TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.3K photos
1.5K videos
211 files
4.1K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
19ኛው አለም አቀፍ የክር(የጨርቃጨርቅ) ኤክስፖ !

ከየካቲት15 እስከ 20 በቱርክ ሀገር ኢስታንቡል ከተማ ይካሄዳል ። ከፍተኛ ጥራት ያለው የክር እና ጨርቃጨርቅ አምራች ኢንደስትሪዎችን እንዲሁም ታላቁን የቱርክ የክር ኢንደስትሪ ይጎበኛሉ።

እንዲሁም ለድርጅትዎ አዳዲስ ፈጠራዎችን እና ግንዛቤዎችን ለማየት፤ ተወዳዳሪነቶን ለማሳደግ፤ የንግድ ግንኙነት የሚፈጥሩበት እና ልምድ የሚቀስሙበት ታላቅ ኤግዚብሽን ላይ እንዲሳተፉ ኢስታንቡል አዲስ አስጎብኚ እና የጉዞ ወኪል ቅድመ ዝግጅቱን ጨርሶ እየጋበዞት ይገኛል።

አድራሻ ቦሌ ዲ ኤች ገዳ ህንፃ 2ተኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 205 ስልክ ቁጥር 0983568383፣ ወይም 0944000006 ላይ ይደውሉ
TIKVAH-ETHIOPIA
ሸዋሮቢት ውስጥ የሰውም ሆነ የባጃጅ እንቅስቃሴ ላይ ገደብ ተጥሏል። የከተማው አስተዳደር ፤ ለከተማው ሰላምና ጸጥታ ሲባል ማንኛውም የባጃጅና የሰው እንቅስቃሴ ከምሽቱ 12 ስዓት ጀምሮ የተከለከለ ነው ሲል አሳውቋል። ለተላለፈው ትዕዛዝ ሁሉም ትብብር እንዲያደርግ ከተማ አስተዳደሩ ጥሪ አቅርቧል። ከሰሞኑን በዚሁ ቀጠና ዳግም ግጭት ተቀስቅሶ በርካቶች የደህንነት ስጋት ላይ ወድቀዋል። @tikvahethiopia
ፎቶ ፦ የሸዋሮቢት ከተማ አስተዳደር ፤ " ሰሞኑን በሸዋሮቢት እና በጅሌ ጥሙጋ ወረዳ አዋሳኝ አካባቢዎች በተደረገ ጦርነት በርካታ የሰው ህይወት ጠፍቷል፤ ንብረትም ውድሟል " ሲል አሳውቋል።

የንብረት ውድመት የደረሰባቸው የከተማው የ05 ቀበሌ ነዋሪዎች #በመንግስት_ቸልተኝነት እና #የላላ_ህግ የማስከበር ተግባሩ የተነሳ በየአመቱ ለሰው ህይወት መጥፋትና ንብረት ውድመት ምክንያት መሆኑን ገልጸዋል።

ነዋሪዎቹ ፤ ውፍጮ ቤቶችና የንግድ ሱቆች ሙሉ በመሉ መውደማቸውን በመግለጽ መንግስት በዚህ ቀጠና ያለውን ጦርነትና የተደራጀ ቡድን ወይም  ኃይል በማጥራት የመንግስት ኃላፊነቱን ሊወጣ ይገባል ብለዋል።

ከሰሞኑን በደረሰው ጥቃት በርካታ ሰው ህይወት የጠፋ ሲሆን የህዝብ መገልገያ ትምህርት ቤቶች ፣ ወፍጮ ቤቶች ፣ የጤና ክሊኒኮች ፣ ሱቆች ፣ የቀበሌ አስተዳደር ቢሮዎች ፣ የግለሰብ ቤቶች ወድመዋል።

