ ዩኒቨርስቲዎች ሊማሩ ይችላሉ ?
- የተባበሩት አርብ ኤምሬትስ ዩኒቨርስቲ ፦ በዓለም አቀፍ ደረጃ 284ኛ ላይ ሲገኝ በአረብ ወሰጥ ካሉ ዩኒቨርስቲዎች ዉሰጥ ደግሞ 5ኛ ደረጃ ላይ ይገኛል። መቀመጫውንም አል አይን በተባለችው የአቡ ዳቢ ከተማ ሲሆን ካሉት ዩኒቨርስቲዎችም በእድሜ ትንሹ ነው።
- አሜሪካን ዩኒቨርስቲ ኦፍ ሻርጃ ፦ በተባበሩት አረብ ኤምሬትስ ዉስጥ ካሉ ዩኒቨርስቲዎች በሰባተኛነት የተቀመጠ ሲሆን የሚሰጣቸው የትምህርት አይነቶችም በአሜሪካ የከፍተኛ ትምህርት ሞዴል መሰረት ነው። በዓለም አቀፍ ተማሪዎችም ተመራጭ የሆነ ዩኒቨርስቲ ነው።
- ካሊፋ ዩኒቨርስቲ ፦ በአለም አቀፍ ደረጃ 211ኛ ላይ ሲገኝ በ2021 በተሰጠው የዩኒቨርስቲዎች ደረጃ ደግሞ በአረብ ዉሰጥ ካሉ ዩኒቨርስቲዎች ውሰጥ በዘጠነኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል። ለትርፍ ያልተቋቋመ ትኩረቱን ሳይንስ ላይ አደረጎ በ2007 የተመሰረተ ዩኒቨርሰቲ ነው። ዩኒቨርሰቲው በአሜሪካ የከፍተኛ ትምህርት ሞዴል የተቃኘም ጭምር ነው። በውሰጡ ሶሰት ኮሌጆች፣ ሶሰት የምርምር ኢኒስቲቲዩቶች፣ 18 የምርምር ማእከላት እና 36 ዲፓርትመንቶችን በተለያዩ የትምህርት መሰኮች ይዟል።
- ዪኒቨርስቲ ኦፍ ሻርጃ ፦ በ1997 የተቋቋመ ሲሆን በመካከለኛው እሩቅ ምሰራቅ እና በዓለም አቀፍ ደረጃ ቀዳሚ የትምህርት ተቋም ለመሆን አልሞ እየሰራ ያለ ዩኒቨርሰቲ ነው።
- ዛይድ ዩኒቨርስቲ ፦ በ1998 የተመሰረተና በተባበሩት አረብ ኤሜሬትስ ስመ ጥር የሆነ ዩኒቨርሲቲ ነው።
https://www.topuniversities.com
#ትምህርት_ሚኒስቴር
@tikvahethiopia
የካቲት 21 ቀን 2015 ዓ/ም ፤ በ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና የላቀ ውጤት ላመጡ 273 ተማሪዎች በሀገር አቀፍ ደረጃ የኢፌዲሪ ጠ/ሚ ዶ/ር ዐብይ አህመድ የእዉቅናና ሽልማት ማበርከታቸውና በዕለቱ ለተማሪዎቹ በተባበሩት አረብ ኤሜሬትስ የውጭ የትምህርት ዕድል መገኘቱን መግለፃቸው ይታወሳል።
ከዚህ የትምህርት እድል ጋር በተያያዘ ትምህርት ሚኒስቴር ዛሬ ማብራሪያ ሰጥቷል።
የትምህርት እድሉ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ባደረጉት ጥረት የተገኘ መሆኑን የገለፀው ሚኒስቴሩ ተማሪዎቹ ከመስከረም/2016 ዓ/ም ጀምሮ እንዲማሩ መመቻቸቱን ገልጿል።
ተማሪዎቹ ወደዉጪ እስኪሄዱ ድረስ ያሉትን ግዜያት #የእንግሊዝኛ_ቋንቋ ማሻሻያ ትምህርት በመማርና ሌሎች ለወደፊታቸዉ የሚያግዙ ቅድመ-ዝግጅቶችን እያደረጉ እንዲቆዩ የሚሰራ መሆኑን ገልጿል።
የተፈጠረዉ የትምህርት ዕድል ለተማሪዎቹም እንዲሁም እንደ አጠቃላይ ለሀገር በጣም ጥሩ እድል መሆኑን የገለፀው ሚኒስቴሩ ነገር ግን ዕድሉ ለተፈጠረላቸዉ ተማሪዎች #እንደግዴታ የሚወሰድ አይደለም ሲል አሳውቋል።
ተማሪዎቹ መማር የምፈልገዉ በሀገር ዉስጥ ባሉ ዩኒቨርስቲዎች ነዉ ብለዉ ካሰቡ የሚገደዱበት ሁኔታ እንደሌለ ሚኒስቴሩ ገልጿል።
በተባበሩት ኤሜሬትስ በየትኞቹ ዩኒቨርስቲዎች ሊማሩ ይችላሉ ?