ነዋሪዎች የሚመለከተው የበላይ የመንግስት አካል ልዪ ትኩረት ሰጥቶ ህይወታችንን ሊታደግ ይገባል ሲሉ ጥሪ አቅርበዋል።

Photo Credit : የሸዋሮቢት ከተማ አስተዳደር

@tikvahethiopia
#Singapore

የዓለም አቀፉ የፖሊስ ተቋም ሲንጋፖር ውስጥ በተፈጸመ ውስብስብ የፈተና ማጭበርበር እጇ አለበት የተባለችው ሴት እንድትያዝ ጥሪ ማቅረቡ ተሰማ።

የ57 ዓመቷ ፖህ ዩዋን ኒይ ስልክ እና ኢርፎን በመጠቀም ተማሪዎች የፈተና ውጤት እንዲያጭበረብሩ የሚያደርግ መዋቅር ዘርግታ እንደነበር ተገልጿል።

የእሷ ሦስት ተባባሪዎቿ በቁጥጥር ሥር ውለዋል ተብሏል።

ግለሰቧ ቀደም ሲል የአስጠኚዎች ማዕከል ኃላፊት ላይ የነበረች ሲሆን የተፈረደባትን የአራት ዓመት እስራት ካለፈው መስከረም ትጀምራለች ተብሎ ቢጠበቅም አስካሁን እጇን አልሰጠችም።

ግለሰቧ ከሴንጋፖር ኮብልላለች ተብሎ ይታሰባል።

የአገሪቱ ፖሊስ የእስር ማዘዣ ያወጣ ሲሆን ለኢንተርፖል ጥቆማ ካደረጉም በኋላ ኢንተርፖል  " ቀይ ማስጠንቀቂያ " አውጥቷል። ያለችበትን የሚያውቁ እንዲያሳውቁ ጠይቋል።

‘ፖኒ’ በሚል ስም የምትጠራው ግለሰብ የወጣባት " ቀይ ማስጠንቀቂያ " በመላው ዓለም ያሉ የሕግ አካላት ያለችበትን እንዲፈልጉና እንዲይዟት ይሁንታ ይሰጣል።

እ.አ.አ. በ2016 በሲንጋፖር የተካሄዱ ሦስት ብሔራዊ ፈተናዎች ላይ ነው ማጭበርበር የተፈጸመው።

ተማሪዎች #ከቆዳቸው ጋር የሚመሳሰል ኢርፎን አድርገው በተለያዩ የፈተና ማዕከሎች ፈተናውን የወሰዱ ሲሆን ተንቀሳቃሽ ስልክ እና ብሉቱዝ #ሰውነታቸው ላይ ተለጥፎ በልብስ እንዲሸፈን ተደርጎ ፈተና ወስደው ነበር።

ያንብቡ : https://telegra.ph/BBC-01-28-3

Credit : BBC

@tikvahethiopia
#EOTC #አሁን

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በአሁኑ ሰዓት በወቅታዊ ጉዳይ መግለጫ እየሰጠች ነው።

ቤተክርስቲያኗ ፤ ከሃያ (20) ዓመታት በላይ በጅማ የም ኮንታ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በመሆን የሚያገለግሉት ብፁዕ አቡነ እስጢፋኖስ ዛሬ በጅማ ዞን  ፖሊስ ታስረው መዋላቸውን ገልጻ ድርጊቱን በፅኑ አውግዛለች።

በአሁኑ ሰዓት ሊቀ ጳጳሱ #በግዳጅ ከጅማ እንዲወጡ መገዳቸውን እና ከሊቀ ትጉሃን ታጋይ ታደለ የኢትዮጵያን የሃይማኖት ተቋማት ጠቅላይ ጸሐፊ ጋር ወደ አዲስ አበባ በመመለስ ላይ መሆናቸውን ቤተክርስቲያኗ አሳውቃለች።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን መገናኛ ብዙሃን ድርጅት ፤ ብፁዕ አቡነ እስጢፋኖስ ከክልል የተሰጠ ትዕዛዝ ነው በማለት በነገው እለት በጅማ የቅድስት ድንግል ማርያም ሕንጻ ቤተመቅደስ ቡራኬ ቤተክርስቲያን ሳያከናውኑ በፀጥታ ኃይሎች ወደ አዲስ አበባ  እንዲመለሱ የተገደዱት ብሏል።

በተጨማሪ ቤተክርስቲያኗ በሰጠችው መግለጫ " በሕገ ወጥ ከተሾሙ አባቶች መካከል ይቅርታ ጠይቀው የተመለሱትና ቅዱስ ሲኖዶስ ይቅርታቸውን የተቀበለው መጋቤ ሐዲስ አባ ጸጋዘአብ አዱኛ ከመንበረ ፓትርያርክ ማረፊያ ተይዘው ወዳልታወቀ ሥፍራ ተወስደዋል " ስትል ገልፃለች።

በመግለጫው መንግሥት ሕግ የማስከበር ኃላፊነቱን እንዲወጣ የጠየቀች ሲሆን ቅዱስ ፓትርያርኩ በሚገኙበት ግቢ አፈና መፈጸሙ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ኦርቶዶክሳውያንን ያሳዘነ ነው ብላለች።

#Update : መጋቤ ብሉይ ወሐዲስ አባ ጸጋ ዘአብ አዱኛ ታፍነው ከተወሰዱበት ተለቅቀዋል።

@tikvahethiopia
ቅናሽ ካለማ…
አዲሱን የአቢሲንያ ባንክ አፖሎ የዲጂታል መተግበርያ ሲጠቀሙ በሲኒማ ትኬት፥ በምግብ እና መጠጥ ትዕዛዝዎ ላይ ቅናሽ ያገኛሉ። አፖሎን አውርደው ዛሬውኑ ይጠቀሙ።
መተግበሪያውን ለማውረድ ሊንኩን ይጠቀሙ።

https://apollo.bankofabyssinia.com/download-apollo
#Apollo #OurNewProduct #DigitalEthiopia #Ethiopia #technology #innovation #digital #BankofAbyssinia #DigitalEthiopia #Ethiopia #የሁሉም_ምርጫ #The_Choice_For_all #Apollodigitalproduct, #AbyssiniaDigital #Abyssiniabank, #poweredbybankofabyssinia, #thechoiceforall
#Afar

የዲጂታል ቴክኖሎጂን ለሰላምና ግንባታ የመጠቀም ልምድ ደካማ በሆነበት ሁኔታ በማኅበራዊ ሚዲያ የሚሰራጩ ሀሰተኛና የጥላቻ ንግግሮች ጉዳታቸው ትልቅ ነው።

በተለይ እነዚህ አደገኛ መረጃዎች በከተማም ሆነ ከተማ ወጣ ባሉ አከባቢዎች የሚፈጥሩት ተጽዕኖ ከፍ ያለ ነው።

ይህንን ታሳቢ ባደረገ መልኩ ከጥር 13 ጀምሮ ለ4 ቀናት በዲጂታል ሰላም ግንባታ እንዲሁም መሰረታዊ የሚዲያ ክህሎት ላይ ትኩረቱን መሰረት ያደረገው የአሰልጣኞች ስልጠና (TOT) በአፋር ክልል ሰመራ ከተማ ተካሂዷል።

በስልጠናው 20 ወጣቶች ተሳታፊ የነበሩ ሲሆን ከክልሉ 4 ወረዳዎች (አሚባራ፣ አፋንቦ፣ ጭፍራ፣ ገዋኔ) ለተወጣጡ ሰልጣኞች የዲጂታል ሚዲያ ክህሎትን ስለማሳደግ፣ የሰላም ግንባታ ሥራዎችን ስለመስራትና ከሀሰተኛና ጥላቻ ንግግሮችን ራስንና ማኅበረሰብን ስለመከላከል በዚህም ምክንያት የሚደርስን ጉዳት መቀነስ በሚቻልበት አግባብ የአሰልጣኞች ስልጠና ተሰጥቷል።