- የተባበሩት አርብ ኤምሬትስ ዩኒቨርስቲ ፦ በዓለም አቀፍ ደረጃ 284ኛ ላይ ሲገኝ በአረብ ወሰጥ ካሉ ዩኒቨርስቲዎች ዉሰጥ ደግሞ 5ኛ ደረጃ ላይ ይገኛል። መቀመጫውንም አል አይን በተባለችው የአቡ ዳቢ ከተማ ሲሆን ካሉት ዩኒቨርስቲዎችም በእድሜ ትንሹ ነው።
- አሜሪካን ዩኒቨርስቲ ኦፍ ሻርጃ ፦ በተባበሩት አረብ ኤምሬትስ ዉስጥ ካሉ ዩኒቨርስቲዎች በሰባተኛነት የተቀመጠ ሲሆን የሚሰጣቸው የትምህርት አይነቶችም በአሜሪካ የከፍተኛ ትምህርት ሞዴል መሰረት ነው። በዓለም አቀፍ ተማሪዎችም ተመራጭ የሆነ ዩኒቨርስቲ ነው።
- ካሊፋ ዩኒቨርስቲ ፦ በአለም አቀፍ ደረጃ 211ኛ ላይ ሲገኝ በ2021 በተሰጠው የዩኒቨርስቲዎች ደረጃ ደግሞ በአረብ ዉሰጥ ካሉ ዩኒቨርስቲዎች ውሰጥ በዘጠነኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል። ለትርፍ ያልተቋቋመ ትኩረቱን ሳይንስ ላይ አደረጎ በ2007 የተመሰረተ ዩኒቨርሰቲ ነው። ዩኒቨርሰቲው በአሜሪካ የከፍተኛ ትምህርት ሞዴል የተቃኘም ጭምር ነው። በውሰጡ ሶሰት ኮሌጆች፣ ሶሰት የምርምር ኢኒስቲቲዩቶች፣ 18 የምርምር ማእከላት እና 36 ዲፓርትመንቶችን በተለያዩ የትምህርት መሰኮች ይዟል።
- ዪኒቨርስቲ ኦፍ ሻርጃ ፦ በ1997 የተቋቋመ ሲሆን በመካከለኛው እሩቅ ምሰራቅ እና በዓለም አቀፍ ደረጃ ቀዳሚ የትምህርት ተቋም ለመሆን አልሞ እየሰራ ያለ ዩኒቨርሰቲ ነው።
- ዛይድ ዩኒቨርስቲ ፦ በ1998 የተመሰረተና በተባበሩት አረብ ኤሜሬትስ ስመ ጥር የሆነ ዩኒቨርሲቲ ነው።
https://www.topuniversities.com
#ትምህርት_ሚኒስቴር
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#አሁን
የኢፌዴሪ ብሄራዊ የተሃድሶ ኮሚሽን ከባለድርሻ እና አጋር አካላት ጋር የቀድሞ ተዋጊዎችን የመልሶ ማቋቋም ሂደት ላይ ያተኮረ የምክክር መድረክ በመቐለ እያካሄደ ይገኛል።
ፎቶ፦ ትግራይ ቴሌቪዥን / ድምፂ ወያነ
@tikvahethiopia
የኢፌዴሪ ብሄራዊ የተሃድሶ ኮሚሽን ከባለድርሻ እና አጋር አካላት ጋር የቀድሞ ተዋጊዎችን የመልሶ ማቋቋም ሂደት ላይ ያተኮረ የምክክር መድረክ በመቐለ እያካሄደ ይገኛል።
ፎቶ፦ ትግራይ ቴሌቪዥን / ድምፂ ወያነ
@tikvahethiopia