በቀጣይም ወጣቶቹ በወሰዱት ሥልጠና መሰረት ወደ ማኅበረሰባቸው ተመልሰው ለሌሎች እኩዮቻቸው ተመሳሳይ ሥልጠናዎችን እንዲሰጡ አስፈላጊውን ድጋፍ በማድረግ በአከባቢያቸው አወንታዊ ተጽዕኖ እንዲፈጥሩ ለማስቻል ታቅዷል።

በተለይ የመረጃ ተደራሽነቱ በተለያዩ ምክንያቶች ለተገደበባቸው አከባቢዎች መሰል የአቻ ሥልጠናዎች ትርጉም ያለው ለውጥ ከማምጣቱም በዘለለ ወጣቱን አሳታፊ ያደረገ የመፍትሔ ሀሳቦች ተግባራዊ እንዲሆኑ እድሉን በሰፊው ያመቻቻል።

ይህንን ስልጠና ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከ Mercy Corps Ethiopia ጋር በጋራ በመሆን ለሥልጠናው ከሚያስፈልገው የሥርዓተ ትምህርት ቀረጻ ጀምሮ በጋራ እየሰሩ ይገኛሉ።

በቀጣይ በድሬደዋና በጅጅጋ ከተሞች መሰል ሥልጠናዎችን የሚሰጡ ይሆናል።

@tikvahethiopia
" በብሔራዊ ፈተናው ከ600 በላይ ውጤት ያመጡ ተማሪዎችን የዩኒቨርሲቲ ወጪ እንሸፍናለን " - አማራ ባንክ

በ2014 ዓም ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ወስደው በመላ ሀገሪቱ ከ600 በላይ ውጤት ያመጡ ተማሪዎችን የዩኒቨርሲቲ ወጪ እንደሚሸፍን አማራ ባንክ አሳውቋል።

ባንኩ በመላው ሀገሪቱ ከ600 በላይ ውጤት ላመጡ ተማሪዎች ለእያንዳንዳቸው በወር 750 ብር እየከፈለ እንደሚያስተምር የባንኩ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሄኖክ ከበደ ገልጸዋል።

ይህ ውሳኔ የባንኩ የማኀበረሰባዊ አገልግሎት አካል መሆኑን ዋና ሥራ አስፈጻሚው ለአሚኮ ጠቁመዋል።

በመላ ሀገሪቱ ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎች በትምህርት ሚኒስቴር እውቅናና ሽልማት ይሰጣቸዋል መባሉ ይታወሳል።

@tikvahuniversity @tikvahethiopia
#ግሬስ

በሀገራችን በአይነቱ የመጀመርያ የአረጋውያን እና ህመሙማን እንክብካቤ ማእከል  (Nursing Home) የሆነው ግሬስ የህሙማን እና አረጋውያን እንክብካቤ ማዕከል የህሙማንን ስቃይ እንዲሁም የአስታማሚዎችን እንግልት ለማቅለል አገልግሎት እየሰጠ ነድ።

በሙያው እውቀት እና ልምድ ባካበቱ ባለሞያዎች ፣ ንፅህናቸውን በጠበቁ የግል እና የጋራ ክፍሎች ፣ አዕምሮን በሚያድስ አርንጓዴ ስፍራ ፣ በቀን 24 ሰአት ከሳምንት እስከሳምንት በቋሚነት አገልግሎት እያቀረበ ነው።

" አላማችን ታካሚዎችን  የሚገባቸውን እንክብካቤ መስጠት አስታማሚዎችን ደግሞ ማሳረፍ  ነው "

ለበለጠ መረጃ ስልክ ቁጥር 0967-03-42-42 / 0954-99-11-90.
አድራሻ - አያት አደባባይ ወደ ለገጣፎ በሚወስደው መንገድ ላይ በቀኝ በኩል በፍሬሽ ኮርነር ገባ ብሎ

ቴሌግራም ግሩፕ - https://t.iss.one/gracenursinghome
#ከቀረጥ_ነፃ

የገንዘብ ሚኒስቴር በማምረቻ ኢንዱስትሪ፣ በግብርና ፣ በሎጀስቲክስ፣ በኮንስትራክሽን፣ የባለኮከብ ሆቴሎች ኢንቨስትምንትን ጨምሮ ለልማት ፕሮጀክቶች የሚውሉ ተሽከርካሪዎች ከቀረጥ ነፃ እንዲገቡ መፍቀዱን ሪፖርተር ጋዜጣ አስነብቧል።

በገንዘብ ሚኒስቴር የተዘጋጀው አዲስ መመሪያ " ለልማት ፕሮጀክቶች ከቀረጥ ነፃ ወደ አገር የሚገቡ ተሽከርካሪዎችን ለመወሰን የወጣ መመሪያ " የሚል ስያሜ የተሰጠው ነው ተብሏል።

ይህም የደረቅ፣ የፍሳሽ ወይም ማቀዝቀዣ የተገጠመለት የጭነት መኪናን ወይም ለተለየ አገልግሎት ተብለው የሚዘጋጁ አውቶብስን፣ ሚኒባስን፣ ሚዲባስን፣ ሽፍን የዕቃ ማጓጓዣ ተሽከርካሪንና የሞተር ብስክሌቶችን ይጨምራል፡፡

መመሪያው የማበረታቻው ተጠቃሚ የኢንቨስትመንት መስኮች ብሎ ከለያቸው ውስጥ ፦

- በማምረቻ ኢንዱስትሪ፣
- የኢንዱስትሪ ፓርክ ልማት፣
- በግብርና
- በሎጀስቲክስ
- በኮንስትራክሽን ሥራ ተቋራጭነት፣
- ባለ ኮከብ ሆቴሎች (የሪዞርት ሆቴሎችን ጨምሮ)
- በባቡር መሠረተ ልማት
- ሞቴሎች
- ሬስቶራንቶችና ሎጆች የተሰማሩ ባላሀብቶች ይገኙበታል፡፡

በተጨማሪም ፦

- በመረጃና መገናኛ ቴክኖሎጂ ልማት፣
- በአስጎብኝ ሥራ
- በኤክትሪክ ኃይል ማመንጫ፣ ማስተላለፊያና ማሠራጫ፣
- በትምህርትና ሥልጠና፣
- የጤና አገልግሎት የኢንቨስትመንት መስኮች የተሰማሩ ባለሀብቶች ተሽርካሪዎችን ከቀረጥ ነፃ እንዲያስገቡ ይፈቅዳል።

የአርክቴክቸርና ኢንጂነሪንግ ሥራዎች የቴክኒክ ምርመራና ትንተና አገልግሎትና ንግድ የሥራ መስኮች አዳዲስ ፕሮጀክቶችን የሚያቋቋሙ ወይም ነባር ደርጅታቸውን የሚያስፋፉ ባለሀብቶችም የዕድሉ ተጠቃሚ እንደሚሆኑ ታውቋል፡፡

ያንብቡ : https://telegra.ph/Reporter-01-29

Credit : Ethiopian Reporter

@tikvahethiopia
በመቆጠብ ከፍተኛ ወለድ ያግኙ!
አፖሎ የ9% ወለድ ተጠቃሚ የሚሆኑበት የዲጂታል መተግበሪያ ነው። የቁጠባ ሂሳብዎን አሁኑኑ ይክፈቱ።

መተግበሪያውን ለማውረድ ሊንኩን ይጠቀሙ።
https://apollo.bankofabyssinia.com/download-apollo

#Apollo #OurNewProduct #highinterestrate #9% #exciting, #interestrate #DigitalEthiopia #Ethiopia #technology #innovation #digital #BankofAbyssinia #DigitalEthiopia #Ethiopia #የሁሉም_ምርጫ #The_Choice_For_all  #Apollodigitalproduct, #AbyssiniaDigital #Abyssiniabank #poweredbybankofabyssinia #thechoiceforall